ethiopian_orthodox | Unsorted

Telegram-канал ethiopian_orthodox - የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

30344

በዚህ Channel ውስጥ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንን ዶግማ ፤ ቀኖና እና ትውፊት የጠበቁ ትምህርቶች ይተላለፉበታል፡፡ ለአስተያየት: ጥቆማና ጥያቄ በዚህ ያግኙን ☞ @Ethiopian_Orthodox_bot Buy ads: https://telega.io/c/Ethiopian_Orthodox

Subscribe to a channel

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

ጥቅምት ፭

የታላቁ አባት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ (ገብረ ሕይወት) የዕረፍታቸው መታሰቢያ

ጻድቁ የተወለዱት ግብፅ (ንሒሳ አካባቢ) ሲሆን አባታቸው ስምዖን እናታቸው አቅሌስያ ይባላሉ:: አባታችን ገብረ ሕይወት የጻድቃን አለቃ የቅዱሳን የበላይ ተጋድሏቸውና ድንቅ ተአምራቸው እንደ ሰማይ ከዋክብት የበዛ ቅዱስ ሰው ናቸው። የጻድቁን ክብር መናገር የሚችል ምን አንደበት ይኖራል? እንደ ምንስ ባለ ብራና ይጻፋል? ዜናቸውንስ ለመስማት የታደለ እንደ ምን ዓይነት ሰው ይሆን?

አባታችን ገብረ መንፈስ ቅዱስ ለ፭፻፷፪(562) ዓመታት በዚህች ዓለም ሲኖሩ እህል ያልቀመሱ /ምግባቸው ምስጋና ነውና/ ልብስ ያልለበሱ /ጠጉር አካላቸውን ይሸፍን ነበርና/ ሐዋርያዊ ሆነው ከግብፅ እስከ ኢትዮዽያ ብዙ ነፍሳትን ያዳኑ አባት፤ ሃገራችንን አስምረው አስራት እንድትሆናቸውም ተቀብለው ምድረ ከብድ አካባቢ አርፈዋል።

ጻድቁ ገብረ መንፈስ ቅዱስም ገብረ ሕይወትም ይባላሉ። በ፭፻፷፪ ዓመታት ሕይወታቸው እንደ ሐዋርያት ከምድረ ግብፅ እስከ ኢትዮጵያ ወንጌልን ሰብከዋል። በዚህም በሚሊዮን (አእላፍ) ለሚቆጠሩ ነፍሳት የድኅነት ምክንያት ሆነዋል።

ጻድቁ እንደ ሰማዕታትም ከከሃዲ ሰዎች ብዙ መከራን ተቀብለዋል። እንደ ባሕታውያን ለብዙ መቶ ዓመታት ሰው ሳያዩ ቆይተዋል። ለ'የ'ት የሚለው ግን የጽድቅ ሕይወታቸው ነው፤ ከዕልፍ አዕላፍ አጋንንት ጋር ተዋግተው ድል ማድረግ ችለዋልና።

የንሒሳው ኮከብ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ለኢትዮጵያ ልዩ ፍቀር አላቸው። ስለ ሃገሪቱና ሕዝቧ ፍቅር ሲሉ ለ፻(100) ዓመታት በደብረ ዝቋላ መከራን ተቀብለዋል። ምሕረትን ሲለምኑ ሥጋቸው አልቆ በአጥንታቸው ቁመው ነበርና ሃገራችን አሥራት ሆና ተሰጠቻቸው።

ስለዚህም ነው በሃገሪቱ ውስጥ ከ፳፻(2,000) በላይ የጻድቁ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳማትና አድባራት ዛሬም ድረስ ያሉት። በ፰(8)ኛው ክ.ዘ አካባቢ የተወለዱት አባታችን ያረፉት በ፲፬(14)ኛው መቶ ክ.ዘ አካባቢ ነው። ፍጥረታትን ሁሉ አዝዘው መጋቢት ፭(5) ቀን ሲያርፉ ግሩማን መላእክት ገንዘው አካላቸውን ሠውረዋል።

ሥላሴን የተሸከመ አካላቸው በጐልጐታ ተቀብሯል የሚሉም አሉ። "ሰላም ለመቃብሪከ ዘኢተከሥተ ለባዕድ: ከመ መቃብሩ ለሙሴ ወልደ ዮካብድ: ዜና መቃብሪከሰ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ጸማድ: ቦ ዘይቤ በኢየሩሳሌም አጸድ: ወቦ ዘይቤ ኀለወ በከብድ።" እንዲል።

ጻድቁ አባታችን አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ እረፍቱ መጋቢት ፭(5) ቀን ነው ይህ ደግሞ በታላቁ ዓብይ ጾም ወቅት ነው። ፍትሃ ነገስት አንቀጽ ፲፭(15) ላይ በዓብይ ጾም በዓል ማክበር ይከለክላል የሀዘን ወቅት ነውና ከበሮ አይመታም እልልታና ጭብጨባ የለም ፍጹም ሀዘን እንጂ :የመጋቢት ፳፯(27) ስቅለት ጥቅምት ፳፯ ቀን እንደሚከበረው ሁሉ የአባታችን አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ እረፍታቸው ወደ ጥቅምት ፭ ቀን ተዛውሮ እንዲከበር ተደረገ፡፡

የጻድቁ አባታችን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ረድኤት በረከታቸው በእኛ በምናምን ላይ ይደርብን!

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

✝️ ሰማዕትነት አያምልጣችሁ ! 🔔

በጥንቱ ዘመን ሰማዕትነት ከዓላዊያን ነገሥታት ጋር ነበር። ዓላዊያን ነገሥታት ክርስቲያኖችን ያሳድድዋቸዋል። ክርስቲያኖችም ጨርቄን ማቄን ሳይሉ ይሰደዳሉ። ስለ ሃብት ንብረታቸው፣ ስለ ምድራዊ ክብራቸው፣ ስለ ሚስቶቻቸው፣ ስለ ልጆቻቸው፣ ስለ ምድራዊት ኑሮአቸው ብዙም አይጨነቁም። ዋናው ጭንቀታቸው ነፍሳቸው ከአምላክዋ ከወዳጅዋ ከሞተላት አፍቃሪዋ ርቃ እንዳትሰደድ ነበር። ታዲያ ለዚህ ብለው የበግና የፍየል ሌጦ ለብሰው ግማሾቻቸው ዱር ለዱር፣ ግማሾቻቸው ተራራ ለተራራ፣ ግማሾቻቸው ዋሻ ለዋሻ፣ ግማሾቻቸው ፍርክታ ለፍርክታ ተቅበዘበዙ። ብዙ የብዙም ብዙ መከራ ተቀበሉ። ነፍሳቸውን ለማትረፍ ብለው ራሳቸውን በየመቃብሩ፣ በየበረሃው ይደብቁ ነበር። በጣም የሚያስደንቀኝ ግን ይህን ያደረጉት በጣም ብዙ እናቶችም መኖራቸው ነው።
ልጆቼ የእኛ ሰማዕትነት ግን እንዲህ አይደለም። የእኛ ሰማዕትነትና ውጊያ በላያችን ላይ ካሉት ነገሥታት ጋር ነው። የእኛ ሰማዕትነት ከምኞቶቻችን ጋር ነው። የእኛ ሰማዕትነት ከስግብግብነት፣ ከእንቅልፍ፣ ከዋዛ ፈዛዛ፣ ከስንፍና፣ ከውሸት፣ ከሐሜት ጋር ነው። የእኛ ሰማዕትነት በጠዋት ተነሥቶ ለጫወታ መሮጥ ሳይሆን ለጸሎት፣ ለስግደት ወደ ቤተ ክርስቲያን መሄድ ነው። የእኛ ሰማዕትነት ወንበራችን እስኪጎደጉድ ድረስ ፊልም ማየት ሳይሆን ቃለ እግዚአብሔርን ማንበብ ነው።
ስለዚህ ልጆቼ! ከምኞቶቻችን ጋር ተጋድሎ እንግጠም። ነፍሳችንን ከአምላክዋ ጋር ከሚያጣሉ ደግሞም ለጊዜው ሳይሆን ለዘለዓለም ከሚለይዋት ፍላጎቶቻችን ጋር እንጋደል። ስለ ምድራዊ ሃብት፣ ስለ ምድራዊ ዝና፣ ስለ ጊዜአዊ ደስታ ብለን ነፍሳችንን ለዓላውያን ነገሥታት (ለምኞቶቻችን) ትንበረከክ ዘንድ አሳልፈን አንስጣት።
ነፍሳችንን ከእነዚህ ነገሥታት መከራ እናድናት። እነዚህን ነገሥታት ድል አድርገን ከአምላክዋ ጋር እናገናኛት። ከእንቅልፍ ጋር ተዋግተን ድልም አድርገን ጠዋት ለጸሎት ፣ ለስግደት እናበርታት። የእኛ ዘመን ሰማዕትነት ይህ ነውና። ........ ✞ ✞ ✞ ..........
☞ ሰማዕትነት አያምልጣችሁ እና ሌሎች በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ[ትርጉም-ገብረ እግዚአብሔር ኪደ] ከሚለው መጽሐፍ የተወሰደ

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

ክበበ ጌራ ወርቅ ዘየኀቱ እምዕንቌ ባሕርይ፤
ማርያም አክሊለ ጽጌ ለጊዮርጊስ ቀጸላ መንግሥቱ።

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

ስርዓተ ማኅሌት ዘካልዕ ጽጌ በዓለ በዓታ ለማርያም
🌺🥀🌺🥀🌺🥀🌺🥀🌺🥀🌺🥀🌺🥀

ነግሥ (የማንኛውም ወርኃ  በዓልና ክብረ በዓል ሥርዐተ ማኅሌት መጀመሪያ)
.....................................................................
ስምዓኒ እግዚኦ ጸሎትየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ወይብጻሕ ቅድሜከ ገዓርየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ወኢትሚጥ ገፀከ እምኔየ፡ በዕለተ ምንዳቤየ አጽምእ ዕዝነከ ኃቤየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ አመ ዕለተ እጼውአከ ፍጡነ ስምዓኒ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ለዓለም ወለዓለመ ዓለም፡ ሃሌ ሉያ ዘውእቱ ብሂል፡ ንወድሶ ለዘሃሎ እግዚአብሔር ልዑል፡ ስቡሕ ወውዱስ ዘሣረረ ኲሎ ዓለመ፡ በአሐቲ ቃል።

መልክዓ ሥላሴ
ሰላም ለኵልያቲክሙ እለ ዕሩያን በአካል፤ዓለመክሙ ሥላሴ አመ ሐወፀ ለሣህል፤እምኔክሙ አሐዱ እግዚአብሔር ቃል፤ተፈጸመ ተስፋ አበው በማርያም ድንግል፤ወበቀራንዮ ተተክለ መድኃኒት መስቀል፡፡

ዚቅ
ሃሌ ሃሌ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሃሌ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሃሌ ሃሌ ሉያ ሐረገ ወይን፤እንተ በምድር ሥረዊሃ ወበሰማይ አዕፁቂሃ ሐረገ ወይን፤እንተ በሥሉስ ትትገመድ ወታፈሪ ለነ አስካለ በረከተ፤ሐረገ ወይን፤ሲሳዮሙ ለቅዱሳን፤ሐረገ ወይን፤ሠርዓ ሰንበተ በቃሉ ወጸገወ ሰላመ ለኩሉ።

ማኅሌተ ጽጌ
በከመ ይቤ መጽሐፍ ማዕከለ ፈጣሪ ወፍጡራን፤ለዕረፍት ዘኮንኪ ትእምርተ(ጽላተ) ኪዳን፤ሰንበተ ሰንበታት ማርያም ዕለተ ብርሃን፤ብኪ ይትፌስሑ ዘገነተ ጽጌ ጻድቃን፤ወብኪ ይወጽኡ ኃጥአን እምደይን፡፡

ወረብ
በከመ ይቤ መጽሐፍ ማዕከለ ፈጣሪ ወፍጡራን ዘኮንኪ ለዕረፍት ትእምርተ ኪዳን/፪/
ብኪ ይትፌስሑ ዘገነተ ጽጌ ጻድቃን ብርሃን ዕለተ ብርሃን/፪/

ዚቅ
ሰንበቶሙ ይእቲ ለጻድቃን ትፍሥሕት፤ሰንበቶሙ ይእቲ ለኃጥአን ዕረፍት፤ኅቡረ ንትፈሳሕ ዮም በዛቲ ዕለት፡፡

ማኅሌተ ፅጌ፦
ከመ ታቦት ሥርጉት በወርቀ ዓረብ ወተርሴስ፤በድንግልና ማርያም ሥርጉተ ሥጋ ወነፍስ፤ ተአምረ ነቢር አርአይኪ በቤተ መቅደስ፤ኢያቄም ወሐና ቀንሞስ ቀናንሞስ፤ እምዘ ጸገዩኪ ለጳጦስ በዓመት ሠላስ

ወረብ፦
እምዘ ጸገዩኪ ለጳጦስ በዓመት ሠላስ  ኢያቄም ወሐና ቀንሞስ ቀናንሞስ/፪/
ተአምረ ነቢር አርአይኪ ተአምረ ነቢር አርአይኪ በቤተ መቅደስ/፪/

ዚቅ
አንቲ ውእቱ ንጽሕት እምንጹሐን ድንግል ኅሪት ዘነበረኪ ውስተ ቤተ መቅደስ ከመ ታቦት ዘግቡር እምዕፅ ዘኢይነቅዝ ሥርግው በወርቅ ንጡፍ ወልቡጥ በዕንቍ ባሕርይ ዘየኃቱ ዘብዙኅ ሤጡ ከመዝ ነበርኪ በቤተ መቅደስ ወመላእክት ያመጽሑ ወትረ ሲሳየኪ ከመዝ ነበርኪ አሠርተ ወክልኤተ ዓመተ እንዘ ትትናዘዚ እምኀበ መላእክት ስቴኪኒ ስቴ ሕይወት ውእቱ ወመብልዕኪኒ ኅብስት ሰማያዊ

ማኅሌተ ጽጌ
እንዘ ተሐቅፊዮ ለሕጻንኪ ጽጌ ፀዓዳ ወቀይሕ ፣አመ ቤተ መቅደስ ቦእኪ በዕለተ ተአምር ወንጽሕ፣ንዒ  ርግብየ  ትናዝዝኒ  እምላህ፣ወንዒ  ሠናይትየ ምስለ ገብርኤል ፍሡሕ፣ወሚካኤል ከማኪ ርኅሩኅ

ወረብ፦
ንዒ ርግብየ ንዒ ርግብየ ምስለ ሚካኤል/፪/
ወንዒ ሰናይትየ ወንዒ ሰናይትየ ምስለ ገብርኤል ፍሡሕ/፪/

ዚቅ፦
ንዒ ርግብየ አግዓዚት ከመ ጎሕ ሠናይት ታቦተ መቅደስ ቅድስተ ቅዱሳን ዕፀ ጳጣስ ደብተራ ፍጽምት ማኅደረ መለኮት

ዓዲ ዚቅ
ንዒ ርግብየ ኲለንታኪ ሠናይት ፀምር ፀዓዳ እንተ አልባቲ ርስሐት መሶበ ወርቅ እንተ መና በትረ አሮን እንተ ሠረፀት።

ወቦ ዘይቤ ዚቅ
ይዌድስዋ ትጉሃን፤ይቄድስዋ ቅዱሳን፤ሰሎሞን ይቤላ ርግብየ ሠናይት፤ጳውሎስኒ ይቤላ ደብተራ ፍጽምት፤ዳዊትኒ ይቤላ ስምዒ ወለትየ ወርይዪ ወአጽምዒ ዕዝንኪ

ማኅሌተ ጽጌ
ክበበ ጌራ ወርቅ ጽሩይ እምዕንቈ ባሕርይ  ዘየኃቱ፤ዘተጽሕፈ ብኪ  ትእምርተ ስሙ ወተዝካረ ሞቱ፤አክሊለ ጽጌ ማርያም  ለጊዮርጊስ ቀጸላ  መንግሥቱ፤አንቲ  ኵሎ ታሰግዲ ሎቱ፤ወለኪኒ ይሰግድ ውእቱ፡፡

ወረብ፦
ክበበ ጌራ ወርቅ ዘየሐቱ እምዕንቈ ባሕርይ/፪/
ማርያም አክሊለ ጽጌ ለጊዮርጊስ ቀጸላ መንግሥቱ/፪/

ዚቅ
ከርካዕ ዘተተክለት በቤተ መቅደስ፤መራኁቱ ለጴጥሮስ፤አንቲ ውእቱ ደብተራ ስምዕ ዘጳውሎስ፤አማን አክሊሉ ለጊዮርጊስ

ሰቆቃወ ድንግል
በቤተ መቅደስ ዘልሕቀት ወለተ ካህናት እንዘ ትሴሰይ ሥሩዓ፣ ኅብስተ ኅቡዓ ወጽዋዓ ወይን ምሉዓ፤እፎ ከመ ነዳይ ሲሳየ ዕለት ዘኃጥአ፤ተአገሠት በብሔረ ግብጽ ረኃበ ወጽምዓ፤አልቦ ከማሃ ዘረከበ ግፍዓ

ወረብ፦
እፎ ከመ ነዳይ ዘኃጥአ ሲሳየ ዕለት/፪/
በቤተ መቅደስ ዘልሕቀት ወለተ ካህናት እንዘ ትሴሰይ ኅብስተ መና ኅቡዓ/፪/

ዚቅ
እሴብሕ ጸጋኪ ኦ ዑጽፍተ ልብሰ ወርቅ እግዝዕትየ ወለተ ዳዊት ንጉሥ ዘተሐፀንኪ በቤተ መቅደስ ወተዓንገድኪ በፈሊስ እምሀገር ለሀገር እንዘ ተዓውዲ በተፅናስ

መዝሙር፦
ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ
ኪነ ጥበቡ መንክር ወእፁብ፤ኪነ ጥበቡ መንክር ወእፁብ ለዘሀሎ መልእልተ አርያም።አርአየ ምሕረቶ በላዕሌነ።ዘከለሎ ለሰማይ በከዋክብት ብሩህ። አርአየ ምሕረቶ በላዕሌነ ወለምድርኒ አሠርገዋ በጽጌያት ንፁህ። አርአየ ምሕረቶ በላዕሌነ ወሠርዓ ሰንበተ ለነባረ ያዕርፉ ባቲ። አርአየ ምሕረቶ በላዕሌ:ማ- መዓዛሆሙ ለቅዱሳን ከመ ፅጌ ደንጎላት ዘውስተ ቆላት። ጸገዩ ቀንሞስ ምስለ ናርዶስ።

አመላለስ፦
መዓዛሆሙ ለቅዱሳን ከመ ፅጌ ደንጎላት ዘውስተ ቆላት/፪/
ጸገዩ ቀንሞስ ምስለ ናርዶስ/፬/

©ያሬዳውያን

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

💠የመንፈስ ፍሬዎች💠

፱.ራስን መግዛት

ራስን ከመግዛት የበለጠ ንጉሥነት የለም። ራስን መግዛት በምን ከተባለ በእግዚአብሔር ሕግ ነው። ራስን መግዛት ስሜታችንን አሸንፎ እውነት በሆነው ቃለ እግዚአብሔር መመራት ነው። ከስሜት በላይ መሆን ነው። ነፍስን በሥጋ ላይ ማሰልጠን ነው። ራስን በራስ መቆጣጠር ነው። ለሰውነታችን ሕግ መሥራት ነው።
ዓይናችን ክፉ እንዳያይ፣ ጆሯችን ክፉ እንዳይሰማ፣ እጃችን ክፉ እንዳይዳስስ፣ ምላሳችን ክፉ እንዳይናገር፣ አፍንጫችን ክፉ እንዳያሸት መቆጣጠር ነው። አንድ ነገር ክፉ የሚባለው ፍጻሜው የእግዚአብሔርን ሕግ ወደመሻር የሚያደርስ ከሆነ ነው። ዓለምን ከመግዛት ራስን መግዛት ይበልጣል። ራሱን የገዛ ሰው ፍጻሜው መንግሥተ ሰማያት ነውና። ንዴትን፣ ሐሜትን፣ ቁጣን፣ ስሜትን መግራት ነው። አርምሞ (ዝምታ) አንደበትን ለመግዛት ዋናው መሳሪያ ነው። የፈቲው ጾርን (አመንዝራነትን) ለማስወገድ መጾም፣ ውሃ አለማብዛት እና እንቅልፍን መቀነስ ዋና መድኃኒቶች ናቸው። ራሳችንን በጾም፣ በጸሎት መግራት መልካም ነው። ራስን
መግዛት ከመንፈስ ፍሬዎች አንዱ ነው። ገላ. ፭፣፳፪።

💥ኑ በራሳችን ላይ እንንገሥ (ንጉሥ እንሁን)።


👉 የመንፈስ ፍሬዎች ጨርሰናል:
አነሣሥቶ ላስጀመረን አስጀምሮ ላስፈጸመን ልዑል እግዚአብሔር ምስጋና ይገባል አሜን!



@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

ወንድሙን በበቀል

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

አመ ፳ወ፮ ለመስከረም ዘቀዳማይ ጽጌ በዓለ ቶማስ ወሀብተማርያም ማኅሌት

ለማንኛውም ወርኃዊ እና ዓመታዊ ሥርዓተ ማኅሌት መጀመሪያ
.....................................................
ስምዓኒ እግዚኦ ጸሎትየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ወይብጻሕ ቅድሜከ ገዓርየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ወኢትሚጥ ገፀከ እምኔየ፡ በዕለተ ምንዳቤየ አጽምእ ዕዝነከ ኃቤየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ አመ ዕለተ እጼውአከ ፍጡነ ስምዓኒ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ለዓለም ወለዓለመ ዓለም፡ ሃሌ ሉያ ዘውእቱ ብሂል፡ ንወድሶ ለዘሃሎ እግዚአብሔር ልዑል፡ ስቡሕ ወውዱስ ዘሣረረ ኲሎ ዓለመ፡ በአሐቲ ቃል።

መልክአ ሥላሴ
ሰላም ለአፉክሙ ዘማዕፆሁ ሰላም፤ጽጌያቲሁ ሥላሴ ለተዋሕዶ ገዳም፤መንገለ አሐዱ አምላክ ንዋየ መጻኢ ዓለም፤ወልጡ አምልኮትየ በጸጋክሙ ፍጹም፤እምአምልኮ ጣዖት ግሉፍ አሐዱ ድርህም።

ዚቅ፦
ለሥሉስ ቅዱስ ጥዑም ቃሎም፤ናርዶስ ጸገየ ዉስተ አፍሆሙ፤
መግቢያ ዘማኅሌተ ጽጌ

ኀለፈ ክረምት ቆመ በረከት፤ተሠርገወት ምድር  

(🌹#በህብረት_ሁሉም🌹)
በስነ ጽጌያት፤ለመርዓዊሃ ትብሎ መርዓት፤ወልድ እኁየ ወረደ ውስተ ገነት።

ማኅሌተ ጽጌ፦
ጽጌ አስተርአየ ሠሪጾ  እምዓጽሙ፤ለዘአምኃኪ ጽጌ ለገብርኤል ምስለ ሰላሙ፤ወበእንተዝ ማርያም ሶበ  ሐወዘኒ ጣዕሙ፤ለተአምርኪ አኀሊ እሙ፤ማኅሌተ ጽጌ ዘይሰመይ ስሙ፡፡

ወረብ
መዓዛ ጣዕሙ ለተአምርኪ ሶበ ሶበ ሐወዘኒ/፪/
ወበእንተዝ ማርያም አኅሊ ለተዓምርኪ/፪/

ዚቅ፦
ሃሌ ሉያ ሃሌ ሃሌ ሉያ ናሁ አስተርአየ ጽጌ መርዓቱኒ ትቤ ወልድ እኁየ ይምዕዝ ከርቤ፤ ዕንባቆም ነቢይ ግብረ ምግባሩ ለወልድ አንከርኩ ይቤ፤ ንጉሠ ሰላም ክርስቶስ ዓቢይ ልዕልናከ ወመንክር ስብሐቲከ፤ለዕረፍት ሰንበት ሠራዕከ፤

ማኅሌተ ጽጌ
እንዘ  ተሐቅፊዮ ለሕጻንኪ ጽጌ ፀዓዳ ወቀይሕ ፣አመ ቤተ መቅደስ ቦእኪ በዕለተ ተአምር ወንጽሕ፣ንዒ  ርግብየ  ትናዝዝኒ  እምላህ፣ወንዒ  ሠናይትየ ምስለ ገብርኤል ፍሡሕ፣ወሚካኤል ከማኪ ርኅሩኅ

ወረብ
እንዘ ተሐቅፊዮ ለሕጻንኪ ጽጌ ፀዓዳ ወቀይሕ /፪/
አመ  ቤተ  መቅደስ ሠናይትየ ሠናይትየ በዕለተ ተአምር ወንጽሕ/፪/

ዚቅ፦
ንዒ ርግብየ ወንዒ ሠናይትየ፤እንተ ሐዋርያት ይሴብሑኪ፤መላእክት ይትለአኩኪ፣ፃዒ እምሊባኖስ ስነ ሕይወት

ማህሌተ ጽጌ
ጽጌኪ ማርያም ኮነኒ ሲሳየ ወአራዘ፤ወጸግወኒ እምትካዝ ተአምረኪ መናዝዘ፤ቶማስ ሎቱ አመ ገቦሁ አኃዘ፤እንዘ ይብል ከርቤ እምእዴየ ውኅዘ፣ረከበ በውስተ ቁስሉ አፈወ ምዑዘ

ወረብ-
አመ ገቦሁ ቶማስ ሎቱ አኃዘ/፪/
እንዘ ይብል ከርቤ እምእዴየ ውኅዘ ረከበ  አፈወ ምዑዘ/፪/

ዚቅ-
ሃሌ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ ወልድ እኁየ ፈነወ ዕዴሁ እንተ ስቊረት፤ለከፎ ሶቤሃ ርስነ መለኮት

ማኅሌተ ጽጌ
ክበበ ጌራ ወርቅ ጽሩይ እምዕንቈ ባሕርይ  ዘየኃቱ፤ዘተጽሕፈ ብኪ  ትእምርተ ስሙ ወተዝካረ ሞቱ፤አክሊለ ጽጌ ማርያም  ለጊዮርጊስ ቀጸላ  መንግሥቱ፤አንቲ  ኵሎ ታሰግዲ ሎቱ፤ወለኪኒ ይሰግድ ውእቱ፡፡

ወረብ
ክበበ ጌራ ወርቅ ጽሩይ ክበበ ጌራ ወርቅ ጽሩይ እምዕንቈ ባሕርይ/፪/
አክሊለ ጽጌ ማርያም ቀጸላ  መንግሥቱ/፪/

ዚቅ
ውድስት አንቲ በአፈ ነቢያት፤ ወስብሕት በሐዋርያት፤አክሊለ በረከቱ ለጊዮርጊስ፤ ወትምክህተ ቤቱ ለ፳ኤል።

ሰቆቃወ ድንግል
በስመ እግዚአብሔር ሥሉስ ሕፀተ ግጻዌ ዘአልቦ፤ሰቆቃወ ድንግል እጽሕፍ በቀለመ አንብዕ ወአንጠብጥቦ፤ወይሌ ወላህ ለይበል ዘአንቦ፤ከማሀ ኀዘን ወተሰዶ ሶበ ለኩለሄ ረከቦ፤ርእዮ ለይብኪ ዓይነ ልብ ዘቦ

ወረብ፦
ከማሀ ኀዘን ከማሀ ኀዘን ወተሰዶ ኀዘን/፪/
ርእዮ ለይብኪ ዓይነ ልብ ዘቦ ዓይነ ልብ ዘቦ/፪/

ዚቅ፦
እወ አማን እምውሉደ ሰብእ አልቦ፤ምንዳቤ ወግፍዕ ዘከማኪ በዉስተ ኩሉ ዘረከቦ፤

መዝሙር ፦
በ ፬
ትዌድሶ መርዓት ፤ እንዘ ትብል ነዐ ወልድ እኁየ ፤ ንፃእ ኀቅለ ፤ ት ፡ ንርአይ ለእመ ጸገየ ወይን ፤ ወለእመ ፈረየ ሮማን ፤ ት ፡ አሰርገወ ሰማየ በከዋክብት ፤ ወምድረኒ በሥነ ጽጌያት ፤ ት ፡ እስመ ውእቱ ወልድ ዋሕድ ፤ እግዚኣ ለሰንበት ፤ ትዌድሶ መርዓት ወትብሎ ፤ ወልድ እኁየ ቃልከ አዳም ።

አመላለስ፦
ትዌድሶ መርዓት ወትብሎ/፪/
ወልድ እኁየ ቃለከ አዳም/፬/

©ያሬዳውያን

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

🥀🌷🌺
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

እኔ አላዝንም

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

💠የመንፈስ ፍሬዎች💠

፮.በጎነት

✞ በጎነት ለራስም ለሌላውም መልካም መሆን ነው። ደግነት እና ቅንነት ይመሳሰሉታል። ነገር ሁሉ ለበጎ ነው ሲባል ለመልካም ነው ለማለት ነው። የመልካምነት መለኪያው የእግዚአብሔር ቃል ነው። አንድ ሰው በጎ የሚባለው እንደ እግዚአብሔር ቃል ሲኖር ነው። በሌሎች ሰዎች ክፉ አለማድረግና ለሌሎች ሰዎች መልካም
ማድረግ በጎነት ነው። ስለሌሎች ሰዎች ጥሩ አስተያየት አነጋገር ካለው በጎ ነው ይባላል። ብናጠፋ፣ ብንበድል እንኳ እግዚአብሔር ፈጥኖ አያጠፋንም። ለእኛ በጎ ስለሆነ የንሥሓ እድሜን ይሰጠናል። እንዲህ ከሆነ ታድያ አንዳንድ ክፉዎችን እግዚአብሔር ፈጥኖ የሚያጠፋቸው ስለምንድን ነው? ቢባል ቢቆዩ ኃጢዓትን
አብዝተው ስለሚሰሩ በሰማይም ፍዳቸው ይቀንስ ዘንድ ቶሎ ያጠፋቸዋል። አንዳንድ መልካሞችንስ ወዲያው የሚያጠፋቸው ለምንድን ነው? ከተባለ ከቆዩ ኃጢዓት ሊሰሩ ይችላሉና። በአሁኑ ጽድቃቸው ዋጋቸውን ለመስጠት ነው። አንዳንድ መልካሞች ብዙ ዘመን ይቆያሉ ለምንድን ነው? ከተባለ ለክብር የሚያበቃቸውን
ሥራ አብዝተው ይሰሩ ዘንድ እና ለኃጥዓን ተግሣጽ ይሆኑ ዘንድ ነው። አንዳንድ ክፉዎችን ደግሞ ብዙ ያቆያቸዋል ለምንድን ነው? ቢሉ የሰሯት መልካም ሥራ ካለች እርሷን በዚህ ምድር በድሎት እንዲኖሩ አድርጎ በሰማይ ፍዳቸው ይበዛ ዘንድ ነው። አንዳንድ ኃጢዓተኞች በዚህ ምድር ደስተኛ ሆነው ይኖራሉ አንዳንድ ኃጢዓተኞች ደግሞ በዚህ ምድር በመከራ ይኖራሉ ለምንድን ነው? ከተባለ። በዚህ ምድር ደስተኛ የሆኑት እንደ ነዌ በሰማይ ፍዳቸው የሚበዛ ሰዎች ናቸው። በዚህ ምድር ኃጢዓተኛ ሆነው በመከራ የሚኖሩት ደግሞ የኃጢዓታቸውን ፍዳ ጥቂቱን በዚህ ምድር ስለተቀበሉ በሰማይ ይቀልላቸዋል።ድኃው አልዓዛር በዚህ ምድር ለምን ተሰቃየ ቢሉ ምንም እንኳ ጻድቅ ቢሆን ሰው ከድንግል ማርያም በስተቀር ጽነት አያጣውምና ለዚያ ፍዳውን በዚህ ምድር ተቀብሎ በሰማይ ዋጋው ይበዛለት ዘንድ ነው። ሰው በዚህ ምድር እስካለ ድረስ ለምን ያህል ጊዜ እንደሚቆይ ስለማያውቀው ሁልጊዜም ለሁሉም ሰው በጎ ሊሆን ይገባል። አንዳንዱን በደለኛ እግዚአብሔር ወዲያው ይቀስፈዋል ለምን ቢሉ በሕይወተ ሥጋ ላሉት ምሳሌ ይሆን ዘንድ ነው። አንዳንዱን በደለኛ እግዚአብሔር በዚህ ምድር ያቆየዋል ለምን ቢሉ ንሥሓ ይገባ ዘንድ ነው። በማንኛውም ጊዜ በማንኛውም ቦታ በማንኛውም ሁኔታ በጎ እንሁን።

👉'እምነት' ይቀጥላል ..........

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

"ቸርነትን አድርግ"

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

" እሰይ አበራ መስቀሉ " ዘማሪት ትርሃስ

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

Enjoy our content? Advertise on this channel and reach a highly engaged audience! 👉🏻

It's easy with Telega.io. As the leading platform for native ads and integrations on Telegram, it provides user-friendly and efficient tools for quick and automated ad launches.

⚡️ Place your ad here in three simple steps:

1 Sign up

2 Top up the balance in a convenient way

3 Create your advertising post

If your ad aligns with our content, we’ll gladly publish it.

Start your promotion journey now!

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

"ኑ በብርሃኑ ተመላለሱ"
ሊቀ መዘምራን ይልማ ኃይሉ

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

ንዒ ርግብየ(፪) ምስለ ሚካኤል፤
ወንዒ ሰናይትየ(፪) ምስለ ገብርኤል ፍሡሕ።

©ያሬዳውያን

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

በከመ ይቤ መጽሐፍ ማዕከለ ፈጣሪ ወፍጡራን ዘኮንኪ ለእረፍት ትእምርተ ኪዳን፤
ብኪ ይትፌሥሑ ዘገነተ ጽጌ ጻድቃን ብርሃን ዕለተ ብርሃን።

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

"ተይ ተመከሪ"
ቀሲስ ምንዳዬ ብርሃኑ

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

"በዙሪያችን ካሉ ድንቅ ምስክሮች" | ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

መስከረም ፳፱
ሰማዕት ቅድስት አርሴማ

የቅድስት አርሴማ አባቷ ቴዎድሮስ ከሌዋውያንና ከኃያላን ነገሥታት ወገን ሲሆን እናቷ አትኖስያ ደግሞ ከጳጳሳት አለቆች ወገን ናት፡፡ ወላጆቿ በሃይማኖት በምግባር ያጌጡ በበጎ ትሩፋት የተመሰገኑ ደጋግ ቅዱሳን ናቸው፡፡ በጾም፣ በጾሎት፣ በምጽዋትና ዓሥራት በኩራትን በማውጣት በመንፈሳዊ ሥራ ሁሉ እየተጉ ቢኖሩም ነገር ግን እስክ እርጅናቸው ዘመን ድረስ ልጅ ስላልነበራቸው ያዝኑ ነበር፡፡ እናቷ ቅድስት አትኖስያ እንደ ነቢዩ ሳሙኤል እናት ሐና ጠዋት ማታ ወደ ቤተ ክርስቲያን በመሄድ በእግዚአብሔር ፊት ታለቅስ ነበር፡፡ እግዚአብሔር የልቧን ፈቃድ ይፈጽምላት ዘንድ ወደደና የቂሣርያውን ሊቀ ጳጳሳት ልድዮስን ስለ እርሷ ይጸልይላት ዘንድ አዘዘው፡፡
ሊቀ ጳጳሳቱም ስለ ቅድስት አትኖስያ ጸለየላት፡፡ እግዚአብሔር አምላክም የሊቀ ጳጳሳቱንና የቅድስት አትኖስያን ጸሎት ሰምቶ መልኳ እጅግ ያማረችን ሴት ልጅ ቅድስት አርሴማን ሰጣት፡፡ እናቷም እየተንከባከበች አሳድጋት ዕድሜዋ ከፍ ሲል አምላክን በወለደች በእመቤታችን ስም ወደተሠራች ቤተ ክርስቲያን ታገለግል ዘንድ ሰጠቻት፡፡ ቅድስት አርሴማ ወጣት በሆነች ጊዜ ወላጆቿ ባል ያጋቧት ዘንድ ወደዱ ነገር እርሷ ይህንን ፈጽሞ አልወደደችምና ወላጆቿን ‹‹እኔ የሰማያዊው የክርስቶስ ሙሽራ ነኝ እንጂ ምድራዊ ሙሽራ አይደለሁም›› አለቻቸው፡፡
ቅድስት አርሴማ ከእርሷ በፊትም ሆነ ከእርሷ በኋላ በመልክና በውበት የሚመስላት የለም፡፡ ይህን ዓለም እንደትቢያ በመቁጠርና ፍጹም በመናቅ ጌታችንን ከተከተሉት ቅዱሳት ደናግል አንስት ውስጥ በመልክና በውበት ቅድስት አርሴማን የሚመስል የለም፡፡ አምላክን ከወለደች ከእመቤታችን በቀር የሚበልጣት ማንም የለም፡፡ እርሷም በምግባር በሃይማኖት ያጌጠች በመንፈሳዊ ተጋድሎ የበረታች በትሩፋት የበለጸገች ናት፡፡ ብሉይን ከሐዲስ አጠናቃ ተማረች፡፡ የአገሮችንም (የሮምያን፣ የጽርዕን፣ የሶርያን፣ የኪልቅያን) ቋንቋዎች ታውቅ ስለነበር ቅዱሳት መጻሕፍትንም ወደ ተለያዩ አገራት ቋንቋዎች ትተረጉማለች፡፡

ቅድስት አርሴማ 15 ዓመት በሆናት ጊዜ ከሃዲውን ዲዮቅልጥያኖስን ሰይጣን አስነሥቶት ነገሠ፡፡ ይኸውም ከሃዲ ንጉሥ ሚስት ያባ ዘንድ በመልኳ ውብ የሆነች ሴት ልጅን ይመርጡለት ዘንድ በሀገሩ ሁሉ እንዲሄዱ ጭፍሮቹን አዘዘ፡፡ ያገኟትንም ውብ የሆነችን ሴት መልኳን ሥለው ያመጡለት ዘንድ ሠዓሊዎችንም አብሮ ላከ፡፡ የተላኩትም ሰዎች ወደ ሮሜ አገር በደረሱ ጊዜ ቅድስት አርሴማ ያለችበትን የደናግል ገዳም አገኙ፡፡ ወደ ገዳሙም ገብተው ቅድስት አርሴማን አይተዋት በመልኳ ማማር እጅግ ተደስተው ‹‹ለንጉሡ ሚስት የምትሆነው ይህች ናት›› ብለው መልኳን በሥዕል ቀርጸው ለንጉሡ ላኩለት፡፡ ንጉሡም ሥዕሏን በተመለከተ ጊዜ ፈጽሞ ተደሰተ፡፡ ስለ ሠርጉ ወደ እርሱ ይመጡ ዘንድ ሕዝቡን ይጠሩአቸው ዘንድ ወደ ነገሥታቱና ወደ መኳንንቱ ሁሉ ላከ፡፡

እሊያ ደናግልም ይህን ነገር በአወቁ ጊዜ ይረዳቸው ዘንድ ድንግልናቸውንም ይጠብቅ ዘንድ አልቅሰው ወደ እግዚአብሔር ለመኑ። ከዚህም በኋላ ተነሥተው በሥውር ሸሹ የንጉሥ ድርጣድስ ግዛት ወደ ሆነ ወደ አርማንያ ሀገርም ደርሰው በአንድ ቦታ ተቀመጡ ከእርሳቸውም ጋር የተሰደዱ ቁጥራቸው ሰባ አምስት የሆነ ወንዶች፣ ሴቶችም ሠላሳ ዘጠኝ የሆኑ ከእርሳቸው ጋራ አሉ። ምግባቸውን አያገኙም ነበርና በታላቅ ችግር ውስጥ ኖሩ ከእነርሱም መብራት የምትሠራ አንዲት ሴት ነበረች ከእርሷም የእጅ ሥራ ከሚገኘው በየጥቂቱ ይመገባሉ።

ንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስም የከበረች አርሴማን በፈለጋት ጊዜ አላገኛትም ግን በአርማንያ አገር እንዳለች ስለርሷ ሰማ። ደግሞ ለአርማንያ ንጉሥ ለድርጣድስ ስለርሷ ከዲዮቅልጥያኖስ ሸሽታ እንደ መጣች የአርሴማን ሥራ ነገሩት እርሱም አንዱን የአርማንያ መኰንን ለእኔ ጠብቃት ወደ እኔም ላካት ብሎ አዘዘው።

ደናግሉም ይህን በሰሙ ጊዜ ወደ ሌላ ቦታ ተሠወሩ ወደ ንጉሥም ወነጀሉአቸው ንጉሡም ቅዱስት አርሴማን በክብር አድርገው ያመጧት ዘንድ አዘዘ እርሷም ወደ እርሱ መምጣትን እምቢ በአለች ጊዜ እየጎተቱ ወስደው ወደርሱ አደረሷት።

የቅድስት አርሴማንም ላህይና ደም ግባቷን በአየ ጊዜ ድንግልናዋን ሊያረክስ ሽቶ እናቷ አጋታን አባብላ እሺ ታሰኝለት ዘንድ አዘዛት አጋታም ወደርሷ ሒዳ ልቧን አስጨከነች እንዲህም አለቻት። ዕወቂ ይህ ርኲስ አረሚ እንዳያረክስሽና ሰማያዊ ሙሽራሽን እንዳትተዪ እርሱም ክብር ይግባውና የእግዚአብሔር ልጅ ሕያው ክርስቶስ ነው።

ንጉሡም ይዞ ወደ እልፍኙ ሊአስገባት ከአደባባይ መካከል ተነሥቶ ድንግል አርሴማን ያዛት። በዚያንም ጊዜ በቅድስት አርሴማ ላይ የእግዚአብሔር ኃይል አደረባትና በምድር ላይ ጣለችው እርሱ ግን በጦርነት እጅግ የጸና አርበኛ ስለ ነበር በታናሽ ሴት ብላቴና ስለተሸነፈ ያን ጊዜ አፈረ። ራሷንም በሰይፍ ይቆርጡ ዘንድ አዘዘና ቆረጧት ከዚህም በኋላ ደናግሉን ሁሉ ከእናታቸው አጋታ ጋር ይገድሏቸው ዘንድ አዘዘ።

አንዲት የታመመች ድንግል ነበረች በዐልጋዋ ላይም እንደተኛች ወደ ወታደሮች ጮኸች መጥተውም እንደ እኅቶቿ ራሷን ቆረጡ ሁሉም የሰማዕትነት አክሊልን ተቀበሉ እነዚያንም ከሮሜ አገር አብረው የመጡ ወንዶችን ገደሏቸው ቁጥራቸውም ሰባ አምስት ናቸው ሥጋቸውም በተራራ ላይ የተጣለ ሁኖ ቀረ።

ሰማዕታትም ከተገደሉ በኋላ በንጉሡ ላይ ጋኔን ተጫነበት መልኩም ተለውጦ እንደ እርያ ሆነ። ቅዱስ ጎርጎርዮስ ወደርሱ መጥቶ በላዩ ጸልዮ እስከ አዳነው ድረስ ስለዚህም ክብር ይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አመነ። የቅዱሳን ሰማዕታትንም ሥጋቸውን ከተጣለበት ሰብስበው በአማረ ቦታ አኖሩአቸው ያማረች ውብ የሆነች ቤተ ክርስቲያንም ተሠራችላቸው። ከእነርሱም ታላላቅ ድንቆች ተአምራት ተገለጡ።

የእናታችን ቅድስት አርሴማ ምልጃዋ ይጠብቀን!

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

💠የመንፈስ ፍሬዎች💠

፰. የዋህነት

✞ የዋህ ማለት ኀዳጌ በቀል ማለት ነው። በዚህ ጊዜ ለቅዱሳን፣ ለቅድስት ድንግል ማርያም፣ ለእግዚአብሔር ይነገራል። እግዚአብሔር የዋህ ነው ብትል ኀዳጌ በቀል ነው መሓሪ ነው ማለት ነው። ቅድስት ድንግል ማርያምን የዋሂት የሚያሰኛት ርግብየ ሠናይትየ የሚያሰኛት ኀዳጌ በቀልነቷ፣ መሓሪትነቷ ነው። ኀዳጌ በቀል ማለት ተበድሎ እንዳልተበደሉ መሆን፣ በደልን ይቅር ማለት ማለት ነው። ቅዱስ ጳውሎስ የመንፈስ ፍሬዎች ብሎ ከጠቀሳቸው ውስጥ ገላ. ፭፣፳፪ የተጠቀሰው የውሃት ይህኛው የውሃት ነው። የዋህነት (Mildness) ጠቢብነትንም (Wisdom) የያዘ ነው። ኩኑ የውሃነ ከመ ርግብ ወጠቢባነ ከመ አርዌ ምድር
እንዲል። እባብ ጠቢብነቱ "ዕፀ ዘዌ የምትባል ዕፅዋት አለች። ፍሬዋን ይወዳታል። ነገር ግን ጥላዋ ካረፈበት መንቀሳቀስ ስለማይችል ጠዋት በምሥራቅ ሆኖ ማታ በምዕራብ በኩል ሆኖ ፍሬዋን ይበላል" ተብሏል። በዚህ በመጀመሪያው ትርጓሜ አንድ ሰው የዋህ ነው ሲባል ገራገር ነው። መልካም አሳቢ (Positive
thinker) ነው ማለታችን ነው። የዋህ ነው ማለት ክፉ ላደረጉባት እንኳ ቂም፣ ጥላቻ፣ በቀል የሌለበት ማለትነው። የዋህ ማለት ሰውን እንደራሱ የሚያይ ደግ ሰው ማለት ነው። ንኩን የዋሃነ። የዋሃን እንሁን። ባለፈው የደረሰብንን በደል እንተወው። የወደፊቱን ሕይወት በጋራ ሆኖ በፍቅር ሆነን ያማረ የሰመረ እናድርገው።
ሁለተኛው ትርጓሜ የላይኛው ተቃራኒ ነው። በግእዝ አንድ ቃል ለሁለት ተቃራኒ ነገሮች ሊያገለግል ይችላል። ለምሳሌ ባረከ "ባረከም ይሆናል ረገመም ይሆናል" ወባረከ ኢዮብ ዓመተ ልደቱ ሲል ረገመ ማለት ነውና። የዋህ ማለት ሞኝ፣ አላዋቂ ማለት ነው። የዋህ ብእሲ ኵሎ ዘነገርዎ የአምን እንዲል። ሞኝ ሰው፣ አላዋቂ ሰው የነገሩትን ሁሉ ያምናል እንደማለት ነው። ነገርን እንደወረደ የሚያምን፣ የማይመረምር፣ በራሱ ሳይሆን በመንጋ የሚያስብ የዋህ ይባላል። ይህ የየዋህ ሁለተኛ ትርጉም ነው። የዚህ ተቃራኒ ብልጥ ነው። ብልጥ የሚባለው ራስ ወዳድ ለራሱ ብቻ የሚያስብ፣ ራሱን ለመጥቀም የዋህ የሆኑ ሰዎችን የሚያታልል ተንኮለኛ ማለት ነው።
✞ በመጀመሪያ ትርጉም ያለውን የዋህ እንሁን። ኢየሱስ ክርስቶስ መፍቀሬ የውሃት እምተቀይሞ እንዳለ ደራሲ የዋህ ስንሆን ክርስቶስን እንመስለዋለን።

👉 'ራስን መግዛት ' ይቀጥላል ..........

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

"አክሊለ ጽጌ"
ሊቀ መዘምራን ይልማ ኃይሉ

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

ጽጌ መዓዛ ሠናይ
🌺🥀🌺🥀🌺🥀🌺🥀🌺🥀🌺🥀🌺🥀
ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ከመስከረም ፳፮ እስከ ኅዳር ፮ ያለውን ወቅት ወርኃ ጽጌ ትለዋለች። ወርኃ ጽጌ የእመቤታችን ስደት የሚታሰብበት ወቅት ነው። ስደት አድካሚ ጉዞ አለው። ረኀብና ጥምም መገለጫው ነው። ጠቢቡ "እነሆ ክረምት ዐለፈ ዝናቡም አልፎ ሔደ፤ አበቦችም በምድር ላይ ተገለጡ፤ የዜማም ጊዜ ደረሰ፤ የቁርዬም ቃል በምድራችን ተሰማ" (መኃ. ፪÷፲፩-፲፪) ብሏል። “ክረምት ዐለፈ” ያለው የአዳም የመከራ ዘመን ማለፉን ሲናገር ነው። ሊቁ ቅዱስ ያሬድም እመቤታችንን መዓዛ ባላቸው ጽጌያት መስሎ "መዓዛሆሙ ለቅዱሳን " ብሏታል።
አባ ጊዮርጊስ በመጽሐፈ ምሥጢር" አዳም እንኳን ተሳሳተ ፣አዳም እንኳን ወደቀ በገነት ውስጥ ቢኖር ኑሮ አዳም ከሔዋን ጋር ዕፀ-ሕይወትን እየበላ ይኖር ነበር እንጂ እኛ አናገኛትም ነበር።፣አዳም ባይሳሳት ኑሮ አንቺ አትወለጅም ነበር። ስለዚህ በገነት የተነፈግነውን ዕፀ-ሕይወት አንቺ ሰጥተሽናልና እናመሰግንሻለን” ብሏታል።
ቅዱስ ዮሐንስ "ታላቅ ምልክትም በሰማይ ታየ፤ ፀሐይን ተጐናጽፋ ጨረቃ ከእግሮችዋ በታች ያላት በራስዋም ላይ የአሥራ ሁለት ከዋክብት አክሊል የሆነላት አንዲት ሴት ነበረች። እርስዋም ፀንሳ ነበር፤ ምጥም ተይዛ ልትወልድ ተጭንቃ ጮኸች። ሌላም ምልክት በሰማይ ታየ፤ እነሆም ታላቅ ቀይ ዘንዶ፤ ሰባት ራሶችና አሥር ቀንዶችም ነበሩት፤ በራሶቹም ላይ ሰባት ዘውዶች ነበሩ"(ራእ. ፲፪÷፫) ብሏል። ፀሐይ የተባለው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። እርሱ በቀንም፣ በሌሊትም የሚያበራ እውነተኛ ብርሃን ነው። ፲፪ የክብር አክሊል የተባሉት ፲፪ ሐዋርያት ናቸው። ቅዱሳን ሐዋርያት ለድንግል ማርያም ጌጦች በመናቸው አክሊል አላቸው። ድንግል ማርያምም ለሐዋርያት ጌጣቸው ናት። "ሞገሶሙ ለሐዋርያት" እንዲል ቅዳሴ ማርያም። በጨረቃ የተመሰለው ዮሐንስ መጥምቅ ነው። ጨረቃ ሠርቅ ካደረገችበት ጀምሮ ብርሃኗ እየጨመረ በ፲፭ኛው ቀን ሙሉ ትሆናለች። ቅዱስ ዮሐንስም አንገቱን ከተቆረጠ በኋላ ፲፭ ዓመት አስተምሯል። ጨረቃን ተጫምታ ነበር ማለት ዮሐንስ ገና ከእናቱ ማኅፀን ሁኖ ለድንግል ማርያም ሰገደ ማለት ነው።
ቅዱስ ዮሐንስ "ምጥ" ያለው ድንግል ማርያም የገጠማትን ጭንቅ ነው። ቅዱስ አትናቴዎስ " ያለ ዘር ፣ያለ ምጥ ወለደችው" (ሃይ.አበው ምዕ•፳፰ ክ፲፬ ቊ ፲፱) በማለት የወለደችው ያለ ምጥ መሆኑን ተናግሯል። እመቤታችን ድንግል ማርያም ስለሦስት ነገሮች ብትጨነቅም ክርስቶስን ስለመውለድ አልተጨነቀችም። ድንግል ማርያም የተጨነቀችው ልጇ በቀራንዮ በተሰቀለ ጊዜ፣ ስለ ኃጥአን ለመከራ መዳረግ እና የሦስት ዓመቱ የግብፅ በረሃ ስደቷ ያስጨንቃት ነበር።
እርሷም "ከእንግዲህ ትውልድ ሁሉ ያመሰግኑኛል” በማለት ትውልደ ሴም፣ ትውልደ ካም፣ ትውልደ ያፌት እንደሚያመሰግናት ተናግራለች። “እነሆ እግዚአብሔር በፈጣን ደመና ሁኖ ወደ ምድረ ግብፅ ይመጣል፤ የግብፅ ጣዖታትም በፊቱ ይርዳሉ"(ኢሳ ፲፱÷፩) ተብሎ የተነገረው በስደቷ ወቅት የተፈጸመውን ነው። ሆሴዕም "ሕፃን በነበረ ጊዜ ወደድኩት፤ ልጄንም ከግብጽ ጠራሁት"(ሆሣ ፲፩÷፩:) ብሏል። ጌታችን የተሰደደው ግብፅን እና ኢትዮጵያን ለመባረክ ነው። አንድም ሰይጣንን ከሰው ልቡና አስወጥቶ ለመስደድ ነው።

በድንግል ማርያም ስደት ምክንያት ክርስቲያኖች የሰማዕትነትን በረከት አግኝተዋል። ሰሎሜ ጌታን በማዘል ድንግል ማርያምን ስትረዳ የመከራዋ ተካፋይ በመሆን አብራ ተንከራታለች። ጥጦስም ጌታን በትከሻው ተሸክሞ ሸኝቷቸዋል። በቅዳሴያችን "በቀኝ የተሰቀለውን ሽፍታ በመስቀል ላይ እንዳሰብከው አቤቱ እኛንም በመንግሥትህ አስበን" በማለት እንማጸናለን። በእመቤታችን ስደት በረከትን ያጡት ሄሮድስ፣ ትዕማር፣ዳክርስ እና መሰሎቻቸው ናቸው። ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን በየዓመቱ የድንግል ማርያምን ስደት በማሕሌት፣ በዝክርና በቅዳሴ ታስባለች። በዚህ ምክንያት ድንግል ማርያምን “አንቲ ውእቱ ጽጌ መዓዛ ሠናይ” በማለት እናመሰግናታለን። 🌺

የእመቤታችን ፍቅሯ በልባችን ምስጋናዋ በአንደበታችን እጥፍ ድርብ ሆኖ በእኛ በምናምን ክርስቲያኖች ላይ ይደርብን!
🥀🥀🥀🥀🥀🥀🥀🥀🥀🥀🥀🥀
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

💠የመንፈስ ፍሬዎች💠

፯.እምነት

✞ እምነት አካሌን የሰጠ፣ የሚያስፈልገኝን ነገር ሁሉ የፈጠረ እግዚአብሔር እስከ ዕለተ ሞቴ ይመራኛል ብሎ ሙሉ ተስፋን በእግዚአብሔር ላይ ማድረግ ነው።እምነት ካለመኖር የፈጠረኝ እግዚአብሔር በመግቦት ያኖረኛል ብሎ ቁርጥ ሀሳብን ለእግዚአብሔር መስጠት ነው። ብዙዎቻችን እምነት የለንም። እምነት ያለው ሰው ስለምንም አይጨነቅም። ከምንም በላይ የሆነው እግዚአብሔር አለኝ ብሎ በልቡ ስለሚያምን የሚያሳስበው የሚፈራው እና የሚያስጨንቀው ጉዳይ አይኖርም። እምነት ከመንፈስ ፍሬዎች አንዱ ነው። ገላ. ፭፣፳፪። እምነት ያለው ሰው ተስፋ አይቆርጥም። ምክንያቱም ምንም ዓይነት ፈተና ውስጥ ቢኖር እግዚአብሔር በጥበቡ ከዚያ እንደሚያወጣው ተስፋ ያደርጋልና። እምነት ያለው ሰው እንደ ዳንኤል አንበሳ ጉድጓድ ውስጥ ሊጣል ይችላል። ነገር ግን እግዚአብሔር አንበሶች እንዳይበሉት ያደርጋል። እምነት ያለው ሰው ሰማዕት ሊሆን መከራ ሊደርስበት ይችላል። ነገር ግን ከሁሉም የምትበልጠውን መንግሥተ ሰማያት ያገኛል። መዓልትና ሌሊትን፣ ክረምትና በጋን እያፈራረቀ የሚመግበን የሚያኖረን እግዚአብሔር ስላለን አንፈራም አንጨነቅም። ሰው እምነት እያጣ ሲሄድ ይጨነቃል፣ ያዝናል። ነገር ግን ከእኛ የሚጠበቀውን የድርሻችንን እየተወጣን ረድኤተ እግዚአብሔርን እየጠየቅን በተስፋ እንኑር። እምነታችን አይጉደል። ቀድሞ ቅዱሳንን የረዳ እግዚአብሔር ነው። አሁንም ያለው ራሱ ነው። እኛንም ይረዳናል። ይረድአነ አምላክነ ወመድኃኒነ። አምላክነሰ አምላከ አድኅኖ። ስብሐት ለአብ ስብሐት ለወልድ ስብሐት ለመንፈስ ቅዱስ። እግዚአብሔርን በሙሉ ልባችን እንመነው። መልካም የሆነውን ሁሉ ያደርግልናል።

👉'የዋህነት ' ይቀጥላል .............

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

የመስቀሉ ነገር ሲገባን
በሊ/መ ይልማ ኃይሉ
የመስቀሉ ፍቅር ሲገባን (፬)
እመቤታችንን እንወዳታለን
የመስቀሉ ፍቅር የገባቸው (፬)
እመቤታችን አለች ከጎናቸው

የመስቀሉ ነገር የገባቸው (፬)
እመቤታችን አለች ከጎናቸው

አባ ሕርያቆስ አባታችን
የመስቀሉ ነገር ቢገባው
ልቤ አፈለቀ አለ መልካም ነገር
ከእመቤቴ ጋራ ሲነጋገር
ከድንግል ማርያም ጋር ሲነጋገር
አዝ---
ነይ ነይ እምዬ ማርያም
ነይ ነይ ቤዛዊት ዓለም{፪}
አንድ ወልዳ ስሙን አበዛችው (፪)
አንዱ ሃገር ስትሄድ መድኃኔዓለም አለችው
አንድ ወልዳ ስሙን አበዛችው (፪)
አንዱ ሃገር ስትሄድ ኢየሱስ አለችው
አንድ ወልዳ ስሙን አበዛችው (፪)
አንዱ ሃገር ስትሄድ ክርስቶስ አለችው
አንድ ወልዳ ስሙን አበዛችው (፪)

ለመናኒው ፀሎት ልዩ እጣን
የዋሻው ሻማ ነሽ እመብሃን
መአዛሽ ሸተተኝ ከግሸን
ትናፍቂኛለሽ ምን ልሁን
ትርቢኝማለሽ ምን ልሁን

የመስቀሉ ነገር ሲገባን(፬)
እመቤታችንን እንወዳታለን

ዳዊት በመዝሙሩ ያነሳሻል
የያዕቆብ ድንኳን ነሽ ይልሻል
የእግዚአብሔር ሃገር የሚሉሽ
እመቤቴ ማርያም አንቺ ነሽ (፪)
ቤተልሔም ስሄድ አይሻለሁ
ቀራኒዮ ስሄድ አይሻለሁ
ፍጹም አትለይም ከልጅሽ
የአንቺስ ልዩ ነው ፍቅርሽ (፪)

የመስቀሉ ነገር ሲገባን(፬)
እመቤታችንን እናያታለን

ነይ ነይ እምዬ ማርያም
ነይ ነይ ቤዛዊት ዓለም{፪}
አንድ ወልዳ ስሙን አበዛችው (፪)
አንዱ ሃገር ስትሄድ አማኑኤል አለችው
አንድ ወልዳ ስሙን አበዛችው (፪)
አንዱ ሃገር ስትሄድ ክርስቶስ አለችው
አንድ ወልዳ ስሙን አበዛችው (፪)
አንዱ ሃገር ስትሄድ አንድዬ አለችው
አንድ ወልዳ ስሙን አበዛችው (፪)

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

መስከረም ፳፩

ብዙኃን ማርያም
በቤተ ክርስቲያናችን ከሚዘከሩ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ክብረ በዓላት መካከል መስከረም ፳፩ ቀን የሚውለው በዓል ‹‹ብዙኃን ማርያም›› በመባል ይታወቃል፡፡ በዓሉ በሁለት ዐበይት ምክንያቶች ይከበራል፤ የመጀመሪያው ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ሃይማኖታዊ ውሳኔ ለማዘጋጀት ከሩቅም ከቅርብም የተሰባበሰቡት ቀን፤ ሁለተኛው ደግሞ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለበት ዕፀ መስቀል በግሸን ደብረ ከርቤ የተቀመጠበት ዕለት መኾኑ ነው።

ጉባዔ ኒቅያ
በ፫፻፳፭ ዓ.ም አርዮስ የሚባል መናፍቅ የእግዚአብሔር ወልድን የባሕርይ አምላክነት አልቀበልም በሚል ክህደት እርሱ ተሰናክሎ ለሌሎችም መሰናክል ኾነ፡፡ ኦርቶዶክሳውያን ሊቃውንት አርዮስ ክህደቱን እንዲተው ቢመክሩትም ሊመለስ አልቻለም፡፡ ይህ የአርዮስ ክህደትም በሊቃውንቱ መካከል መለያየትን ፈጥሯል፡፡ ጊዜው ታላቁ ንጉሥ ቈስጠንጢኖስ ‹‹አብያተ ጣዖታት ይትአጸዋ አብያተ ክርስቲያናት ይትረኀዋ፤ የጣዖታት ቤቶች ይዘጉ! አብያተ ክርስቲያናት ይከፈቱ!›› የሚል ዐዋጅ የነገረበት ወቅት ነበርና ንጉሥ ቈስጠንጢኖስ በአርዮስ ክህደት ምክንያት በኒቅያ የሃይማኖት ጉባኤ እንዲካሔድ በየአገሩ ላሉ ሊቃውንት መልእክት አስተላለፈ፡፡

በዚህም መሠረት ከሚያዝያ ፳፩ ቀን ጀምሮ እስከ መስከረም ፳፩ ቀን ድረስ ፳፫፻፵፰ (ሁለት ሺሕ ሦስት መቶ ዐርባ ስምንት) ሊቃውንት በኒቅያ ተሰበሰቡ፡፡ ኒቅያ ለዚህ ጉባኤ የተመረጠችበት ምክንያትም ጳጳሱን ከማኅበረ ካህናቱ፤ ንጉሡን ከሠራዊቱ ጋር አጠቃላ ለመያዝ የምትችል ሰፊና ምቹ ቦታ ከመኾኗ ባሻገር ለኹሉም አማካይ ሥፍራ ስለ ነበረች ነው፡፡ በጉባኤው ከተሰበሰቡ ሊቃውንት መካከልም እንደ ቅዱሳን ሐዋርያት ሙታንን ያስነሡ፣ ለምጽ ያነጹ፣ አንካሳ ያረቱ፣ የዕውራንን ዓይን ያበሩ ድውያንን የፈወሱ፣ ሌላም ልዩ ልዩ ተአምር ያደረጉ፤ እንደዚሁም ስለ ርትዕት ሃይማኖታቸው በመጋደል ዓይናቸው የፈረጠ፣ እጃቸው የተቈረጠ ይገኙበታል፡፡

ሊቃውንቱ ሱባዔ ይዘው በጸሎት ከቆዩ በኋላ ኅዳር ፱ ቀን በንጉሥ ቈስጠንጢኖስ ሊቀ መንበርነት፣ በእለእስክንድሮስ አፈ ጉባኤነት ጉባኤው ተጀመረ፡፡ ንጉሡ ሊቃውንቱን "ስማችሁን፣ አገራችሁንና ሃይማኖታችሁን ጽፋችሁ ስጡኝ" ባላቸው ጊዜም ከ፳፫፻፵፰ቱ (2348) መካከል ፫፻፲፰ (318) ሊቃውንት ሃይማኖታቸውን ሲገልጹ እንደ አንድ ልብ መካሪ፣ እንደ አንድ ቃል ተናጋሪ ኾነው "ዘዕሩይ ምስለ አብ በመለኮቱ፤ ወልድ ከአብና ከመንፈስ ቅዱስ ጋር በመለኮት፣ በሥልጣን፣ በፈቃድ፣ በህልውና አንድ ነው" ብለው ጽፈው ሰጡት፡፡ ንጉሡም "ሃይማኖት እንደ ፫፻፲፰ቱ ሊቃውንት ይኹን" ብሎ ዐዋጅ አስነግሯል፡፡ እነዚህ ሊቃውንት በኦሪት ዘፍጥረት የተጠቀሱት ፫፻፲፰ቱ የአብርሃም ብላቴኖች ምሳሌዎች ናቸው /ዘፍ.፲፬፥፲፬/፡፡

፫፻፲፰ቱ ሊቃውንት በጉባኤው አርዮስን አውግዘው በመለየት "ነአምን በአሐዱ አምላክ፤ በአንድ አምላክ እናምናለን" የሚለውን የሃይማኖት ጸሎት (የሃይማኖት መሠረት) እና ሌሎችንም የሃይማኖት ውሳኔዎችን ደንግገዋል፡፡ ሊቃውንቱ ጉባኤውን ያካሔዱት ኅዳር ፱ ቀን ይኹን እንጂ በአንድነት የተሰባሰቡት መስከረም ፳፩ ቀን ስለ ነበረ ይህ ዕለት "ብዙኃን ማርያም" እየተባለ ይጠራል፡፡ ብዙ የቤተ ክርስቲያን አባቶች ለሃይማኖታዊ ጉባኤ የተሳባሰቡበት ዕለት ነውና፡፡
@Ethiopian_Orthodox

ዕፀ መስቀል/ግሸን ማርያም
በሌላ በኩል መስከረም ፳፩ ቀን የጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል በአምባሰል ተራራ በግሸን ደብረ ከርቤ የገባበትና በዓሉ የከበረበት ዕለት ነው፡፡ ታሪኩም በአጭሩ የሚከተለው ነው፤

ዐፄ ዳዊት መንፈሳዊና ደግ ንጉሥ ነበሩ፡፡ በዘመናቸው በኢትዮጵያ ቸነፈር ተከሥቶ ሕዝቡ ስለ ተሰቃየባቸው እጅግ አዘኑ፤ በጸሎት ወደ እግዚአብሔር ቢያመለክቱም ከእግዚአብሔር ዘንድ የተላኩ ባሕታዊ መጥተው "የጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን መስቀል አስመጥተህ በአገርህ በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን አሠርተህ ብታስቀምጥ ረሃቡ፣ ቸነፈሩ ኹሉ ይታገሥልሃል" አሏቸው፡፡ ዐፄ ዳዊትም ከብዙ ገጸ በረከት (ስጦታ) ጋር "የጌታችንን መስቀል ላኩልኝ" የሚል መልእክት አስይዘው መልእክተኞችን ወደ ኢየሩሳሌም ሰደዱ፡፡ መልእክተኞቹም በታዘዙት መሠረት መስቀሉን ይዘው መምጣታቸውን ዐፄ ዳዊት ሲሰሙ "ክተት ሠራዊት ምታ ነጋሪት" ብለው መስቀሉን ለመቀበል ጉዞ ጀመሩ፡፡

ዐፄ ዳዊት ስናር (ሱዳን) ደርሰው ከመልእክተኞቹ ጋር ተገናኝተው መስቀሉን በክብር አጅበው ወደ መካከል ኢትዮጵያ ለማስገባት ሲነሡም ከበቅሏቸው ወድቀው ጥቅምት ፱ ቀን ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ፤ በዚህም ሠራዊታቸው ተደናግጠው የጌታችንን መስቀል እዚያው ትተው የዐፄ ዳዊትን አስከሬን ይዘው ተመለሱ፡፡ መስቀሉ በስናር ከቆየ በኋላ የዐፄ ዳዊት ልጅ ዘርዐ ያዕቆብ ሲነግሡ ወደ መሃል ኢትዮጵያ አምጥተው ቤተ ክርስቲያን አሠርተው ለማስቀመጥ ቢያስቡም ምቹ ቦታ ግን ሊያገኙ አልቻሉም ነበር፡፡ ንጉሡና ሠራዊታቸው ምቹ ቦታ ሲፈልጉ መስቀሉን በኤረር ተራራ፣ በደብረ ብርሃን፣ በመናገሻ ማርያም ዓምባ፣ በእንጦጦ ጋራ ብዙ ጊዜ አስቀምጠውት ቆይተዋል፡፡

መስቀሉ በእንጦጦ ጋራ ሳለ እግዚአብሔር አምላክ "አንብር መስቀልየ በዲበ መስቀል፤ መስቀሌን በመስቀለኛ ተራራ ላይ አስቀምጥ" የሚል ቃል ለንጉሡ በራእይ ነገራቸው፡፡ መስቀሉን ወደ ወሎ ሀገረ ስብከት እንዲወስዱትም አዘዛቸው፡፡ ንጉሡና ሠራዊታቸው በእግዚአብሔር መሪነት መስቀሉን ይዘው ወሎ ሲደርሱም ጌታችን ወደ አምባሰል እያመለከተ "አንብር መስቀልየ በዲበ መስቀል፤ መስቀሌን በመስቀለኛ ተራራ ላይ አስቀምጥ" ይላቸው ነበር፤ ንጉሡ መስቀሉን ይዘው ወደ ቦታው ሲያመሩ መስቀለኛው የግሸን ተራራን አገኙ፤ በዚያም ቤተ ክርስቲያን አሠርተው በ፲፬፻፵፮ (1446) ዓ.ም የጌታችንን መስቀል በክብር አስቀምጠውታል፡፡

ከዚህ በኋላ ንጉሡ ‹‹መካከሏ ገነት፤ ዳሯ እሳት ይኹን! የበረረ ወፍ፣ የሠገረ ቆቅ አይታደንባት! በድንገት ሰው የገደለ፣ ቋንጃ የቈረጠ ወንጀለኛ አይያዝባት!›› ብለው ዐዋጅ ነግረዋል፡፡ የእመቤታችን ጽላትም አብሮ በግሸን ደብረ ከርቤ እንዲቀመጥ አድርገዋል፡፡ ስለዚህም መስከረም ፳፩ ቀን በየዓመቱ በቤተ ክርስቲያናችን በድምቀት ይከበራል፡፡ ኀጢአታቸውን ለካህን ተናዘው፣ ንስሐ ገብተው በዚህ ዕለት ወደ ግሸን ደብረ ከርቤ በመሔድ የሚጸልዩና የሚማጸኑ ምእመናን ኹሉ እስከ ሰባት ትውልድ ድረስ የምሕረት ቃል ኪዳን እንደሚያገኙም ጤፉት በተባለው መጽሐፍ ተጠቅሷል፡፡ መጽሐፉ እንደሚለው በሃገራችን ያለው ግማደ መስቀሉ (የቀኝ እጁ) ብቻ ሳይሆን ሙሉው ዕፀ መስቀል ነው።

የእመቤታችን ማርያም ምልጃና ጥበቃ አይለየን!

©ማኅበረ ቅዱሳን

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

💠የመንፈስ ፍሬዎች💠

፭.ቸርነት

✞ ቸርነትን ግእዙ "ምጽዋት" ይለዋል። ከተቀባዩ ምንም ሳይፈልጉ የሚሰጡት ስጦታ ነው። አሁን ያሉ የኢትዮጵያ የአብነት መምህራን በችግር ተምረው ያገኙትን እውቀት በነጻ ያስተምራሉ። እውቀት ይመጸወታል። ገንዘብ ይመጸወታል። ጉልበትም ይመጸወታል። ሁሉም የቸርነት ሥራዎች ናቸው። ቸሩ እግዚአብሔር እንዲምረን እኛም ቸር እንሁን። ሰው በቸርነት ፈጣሪውን ይመስላል። እግዚአብሔር ቸር ስለሆነ እኛነታችንን፣ አካላችንን፣ ተፈጥሮን ሰጥቶናል። ከዚህ በኋላ በታናናሾች አድሮ ምጽዋትን እየተቀበለ ሰማያዊ ዋጋን ይሰጠናል። በኋላ በምጽአት ጻድቃንንና ኃጥዓንን ሲለይ በዋናነት የሚጠይቀው ቸርነትን (ምጽዋትን) ነው። ብራብ አብልታችሁኛል፣ ብጠማ አጠጥታችሁኛል፣ ብታረዝ አልብሳችሁኛል፣ እንግዳ ብሆን ተቀብላችሁኛል፣ ብታመም ጠይቃችሁኛል፣ ብታሰር አስፈትታችሁኛል የሚሉት ቃላት
ምሥጢራቸው ቸርነት ነው። ምጽዋት (ቸርነት) ሰው ፈጣሪን የሚመስልበት መልካም ሥራ ነው። ፈጣሪ ሁሉን በነጻ እንደ ሰጠን የሚመጸውት ሰውም ፈጣሪ ከሰጠው ጸጋ በነጻ የሚሰጥ ነው። ቸርነት (ምጽዋት) በከንቱ ዘነሳእክሙ በከንቱ ሀቡ ያለውን የሐዋርያውን ቃል በተግባር ማዋል ነው። ቸርነት ሰው ሌላውን ሰው
እንደራሱ ከመውደዱ የተነሳ የሚደረግ የመንፈስ ፍሬ ነው። ለዚያ ነው ቅዱስ ጳውሎስ ለገላትያ ሰዎች የመንፈስ ፍሬዎችን ሲነግራቸው አንዱ ቸርነት ነው ያላቸው። ገላ. ፭፣፳፪። የቸርነት ሥራዎች ለከንቱ ውዳሴ ከዋሉ ዋጋ አያሰጡም። ጌታ ሲያስተምር ቀኝህ የሰጠችውን ግራህ አትወቅ ምጽዋትህ ሰው ይይልኝ ብለህ
ሳይሆን በስውር ይሁን ያለን። አሁን ሰው መጽውቶ በማኅበራዊ ሚዲያ ካልተነገረለት ይከፋል። መምህር አስተምሮ ማስተማሩ በሁሉ ካልታወቀለት ይከፋዋል። ቸርነትና ውዳሴ ከንቱ አይስማሙም። በአደባባይ ከመወደስ በአደባባይ መሰደብ ይሻላል። ቸሩ መድኃኔዓለም ይቅር እንዲለን ቸርነትን ገንዘብ እናድርግ።

👉' በጎነት ' ይቀጥላል ...........

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

መስከረም 17 ቀን ማለትም የደመራ በዓል ማግስት የምናከብረው የመስቀል በዓል ደግሞ ንግሥት እሌኒ ደመራ አስደምራ እጣን አጢሳ (አስጢሳ) የመስቀሉን ቦታ ካወቀች በኋላ #ቁፋሮውን_ያስጀመረችበት ዕለት ስለሆነ ነው፡፡ ከቁፋሮውም በኋላ የጌታችን የመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል ዳግመኛ በእግዚአብሔር ፈቃድ፤ በእሌኒ ተነሳሽነት፤ በረዳቶቿ አጋዥነት ቁፋሮ በተጀምረ ከ5 ወር ከ23 ቀን በኋላ መስቀሉ መጋቢት 10 ተገኝቷል፤ ከ10 ዓመት በኋላም ቤተ መቅደሱ ታንጾ ቅዳሴ ቤቱ ተከብሯል፡፡ መስቀሉም እንደቀድሞ ድውያንን ሲያድን፣ ለምጻምን ሲያነጻ፣ ሽባዎችን ሲያቀና፣ ሙታንን ሲያስነሳ፣ የማያምኑትን ወደ ማመን ሲመልስ ነበር፡፡ ዛሬም የክርስቶስ መስቀል በዓለም እያበራ ሕሙማንን እየፈወሰ ይገኛል፡፡ ይህ የጌታ #ዕፀ መስቀልም በዓፄ #ዳዊት ዘመን ወደ ሃገራችን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ በተለያዩ ቅዱሳት መካናት (እንጦጦ #ማርያም፣ ጋራ #መድኃኔዓለም፣…..) ሲያርፍ ቆይቶ በስተመጨረሻው ‹‹አንብር መስቀልየ በዲበ መስቀል›› ተብሎ ለዓፄ #ዘርዓ ያዕቆብ በተነገረው መሠረት በደብረ ከርቤ ግሸን ማርያም በክብር አርፏል፡፡ እኛንም በመስቀሉ ፈዋሽነት ይማረን የመስቀሉን ፍቅር በልባችን ይሳልብን አሜን፡፡

* "መስቀል መልዕልተ ኩሉ ነገር: ያድኅነነ እምጸር" /ሊቁ ቅዱስ #ያሬድ/
* ‹‹ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል በቀር ሌላ ትምክህት ከእኔ ይራቅ።›› /ብርሃነ ዓለም ቅዱስ #ዻውሎስ ገላ.6፥14፣ 1ኛቆሮ.1፥18/

የመስቀል ክብረ በዓላት

መስከረም 16 የደመራ በዓል
መስከረም 17 የመስቀል በዓል
መስከረም 10 ተቀጸል ጽጌ
መጋቢት 10 መስቀሉ የተገኘበት በዓል

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

ጥልን በመስቀሉ ገደለ

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…
Subscribe to a channel