ethiopian_orthodox | Unsorted

Telegram-канал ethiopian_orthodox - የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

29777

በዚህ Channel ውስጥ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንን ዶግማ ፤ ቀኖና እና ትውፊት የጠበቁ ትምህርቶች ይተላለፉበታል፡፡ ለአስተያየት: ጥቆማና ጥያቄ በዚህ ያግኙን ☞ @Ethiopian_Orthodox_bot Buy ads: https://telega.io/c/Ethiopian_Orthodox

Subscribe to a channel

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

"በቁስሌ ላይ"
ዲ/ን ዘማሪ በኃይሉ ተበጀ

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

ጥቅምት ፳፯
መድኃኔ ዓለም ክርስቶስ

ጌታችን መድኃኔ ዓለም ክርስቶስ ለእኛ ሲል በፈጸመው የማዳን ሥራ ክፉዎች አይሁድ ከምሽቱ 3:00 ጌቴሴማኒ ውስጥ ያዙት::

¤ሙሉውን ሌሊት ከቀያፋ ወደ ሐና: ከሐና ወደ ቀያፋ ሲያመላልሱት: አስረው ሲደበድቡት አድረዋል::

ዝም ቢላቸው ዓይኑን ሸፍነው በጥፊ መቱት::
¤ምራቃቸውን ተፉበት:: ዘበቱበት::
¤ራሱንም በዘንግ መቱት::
¤እርሱ ግን ሁሉን ታገሰ::
¤በጧት ከገዢው ዘንድ ሞት እንዲፈረድበት አቀረቡት::

በሠለስት (3:00 ላይ) አካሉ እስኪያልቅ እየተዘባበቱ 6,666 ገረፉት::

ሊቶስጥሮስ አደባባይ ላይ እርጥብ መስቀል አሸክመው ወደ ቀራንዮ ወሰዱት:: 6:00 ላይ በረዣዥም ብረቶች 5 ቦታ ላይ ቸንክረው ሰቀሉት::

7 ታላላቅ ተአምራት በምድርና በሰማይ ታዩ:: ዓለም በጨለማ ሳለች ጌታ በመስቀል ላይ 7 ቃላትን
ተናገረ:: ከቀኑ 9:00 አካባቢ በባሕርይ ስልጣኑ ቅድስት ነፍሱን ከቅዱስ ሥጋው ለየ::

በዚያች ሰዓትም ወደ ሲዖል ወርዶ የታሠሩትን ሁሉ ፈታ::

11:00 ላይ ደጋጉ ዮሴፍና ኒቆዲሞስ ከታላቅ ክብርና ሐዘን ጋር በአዲስ መቃብር ቀበሩት:: በዚአች ቀን ድንግል ማርያም ልቧ በሐዘን ተቃጠለ:: ወዳጁ ቅዱስ ዮሐንስም ፍፁም ለቅሶን አለቀሰ:: ቅዱሳት አንስት በዋይታ ዋሉ::

ፈጣሪያችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለው መጋቢት 27 ቀን ቢሆንም በዓሉ ወደ ጥቅምት እንዲመጣ ያደረጉት አበው ሊቃውንት ናቸው:: ምክንያቱም ብዙ ጊዜ መጋቢት 27 የሚውለው ዓቢይ ጾም ውስጥ በመሆኑና የንግሥ በዓላት በዓቢይ ጾም ስለማይፈቀዱ ነው::

ምንም እንኩዋ በቅርብ ጊዜ በዓቢይ ጾም የሚያነግሡ አንዳንድ አብያተ ክርስቲያናት ቢኖሩም አባቶቻችን ግን እንዲህ ያለውን ሥርዓት አላቆዩልንም:: ከበሮና የቸብቸቦ ዝማሬም በወቅቱ የተፈቀደ አይደለም::

+በዚህም ምክንያት የበዓለ ስቅለት ንግሡ ወደ ጥቅምት 27 ሲመጣ: የመጋቢት 5 ገብረ መንፈስ ቅዱስ ንግሥ ወደ ጥቅምት 5: የመጋቢት 10 መስቀል ወደ መስከረም 17 መጥቶ እንዲከበር ሆኗል::

አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በቸርነቱ ይማረን ለሀገራችን ሰላሙን ይላክልን፤ አሜን!

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

"ማርያም ጎየይኪ"
ማርያም ጎየይኪ እምገጸ ሄሮድስ/፪/
ለአርእዮ/፬/ ተአምረ ግፍዕኪ/፪/

ትርጉም፦ ማርያም ሆይ የግፍሽን ተአምር ለማሳየት ከሄሮድስ ፊት ሸሸሽ ፡፡

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺
የ፳፻፲፰ ዓ.ም የጥቅምት ፲፮(የሦስተኛው ሰንበት) የጽጌ ማኅሌት

ዘሣልሳይ ሰንበት

🌴🌴🌴🌴🌴🌴🌴🌴🌴🌴🌴

የማንኛውም ወርኀ በዓልና ክብረ በዓል ሥርዐተ ማሕሌት መግቢያ

ስምዓኒ እግዚኦ ጸሎትየ፨
ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፨
ወይብጻሕ ቅድሜከ ገዐርየ፨
ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፨
ወኢትሚጥ ገጸከ እምኔየ በዕለተ ምንዳቤየ አጽምእ ዕዝነከ ኀቤየ፨
ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፨
አመ ዕለተ እጼውአከ ፍጡነ ስምዓኒ፨
ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ
ለዓለም ወለዓለመ ዓለም፨

ሃሌ ሉያ ዘውእቱ ብሂል፨
ንወድሶ ለዘሀሎ እግዚአብሔር ልዑል፨
ስቡሕ ወውዱስ ዘሣረረ ኵሎ ዓለመ፨
በአሐቲ ቃል።

መልክአ ሥላሴ

ሰላም ለኵልያቲክሙ እለ ዕሩያን በአካል፤
ዓለመክሙ ሥላሴ አመ ሐወጸ ለሣህል፤
እምኔክሙ አሐዱ እግዚአብሔር ቃል፤
ተፈጸመ ተስፋ አበው በማርያም ድንግል፤
ወበቀራንዮ ተተክለ መድኃኒት መስቀል።

ዚቅ

ሃሌ ሃሌ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሃሌ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሃሌ ሃሌ ሉያ፤
ሐረገ ወይን፤
እንተ በምድር ሥረዊሃ ወበሰማይ አዕፁቂሃ፤
ሐረገ ወይን፤
እንተ በሥሉስ ትትገመድ ወታፈሪ ለነ አስካለ በረከት፤
ሐረገ ወይን፤
ሲሳዮሙ ለቅዱሳን፤
ሐረገ ወይን፤
ሠርዐ ሰንበተ በቃሉ ወጸገወ ሰላመ ለኵሉ።

ዓዲ ዚቅ

ስብሐት ለአብ ለአኃዜ ኵሉ ዓለም፤
ስብሐት ለወልድ ለዘአክበራ ለማርያም፤
ስብሐት ለመንፈስ ቅዱስ ለዘአሰርገዋ ለምድር በጽጌያት።

፩ኛ. ማሕሌተ ጽጌ

ቀስተ ደመና ማርያም ትምእርተ ኪዳኑ ለኖኅ
ዘእግዚአብሔር ሤመኪ ለተዝካረ ምሕረት ወፍትሕ፤
ህየንተ ቀሰፋ ለምድር ወአማሰና በአይኅ፤
በእንቲኣኪ አሰርገዋ በጽጌ ኵሉ አቅማሕ፤
ከመ ለከዋክብት አሰርገዎ ለሰማይ ስፉሕ።

ዚቅ

ንጉሥኪ ጽዮን አሰርገዋ ለምድር በጽጌያት፤
ወለሰማይና በከዋክብት፤
ውእቱ ክብሮሙ ለቅዱሳን።

፪ኛ. ማሕሌተ ጽጌ

እንዘ  ተሐቅፊዮ ለሕፃንኪ ጽጌ ጸዓዳ ወቀይሕ፤
አመ ቤተ መቅደስ ቦእኪ በዕለተ ተአምር ወንጽሕ፤
ንዒ  ርግብየ  ትናዝዝኒ  እምላሕ፤
ወንዒ  ሠናይትየ ምስለ ገብርኤል ፍሡሕ፤
ወሚካኤል ከማኪ ርኅሩኅ።

ዚቅ

በሰላም ንዒ ማርያም ትናዝዝኒ ሐዘነ ልብየ፤
በሰላም ንዒ ማርያም ምስለ ሚካኤል ወገብርኤል፤
በሰላም ንዒ ማርያም ምስለ ሱራፌል ወኪሩቤል፤
በሰላም ንዒ ማርያም ምስለ ኵሎሙ ቅዱሳን፤
በሰላም ንዒ ማርያም ምስለ ወልድኪ አማኑኤል፤
በሰላም ንዒ ማርያም ለናዝዞ ኵሉ ዓለም።

፫ኛ. ማሕሌተ ጽጌ

ክበበ ጌራ ወርቅ ጽሩይ እምዕንቈ ባሕርይ  ዘየኀቱ፤
ዘተጽሕፈ ብኪ  ትእምርተ ስሙ ወተዝካረ ሞቱ፤
አክሊለ ጽጌ ማርያም  ለጊዮርጊስ ቀጸላ  መንግሥቱ፤
አንቲ  ኵሎ ታሰግዲ ሎቱ፤
ወለኪኒ ይሰግድ ውእቱ፡፡

ዚቅ

በወርቅ ወበዕንቍ ወበከርከዴን፤
ስርጉት ስርጉት በስብሐት፤
ወነገሥት ይትቀነዩ ለኪ፤
ትርሲተ መንግሥቱ አንቲ መድኃኒቶሙ ለነገሥት፤

ዓዲ ዚቅ

ርግብ ጸዓዳ ዘዕንቍ ድዳ፤
ወዘጳዝዮን ማኅፈዳ፤
ተወልደ ዮም በምድረ ይሁዳ።

፬ኛ. ማሕሌተ ጽጌ

ይትባረክ ጽጌኪ ማርያም ለልብየ ፍቅርኪ ዘከፈሎ፤
ወኢያርኀቀ እምኔየ ለኪዳንኪ ሣህሎ፤
ትእምርት ኪዳንኪ ይሁብ ለዘማውያን ተደንግሎ፤
ሶበሰ ኪዳንኪ ምክንያተ ድኂን ኢሀሎ፤
ፈለገ እሳት ወደይን እምአስጠመ ኵሎ።

ዚቅ

አስተብፅዕዋ ወይቤልዋ እለ ይነብሩ ፈለገ እሳት፤
ሰአሊ ለነ ማርያም ቅድስቱ ለእግዚአብሔር።

ዓዲ ዚቅ

ይጸድቁ ኃጥአን በኪዳንኪ፤
እለ ገብሩ ተዝካረኪ ወጸውዑ ስመኪ፤
ይጸድቁ ኃጥአን በኪዳንኪ፤
ወዘሐለዩ ካህናት ማሕሌተ በበዓልኪ፤
ማርያም በሊዮ ለወልድኪ ይሰምዐኪ፤
ይጸድቁ ኃጥአን በኪዳንኪ፤
ይጸድቁ ኃጥአን በኪዳንኪ።

፭ኛ. ሰቆቃወ ድንግል

ብክዩ ሕዙናን ኀልየክሙ ስደታ፤
ወላሕዉ ፍሡሓን ተዘኪረክሙ ብዝኀ ሠናይታ፤
ማርያም ተዐይል ከመ ዖፍ ውስተ አድባረ ግብፅ ባሕቲታ፤
ተአወዩ በኃጢኦታ ሀገረ አቡሃ ኤፍራታ፤
ወደመ ሕፃናት ይውኅዝ በኵሉ ፍኖታ።

ዚቅ

አመ አጕየይኪ እምሰይፍ ዕጓለኪ በሐቂፍ፤
አድባራተ ዔልኪ ከመ ዖፍ፤
እንዘ ከመ ዝናም ያንጸፈጽፍ፤
እምአዕይንትኪ እንብዕ ወእመላትሕኪ ሐፍ።

🪷🪷🪷🪷🪷🪷🪷🪷🪷🪷🪷
መዝሙር በ

ወመኑ መሓሪ ዘከማከ፤
ወመኑ መሓሪ ዘከማከ፤
ምስለ ኖኅ ኪዳነ ዘዐቀምከ
ወመኑ መሓሪ ዘከማከ፤
ምስለ ኖኅ ኪዳነ ዘዐቀምከ፤
ለደቂቀ ፳ኤል መና ዘአውረድከ፤
ወመኑ መሓሪ ዘከማከ፤
ለደቂቀ ፳ኤል መና ዘአውረድከ፤
ወበጽጌያት ምድረ አሰርጎከ፤
ወመኑ መሓሪ ዘከማከ፤
ወበጽጌያት ምድረ አሰርጎከ፤
ወሥነ ገዳምኒ ምስለ ቅዱሳኒከ፤
ወመኑ መሓሪ ዘከማከ፤
ወከመ ወሬዛ ኀየል መላትሒሑ፤
ጕርዔሁ መዓርዒር አምሳሉ ዘወይጠል፤
ወመኑ መሓሪ ዘከማከ፤
ሰማየ ወምድረ ዘአንተ ፈጠርከ፤
ፀሐየ ወወርኀ ዘአስተዋደድከ፤
ወመኑ መሓሪ ዘከማከ፤
በከዋክብት ሰማየ ዘከለልከ፤
ወበጽጌያት ምድረ አሰርጎከ፤
ወመኑ መሓሪ ዘከማከ፤
ቀደሳ ወአክበራ አዕበያ ለሰንበት፤
ወአልዐላ እምኵሉ ዕለት፤
ወመኑ መሓሪ ዘከማከ፤
ወኵሉ ይሴፎ ኪያከ።
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿

©ማሕሌተ ያሬድ
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

"የስደት ዘመንሽ"
መከራን ታግሰሽ ገሊላ የገባሽ ፣
ለዓለም መፅናኛ ነው የስደት ዘመንሽ

በጠላት ፈተና ከሀገር ተሰደሽ
 ስትንከራተቺ አምላክን ታቅፈሽ
 ከገሊላ አንስቶ እስከ ግብፅ በረሃ
የሚያዝንልሽ አጣሽ የሚሰጥሽ ዉኃ   

አዝ......

ሰሎሜ ትመስክር ያየሽውን ጭንቀት
 ዮሴፍም ይናገር የሀዘንሽን ብዛት
 እመቤቴ ማርያም ከአንድ ልጅሽ ጋራ
 በግብፅ በረሃ ያየሽዉ መከራ  
አዝ......

  ውርጭና ፀሓዩ ሲፈራረቅብሽ
  ረሀብና ጥሙ እንዲያ ሲያንገላታሽ     
  በለጋነት ዕድሜ በሄሮድስ ቅናት
  ከልጅሽ ጋር አየሽ መከራ ስደት   
አዝ......

   ልጅሽ አንዲምረን ስለእኛ እንዲራራ
ለበረከት ሆነ ያየሽው መከራ    
   መልካም ፍሬ አፈራ ያነባሽው ዕንባ
   ምክንያት ለኛ ሆነ ገነት እንድንገባ
አዝ......


@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

፬ኛ የልጇን ጫማ በወሰዱባት ጊዜ
ከነጥጦስ የተረፈው የጌታችን ጫማ ዲያብሎስ ባስቀመጣቸው የመንደር ምልምሎች ከመወሰድ አልዳነም፡፡ ነገሩ እዲህ ነው፡- ከዕለታት አንድ ቀን ቁራሽ ልመና ስትሄድ የልጇን ልብስ እና ጫማ ከአንድ ዋሻ ውስጥ አስቀምጣ ነበር የሄደችው፤ ብትሄድ ሰይጣን እንደ ፈርዖን የሰውን ልብ አፅንቶት ምንም ቁራሽ ሳታገኝ ተመለሰች፡፡ እንኳን ቁራሽ እፍኝ ውኃ መስጠትንም ከለከሏት፤ ከዚህም ብትመለስ የልጇን ጫማ አጣች፤ ያን ጊዜ “ሰአልክወሙ ማየ ኢወሀቡኒ በሕቅ ወኀጐልኩ ለወልድየ አሳዕኖ ዘወርቅ፤ ጥቂትን ውኃን ለመንሁ አልሰጡኝም የልጄን ጫማም አስወሰድኩስትል አምርራ አለቀሰች፡፡
ቤተክርስቲያን በዚህ ዓለም ክርስቶስን ተሸክማ በስሙ ተጠርታ እስከ ዓለም ፍጻሜ የምትሰደደውን መሰደድ ድንግል ጀመረችው፡፡ በዚህም በመጻሕፍት ሁሉ ስሟ ሲጠራ እመ ስማዕታት መዋዕያን፤ ያሸናፊዎች ሰማዕታት እናት እየተባለች ትጠራለች በተለይም በዘመኑ መጨረሻ ሐሳዊ መሲሕ ነግሦ ቤተክርስቲያንን ለአርባ ሁለት ወራት የሚያሳድዳት መሆኑን አስቀድሞ በሄሮድስ ንግሥና እመቤታችን ለአርባ ሁለት ወራት በመሰደዷ ነገረን፡፡
እመቤታችን የስደቷ መከራ እያንዳንዱ ቢነገር አስገራሚ እና አሳዛኝ ሲሆን ከሦስት ዓመት ከመንፈቅ በኋላ ግንቦት ሃያ ስድት ቀን ተጀምሮ ኅዳር 6 ቀን በድል ተጠናቀቀ፡፡ ብዙ ሕጻናትን የፈጀው ሄሮድስ ሐሳቡ ሳይሳካ ግብዓተ መሬቱ ተፈጸመ፡፡ የሕፃናቱ ጩኸት፣ የእናቶቻቸውም ለቅሶ እና ዋይታ የተሰማባት ገሊላ ዛሬ ስለ ልጆቿ መጽናናትን እምቢ የምትለዋ ራሔል ሳትሆን የምታለቅስበት የንጉሥ ቤተሰቦች የለቅሶ ስፍራ ናት፡፡
የዚህ ዓለም ደስታ በፈረቃ ነውና ከ1260 ቀናት በኋላ ያዘነችው ድንግል ደስ ይላት ዘንድ በበረሐ ሳለች “መከራዬን አይቶ ይረዳኝ ዘንድ ትጸንሻለሽ ብሎ ያበሠረኝ መላክ ወዴት ነው?'' ስትለው የነበረው መላክ ቅዱስ ገብርኤል መጥቶ ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ነገራቸው፡፡
ጌታ ጠላቶቹን መምታት የጀመረው ከሄሮድስ ጀምሮ ነው፤ የመጨረሻው ዲያብሎስ ነው፡፡ እንዲህ የሚመስሉ ብዙ የመዳን ተስፋዎችን የያዘው የግብፅ መልሳቸው ከዚህ በላይ የአበው ነቢያት ተስፋ ትንቢትን ፍጹም ያደረገ ቀን ነበር፡፡ በትንቢታቸው ቅዱስ መጽሐፍ ከመዘገባቸው ዐበይት እና ደቂቅ ነቢያት ቃለ ትንቢታቸው ተናግረውት እስካልተመዘገበላቸው የቃል ነቢያት ድረስ የመመለሱን ዜና ለዓለም አውጀዋል፡፡
ከነቢያት አንዱ “እምግብፅ ጸዋዕክዎ ለወልድየ፤ ልጄን ከግብፅ ጠራሁት" ሆሴ 11፥1 ብሎ ስለ ግብፁ ስደተኛ ክርስቶስ በባሕርይ አባቱ ዘንድ የታሰበውን ሲገልጽ ሌላው ነቢይ ደግሞ “አንቺ ሱላማጢስ ሆይ ተመለሽ ተመለሽ እናይሽ ዘንድ ተመለሽ" መኃ 7፥1 ሲል ናፍቆቱን ይገልጽላታል፡፡
ከቃል ነቢያት አንዱ ስሙ ያልታወቀ ነቢይም “ልጄ ናዝራዊ ይባላል" ብሎ የተናገረው ሳይደርስ እንደደረሰ፣ ሳይደረግ እንደተደረገ አድርጐ የተናገረው እንዲፈጸም ከቦታዎቹ ሁሉ ናዝሬትን መርጠው ተቀመጡ፡፡
ልብ በሉ! የእመቤታችን ወደ ናዝሬት መመለስ የእኛን ወደ ገነት የመመለስ ምሥጢር የያዘ በመሆኑ ነው በነቢያት ሁሉ በናፍቆት ይጠበቅ የነበረው፡፡ ይህ ደግሞ የተፈጸመው ነፍሰ ገዳዩ ንጉሥ ሄሮድስ ዓለምን ተሰናብቶ ማለቂያ ወደ ሌለው የጨለማ ዓለም ከተዛወረበት በኋላ መሆኑ ከጥንት ጀምሮ በእውነት የማይቆመው ነፍሰ ገዳዩ የአባቶቻችን ከሳሽ ዲይብሎስ ከተገደለ በኋላ አማናዊው የሰው ልጆች መዳን የሚፈጸም መሆኑን አመላካች ነው፡፡

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

፩ኛ ምጽአተ ዮሳ ወልደ ዮሴፍ
ዮሳ በመጽሐፍ የጌታ ወንድሞች ተብለው አይሁድ ከዘረዘሯቸው ስዎች አንዱ ሲሆን ማቴ 13፥55 የስደቱ ታሪክ በተጀመረበት ሌሊት አብሮ ከዚህ ታሪክ ተካፋይ ነበር፡፡ ጥቂት እንደሄደ ግን ከበረከተ ስደቱ ሊካፈል የማይገባው ሰነፍ ሰው በመሆኑ ከጐዳናው ላይ ተለይቶ ቀረ፡፡
በኋላ ግን ዘመዶችህን ሊያስገድል ሄሮድስ ጭፍራ ሰደደ ሲሉ ቢሰማ እግሮቹ ለበረከት ባይሆንም ለመርገም ፈጣኖች በመሆናቸው ማንም ሳይቀድመው ለስደተኞች የወሬ ስንቅ ተሸክሞላቸው ሮጠ፡፡ ሲደርስ ደክመው ጥላ ሥር አርፈው አገልጋይቱ ሰሎሜ ሕጻኑ ኢየሱስ ክርስቶስን ስታጥበው ከወንዝ ዳር ነበር ያገኛቸው፡፡ ከመድረሱ ቸር ዋላችሁ፣ ቸር አደራችሁ እንኳን አላለም፤ ይህን ሕጻን ልታስገድሉት ከዚህ ተቀምጣችኋል ሄሮድስ ጭፍሮችን በየሀገሩ አሰማርቷል ሲል እመቤታችን ከሰሎሜ እጅ ሕጻኑን ተቀብላ ይህን ሁሉ መከራ የተቀበልኩት ላላድንህ ነው ብላ ምርር ብላ አልቅሳለች፡፡
፪ኛ ሁለቱ ወንበዴዎች ባገኟት ጊዜ
ጥጦስን እና ዳክርስን ያስተባበራቸው ቃል ኪዳናቸው ውንብድና ነው፡፡ ለማንም ላይራሩ ተማምለው ሥራውን ከጀመሩ ሰነባብተዋል፡፡ በጥጦስ መምህርነት፣ በዳክርስ ተማሪነት የተጀመረው ይህ ተግባር በድሃውም በባለጠጋውም እንዲጨክኑ አድርጎአቸዋል፡፡
በዚህ ወቅት ነው ድንግል ከነልጇ በዚህ ጫካ ያገኘቻቸው፤ የጠፉትን ፍለጋ የመጣው ጌታችን ግን የራሱ የሆነ ጉዳይ ነበረው ወደ ዚህ በረሐ የመጣበት፤ ከነዚህ ሽፍቶች አንዱ ከደጋጉ ቅዱሳን ከነ አብርሃም፣ ይስሐቅ፣ ያዕቆብ ተቀድሞ ደመ ማኅተሙን ይዞ ገነት የሚገባ ነውና አስቀድሞ ይህን የምሥራች ሊነግረው ወደ ዚህ መጣ፡፡
ሊቀሟቸው እየተሯሯጡ ሲመጡ ሰሎሜ አስቀድማ ልብሷን ጥላ ሸሸች የእመቤታችን መጐናጸፊያውንና የጌታን ሰብአ ሰገል የገበሩለትን የወርቅ ጫማና ቀሚስ ነጥቀው ወሰዱ፡፡ አዳም እና ሔዋን የብርሃን መጐናጸፊያቸውን ተገፈው ነበርና ለዚያስ ካሳ እንዲሆን ነው፡።
እመቤታችንን ያስለቀሳት ግን የልብሱ መነጠቅ ሳይሆን ጥቂት አለፍ ብለው ነገር መጀመራቸው ነው፡፡ እነሱ የሚመክሩት የቀሙትን ልብሳቸውን የሚመልሱበትን መንገድ ሲሆን እመቤታችን ደግሞ ሌባ አዩኝ አላዩኝ ብሎ ያገኘውን ዘርፎ ይሄዳል እንጂ እንዲህ የልብ ልብ ተሰምቶት ይቆማልን? እኒህማ ልጄን ሊገድሉ የተላኩት ይሆናሉ ስትል ስለ ልጇ ዳግመኛ አምርራ አለቀሰች፡፡ በቅዱሳት እጆቹ የተወደደ ልጇ እንባዋን ከዓይኗ እስከጠረገላት ድረስ በተወደደ ልጇ ደረት ላይ እንባዋን አፈሰሰች፡፡
፫ኛ ቤተ ኮቲባ
አንዳንዱ ቤት ከሰው እስከ ስማያዊው አምላክ የሚስተናገዱበት፣ የሰማዩ አባታችን የእግዚአብሔር ፈቃድ የሚፈጸምበት ማኅደረ እግዚአብሔር ይሆናል፡፡ አንዳንዱ ደግሞ ሰይጣን ጥላውን ይጥልበትና በረከት አልባ፣ ሊተኙበት የሚያባባ፣ ባል እና ሚስትን የማያግባባ፣ አስቸጋሪ ይሆናል ቤተ ኮቲባም እንዲህ ነበር፡፡
በወቅቱ ከነበሩት የምድር ባለጠጐች የአንዱ ቤት ሲሆን ከብዙ ሀብት መካከል ጥቂት ቸርነት ካልተገኘ አስቸጋሪ ነውና እመቤታችን ስመ እግዚአብሔር ጠርታ ስትለምን የተመለከተች የቤቱ ባለቤት ልብን ከመዶሻ ይልቅ የሚሰብር ጨካኝ ቃላትን ተናገረች፡፡ የሰነፍ ሰው ንግግር እንደ አሸዋ ከባድ ነው፤ እንደ ፍላፃም ተዋጊ ነው፡፡ “አንቺ ሴት ደረቅ ሴት ነሽ መስለኝ እንጂ እንደ አንች ያለ መልከ መልካም ሴት ከመጋረጃ ይወጣ ነበርን" ስትላት አረጋዊው ዮሴፍ ተቀብሎ "ለለማኝ ቢኖር ይሰጡታል ባይኖር ካለው ያድርስህ ይሉታል እንጅ እንዲህን በነገር ይወጉታል” አላት፡፡
ኮቲባ የተሰኘችው አገልጋይ ደርቡን እያናወጠች ወርዳ ዮሴፍን በጥፊ ቃጥታ ጌታን ከእመቤታችን ጀርባ ነጥቃ ከመሬት ቀላቀለችው፤ ሕጻኑ ትክን ትክን ብሎ ሲያለቅስ እመቤታችንም ጩኸት እና ድንጋጤ የከበበው ብርቱ ለቅሶን አልቅሳለች፡፡
ይቀጥላል .....

(ሕይወተ ማርያም - በሊቀ ሊቃውንት ስምዐኮነ መልአክ)

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

እመቤታችን ከመልአከ ብሥራቷ ከቅዱስ ገብርኤል በተረዳችው መሠረት ወደ ምድረ አፍሪቃ ይዛው ስትመጣ ያን ጊዜ አባቶቿ ነቢያት የተናገሩት ተፈጸመ “ጌታ በፈጣን ደመና ተጭኖ ወደ ግብጽ ይመጣል" ኢሳ 19፥1 የነቢያት ቃል እንዲፈጸም ብቻም ሳይሆን በዓለማችን ልዩ ልዩ ክፍላት ተሰማርተው ጣዖት ያስመልኩ፣ ኃጢአት ያሠሩ የነበሩ አጋንንት፣ ሊቃነ አጋንንት ከምድር ጨርሰው እስኪሰደዱ ጌታ ተሰደደ፡፡
እመብርሃን ድንግል በዚያ ወቅት በብዙ መንገድ ተፈተነች፤ የሄሮድስ ሠራዊቶች ከተማ ለከተማ ይሄዱ፣ ጐዳናውን ይዘው ይከታተሏቸው ነበርና ከዚያ ለማምለጥ ጫካ ለጫካ ይሄዱ ስለነበር በከባድ ረሐብና በታላቅ ውኃ ጥም ተፈተኑ፡፡ የእስራኤልን መና፣ የዐለቱን ልብ አላልቶ ውኃን የሚያጠጣውን ጌታ በጀርባዋ ይዛ ተራበች፣ ተጠማች፤
አባቷ አዳም እናቷ ሔዋንን ከዘለዓለማዊ የነፍስ ረሐብና ጥም የሚያድነውን ጌታ ነውና የያዘችው ተራበች፣ ተቸገረች፡፡ ከዕለታት በአንድ ቀን እንኳን ወደ መንደር ገብተው ቁራሽ እንጀራ ጥርኝ ውኃ ሲለምኑ የሚሰጣቸው አልነበረም፡፡ ዓለም ምን አላትና ሁሉን በእጁ ለያዘው ምን ትሰጠዋለች ጌታ ራሱን እስኪሰጠን ድረስ የምንሰጠው አንዳች ነገር የሌለን ድሆች ነበርን፤ ባለጠጐች የሆንነው ባለጠጋው ጌታ ራሱን የሰጠን ጊዜ ነው፡፡ ከረሐቡ ጋር አብሮ የማይረሳው ደግሞ በግብፅ ምድረ በዳ የተደረገው ጉዞ ነው፤ የግብፅ በረሐ በአሸዋ የተሞላ ሰውነትን የሚያሳርፍ ምንም ዓይነት ለምለም ነገር የሌለው፣ አሸዋው እግርን የሚያቃጥል የፀሐዩ ግለት ነፍስን ከሥጋ ለይቶ የሚጥል እሾህ እና አሜካላን የሚያበቅል ምድረ በዳ ነው፡፡
ከአዳም በደል የተነሣ የረከሰችውን ምድር ሊቀድሳት የተረገመችውን ሊባርካት የመጣው ጌታ የሰውን ሕማም በሥጋው መከራን ሲቀበል ዳግማዊት ሔዋን እመቤታችንም እንደ እናቷ ሔዋን ከብርቱ እንባ ጋር መከራን ተቀበለች፡፡ ሔዋን በሕማም፣ በምጥ እንድትወልድ ሲፈርድባት ላለቀሰችው እንባ አምሳል የሚሆን እንባ በመውለዷ ጊዜ ይህ ሁሉ ያልደረሰባት እመቤታችን አነባች፡፡ ሦስት ዓመት ከመንፈቅ መከራው ያልተለያት ቢሆንም በተለይ አራቱ ፀዋትወ መከራዎቿ ሁል ጊዜ ሲታወሱ ይኖራሉ፡፡

ይቀጥላል .....

(ሕይወተ ማርያም - በሊቀ ሊቃውንት ስምዐኮነ መልአክ)

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺
የ፳፻፲፰ ዓ.ም የጥቅምት ፱(የሁለተኛው ሰንበት) የጽጌ ማኅሌት

ዘካልኣይ ሰንበት

🌴🌴🌴🌴🌴🌴🌴🌴🌴🌴🌴🌴🌴🌴

የማንኛውም ወርኀ በዓልና ክብረ በዓል ሥርዐተ ማሕሌት መግቢያ

ስምዓኒ እግዚኦ ጸሎትየ፨
ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፨
ወይብጻሕ ቅድሜከ ገዐርየ፨
ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፨
ወኢትሚጥ ገጸከ እምኔየ በዕለተ ምንዳቤየ አጽምእ ዕዝነከ ኀቤየ፨
ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፨
አመ ዕለተ እጼውአከ ፍጡነ ስምዓኒ፨
ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ
ለዓለም ወለዓለመ ዓለም፨

ሃሌ ሉያ ዘውእቱ ብሂል፨
ንወድሶ ለዘሀሎ እግዚአብሔር ልዑል፨
ስቡሕ ወውዱስ ዘሣረረ ኵሎ ዓለመ፨
በአሐቲ ቃል።


መልክአ ሥላሴ

ሰላም ለአፉክሙ ዘማዕፆሁ ሰላም
ጽጌያቲሁ ሥላሴ ለተዋሕዶ ገዳም
መንገለ አሐዱ አምላክ ንዋየ መጻኢት ዓለም
ወልጡ አምልኮትየ በጸጋክሙ ፍጹም
እምአምልኮ ጣዖት ግሉፍ አሐዱ ድርህም።

ዚቅ

ለሥሉስ ቅዱስ ጥዑም ቃሎም
ናርዶስ ጸገየ ውስተ አፉሆሙ።

፩. ማሕሌተ ጽጌ

በከመ ይቤ መጽሐፍ ማዕከለ ፈጣሪ ወፍጡራን
ለዕረፍት ዘኮንኪ ትእምርተ ኪዳን
ሰንበተ ሰንበታት ማርያም ዕለተ ብርሃን
ብኪ ይትፌሥሑ ዘገነተ ጽጌ ጻድቃን
ወብኪ ይወጽኡ ኃጥአን እምደይን፡፡

ወረብ

በከመ ይቤ መጽሐፍ ማዕከለ ፈጣሪ ወፍጡራን ዘኮንኪ ለዕረፍት ትእምርተ ኪዳን/፪/
ብኪ ይትፌሥሑ ዘገነተ ጽጌ ጻድቃን ብርሃን ዕለተ ብርሃን/፪/

ዚቅ

ሰንበቶሙ ይእቲ ለጻድቃን ትፍሥሕት፤
ሰንበቶሙ ይእቲ ለኃጥአን ዕረፍት፤
ኅቡረ ንትፈሣሕ ዮም በዛቲ ዕለት፡፡

፪. ማሕሌተ ጽጌ

እንዘ ተሐቅፊዮ ለሕፃንኪ ጽጌ ጸዓዳ ወቀይሕ
አመ ቤተ መቅደስ ቦእኪ በዕለተ ተአምር ወንጽሕ
ንዒ ርግብየ ትናዝዝኒ እምላሕ
ወንዒ ሠናይትየ ምስለ ገብርኤል ፍሡሕ
ወሚካኤል ከማኪ ርኅሩኅ።

ወረብ

ንዒ ርግብየ ንዒ ርግብየ ምስለ ሚካኤል/፪/
ወንዒ ሠናይትየ ወንዒ ሠናይትየ ምስለ ገብርኤል ፍሡሕ/፪/

ዚቅ

ንዒ ርግብየ ሰላማዊት ንባብኪ አዳም ከመ ፍሕሶ ቀይሕ ከናፍሪሃ እሞሙ ለሰማዕት ወእኅቶሙ ለመላዕክት አልቦ ዘይመስል ዘከማኪ ክብረ እግዚኣ ለሰንበት በማሕፀንኪ ተጸውረ።

፫. ማሕሌተ ጽጌ

ክበበ ጌራ ወርቅ ጽሩይ እምዕንቄ ባሕርይ ዘየኀቱ
ዘተጽሕፈ ብኪ ትእምርተ ስሙ ወተዝካረ ሞቱ
አክሊለ ጽጌ ማርያም ለጊዮርጊስ ቀጸላ መንግሥቱ
አንቲ ኵሎ ታሰግዲ ሎቱ
ወለኪኒ ይሰግድ ውእቱ።

ወረብ

ክበበ ጌራ ወርቅ ዘየኀቱ እምዕንቈ ባሕርይ/፪/
ማርያም አክሊለ ጽጌ ለጊዮርጊስ ቀጸላ መንግሥቱ/፪/

ዚቅ

ይእቲ ተዐቢ እምአንስት እሞሙ ለሰማዕት ወእኅቶሙ ለመላእክት መድኃኒቶሙ ለነገሥት አክሊል ንጹሕ ለካህናት ብርሃኖሙ ለከዋክብት።

፬. ማሕሌተ ጽጌ

አንብርኒ ማርያም ውስተ ልብኪ ከመ ኅልቀት
በከመ ማዕተብ ጹርኒ በመዝራዕትኪ ልዕልት
በእንተ ርስሐትየሰ ኢትመንንኒ ንግሥት
እስመ ወሀብኩ ንብረትየ ለፍቅርኪ ሞት ዘአሰርገዎሙ ለሰማዕት በጽጌሁ ሕይወት።

ወረብ

አንብርኒ ማርያም ውስተ ልብኪ ከመ ኅልቀት በከመ ማዕተብ ጹርኒ በመዝራዕትኪ ልዕልት/፪/
በእንተ ርስሐትየሰ ኢትመንንኒ ኢትመንንኒ ንግሥት በእንተ ርስሐትየሰ/፪/

ዚቅ

በከመ ከዋክብት ያሰረግውዎ በሰማይ በሥኖሙ ከማሁ ሰማዕትኒ ያሰረግውዋ ለቤተ ክርስቲያን በገድሎሙ።

ዓዲ ዚቅ

አሠርገዎሙ ለሰማዕት በሰማያት አሰርገዎሙ ለሰማዕት በሰማያት
ሰንበተ ክርስቲያን ለዕረፍት ሠርዐ ሎሙ አሠርገዎሙ ለሰማዕት በሰማያት
ከመ ወርቅ በእሳት ፈተኖሙ
አሠርገዎሙ ለሰማዕት በሰማያት
ወከመ ጽንሓሐ መሥዋዕት ተወክፎሙ አሠርገዎሙ ለሰማዕት በሰማያት

ሰቆቃወ ድንግል

ኢየሱስ ስዱድ ተስፋሆሙ ለስዱዳን
ኢየሱስ ግፉዕ  ምስካዮሙ ለግፉዓን
እግዚአብሔር ማኅደር  ዘአልቦ  ከመ  ነዳያን
ኢየሱስ ነግድ  ወፈላሲ እንዘ ውእቱ ሕፃን
ወልደ አብ ፍቁር  ዘበኀበ ሰብእ ምኑን
መኃልየ  ብካይ ኮነኒ ዘእሙ  ሐዘን።

ወረብ

ኢየሱስ ስዱድ ተስፋሆሙ ለስዱዳን/፪/
መኃልየ ብካይ ኮነኒ ኮነኒ ዘእሙ ሐዘን/፪/

ዚቅ

አንተ ውእቱ ምርጕዞሙ ለጻድቃን
ተስፋሆሙ ለስዱዳን
መርሶሙ ለእለ ይትሀወኩ
ብርሃነ ፍጹማን ወልደ አምላክ ሕያው ።

ዓዲ ዚቅ

ሰርጐሙ ለሐዋርያት ንዋየ ነዳያን ወምስካየ ግፉአን ሠርከ ነአኵተከ መሐሪ ንጉሥ ዘኢይትኄየይ ተግባሮ።

🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
መዝሙር በ፫

ኪነ ጥበቡ መንክር ወዕጹብ
ኪነ ጥበቡ መንክር ወዕጹብ
ለዘሀሎ መልዕልተ አርያም
አርአየ ምሕረቶ በላዕሌነ
ዘከለሎ ለሰማይ በከዋክብት ብሩህ
አርአየ ምሕረቶ በላዕሌነ
ወለምድርኒ አሰርገዋ በጽጌያት ንጹሕ አርአየ ምሕረቶ በላዕሌነ
ወሠርዐ ሰንበተ ለነባሪ ያዕርፉ ባቲ
አርአየ ምሕረቶ በላዕሌነ
ማ፦ አርአየ ምሕረቶ በላዕሌነ
መዓዛሆሙ ለቅዱሳን ከመ ጽጌ ደንጐላት ዘውስተ ቈላት
ጸገዩ ቀንሞስ ምስለ ናርዶስ።

ሰላም በ

ሐረገ ወይን
እንተ በምድር ስረዊሃ ወበሰማይ አዕጹቂሃ
ሐረገ ወይን
እንተ በሥሉስ ትትገመድ ወታፈሪ ለነ አስካለ በረከት
ሐረገ ወይን
ሲሳዮሙ ለቅዱሳን
ሐረገ ወይን
ሠርዐ ሰንበተ በቃሉ ወጸገወ ሰላመ ለኵሉ።
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿


©ማሕሌተ ያሬድ
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

. ቅድስት ሥላሴ
⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️
በ ‹‹ምሥጢረ ሥላሴ›› ትምህርት እንደምንረዳው ቅድስት ሥላሴ አንድም ሦስትም ናቸው፡፡ ‹‹ሥላሴ›› የሚለው ቃል ‹‹ሠለሰ፤ ሦስት አደረገ›› ከሚለው የግእዝ ግሥ የተገኘ ሲሆን ትርጉሙ ሦስትነት ማለት ነው፡፡ (መጽሐፍ ሰዋስው ወግስ ወመዝገበ ቃላት ገጽ ፮፻፷፱)

ቅድስት ሥላሴ ስንልም አብ፣ ወልድ፣ መንፈስ ቅዱስ ማለታችን ነው፡፡ ‹‹ቅድስት›› ተብሎ ደግሞ በሴት አንቀጽ /ቅድስት ሥላሴ/ ይጠራል፤ ‹‹ቅድስት›› እና ‹‹ልዩ ሦስት›› የሚባልበትም ሃይማኖታዊ ምሥጢር፡-

፩. ቅድስት

ሥላሴ ‹‹ቅድስት›› ተብለው በሴት አንቀጽ መጠራታቸው ሴት /እናት/ ልጅዋን መውለዷን እንደማትጠረጥረው ሁሉ ሥላሴም ይህን ዓለም መፍጠራቸውን ስለማይጠረጥሩ ነው፡፡ ሁሉም ከእነርሱ፣ ለእነርሱ፣ በእነርሱ ሆኗልና፡፡ ሴት ወይንም እናት ልጅዋ ቢታመምባት እንዲሞትባት አትሻም፤ ሥላሴም ከፍጥረታቸው አንዱ እንኳን በጠላት ዲያብሎስ እንዲገዛባቸው አይፈቅዱም፡፡ ሴት ፈጭታ ጋግራ ቤተሰቦቿን እንደምትመግበው ሥላሴም በዝናም አብቅለው በፀሐይ አብስለው ፍጥረቱን ሁሉ ስለሚመግቡ ‹‹ቅድስት ሥላሴ›› እያልን እንጠራቸዋለን፡፡

፪. ልዩ ሦስትነት
በትምህርተ ሃይማኖት ሥላሴ በቅድምና፣ በፈጣሪነት፣ በሥልጣን፣ በመመስገን፣ በክብር፣ በፈቃድ አንድ /እግዚአብሔር/ ሲሆኑ በስም፣ በአካል፣ በግብር ሦስት መሆናቸውን ይገልጻል፡፡

ሀ. በስም

የቅድስት ሥላሴ የስም ሦስነትነት አብ፣ ወልድ፣ መንፈስ ቅዱስ ተብለው መጠራታቸው ነው፡፡ አብ በራሱ ስም አብ ይባላል እንጂ ወልድ፣ መንፈስ ቅዱስ አይባልም፡፡ ወልድም ወልድ ይባላል እንጂ አብ ወይንም መንፈስ ቅዱስ አይባልም፡፡ መንፈስ ቅዱስም መንፈስ ቅዱስ ቢባል እንጂ አብ ወይንም ወልድ አይባልም፤ ስማቸው ፈጽሞ የማይፋለስ ነውና፡፡

ከቅዱስ ጴጥሮስ ቀጥሎ በሦስተኛነት በአንጾኪያ ተሹሞ የነበረው ቅዱስ አግናጥዮስ ‹‹አብሂ ውእቱ አብ ወኢኮነ ወልደ ወኢ መንፈሰ ቅዱሰ፣ ወልድሂ ውእቱ ወልድ ወኢኮነ አበ ወኢ መንፈሰ ቅዱሰ፣ ወመንፈስ ቅዱስሂ መንፈስ ቅዱስ ውእቱ ኢኮነ አበ ወኢ ወልደ፣ ኢይፈልስ አብ ለከዊነ ወልድ ወመንፈስ ቅዱስ፣ ወኢ ወልድ ለከዊነ አብ ወወልድ፤ ወኢ መንፈስ ቅዱስ ለከዊነ አብ ወወልድ፤ አብም አብ ነው እንጂ ወልድን መንፈስ ቅዱስን አይደለም፤ ወልድም ወልድ ነው እንጂ አብን መንፈስ ቅዱስንም አይደለም፡፡ መንፈስ ቅዱስም መንፈስ ቅዱስ ነው እንጂ አብን ወልድን አይደለም፤ አብ ወልድን መንፈስ ቅዱስን ወደመሆን አይለወጥም፤ ወልድም አብን መንፈስ ቅዱስን ወደመሆን አይለወጥም፤ መንፈስ ቅዱስም አብን ወልድን ወደመሆን አይለወጥም›› ብሏል፡፡ (ሃይ. አበው ዘቅዱስ አግናጥዮስ ምዕ. ፲፩. ገጽ. ፴፯)

የቅድስት ሥላሴ ስማቸው ከአካላቸው፣ አካላቸው ከስማቸው ሳይቀድም ቅድመ ዓለም የነበረ ስም ነው እንጂ ድኅረ ዘመን የተገኘ አይደለም፡፡ ቅድምናቸው ዘመኑን ቢወስነው እንጂ ዘመኑ ቅድምናቸውን አይወስነውምና፡፡ (መንገደ ሰማይ-በብፁዕ አቡነ መቃርዮስ ገጽ. ፴፪)

ስለዚህም ሊቁ ቅዱስ ጎርጎርዮስ ገባሬ መንክራት ‹‹ወናሁ ንቤ ካዕበ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ወአኮ እሉ አስማት ዘቦኡ ላዕሌሆሙ ድኅረ አላ እሙንቱ እስመ አካላት፡፡ ወብሂለ ሰብእሂ አኮ ውእቱ ስም ዳዕሙ ፍጥረት ውእቱ… ወአካሎሙኒ ለሥሉስ ቅዱስ ወአስማቲሆሙ አልቦ ውስቴቶሙ ዘይዴኀር አላ እሉ እሙንቱ ብሉያነ መዋዕል እምቀዲሙ ዘእንበለ ጥንት ወዘመን፤ አሁን ደግሞ አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ እንላለን ግን አካላት ተቀድመው ተገኝተው እሊህ ስሞች ኋላ የተጠሩባቸው አይደለም፤ ሰው ማለት ኋላ የወጣ ስም አይደለም፡፡ ባሕርዩ ነው እንጂ የሥላሴ አካላቸውም ቀድሞ ስማቸው ከአካላቸው በኋላ የተገኘ አይደለም፡፡ ጥንት ሳይኖራቸው ዘመን ሳይቀድማቸው የነበሩ ናቸው እንጂ›› ብሎ ተናግሯል፡፡ (ሃይ-አበው ዘቅዱስ ጎርጎርዮስ ገባሬ መንክራት ፲፫፥፬-፰ ገጽ ፵)

ለ. በአካል

የቅድስት ሥላሴ የአካል ሦስትነታቸው ደግሞ አብ ፍጹም አካል፣ ፍጹም ገጽ፣ ፍጹም መልክእ አለው፡፡ ወልድም ፍጹም አካል፣ ፍጹም ገጽ፣ ፍጹም መልክእ አለው፡፡ መንፈስ ቅዱስም ፍጹም አካል፣ ፍጹም ገጽ፣ ፍጹም መልክእ አለው፡፡ ሊቁ አቡሊዲስ ስለ ሥላሴ የአካል ሦስትነት ሲገልጽ ‹‹ነአምን በአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ከመ ሠለስቱ ገጻት ፍጹማነ መልክእ ወአካል እሙንቱ እንዘ አሐዱ መለኮቶሙ ዘበአማን፤ ባሕርያቸው በእውነት አንድ ሲሆን በመልክ፣ በአካል ፍጹማን እንደሆኑ ሦስት ገጻት እንደሆኑ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ እናምናለን›› ብሏል፡፡ (ሃይ. አበ. ዘአቡሊዲስ ምዕ. ፴፱፥፫ ገጽ ፻፴፯)

ሐ. በግብር

የቅድስት ሥላሴ የግብር ሦስትነታቸው ሲተረጎም የአብ ግብሩ መውለድ ማሥረፅ ነው፤ ወልድን ወልዷል፣ መንፈስ ቅዱስንም አሥርፇልና፡፡ የወልድ ግብሩ መወለድ ነው፤ ከአብ ተወልዷልና፡፡ የመንፈስ ቅዱስ ግብሩ መሥረፅ ነው፤ ከአብ ሠርፇልና፡፡

አብ ወልድን ቢወልድ፣ መንፈስ ቅዱስንም ቢያሠርፅ እንጂ አይወለድም፣ አይሠርፅም፡፡ ወልድ ቢወለድ እንጂ አይወልድም፤ አይሠርፅም፤ አያሠርፅም፡፡ መንፈስ ቅዱስ ቢሠርፅ እንጂ አይወለድም፤ አያሠርፅም፤ በመሆኑም ቅድስት ሥላሴ በዚህ ግብራቸው አብ ወላዲ፣ ወልድ ተወላዲ፣ መንፈስ ቅዱስ ሠራፂ ተብለው ይጠራሉ፡፡

በእርግጥ ምሥጢረ ሥላሴን በሚገባ መርምሮ መረዳት ለማንም ቢሆን አይቻለውም፡፡ እርሱ ባወቀ ግን ምሥጢረ ሥላሴ በምሥጢረ ጥምቀት ተገልጧል፡፡ እንግዲህ እምነታችንን በቅድስት ሥላሴ ላይ በማድረግ በቀናች ሃይማኖት ልንጸና ይገባል፡

©Mahibere kidusan

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

✞የግብጽን በረሀ✞

የግብጽን በረሀ እንዴት ብለሽ ቻልሽው
አምላክን ታቅፈሽ ስደት የወጣሽው
የሕይወት ውኃ ምንጭ በክንድሽ እያለ
ትሑት ሰውነትሽ በጥም ተቃጠለ


የንጉሡ እናት ሆነሽ እንደ ነዳይ
ውኃ ስትለምኚ ልጅሽ ከሰጠው ላይ
እጅግ ሲበረታ የጌታ ዝምታ
ምን አሰበ ልብሽ ድንግል የዛንለታ

አዝ


ንጉሡን ታቅፈሽ ከሞት ልታመልጪ
በፍርሀት ተውጠሽ ለሽሽት ስትወጪ
ከባሕርይ ዓለማት ዓለም ሲያሰድደው
የወለደ አንጀትሽ ከቶ እንደምን ቻለው


አዝ


የትዕማን ትዕቢት የኮቲባ ቁጣ
የሄሮድስ ክፋት ገዝፎ ልኩን ሲያጣ
በበረሀው ሐሩር ሲያቃጥልሽ ፀሐይ
ማን ውኃ ቀበለሽ ዐይቶ ያንን ስቃይ


አዝ


ከዐይንሽ በፈሰሰው በመረረ እንባ
ድንግል ተማጽነናል ሲዖል እንዳንገባ
በአሳለፍሽው ሐዘን በዐየሽው መከራ
የዐሥራት ሀገርሽን ኢትዮጵያን አደራ


አዝ


@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺
የ፳፻፲፰ ዓ.ም የጥቅምት ፪(የመጀመሪያው ሰንበት) የጽጌ ማኅሌት

የማንኛውም ክብረ በዓልና ወርኀ በዓል ሥርዐተ ማሕሌት መግቢያ

ስምዐኒ እግዚኦ ጸሎትየ፤ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፤
ወይብጻሕ ቅድሜከ ገዐርየ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፤
ወኢትሚጥ ገጸከ እምኔየ በዕለተ ምንዳቤየ አጽምእ ዕዝነከ ኀቤየ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፤
አመ ዕለተ እጼውዐከ ፍጡነ ስምዐኒ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፤
ለዓለም ወለዓለመ ዓለም፤
ሃሌ ሉያ ዘውእቱ ብሂል፤
ንወድሶ ለዘሀሎ እግዚአብሔር ልዑል፤ ስቡሕ ወውዱስ ዘሣረረ ኵሎ ዓለመ፤ በአሐቲ ቃል።

መልክአ ሥላሴ

ሰላም ለኵልያቲክሙ እለ ዕሩያን በአካል፤ ዓለመክሙ ሥላሴ አመ ሐወጸ ለሣህል፤ እምኔክሙ አሐዱ እግዚአብሔር ቃል፤ ተፈጸመ ተስፋ አበው በማርያም ድንግል፤ ወበቀራንዮ ተተክለ መድኃኒት መስቀል።

ዚቅ

ወልድ እኍየ ወረደ ውስተ ገነት፤
ኀበ ቀደሳ ወአክበራ ለሰንበት፤
ወልድ እኍየ ወረደ ውስተ ገነት፤
ኀበ ባረካ ዓመተ ጻድቃን፤
ወልድ እኍየ ወረደ ውስተ ገነት፤
ኀበ ምድረ ርስት ጽዕዱት ወብርህት፤
ወልድ እኍየ ወረደ ውስተ ገነት፤
ምድረ ርስት ምንባር ለጻድቃን ማኅደር።


ዓዲ ዚቅ

ኀበ ጸገየ ወይን ወፈረየ ሮማን፤
ወልድ እኍየ ወረደ ውስተ ገነት፤
ዬዬዬ ወልድ እኁየ ወረደ ውስተ ገነት፤
ውስተ ገነት ብሂል ውስተ ርስቶሙ ለኵሎሙ ሐዋርያት ብሂል።


የማሕሌተ ጽጌ መግቢያ


ኀለፈ ክረምት ቆመ በረከት፤
ተሰርገወት ምድር  

#ዘሕብረት_የሁሉም
በሥነ ጽጌያት፤
ለመርዓዊሃ ትብሎ መርዓት፤
ወልድ እኁየ ወረደ ውስተ ገነት።

፩ኛ. ማሕሌተ ጽጌ

ጽጌ አስተርአየ ሠሪጾ እምዐፅሙ፤
ለዘአምኀኪ ጽጌ ለገብርኤል ምስለ ሰላሙ፤
ወበእንተዝ ማርያም ሶበ ሐወዘኒ ጣዕሙ፤
ለተአምርኪ አሐሊ እሙ፤
ማሕሌተ ጽጌ ዘይሰመይ ስሙ፡፡

ወረብ

መዓዛ ጣዕሙ ለተአምርኪ ሶበ ሶበ ሐወዘኒ/፪/
ወበእንተዝ ማርያም አሐሊ ለተአምርኪ/፪/

ዚቅ

ሃሌ ሉያ ሃሌ ሃሌ ሉያ ናሁ አስተርአየ ጽጌ መርዓቱኒ ትቤ ወልድ እኁየ ይምዕዝ ከርቤ፤ ዕንባቆም ነቢይ ግብረ ምግባሩ ለወልድ አንከርኩ ይቤ፤ ንጉሠ ሰላም ክርስቶስ ዐቢይ ልዕልናከ ወመንክር ስብሐቲከ፤ ለዕረፍት ሰንበተ ሠራዕከ፤

፪ኛ. ማሕሌተ ጽጌ

እንዘ  ተሐቅፊዮ ለሕፃንኪ ጽጌ ጸዓዳ ወቀይሕ፤
አመ ቤተ መቅደስ ቦእኪ በዕለተ ተአምር ወንጽሕ፣
ንዒ  ርግብየ  ትናዝዝኒ  እምላሕ፣
ወንዒ  ሠናይትየ ምስለ ገብርኤል ፍሡሕ፣
ወሚካኤል ከማኪ ርኅሩኅ።

ወረብ

እንዘ ተሐቅፊዮ ለሕፃንኪ ጽጌ ጸዓዳ ወቀይሕ /፪/
አመ  ቤተ  መቅደስ ሠናይትየ ሠናይትየ በዕለተ ተአምር ወንጽሕ/፪/

ዚቅ

ንዒ ርግብየ ወንዒ ሠናይትየ፤
እንተ ሐዋርያት ይሴብሑኪ፤
መላእክት ይትለአኩኪ፣
ፃዒ እምሊባኖስ ሥነ ሕይወት።

፫ኛ. ማሕሌተ ጽጌ

ሰዊተ ሥርናዩ ለታዴዎስ ወለበርተሎሜዎስ ወይኑ፤
እንተ ጸገይኪ አስካለ በዕለተ ተከለኪ እደ የማኑ፤
ማርያም ለጴጥሮስ ጽላሎቱ ወለጳውሎስ ሰበኑ፤
ብኪ መውታን ሕያዋነ ኮኑ፤
ወሐዋርያት መላእክተ በሰማይ ኰነኑ።

ወረብ

ማርያም ለጴጥሮስ ጽላሎቱ ጽላሎቱ ወለጳውሎስ ሰበኑ/፪/
ወሐዋርያት መላእክተ መላእክተ በሰማይ ኰነኑ/፪/

ዚቅ

ኦ መድኃኒት ለነገሥት ማሕበረ ቅዱሳን የዐውዱኪ፤
ነቢያት የአኵቱኪ ወሐዋርያት ይዌድሱኪ፤
እስመ ኪያኪ ኀረየ ለታዕካሁ ከመ ትኩኒዮ ማኅደረ፤
መላእክት ይኬልሉኪ ጻድቃን ይባርኩኪ፤
አበው ይገንዩ ለኪ እስመ ኪያኪ ኀርየ፤
ለታዕካሁ ከመ ትኩኒዮ ማኅደረ።

፬ኛ. ማሕሌተ ጽጌ

ክበበ ጌራ ወርቅ ጽሩይ እምዕንቈ ባሕርይ  ዘየኀቱ፤
ዘተጽሕፈ ብኪ  ትእምርተ ስሙ ወተዝካረ ሞቱ፤
አክሊለ ጽጌ ማርያም  ለጊዮርጊስ ቀጸላ  መንግሥቱ፤
አንቲ  ኵሎ ታሰግዲ ሎቱ፤
ወለኪኒ ይሰግድ ውእቱ፡፡

ወረብ

ክበበ ጌራ ወርቅ ጽሩይ ክበበ ጌራ ወርቅ ጽሩይ እምዕንቈ ባሕርይ/፪/
አክሊለ ጽጌ ማርያም ቀጸላ  መንግሥቱ/፪/

ዚቅ

ውድስት አንቲ በአፈ ነቢያት፤
ወስብሕት በሐዋርያት፤
አክሊለ በረከቱ ለጊዮርጊስ፤
ወትምክሕተ ቤቱ ለ፳ኤል።

፭ኛ. ማሕሌተ ጽጌ

ቅዳሴኪ ማርያም ጸገየ መለኮተ፤
ወፈረየ ብኪ ለቅዱሳን ቅድሳተ፤
ለላዕካኒሁ እምግዘት ከመ የሀቡ ፍትሐተ፤
አርአዮሙ ለመምህራን ዐበይተ ኃይላተ፤
እንዘ ይገብር ተአምረ ወመንክረ በኀበ ተአኵተ፤
ወለማይኒ ረሰዮ ኅብስተ።

ወረብ

አርአዮሙ ለመምህራን ዐበይተ ኃይላተ ዐበይተ ኃይላተ/፪/
እንዘ ይገብር ተአምረ  ወመንክረ በኀበ ተአኵተ/፪/

ዚቅ

ቅድሳት ለቅዱሳን አሐዱ አብ ቅዱስ አሐዱ ወልድ ቅዱስ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ።

ዓዲ ዚቅ

ኦ እግዚኦ በከመ አሜሃ ዘንተ ኅብስተ፤ ባርክ ወፈትት ወሀብ፤
ኦ እግዚኦ በከመ አሜሃ ዘንተ ጽዋዐ እተብ ወቀድስ ወመጡ።

ሰቆቃወ ድንግል

በስመ እግዚአብሔር ሥሉስ ሕጸተ ግጻዌ ዘአልቦ፤
ሰቆቃወ ድንግል እጽሕፍ በቀለመ አንብዕ ወአንጠብጥቦ፤
ወይሌ ወላሕ ለይበል ዘአንበቦ፤
ከማሃ ሐዘን ወተሰዶ ሶበ በኵለሄ ረከቦ፤
ርእዮ ለይብኪ ዐይነ ልብ ዘቦ።

ወረብ

ከማሃ ሐዘን ከማሃ ሐዘን ወተሰዶ ሐዘን/፪/
ርእዮ ለይብኪ ዐይነ ልብ ዘቦ ዐይነ ልብ ዘቦ/፪/

ዚቅ

እወ አማን እምውሉደ ሰብእ አልቦ፤
ምንዳቤ ወግፍዕ ዘከማኪ በውስተ ኵሉ ዘረከቦ።

መዝሙር በ፫


ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፤ ሃሌ ሃሌ ሉያ፤
ትዌድሶ መርዓት፤ እንዘ ትብል ነዓ ወልድ እኍየ፤ ንፃዕ ሐቅለ፤
ትዌድሶ መርዓት፤ ንርዓይ ለእመ ጸገየ ወይን፤ ወለእመ ፈረየ ሮማን፤
ትዌድሶ መርዓት፤ አሰርገወ ሰማየ በከዋክብት፤ ወምድረኒ በሥነ ጽጌያት፤
ትዌድሶ መርዓት፤ እስመ ውእቱ ወልድ ዋሕድ፤ እግዚአ ለሰንበት፤
ማ፦ ትዌድሶ መርዓት ወትብሎ
ወልድ እኍየ ቃልከ አዳም።

©ማሕሌተ ያሬድ
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

5. የባልና ሚስት የኑዛዜ አፈጻጸም ምን ዓይነት መልክ አለው አንዱ ተለይቶ ሊናዘዝ አይችልምን?
✞ የባለትዳሮች የኑዛዜ አፈጻጸም ላይ የካህኑ የአገልግሎት ሂደት ይወስነዋል የግድ በአንድነት ካልሆነ ብሎ የሚያስገድድ ስርዓት ባይኖርም ሁለቱም ቤተሰባቸውን ጨምሮ ለንስሐ አባታቸው ይናዘዛሉ ካህኑም እንደ ሁኔታው ባልና ሚስቱ በጋራ የሰሩትን በጋራ እንዲናዘዙ ያደርጋቸዋል በተናጥል የፈጸሙት ካለ በተናጥል ያናዝዛቸዋል የቤተሰቡን አባላት የየአንዳንዱን ኑዛዜ ካህኑ በምስጢር ይይዛል፡፡
6. ለንስሐ አባቴ እየመላለሱ መናዘዝ ቢያስፈራኝስ ምርጫዬ ምንድነው?
✞ ምንም ምርጫ የሎትም ኃጢአታችንን እንዳንናዘዝ ሰይጣን ከሚጠቀምባቸው መሳሪያዎች አንዱ መናዘዝን ማስፈራራት ነው ይህ ደግሞ እርሱ እንቅልፍ አጥቶ የገነባውን የኃጢአት ህንፃ እንዳልነበር ስለሚያደርግበት እና በኃጢአት የቆሸሸ ሕይወት ወዳጁ እንደሆነ በመናዘዝ ንስሐ የገባ ሕይወት ደግሞ ጠላቱ ስለሚሆነው አጥብቆ መናዘዝን ያስፈራራዎታልና ይጠንቀቁ / ሲራ 5፥5/
7. ምቹ ጊዜ እስከማገኝ ያለ ንስሐ አባት ብኖርስ ምን ጉዳት ይኖረዋል?
✞ ራስዎን ያለ እረኛ እንዳስቀመጡ ያስቡ የመንፈሳዊ ሕይወት ዕድገትም የተገታ ወይም ባለበት የሚቆጭ ይሆናል ጠቢቡ ሰሎሞን “አንድ ከመሆን ሁለት መሆን ይሻላል አንዱም ቢወድቅ ሁለተኛው ያነሣዋልና አንዱ ብቻውን ሆኖ በወደቀ ጊዜ ግን የሚያነሣው ሁለተኛ የለውምና ወዮለት” ብሏል /መከ 4፥10/
8. የንስሐ አባቴ ሊጐበኙን እስኪመጡ መጠበቅ ይኖርብኛል? ብዙ ጊዜ አይመጡም፡፡
✞ የግድ የንስሐ አባትዎን የጐበኝት ጊዜ መጠበቅ አይኖርብዎትም ወይም እርሳቸው ወደኔ መቼ ይመጡና ማለት አይኖርብዎትም ባስፈለገዎ ጊዜ ሁሉ ተነስተው የንስሐ አባትዎ ወደሚገኙበት ቤተክርስቲያን /ገዳም/ መሄድ ይኖርብዎታል፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አስሩን ለምፃሞች ካነፃ በኋላ “ሂዱና ራሳችሁን ለካህን አሳዩ" ብሎ አዟቸዋል፡፡ /ሉቃ 17፥11-14/
9. ኑዛዜ ለገባሁበት ችግር መፍትሔ ይሆናል?
✞ የንስሐ መሰረታዊ ጥቅሙ ሥርየተ ኃጢአት ነው ይህ ደግሞ ከዘላለም ሞት መዳን ነው፡፡ ያጡትን እግዚአብሔር መልሶ ማግኘት ነው ይሁን እንጂ የንስሐ ጸጋ ብዙ ስለሆነ ከውስብስብ ችግሮች ነፃ ያወጣናል ባጠቃላይ ንስሐ ማህበራዊ ጠቀሜታ ጭምር እናገኝበታለን፡፡
10.ኃጢአቴን ለእርሱ ከተናዘዝኩ ጸጋው አይበቃኝም? የግድ መናዘዝ መቀጣት ያስፈልገኛል?
✞ እንድናዘዝ የእግዚአብሔር ትዕዛዝና ጥሪ ነው ሐዋርያትን ኃጢአቱን የያዛችሁበት እኔ እይዝበታለሁ የተዋችሁለትንም እተውለታለሁ ብሏቸዋል መቀጣታችንም ቅዱስ ጴጥሮስ “ጻድቅ በጭንቅ የሚድን ከሆነ ኃጢአተኛው ወዴት ይታይ ዘንድ አለው” /1ጴጥ 4፥18/ በማለት ያስረዳል ስለዚህ ኑዛዜዎም ሆነ ከካህኑ የሚቀበሉት ቀኖና የጸጋው ትርፍ መሆኑን ልብ ይበሉ፡፡
11. ፍጹም የረሳሁት ኃጢአት ቢኖርስ?
✞ እስቀድሞ ይህ ለምን እንደሆነ ራሰዎን ይመርምሩ ከዛም መመለስን የሚወድ እግዚአብሔር እንዲረዳዎ ይጸልዩ ለኑዛዜ የሚረዱ መሰል መጽሐፍቶችን ማንበብ ልምድዎ ያድርጉ ለራስም የአርምሞ ጊዜ ይውሰዱ ፀጥ ባለ ቦታ ሆነው ራስዎን የሚያዳምጡበት ጊዜ ይኑርዎ በተረፈ በተናዘዙትና ካህኑ በሰጥዎት ቀኖና ከልብ እየፀለዩ እግዚአብሔርን ምሕረት ይማፀኑ እርስዎ እንጂ እርሱ ስላልረሳው ይቅር ይልዎታል ሳይጠራጠሩ ይለምኑ፡፡
12. ኑዛዜዬን ባርዕስት ባደርገውስ? ለምሳሌ ትዕዛዛትን ሁሉ አልጠበቅኩም ብዬ?
✞ ኑዛዜ በጥልቀት በዝርዝርና በጸጸት ሊፈጸም ይገባዋል፡፡ የዚህም መጽሐፍ ዝግጅት ዓላማ ለዚህ ነው በጥያቄዎ መልክ ባርዕስትና በጥቅል መናገሩ ለመሸሽ አልያም ለመደበቅ የሚደረግና ከልባዊ ጸጸትም ጋር ያልተገናኘና የኑዛዜን ትርጉም የለቀቀ ነው ለዚህ ነው “በጌታ ፊት ልብሽን እንደ ውኃ አፍስሺ” የተባለው /ሰቆ ኤር 2፥19/

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺
የ፳፻፲፰ ዓ.ም የጥቅምት ፳፫(የዐራተኛው ሰንበት) የጽጌ ማኅሌት

ዘራብዓይ ሳምንት

🌴🌴🌴🌴🌴🌴🌴🌴🌴🌴🌴

የማንኛውም ወርኀ በዓልና ክብረ በዓል ሥርዐተ ማሕሌት መጀመሪያ

  ስምዓኒ እግዚኦ ጸሎትየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡
ወይብጻሕ ቅድሜከ ገዓርየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ወኢትሚጥ ገጸከ እምኔየ፡ በዕለተ ምንዳቤየ አጽምእ እዝነከ ኀቤየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡
አመ ዕለተ እጼውአከ ፍጡነ ስምዐኒ፡ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ለዓለም ወለዓለመ ዓለም፡
ሃሌ ሉያ ዘውእቱ ብሂል፡
ንወድሶ ለዘሀሎ እግዚአብሔር ልዑል፡
ስቡሕ ወውዱስ ዘሣረረ ኵሎ ዓለመ፡
በአሐቲ ቃል።

ለገባሬ ኵሉ

ሰላም ለአብ ገባሬ ኵሉ ዓለም
ለወልድ ሰላም ወለመንፈስ ቅዱስ ሰላም ለማርያም ሰላም ወለመላእክት ሰላም
ሰላም ለነቢያት ወለሐዋርያት ሰላም
ለሰማዕታት ሰላም ወለጻድቃን ሰላም።

ዚቅ

ዛቲ ይእቲ እኅተ ትጉሃን መላእክት
ወለተ ኄራን ነቢያት
እሞሙ ለሐዋርያት
ሞገሶሙ ለጻድቃን ወሰማዕት።

፩ኛ. ማሕሌተ ጽጌ

ትመስል እምኪ ማርያም ዕለተ ሣልስተ ወራብዕተ
ዘወለደት ጽጌ ወፀሐየ ዓለም ብርህተ
ወካዕበ ትመስል ሳብዕተ ዕለተ
እስመ ፈረየት ኪያኪ ተአምረ ግዕዛን ሰንበተ
ለእለ በሰማይ ወምድር ዘኮንኪ ዕረፍተ።

ወረብ

ትመስል እምኪ ማርያም ዕለተ ሣልስተ ወራብዕተ ትመስል እም/፪/
ዘወለደት ጽጌ ጽጌ ጽጌ ወፀሐየ ዓለም/፪/
 
ዚቅ

እምኵሉ ዕለት ሰንበተ አክበረ ወእምኵሎን አንስት ማርያምሃ አፍቀረ ከመ ትኩኖ ማኅደረ ለመንፈስ ቅዱስ ወምስጋድ ለኵሉ ዓለም።

፪ኛ. ማሕሌተ ጽጌ

እንዘ  ተሐቅፊዮ ለሕፃንኪ ጽጌ ጸዓዳ ወቀይሕ
አመ ቤተ መቅደስ ቦእኪ በዕለተ ተአምር ወንጽሕ
ንዒ  ርግብየ  ትናዝዝኒ  እምላሕ
ወንዒ  ሠናይትየ ምስለ ገብርኤል ፍሡሕ
ወሚካኤል ከማኪ ርኅሩኅ ።

ወረብ

እንዘ ተሐቅፊዮ ለሕፃንኪ እንዘ ተሐቅፊዮ አመ ቤተ መቅደስ ቦእኪ/፪/
ንዒ ርግብየ  ምስለ ገብርኤል ፍሡሕ ወሚካኤል ከማኪ ርኅሩኅ/፪/

ዚቅ

ንዒ ርግብየ ወንዒ ሠናይትየ ቃልኪ አዳም ይጥዕመኒ እምአስካለ ወይን አርአዮ ለሙሴ ግብራ ለደብተራ ወተናግሮ በዐምደ ደመና እሞሙ ይእቲ ለሰማዕት ወእኅቶሙ ለመላእክት አርአዮ ለሙሴ ግብራ ለደብተራ ወተናገሮ በዐምደ ደመና።

፫ኛ. ማሕሌተ ጽጌ

ክበበ ጌራ ወርቅ ጽሩይ እምዕንቈ ባሕርይ  ዘየኀቱ
ዘተጽሕፈ ብኪ  ትእምርተ ስሙ ወተዝካረ ሞቱ
አክሊለ ጽጌ ማርያም  ለጊዮርጊስ ቀጸላ  መንግሥቱ
አንቲ  ኵሎ ታሰግዲ ሎቱ
ወለኪኒ ይሰግድ ውእቱ፡፡

ወረብ

ክበበ ጌራ ወርቅ ጽሩይ ክበበ ጌራ ወርቅ ጽሩይ ዘየኀቱ እምዕንቈ ባሕርይ/፪/
አክሊለ ጽጌ ማርያም ቀጸላ መንግሥቱ ለጊዮርጊስ/፪/

ዚቅ

ሰአሊ ለነ ማርያም አክሊለ ንጹሐን ብርሃን  ቅዱሳን።

ዓዲ ዚቅ

መሰንቆሁ ለዳዊት ወአክሊሉ ለሰሎሞን ገነት ዕፁት አዘቅተ ኅትምት መሶበ ጽንስ ምስለ ድንግልና ዘኢሳይያስደ


፬ኛ. ማሕሌተ ጽጌ

ዘንተ ስብሐተ ወዘንተ ማሕሌተ
ተአምርኪ ጸገየ ወፈረየ ሊተ
ከመ እሰብሕ ዳግመ እንዘ እጸውር ጸበርተ
ምስለ እለ ኀፀቡ አልባሲሆሙ በደመ በግዑ ድርገተ
ውስተ ባሕረ ማኅው ድንግል ክፍልኒ ቁመተ።

ወረብ

ምስለ እለ ኀፀቡ አልባሲሆሙ አልባሲሆሙ በደመ በግዑ/፪/
ክፍልኒ ቁመተ ድንግል ድንግል ውስተ ባሕረ ማኅው/፪/

ዚቅ

ገጹ ብሩህ ከመ ፀሐይ ወእምኵሉ ሥነ ሠርጐ ሰማይ ለጊዮርጊስ ኅሩይ ዘተወልደ እመንፈስ ቅዱስ ወማይ አልባሲሁ በደመ በግዕ ዘሐፀበ ወእምሠረቅት መርዔቶ ዐቀበ ።

ሰቆቃወ ድንግል

እስከ ማእዜኑ እግዝእትየ ማርያም ውስተ ምድረ ነኪር ትሄልዊ
ሀገረኪ ናሁ ገሊላ እትዊ
ለወልድኪ ሕፃን ዘስሙ ናዝራዊ
ለክብረ ቅዱሳን በከመ ይቤ ዖዝያን ዜናዊ
እምግብጽ ይጼውዖ አቡሁ ራማዊ።

ወረብ

በከመ ይቤ ዖዝያን ዖዝያን ለክብረ ቅዱሳን/፪/
እምግብፅ ይጼውዖ ለወልድኪ አቡሁ ራማዊ አቡ/፪/

ዚቅ

ትንቢተ ኢሳይያስ ዘተብህለ እምግብፅ ጸዋዕክዎ ለወልድየ ለክብረ ቅዱሳን ጸዋዕክዎ።

መዝሙር በ፭


ጸገየ ወይን ወፈርየ ሮማን፤
ወፈርዩ ኵሉ ዕፀወ ገዳም ቀንሞስ ዕቍረ ማየ ልብን፤
ሠርዐ ለነ ሰንበተ ለዕረፍተ ዚኣነ፤
ጸገዩ ጽጌያት ጸገዩ ደንጐላት፤
ሠርዐ ለነ ሰንበተ ለዕረፍተ ዚኣነ፤
ኀለፈ ክረምት ቆመ በረከት ተሰርገወት ምድር በሥነ ጽጌያት፤
ሠርዐ ለነ ሰንበተ ለዕረፍተ ዚኣነ፤
እግዚኣ ለሰንበት ወአቡሃ ለምሕረት፤
ማ፦ ሠርዐ ለነ ሰንበተ ለዕረፍተ ዚኣነ፤
ሠርዐ ለነ ሰንበተ ለዕረፍተ ዚኣነ፤
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿

©ማሕሌተ ያሬድ
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

«ድንግል ሆይ አንቺን ያሳደደሽ ሄሮድስ እኔን የማያሳድደኝ ጌታ በእቅፌ ስለሌለ ነው። እኔ በልቤ ያነገሥሁት 'የተወለደውን የአይሁድ ንጉሥ' ስላልሆነ ሄሮድስ ከእኔ ጋር ጠብ የለውም ። የሄሮድስን ስልጣን አደጋ ላይ የሚጥል ንጉሠ ሰላም በእኔ እቅፍ የለም። አሁን ግን ፍቀጂልኝና ሄሮድስን ማስደሰት ትቼ  ልጅሽን በልቤ ልቀበለው ።የልቤን ክርስቶስ ሄሮድስ እንዳይገድልብኝ እኔም እንዳንቺ ልሰደድ።እርሱን አቅፌ መከራን ቢደርስብኝ እንኳን ጽናት እንደማገኝ በአንቺ አይቻለሁ እና የልጅሽን ፍቅር  በልቤ አኑሪልኝ። ለሦስት ቀናት ከፊትሽ ዘወር ቢል ፍለጋ የወጣሽዋ ድንግል ሆይ ከእኔ ሕይወት ልጅሽ ከተሠወረ ቆይቶአልና ያለ እርሱ መሰንበት የማልችል የፍቅሩ ምርኮኛ አድርጊኝ ።»

[የብርሃን እናት-በዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ]


@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

"አቡነ አረጋዊ"
ጽድቅህ ጠርቶናል አባትነትህ
በቅድስና ያማረ ሕይወትህ
ጌጥ ውበታችን አባ አረጋዊ
መናኝ መነኩሴ መልአክ ምድራዊ (፪)

ተቃኝተህ ስላደግክ በመንፈስ ቅዱስ
ወደ ፅርዕ ተጓዝክ ወደ አባ ጳኩሚስ
ተዘጋጅተህ ነበር ለችግር ፈተና
ዘሚካኤል አለህ ሰጥቶህ ምንኩስና (፪)
     አዝ---
ለኢትዮጵያ ምእመናን አባት ተብለሃል
ወንጌል በማስተማር ብዙ አትርፈሃል
መጻሕፍት ተርጉመህ ያበረከትክ ለአበው
የአንተስ ትሩፋት እፁብ ነው ድንቅ ነው (፪)
    አዝ---
የዓለም ጨው ሆነህ አጣፈጥካት ምድርን
በልባችን ሳልካት ቤተ ክርስቲያንን
ደብረ ሀሌ ሉያ ደብረ ዳሞ ቅድስት
የፈውስ ቦታ ናት መካነ ትኅርምት (፪)
   አዝ---
ልክ እንደ አባቶችህ አስተዋይ ስለሆንክ
ገና ወጣት ሳለህ አረጋዊ ተባልክ
የሥጋን ሞት ሳታይ ተሰውረህ ከምድር
ብሔረ ሕያዋን ተቀላቀልክ በክብር (፪)
  አዝ---

በቦሌ ደብረ ገነት ቅ/ጊዮርጊስ እና ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍሬ ሃይማኖት ሰ/ት/ቤት መዘምራን

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

ጥቅምት ፲፬
ጻድቁ አቡነ አረጋዊ


‹‹ወበዛቲ ዕለት ኮነ ተዝካሩ ለዐብይ ወክቡር አቡነ አረጋዊ ዘይሰመይ ዘሚካኤል››
‹‹በዚህች ቀን የታላቁ እና የከበረ አባታችን አቡነ አረጋዊ ዘሚካኤል የሚባለው መታሰቢያ ነው››


አባታችን ‹‹አቡነ አረጋዊ›› በሀገራችን ስም አጠራራቸው ከከበሩ አባቶች አንዱ ጻድቅ ናቸው፡፡ ጻድቁ የተወለዱት በ5ተኛው መቶ ክፍለ ዘመን አጋማሽ አከባቢ ሲሆን ወላጆቻቸው አባታቸው ንጉሥ ይስሐቅ እናታቸው ደግሞ ቅድስት እድና ይባላሉ፡፡ የተወለዱት ደግሞ በታላቋ ሮም ነው፡፡ ስማቸው ብዙ አይነት ነው ወላጆቻቸው ‹‹ ዘሚካኤል›› ሲሏቸው፣ በበረሀ ‹‹ገብረ አምላክ ››ተብለዋል፡፡
በኢትዮጵያ ደግሞ ‹‹አረጋዊ›› ይባላሉ፡፡ አቡነ አረጋዊ ምንም የንጉሥ ልጅ ቢሆኑም በልጅነታቸው መጽሐፍ ተምረዋልና ጠፍተው ገዳም ገቡ፡፡ በዚያም በገዳሙ ዳውንስ (ግብፅ) የታላቁ ቅዱስ "ጳኩሚስ" ደቀ መዛሙርት ሆነው ከነአባ ቴዎድሮስ ጋር ሥርዓተ መነኮሳትን ተምረዋል፡፡ ከመነኮሱ ከዓመት በኋላ ወደ ሀገራቸው ሮም ተመልስው በማስተማር ሰባት ያህል የቤተ መንግሥት ስዎች ወደ ምናኔ ማርከዋል ፡፡
451 ዓ.ም በተካሄደው የኬልቄዶን ጉባዔ ላይ የሁለት ባሕርይ ትምህርት አንቀበልም በማለታቸው በቤዛንታይን ነገሥታት ስቃይ እና መከራ ፀናባቸው :: በዚህ ጊዜ ኢትዮጵያ ከሁለት ባሕርይ ትምህርት የፀዳች እና ታላቅ አምልኮተ እግዚአብሔር እንደሚፈፀምበት ስለ አወቁ ከሌሎች ስምንት ቅዱሳን ጋር በሁለተኛው የኢትዮጲያ ጳጳስ በአባ ሚናስ ጊዜ በንጉሥ አልዓሜዳ ዘመነ መንግሥት በ5ተኛው መቶ ክ/ዘመን ማብቂያ 480/81 ዓ.ም ወደ ሀገራችን ገቡ፡፡ ከአባታችን ከአቡነ አረጋዊ ጋር የነበሩት ስምንቱ ቅዱሳን ከሮም ፤ከቤዛንታይን ፤ ታናሿ እስያ፤ሶሪያ ግዛትና አካባቢዎች የመጡ ናቸው፡፡ ስማቸውም አባ ገሪማ (አባ ይስሐቅ) ፣ አባ ጰንጠሌዎን፣ አባ አሌፍ፣ አባ ጉባ ፣አባ ሊቃኖስ ፣ አባ ይምዓታ ፣አባ ጽሕማ፣አባ አፍጼ ናቸው :: ስለ ተሰዓቱ ቅዱሳን ወደ ኢትዮጵያ የገቡበት መንገድ ሁለት ዓይነት ምንጮች ይገኛሉ፡፡ የመጀመሪያው አምደ ሃይማኖት ኢትዮጲያዊው ቄርሎስ የሚባለው ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ቅዱሳኑ ወደ ኢትዮጲያ ሲመጡ ነገሥታት እና መኳንንትን አስከትለው መጽሐፍትን ይዘው ስለነበር የመጡት ሀገር ለመውረር መስሏቸው ኢትዮጲያውያን ደንግጠው ነበር ፡፡ ነገር ግን በእጃቸው የተለያየ ተአምራትን ማየት ስለቻሉ ለመንፈሳዊ ተልዕኮ መምጣታቸውን ተረዱ ከተአምራቱ መካከል በዕራፈ የእሳት ፍም የቋጠሩ፣ ጠዋት ዘርተው ለሠርክ ቅዳሴ ማድረሳቸው (አቡነ ገሪማ)፣ በወንፊት ውሃ ተሸክመው መሄዳቸው፣ አሥሩ የእጅ እና የእግር ጣቶቻቸው እንደ ፀሐይ ያበሩ መሆናቸውን አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ጠቅሰዋል ሁለተኛው ምንጭ አባታችን አቡነ አረጋዊ መጀመሪያ ብቻቸውን መጥተው የኢትዮጲያውያንን ደግነት እና ታማኝነት ስለተረዱ ተመልሰው ሄደው ለ8ቱ ቅዱሳን በመግለፅ ይዟቸው መጥተዋል የሚሉ ምንጮች ናቸው ::
አባታችን አቡነ አረጋዊ ሲመጡ እናታቸው ቅድስት እድና እና ደቀ መዝሙራቸው አባ ማትያስ አብረው ነበሩ :: ንጉሡም ተቀብለው በቤተ ቀጢን ( አክሱም) አሳረፏቸው በዚያ ተቀምጠው መጽሐፍትን እየተረጎሙ ወንጌልን እየሰበኩ ቆይተዋል፡፡ አባታችን ለብዙ ጊዜ በዓት ፍለጋ ደክመዋል በመጨረሻም ደብረዳሞ ማርካቸዋለች ፡፡ፃድቁ አባታችን እያስተማሩ ደብረዳሞ ሲደርሱ ወደሰማይ ቀጥ ያለች ተራራ ሰው በምንም መንገድ ሊደርስበት ወይም ሊወጣበት የማይቻለውን ቦታ እሳቸው ተመኙ፡፡ ‹‹ አሁን ይህንን ተራራ በምን ልወጣ እችላለሁ›› እያሉ ሲያወጡ ሲያወርዱ በንግግር ሐሰት የሌለበት አምላካችን በነብዩ ዳዊት ላይ አድሮ እንደተናገረ ( መዝ 90 (91) ÷11-16) የታዘዘ ዘንዶ መጥቶ ስድስት ክንድ በሚያህል ጅራቱ ጠምጥሞ ቅዱስ ሚካኤል ሠይፈ እሳት ይዞ እየጠበቃቸው ከተራራው አናት አድርሷቸዋል ፡፡ ወዲያው “ሀሌ ሉያ ለአብ ሀሌ ሉያ ለወልድ ሀሌ ሉያ ለመንፈስ ቅዱስ" ብለው አመስግነዋል። ቦታውም <<ደብረ ሀሌ ሉያ>> ተብሏል ፡፡ በዚህችም እለት ግማሽ ህብስት በልተው ጠገቡ፡፡ ከዚህ በኋላ ግን ምድራዊ ህብስትን አልበሉም፡፡ በሰንበተ ክርስቲያን ከቅዳሴ በኋላ ህብስተ ሰማይ እያመጡላቸው ይመገቡ ነበር ፡፡
ፃድቁ አባታችን የምንኩስና ኑሮ ሥነ ሥርዓት በማስተማራቸውና በማስፋፋታቸው <<አቡሆሙ ለመነኮሳት ዘኢትዮጵያ፤ የኢትዮጵያ መነኮሳት አባት>> ይባላሉ። ግዕዝን በመማር መጽሐፍ ወደ ግዕዝ ቋንቋ ተርጉመዋል። ከአፄ ገ/መስቀል እና ከቅዱስ ያሬድ ጋርም ወዳጆች ነበሩ፡፡ በደብረዳሞ ተራራ ግርጌ የኪዳነ ምህረት ቤተክርስቲያን ለሴቶች ገዳም አድርገው ሰጥተዋል። ቀዳሚ መነኩሴም የሆኑት እናታቸው ቅድስት እድና ናቸው፡፡ በመጨረሻም ከጌታችን ከመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስማቸውን ለሚጠራ መታሰቢያቸውን ለሚያደርግ ቃልኪዳን ተቀበሉ፡፡ በመምህራቸው አባ ጳኩሚስ እንደተማሩት ለልጆቻቸው መነኮሳት ሥርዓተ ማኅበርን ሰሩላቸው፤ ከዚያ በኋላ በእግዚአብሔር ቸርነት እንደሄኖክ እንደ ኤልያስ ከሞት ገፅ ጥቅምት 14 ቀን በደብረ ዳሞ ተሰወሩ።

ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በፃድቁ ጸሎት ይማረን፤ በረከታቸው ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

ይሄን ሁሉ ምሥጢር መነጽር ሆና ያሳየችን ድንግል ማርያም በገሊላ አውራጃ በምትገኝ የዮሴፍ ደሳሳ ጐጆ ውስጥ ሆና እናታቸውን ያጡ የዮሴፍን ልጆች ጨምራ እናት ሆነቻቸው፡፡ እናት አጥቶ በሞት መዳፍ ውስጥ ለወደቀው ዓለም እናት እስክትሆን እናትነቷን በቤተ ዮሴፍ ጀመረች፡፡ ብዙ ጊዜ ሕጻኑ ልጇ ከሚያደርጋቸው ልዩ ልዩ ተአምራቶች የተነሣ የአካባቢው ሰዎች ስለ ልጇ ይከሷት እና ይወቅሷት ነበር፡፡
እርሱ በመስኮት ዘልቆ ወደ ቤት በሚገባው የፀሐይ ጨረር ላይ ሲራመድ ሕጻናቱ ሲመለከቱ እንደ እርሱ እናደርጋለን እያሉ ከመስኮት እየወደቁ አንዳንዶቹ ሲሞቱ ከሞት የተረፉት ደግሞ ተሰበሩ፤ ሌላ ጊዜ ደግሞ ጭቃውን አድቦልቡሎ ሕይወትን የሚያድል እስትንፋሱን ሲለግሳቸው በረው በረው ሲሄዱ ሕጻናቱ ተመልክተው በእስትፋሳቸው ሕይወትን እንፈጥራለን ብለው እፍ ሲሉ ዋሉ፤ ሲመሽ ጉሮሮአቸው አበጠ፣ ልባቸው ወለቀ፡፡
ይህንን የተመለከቱ የገሊላ መንደር ነዋሪዎች በእመቤታችን ላይ በጠላትነት ተነሡባት ልጅሽ ልጆቻችንን ገሏል አሏት፤ ሁሉን ቻይ ልጇ የሞቱትን አሥነስቶ በውኑ የገደልኳችሁ እኔ ነኝን? ብሎ በሕዝቡ መካከል ሙታን ምስክርነትን እንዲሰጡ እስካደረገበት ጊዜ ድረስ የአባቶቻችን ከሳሽ እርሱ ክሱን አላቆመም ነበር፡፡
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሲያድግ እንደ ሁሉም ምድራውያን ሕጻናት ነውና ለእናቱ በነገር ሁሉ ይታዘዝ ነበር፤ ውኃ እንዲቀዳ ስታዘው ውኃውን በወንፊት ቀድቶ ያመጣላት ነበር፤ ውኃውን ቋጥሮ በነፋስ ምስሶ ላይ ሰቅሎ፣ ስሙን ሰማይ ብሎ ለሚጠራው ለእርሱ በወንፊት ውኃን መቅዳቱ ምን ይገርማል፡፡
እንጨትም ልቀም ከተባለ ለቅሞ በነፋስ ትክሻ ላይ ጭኖ እያመጣላት ለእናቱ እና ለዘመዶቹ ሁሉ ያገለግል ነበር ሉቃ2÷51፡፡ በዚህ ሁሉ ነገር መላእክት እና ሊቃነ መላእክት ይገረማሉ፤ አጋንንት ይደነግጣሉ ባለመታዘዝ የተጀመረውን ኃጢአት በመታዘዝ ሊሽር መጥቷልና፤
ይህን አገልግሎቱን ሲያዩ መላእክት በመገረም ዝም ይላሉ ሊያገለግሉት እንጅ ሊያገለግል የማይገባው ሆኖ ሳለ በፈቃዱ ይህን አድርጓልና፡፡ በነገር ሁሉ እንደ ሕጻናት ሆነ እንጂ ከሕጻናት የተለየበት ምንም መንገድ አልነበረም፡፡ ሁለት የሰው ልጅ ሊያልፍባቸው የሚችሉ ሕግጋትን ፈጸመ47::
❖ ሕግ ጠባይዓዊ - በተፈጥሮ የተሰጠ የፍጥረት ሕግ ሲሆን በቀዳማዊው ልደቱ ይህ አልነበረበትም፤ በደኃራዊ ልደት ከድንግል ሲወለድ ግን ይህን የተፈጥሮ ሕግ ሳያዛባ ከማሕጸን ጀምሮ በየጥቂቱ አሳደገችው እንጂ አምላክ ነኝና ዕለቱን ተወልጄ ዕለቱን ልደግ አላለም፡፡
❖ ሕግ መጽሐፋዊ፡- ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህ ሕግ ሥር እንዲያልፍ እድሜው ለትምህርት ሲደርስ እመቤታችን ወስዳ ለገማልያል አስተምርልኝ ብላ ሰጠችው፡፡ ሰው የሚሆነውን ለመሆን ይህን አደረገው እንጂ የመምህራን መሪያቸው፣ የአዋቂዎች እውቀታቸው እርሱ እኮ ነው፡፡
እናቱ ድንግል ማርያም ግን ነገሮችን ሁሉ በልብዋ እየጠበቀች ታስቀምጥ ነበር ለበዓል በኦሪታውያን ልማድ ወደ ቤተ መቅደስ የወጣችም እንደሆነ አስከትላው ትሄድ ነበር፤ ወደ ቤተ መቅደስ መሄድን የጀመረው ልክ አስራ ሁለት ዓመት ሲሞላው እንደነበር መጽሐፍ ይመሰክራል፡፡
በሌሎች ሌዋውያን ከሃያ ዓመት በታች እንዳይወጡ ሥርዓት ተሠርቶባቸዋል እርሱ ግን የሚወጣው በሊቃውንቱ መካከል ተገልጦ ለማስተማር ነውና በዚህ ታናሽ እድሜ ወጥቷል፡፡

(ሕይወተ ማርያም - በሊቀ ሊቃውንት ስምዐኮነ መልአክ)

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

"አዝላው ወረደች"
አዝላው ወረደች ወደ ግብፅ /2/
ስደተኛዋ የአምላክ እናት
ይህ ዓለም ለእርሷ መች ተገባት

አዝ

ዓለም በምኗ ታስተናግዳት
የፍቅር ምንጯ ተሟጦባት
እነ ኮቲባን እየላከች
የአምላክን እናት ተሳደበች
እነ ሄሮድስን እየላከች
ህፃኑን ልትገድል አሳደደች
አዝ

የክብርን ጌታ ተሸክማ
ውርደት ለበሰች እንደ ሸማ
የሀብቱን ጌታ በጀርባ አዝላ
ሰው ተዘከራት ተቸግራ
አዝ

በቃሉ ትዕዛዝ ምድርን ሠርቶ
ተንከራተተ ማደሪያ አጥቶ
ጌታ ሲወለድ የምሥራች
በረት ሰጠችው ዓለም ታካች
አዝ

ግና መላእክት በሰማያት
ሃሌ ሉያ አሉ በፍርሃት
ወልድን በአብ ቀኝ ከላይ አይተው
ደግሞም በምድር ከድንግል ክንድ
ከላይም ሳይጎድል ተመልክተው /2/
አዝ

ዓለም በምኗ ታስተናግዳት
የፍቅር ምንጯ ተሟጦባት
እነ ኮቲባን እየላከች
የአምላክን እናት ተሳደበች
እነ ሄሮድስን እየላከች
ህፃኑን ልትገድል አሳደደች
አዝ

የክብርን ጌታ ተሸክማ
ውርደት ለበሰች እንደ ሸማ
የሀብቱን ጌታ በጀርባ አዝላ
ሰው ተዘከራት ተቸግራ
አዝ

በቃሉ ትዕዛዝ ምድርን ሠርቶ
ተንከራተተ ማደሪያ እጥቶ
ጌታ ሲወለድ የምሥራች
በረት ሰጠችው ዓለም ታካች
ሊቀ መዘምራን ይልማ ኃይሉ

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

ተመለሺ ሱላማጢስ

ተመለሺ ሱላማጢስ ተመለሺ
እናይሽ ዘንድ ተመለሺ (እመቤቴ)
የአባትሽን ቤት አትርሺ


ኢሳይያስ ተንብዮልሽ
ፈጣን ደመና ያለሽ
ጌታን በጀርባሽ አዝለሽ
በግብጽ በረሃ የዞርሽ
የበረሃው ሙቀት ንዳድ
የሌሊቱ ግርማ ከባድ
በአራዊቱ ድምጽ ሁካታ
ልብሽ በጭንቅ ሲንገላታ።
      

አዝ..............


ስለ ልጅሽ ተርበሻል
ጥማትንም ተጠምተሻል
ድካም መንገድ እንግልቱ
እንዴት ቻልሽው አዛኝቱ
የልጅሽን ነፍስ የሻቱ
ጠላቶቹ ስለሞቱ
መሰደዱ ይበቃሻል
ቅድስት አገር ይሻልሻል
      
አዝ..............


በኢትዮጲያም እለፊ
ደብረ ቁስቋም ላይም እረፊ
ለዘላለም ከብረሽ
በአርያም ንገሽ
     
አዝ..............


የበደሌ ሸክም በዝቶ
ብሰደድም ጽድቄ ጠፍቶ
በይ መልሺኝ ከደጃፍሽ
በክንዶችሽ እቅፍ አርገሽ
በዓለም ስጓዝ አንቺን ትቼሽ
ከእኔ እርቆ ፍቅር ጣዕምሽ

በበደሌ በኃጢአቴ ዛሬ እንኳን ብሸሽ
ተመለስ በይኝ እመቤቴ በእናትነትሽ
      
ተመለሺ እመቤቴ ተመለሺ}
ከልቤ ኑሪ ተመለሺ  }
ስለ ኃጢአቴ አትሽሺ   }፪


ለአዳም ተስፋው መድኃኒቱ
ድንግል ማርያም አዛኝቱ
በኃዘንሽ በስደትሽ
ታጥቦ ይጥራ እድፌ በእንባሽ
በቃኝ ዛሬስ ተሸነፍኩኝ
እናቴ ሆይ በይ መልሺኝ
ፍቅር ጣዕምሽ ታትሞብኝ
ዛሬ ድህነት በአንቺ እንዳገኝ

ተመለሺ እመቤቴ ተመለሺ}
ከልቤ ኑሪ ተመለሺ  }
ስለ ኃጢአቴ አትሽሺ   }፪
       
አዝ..............


"አንቺ ሱላማጢስ ሆይ ተመለሺ ተመለሺ እናይሽ ዘንድ ተመለሺ ተመለሺ" መኃልዬ መኃልይ ፯፥፩ 🌺

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

✞ሦስት ዓመት ከመንፈቅ
ይህ ዘመን እመቤታችን ከኢየሩሳሌም ውጪ የኖረችበት ዘመን ነው፤ ጌታ በተወለደ በሁለት ዓመቱ ሰብአ ሰገል በመጡበት ወራት ከሄሮድስ ቁጣ የተነሣ ድንግል ከነልጇ በከተማ መቀመጥ አልቻለችም፡፡ ሰይጣን የሰው ልጆችን የመዳን ሥራ ሲጀመር ሲመለከት ዝም አላለም፤ ገና ይወርዳል፣ ይወለዳል ሲባል ትንቢቱን በመስማቱ እነ ኢሳይያስን በመጋዝ አስተርትሮ፣ በኩላብ አሰቅሎ አስገድሎ ነበር ሲወለድም የተወለደውን ሕጻን ማሳደድ ጀመረ፤
በተለይም ሊወለድ ሃያ አምስት ቀን ሲቀረው መላእክት የሚወለድበትን ሥፍራ ቤተልሔምን ተግተው ይጠብቁ ነበርና አጋንንት በጣዖታት አድረው መመለክ ስለተሳናቸው ጣዖታቱም ወድቀው ወድቀው በማለቃቸው ይህንን ምልክት አድርጎ ዲያብሎስ አዳኝነቱን ጀመረ፡፡
የአባቶቻችን አዳኝ እርሱ በእመ አምላክም ላይ ከሰው እስከ አጋንንት የክፋት ሠራዊቶችን አስከትሎ ለሠልፍ ተነሳ፡፡ አስቀድሞ በመጽሐፍ ስለዚች ቀን የተነገረው የመጀመሪያው ትንቢታዊ ቃል በዚህ ጊዜ ተፈጸመ “በአንቺ እና በሴቲቱ መካከል በዘርሽ እና በዘሯም ላይ ጠላትነትን አደርጋለሁ"ይህ ቃል በገነት ውስጥ ከተነገሩ የወደፊት የሰው ሕይወት ጠቋሚ ቃላት አንዱ ሲሆን እመቤታችንና የቀደመው እባብ ተብሎ በሚጠራው ጥንተ ጠላታችን በሠራዊተ አጋንንት እና በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ መካከል የሚደረገውን ጦርነት የሚያመላክት ቃል ነው፡፡እግዚአብሔር የተናገረው ሊፈጸም ግድ ነውና የንጉሠ ሰማይ ወምድር እናቱ እመቤታችን ድንግል ማርያም የሰይጣን ውጥን ጨራሽ በሆኑ ምድራውያን ነገሥታት ከሀገር ወደ ሀገር ተሰደደች፡፡
ዓለማችን እንዲህ ናት ዓመፀኞች የሚገኑባት፣ እውነት የሚሰደድባት የእሪያ ዓይነት ልማድ ያላት ዓለም ናት፡፡ እሪያ አብሮ የሚኖረው መልኩን ላለማየት እውነተኛ መልኩን ያሳየውን እንቍ ረግጦ ይሰብረዋል፤ ችግሩ እኮ የመልኩ ክፉነት እንጂ እንቍውማ ያለውን መልኩን ነበር ያሳየው፡፡ ዓለማችንም በኃጢአት የበለዘ ፊቷን የሚያሳዩዋት የእውነት መቅረዞችን እንደምንም ተሯሩጣ መርገጥ ትፈልጋለች፤ አሳድዳ የዋጠቻቸው ብዙ ሲሆኑ በለመደችው አሁንም የዋጣትን የኃጢአት ረግረግ ሊያደርቅ የመጣውን ጌታ ለመዋጥ አፏን ከፈተች፡፡
የተከፈተ አንደበቷን ሞት እስኪዘጋው፣ መቃብርም እስኪያትመው ድንግል ከዘንዶው ከሄሮድስ ፊት ሸሸች፤ ከመካከለኛው ምሥራቅ ወደ ምድረ አፍሪቃ ከነልጇ መጣች፤ ከሁለቱ አገልጋዮቿ ከዮሴፍ ከሰሎሜ በቀር ከዘመዶቿ የተከተላት ማንም አልነበረም፡፡
አምላካችን ክርስቶስ ንጉሠ ነገሥት ነውና ከሦስት ነገሥታት ግብርን ተቀበለ ይህን ካደረገ በኋላ ነገሥታቱ ግብራቸውን አቅርበው ሲመለሱ ሰውነቱ ፍጹም እንደሆነ ለማጠየቅ እናቱ ይዛው ተሰደደች በምድር እልፍ እልፍ ሠራዊት የተከተላቸው ሦስት ነገሥታት የሰገዱለት፣ በሰማይ ሥፍር ቁጥር የሌላቸው ሠራዊተ መላእክት የሚገዙለት ሲሆን ተስደደ፡፡

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

✞ሥላሴ ✞ አምባዬ✞

ሥላሴ አምላኬ ብዬ እዘምራለኹ
ሥላሴ አምባዬ ብዬ እቀኛለኹ
ሰማይና ምድር ደመናት ሳይቀሩ
አዕዋፍ አዝርዕት በእርሱ ተፈጠሩ

አዝ......

ብርሃን ጨለማ እንዲኾን በተራ
በዓለሙ ኹሉ ፀሐይ እንዲያበራ
እንድትሰለጥን ጨረቃ በሌሊት
ሥላሴ አስውቦ ፈጠረ ከዋክብት
አዝ.......

በእግር የሚኼዱ በክንፍ የሚበርሩ
በምድር ላይ ያሉ በጥልቅ የሚኖሩ
በሥላሴ ዘንድ ወላቸው ታውቀዋል
በከሃሊነቱ ፍጥረት ተፈጥረዋል
አዝ.......

አስቀድሞ ያለ ዓለም ሳይፈጠር
ሥላሴ ነበረ ዘመን ሳይቆጠር
ዘመን አሳልፎ ዘመን የሚያመጣ
ለክፉ ለደጉ ፀሐይ የሚያወጣ
አዝ......


@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

"የአምላክ አቃቤ ሕግ"

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

ጥቅምት ፭

የታላቁ አባት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ (ገብረ ሕይወት) የዕረፍታቸው መታሰቢያ

ጻድቁ የተወለዱት ግብፅ (ንሒሳ አካባቢ) ሲሆን አባታቸው ስምዖን እናታቸው አቅሌስያ ይባላሉ:: አባታችን ገብረ ሕይወት የጻድቃን አለቃ የቅዱሳን የበላይ ተጋድሏቸውና ድንቅ ተአምራቸው እንደ ሰማይ ከዋክብት የበዛ ቅዱስ ሰው ናቸው። የጻድቁን ክብር መናገር የሚችል ምን አንደበት ይኖራል? እንደ ምንስ ባለ ብራና ይጻፋል? ዜናቸውንስ ለመስማት የታደለ እንደ ምን ዓይነት ሰው ይሆን?

አባታችን ገብረ መንፈስ ቅዱስ ለ፭፻፷፪(562) ዓመታት በዚህች ዓለም ሲኖሩ እህል ያልቀመሱ /ምግባቸው ምስጋና ነውና/ ልብስ ያልለበሱ /ጠጉር አካላቸውን ይሸፍን ነበርና/ ሐዋርያዊ ሆነው ከግብፅ እስከ ኢትዮዽያ ብዙ ነፍሳትን ያዳኑ አባት፤ ሃገራችንን አስምረው አስራት እንድትሆናቸውም ተቀብለው ምድረ ከብድ አካባቢ አርፈዋል።

ጻድቁ ገብረ መንፈስ ቅዱስም ገብረ ሕይወትም ይባላሉ። በ፭፻፷፪ ዓመታት ሕይወታቸው እንደ ሐዋርያት ከምድረ ግብፅ እስከ ኢትዮጵያ ወንጌልን ሰብከዋል። በዚህም በሚሊዮን (አእላፍ) ለሚቆጠሩ ነፍሳት የድኅነት ምክንያት ሆነዋል።

ጻድቁ እንደ ሰማዕታትም ከከሃዲ ሰዎች ብዙ መከራን ተቀብለዋል። እንደ ባሕታውያን ለብዙ መቶ ዓመታት ሰው ሳያዩ ቆይተዋል። ለ'የ'ት የሚለው ግን የጽድቅ ሕይወታቸው ነው፤ ከዕልፍ አዕላፍ አጋንንት ጋር ተዋግተው ድል ማድረግ ችለዋልና።

የንሒሳው ኮከብ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ለኢትዮጵያ ልዩ ፍቀር አላቸው። ስለ ሃገሪቱና ሕዝቧ ፍቅር ሲሉ ለ፻(100) ዓመታት በደብረ ዝቋላ መከራን ተቀብለዋል። ምሕረትን ሲለምኑ ሥጋቸው አልቆ በአጥንታቸው ቁመው ነበርና ሃገራችን አሥራት ሆና ተሰጠቻቸው።

ስለዚህም ነው በሃገሪቱ ውስጥ ከ፳፻(2,000) በላይ የጻድቁ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳማትና አድባራት ዛሬም ድረስ ያሉት። በ፰(8)ኛው ክ.ዘ አካባቢ የተወለዱት አባታችን ያረፉት በ፲፬(14)ኛው መቶ ክ.ዘ አካባቢ ነው። ፍጥረታትን ሁሉ አዝዘው መጋቢት ፭(5) ቀን ሲያርፉ ግሩማን መላእክት ገንዘው አካላቸውን ሠውረዋል።

ሥላሴን የተሸከመ አካላቸው በጐልጐታ ተቀብሯል የሚሉም አሉ። "ሰላም ለመቃብሪከ ዘኢተከሥተ ለባዕድ: ከመ መቃብሩ ለሙሴ ወልደ ዮካብድ: ዜና መቃብሪከሰ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ጸማድ: ቦ ዘይቤ በኢየሩሳሌም አጸድ: ወቦ ዘይቤ ኀለወ በከብድ።" እንዲል።

ጻድቁ አባታችን አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ እረፍቱ መጋቢት ፭(5) ቀን ነው ይህ ደግሞ በታላቁ ዓብይ ጾም ወቅት ነው። ፍትሃ ነገስት አንቀጽ ፲፭(15) ላይ በዓብይ ጾም በዓል ማክበር ይከለክላል የሀዘን ወቅት ነውና ከበሮ አይመታም እልልታና ጭብጨባ የለም ፍጹም ሀዘን እንጂ :የመጋቢት ፳፯(27) ስቅለት ጥቅምት ፳፯ ቀን እንደሚከበረው ሁሉ የአባታችን አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ እረፍታቸው ወደ ጥቅምት ፭ ቀን ተዛውሮ እንዲከበር ተደረገ፡፡

የጻድቁ አባታችን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ረድኤት በረከታቸው በእኛ በምናምን ላይ ይደርብን!

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

"✞ ድንግል ሆይ ከሚያስብ ሁሉን ከማይዘነጋ ከልጅሽ ዘንድ አሳስቢ
✞ ድንግል ሆይ፣ በቤተ ልሔም ካንቺ የተወለደውን መወለድ ፣ በጨርቅ የተጠቀለለውንም አድግና (አህያና) ላም በብርድ ወራት እስትንፋስን ያሟሟቁትንም አሳስቢ ፣
✞ ድንግል ሆይ ፣ ርጉም በሆነ በሄሮድስ ዘመን ከርሱ ከአገር ወደ አገር ስትሽሺ ካንቺ ጋራ መሰደዱን አሳስቢ
✞ ድንግል ሆይ፣ከዓይኖችሽ የፈሰሰውንና በተወደደ ልጅሽ ፊት የወረደውን መሪር እንባ አሳስቢ ፣
✞ ድንግል ሆይ ረኃቡንና ጥሙን ችግሩንና ኃዘኑን ከርሱ ጋራ የደረሰብሽንም ጭንቀት ሁሉ አሳስቢ፣
✞ ጥፋትን ያይደለ ይቅርታን አሳስቢ፣ መዓትን ያይደለ ምሕረትን አሳስቢ፣
✞ ለጻድቃን ያይደለ ለኃጥአን አሳስቢ፣ ለንጹሐን ያይደለ ለተዳደፉት አሳስቢ
አሁንም አብንና ወልድን መንፈስ ቅዱስንም እናመስግነው ለዘለዓለሙ አሜን!"
(ቅዳሴ ማርያም )

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

ፈሊጣዊ ምክር
✞የእኔ ኃጢአት ከሌሎች በዓይነቱ ልዩ መሆኑን ሳስብ ኃጢአቴ ከማንም ቢበልጥ እንጂ እንደማያንስ ተሰማኝ እኔ አልፈርድም፡፡
✞ዘመኔን በስንፍና መጨረሴን ሳስበው አምላኬ የመከረኝን አለመስማቴ ዛሬ ቆጭቶኛል፡፡
✞እንቅልፍ መውደዴ ትርፉ ምንድነው ብዬ ሳስበው እድሜዬን በህልም ብቻ መጨረሴ ታየኝ የማይጨበጥ ሀብት፡፡
✞አለል ዘለል ስል የጨረስኩት እድሜ ወደ ኋላ ዞሬ ሳየው ደግሜ የማላገኘው የእግር እሳት ሆነብኝ፡፡
✞ጸሎት በፈለግኩ ጊዜ የማደርገው ቀላል ጉዳይ አድርጌ መገመቴ አስገረመኝ በዚህች ምድር ካልታደሉ ተግተው የማይፈጽሙት ከባድ ሥራ እርሱ መሆኑ የገባኝ ሳልጠቀምበት በመቅረቴ የተጎዳሁትን ባሰብኩ ጊዜ ነው፡፡
✞ለአንድ ደቂቃ ልገራው ያልቻልኩት ምላሴ ነው ከራስ ይልቅ ስለሌላው ማውራት ያልተመረኩበት ከንቱ ዕውቀት ሆኖብኝ ኖርኩ፡፡
✞ከማየት ጠግቦ ከመስማት ሞልቶ የማያውቀው ዓይኔና ጆሮዬ የሚጠቅመኝን ሰብስበው ቢሆን ኖሮ ዛሬ መኖሪያዬ ይህ ፕላኔት ባልሆነም ነበር፡፡
✞እራሴን ሞኝ ሆኜ አገኘሁት ከሰው መጠበቄ! ለካ የዚህ ዓለም የአኗኗር ዘዴ እኔ ለሰው ሆኜ መገኘቴን እያረጋገጡ ማለፍ ብቻ ነው፡፡
✞ለሰው ፊት አድልቼ እግዚአብሔርን ስበድል መኖሬን ሳስበው ለስንፍናዬ መጠን የምለካበት መሳሪያ አጣሁ፡፡
✞በቆንጆ የሚማልልና በወንዝ የሚወሰድ አንድ አይነት ናቸው ሁለቱም እየሳቁ ይሞታሉ፡፡
✞ሃይማኖት የሌለው ሰው እና መልህቅ የሌለው መርከብ አንድ ናቸው ከመዋለልና ከመስጠም ውጪ ለህልውናቸው አማራጭ የላቸውም፡፡
✞ከሰይጣን ጋር ውል መግባት ለጠላት ጩቤ ማቀበል ነው ምቹ ጊዜ ላይ ሊገልኸ እንጂ ባላጋራነቱን የሚያስቀይር ባሕርይ ኖሮት እንዳይመስልህ፡፡
✞እግዚአብሔር የሰጠህን ነፃ ፈቃድ መልሶ ሊደፍርብህ እንኳ አይፈልግም በገዛ እጅህ ለሰይጣን ከሰጠኸው ግን በመናፍስቱ ዓለም እንደአሻንጉሊት መጫወቻቻቸው ትሆናለህ
✞ከገንዘብ ሰው ይበልጣል ገንዘብ ካላሉ ግን በገንዘቡ ሰው ሞት ይገዛል
/ከአዘጋጁ/
✞✞✞✞✞✞✞ ተፈጸመ ✞✞✞✞✞✞✞


@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

እንዴት እና ምን ብዬ ልናዘዝ?
ምዕራፍ ፲ ክፍል ፪
.........................................

✞12ቱ ጥያቄዎችና መልሶቻቸው
1. ከመናዘዜ በፊት ልረሳው የማይገባ ቁም ነገር ምንድር ነው?
✞ ከመናዘዞ በፊት በጥልቀት ራስን መመርመርና በሕይወት ያለፉበትን ኃጢአት ማስታወስ ፈፀምኳቸው በሚሏቸው ኃጢአቶች ላይ ጸጸትና ውስጣዊ ጥላቻ በልብዎ መፈጠሩን ማረጋገጥ ያስፈልጋል፡፡
2. ኃጢአቴን ተናዝዤ ቀኖናዬን ከፈጸምኩ በኋላ ብሎም ቅዱስ ቁርባን ልወስድ እየተዘጋጀሁ ዘንግቼ ለካህኑ ሳልናገር የረሳሁት ኃጢአት ትዝ ቢለኝስ?
✞ ቅዱስ ቁርባን ከመቀበል ይታቀቡ እንደገናም ወደ ንስሐ አባትዎ ሄደው ትዝ ያለዎትን ኃጢእት ይንገሯቸው።
3. ኃጢአቴን ተናዝዤ በቀኖና ላይ ሳለሁ ወይም ቀኖናዬንም ፈጽሜ እንደገና በኃጢአት ላይ ብወድቅስ?
✞ ኑዛዜ የክርስትና ሕይወት ፍፃሜ አይደለምና ፈጽሞ ተስፋ አይቁረጡ ወደ ንሰሐ እባትዎ ሄደው የወደቁበትን ኃጢአት ይናዘዙ ከዚህ ድካም ለመውጣት ምን ማድረግ እንዳለብዎ በጥልቀት ከንስሐ አባትዎ ይመካከሩ በሐፍረት በይሉኝታ እኔ አልጠቀምም በማለት ወድቀው እንዳይቀሩ ይጠንቀቁ "ጻድቅ ሰው ሰባት ጊዜ ይወድቃል ይነሳማል” /ምሳ 24፥16/
4. ካህን በሌለበት ባዕድ ሀገር ብኖርስ እንዴት ንስሐ እገባለሁ?
✞ ካህናት በሌሉበት አካባቢ ቢሆኑም ያለ ንስሐ ለመኖር አይዘናጉ ራስዎን ከመረመሩ በኋላና አጋዥ መንፈሳዊ መጽሐፍትን ካነበቡ በኋላ ኑዛዜዎችን በሙሉ በደብዳቤ ጽፎ በማዘጋጀት ለንስሐ አባቶቻችሁ ባሉበት ሀገር እንዲደርሳቸው ያድርጉ በዘመናችን የመገናኛ አውታሮች ብዙ ስለሆኑ አመቺውን ተጠቅመው ካህኑን ያግኙአቸው።“ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊና ቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሳርያ የዘማዊቷን ሴት ኃጢአት በደብዳቤ አስተሰርየውላታል"

Читать полностью…
Subscribe to a channel