ethiopian_orthodox | Unsorted

Telegram-канал ethiopian_orthodox - የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

30344

በዚህ Channel ውስጥ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንን ዶግማ ፤ ቀኖና እና ትውፊት የጠበቁ ትምህርቶች ይተላለፉበታል፡፡ ለአስተያየት: ጥቆማና ጥያቄ በዚህ ያግኙን ☞ @Ethiopian_Orthodox_bot Buy ads: https://telega.io/c/Ethiopian_Orthodox

Subscribe to a channel

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

"ሞትማ ለመዋቲ ይገባል"
ሞትማ ለመዋቲ ይገባል(፪){፪}
የድንግል አሟሟት እጅጉን ይደንቃል{፪}

ለልጇ ስትነግር ሞት እንደምትፈራ{፪}
ወሰዷት በሐሴት መላእክተ ሐራ{፪}
ጭንቀቱ ሳይገጥማት ሳታስብ ድንገት{፪}
እንደ እንቅልፍ ወሰዳት ያ መልአከ ሞት{፪}

አዝ =

ይገርማል ይደንቃል የድንግል ፍልሰታ{፪}
በምስጋና አረገች ከልጇ ተጠርታ
በይባቤ አረገች ከልጇ ተጠርታ
እያሸበሸቡ መላእክተ ሰማይ{፪}
ወስደው አቀረቧት ከልጇ መንበር ላይ{፪}

            አዝ =

ሱባኤ እንደገቡ እንደ ሐዋርያት{፪}
እኔም ከቤት ወጣሁ አንቺኑ በመሻት{፪}
ትንሳኤሽን በክብር እንዳሳየሻቸው{፪}
እኔንም ለዚህ አብቂኝ ብርሃንሽን እንዳየው{፪}

©በሊቀ መዘምራን ኪነጥበብ ወ/ቂርቆስ
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

ጥር ፳፩
በዓለ አስተርዕዮ ማርያም


ጥር ሀያ አንድ በዚህች ቀን አምላክን ለወለደች ለእመቤታችን ለከበረች ድንግል ማርያም የእረፍቷ በዓል መታሰቢያ ነው።ያን ጊዜ እመቤታችን በልጇ በጌታችን በፈጣሪያችንና በመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በከበረ መቃብሩ ቦታ ትፀልይ ነበረ ከዚህም ዓለም እንደምትለይ መንፈስ ቅዱስ ነገራት። ከዚህም በኋላ ከደብረ ዘይት ደናግል መጡ ጌታችን ነግሯቸዋልና እርሷም ነገረቻቸው።

በዚያንም ጊዜ እመቤታችን እንዲህ ብላ ፀለየች፦ "ልጄ ወዳጄ ጌታዬና ፈጣሪዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ልመናዬን ተቀብለህ ደቀ መዝሙርህን ዮሐንስን በዚች ሰዓት አምጣው።እንዲሁም ህያዋን እንደሆኑ ሐዋርያትን ሁሉንም ነፍሳቸውንም የለየሀቸውን አምጣቸው አንተ የህያዋንና የሙታን አምላክ ነህና ላንተም ምስጋና ይሁን ለዘለዓለሙ አሜን።"

በዚያንም ጊዜ በመንፈስ ቅዱስ ትእዛዝ ከኤፌሶን አገር ዮሐንስን ደመና ተሸክማ ወደ እመቤታችን ማርያም አደረሰችው ሰገደላትና በፊቷ ቁሞ እንዲህ አላት "ሰላምታ ይገባሻል ጌታችንን ፈጣሪያችንንና መድኃኒታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን የወለድሺው ፀጋን የተመላሽ ደስ ይበልሽ አንቺ ከዚህ ዓለም ተለይተሽ በክብር በምስጋና ወደ ዘለዓለም ህይወት ትሄጃለሽና። ይህም ስሙ ክቡር ምስጉን የሆነ ጌታችንና ፈጣሪያችን ድንቆች ተአምራቶችን በአንቺ ላይ ከገለጠ በኋላ ነው።"

እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም ይህን በሰማች ጊዜ እጅግ ደስ አላት እግዚአብሔርንም እንዲህ ብላ አመሰገነችው "ፈጣሪዬ ጌታዬ ላንተ ምስጋና ይሁን አንተ የለመንኩህን ሰጥተኸኛልና አሁንም ነፍሴን ተቀብለው ወደ ሰማይ ወደ አንተ ሊያሳርጓት ከሚመጡ መላእክቶችህ ጋር በመምጣትህ የምለምንህን ሁሉ ስጠኝ።"

በዚያንም ጊዜ ከሰማይ እንዲህ የሚል ቃል መጣ "እነሆ አሁን መላእክት ይደርሳሉ ሐዋርያትም ሁሉ ከምድር ዳርቻ በደመና ተጭነው ለሰማይና ለምድር ጌታ ለኢየሱስ ክርስቶስ እናቱ ወደ ሆነች ወደ ቅድስት ድንግል ይደርሳሉ።"

ወዲያውኑ ሁሉም ሐዋርያት የሞቱትም ከመቃብራቸው ተነስተው ወደ እመቤታችን ደርሰው ሰገዱላት "አምላካችን ከአንቺ የተወለደ ፀጋን የተመላሽ ሆይ ደስ ይበልሽ። እርሱ ከዚህ ዓለም ለይቶ ቃል ኪዳን እንደሰጠሽ በክብር በምስጋና ከርሱ ጋር ያሳርግሻልና" አሏት።

በዚያንም ጊዜ እመቤታችን በአልጋዋ ላይ ተቀመጠች ሐዋርያትንም እንዲህ አለቻቸው "ፈጣሪዬ ፈጣሪያችሁ ኢየሱስ ክርስቶስ እንደሚመጣ እናንተንም እንዳየኋችሁ እንደማየው አሁን አወቅሁ ከዚህ ከስጋዬም ወጥቼ ወደዘለዓለም ህይወት እሄዳለሁ ነገር ግን ትነግሩኝ ዘንድ እሻለሁ ከዚህም ዓለም እንደምለይ ከወዴት አወቃችሁ?"

ጴጥሮስና ሐዋርያት ሁሉም "ወዳንቺ እንመጣ ዘንድ መንፈስ ቅዱስ አዘዘን በደመና ላይም በተጫንን ጊዜ ወዳንቺ እንደ አይን ጥቅሻ ፈጥነን ደረስን።" አሏት።

እመቤታችን ማርያምም ይህን ነገር ከሐዋርያት በሰማች ጊዜ ድምጿን ከፍ አድርጋ እንዲህ አለች "ጌታዬና ፈጣሪዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ክቡር ምስጉን የሆነ ስምህን ፈፅሜ አመሰግናለሁ።የእኔን የአገልጋይህን መከራ ተመልክተህ ድንቅ ኃይልህን አድርገህልኛልና ከእንግዲህ ወዲያ ትውልድ ሁሉ ያከብሩኛል ያመሰግኑኛል።"

ፀሎቷንና ምስጋናዋን ስትጨርስ ሐዋርያትን እንዲህ አለቻቸው "እጣን አምጥታችሁ በማጠን የጌታዬን ኢየሱስ ክርስቶስን ስሙን ጥሩት" እነርሱም እንዳዘዘቻቸው አደረጉ። በዚያንም ጊዜ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እልፍ አእላፍት መላእክት አጅበው እያመሰገኑት መጣና አረጋጋት ያዘጋጀላትንም ተድላ ደስታ ነገራት በዚያንም ብዙዎች ድንቆች ተአምራቶች ተደረጉ እውሮች አይተዋልና፣አንካሶች ቀንተው ሄደዋልና ደንቆሮዎች ሰምተዋልና ለምፃሞች ነፁ አጋንንትም ከሰዎች ወጥተው ሄዱ ዲዳዎች ተናገሩ በሽታና ደዌ ያለበት ሁሉ ዳነ እመቤታችን ድንግል ማርያም ወዳለችበት ቤት በቀረቡ ጊዜ ከደዌያቸው ይፈወሳሉና።

ከዚህም በኋላ እመቤታችን ተወዳጅ ልጇን እንዲህ አለችው "በአየር ውስጥ ተበትነው ከሚኖሩ ከሚያስደነግጡ ግሩማን መላእክት የተነሳ ከእሳት ባህርም እፈራለሁ" ጌታችንም "ከእናንተ ለማንም በአለሁ ላይ ስልጣን የለውም" አላት።

ከስጋዋም የምትለይበት ጊዜ ሲደርስ ሐዋርያትና ደናግል ትባርካቸው ዘንድ እያለቀሱ ለመኗት እጇን በላያቸው ዘርግታ ባረከቻቸው በዚያንም ጊዜ ጌታችን ንፅህት ነፍሷን ከስጋዋ ለይቶ በመለኮታዊ እጆቹ ይዞ በብርሀን ልብስ አጎናፅፎ ወደ ከፍተኛ መኖሪያ ከእርሱ ጋር አሳረጋት ስጋዋን ግን እንደሚገባ ገንዘው ወደ ጌቴሴማኒ ተሸክመው እንዲወስዷት ሐዋርያትን አዘዛቸው።

ነፍሷ ከስጋዋ ከመውጣቷ በፊት በሰው አንደበት ይህ ነው ተብሎ የማይነገር ብርሀንን እያየች ነበር የክብር ባለቤት ጌታችን ክርስቶስም "እንግዲህ ስጋሽን ተድላ ወዳለበት ገነት አፈልሳለሁ። ዳግመኛም ስጋሽን ከነፍስሽ ጋር አዋህጄ አስነስቼ መላእክት በውስጡ በፊትሽ ሆነው በሚያመሰግኑበት ተመሳሳይ በሌለው ተድላ ደስታ በአለበት ማደሪያ አኖርሻለሁ" አላት።

እመቤታችንም እንዲህ አለች "አቤቱ በረቀቀ ጥበብህ ይህን ሁሉ የሰራህ አመሰግንሀለሁ ሁለተኛም ልመናዬን ትሰማ ዘንድ እለምንሀለሁ በስሜ ወደ አንተ የሚለምነውን ሁሉ ልመናውን ተቀበለው በመከራም ውስጥ ሆኖ ስሜን ጠርቶ ወዳንተ የሚለምነውን ከመከራው ሁሉ አድነው በሰማይም በምድርም በስራው ላይ ሁሉ አንተ ከሀሊ ነህና መታሰቢያዬን በውስጧ የሚያደርጉትን ቦታ ሁሉ ባርክ በእኔ ስም የሚያቀርቡትን የሁሉንም መስዋእታቸውን ተቀበል።"

ጌታችንም እንዲህ ብሎ መለሰላት "የለመንሽኝን ሁሉ አደርግልሻለሁ ደስ ይበልሽ ከእኔ ከአባቴ ከመንፈስ ቅዱስ ዘንድ ፀጋ ክብር ባለሟልነት ተሰጥቶሻልና ስምሽንም ጠርቶ የሚለምን ሁሉ በዚህም ዓለም በሚመጣውም አለም አይጠፋም።"

እመቤታችንም ካረፈች በኃላ ጌታችን እንዳዘዘ ወደ ጌቴሴማኒ ሊወስዷት ሀዋርያት ገንዘው ተሸከሟት። አይሁድም በሰሙ ጊዜ ስጋዋን ሊያቃጥሉ ወጡ ከእነርሱም አንዱ ከምድር ላይ ይጥላት ዘንድ የእመቤታችንን አልጋዋን ያዘ ያን ጊዜ ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልአክ እጆቹን በእሳት ሰይፍ ቀጣውና እጆቹ በአልጋዋ ላይ ተንጠለጠሉ።

ያን ጊዜ በጌታችን አምኖ ወደ እመቤታችን እያለቀሰ እንዲህ ብሎ ለመነ "የእውነተኛ አምላክ የጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ እናት አንቺ በእውነት ድንግል የሆንሽ በእኔ ላይ ይቅርታ ታደርጊ ዘንድ እለምንሻለሁ" በሐዋርያትም ልመና እጆቹ ተመልሰው እንደቀድሞው ደኅነኞች ሆኑ።

በቀበሩዋትም ጊዜ ከዚያ ሶስት ቀን ኖሩ እረፍቷም የሆነው እሁድ ቀን በጥር ወር በሀያ አንድ በዚች ቀን ነበረ ጌታችንም ብርሀናውያን መላእክትን ላከ እነርሱም ስጋዋን ከመቃብር ወስደው በገነት ውስጥ በእፀ ህይወት ስር አኖሩዋት።

ሐዋርያ ቶማስ ግን ያን ጊዜ አልነበረም በደመና ላይ ተጭኖ እርሱ ሲመጣ መላእክት ሲያሳርጓት እመቤታችንን አገኛት መላእክትም ለአምላክ እናት ለእመቤታችን ድንግል ማርያም ና እጅ ንሳ አሉት እርሱም ሰገደላትና ተሳለማት ከእርሷም ተባረከ ከዚህም በኃላ ወደ ሐዋርያት ደረሰ ። እነርሱም እመቤታችንን ማርያምን እንደ አረፈችና እንደ ቀበርዋትም ነገሩት ቶማስም ስጋዋን እስከማይ አላምንም አላቸው።

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

ስለሆነም በተደጋጋሚ እየተፈጸሙባት የሚገኙትን እነዚህን እኩይ ተግባራት ከዚህ በላይ በዝምታና በትዕግስት ማለፍ መንፈሳዊ ተልዕኮዋን በአግባቡ እንዳትወጣ የሚያደርጋት ከመሆኑም በላይ መብቷን በእጅጉ የሚጋፋ፣ጥንታዊያን አባቶች ለሥርዓተ አምልኮ መፈጸሚያ ሲጠቀሙባቸው የነበሩና በትውልድ ቅብብሎሽ አሁን ያለው ትውልድ የተረከባቸው ንዋያተ ቅድሳቶቿን አደጋ ላይ የሚጥል ሁኔታ ከመፈጠሩም በላይ በሥርዓተ አምልኮዋ ላይ በማላገጥ በምዕመናን ዘንድ ቁጣ እንዲቀሰቀስ የሚያደርጉ በርካታ ተግባራት እየተፈጸሙ በመምጣታቸው ምክንያት እነዚህ እኩይና ጸብ አጫሪ ተግባራት ሕጋዊ እልባት እንዲያገኙ ማድረግ የግድ የሚልበት ደረጃ ላይ ደርሳለች።

ስለሆነም ቅድስት ቤተክርስቲያናችን ጉዳዩን በልዩ ሁኔታ ማጥናት፣መከታተልና ሕግን መሰረት ያደረገ መፍትሔ እንዲያገኙ ማድግ አስፈላጊ ሆኖ ስላገኘችው ወቅታዊ ሁኔታውን በዝርዝር በማጥናት ተቋማዊ እልባት የሚያገኝበትን መንገድ የሚያጠና ኮሚቴ ተቋቁሞ ወደ ሥራ እንዲገባ ያደረገች ሲሆን የቤተ ክርስቲያናችን የሕግ አገልግሎት መምሪያም በሕግ አግባብ ተጠያቂነትን በማረጋገጥ ፍትሕ ማግኘት የሚቻልበትን ሁኔታ ለመፍጠር አስፈላጊውን መረጃ በማሰባሰብና በማደራጀት ክስ መመስረት የሚያስችለውን ሁኔታ በማመቻቸት ወደ ተግባር ለመለወጥ በዝግጅት ላይ ይገኛል።

ከዚህ ጎን ለጎንም ከፍ ሲል እንደተገለጸው በጠቅላይ ቤተክህነት ከሚገኙ መምሪያዎች መካከል ጉዳዩ በቀጥታ የሚመለከታቸውን መምሪያዎች በማካተት የተቋቋመው ኮሚቴም ዝርዝር ጥናቶችን በሚገባ በማጥናትና ችግሮቹን ለይቶ ከመፍትሔ ሀሳብ ጋር በአጭር ጊዜ ውስጥ በማቅረብ በቤተክርስቲያኒቱ ማዕከላዊ አስተዳደር አማካኝነት ተቋማዊ አቋም የሚወሰድበትና በቅዱስ ሲኖዶስ ደረጃ የማያዳግም መፍትሔ የሚሰጥበትን ሁኔታ ለማመቻቸት የሚያስችል ሥራ በመሥራት ላይ መሆኑን እየገለጸች በሁለቱም ዘርፎች የተገኙ ውጤቶችን በተመለከተ በተከታታይ ለሕዝበ ክርስቲያኑ እንዲገለጽ የምታደርግ መሆኑን ከወዲሁ እያስታወቀች በጉዳዩ ዙሪያ ሙያዊ ድጋፍ ለመስጠት ፈቃደኛ የሆኑ ምዕመናንና ምዕመናት በተቋቋመው ኮሚቴ አማካኝነት የሚደረግላቸውን ጥሪ ተቀብለው ለቤተክርስቲያናችን መብት መከበር የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ እናት ቤተክርስቲያን ጥሪዋን ታቀርባለች።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን
መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት
አዲስአበባ -ኢትዮጵያ
ጥር ፲፯ቀን ፳፻ ፲ወ፯ ዓ.ም

@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

"ቂርቆስ አንጌቤናይ"
ቂርቆስ ሕጻን አንጌቤናይ (፪)
አንጌቤናይ ወልደ አንጌቤናይት(፪)

ገና በሦስት ዓመት ወንጌልን ሰብከኻል
ስለ ጌታ ፍቅር ቆመህ መስክረሃል
እኔ ክርስቲያን ነኝ ብለህ ስትናገር
ቅድቲቷ እናትህ ተደስታ ነበር
       አዝ= = = = =
ስለ ክርስትና መከራ ቢያበዙ
ጦርና ጋሻውን ሰይፍንም ቢመዙ
በእምነትህ ጸናህ ያለመደራደር
ከንጉሥ ፊት ስትቆም አስረውህ የፊጥኝ
       አዝ= = = = =
ነበልባለ እሳትን በአንተ ላይ ቢያነዱ
ውኃው የሚያጓራ እንደ ነጎድጓዱ
ቅድስቲቷ እናትህ ኢየሉጣም ፈርታ
ጸለይክላት ቂርቆስ ልቧ እንዲበረታ
       አዝ= = = = =
እኔ ቅርንጫፍ ነኝ እናትህን ብትላት
ስለ እናትህ ብለህ ጽናትን አድላት
ብለህ በለመንከው በጸለይከው ጸሎት
ዳግም እናትህን በእምነት ወለድካት
       አዝ= = = = =
ከእሳት ነጎድጓድ ድምጹ ከሚያስፈራው
ከሚንተከተከው ፍል ውኃ ከሆነው
ከእናትህ ጋራ ብትገቡ ከእሳቱ
ገብርኤል ሲመጣ ሁሉም ሆነ ከንቱ
      አዝ= = = = =
መዳንህን አይቶ ንጉሡ አፈረ
ፍጹም በመናደድ ልብሱን ተረተረ
ወታደሩን ጠርቶ አንገትህን ሰየፈው
ከቅዱሳን ሕብረት ነፍስህን ደመረው

©በመካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤ/ክ ውሉደ ብርሃን ሰ/ት/ቤት መዘምራን
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

ዳግመኛም ከጥዋት እስከ ማታ ከሥቃይ መሣሪያዎች ውስጥ ጨምረው አዋሏቸው ግን ማሠቃየት ተሳናቸው። ከዚህም በኋላ ከማምጠቂያው ውስጥ ጨምረው መገዙአቸውና አመድ እስከሆኑ ከቅባትና ከጨው ጋር በብረት ምጣድ ውስጥ ቆሉአቸው ጌታችንም ከሞት አስነሥቶ አዳናቸው።

ወደ መኰንኑም በገቡ ጊዜ እንዲህ አላቸው በእውነት ከሙታን ተለይታችሁ የተነሣችሁ ከሆነ ይህ ጫማዬ ከእግሬ ወጥቶ እንደ ቀድሞው ሕያው እንዲሆን አድርጉ ሕፃን ቂርቆስም በጸለየ ጊዜ ያ ጫማ ታለቅ በሬ ሆነ ከአንገቱም ፍየል ወጣ።

በዚያንም ሰዓት ለዐሥራ አንድ ሽህ አራት ሰዎች በሬውንና ፍየሉን አርደው ምሳ እንዲያደርጉላቸው መኰንኑ አዘዘ እንዲህም አለ ይህ በቅቷቸው ከጠገቡ ከዚህም ሌላ ምግብ ካልፈለጉ የተሠራው ሁሉ ዕውነተኛ ነዋሪ ነው። ከዚህም በኋላ አርደው ምሳ አደረጉላቸውና ከፍየሉ ሥጋ ስድስት እንቅብ ከበሬው ሥጋ አራት እንቅብ አተረፉ መኰንኑም የተረፈውን ሥጋ አይቶ ወደ ባሕር እንዲጥሉት አዘዘ።

መኰንኑም ቢያፍር የሕፃኑን ምላስ ይቆርጡ ዘንድ አዘዘ ጌታችንም ምላሱን መለሰለት ዳግመኛም በታላቅ ጋን ውኃ እፍልተው ሕፃን ቂርቆስንና እናቱን ኢየሉጣን ይጨምሩአቸው ዘንድ አዘዘ እናቱም አይታ ፈረች። ልጅዋም ወደ እግዚአብሔር በጸለየላት ጊዜ አምላካዊ ኃይልን አሳደረባትና ከልጅዋ ጋር ወደ ጋኑ ገባች። እንደ ውርጭም ቀዝቀዛ ሆነ ደግሞም በውስጡ መንኰራኲር ወዳለበት የብረት ምጣድ እንዲጨምሩአቸውና ሥጋቸው እሰከሚቦጫጨቅ እንዲስቡአቸው አዘዘ የእግዚአብሔርም መልአክ በሕይወት አወጣቸው።

መኰንኑም እነርሱን ማሸነፍ በተሳነው ጌዜ ቸብቸቧቸውን በሰይፍ ይቆርጡ ዘንድ አዘዘ በዚያን ጊዜ ለስም አጠራሩ ስግደት የሚገባው የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወረደ ሕፃን ቂርቆስንም የምትሻውን ለምነኝ አለው።

ሕፃኑም ሥጋዬ በምድር አይቀበር ስሜን ለሚጠራ መታሰቢያዬን ለሚያደርግ ቤተ ክርስቲያኔን ለሚሠራ የተጋድሎዬን መጽሐፍ ለሚጽፍና ለሚያጽፍ ወይም ለሚያነበው ለቤተ ክርስቲያኔ መባ ለሚያገባ በውስጧም ለሚጸልይ ለሁሉም ፍላጎታቸውን ስጣቸው ኃጢአታቸውንም ይቅር በል ስሜም በሚጠራበት በዚያች ቦታ የከብት ዕልቂት አይምጣ በሰውም ላይ እባር ቸነፈር በእህልም ላይ ድርቅ የውኃም ማነስ አይሁን።

መድኃኒታችንም የለመንከኝን ሁሉ እሰጥሃለሁ አንተም በቀኜ ትኖራለህ ሥጋህንም ኤልያስ በዐረገበት ሠረገላ ውስጥ አኖራለሁ አለው ሕፃን ቂርቆስም በሰማ ጊዜ እጅግ ደስ ብሎት ጌታችንን አመሰገነው። ከዚህም በኋላ በሌሊቱ እኩሌታም ከእናቱ ጋር አንገቱን ተቆረጠ መድኃኒታችንም በማይጠፋ አክሊል ጋረደው ነፍሶቻቸውንም በታላቅ ክብር ከእርሱ ጋር አሳደገ።

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

"አቡነ አረጋዊ"
ጽድቅህ ጠርቶናል አባትነትህ
በቅድስና ያማረ ሕይወትህ
ጌጥ ውበታችን አባ አረጋዊ
መናኝ መነኩሴ መልአክ ምድራዊ (፪)

ተቃኝተህ ስላደግክ በመንፈስ ቅዱስ
ወደ ፅርዕ ተጓዝክ ወደ አባ ጳኩሚስ
ተዘጋጅተህ ነበር ለችግር ፈተና
ዘሚካኤል አለህ ሰጥቶህ ምንኩስና (፪)

ለኢትዮጵያ ምእመናን አባት ተብለሃል
ወንጌል በማስተማር ብዙ አትርፈሃል
መጻሕፍት ተርጉመህ ያበረከትክ ለአበው
የአንተስ ትሩፋት እፁብ ነው ድንቅ ነው (፪)

የዓለም ጨው ሆነህ አጣፈጥካት ምድርን
በልባችን ሳልካት ቤተ ክርስቲያንን
ደብረ ሀሌ ሉያ ደብረ ዳሞ ቅድስት
የፈውስ ቦታ ናት መካነ ትኅርምት (፪)

ልክ እንደ አባቶችህ አስተዋይ ስለሆንክ
ገና ወጣት ሳለህ አረጋዊ ተባልክ
የሥጋን ሞት ሳታይ ተሰውረህ ከምድር
ብሔረ ሕያዋን ተቀላቀልክ በክብር (፪)

©በቦሌ ደብረ ገነት ቅ/ጊዮርጊስ እና ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ በፍሬ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት መዘምራን
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

ጥር ፲፬
ጻድቁ አቡነ አረጋዊ (ዘሚካኤል)


ጥር አሥራ አራት በዚህች ቀን ታላቁና የከበረው አባታችን አቡነ አረጋዊ (ዘሚካኤል) የተወለዱበት እና ወደ ደብረ ዳሞ የወጡበት ነው።

እኚህ አባት ከ9 ቅዱሳን አባቶች አንዱ ሲሆኑ አባታቸው ይስሐቅ የሮም ንጉስ ነበሩ፡፡ እናታቸው ንግስት እደና ይባሉ ነበር፡፡ የመጀመሪያ ስማቸው ዘሚካኤል ነው፡፡ ጥበብ መንፈሳ ሲማሩ አድገው ወደ እስክንድርያ ገዳም ገቡ፡፡ አበምኔቱ አባ ጳኩሚስ በፈቃደ እግዚአብሔር የመጡ መሆናቸውን አውቀው መዓረገ ምንኩስና ሰጥተዋቸዋል፡፡

የንጉሳዊ የቅንጦት ኑሮ ንቀው ትተው ገዳም ገብተው በምንኩስና ተወስነዋል፡፡ አባታችን በተጋድሏቸውም ከአባ እንጦንስ፣ ከአባ ጳውሊ እና ከአባ መቃርስ ቀጥሎ በአራተኛ ማዕረግ አበ መነኮሳት ሆነው ተመርጠዋል።

በገዳመ ዳውናስ 7 ዓመት ከቆዩ በኋላ ወደ ሮም ተመልሰው ሲያስተምሩ የሀገራችን ኢትዮጵያን ዜና ሰምተው ለመምጣት በ480 ዓ.ም ከአባ ፍሬምናጦስ በኋላ መንገድ ጀመሩ፡፡ ቅዱስ ሚካኤልም በክንፉ ተሸክሞ አክሱም አድርሷቸዋል፡፡

ተመልሰውም ሄደው ስለ ቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ መስክረዋል፡፡ ሐዋርያ ሳይላክላት በሃይማኖት በምግባር ጸንታ ትኖራለች ብለው ለሰባቱ ዘመዶቻቸው አበው መነኮሳት ነገሯቸው፡፡ ስምንቱም ጓዛቸውን ጠቅልለው በሮም ነግሶ የነበሩ ይስሐቅን (አባ ገሪማን) ጨምረው ንጉስ አልአሜዳ በነገሰ በአምስተኛ ዓመት ማለትም በ480 ዓ.ም ወደ ኢትዮጵያ ዘጠኝ ሆነው መጥተዋል፡፡

አባ አረጋዊ እናታቸው ቅድስት እድናን ደቀ መዝሙራቸውን ማትያስን አስከትለው እግረ መንገዳቸውን እያስተማሩና ድውያንን እየፈወሱ ደብረ ዳሞ ደረሰዋል፡፡

ከእግረ ደብር ሆነው አሁን ይህን ተራራ በምን ልወጣው እችላለሁ እያሉ ሲያወጡ ሲያወርዱ በንግግሩ ሐሰት የሌለበት አምላካችን በነቢዩ ዳዊት ላይ አድሮ በመዝሙር 90/91፥11-16 ላይ “በመንገድህ ሁሉ ይጠብቁህ ዘንድ መላእክቱን ስለ አንተ ያዝዛቸዋልና፤ እግርህም በድንጋይ እንዳትሰናከል በእጆቻቸው ያነሡሃል። በተኵላና በእባብ ላይ ትጫማለህ፤ አንበሳውንና ዘንዶውን ትረግጣለህ። እንዳለው የታዘዘ ዘንዶ መጥቶ ስደሳ ክንድ በሚያህል ጅራቱ ጠምጥሞ ቅዱስ ሚካኤል ሰይፈ እሳት ይዞ እየጠበቃቸው ከተራራው አናት አድርሷቸዋል፡፡

ወዲያው ሃሌ ሉያ ለአብ ሃሌ ሉያ ለወልድ ሃሌ ሉያ ለመንፈስ ቅዱስ ብለው አመስግነዋል፡፡ ቦታውም ደብረ ሃሌ ሉያ ተብሏል፡፡ በዚያ ዕለት ግማሽ ህብስት በልተው ጠገቡ፤ ከዚያ በኋላ ግን ምድራዊ ሕብስት አልተመገቡም፡፡ በሰንበተ ክርስታያን ከቅዳሴ በኋላ ሕብስተ ሰማያዊ እያመጡላቸው ይመገቡ ነበር እንጂ፡፡ ኋላም ዜና ጽድቃቸውን ሰምተው ከስድስት ሺህ ያላነሱ ደቀ መዛሙርት ተሰብስበውላቸዋል፡፡

ዘጠና ዘጠኝ አመት ሲሞላቸው ጌታ በመንፈቀ ሌሊት ተገልጾ ምድራዊ መንግስትህን ትተህ ስላገለገልከኝ ህልፈት ሽረት የሌለባት ሰማያዊ መንግስቴን አወርሰሃለሁ ብሎ ቃልኪዳን ሰጣቸው፡፡ በስምህ የተማጸነውን እስከ አስራ አምስት ትውልድ ድረስ እምርልሃለሁ አንተም ከሞት ገጽ ትሰወራለህ ብሎ ተስፋቸውን ነገራቸው፡፡ እሳቸው መነኮሳቱን ሰብስበው ከእንግዲህ በሥጋ አታዩኝም ብለው ነግረዋቸው አበምኔት ሾመውላቸው በደብረ ዳሞ ተራራ በስተምስራቅ አቅጣጫ ተሰውረዋል፡፡

የጻድቁ አባታችን ረድኤት በረከታቸው እንዲሁም አማላጅነታቸው አይለየን!

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

ጥር ፲፪
ቃና ዘገሊላ


"የኢየሱስም እናት በዚያ ነበረች"
ዮሐ ፪:፭

@Ethiopian_Orthodox

ቃና ከናዝሬት ከተማ በሰሜናዊ ምዕራብ በገሊላ አውራጃ የምትገኝ ከተማ ስትሆን በወቅቱ ትንሽና ገጠራማ መንደር ናት፡፡ ነገር ግን በውስጧ በተደረገው ተአምር መጽሐፍ ቅዱስ ስለመዘገባት ሁሌም የሚታወስ ታሪክ ያላት ሥፍራ ናት፡፡

ቃና ጌታችን ሁለት ታላላቅ ተአምራት ያደረገባት መንደር ስትሆን አንዱን ተአምር በቅርበት (በአካል ተገኝቶ) ሁለተኛውን ደግሞ በርቀት (ቃል ብቻ ተናግሮ) ያደረገው ተአምር እንደሆነ ተጠቅሷል፡፡ ይህውም የጌታችን ቀዳሜ ተአምር የሆነው ቃና ሠርግ ቤት ተአምር ሲሆን፤ ሁለተኛው በቅፍርናሆም የንጉሥ ባለሟል የሆነ አንድ ሹም ጌታ ወደ ገሊላ እንደመጣ ሰምቶ ከቅፍርናሆም ሠላሳ ኪሎ ሜትር ተጉዞ በመምጣት ልጁ በንዳድ (yellow fever) መታመሙን ነግሮት ወደቤቱ ወርዶ እንዲፈውስለት ለመነው ፡፡ ዛሬ በሚሊየን የሚቆጠሩ ህጻናትና ነፍሰጡር እናቶች በአፍሪካና ኢስያ ብሎም በኢትዮጵያ ለሞትና ለስቃይ የሚዳረጉበት ህመም መሆኑን ልብ ይበሉ፡፡ ለአፍሪካ ህጻናትና እናቶች ሞት ይርቅ ዘንድ ጌታ ሆይ ቃል ተናገር ሞት ሰምቶ ይደንግጥ ያለ እድሜ ሞት ይጥፋ እንበለው፡፡ጌታ ግን ለሹሙ ልጁ እንደማይሞት ሲነግረው ይህንን አምኖ ሄደ ልጁ ባለበት ቦታ ሆኖ ጌታ በተናገረበት ሰዓት ተፈወሰለት፡፡ ይህንን ነው በርቀት የተደረገ ተአምር የምንለው፡፡ ዮሐንስ ፬፥፵፮-፶፬

የቃና ዘገሊላ ሠርግ የጌታችን የመጀመሪያ ተአምር ነው ሲባል ከልጅነቱ ጀምሮ ተአምራትን ያደርግ እንደነበር ቅዱሳት መጻሕፍት ያስረዱናል፡፡ ነገር ግን በግልጥ በአደባባይ በህዝብ ፊት ማስተማር የጀመረው ከሠላሳ ዓመቱ በኋላ ነበር፡፡ይሄውም በብሉይ ልማድ ለማስተማር በነቢያነት የሚመረጡትና የሚላኩት ከሠላሳኛው እድሜ በኋላ ነበርና ነው፡፡ የቃና ገሊላ ሠርገኞችን ስም መጽሐፍ ቅዱስ በስም ባይጠቅስልንም ሊቃውንት ዶኪማስ እንደሆነ ሲያስተምሩ ለእመቤታችን ዘመድ መሆኑንም የሚጽፉም አሉ፡፡

ቅዱስ ዮሐንስ ይህንን ተአምር ሲናገር “እንዲህ በሦስተኛውም ቀን በገሊላ ቃና ሠርግ ነበረ፥ የኢየሱስም እናት በዚያ ነበረች፤ ይላል”፡፡ በሰርጉ ጌታ የተገኘው ብቻውን አይደለም እናቱና ደቀመዛሙርቱ ነበሩ፡፡ ይህ ነው እንግዲህ ቤተክርስቲያን ፈጣሪ የሆነውን ኢየሱስ ክርስቶስን ስትሰብክ እመቤታችንን ቅዱሳንን የማትለየው፡፡ ይህንን እንድንሰብክ የነገረን ቅዱስ ዮሐንስ ነው፡፡

በክርስቲያኖች ልብ በህይወታችን በኑሮአችን ጌታን እንደማንለየው ድንግል ማርያምን ቅዱሳንን አንለይም፡፡እርሱ በአምላክነቱ ድንግል ማርያም በእናትነትዋ ቅዱሳን በምልጃቸው አንለያቸውም ፡፡ “እኔ የወይን ግንድ ነኝ እናንተም ቅርንጫፎች ናችሁ”። ዮሐ ፲፭፥፭ ዛሬ የአለም ሩጫ የመናፍቃን ተንኮል ትውልዱን ከድንግል ማርያም መለየት ከቅዱሳን መለየት አላማቸው አድርገውታል፡፡ ምናልባት መብቱን ቢያገኙ ቅዱስ ዮሐንስን በዚህ ምዕራፉ ጌታን አልሰበከም ይሉት ይሆን?

ጌታ በቃና ዘገሊላ ተአምር የጀመረው በሠርግ ቤት መሆኑን ቅዱስ ዮሐንስ ሲናገር በቃና ሠርግ ነበር ነው የሚለው፡፡ ይሄውም ሠርግ ቤትን የተአምር መጀመሪያ ያደረገበት ምክንያት ሰይጣን የሰውን ልጅ የመጀመሪያ ኃጢያት በማሰራት ያፈረሰው የጋብቻን አንድነት በመሆኑ በማዳኑም ሂደት የጉሰቆለ ጋብቻን ወደ ቀደመ ቅድስናው ለመመለስ ጋብቻን ለመባረክ በሠርግ ቤት ጀመረ፡፡

ሰይጣን አዳምንና ሔዋንን ከእግዚአብሄር ከለያቸው (ዕፀ በለስን ከበሉ) በኋላ መግባባት መስማማት አቃታቸው፤ አንዱ አንዱን ይከስ ጀመር አንድ አካል መሆናቸው ቀረ፡፡አዳም ህይወቴ ያላትን ሔዋንን አጥፊዬ ናት አላት፡፡ የጋብቻ አንድነት ጠፋ፤ ውድቀት ወደ ቤተሰብ ገባ፡፡አለመታዘዝ በዘር ወደ ሰው ልጅ ሁሉ ደረሰ፡፡ “ስለዚህ ምክንያት ኃጢአት በአንድ ሰው ወደ ዓለም ገባ በኃጢአትም ሞት፥ እንደዚሁም ሁሉ ኃጢአትን ስላደረጉ ሞት ለሰው ሁሉ ደረሰ”፡፡ ሮሜ ፭፥፲፪

ስለሆነም ጋብቻን ይቀድስ ያከብር ዘንድ የሰው ልጆችን ብሎም የአዲሲቷን የክርስቶስ አካል የሆነችው ቤተክርስቲያን መሰረት የሆነው ቤተሰብ የሚመሠረተው ከተቀደሰ ቤተሰብ በመሆኑ ጋብቻን መባረክ የመጀመሪያ ተአምር እንዳደረገ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ይነግረናል፡:

የቃና ገሊላ ሠርግ የጌታችን ፍጥረታት የሚታዘዙት፤ እንዲሁም የእመቤታችን ምልጃ የተገለጠበት ተአምር ነበር ፡፡ይህንንም የወይን ጠጅም ባለቀ ጊዜ የኢየሱስ እናት፦ “የወይን ጠጅ እኮ የላቸውም አለችው”። ሠርጉ መካከል ላይ ወይን ጠጅ አለቀ ይህ ለሰርገኛው ትልቅ ሀፍረት ነው ነገር ግን እርሷ ግን ጭንቀታቸውን፤ችግራቸውን ስላወቀች ያውም ሳያማክሯት የልባቸውን ሐዘን አውቃ ወይኑ ማለቁን ነገረችው፡፡ ከዚህ በላይ ለእመቤትችን የምልጃ ማስረጃ ምን ይሆን? ፡፡ዛሬም እንደዶኪማስ ሠርግ ሕይወታችን ብዙ ነገር ያልቅበታል። በተለይ ያለንበት ዘመን በሰዎች ዘንድ ፍቅር፤እምነት፤ሰላም የጠፋበት መተማመን የጎደለበት በመሆኑ እመቤትችን ልጅዋን ፍቅር እኮ የላቸውም፤ እምነት እኮ የላቸውም፤ ሰላም እኮ የላቸውም፤ በማለት የጎደለንን እዲሞላልን ትጸልያለች፤ጌታም ልመናዋን ወዶ ሲመልስ ጊዜዬ ገና አልደረሰም ሲል አማናዊውን ወይን ደሜን የምሰጥበት ጊዜ ገና አልደረሰም ማለቱ ነው፡፡ ጌታም ለእናቱ ልመና ይህንን የማላደርግበት ምክንያት የለም በማለት ሲመል፤ “ኢየሱስም፦ አንቺ ሴት፥ ከአንቺ ጋር ምን አለኝ? ጊዜዬ ገና አልደረሰም አላት”። ይህንን ቃል ነው እንግዲህ ካንቺ ጋር ምን አለኝ ስላላት ምልጃዋን አልተቀበለም በማለት ትርጉሙን ማጣመም የሚፈልጉት፡፡ ነገር ግን የንባቡም ሆነ ትርጉሙ ልመናሽን የማልቀበልበት የማላደርግበት ምክንያት የለም ማለት እንደሆነ ግልጽ ነው፡፡ ይህንንም ቅዱሳት መጻሕፍት ሲያስረዱ፡- ኤልያስን በቤቷ የተቀበለች የሰራጵታዋ ሴት ልጅዋ በሞት ሲለይባት ታገለግለው የነበረውን የእግዚአብሔር ሰው ኤልያስን፦ "የእግዚአብሔር ሰው ሆይ፥ ከአንተ ጋር ምን አለኝ ኃጢአቴንስ ታሳስብ ዘንድ፥ ልጄንስ ትገድል ዘንድ ወደ እኔ መጥተሃልን?" አለችው። ፩ኛ ነገ ፲፯፥፲፰ ይህን ማለቷ በእኔና ባንተ መካከል ምን ጠብ አለ ለማለት እንጂ የንቀት አነጋገር እንዳልሆነ መገንዘብ ይገባል፡፡
ከሰው የወጣው መናፍስት ኢየሱስን ባየው ግዜ “በታላቅ ድምፅም እየጮኸ፦ የልዑል እግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ ሆይ፥ ከአንተ ጋር ምን አለኝ? እንዳታሠቃየኝ በእግዚአብሔር አምልሃለሁ አለ” በማለት ሲናገር አንተ እኔን ማዘዝ አትችልም የሚል ትርጉም አይሰጥም፡፡

በዚህም መሰረት የእናቱን ልመና ስለተቀበለ "እርሷም እናቱም ለአገልጋዮቹ፦ የሚላችሁን ሁሉ አድርጉ አለቻቸው፡፡" ይላል በዚህም ሰው አምላኩን ፈጣሪውን ይሰማ ይታዘዝ ዘንድ እንዲገባ አስተማረችን፡፡ የስራውን መጀመሪያ ባደረገው በዮርዳኖስ ሲጠመቅ እግዚአብሄር አብ የኢየሱስን ተወዳጅ ልጅነት እንዲሁም በደብረ ታቦር ላይ “በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው፤ እርሱን ስሙት የሚል ድምፅ መጣ”። ማቴ 17፡5 እመቤታችንም የተናገረችው እግዚአብሄር አብ በዮርዳኖስ የተናገረውን በደብረ ታቦር ስለ ልጁ የመሰከረውን ቃል ነው፡፡

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
"ከውኃ እንዴት እንወለዳለን የሚል ሰው ካለ እንዴት ከአፈር ተወለድን ብዬ እጠይቀዋለሁ!!!" ሊቁ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ በሰላም በጤና አደረሰን፥ አደረሳችሁ።
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

ሥርዓተ ማኅሌት ዘጥምቀት

"ሥርዓተ ነግሥ"
ስምዓኒ እግዚኦ ጸሎትየ ሃሌ ሉያ፤ ሃሌ ሉያ ወይብጻሕ ቅድሜከ ገዓርየ ሃሌ ሉያ፤ ሃሌ ሉያ ወኢትሚጥ ገፀከ እምኔየ፤ በዕለተ ምንዳቤየ አጽምእ ዕዝነከ ኀቤየ ሃሌ ሉያ፤ ሃሌ ሉያ አመ ዕለተ እጼውአከ ፍጡነ ስምዓኒ ሃሌ ሉያ፤ ሃሌ ሉያ ለዓለም ወለዓለመ ዓለም፤ ሃሌ ሉያ ዘውእቱ ብሂል፤ ንወድሶ ለዘሃሎ እግዚአብሔር ልዑል፤ ስቡሕ ወውዱስ ዘሣረረ ኲሎ ዓለመ፤ በአሐቲ ቃል።

መልክአ ሥላሴ
ሰላም ለአእዛኒክሙ አናቅጸ ጸሎት ሠናይ፤ ምሥጢራተ ሰሚዕ ሥላሴ ዘይተልዎ ርእይ፤ በአብትረ ያዕቆብ በርሀ ሥላሴክሙ ፀሐይ፤ ወተመሰሉ ሰብአ ዓይን አባግዓ ላባ ወማይ፤ ለኀበ አባግዕ ዘዮም ወጥምቀት ዓባይ።

ዚቅ
መኑ ይወርድ ውስተ ቀላይ፤ ክርስቶስ ውእቱ ዘወጽአ እማይ፤ እመንፈስ ቅዱስ ሠለስቲሆሙ፤ እለ አሐዱ እሙንቱ ፫ቲሆሙ፤ እለ ይከውኑ ሰማዕተ ፫ቲሆሙ፤ ለሊሁ ወረደ መንፈስ ቅዱስ፤ ከመ ይቀድስ ማያተ፤ ስቡሕኒ ውእቱ ወልዑልኒ ውእቱ ለዓለም፤ ጸጋ ወጽድቅሰ፤ በኢየሱስ ክርስቶስ ኮነ።

ነግሥ
ሰላም ለማየ ዮርዳኖስ ዮሐንስ ዘአተቦ፤ መንፈስ ቅዱስ ከመ አጥበቦ፤ ሶበ መጽአ ቃል እምሰማይ ለተናብቦ፤ ነድ ለማየ ባሕር ከበቦ፤ ማይ ኀበ የሐውር ጸበቦ።

ዚቅ
ርእዩከ ማያት እግዚኦ፤ ርእዩከ ማያት ወፈርሑ፤ ደንገፁ ቀላያተ ማያት ወደምጸ ማያቲሆሙ።

ወረብ
ርእዩከ 'እግዚኦ'/፪/ ርእዩከ ማያት/፪/
'ደንገፁ'/፪/ ቀላያተ ማያት ደንገፁ ቀላያተ ማያት/፪/

ትምህርተ ኅቡዓት
እምሰማያት እምኀበ አብ አይኅዓ፤ በሕማማተ ሥጋሁ ቤዘወነ፤ ወደሞ ክቡረ መንፈሰ ሕይወት፤ ወቅድሳተ መንፈስ ወሀበነ፤ ወማየ መንጽሔ ዚአነ።

ወረብ
'ወደሞ ክቡረ'/፪/ መንፈሰ ሕይወት ወቅድሳተ መንፈስ ወሀበነ/፪/
ወማየ መንጽሔ ዚአነ/፬/

ምልጣን
ክርስቶስ ተወልደ ክርስቶስ ተጠምቀ፤ ወለደነ ዳግመ እማይ ወእመንፈስ ቅዱስ፤ እሙነ ኮነ ለፀሐየ ጽድቅ አስተርእዮቱ፤ አማን፤ መንክር ስብሐተ ጥምቀቱ።

ወረብ
ክርስቶስ ተወልደ ክርስቶስ ተጠምቀ ክርስቶስ ተወልደ/፪/
'ወለደነ ዳግመ'/፪/ እመንፈስ ቅዱስ ወማይ/፪/

እስመ ለዓለም
ሖረ ኢየሱስ እምገሊላ ኀበ ዮሐንስ፤ ከመ ያጥምቆ በፈለገ ዮርዳኖስ፤ ወወጺኦ እማይ ተርኅወ ሰማይ፤ መጽአ ቃል እምደመና ዘይብል ዝንቱ ውእቱ ወልድየ፤ ዘአፈቅር ሎቱ ስምዕዎ።

ወረብ
ሖረ ኢየሱስ እምገሊላ ኀበ ዮሐንስ/፪/
ከመ ያጥምቆ በፈለገ ፈለገ ዮርዳኖስ/፪/

ዕዝል
ቀዳሚሁ ቃል ውእቱ ቃል፤ ቃለ እግዚአብሔር፤ ውእቱ ቃል ሥጋ ኮነ፤ ወተገሠ በሥጋ፤ መንፈስ ዘኢይትገሠሥ ወዘኢይትለከፍ፤ ዘመልዕልተ ሰማያት ዘመልዕልተ ሥልጣናት፤ ወገብረ መንጦላዕተ ሥጋ ሰብእ መዋቲ፤ ወረደ ዲበ ምድር፤ ወአንሶሰወ ውስተ ዓለም፤ በበህቅ ልህቀ በ፴ ክረምት፤ በዮርዳኖስ ተጠምቀ።

ምልጣን
ዘመልዕልተ ሰማያት ዘመልዕልተ ሥልጣናት፤ ወገብረ መንጦላዕተ ሥጋ ሰብእ መዋቲ።

አመላለስ
ወገብረ መንጦላዕተ/፪/
ሥጋ ሰብእ መዋቲ/፪/

አቡን
በ፭: እስመ ሰምዓ ይቀውም ሎቱ አብ ናዛዚ በርእየተ ርግብ ውስተ ምጥማቃት እንዘ ይብል፤ ዝንቱ ውእቱ ወልድየ ዘአፈቅር፤ ዘኪያሁ ሠምርኩ ይቤ፤ ወበይእቲ ሥጋ እንተ ነሥአ መድኅን እምቅድስት ድንግል፤ ኪያሃ ሠምረ አብ በሥጋ ምጽአቶ።

ቅንዋት
እምሰማያት ወረደ፤ ወእማርያም ተወልደ፤ ከመ ይሥዓር መርገማ ለሔዋ ዲበ ዕፅ ተሰቅለ፤ በ፴ ክረምት በዮርዳኖስ ተጠምቀ፤ ዘነቢያት ሰበክዎ ወአስተርአየ ገሃደ።

ሰላም
ተሣሐልከ እግዚኦ ምድረከ ሃሌ ሉያ፤ ዮም ፍሥሐ ኮነ በእንተ ልደቱ ለክርስቶስ፤ ወበእንተ ጥምቀቱ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፤ ኃዲጎ ፺ወ፱ ነገደ፤ ቆመ ማዕከለ ባሕር፤ ገብአ ወወጽአ በሰላም።

ምልጣን
ኃዲጎ ፺ወ፱ ነገደ፤ ቆመ ማዕከለ ባሕር፤ ገብአ ወወጽአ በሰላም።

ወረብ
ኃዲጎ ፺ወ፱ ነገደ/፪/
ማዕከለ ባሕር ቆመ ማዕከለ ባሕር/፪/

💠 መልካም በዓል! 💠

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

ርዕዩከ ማያት
ርዕዩከ ማያት እግዚኦ ፥ ርዕዩከ ማያት ወፈርሁ፣/፪/
ደንገጹ ቀላያተ ማያት፥ ወደምጸ ማያቲሆሙ።/፬/ኧኸ

አቤቱ፥ ውኆች አዩህ፥ ውኆችም አይተውህ ፈሩህ፣/፪/
ጥልቆች ተነዋወጡ፥ ውኆችም ጮኹ።/፬/ኧኸ
              ~ መዝ ፸፯፥፲፮ ~

©በማኅበረ ቅዱሳን መዘምራን

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

ከተራ

ከተራ ማለት ምን ማለት ነው!?
የበዓለ ጥምቀት ዋዜማ የታቦቱ ወደ ወንዝ መውረድና ባሕረ ጥምቀቱን ማዘጋጀት ሃይማኖታዊ ታሪክና ምሳሌ አለው። የቃልኪዳኑን ታቦት አክብሮ መጓዝና ወደ ወንዝ መዉረድ የተጀመረዉ በአሮን ልጅ በአልዓዛር ጊዜ ነዉ።
እያሱ በሙሴ እግር ተተክቶ ሕዝበ እስራኤልን እየመራ ከዮርዳኖስ ወንዝ ሲደርስ ባሕሩ ለሁለት ይከፈልና ወራጅም ይቆም/ይከተር/ነበር። እስራኤል ዘስጋ ወደምድር ርስት ለመግባት ሲሻገሩ ፤ድንካን ጥለዉ የቃል ኪዳኑ ታቦት በድንካኑ ዉስጥ አድርገዉ ለዋዉያኑ በዙርያው ፣ካህናት ደግሞ በዉስጥ ሁነዉ እግዚአብሔርን እያመሰገኑ አድረው በማለዳ ተሻግረዋል (ኢያሱ3፥8-9)። ካህናቱ የቃልኪዳኑን ታቦት አክብረዉ የወንዙን ዳርቻ በረገጡ ጊዜ እንደ ክረምት ማዕበል ይወርድ የነበረው ዉሀ ግራና ቀኝ ተከፍሎ እንደግድግዳ ወደ ላይ ይቆማል ።

➱ሕዝቡ ተሻግሮ እስከሚያበቃ ታቦተ ፅዮንን ያከበሩት ካህናት ከወንዙ መሀል ይቆሙ ነበር። በዚሁ መሰረት "ወተጠምቀ እገሪሆሙ ለካህናት "ወይም የካህናት እግሮቻቸው የዮርዳኖስ ዉሀን በመርገጣቸዉ እንደክረምት ሆኑአቸው ።
በሐዲስ ኪዳን ጌታችን ለመሰረተዉ ሥርዓተ ጥምቀት ምሳሌ ነበረ።ቤተክርስቲያንም የጥምቀት ዋዜማ ከተራ ብላ የጠራቺዉ ከዚህ በመነሳት ነዉ።

➱ጌታችን በተጠመቀ ጊዜ የዮርዳኖስ ወንዝ የላይኛዉ ሸሽቶ ወደላይ ተመልሶ ሽቅብ ፈሷል።የታቹም ወደላይ ሸሽቷል የላይኛዉ ፈሳሽ ተቋርጦ እንደክምር ተቆልሎ ቀርቷል።

ቅዱስ ዳዊት የተመለከተዉ ይሄንኑ ነዉ።ከአዳም ጀምሮ እስከ ክርስቶስ ድረስ በዘር ይወርድ የነበረው ፍዳ መርገም በክርስቶስ ቤዛነት ተቋርጦ ፣የታቹም ፈፅሞ መድረቁ ኃጢአተ አዳም የመጥፋቱ ምሳሌ ነዉ። እስራኤል ፈለገ ዮርዳኖስን ተሻግረው ወደ ኢያሪኮ መሄዳቸው ምእመናን የጥምቀት ከኃጢአት ቁራኝነት ተላቀዉ እግራቸዉ ወደ ልምላሜ ገነት ወደ እረፍት መንግስት ሰማያት አቅንተዉ ለመሄዳቸዉ ምሳሌ ነዉ።
🌿ኢያሱ እንደ ጌታ
🌿እስራኤልን እንደ ምእመናን
🌿ዮርዳኖስን ጥምቀት
🌿ምድረ ርስት ለገነት መንግስተ ሰማያት ምሳሌ ነዉ።
🌿ታቦቱን አክብሮ የሚሄደው ካህን የቅዱስ ዮሐንስ ፣ታቦቱ የጌታችን፣ ባሕረ ጥምቀት የዮርዳኖስ ወንዝ።

ታቦቱን አጅበው የሚሄዱት በዓሉን የሚያከብሩ ምእመናን ወደ ቅዱስ ዮሐንስ እየመጡ የንስሐን ጥምቀት ሲጠመቁ የነበሩት ሰዎች ምሳሌ ናቸውና ።

ታቦታቱ በጥምቀት ዋዜማ ከመንበራቸው ወደ ጥምቀት ባሕር መዉረዳቸዉና በዚያን ማደራቸዉ የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ በእደ ዮሐንስ በፈለገ ዮርዳኖስ ከማታዉ ጀምሮ መዉረድንና ተሰልፎ ተራዉን ሲጠብቅ ማደሩን ያጠይቃል ።

🌿ጥምቀት የሞቱና የትንሳኤዉ ምሳሌ ነዉ። ከኃጥአን ጋር ተቆጥሮ እንዲጠመቅና እንዲሰቀል የተፃፈዉ ቃል ንስሐን ጥምቀትን የማያስፈልገዉ ሲሆን ነገር ግን ፍፁም ኃጥእ መስሎ በዮሐንስ እጅ ጥምቀትን ለመፈፀም በማየ ዮርዳኖስ እግር ተጠመቀ (ኪ.ወ.ክ517)
🌿ጌታችን የተጠመቀው በወርሐ ጥር በእስራኤላውያን ዘንድ የዝናብ ፣የበረዶ ጊዜያት ነዉ። ከወንዝ ዳር ያለመጠለያ መዋልና ማደር አልቻሉም በመሆኑም ከዮሐንስ ለመጠመቅ የሚሄድ ሰዎች ሁሉ በዮርዳኖስ ዙርያ ድንኳናቸው ተክለዉ ያርፉ ነበረ።

🌿በዚህ አንፃር ዛሬም በባሕረ ጥምቀት ዙርያ ድንዃኖች ዳሶች ይጣላሉ ።

👉በሀገራችን በተለያዩ አከባቢዎች በተለይም በአክሱም የንግስተ ሳባ መዋኛን፣ ጎንደር የአፄ ፋሲለደስ መዋኛን፣በላስታ የላሊበላን መዋኛ፣በሸዋ የዘርአ ያዕቆብም ፍርድ መስጫ አደባባይ ፣አርባ አራቱ ታቦት የሚያድርበት የሸንኮራ ሜዳን"ራብቴ ወንዝን"፣በአዲስአበባ ደግም ጃን ሆይ ሜዳ(ጃን ሜዳን)ወዘተ የመሳሰሉትን እንደምሳሌ መጥቀስ ይቻላል ።
👉እነዚህ ቦታዎች ዛሬም ድረስ ተከብረዉ ይገኛሉ። እኛ በዚህ ወቅት ታቦት ይዘን ፣ከወንዝ ወርደን፣ድንኳን ተክለን ማክበራችን ይፈፀማል ።

ከተራ በመባል የሚታወቀው በዋዜማው ሠርገዉ/1981፣8/እንደገለፁት
ከተራ የሚለዉ ቃል ከተረከበ ካለዉ የግእዝ ግስ ነዉ። ከተራ ፍቺዉ ውኃ መከተር ፣ወይም መገደብ ማለት ነዉ።ብለዉ ሲፈቱ ደስታ ተክለወልድ /1962፣694/ ደግሞ የጥምቀት ዋዜማ ጥር 10 የጠራ ወራጅ ውኃ የሚከተርበት ፣ ታቦትና ሰዉ ወደ ዠማ ወንዝ የሚወርድበት ጊዜ ነዉ በማለት ሊቃዉንት ይፈቱታል በየዓመቱ ጥር 10ቀን የምእመናኑን አብዛኛው ስራ ውኃን መከተርና መገደብ መሆኑ ዕለቱ ከተራ የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል ውኃው የሚከተረዉ በማግስት ጥር 11 ቀን የጥምቀት በዓል ስለ ሚከበር ለህዝቡ መጠመቂያ እንዲሆን ነዉ።በየሰበካዉ ቦታ ተለይቶና ተከልሎ ታቦቱ በዳስ ወይም በድንኳን የሚያድርበት የተለያዩ የውኃ ግድብ የሚበጅበት ስፍራ (ባሕረ ጥምቀት ) የታቦት ማደሪያ እየተባለ ይጠራል።ባሕር ፦የውኃ ማሰባሰቢያ (ምእላደ ማይ፣ የውኃ ማከማቻ )ምቁመ ማይ።በሌላ አነጋገር የውኃ አገር ዓለም ማይ ነዉ።

እንኳን አደረሳችሁ!

🟩🟩🟩🟩🟩🟩🟩🟩🟩🟩🟩🟩
🟨🟨🟨🟨🟨🟨🟨🟨🟨🟨🟨🟨
🟥🟥🟥🟥🟥🟥🟥🟥🟥🟥🟥🟥

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

ስጋዋንም ያሳዩት ዘንድ ወደ መቃብሯ ባደረሱት ጊዜ በመቃብር ውስጥ ስጋዋን አላገኙም ደንግጠውም አደነቁ ያን ጊዜ ከመላእክት ጋር ወደ ሰማይ ስታርግ እመቤታችንን እንዳገኛት ቶማስ ነገራቸው። ሐዋርያትም ይህን በሰሙ ጊዜ የእመቤታችንን እርገቷን ስላላዩ እጅግ አዘኑ ስጋዋን በምድር ውስጥ ይተው ዘንድ እንዳልወደደ መንፈስ ቅዱስ አስገነዘባቸው። ከዚህም በኋላ አንድ ጊዜ ደግሞ እርሷን ያሳያቸው ዘንድ እንዳለው ጌታችን ቃል ኪዳን በማድረግ ተስፋ ሰጣቸው እነርሱም እስከ ነሐሴ አስራ ስድስት በተስፋ ኖሩ።

የእመቤታችንም የእድሜዋ ዘመን ስልሳ አራት ዓመት ነው፤ በአባትና እናቷ ቤት ሶስት ዓመት ከሰባት ወር ፣ በቤተ መቅደስም አስራ ሁለት ዓመት ፣ በዮሴፍም ቤት ሰላሳ አራት ዓመት ከሶስት ወር ፣ ከጌታ እርገት በኃላ በወንጌላዊ ዮሀንስ ቤት አስራ አራት ዓመት ነው።

የእመቤታችን ፍቅሯ፤ በረከቷ ፤ አማላጅነቷ በእኛ በምናምን ክርስቲያኖች ላይ እጥፍ ድርብ ሆኖ ይደርብን! የአስራት ሐገሯን ኢትዮጵያን ከፈተና ትጠብቅልን! አሜን!

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

"ጊዮርጊስ በዚያች ቀን"
ጊዮርጊስ በዚያች ቀን ከፈተናው አንፃር
ስለሃይማኖቱ የታየው ምን ነበር

ያመነውን አምላክ አላውቀውም እንዲል
በሥልጣን በገንዘብ እርሱን ለመሸንገል
የዱዲያኖስ ጭፍሮች ነገር ሲያሴሩበት
ልቡናው ምን አለ ሲቀርብ ለመሥዋዕት

ስገድ ባሉት ጊዜ ሰው ለሠራው ምስል
ትዝ አለው ጊዮርጊስ የአምላኩ ሕያው ቃል
ከሠለስቱ ደቂቅ ከዳንኤል ጋር
በእሳት ነበልባል ውስጥ ተአምር ሲሠራ

ቂርቆስ ኢየሉጣን ከመቃጠል ዋጅቶ
ያቀዘቀዘውን ፍሉን ውኃ አጥፍቶ
አስታውሷል ጊዮርጊስ ያንን ኃያል ጌታ
መስቀል መሸከሙን በዚያች ጎሎጎታ

ጴጥሮስና ጳውሎስ አባቶቹን መስሎ
ሞትን አሸነፈ በእምነት ተጋድሎ
እንድንጸና በእምነት ይህችን ዓለም ንቀን
በሰማዕቱ ምልጃ አምላክ ይጠብቀን

©በማኅበረ ቅዱሳን መዘምራን

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

ጥር ፲፰
ዝርወተ አፅሙ ለቅዱስ ጊዮርጊስ


ጥር ዐስራ ስምንት በዚች ቀን የሰማዕታት አለቃ የቅዱስ ጊዮርጊስ አፅሙ ተቃጥሎ ተደቁሶ የተበተነበት ነው፡፡

ይኸውም ሰባ ነገሥታት ማሰቃየት በሰለቻቸው ጊዜ ቅዱስ ጊዮርጊስን እንደ መጭመቂያ ሆኖ ከተሠራ የስቃይ መሣሪያ ላይ አውጥተው ሰውነቱን እንዲሰነጥቁት ንጉሥ ዱድያኖስ አዘዘ፡፡ አንጀቱ ሁሉ ወጥቶ ከምድር ላይ እስኪዘረግፉት ድረስ እንዲህ አደረጉበት፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከስቃይ ብዛት የተነሳ ነፍሱ ከሥጋው ተለየች ሥጋውንም በሙሉ በእሳት አቃጠሉት አመድም ሆነ፡፡

ከሐዲው ንጉሥ ዱዲያኖስ የተቃጠለውን የሥጋውን አመድ አፍሰው በቀፎ አድርገው ይድራስ ወደሚባል ተራራ ወስደው ምዕመናን ራሩን አመዱን እንኳን እንዳያገኙት በነፋስ እንዲዘሩት አዘዘ፡፡ ደብረ ይድራስ ማለት ምድረ በዳ ማለት ነው፡፡ ወታደሮቹም የሥጋውን አመድ በተራራ ላይ ነስንሰው የተመለሱበት፣ የሥጋው አመድ ያረፈበት ዕፅዋት ሁሉ ጊዮርጊስ ጊዮርጊስ ያሉበት፣ ጌታችን ከመላእክት ጋር ተገልጦ አራቱን የምድር ነፋሳትንም የቅዱስ ጊዮርጊስ የሥጋውን ትቢያ እንዲሰበስብ አዝዞ "የኔ ሆይ! የመረጥኩህ ወዳጄ ጊዮርጊስ ከሞት ተነሥ አትፍራ፤ እኔ አዝዤሀለሁና" ሲል ኀያሉን ሰማዕት ቅዱስ ጊዮርጊስ ጠራው። ያን ጊዜ ልዑል ንዑድ ጊዮርጊስም ከጫጉላ ቤት እንደሚወጣ ሙሽራ ምንም ሕማም ሳይኖርበት ተነሣ።

መድኃኒታችንም ባረከው። "አትፍራ፤ ይኸንን ከሀዲ ንጉሥም እስክታሳፍረው ድረስ እኔ አጸናሀለሁ። 'ከእንዲህስ ወዲህ አምላኩ ከእጃችን ሊያድነው አይችልም' እንዳይሉ እነዚህን ከሐድያን ነገሥታትና የረከሱ ጣዖታቸውን ታሳፍራቸው ዘንድ ተነሣና ወደ አገር ውጣ፤ ሰላሜ ለዘለዓለም ከአንተ ጋር ይሁን።" አለው፤ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ይህን ተናግሮ ሳመው። በፍጹም ምስጋናም ወደ ሰማይ ዐረገ። ቅዱስ ጊዮርጊስ ከጌታችን ይህንንም ቃል ኪዳን የተቀበለበት ቀን ነው፡፡

አምላካችን ከሊቀ ሰማዕት ቅዱስ ጊዮርጊስ ረድኤት በረከት ይክፈለን! ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን እንዲሁም ሐገራችን ኢትዮጵያን ሰማዕቱ ከፈተና ይጠብቅልን! አሜን!

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

የቤተክርስቲያንን መብትና ጥቅም ለማስከበር እና የሕግ ተጠያቂነትን ለማረጋገጥ በጥብቅ እየተሰራ ነው።

ጥንታዊት፣ታሪካዊትና ዓለም አቀፋዊት የሆነችው የኢትዮጵያ ኦርቶዶከስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መንፈሳዊ አገልግሎቷን ለማስፋፋት በምታደርጋቸው እንቅስቃሴዎች ሁሉ የሌሎችን መብትና ጥቅም ባለመንካት በትዕግሥትና በማስተዋል የምትጓዝ አገራዊ ኃላፊነት የሚሰማት ሰላምን አብዝታ የምትሰብክ መንፈሳዊት ተቋም መሆኗ ይታወቃል።

ቤተክርስቲያናችን ሥርዓተ አምልኮቷን ለማስፋፋት በተጓዘችባቸው አያሌ ዓመታት አገራችን ኢትዮጵያ የራሷ ፊደላትና የራሷ የቀን አቆጣጠር ባለቤት እንድትሆን ያስቻለች፣በሊቃውንቶቿ የመጠቀ እውቀት አማካኝነት የሥነ ጥበብ፣የሥነ ስዕል፣የዕጽዋትና የጠፈር ምርምርና ጥናቶችን በማከናወን ተጨባጭ ውጤቶችን ለዓለም ያበረከተች ጥንታዊት ተቋም ስለመሆኗም አያሌ ማስረጃዎችን ማቅረብ ይቻላል።

ይሁን እንጂ ይህች ለአገረ መንግስት መመስረትና መጽናት፣ለእውቀት መስፋፋት፣ ለአብሮነት መጎልበት፣ ትውልድን በሥነ ምግባር ቀርጻ ፍቅርና አንድነትን በተግባር የሰበከች እናት ቤተክርስቲያን ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በተለያዩ አካላት መብትና ጥቅሟን የሚነኩ፣በአስተምህሮቿ፣በዕምነቷ፣በንዋያተ ቅድሳቶቿ ላይ መሰረታቸውን ያደረጉና ትዕግስቷን የሚፈታተኑ ክብርና ሉአላዊነቷን የሚዳፈሩ እኩይ የትንኮሳ ተግባራት እየተፈጸመባት ይገኛል።

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

ጥር ፲፭
ቅዱስ ቂርቆስና እናቱ ቅድስት ኢየሉጣ


ጥር ዐሥራ አምስት በዚህች ዕለት የከበረ ሕፃን ቂርቆስ :እናቱ ብፅዕት ኢየሉጣ ዳግመኛ ለከበረ ሕፃን ቂርቆስ ማኅበር የሆኑ ዐሥራ አንድ ሺህ አራት ሰዎች በሰማዕትነት ሞቱ።

በዚያንም ወራት የክብር ባለቤት የሆነ ክርስቶስን በሚያምኑ የክርስቲያን ወገኖች ላይ ታላቅ መከራና ስደት ሆነ። ስሟ ኢየሉጣ የሚባል አንዲት ሴት ነበረች እርሷም ከታናሽነቷ ጀምራ ደግ ናት ስደትም እንደሆነ በሰማች ጊዜ መኰንኑን ከመፍራት የተነሣ ሕፃኗን ይዛ ከሮም ከተማ ተሰዳ የኪልቅያ አውራጃ ከሆነ ከጠርሴስ ደርሳ ከዚያም በሀገሮች ውስጥ እየተዘዋወረች ተቀመጠች።

ወደዚያች አገርም ያ ከእርሱ የሸሸችው መኰንን እለእስክንድሮስ መጣ ጭፍሮቹም ክርስቲያኖችን ፈለጓቸው። ይቺንም ቅድስት ኢየሉጣን አግኝተው ያዝዋትና ወደ መኰንኑ አደረሷት የክርስቲያን ወገንም እንደሆነች ነገሩት።

መኰንኑም ሴትዮ ተናገሪ ከወዴት ሕዝብ ወገን ነሽ ነገድሽ ምንድን ነው ሀገርሽስ ወዴት ነው አላት። የከበረች ኢየሉጣም እንዲህ ብላ መለሰችለት የአንጌቤን ሰው ለሆንኩ ለእኔ ወገኖቼ ለኢቆንዮን አገር አለቆች የሆኑ ኤሳውሮሳውያን ናቸው እኔም በአንተ ምክንያት ሸሽቼ ነበር እነሆ ዛሬ ግን በእጅህ ውስጥ ነኝ አለችው።

መኰንኑም በእጄ ውስጥ እንደተገኘሽ ታውቂያለሽን አላት አሁንም የሚሻልሽን ምረጪ ስምሽንም ተናገሪ እኔንም እሺ በይኝና ለአማልክት ሠዊ የከበረች ኢየሉጣም ለረከሱ አማልክት እኔ አልሰዋም አለችው መኰንኑም ስምሽን ስጪ ተናገሪ አላት እርሷም የኔ ስም ክርስቲያን መባል ነው አለችው። መኰንኑም ይህስ ስንፍና ነው የሚጠቅምሽ አይደለም እንዳትሞቺ ስምሽን ስጪ ተናገሪ አላት። የከበረች ኢየሉጣም የኔ ስም ክርስቲያን መባል እንደሆነ ነገርኩህ ሞት የሚሽረው በሰዎች ዘንድ የምጠራበትን ከፈለግህ ስሜ ኢየሉጣ ነው ብላ መለሰችለት።

መኰንኑም ጽኑ የሆኑ ሥቃዮችን በላይሽ ሳይመጣ ተነሥተሽ መሥዋዕትን ለአማልክት አቅርቢ አላት። የከበረች ኢየሉጣም ዕወነት ነገርን ለመሥራት የምትሻ ከሆነ ዕድሜው ሦስት ዓመት የሆነ ሕፃን ልጅ ይፈልጉ ዘንድ ወደ ሀገሩ መንደር ላክ ወዳንተም ያምጡትና የምንገዛለትንና የምናመልከውን እርሱ ይንገረን አለችው።

ያን ጊዜም የሦስት ዓመት ልጅ ይፈልጉ ዘንድ መኰንኑ ወታደሮችን ላከ የሀገር ሰዎችም ልጆቻቸውን ሠውረዋልና አላገኙም ከዚያም ከከተማው ቅጽር ውጭ በፀሐይ መውጫ ወዳለው በረሀ በኩል ወጡ የቅድስት ኢየሉጣንም ልጅ አገኙት ይህ ሕፃን የስንት ዓመት ልጅ ነው ብለው ስለርሱ ጠየቁ ሰዎችም ይህ ሕፃን የሦስት ዓመት ሲሆን የክርስቲያናዊት መበለት ልጅ ነው አሏቸው።

ያንንም ሕፃን ይዘው ወደ መኰንኑ ወሰዱት መኰንኑም መልኩ የሚያምርና ደም ግባት ያለው እንደሆነ በአየው ጊዜ ደስ የምትል ደስተኛ ሕፃን ሰላምታ ይገባሃል አለው። ሕፃኑም እኔን ደስተኛ ማለትህ መልካም ተናገርክ ላንተ ግን ደስታ የለህም እግዚአብሔር ለዝንጉዎች ደስታ የላቸውም ብሏልና ብሎ መለሰለት መኰንኑም ሕፃኑን ሳልጠይቅህ ይህን ያህል ትመልስልኛለህን አለው። ሕፃኑም ገና ከዚህ የሚበዛ ነገርን እመልስልሃለሁ አለው።

መኰንኑም ሕፃኑን ስምህ ማን ነው አለው ከንጹሕ ዐዘቅትና ከማይለወጥ ከማይጠፋ ውኃ የተገኘ ሕፃን ስሜ ክርስቲያን መባል ነው ብሎ መለሰለት። መኰንኑም ዳግመኛ እንዳትሞት ስምህን ንገረኝ አለው የከበረ ሕፃንም ስሜ ክርስቲያን መባል እንደሆነ ነገርኩህ ሞክሼ ስም የምትሻ ከሆነ እናቴ የሰየመችኝ ቂርቆስ ነው።

መኰንኑም ሕፃን ቂርቆስን እሺ በለኝና ለአማልክት ሠዋ በሥጋህም ስታድግ እሾምሃለሁ በብዙ ወርቅና ብርም አከብርሃለሁ አለው። ሕፃኑም የሰይጣን መልእክተኛ ለዕውነትም ጠላቷ የሆንክ ከእኔ ራቅ አለው።

መኰንኑም ሰምቶ ተቆጣ ደሙ እንደ ውኃ እስከሚፈስ ቆዳውን እንዲጨምቁትና እንዲገፉት አዘዘ። የከበረች ኢየሉጣም የልጅዋን ትዕግሥት ባየች ጊዜ እግዚአብሔርን አመሰገነችው።

ከዚህም በኋላ መኰንኑ ጨውና ሰናፍጭ አምጡ አለ የሁለቱንም አፍንጮቻቸውን ከፍተው ያንን ጨውና ሰናፍጭ እንዲጨምሩባቸው አዘዘ ያን ጊዜ ሕፃኑ ትእዛዝህ ለጕረሮዬ ጣፋጭ ሆነ ከማርና ከስኳርም ለአፌ ጣመኝ ብሎ ጮኸ።

ሁለተኛም መኰንኑ እንዲህ ብሎ አዘዘ የረዘሙና የተሳሉ በእሳትም እንደ ፍም የጋሉ ዐሥራ አራት የብረት ችንካሮች አምጡ ሰባቱን በእናቱ አካላት ውስጥ ጨምሩ በሕፃኑም ሁለት በጆሮዎቹ ሁለት በዐይኖቹ ሁለት በአፉና በአፍንጫው አንድ በልቡ ጨምሩ እንዲህ ሲጨመርበት ጆሮዎቹ እንዲአሩ ዐይኖቹም ይጠፉ ዘንድ አንደበቱም ይቃጠል ዘንድ ወደ ልቡም ጽኑ ሕማም ገብቶ እርሱ ከዚህ ዓለም በሞት እንዲለይ ለእናቱም እንዲሁ አድርጉ ችንካሮችም በቅዱሳኑ በሥጋቸው ሁሉ ተጨመሩ።

የክብር ባለቤት በሆነ በጌታችን ትእዛዝ የብረቶቹ ግለት ጠፍቶ እንደ በረዶ ቀዘቀዘ ጤነኞችም ሆኑ መኰንኑም ወደ ወህኒ ወስዳችሁ በዚያ አሥራችሁ ዝጉባቸው አለ።

ከዚህም በኋላ መኰንኑ የሥቃይ መሣሪያ ይሠራ ዘንድ አንዳዝዘው ብረትን የሚያቀልጥ ሰው አምጡልኝ አለ። በአመጡለትም ጊዜ ሰይጣኑ ወደ መኰንኑ ልብ ገብቶ አንደበቱን ዘጋውና መናገር ተሳነው ሕፃኑ ፈጥኖ አክሊልን ለመቀበል እንደሚተጋ ሰይጣን ስለ አወቀ ስለዚህ ዘጋው።

ከዚህም በኋላ ሕፃኑ ሠራተኛውን ጠርቶ እኔንና እናቴን የሚያሠቃዩበትን የሥቃይ መሣሪያ መሥራት ትችላለህን ይህ መኰንን ግን ምንም የሚያውቀው ነገር የለም አለው ሠራተኛውም እንደምትሻው በል ንገረኝ እንደምታዝዘኝ እኔ መሥራት እችላለሁ አለው።

ሕፃን ቂርቆስም ሊአዝዝ ጀመረ እንዲህም አለ ሁለት መላጫዎች ስፋታቸው አራት ክንድ የሆነ ለእኔና ለእናቴ ሥራ። ዳግመኛም የሚያስጨንቅ ራስን የሚመታና የሚሰብር አንገትንም የሚያሥር የሚዝቅም ሹካ ዐይንንም የሚያወልቅ አካልንም የሚበሳሳ አፍንጫንም የሚያጣምምና የሚሰብር ጆሮንም የሚልጥ ሕዋሳትን የሚፈታና የሚለያይ እንደ ልጓም ሁኖ ምላስን የሚቆርጥ በሰውነትም ውስጥ ገብቶ የሚንቀሳቀስ ቆላፋ ጉጠትን ጐኖችንም የሚፍቅና የሚቆለምም አስጨናቂ የሆነ ጉልበቶችንና ጭኖችን የሚሰብር ጅማቶችንም የሚቆራርጥ ሥሮችንም የሚመዝ በዚችም አስጨናቂ መሣሪያ ጅማቶችን የሚታታ አድርግ።

ዳግመኛም በላም አምሳል ሰፊ መቀመጫ ከናስ ሥራ ሦስት ቀዳዳዎችንም በዚያ መቀመጫ ውስጥ ቅደድ። በቁመቴም ልክ ሦስት ችንካሮችን ሥራ የችንካሮቹንም ራስ ከናስ አድርገህ በውስጡ ከሚጠሩት ዘንድ ፈጽሞ የማይለይ ልዩ ሦስት ብለህ ጻፍ።

ዳግመኛም ጠምዝዞ ወደ ላይ የሚያወጣ ሁለት መሣሪያ ሁለት መጋዞችን ሁለት የብረት ምጣዶችን ሥራ አሁንም አንድ ታላቅ ጋን ሠርተህ በውስጡ አንገትን የሚጠመዝዝና የሚሠነጥቅ ተሽከርካሪ መሣሪያ አድርግ።

በውስጥ የተሸሸገ የሆድ ዕቃን የሚመረምር እጅን ከብረት ሥራ እኔ የጻዕር ስቃይን የምሠቃይበት ይህ ነው አለ። ብረት ሠሪውም ሰምቶ እጅግ አደነቀ የሚረዱትንም ከሀገር ውስጥ መቶ ሠራተኞችን ሰብስቦ መሥራት ጀመረ በአርባ ቀንም ጨረሰ።

ከዚህም በኋላ መኰንኑ እለእስክንድሮስ ቂርቆስንና እናቱን ወደ አደባባይ ያመጡአቸው ዘንድ አዘዘ ያን ጊዜ አንደበቱ ተፈትቶ ነበርና እንዲህም አለ ሕፃኑንና እናቱን ከቆዳቸው ጋር ራሳቸውን ላጩአቸውና በላያቸው የእሳት ፍሞችን ጨምሩ እርር ብለው እንዲቃጠሉ ዳግመኛም አራት ችንካሮችን ከትከሻዎቹ እስከ ተረከዙ ድረስ እንዲተክሉበት አዘዘ የእግዚአብሔርም መልአክ መጥቶ ሥቃዮችን ከርሱ አራቀ።

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

"እንዘ ስውር"
እንዘ ስውር እምኔነ ይእዜሰ ክሱተ ኮነ(፪)
ተአምረ ወመንክረ ገብረ መድኃኒ በቃና ዘገሊላ ከብካብ ኮነ ማየ ረሰየ ወይነ(፪)

©በማኅበረ ቅዱሳን መዘምራን

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

በአጠቃላይም የመጽሀፍትን ትርጉምና የአነጋገር ዘይቤ ካለማወቅ የሚመጣ ስህተት ከመሆኑም ባሻገር ለገዛ ጥፋት መጻሕፍትን የሚያጣምሙ ስለመኖራቸው፤ ሲናገር “ያልተማሩትና የማይጸኑትም ሰዎች ሌሎችን መጻሕፍት እንደሚያጣምሙ እነዚህን ደግሞ ለገዛ ጥፋታቸው ያጣምማሉ”። ፪ኛ ጴጥ. ፫፥፲፮
ከዚያም በውሃ የተሞሉ ጋኖች ወደ ወይን ተለወጡ፡፡ ይህ ተአምር በዮሐንስ ወንጌል ከተጻፉት አምላክነቱን ከገለጸባቸው ሰባት ምልክቶች (ተአምራት) ውስጥ ሲሆን በፍጥረታት ላይ ስልጣን እንዳለው ያሳየበትም ነበር፡፡ መርከቢቱን ከማእበል መናወጽ ፤ደቀመዛሙርቱን ከመጨነቅ አድኖ ማእበሉን ጸጥ ባደረገ ጊዜ ደቀመዛሙርቱ ፍጥረታት ለእርሱ መታዘዙን ሲያዩ፤”ነፋሳትና ባሕርስ ስንኳ የሚታዘዙለት፥ ይህ እንዴት ያለ ሰው ነው? እያሉ ተደነቁ “። ይላል፡፡ ከዚህም ባሻገር እርሱ ሰው ሆኖ ተገልጦ የሰውን አልጫ ማንነት በእርሱ የድህነት ሥራ ለወጠ፡፡ የብዙዎቻችንን የትላንት ማንነት በኃያአት ያሳለፍነውን ጊዜ ውሃችንን ለውጦት ነው በቤቱ እንድንኖር ያደረገን፡፡ ኢሱስም ቀድተው ለአሳዳሪው እንዲሰጡ አዘዘ፡፡

በዚህመ ዶኪማስ ተደነቀ በደስታ ተሞላ ታዳሚዎቹም የተለወጠው ወይን ጠጅ ከመጀመሪያው በእጅጉ በመብለጡ ተገርመው “ሰው ሁሉ አስቀድሞ መልካሙን የወይን ጠጅ ያቀርባል፥ ከሰከሩም በኋላ መናኛውን፤ አንተስ መልካሙን የወይን ጠጅ እስከ አሁን አቆይተሃል አለው”። ሰውም በአግዚአብሄር ሲለወጥ እንዲሁ ነው። በኃጢአት ያሳለፈው ህይወት መራራ ነው። በእግዚአብሔር መደገፍ ሲጀምር፤ ማመን ሲጀምር፤ የመረረ ሀይወቱ ተለውጦ ለሌሎች መጣፈጥ ይጀምራል፡፡ ሰው የእግዚአብሔርን ፍቅር ካልቀመሰ በቀር ሊያውቀው አይችልም፤ እርሱን ለማወቅ ቃሉን መጠጣት፤ ስጋውና ደሙን መንፈሳዊውን ምግብ መመገብ ይኖርበታል፡፡ ይህ ነው የክርስቲያኖች እምነት መንፈሳዊ ህይወት የሚቀይረው፤ ለመንግስቱ የሚያበቃው፡፡ ደቀመዛሙርቱ ይህንን ቃና ወይን መለወጥ ባዩና በቀመሱ ግዜ እምነታቸው ጨመረ “ኢየሱስ ይህን የምልክቶች መጀመሪያ በገሊላ ቃና አደረገ፤ ክብሩንም ገለጠ፥ ደቀ መዛሙርቱም በእርሱ አመኑ” ይለናል፡፡ በአጠቃላይ የቃና ዘገሊላ በዓል ብዙ የምንማርበት ሲሆን የጌታ ህይወት ለዋጭነት፤ የድንግል ማርያምን አማላጅነት ተገልጦ፤ ያየንበት መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትምህርት ነው፡፡

የአምላካችን ቸርነት የድንግል ማርያም አማላጅነት አይለየን፡፡

ወስብሐት ለእግዚአብሔር

©መ/ር ንዋይ ካሳሁን

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

መጽዐ ቃል እም ደመና ዘይብል ዘይብል፤(፪)
ዝንቱ ውእቱ ወልድየ ዘአፈቅር።(፪)

መጣ ቃል ከደመና እንደዚህ የሚል፤(፪)
የምወደው የማፈቅረው ልጄ ይኽ ነው።(፪)

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

"መኑ ይወርድ"
መኑ ይወርድ ውስተ ቀላይ{፪}
አሐዱ እምነ ሠለስቱ ወልድ/ክርስቶስ ውእቱ{፪}

ዳዊት በመዝሙሩ የተነበየለት
ውኆች አይተው ደንግጠው የሸሹት
ኮረብቶች እንደእንቦሳ ዘለው ያከበሩት
በውኃ የተጠመቀው እርሱ(፪) ነው መድኃኒት

በልዩነት መንፈስ ታጥሮ ለነበረው
ህዝብና አህዛብ ተብሎ ለተለየው
በዮርዳኖስ ተጠምቆ አንድ ያደረገን
ኢየሱስ ክርስቶስ እርሱ እግዚአብሔር ነው

በአዳም እና ሄዋን የነበረውን እዳ
ደምስሶ ሊያድነን ከዘለዓለም ፍዳ
በሰውነቱ ረቅቆ በአምላክነቱ የሻረው
ወልደ እግዚአብሔር ወልደ(፪) ማርያም ነው

ጌታችን ሲጠመቀ በዮሐንስ እጅ
ምሥጢር ተገለጠ የድኅነት አዋጅ
መንፈስ ቅዱስ በእርግብ አብም በደመና
ተገልጠው አሳዩ ወልድ ወልደ አምላክ ነውና

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

ጥር ፲፩
ጥምቀተ ኢየሱስ


ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሰላሳ ዓመት ሲመላው ዮሐንስ ሰላሳ ዓመት ከስድስት ወር ሲሆነው በዮሐንስ እጅ ሊጠመቅ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ ሄደ፤
🌿 ለምን ወደዮሐንስ ሄደ ዮሐንስ ወደ ኢየሱስ ለምን አልመጣም ቢሉ ባሪያ በጌታው እጅ ይጠመቃል እንጂ ጌታ በባሪያው እጅ ይጠመቃልን ቢሉ ?

1. ለትህትና

ጌታችን ከሰማየ ሰማያት ወርዶ ሰው የሆነው ለትህትና ነው እንጂ ለልእልና አይደለምና

2. አብነት ለመሆን

ጌታችን ዮሐንስን መጥተህ አጥምቀኝ ቢለው ዛሬ ነገሥታት መኳንንት ሀብታሞች መጥታችሁ አጥምቁን ይሉ ነበርና ሂዳችው ተጠመቁ ለማለት።

🌿 ከሌሎች ወንዞች ለይቶ ጥምቀቱን ለምን በዮርዳኖስ አደረገው ቢሉ?

1. ትንቢቱን ለመፈፀም

ዮርዳኖስ ወደሃላው ተመለሰ ብሎ መዝሙረኛው ዳዊት ስለ ዮርዳኖስ ትንቢት ተናግሮ ነበርና ለመፈፀም ነው።

2. የአዳምና የሄዋን የእዳ ደብዳቤአቸውን ለመደምሰስ

ከእለታት አንድ ቀን ዲያብሎስ በአዳምና በሔዋን ላይ የጨለማ መጋረጃ ጋርዶ ስቃይ አጽንቶ ስመ ግብርናታችውን ጽፋችሁ ብትሰጡኝ ስቃይ አቀልላችኋለሁ ብሏቸው ስቃዩን ያቀለለልን መስሏቸው።

አዳም የዲያብሎስ ባሪያ ነው ሔዋን የዲያብሎስ ባሪያ ናት ብለው ጽፈው ሰጡት።

ያን ተቀብሎ በሁለት እብነ ሩካም ጽፎ አንዱን ሲኦል አንዱን ዮርዳኖስ ጥሎት ነበርና በዮርዳኖስ የተጣለውን በጥምቀቱ ለመደምሰስ ዮርዳኖስን መርጧል።

ሲጠመቅም እንደአምላክነቱ አቅልጦ እንደ ሰውነቱ ረግጦ የእዳ ደብዳቤአቸውን አጥፍቶላቸዋል ።

በሲኦል የጣለውን በዕለተ ዓርብ በአካለ ነፍስ ወርዶ ደምስሶታል።

ጌታችን ዮሐንስን "አጥምቀኝ" ሲለው

"ሌላውን
በአንተ ስም
በአብ ስም
በመንፈስ ቅዱስ ስም አጠምቃለው አንተን በማን ስም ላጥምቅህ?" አለው።

"የቡሩክ አብ ልጁ ብርሃንን የምትገልጥ ይቅር በለን የዓለምን ኀጢአት የሚያስወግደው የእግዚአብሔር በግ እነሆ ክህነትህ እንደ መልከጼዴቅ ክህነት ለዘለአለም ነው" እያልክ አጥምቀኝ አለው።

+የአብ ልጅ መሆኑን

+ብርሃን የሚገልጥ መሆኑን

+ይቅር ባይ መሆኑን

+የዓለምን ኀጢአት የሚያስወግድ የእግዚአብሔር በግ መሆኑን

+ክህነቱ ዘለዓለማዊ መሆኑን እየመሰከረ አጥምቆታል

🌿ጥምቀቱን በውሃ ያደረገው ስለምን ነው ቢሉ?

+ውሃ በዙፋን ካለ ንጉሥ በአደባባይ እስካለ ጽኑስ ለሁሉ የሚገኝ ነው።

+ውሃ ጽንፍ እስከ ጽንፍ ይፈሳል ጥምቀትም ጽንፍ እስከ ጽንፍ ይደርሳልና

+ውሃ ከእድፍ ያነጻል ጥምቀትም ከኀጢአት ያነጻልና

+ውሃ የወሰደው ፍለጋ የለውም በጥምቀትም የተሰረየ ኀጢአት በፍዳ አያስዝምና

+ውሃ መልክ ያሳያል መልክ ያለመልማል

ጥምቀትም መልክአ ነፍስ ያሳያል መልክአ ነፍስ ያለመልማልና

+በውሃ የታጠበ ልብስ እየቀደም እየነፃ ኃይል ግዘፍ እየነሳ ይሄዳል

ምእመናንም ተጠምቀው ገድል ትሩፋት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየሰሩ እየጨመሩ ይሄዳሉና

+ርብቃ ለይስሐቅ የታጨችው ውሃ ስትቀዳ ነው

ምእመናንም ለክርስቶስ ሙሽራነት የሚታጩት በውሃ ተጠምቀው ነውና

+በውሃ ቀድሞ ሰብአ ትካት ሰብኣ ግብጽ ጠፍተው ነበርና ውሃ ለመአት እንጂ ለምሕረት አልተፈጠረም ብለውት ነበርና ለመአትም ለምሕረትም እንደተፈጠረ ለመግለጽ ከሁሉም ውሃን መርጦ በውሃ ተጠመቀ።

በመአር በወተት በወይን በዘይት ተጠምቆ ቢሆን ኑሮ ሀብታሞች እንጂ ድሃዎች አያገኙትምና ሁሉ በሚያገኘው በውሃ ተጠመቀ።

ሲጠመቅም መንፈስ ቅዱስ በርግብ አምሳል ወርዷል።

🌿መንፈስቅዱስን ስለምን ርግብ አለው ቢሉ?

+ርግብ ሀዳጊተ በቀል ናት መንፈስ ቅዱስም ሀዳጌ በቀል ነውና

+ርግብ በኖህ ጊዜ ኀፀ ማየ አይኅ ነትገ ማየ አይኅ ስትል ቆጽለ እፀ ዘይት ይዛ ተገኝታለች መንፈስ ቅዱስም ተስፋ መስቀልን ያበስራልና

+ርግብ ክንፋን ቢመቷት እንቁላልዋን ቢሰብሩባት ቤታን ካላፈረሱባት ቦተዋን አትለቅም መንፈስ ቅዱስም ኀጢአት ቢሰሩም ለንስሓ ይጠራል እንጂ ፈፅሞ ካልካዱት አይርቅምና ።

🌿ጥምቀቱን በመአልት ያላደረገው በሌሊት ያደረገው ስለምነው ቢሉ?

በመአልት አድርጎት ቢሆን መንፈስ ቅዱስ በቁሙ ርግብ ነው ብለው በተጠራጠሩ ነበና

🌿አሁንስ ርግብ አለመሆኑ በምን ይታወቃል ቢሉ ?
ጌታችን የተጠመቀ ከሌሊቱ አስር ሰአት ነው ፤በአስር ሰአት ወፎች ርግቦች አይበሩም ተሀዋስያን ከቦታቸው አይንቀሳቀሱምና በዚህ ርግብ አለመሆኑ ይታወቃል።

መንፈስ ቅዱስ የወረደው ከውሀው ከወጣ ከዮሀንስ ከተለየ በሇላ ነው፤ ከውሃው ሳለ ወርዶ ቢሆን ለቀድሶተ ማያት የወረደ ነው ባሉ ነበርና።

ከዮሐንስ ጋራም ሳለ ቢሆን ስለ ክብረ ዮሐንስ የወረደ ነው ባሉ ነበርና ።

ሲወርድም ረቦ ወርዷልቢሉ
አብ ምሉእ ነው ፤አንተም ምሉእ ነህ
እኔም ምሉእ ነኝ ሲል ነው።

አንድም አሰይፎ ወርዷል ቢሉ፤ የብሉየ መዋእል የአብሕይወት ነኝ፤የብሉየ መዋእል የአንተም ህይወት ነኝ።

እኔም ብሉየ መዋእል ሕይወት ነኝ ሲል ነው።
ወርዶም ራሱን ቆንጠጥ አድርጎ ይዞታል

አብ አኃዜ ዓለም ነው
አንተም አኀዜ ዓለም ነህ
እኔም አኀዜ ዓለም ነኝ ሲል ነው።

መውረዱ ለአብነት ነው

እናንተም ስትጠመቁ እንደዚህ እወርድላችዋለው ሲል ነው።

ከዚህ በሃላ አብ በደመና ሁኖ የምወደው ልጄ ይህ ነው እርሱን ስሙት ብሎ ልጁ መሆኑን መስክሯል።

🌿ጌታችን ሲጠመቅ አንድነት ሶስትነት ተገልፇል

ወልድ በመጠመቅ
መንፈስ ቅዱስ በርግብ አምሳል በመውረድ
አብ በደመና ሁኖ በመመስከር

አንድ ሲሆኑ ሶስት ሶስት ሲሆኑ አንድ መሆናቸው ተገልጧል ማቴ 3÷13-17።

+++መልካም በዓል+++

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

"እግዚኡ መርሐ"
እግዚኡ መርሐ ዮርዳኖስ አብፅሃ /፪/
ወበህየ ዮሐንስ ወበሕየ ፍፁመ ተፈሥሐ /፪/

ጌታውን መራና ዮርዳኖስ አደረሰው /፪/
በዚህም ዮሐንስ በዚህም ፈጽሞ ደስ አለው /፪/

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

"ቅዱስ እግዚአብሔር"
ቅዱስ እግዚአብሔር ኃያል ሕያው ዘኢይመውት/፪/
ዘተወልደ እማርያም ወተጠምቀ በዮርዳኖስ
ዘተወልደ እማርያም ተሰሀለነ/፪/

ቅዱስ እግዚአብሔር ኃያል ሕያው የማይሞት/፪/
ከድንግል የተወለድክ በዮርዳኖስ የተጠመቅክ
ከድንግል የተወለድክ ይቅር በለን/፪/

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…
Subscribe to a channel