በዚህ Channel ውስጥ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንን ዶግማ ፤ ቀኖና እና ትውፊት የጠበቁ ትምህርቶች ይተላለፉበታል፡፡ ለአስተያየት: ጥቆማና ጥያቄ በዚህ ያግኙን ☞ @Ethiopian_Orthodox_bot Buy ads: https://telega.io/c/Ethiopian_Orthodox
"የምስራች ደስ ይበለን"
የምስራች ደስ ይበለን (፪)
የዓለም መድኃኒት ተወለደልን
ምስራች ደስ ይበለን
ኢየሱስ የዓለም ቤዛ (፪)
የዓለም ቤዛ (፫) ለኛ ተወለደልን
አዝ = = = = =
ንጉሥ ሄሮድስ ይህን ሲሰማ (፪)
ፈልጋችሁ አምጡት በቀን በጨለማ (፪)
አዝ = = = = =
ሰብዐ ሰገል እንደታዘዙት (፪)
በኮከብ ተመርተው ህፃኑን አገኙት (፪)
አዝ = = = = =
ሰገዱለት ከመሬት ወድቀው (፪)
ወርቅ እጣን ከርቤውን በረከቱን ሰጥተው (፪)
አዝ = = = = =
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
ታኅሣሥ ፳፱
ልደተ ክርስቶስ
ታኅሣሥ ሃያ ዘጠኝ በዚህች ቀን የከበረና የተመሰገነ ታላቅ የልደት በዓል ሆነ የጌታችንና የመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከእመቤታችን ከከበረች ድንግል ማርያም የተወለደባት ዕለት ከበዓላት ሁሉ ተለይታ ከፍ ከፍ ያለች ናት።
የቤተ ክርስቲያን መምህራን አባቶቻችን የከበረ የልደትን በዓል በሁለት ቀኖች ያከብሩ ዘንድ በምክራቸው ተስማሙ ከወደኋላ ባለ በሃያ ስምንት ሌሊቱ የልደት በዓል ነው በሃያ ዘጠኝ መዓልቱ ጳጉሜን ስድስት በሆነ ጊዜ በዚያች ዓመት የልደት በዓል በሃያ ስምንት በመዓልት ይከበራል። ጳጉሜን አምስት ከሆነ ግን በሃያ ዘጠኝ ይሆናል ስለዚህ የበዓላት ሁሉ ራስ የሆነ የከበረ የልደት በዓል በሁለቱ ቀኖች እንዲከበር አዘዙ ወሠኑ።
የበዓላት ራስ ስለሆነ ስለ ከበረ የልደት በዓል የከበረ ወንጌል እንዲህ አለ። በንጉሡ በኄሮድስ ዘመን በይሁዳ ዕፃ በቤተልሔም ጌታ ኢየሱስ በተወለደ ጊዜ እነሆ የፍልስፍና ሰዎች ከምሥራቅ መጥተው ወደ ኢየሩሳሌም ደረሱ። ኮከቡን በምሥራቅ አይተን እንሰግድለት ዘንድ መጥተናልና የተወለደው የአይሁድ ንጉሥ ወዴት ነው እያሉ።
እሊህ ፈላስፎች ከበለዓም ወገን ናቸው እነርሱም በከዋክብት የሚፈላሰፉ ናቸው በመጽሐፋቸው በበለዓም መጽሐፍም የአይሁድ ንጉሥ ሊወለድ እንዳለው ተጽፎአል እርሱ በለዓም ከያዕቆብ ኮከብ ይወጣል ከእስራኤልም ንጉሥ ብሎ ነበርና።
ይቅር ባይ እግዚአብሔርም በረቀቀ ጥበቡ አለበማቸው በሚያምኑበትም ሳባቸው እነርሱ ከዋክብትን በመጠባበቅ የሚፈላሰፉ ናቸውና ይህንንም ኮከብ ገለጠላቸው በአዩትም ጊዜ ደስ አላቸው መልኩ በብዙ አይነት ልውጥ ነውና። ሕፃን የታቀፈች ድንግል ብላቴናን ይመስላል እርሱም በቀን ይጓዛል በሌሊትም ይሠወራል ከሰውም ሲገናኙ ይሠወርና ሲቆሙ በሌላ አንጻር ይገለጥላቸዋል።
እነርሱም ወደ ኢየሩሳሌም ሲደርሱ ያ ኮከብ ተሠወራቸው እጅግ አዘኑ የሚያደርጉትንም አላወቁም ከዚህም በኋላ ወደ ኢየሩሳሌም ከተማ ገብተው ስለተወለደው ንጉሥ ጠየቁ። የእሊህም ሰዎች ቊጥራቸው ሠላሳ ሽህ ነው ነገሥታቱ ሦስት ናቸው ለየእንዳንዱ ንጉሥ ዐሥር አሥር ሽህ ሠራዊት አለው።
ንጉሡ ኄሮድስም በሰማ ጊዜ ደነገጠ ኢየሩሳሌምም በመላዋ ከእርሱ ጋር ደነገጠች። የካህናት አለቆችና የሕዝቡን ጸሐፊዎች ሁሉ ሰብስቦ ክርስቶስ በየት ይወለዳል ብሎ ጠየቃቸው። በይሁዳ ዕፃ በቤተልሔም ነው አሉት በነቢይ እንዲህ ተብሎ ተጽፏልና።
የኤፍራታ ዕፃ ቤተልሔም አንቺም ከይሁዳ ነገሥታት አታንሺም ወገኖቼ እስራኤልን የሚጠብቅ ንጉሥ ካንቺ ይወለዳልና። ከዚህም በኋላ ኄሮድስ ሰብአ ሰገልን በጭልታ ጠርቶ ኮከቡ የታየበትን ዘመን ከነሱ ተረዳ።
ሒዳችሁ የዚያን ሕፃን ነገር እርግጡን መርምሩ ያገኛችሁትም እንደሆነ እኔም መጥቼ እሰግድለት ዘንድ በኔ በኩል ተመልሳችሁ ንገሩኝ ብሎ ወደ ቤተልሔም ሰደዳቸው። የነገራቸውንም ሰምተው ከንጉሡ ሔዱ እነሆ በምሥራቅ ያዩት ከከብ ወደ ቤተልሔም እስኪያደርሳቸው ይመራቸው ነበር ሕፃኑ ካለበትም ዋሻ ላይ ደርሶ ቆመ።
ኮከቡንም ባዩ ጊዜ እጅግ ደስ አላቸው ወደ ቤትም በገቡ ጊዜ ሕፃኑን ከእናቱ ከድንግል ማርያም ጋር አገኙት ወድቀውም ሰገዱለት ሣጥናቸውንም ከፍተው ወርቅ ከርቤ ዕጣን እጅ መንሻ አቀረቡለት።
በእግዚአብሔርም ፈቃድ ዮሴፍ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሕፃኑ ጌታ ኢየሱስም በዚያች ዕለት ወደ ቤተልሔም መጡ ስለዚህም ሰብአ ሰገል አገኙአቸው የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ያለ ናዝሬት በሌላ ቦታ አላደገምና ከተወለደም ዕድሜው ሁለት ዓመት ሆኖት ነበር።
አምላክ ነውና ስለ መንግሥቱ ወርቅን ገበሩለት ክህነትም ገንዘቡ ነውና ዕጣንን ገብሩለት ማሕየዊ ለሆነ ሞቱ ምልክትም ከርቤን ገበሩለት። ወደ ኄሮድስም እንዳይመለሱ በሕልም ነገራቸው በሌላ መንገድም ወደ አገራቸው ተመልሰው ገቡ። አምላክ በሥጋ ስለመገለጡ ዓዋጅ ነጋሪዎችና ሰባኪዎች ሆኑ።
ይችም ዕለት ነቢዩ ኢሳይያስ ትንቢት ስለርሷ የተናገረላት ናት እንዲህ ብሎ እነሆ ድንግል ፀንሳ ወንድ ልጅን ትወልዳለች ስሙንም ዐማኑኤል ትለዋለች ትርጓሜውም እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ማለት ነው።
ስለዚችም የከበረች ድንግል ነቢይ ሕዝቅኤል እንዲህ ብሎ ትንቢት ተናገረ እግዚአብሔርም አለኝ ይህች በር ተዘግታ ትኖራለች አትከፈትም የሚገባበትም የለም የእስራኤል ፈጣሪ እግዚአብሔር እንደተዘጋች ይገባባታልና ተዘግታ ትኑር አለ።
ነቢዩ ዳንኤልም አለ ሌሊት በራእይ አየሁ እነሆ ታላቁ እንደ ሰው ልጅ በሰማይ ደመና መጣ ዘመኑን ወደ ሚያስረጅ ደረሰ ከፊቱም አቀረቡት የዘላለም አገዛዝ ጌትነት መንግሥት ተሰጠው ሕዝቡና አሕዛቡ ሁሉ መንደር መንድረው የሚኖሩትና ነገዱም ነገሥታቱም ሁሉ ይገዙለታል አገዛዙም የዘላለም አገዛዝ ነው መንግሥቱም የማያልፍ የማይጠፋ ነው።
ዳግመኛም ኢሳይያስ እግዚአብሔር እንደ እኔ የሥጋ መጋረጃ በመጋረድ ተገለጸልኝ አለ። አሁንም ደግሞ አዲስ ሰማይ አዲስ ምድር እሠራ ዘንድ አለኝ አለ ሁለተኛም ከዕሴይ ሥር በትር ትወጣለች ከእርሷም ጽጌ አበባ ይወጣል አለ። ዳግመኛም ሕፃን ተወልዶልናልና ወንድ ልጅም ተሰጥቶልናልና ይኸውም ሥልጣን በጫንቃው የሆነ ክርስቶስ ነው። ስሙም ድንቅ መካር የዘላዓለም አባት የሰላም አለቃ ይባላል አለ።
ኤርምያስም አለ እግዚአብሔር እንዲህ አለ በዚያን ወራት ለዳዊት ብርሃንን አወጣለሁ በምድርም የቀና ፍርድን ያደርጋል እግዚአብሔርም ያመኑበትን ያድናቸዋል።
ኤልሳዕም እንዲህ አለ።እ ግዚአብሔር ከሰማይ ይወርዳል በእስራኤል ልጆች አደባባይም በመመላለስ ለሕዝቡ ዕውነትን ያስተምራቸዋል ከአብርሃም ልጅነት ልዩ ከሆኑ ወገኖች በቀር አሕዛብ ሁሉ ይታዘዙለታል። ናሆም ነቢይም እንዲህ አለ። እግዚአብሔር በእኔ አርአያ ይመጣል ልብሱም እንደልብሴ ነው።
ነቢዩ ኢዩኤልም እንዲህ ተናገረ የእግዚአብሔር ዙፋን የሆነች ብላቴና ድንግልን አየሁ እርሷም እንደ እሳት ያልባት ነበር ስለርሷም ይቺ ማን ናት ብዬ ኪሩብን ጠየቅሁት ከአዳም ልጆች የተመረጠች የእግዚአብሔር ዙፋን ይህች ድንግል ናት በርሷም የተጐሳቈሉ አሕዛብ ይድናሉ ለአመነባትም ረድኤትና መጠጊያ ናት።
ዳዊትም በመዝሙሩ እንዲህ አለ እግዚአብሔር አንተ ልጄ ነህ ዛሬም በተዋሕዶ ወለድኩህ አለኝ። ለምነኝ አሕዛብን ርስት አድርጌ እሰጥሃለሁ ግዛትህም በመላው ዓለም ነው። ዳግመኛም አብ አለ ቀዳማዊ ወልድ በኃይል ቀን ካንተ ጋራ ሳለሁ ከአጥቢያ ኮከብ በፊት ከሆድ ወለድኩህ እንደ መልከጼዴቅ ሥርዓት አንተ የዓለሙ አገልጋይ ካህን ነህ ብሎ እግዚአብሔር ማለ ከማለም አይጸጸትም።
ቤዛ ይስሐቅ በግዕ ከኅቱም ዕፀ ሳቤቅ እንደተገኘ ለእስራኤልም በበረሀ ውስጥ ከኅቱም አለት ውኃ እንደ ፈለቀ የደነቀች የአሮን በትርም እንደለመለመችና እንደ አፈራች። በሶምሶንም እጅ ውስጥ ከአህያ መንጋጋ ዐጥንት ውኃ እንደ ፈሰሰ።
እንዲሁ የጌታችን ልደት በኅቱም ድንግልና ሆነ። በዕፀ ጳጦስ ውስጥ እሳት እንደ ነደደች ዕፂቱም እንዳልተቃጠለች እንዲሁ የመለኮቱ እሳት ድንግልን አላቃጠላትም።
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
እንኳን አደረሳችሁ!
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
ጌታችን ስለተወለደባት ምሽት ቅዱስ ኤፍሬም አንዲህ አለ.....
‹‹ይህች ምሽት ንጹሕ የሆነውና እኛን ሊያነጻን የመጣው (አምላክ) የተገለጠባት ንጽሕት ምሽት ናት፡፡ ጆሮአችን ንጹሕ ይሁን፤ ዓይኖቻችንም ወደ ንጹሕ ነገር ይመልከቱ፤ የልባችን ስሜት ቅዱስ ይሁን! ንግግራችንም አክብሮትን ይሞላ!
ይህች ምሽት የዕርቅ ምሽት ናት፤ ስለዚህ ማንም ሰው ወንድሙን ተቆጥቶ እንዳያስቀይም! ይህች ምሽት ለዓለም ሁሉ ሰላምን ያስገኘች ምሽት ስለሆነች ማንም ሰው አይሸበርባት፡፡ ይህች ምሽት የደግነት ምሽት ስለሆነች ማንም ሰው ክፉ አይሁን! ይህች ምሽት የትሕትና ምሽት ናትና ማንም ሰው እንዳይታበይባት! ይህች ምሽት የደስታችን ቀን ስለሆነች የበደሉንን አንበቀልባት! የበጎ ፈቃድ ቀን ናትና የጭካኔ ቀን አናድርጋት! የጸጥታ ቀን ናትና በቁጣ የምንነድባት ቀን አናድርጋት!
ዛሬ እግዚአብሔር ወደ ኃጢአተኞች የመጣበት ቀን ነው ፤ ስለዚህ ጻድቅ ሰው በኃጢአተኞች ላይ አይኩራባቸው! ዛሬ እጅግ ባለጠጋ የሆነው አምላክ ስለ እኛ ደሃ የሆነበት ቀን ነው፤ ስለዚህ ሀብታም ሰው ድሆችን ወደ ገበታው ይጥራቸው፡፡ ዛሬ ያልጠየቅነውን ሥጦታ የተቀበልንበት ዕለት ነው፡፡ ስለዚህ እጆቻቸውን ዘርግተው እየጮኹ ለሚለምኑን ሰዎች የእርዳታ እጃችንን እንዘርጋ!
የዛሬዋ ዕለት ለጸሎቶቻችን የሰማያትን በር ከፍታልናለች ፤ እኛም ይቅርታን ለሚጠይቁን ሰዎች በራችንን እንክፈት! ዛሬ አምላክ የሰውነትን ማኅተም በራሱ ላይ አተመ ፤ ሰውም የአምላክነትን ማኅተም ተጎናጸፈ!››
እንኳን ለአምላካችን ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ!
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርክ፤
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡
በሀገራችን በኢትዮጵያ በገጠርና በከተማ የምትኖሩ፤
ከሀገር ውጭ በተለያዩ አህጉር የምትገኙ፤
የሀገራችንን ዳር ድንበር ለመጠበቅና ለማስከበር በየጠረፉ የቆማችሁ፤
በሕመም ምክንያት በየፀበሉና በየሆስፒታሉ ያላችሁ፤
እንዲሁም የሕግ ታራሚዎች ሆናችሁ በየማረሚያ ቤቱ የምትገኙ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያት በሙሉ፤
በምሉእ ፍቅሩ ሰውን ከባርነት ወደ ነጻነት ለመመለስ በሥጋ ሰብእ የተወለደው ጌታችን ኣምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንኳን ለሁለት ሺሕ ዐሥራ ሰባት ዓመተ ምሕረት የልደት በዓል በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ፡፡
“ስብሐት ለእግዚአብሔር በሰማያት ወሰላም በምድር ለዘሠምሮ ለሰብእ፤ ክብር በሰማያት ለእግዚአብሔር ይሁን›› በምድርም እጅግ ለወደደው የሰው ልጅ ሰላም ይሁን” (ሉቃ ፪÷፲፬)
ይህ ቃለ ሰላም በጌታችን ዕለተ ልደት የተነገረ ነው፣ ቃሉ የተነገረው እንዲሁ እንደ ተራ ነገር ሳይሆን በቃለ መዝሙር እየተደጋገመ ነው፡፡ የተዘመረውም በምድራውያን ደራሲዎች ሳይሆን በሰማያውያን መላእክተ እግዚአብሔር ነው፣ የያዘው መልእክትም ሰማያውያንና ምድራውያንን ሁሉ ያካለለ ነው፡፡ የመልእክቱ ገዢ ሓሳብም አምላክ ከሰውነታችን ጋር ባለመለያየት፣ ባለመጠፋፋት፣ ባለመቀላቀል፣ ባለመዋዋጥ፣ ባለመለዋወጥና ያለባዕድና አንድ አካል፣ አንድ ክዋኔ፣ አንድ ጠባይ ሆኖ በተዋሕዶ ተገልጾኣልና እግዚአብሔር ይክብር ይመስገን፡፡ የተዋሕዶውም ምስጢር ሰላምን ያሰፍናልና እግዚአብሔር ሰውን በእጅጉ መውደዱ ከዚህ ተዋሕዶ ዓውቀናል የሚል ነው፡፡
"ኖላዊነ ኄር- መድኃኔዓለም "
ኖላዊነ ኄር መድኃኔዓለም
ለነፍስ ወለሥጋ ወለኵሉ ዓለም
ዕቀበነ (፫) ለዓለመ ዓለምን
ድምጼን ይለዩታል በጎቼ በሙሉ
አያስታቸውም መንገደኛ ሁሉ
በራሱ በአምላክ የተባለላችሁ
በጎች ተሰብሰቡ ወደ በረታችሁ
አዝ...
ነብይ ነኝ የሚል የሠፈር ዜናዊ
አድርጎ የሾመ ራሱን ወንጌላዊ
ነጣቂ ተኩላው ተበራክቷልና
መንጋህን ጠብቀው በእምነት እንዲጸና
አዝ...
ከአምላክ የተላከ እውነተኛ እረኛ
ለመንጋው የሚያስብ ያይደለ ምንደኛ
ፊት የተማረ ነው ኋላም የተሾመ
በሐዋርያዊ ክህነት በእውነት የታተመ
አዝ...
ከጌታ የመጣ ካልሆነ ክህነቱ
ከአበው የተለየ ከሆነ ትምህርቱ
በበሩ ያልገባ ሌባ ነው ስላለ
ምዕመናን አትስሙት አሳቹ ስላለ
አዝ...
ጩኸታችን ሰምተህ ጭንቀታችን ዓይተህ
በየዘመናችን የሚታደግ ልከህ
እውነተኛው መምህር የበጎች እረኛ
አንተው አሰማራን ተመልከት ወደ እኛ
በዘማሪ ቀሲስ እስክንድር ወልደማርያም
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
ቸር ጠባቂ ለበጎቹ መልካም መሰማርያን ያዘጋጃል፤ ያሰማራቸዋልም።
ቸር ጠባቂ በጎቹን በመልካም ስፍራ ለማሰማራት መሰማርያን ያዘጋጃል። ነቢየ እግዚአብሔር ክቡር ዳዊት ‹‹እግዚአብሔር እረኛዬ ነው፤ የሚያሳጣኝም የለም፤ በለመለመ መስክ ይመራኛል(መዝ 22፡1)።›› እንዳለው ቸር ጠባቂ በጎቹን በለመለመ መስክ ያሰማራቸዋል። ‹‹በሙሴና በአሮን እጅ ህዝብህን እንደ በጎች መራሀቸው›› መዝ 76፡20 እንደተባለም በበጎ ይመራል። የለመለመ መሰማርያ የተባለም የቤተክርስቲያን መንፈሳዊ የአገልግሎት ዘርፍ ነው።
ምንደኛ ግን ራሱን ያሰማራል። በትንቢተ ሕዝቅኤል በምዕራፍ 43 ቁጥር 2 ላይ እንደተገለፀው ክፉ እረኛ ራሱን በበጎቹ መካከል ያሰማራል። ጠቦቶቹንም ያርዳቸዋል፤ ይበላቸዋልም። ‹‹ጮማውን ትበላላችሁ፤ ጠጉሩንም ትለብሳላችሁ፤ የወፈሩትንም ታርዳላችሁ፤ በጎቹን ግን አታሰማሩም (ሕዝ 34፡23)።›› እንዳለ መሰማርያውንና ውኃውን ይረግጣል፤ ያፈርሳልም። ለራሱና ለራሱ ብቻ መሰማርያን ያዘጋጃል። ለእኛ ግን ለነፍስም ለሥጋም የሚሆን መሰማርያን የሚያዘጋጅልን እርሱ ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።
ቸር ጠባቂ በጎቹን ያበዛል።
ቸር ጠባቂ በበረት ያሉትንና በውጭ ያሉትን በጎች አንድ ለማድረግ ይተጋል። በውጭ ያሉትን በጎች ወደ በረት ለማስገባት ሌትና ቀን ይሠራል። ይህንንም መርህ በማድረግ ቅዱሳን ሐዋርያት ወንጌልን ለዓለም በመስበክ በጎችን አብዝተዋል። ቅጥረኛ ግን በውጭ ያሉት በጎች በዚያው ቢቀሩ አይገደውም። በበረት ያሉትንም ጭምር በመከፋፈል ከበረት አስወጥቶ ይበትናል። እርሱ ስለራሱ ጥቅም እንጂ ስለበጎቹ ምንም የማይገደው ምንደኛ ነውና። ነገር ግን ‹‹የማሰማሪያዬን በጎች ለሚያጠፉና ለሚበትኑ እረኞች ወዮላቸው (ኤር 23፡1)።›› እንደተባለ በመጨረሻው ቀን መጠየቁ አይቀርም። እኛ ግን የጠፉትን የሚፈልግ፣ ያሉትን የሚያፀና እውነተኛ ጠባቂያችን እርሱ ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው ብለን እናምናለን።
ነቢየ እግዚአብሔር ክቡር ዳዊት ‹‹እኔ ባሪያህ የአባቴን በጎች ስጠብቅ አንበሳና ድብ ይመጣ ነበር፥ ከመንጋውም ጠቦት ይወስድ ነበር። በኋላውም እከተለውና እመታው ነበር፥ ከአፉም አስጥለው ነበር፤ በተነሣብኝም ጊዜ ጕሮሮውን ይዤ እመታውና እገድለው ነበር (1ኛ ሳሙ 17፡34)። ›› እንዳለው ከዲያብሎስ ጉሮሮ ከአንበሳም መንጋጋ ያዳነን እውነተኛው ጠባቂያችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።
ቸር ጠባቂ ስለበጎቹ መስዋእት ይሆናል።
ቸር ጠባቂ ራሱን ስለ በጎቹ አሳልፎ ይሰጣል። ተኩላ ሲመጣ ጥሎ አይሸሽም፤ ከበጎቹ ቀድሞ ይዋጋል እንጂ። ‹‹ነፍሱን ስለ ወዳጆቹ ከማኖር ይልቅ ከዚህ የሚበልጥ ፍቅር ለማንም የለውም (ዮሐ 15፡13)።›› እንደተባለ ቸር ጠባቂ ስለ በጎቹ መስዋእት ይሆናል። ምንደኛ ግን በጎቹን ስለ ራሱ አሳልፎ ይሰጣል። ተኩላ ሲመጣም በጎቹን ጥሎ ይሸሻል፤ በጎቹም ለምድር አራዊት መብል ይሆናሉ።
‹‹ቸር ጠባቂ እኔ ነኝ። ቸር ጠባቂ ስለ በጎቹ ነፍሱን ይሰጣል። ጠባቂ ያይደለ፥ በጎቹም ገንዘቡ ያልሆኑ ምንደኛ ግን ቅጥረኛ ግን ተኵላ ሲመጣ ባየ ጊዜ በጎቹን ትቶ ይሸሻል፤ ተኵላም መጥቶ በጎቹን ይነጥቃቸዋል፤ ይበትናቸዋልም። ምንደኛስ ይሸሻል፤ ስለ በጎቹም አያዝንም፤ ምንደኛ ነውና። ቸር ጠባቂ እኔ ነኝ፥ የእኔ የሆኑትን መንጋዎቼን አውቃለሁ፡፡ የእኔ የሆኑትም ያውቁኛል፡፡ አብ እኔን እንደሚያውቀኝ እኔም አብን አውቀዋለሁ፤ ለበጎች ቤዛ አድርጌ ሰውነቴን አሳልፌ እሰጣለሁ (ዮሐ 10፡11-15)።›› እንዳለ ነፍሱን ስለ በጎቹ አሳልፎ የሰጠ እውነተኛ ጠባቂያችን ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። እርሱ እንደተናገረው ቸር ጠባቂ እርሱ ነው፤ በዘላለም ኪዳን ደም ለበጎቹ ትልቅ ጠባቂ የሆነው እርሱ ነው (ዕብ 13፡20)። የነፍሳችን ጠባቂ የሆነው እርሱ ነው (1ኛ ጴጥ 2፡23)። የእስራኤል ዘነፍስ ጠባቂ የሆነውም እርሱ ነው (መዝ 79፡1)። እውነተኛም ጠባቂ እርሱ ነው (ዮሐ 10፡7)።
በጎችን የመጠበቅ ኃላፊነትና ተጠያቂነት
በጎችን የመጠበቅ ኃላፊነት ከተጠያቂነት ጋር አብሮ ለጠባቂዎች (ለሐዋርያትና ከሐዋርያት ቀጥሎ እስከ ዕለተ ምጽዓት ለሚነሱ እውነተኛ መምህራን) ተሰጥቷል። ‹‹ግልገሎቼን አሰማራ፤ ጠቦቶቼን ጠብቅ፤ በጎቼን አሰማራ።›› ብሎ የመጠበቅ ኃላፊነትን በጴጥሮስ በኩል ለሐዋርት ሰጥቷል (ዮሐ 21፡15-17)። ‹‹በጎቼን ከጠባቂዎች እጅ እፈልጋለሁ›› ብሎም በጎችን የመጠበቅ አገልግሎት ተጠያቂነትም እንዳለበት ተናግሯል (ሕዝ 34፡10)። በጎች (ምዕመናን) የክርስቶስ ተከታዮች እንጂ የእረኞቹ ተከታዮች አይደሉም፤ ጠባቂዎችም ባለአደራዎች እንጂ የበጎቹ ባለቤቶች አይደሉምና።
ዛሬስ የጠባቂዎች ድርሻ ምንድን ነው?
ጌታችን እንዳስተማረው የጠባቂዎች (የካህናትና የመምህራን) ድርሻ የሚከተሉትን ያጠቃልላል።
በበሩ መግባት፡- በተዋሕዶ ላይ መመሥረት፣ በሥርዓት መመራት፣ በእምነት መኖር
በጎቹን ማወቅ፡- በግና ተኩላን ለይቶ ማወቅ፣ የራስንና የሌላውን ለይቶ ማወቅ፣ ለበጎቹም ግልፅ መሆን
በጎቹን መጠበቅ፡- በጎችን ነቅቶ መጠበቅ (እንዳይነጠቁ)፣ ባክነው እንዳይጠፉ መንከባከብ
መሠማርያውን ማዘጋጀት፡- የሚያስፈልጋቸውን ትምህርት፣ ተግሳፅና ምክር መስጠት
በመልካም ስፍራ ማሰማራት፡- ከፊት ሆኖ በመምራት (በማገልገል) ለሥጋ ወደሙ ማብቃት
አንድነትን ማጠናከር፡- ከውጭ ያሉትን በማምጣትና ከውስጥ ያሉትን በማፅናት አንድነትን ማጠናከር
መስዋዕትነትን መክፈል፡- እውነትን በመመስከር መልካም አርአያ መሆን
የበጎች (የተጠባቂዎች) ድርሻስ ምንድን ነው?
በጌታችን ትምህርት መሠረት በጎች (ተጠባቂዎች) ጠባቂያቸውን በሚገባ ድምፁን ማወቅና እርሱንም መከተል፣ እውነተኛ ጠባቂ ያልሆነውን (ክፉውን እረኛ ወይም ምንደኛውን) መለየትና ከእርሱም መራቅ፣ ዛሬ እውነተኛ የሆነው ጠባቂያቸው ወደ ምንደኛነት ቢቀየር እንኳን ቶሎ ነቅቶ መለየት መቻልና ራሳቸውንም መጠበቅ ይኖርባቸዋል። እውነተኛና ቸር ጠባቂያችን ኢየሱስ ክርስቶስ መልካም በጎች ያድርገን፤ አርአያ የሚሆኑ ደገኞች ጠባቂዎችንም አያሳጣን።
የኖላዊ ክብረ በዓል ከታህሳስ 21-27 ባለ እሁድ ቀን ብቻ የሚከበር ሲሆን ይህ በዓል በተለይም በምስራቅ ጎጃም ሀገረ ስብከት በጣባ የጎደና ቀበሌ በኢትዮጵያ ብቸኛ በሆነው ጣባ ኖላዊ ቤተ ክርስቲያን በድምቀት ይከበራል ።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
"አባ ተክለ ሃይማኖት"
አባ አቡነ አባ መምህርነ/፪/አባ ተክለ ሃይማኖት /፪/
እም አእላፍ/፪/ ኅሩይ እም አእላፍ ኅሩይ/፪/
አዝ…
አምላክ የጠራህ ለታላቅ ክብር፣
ተክለ ሃይማኖት ትጉ መምህር፣
ሐዋርያ ነህ በዚች በምድር፣/፪/
ጸሎት ምኅላህ በእውነት ተሰማ፣
ክብርህ ታወቀ በላይ በራማ።/፪/
አዝ…
ደብረ ሊባኖስ ተቀደሰች፣
በእጅህ መስቀል ተባረከች፣/፪/
ኤልሳዕ ልበልህ ቅዱስ ዮሐንስ፣
ተክለ ሃይማኖት ጻድቅ ነህ ቅዱስ።/፪/
አዝ…
ተክለ አብ ተክለ ወልድ ተክለ መንፈስ ቅዱስ፣
ጸሎትህ ሆኖናል መድኃኒትና ፈውስ፣/፪/
ዛሬም ስንጠራህ ቃል ኪዳንህን አምነን፣
ጠለ በረከትህ ለሁላችን ይሁን።/፪/
አዝ…
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
መንፈስ ቅዱስ›› ብሎ የሹመትን ሀብት አሳደረባቸው፡፡ ዳግመኛም ‹‹በምድር ያሰርከው በሰማይ የታሰረ ይሁን፤ በምድርም የፈታኸው በሰማይ የተፈታ ይሁን፤ አንተን የሰማ እኔን መስማቱ ነው፤ የላከኝ አባቴንም መስማቱ ነው፡፡ አንተን እንቢ ያለ እኔን እንቢ ማለቱ ነው፡፡ የላከኝ አባቴንም እንቢ ማለቱ ነው፡፡ ይህን ሥልጣን ቀድሞ ለሐዋርያት ሰጥቻቸው ነበር፡፡ ከሐዋርያትም ሹመትን የተቀበለ ጳጳሱ ትሾምና ትሽር፣ ትተክልና ትነቅል ዘንድ ሥልጣንን ሰጠህ፡፡ ይህንንም ያደረኩልህ የጳጳሱን ቃል በመናቅ አይደለም፡፡ የፍቅሬን ጽናት ባንተ እገልጽ ዘንድ ነው እንጂ፡፡ ሐዋርያት ወዳልደረሱበት ሕዝብ በመምህርነት እልክህ ዘንድ በሚካኤል ቃል አዲስ ስም አወጣሁልህ፡፡ አንተም በማናቸውም ሥራ ከእነርሱ አታንስም፣ ሐዲስ ሐዋርያ አድርጌሃለሁና፡፡ ሰውን ሁሉ በእኔ ስም እያስተማርክ ታሳምን ዘንድ፣ ሚካኤልም ባሰብከው ሥራ ሁሉ ረዳት ይሁንህ፣ ሁል ጊዜ ካንተ አይለይም፤ በምትሄድበትም ጎዳና ሁሉ እርሱ መሪ ይሁንህ፤ እኔም ባለ ዘመንህ ሁሉ አልለይህም›› ካላቸው በኋላ ሰላምታ ሰጥቷቸው ዐረገ፡፡
ብፁዕ አባታችንም እጅ ነሥተው ‹‹ለእኔ ለኀጥኡ የማይገባኝ ሲሆን ይህን ሁሉ ጸጋ የጠኸኝ ስምህ በሰማይ በምድር የተመሰገነ ይሁን›› አሉ፡፡ ከዚያች ቀን ጀምሮ ሀብተ ኃይልን የተመሉ ሆኑ፡፡ ወደቤታቸው ተመልሰው ያላቸውን ሀብት ንብረት ሁሉ ለቤተ ክርስቲያን፣ ለድኆችና ለጦም አዳሪዎች ሰጥተው ጨረሱ፡፡ ከዚያም ‹‹አቤቱ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ! የመንግሥተ ሰማያትን በር ትከፍትልኝ ዘንድ እነሆ ቤቴን እንደተከፈተ ተውኩልህ›› ብለው ቤታቸውን እንደተከፈተ ትተው ወንጌልን ለማስተማር ወጡ፡፡ ጻድቁ አባታችን በሀገራችን ኢትዮጵያ እየተዘዋወሩ ሕዝቡን ከኃጢአት ወደ ገቢረ ጽድቅ፣ ከክህደት ወደ ኃይማኖት ስለመለሱት በዚህም የተነሣ ለኢትዮጵያውያን ብርሃን ተብለዋል፡፡
የአባታችን ረድኤት በረከታቸው በእኛ በምና'ምን ክርስቲያኖች ላይ እጥፍ ድርብ ይሁንልን! አሜን!
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
"ጥሩልኝ ዳዊትን"
ዘማሪ አቤል ተስፋዬ
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
ታኅሣሥ ፳፫
ዕረፍቱ ለልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት
ቅዱስ መጽሐፍ እንዲህ ይላል:- "እግዚአብሔር ለዳዊት በእውነት ማለ: አይጸጸትም::" (መዝ. 131:11) አሁን በእግዚአብሔር መጸጸት ኑሮበት አይደለም:: ቅዱስ ዳዊት የማያጸጽት ፍጹም ወዳጅ መሆኑን ሲገልጥ ነው እንጂ:: ጌታ ቅዱስ ዳዊትን "እንደ ልቤ የሆነ: ፈቃዴን የሚፈጽም: ባሪያዬን ዳዊትን አገኘሁት" (መዝ. 88:20)
እንደ አምላክ ልብ ሆኖ መገኘት ምን ይረቅ?! ምንስ ይደንቅ? ለዚህ አንክሮ ይገባል።
ቅዱስዳዊት አባቱ እሴይ እናቱ ሁብሊ ይባላሉ። በነሐሴ 13 ቀን ተጸነሰ በሚያዝያ 6 ቀን በይሁዳ በቤተልሔም ሀገር ተወለደ። (1ሳሙ. 16፡10-11) ዳዊት ማለት ልበ አምላክ ማለት ነው። እረኛና ብላቴና ነበር።
የፍልስጤማውያኑን ሰው ጎልያድን በ12 ዓመቱ 5 ጠጠርን ከወንዝ ለቅሞ በወንጭፍ ወርውሮ የገደለ (1ሳሙ.12፡45-51)፣ ንጉሥ ሳዖል በጌልቦአ ተራራ በራሱ እጅ ከሞተ በኋላ አስቀድሞ በይሁዳ 7 ዓመት በመላው እስራኤል 33 ዓመት የነገሠ (2ሳሙ. 2፡4፤ 2ሳሙ. 5፡1-5) ቅዱስ አባት ነው።
“እግዚአብሔር እንደ ልቡ የሆነ ሰው መርጧል” (1ሳሙ.13፡14) ተብሎ በእግዚአብሔር የተመረጠና ነገረ ሥጋዌን፣ ምሥጢረ ትንሣኤ ሙታንን፣ ዳግም ምጽዓትን፣ ነገረ ማርያምን፣ ክብረ ቅዱሳንን፣ በስፋትና በጥልቀት የተናገረ የብሉይ ኪዳን “ወንጌላዊ” ነበር።
🌿(መዝ.21 (22)፡ 16-18 “ብዙ ውሾች ከብበውኛልና የክፋተኞች ጉባኤም ያዙኝ እጆቼንና እግሮቼን ቸነከሩኝ። አጥንቶቼ ሁሉ ተቆጠሩ እነርሱም አዩኝ ተመለከቱኝም። ልብሶቼን ለራሳቸው ተከፋፈሉ፥ በቀሚሴም ላይ ዕጣ ተጣጣሉ።…”፣
🌿መዝ. 46(47)፡4-5 አምላክ በእልልታ፥ እግዚአብሔር በመለከት ድምፅ ዐረገ።”
🌿መዝ.49(50)፡ 1-5 “ከክብሩ ውበት ከጽዮን እግዚአብሔር ግልጥ ሆኖ ይመጣል። አምላካችን ይመጣል ዝምም አይልም እሳት በፊት ይቃጠላል፥ በዙሪያውም ብዙ ዐውሎ አለ።”፣
🌿መዝ. 44(45)፡9 “የንጉሦች ሴት ልጆች ለክብርህ ናቸው በወርቅ ልብስ ተጐናጽፋና ተሸፋፍና ንግሥቲቱ በቀኝህ ትቆማለች።”
ዳዊት ታላቅና ገናና ንጉሥ ከመሆኑ የተነሳ መንግሥቱ የመሲህ መንግሥት ምሳሌ ሆኗል፤ መሲሁም ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዳዊት ስም ብዙ ጊዜ በመጽሐፍቅዱስ ተጠቅሶ ይገኛል። (ት.ኢሳ.9፡7፣ ኤር.23፡5-6፣ ኤር.3314-17፣ ህዝ. 34፡23፣ሆሴዕ 3፡5)
ቅዱስ ዳዊት 7 ሀብታት የተሰጡት አባት ነበር፤ እነዚህም:
፩. ሀብተ ክህነት
፪. ሀብተ መንግሥት
፫. ሀብተ መዊዕ
፬. ሀብተ ትንቢት
፭. ሀብተ ኀይል
፮. ሀብተ በገና
፯. ሀብተ ፈውስ ናቸው።
እድሜ ዘመኑን እግዚአብሔርን በማገልገልና በመፍራት ኖሮ በታህሳስ ፳፫ ቀን አርፎ በኢየሩሳሌም ተቀብሯል።
የልበአምላክ ቅዱስ ዳዊት ረድኤትና በረከቱ ከእኛ ከምናምን ክርስቲያኖች ጋር ለዘለዓለም ይኑር: አሜን!
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
"▫️እጅህ ላይ ባለው ነገር ከታመንህ እግዚአብሔር አምላክ በእጁ ውስጥ ያለውን ነገር ይሰጥሃል።
▫️በውስጥህ ያለውን አቅም መጠቀም ከቻልህ እግዚአብሔር የአንተ ያልሆነ ተጨማሪ አቅም ይሰጥሃል።
▫️ከእግረኞች ጋር ሳትደክም እኩል መራመድና መቅደም ከቻልህ እግዚአብሔር ፈረስን ለውድድር ይሰጥሃል። ኤር. 12፥5
▫️የሚታዩ ኃጢአቶችን ለመዋጋት ታምነህ ከተገኘህ እግዚአብሔር የተሸሸጉና የማይታዩ ኃጢአቶችን ድል እንድትነሣ ይሾምሃል።
▫️በሕፃንነትህ በልጅነትህ ለእግዚአብሔር የታመንህ ሆነህ ከተገኘህ እርሱ በወጣትነትህ በምታደርገው ውጊያ ውስጥ ታማኝነትን ያድልሃል።
▫️ልያን ለመቀበል ታማኝ ሆነህ ከተገኘህ እግዚአብሔር ራሔልን ሚስት አድርገህ ታገባት ዘንድ ይሰጥሃል። ዘፍ. 29፥27
▫️በሲና ምድረ በዳ ለመቀመጥ ታማኝ ሆነህ ከተገኘህ እግዚአብሔር አምላክ የተስፋይቱን ምድር ከንዓንን ያወርስሃል።
▫️በዚህ በተወሰነና አጭር ሕይወት ታማኝ ሆነህ ከተገኘህ እግዚአብሔር መጨረሻ የሌለውን ዘላለማዊ ሕይወት ያድልሃል።
▫️ትልቁ ቁም ነገር በእጅህ ውስጥ የገባው ነገር ትንሽም ይሁን ጥቂት በእርሱ መታመን መቻልህ ነው።
▫️ስለሆነም ባለህ አንድ መክሊት ታምነህ ስትገኝ እግዚአብሔር አምስት መክሊቶችን በአደራ ይሰጥሃል።
▫️አንተ በሚታዩት ነገሮች ላይ ታማኝ ሆነህ ስትገኝ እርሱ በማይታዩት ነገሮች ላይ ይሾምሃል።
✨በመሆኑም ዓይን ያላየችውን ጆሮ ያልሰማውን በሰው ልብ ያልታሰበውን መንግሥቱን ያወርስሃል። 1ኛ ቆሮ 2፥9"
(➥አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ - መንፈሳዊው መንገድ መጽሐፍ አያሌው ዘኢየሱስ እንደተረጎመው።)
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
"አይ ሞኝነቴ ሞቴን መርሳቴ"
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
🔊ልደትን በባለልደቱ ቤት!
በእርግጥም እግዚአብሔር ሰውን ለመውደዱ ከዚህ የበለጠ ማሳያ ወይም ማስረጃ የለም፤ እንከን የለሽ ንጹህ አምላክ የእኛን ኃጢአተኛ ሰውነት አካሉ አድርጎ ተወለደ ሲባል ላስተዋለው ሰው ምንኛ ቢወደን ነው የሚለው ጥልቅ አድናቆትን ያጭራልና ነው፡፡ይህ ብቻም አይደለም በዚህ ነገረ ተዋሕዶ ምክንያት ሰውነታችን አምላክ ሆኖ በመንበረ ጸባኦት እንዲቀመጥ መብቃቱ የድኅነታችንና የክብራችን ከፍታ ምን ያህል አስተማማኝ ደረጃ ላይ እንደደረሰ መንፈሳችን በአንክሮ ይረዳዋል፡፡ድምር ውጤቱም በእግዚአብሔርና በሰው መካከል ፍጹምና አስተማማኝ ሰላም መፈጠሩን ያስረዳናል፤ ሰማያውያኑ መላእክተ እግዚአብሔር በመዝሙራቸው ያበሰሩን ይህንን የምስራች ነው፡፡
የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት!
እኛ ክርስቲያኖች እግዚአብሔር ፍቅር ነው፣ እግዚአብሔር በእጅጉ ይወደናል ስንል እንዲሁ ከሜዳ ተነሥተን ኣይደለም፡፡ በበደላችንና በኃጢአታችን ሳይጸየፈን ሰውነታችንን በረድኤት ወይም በኅድረት ያይደለ በኩነት ተዋሕዶ ወደ አምላክነት ደረጃ ከፍ ስላደረገው ነው እንጂ፡፡ እግዚአብሔር በዚህ ፍጹምና ምሉእ ፍቅሩ ሰውነታችንን በመበረ ጸባኦት ኣስቀምጦ መላእክት ሳይቀሩ ፍጥረታትን በሙሉ እንድንገዛ አድርጎናል፤ ምክንያቱም መላእክት በዕለተ ልደት የዘመሩለት በተዋሕዶ አምላክም ሰውም ለሆነ ለቤተ ልሔሙ ሕፃን እንጂ ለመለኮት ብቻ ኣይደለምና ነው፡፡ የዕለተ ልደት መዝሙር ዛሬም በሰማያትም ሆነ በምድር በተዋሕዶ ሰውም ኣምላክም የሆነ አንዱ ኢየሱስ ክርስቶስ ይመለክበታል፣ ይመሰገንበታል፡፡የሰማዩና የምድሩ ዕርቅ ወደ ኋላ ላይመለስ ላንዴና ለመጨረሻ ጊዜ በዚህ ተከናውኖኣል፣ የእግዚአብሔር ፈቃድ የሰውም አዋጭ ምርጫ ይህ ዕርቅ ተጠብቆ እንዲኖር ነው፣ ያለ ዕርቅ ሰላም ሕይወት የለውምና፡፡
የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት!
የእግዚአብሔር ክብርና ሰላም በእጅጉ የተሳሰሩና የተቆራኙ ናቸው፤ እኛ እግዚአብሔርን ካከበርነው፣ ካዳመጥነው፣ ከታዘዝነውና ከተከተልነው ሰላም አለ ማለት ነው፡፡ ለሱ ካልታዘዝንና እሱን ካላከበርን ግን ዘላቂ ሰላምን ማግኘት ፈጽሞ የማይታሰብ ነው፤ ምክንያቱም ሰላምን ጨምሮ መልካም ነገር ሁሉ ያለው በእግዚአብሔር እጅ ነውና፡፡ ዛሬ በሁሉም የዓለማችን ማዕዘን የሚታየው የሰላም መደፍረስ እግዚአብሔርን ካለማክበራችንና ለሱ ካለመታዘዛችን የተነሣ እንደሆነ መዘንጋት የለብንም፡፡ ዓለም ከእግዚአብሔር ቃል ርቃ ለመሄድ በእጅጉ እየኳተነች ነው፤ በዚህ እኩይ ተግባርዋ ደግሞ እግዚአብሔር ለስጋትና ለጉስቁልና አሳልፎ እየሰጣት ነው፡፡ እግዚአብሔር በምስጢረ ሥጋዌው ቢታረቃትም ዕርቁን ማክበር አቅቶአታል፤ ይህንን የእግዚአብሔር ጸጋ ቸል ብላ የምታደርገው ሩጫ የትም ሊያደርሳት እንደማይችል ብታውቅና በንስሓ ብትመለስ እግጅ ተጠቃሚ ትሆናለች፡፡
የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት!
የእግዚአብሔር ቃል “እናንተስ ከማይጠፋ ዘር ተወለዳችሁ” ብሎ ተስፋውን እንደነገረን ምድባችን ከማይጠፋ ዘር እንዲሆን ክርስቲያኖች የሆን ሁላችን በአእምሮ ጐልብተን፣ በሥነ-ምግባር ኣምረን፣ ጤናማ ሕይወትን ልንመራ ይገባናል፡፡
የአምላካችንን በዓለ ልደት ስናከብር ነገረ እግዚአብሔርን፣ ነገረ ፍቅርን፣ ነገረ ዕርቅንና ነገረ ሰላምን በማኅበረሰባችን የማሥረጽ አጀንዳ ይዘን ልናከብር ይገባል፡፡
ጠቡ ፣ ጥላቻው፣ መለያየቱ፣ መጠፋፋቱ፣ ለወንድሜ ከማለት ይልቅ ለኔ ለኔ ማለቱ ሲጎዳን እንጂ ሲጠቅመን ኣላየንም፡፡ አሁንም ወደ ልባችን እንመለስና በፍቅር፣ በዕርቅና በእኩልነት፣ በስምምነትና በወንድምነት ወደሚገኝ አንድነት እንምጣ፤ የልደቱ መዝሙር ያስተማረን ይህና ይህ ብቻ ነውና፡፡ በሌሎቹ ክፍለ ዓለማት እንደሆነው ሁሉ በሀገራችን የተከሠተው አላስፈላጊ ግጭት ብዙዎችን አሳጥቶናል፤ ብዙዎችንም ከቤት ንብረታቸው አፈናቅሎ ሜዳ ላይ ፈሰው የሰቆቃ ኑሮ እንዲገፉ አድርጎብናል፡፡ የሀገር ሀብት እንዲወድም ሆኖአል፤ ልጆቻችን ምናለ ከእንግዲህ ወዲህ ቢበቃንና ምድሪቱን የሰላም አየር እንድትተነፍስ ብንፈቅድላት፤ ይህ የወቅቱ የቤተክርስቲያናችን ዋነኛ መልእክትና ጥሪ ነው፡፡
በመጨረሻም፡-
በዓለ ልደት የእግዚአብሔር በዓል ነውና፣ እግዚአብሔር በምድራችን ሰላምን ያወርድ ዘንድ ካለን ከፍለን ለተፈናቃዮች፣ ለነዳያን እና ለአካል ጉዳተኞች በመለገስ በዓሉን በመንፈሳዊ ደስታና በሰላም እንድናከብር አባታዊ መልእክታችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን፤
መልካም በዓለ ልደት ያድርግልን፡፡
እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ
ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን!
አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ
ተክለሃይማኖት
ታኅሣሥ ፳፱ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
@Ethiopian_Orthodox
"ሣር ቅጠሉ ሰርዶው"
ሣር ቅጠሉ ሰርዶው ሰንበሌጥ ቄጤማው
በዚያች ቀን በዚያች ወር ለምለም የነበረው
በእልልታ ዘመሩ በደስታ ተሞልተው
ጌታ መወለዱን የምስራች ሰምተው
እልል በይ ቤተልሔም ሃሌ ሃሌ ሉያ
የፍቅር የሰላም ነሽና ገበያ (፪)
ያ ትሁት እረኛ ሳለ በትጋት
ብርሃንን ለበሰ በእኩለ ሌሊት
ጥሪ ተደርጎለት ከሰማይ ሠራዊት
ለመመልከት በቃ የጌታውን ልደት
አዝ= = = = =
የእረኝነት ሥራ ተንቆ እንዲቀር
ብሎ ሰው በልማድ ደንግጎ ነበር
የብዙ ሰው ራስ መሆኑን እረኛ
ክርስቶስ ሲወለድ ተረዳነው እኛ
አዝ= = = = =
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
ጾመ ገሐድ እና በዓለ ልደት
ገሐድ፡- መገለጥ፣ ማታየት፣ መታወቅ፣ ማለት ሲሆን፤
ጋድ፡- ማለት ደግሞ ምትክ፣ ለውጥ፣ ቅያሪ ማለት ነው፡፡
በዓለ ልደት በመጣ ጊዜ ሁሉ በተለይም በዓሉ ዓርብና ረቡዕ ከዋለ ጥያቄዎች ይበዛሉ፡፡ የጥያቄው ምክንያት ደግሞ ደንታ-ቢስነት፣ አለመማር፣ ጥያቄን እንጂ መልስን አለመያዝ ያመጣው ጣጣ ነው፡፡
ማንኛውም ክርስቲያን ስለ ሰባቱ አጽዋማት በቂ ዕውቀት መያዝ አለበት፡፡ ትምህርቱም ከአንድ ቀን የማያልፍ ግፋ ቢል በሁለት ቀን ቁጭብሎ መማር በሚገባ ሊታወቅ የሚችል ቀላል ትምህርት ነው፡፡ አብዛኛው ክርስቲያን ግን ለሃይማኖታዊ ጉዳዮች የሚሰጠው ጊዜና ትኩረት ዝቅ ያለና በደንታ-ቢስነት የተመላ ስለሚሆን እንደዚህ ያሉ ቀላል ጉዳዮች ሳይቀሩ በየዓመቱ ጥያቄ ሁነው እንዲኖሩ አድርጓቸዋል፡፡
ወቅሶ ከማለፍ ድርሻን መወጣት ይሻላልና ቀላል ትምህርት ነው ያልኩትን ጾም ከተነሣሁበት ከገሐድ ጀምሬ ለማብራራት ልሞክር ሰባት ዓመት የሞላው ጤነኛ ክርስቲያን ሊጾማቸው የታዘዙ ሰባት የአዋጅ አጽዋማት አሉ። እነርሱም፦
1. ገሐድ [ጋድ] ትርጉሙን ከላይ ስላስቀመጥኩት ወደ ምሥጢሩ ስገባ ይህ ጾም የልደትና የጥምቀት ዋዜማ ነው። ፍትሐ ነገሥቱ አንቀጽ 15 ቁጥር 567 ላይ ‹‹እንደ ዐቢይ ጾም በመጠንቀቅ የሚጾም አለ ብሎ ሌሎቹን ከዘረዘረ በኋላ…ወጾመ ድራረ ልደት ወጾመ ድራረ ጥምቀት፡- የልደትና የትምቀት ዋዜማ ጾም ነው ይላል፡፡ አንዳንዶች በጾም ላይ ጾም የለምና ለገና ጋድ የለውም ለማለት ይሞክራሉ ቁምነገሩ ግን ጾሙን ደርበን ሳይሆን ለብቻ አንድ ዕለት ጨምረን ነው እየጾምን ያለንው፡፡
ከኅዳር 15 እስከ ታኅሣሥ 28 ያለው ቀን ሲቆጠር 44 ነው፡፡ ይኸውም 40ው የነቢያት ጾም ነው ሦስቱ ቀናት አንዱ የመበሥር የጌታ፣ ሁለተኛው የተበሣሪ የእመቤታችን ሦስተኛው የአብሣሪ የቅዱስ ገብርኤል ነው፡፡ በሌላ መንገድ ሦስቱ ቀን የአብርሃም ሦርያዊ ጾም ነው፡፡ ይህ አባት በሦስት ቀን ሱባኤ ተራራ ማፍለሱን ታኅሣሥ 6 የሚነበበው ስንክሳር ይነግረናል፡፡ ስለዚህ ከ44ቱ ቀናት 40ው የነቢያት፣ ሦስቱ የጌታ፣ የእመቤታችን፣ የቅዱስ ገብርኤል /የአብርሃም ሦርያዊ/ የፊልጶስ ደቀ መዛሙርቱ ሊቀብሩት ሥጋው ተሠውሮባቸው ሦስት ቀን ጹመው ያገኙበት/፣ 44ኛዋ ቀን ግን ያለምንም ተቀናቃኝ ገሐድ ወይም ጋድ ናት፡፡ ገሐድ መገለጥ ነው፤ በባሕርየ መለኮቱ የማይታየው ጌታ በተዋሕዶተ ትስብእት ስለተገለጠልን መቀበያ አድርገን እንጾመዋለን።
ጋድ ባለው ግን የጥምቀትና የልደት በዓል ዓርብና ረቡዕ ቢውሉ ጾም የለምና ለዚያ ምትክ ማለት ነው፡፡ ይህንን ፍትሐ ነገሥት አንቀጽ 15 ቁጥር 566 እንዲህ ገልጾታል፦ "ወዓዲ ረቡዐ ወዓርበ በኵሉ ሱባኤ ዘእበለ መዋዕለ ኃምሳ ወበዓለ ልደት ወጥመቀት ሶበ ኀብሩ ቦሙ፤ ዳግመኛም ረቡና ዓርብን በየሳምንቱ ሊጾሙ ይገባል፤ ከበዓለ ኃምሳ በስተቀር እንዲሁም ልደትና ጥምቀት ጊዜ ገጥሟቸው ረቡና ዓርብ ከሚውሉበት ጊዜ በቀር፡፡" ከዚህ የምንረዳው ልደትና ጥምቀት ዓርብና ረቡዕ ሲውሉ ጾም አለመኖሩን ሲሆን ምክንያቱ ደግሞ በምትካቸው አንድ ቀን የምንጾምላቸው መሆኑ ነው፡፡
የጥር 11 ቀን ስንክሳርም እንዲህ ይላል፥ ከላይ የገሐድን ነገር እያብራራ ከመጣ በኋላ…... በዚች ዕለት ምእመናን እስከምሽት እንዲጾሙ ያዘዙበት፣ ምክንያቱ ይህ ነው፡፡ የልደትና የጥምቀት በዓል በረቡዕ ወይም በዓርብ ቀን ቢሆን በበዓለ ኃምሳ የሚበላውን የጥሉላት መብል (ሥጋ፣ ወተት፣ ዕንቁላል) በጥዋት በመብላት ምእመናን ሁሉ በዓሉን እንዲያከብሩ የከበሩ አባቶቻችን ሐዋርያት አዝዘዋል እሊህ ሁለቱ የእግዚአብሔር ታላላቅ በዓላት ናቸውና፡፡
እኛ በዚህ በኃላፊው ዓለም ተድላ ደስታ ደስ የሚለን እንዳይመስላቸው እንደ አይሁድና እንደ አረማውያን በዓል በመብልና በመጠጥ ብቻ እንዳናደርግ ስለዚህ ከልደትና ከጥምቀት በዓል በዋዜማ ያሉትን ሁለቱን ዕለታት እንድንጾም አዘዙን…... እያለ ይቀጥላል፡፡
ይህ ሁኖ ሳለ አንዳንድ ሰዎች በዚሁ በጥር 11 ቀን ስንክሳር መጨረሻ ላይ ያለውን አርኬ ጠቅሰው ከላይ የተነበበውን ሙሉ ንባብ ዘንግተውና ትተው ለገና ገሐድ የለውም ለማለት "ሰላም እብል ለጾመ ዕለት ዋሕድ፤ ዘስሙ ገሐድ ፤ ስሙ ገሐድ ለሚባል የአንድ ቀን ጾም ሰላም እላለሁ" የሚለውን ይጠቅሳሉ።
ጥቅሱ ቁርበተ ነክ ነው። ሙሉ ስንክሳሩ ሲነበብ አንቀላፍቶ ወይም ስንክሳሩን ሳይሰማ ከአርኬው ብቻ ለደረሰ ሰው ይመስለዋል እንጂ የጥር 11ዱ ስንክሳርስ በማያሻማ ሁኔታ በግልጽና በዝርዝር አስቀምጦታል። ገሐድም ለለልደትም ለጥምቀትም የተሠራ ነው፡፡ ዋሕድ ያለው የልደትና የጥምቀት ገሐድ አንድ ተብሎ ስለሚቆጠር ነው 44ቱ ጾመ ነቢያት አንድ ተብሎ እንደሚቆጠር፡፡
ገሐድ የሌላቸው ጾመ ሐዋርያት፣ ጾመ ፍልሰታ.... ፋሲካቸው ከረቡዕና ከዓርብ ላይ ሲሆን ይጾማሉ፡፡
2. ከላይ ዝርዝሩን የገለጽነው ጾመ ነቢያት (ከኅዳር 15 እስከ ታኅሥሥ 28)
3. ጾመ ነነዌ (የነነዌ ሰዎች ከእሳት የዳኑበት)
4. ዐቢይ ጾም (ዐቢይ እግዚአብሔር ወልድ ሰው ሁኖ የጾመው)
5. ጾመ ሐዋርያት (አባቶቻን ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስን ተቀብለው ለስብከተ ወንጌል ከመውጣታቸው በፊት የጾሙት)
6. ጾመ ፍልሰታ ለማርያም (ጾመ ማርያም ሐዋርያት የእመቤታችን ትንሣኤና ዕርገት ለማየት ያበቃቸው ጾም)
7. ጾመ ረቡዕ ወዓርብ፤ (ረቡዕ የጌታችን ሞቱ የተወሰነበት፣ ዓርብ ተሰቅሎ የሞተበት ነው) ይህን ዐውቆ የማይጾም እየጾመም የማያውቅ ክርስቲያን ሰነፍ ደካማ ይባላልና እናት ተምራ ለልጇ፣ አባት ተምሮ ለልጁ ሊያስተምረው ይገባል።
©መ/ር ኃይለማርያም ዘውዱ
እንኳን ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል አደረሳችሁ!
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
ኖላዊ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የበዓላት ቀኖና መሠረት ከህዳር 15 እስከ ጌታችን ልደት (ታህሳስ 28/29) ድረስ ያለው ወቅት በዘመነ ብሉይ የነበሩ ቅዱሳን ነቢያት የጌታን ልደት በተስፋ እየጠበቁ የገቡትን ሱባኤ፣ የጾሟቸውን አጽዋማት በማሰብ ልዩ ልዩ ክብረ በዓላት ይከበራሉ። ለእያንዳንዱ በዓልም የተለየ የቅዱሳት መጻሕፍት ንባብና ትርጓሜ፣ የተለየ የምስጋና መዝሙር ይዘመራል። በጾመ ነቢያት ውስጥ ያሉት የመጨረሻዎቹ ሦስት ሣምንታት በተለየ መልኩ ይከበራሉ። ወቅቱም ትንቢተ ነቢያትን በማሰብ ዘመነ ስብከት ይባላል። የነቢያት የስብከታቸው ማዕከል የክርስቶስ ሰው የመሆን ተስፋ ነውና።
የዘመነ ስብከት የመጀመሪያው ሣምንት ስብከት ይባላል(ከታኅሣሥ 7-13)፤ ሁለተኛው ሣምንት ብርሃን ይባላል(ከታኅሣሥ 14-20)፤ ሦስተኛው ሳምንት ኖላዊ ይባላል(ከታኅሣሥ 21-27)። ኖላዊ ማለት ጠባቂ ማለት ሲሆን ቅዱሳን ነቢያት እውነተኛው ጠባቂ የእግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ ክርስቶስ ይገለጣል ብለው በትንቢት መናገራቸውና ኢየሱስ ክርስቶስም ቸር ጠባቂ መሆኑን እያሰበች ቤተክርስቲያን የምትዘምርበት፣ የምታመሰግንበትና የምታስተምርበት ዕለት በመሆኑ ኖላዊ ተብሎ ተሰይሟል። በዚህ ዕለት ጌታችን በወንጌሉ እርሱ ቸር ጠባቂ እንደሆነ ያስተማረበት ዮሐ 10፡1-22 ያለው የወንጌል ክፍል ይነበባል፣ ከተያያዥ የቅዱሳት መጻሕፍት ምስጢራት ጋርም ይሰበካል፣ ይተረጎማል።
የዚህ የጌታችን ትምህርት መነሻ ‹‹እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ወደ በጎች ስፍራ በበሩ የማይገባ በሌላም በኩል የሚገባ ሌባ፥ ወንበዴም ነው፤ በበሩ የሚገባ ግን የበጎች ጠባቂ ነው። ለእርሱ በረኛው ይከፍትለታል፤ በጎቹም ድምፁን ይሰሙታል፥ የራሱንም በጎች በየስማቸው ይጠራቸዋል፤ አውጥቶም ያሰማራቸዋል። ሁሉንም አውጥቶ ባሰማራቸው ጊዜ በፊት በፊታቸው ይሄዳል፥ በጎቹም ቃሉን ያውቃሉና ይከተሉታል፤ ከሌላው ግን ይሸሹታል እንጂ አይከተሉትም፥ የሌላውን ቃሉን አያውቁምና(ዮሐ 10፡1-5)። ›› የሚለው ነው።
ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ይህንን ‹‹ቸር ጠባቂ›› የተባውን ትምህርት ስለ ሦስት ምክንያቶች አስተምሯል። የቸር ጠባቂ መገለጫዎችን ለይቶ ለማሳወቅ፤ የቸር ጠባቂና የምንደኛን ልዩነት ለማስረዳትና ቸር ጠባቂ እርሱ መሆኑን ለመግለጽ ያስተማረው ነው። በትምህርቱም ሰባት የቸር ጠባቂ መገለጫዎችን አስቀምጧል። እነዚህም፡-
ቸር ጠባቂ በበሩ ይገባል፤ በበሩም ይወጣል።
ቸር ጠባቂ ወደ በጎች በረት በበሩ ብቻ ይገባል፤ በበሩም ብቻ ይወጣል። በጎቹን ከበረታቸው አውጥቶ ሊያሰማራ በግልፅ በበሩ ይገባል፤ ይዟቸውም በግልፅ (በብርሃን) በበሩ ይወጣል። የሌሊት ጠባቂውም ይከፍትለታል። ሌባ ግን አጥር ጥሶ ቅጥር አፍርሶ ይገባል እንጂ በበሩ አይገባም፤ እንደዚያውም ይወጣል። በጨለማ ይገባል እንጂ በግልፅ (በብርሃን) አይገባም። ምንደኛ መምህርም እንደዚሁ እምነትን አጉድሎ ሥርዓትን አፍርሶ ወደ ቤተክርስቲያን በተንኮል ይገባል።
የበጎች በር የተባለውም ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። በእርሱ ያላመነ (በበሩ ያልገባ) እውነተኛ ጠባቂ ሊሆን አይችልምና። እምነትን ሥርዓትን ያልጠበቀ እውነተኛ ጠባቂ ሊሆን አይችልም። በበሩ የገባ (ተመስክሮለት የመጣ) በበሩም መግባትን ያስተማረን ጠባቂ እርሱ ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። የክርስቶስን አርዓያ የተከተሉ ደገኛ መምህራንም በበሩ ይገባሉ፤ በበሩ ይወጣሉ።
ቸር ጠባቂ በጎቹን ያውቃቸዋል፤ እነርሱም ያውቁታል።
ቸር ጠባቂ በጎቹን በየስማቸው ይጠራቸዋል። እነርሱም ድምፁን ይሰሙታል፤ ያውቁታልም። በትክክለኛው ስማቸው (ግብራቸውን በሚገልፅ) ይጠራቸዋል። እነርሱም ድምፁን ስለሚያውቁ ይሰሙታል። ቃሉን (አስተምህሮውን) ያዉቁታል። ወንበዴ ግን የበጎቹን ስም ከቶ አያውቅም፤። በጎቹም ድምፁን አያውቁትም። እንደ ይሁዳ ዘገሊላ እንደ ቴዎዳስ ዘግብፅ ያሉት እንደዚህ ሐሰተኛ ጠባቂዎች ነበሩ (ሐዋ 5፡33-39)። አስተምህሮአቸው ከእግዚአብሔር ስላልሆነ ለጊዜው ተከታይ ቢያገኙም ምዕመናን አልሰሟቸውም። እነርሱም ጊዜአቸው ሲደርስ ጠፍተዋል። በጎቹን የሚያውቅ እነርሱም ድምፁን የሚያውቁት እውነተኛ እረኛችን ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ‹‹ዮሴፍን እንደ መንጋ የምትመራ፥ የእስራኤል ጠባቂ ሆይ፥ አድምጥ፤ በኪሩቤል ላይ የምትቀመጥ፥ ተገለጥ (መዝ 79፡1)።›› እንደተባለ የቤተክርስቲያን ጠባቂዋ እርሱ ነው። የክርስቶስን አርዓያ የተከተሉ ደገኛ መምህራንም በጎች የተባሉ ምዕመናንን ሐዋርያዊ ትምህርትን እያስተማሩ በምግባር በሃይማኖት ያጸኗቸዋል።
ቸር ጠባቂ በጎቹን ይመራቸዋል፤ እነርሱም ይከተሉታል።
ቸር ጠባቂ በበጎቹ ፊት ፊት ይሄዳል። እነርሱም እርሱን እየተከተሉት ይሄዳሉ። እርሱ ቀድሞ በጎቹ ይከተሉታል። ወደ መሰማርያችውም ይመራቸዋል። አንድ በግ ቢቀርበት ወይም ቢጠፋበት እንኳን ሌሎቹን ትቶ የጠፋውን ይፈልጋል (ሉቃ 15፡2ሌባ ግን ከበጎቹ ኋላ ኋላ ይሄዳል፤ በጎቹንም ሊሠርቅ ከኋላ ሆኖ በጎቹን በአይነ ቁራኛ እየተመለከተ ይከተላል። በጎቹ ቢጠፉም አይገደውም፤ ሊሠርቅ እንጂ ሊመራቸው አልመጣምና። እኛን ወደ ለመለመ መስክ የሚመራን እኛም ድምፁን ሰምተን የምንከተለው እውነተኛ ጠባቂያችን እርሱ ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።
የሰቡትና የወፈሩት አንዳንድ በጎች፣ ምስኪኖችንና የከሱትን በጎች እየገፉ ከበረት ሲያስወጡአቸው፣ በቀንዳቸው ሲወጉአቸው፣ ሲያቆስሉአቸው፣ ሲያደሙአቸው፣ የሚጠጡትን ውኃ ሲያደፈርሱባቸው፣ ምግባቸውን ሲረግጡባቸው እያዩ ከመቀመጫቸው ላለመነሳት ዝም ብለው እንደሚያዩ ምንደኞች ያይደለ እውነተኛ እረኛ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። የክርስቶስን አርዓያ የተከተሉ ደገኛ መምህራንም በጎች የተባሉ ምዕመናንን በእውነተኛ ትምህርት ይጠብቋቸዋል። ምንደኛ የሆኑ ክፉ መምህራን ግን በጎች የተባሉ ምዕመናንን አቁስለውና አድምተው ከበረት ያወጧቸዋል፤ በሌሎች ፈተናዎች ምዕመናንን ከመጠበቅ ቸል ይላሉ።
ቸር ጠባቂ በጎቹን ይጠብቃል፤ ይንከባከባቸዋልም።
ቸር ጠባቂ በጎቹን ከክፉ ሁሉ ይጠብቃል፤ የሚያስፈልጋቸውንም ነገር ሁሉ ያውቃል። ጠቦቶቹን በክንዱ ሰብስቦ በብብቱ ይሸከማቸዋል። የሚያጠቡትንም በቀስታ ይመራል (ኢሳ 40፡11)። ጭቃውን ሳይጠየፍ ይሸከማቸዋል፤ ይንከባከባቸዋል (ሉቃ 15፡6)። ምንደኛ የሆነ እረኛ ግን የራሱን ፍላጎት እንጂ የበጎቹን ፍላጎት አያውቅም፤ እነርሱም አያውቁትም። በጎቹን ይበትናቸዋል፤ በጎቹን ይጠቀምባቸዋል እንጂ አይጠብቃቸውም፤ አይጠቅማቸውምም። ጠፍተን ሳለ የፈለገን የሚንከባከበንና የሚመግበን ቸር ጠባቂያችን ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።
እንደ ምንደኛ (ቅጥረኛ) በጎቹን በማሰማራት ፈንታ ወደ እረፍት መስክ ራሱን ያላሰማራ፤ በአደራና በጠባቂነት የተሰጣቸውን በጎች እያረዱ እየበሉ አውሬ በላቸው እንደሚሉ ቅጥረኞች ያይደለ፤ በጎች እሰከሚበርዳቸው ድረስ ያለ አግባብ ፀጉራቸውን እንደሚሸልቱ ቅጥረኛ ያልሆነ፤ ታማሚ በጎችን እንዳላከሙ፤ ደካሞችን እንዳላዳኑ፤ ሰባራዎችን እንዳልጠገኑ፤ የጠፉትን በጎች ወደ መንጋው በመመለስ ፈንታ ወሬያቸውን በመሰለቅ በወንበራቸው ተቀምጠው እንዳልሰበሰቡ እረኞች ያይደለ የጠፉትን የሚሰበስብ የቤተክርስቲያን ጠባቂዋ እርሱ ነው።
ታኅሣሥ ፳፬
ልደቱ ለአቡነ ተክለ ሃይማኖት
ታኅሣሥ ሃያ አራት በዚህች ዕለት ጌታችን በቃሉ ''ሐዲስ ሐዋርያ'' ብሎ የሾማቸው የኢትዮጵያ ብርሃኗ የሆኑ የደብረ ሊባኖሱ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ልደታቸው ነው፡፡
እግዚአብሔር አምላካችን ለኢትዮጵያ ሐዲስ ሐዋርያ አድርጎ የመረጣቸው ጻድቁ አባታችን ተክለ ሃይማኖት በሊቀ መላእክት በቅዱስ ሚካኤል አብሳሪነት ከአባታቸው ከካህኑ ጸጋ ዘአብና ከእናታቸው ከቅድስት እግዚእ ኀረያ መጋቢት 24 ቀን ተፀንሰው ታኅሣሥ 24 ቀን 1197 ዓ.ም ተወለዱ፡፡ ጻድቁ በተወለዱ በሦስተኛው ቀን ከእናታቸው ዕቅፍ ወርደው ‹‹አሐዱ አብ ቅዱስ አሐዱ ወልድ ቅዱስ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ›› ማለትም ‹‹አንዱ አብ ቅዱስ ነው አንዱ ወልድ ቅዱስ ነው አንዱ መንፈስ ቅዱስ ቅዱስ ነው›› በማለት የፈጠራቸውን አምላክ አመስግነውታል፡፡ ወላጆቻቸውም ስማቸውን ፍሥሐ ጽዮን አሏቸው፡፡ ይኸውም የጽዮን ተድላዋ ደስታዋ ማለት ነው፡፡ የወላጆቻቸው የቀድሞ ስማቸው ዘርዐ ዮሐንስና ሣራ ይባል ነበር፡፡
ቅዱሳን አባቶቻችን እነ አቡነ ተክለ ሃይማኖትና እነ አቡነ ዜና ማርቆስ ሌሎቹም እነ አቡነ ሳሙኤል ዘወገግ፣ አቡነ ሕፃን ሞዐ፣ አቡነ አኖሪዮስ(ትልቁ)፣ አቡነ ገላውዲዮስ፣ አቡነ ማትያስ ዘፈጠጋርና አቡነ ቀውስጦስ ዘመሐግል የትውልዳቸው መሠረት ኢያሱ ለሌዋውያን ክፍል ትሆን ዘንድ ከለያት ከኢየሩሳሌም ነው፡፡ ስማቸው የተጠቀሱት እነዚህ ቅዱሳን አባቶቻችን የወንድማማቾች ልጆች ሲሆኑ ከአዳም ጀምሮ 61ኛ ትውልድ ናቸው፡፡ ይኸውም እንዴት ነው ቢሉ ትውልዱ ከአዳም ጀምሮ በካህኑ አሮን በኩል የሆነውና የሌዋዊያን ሊቀ ካህን የነበረው የሳዶቅ ልጅ አዛርያስ በንጉሥ ሰሎሞን ዘመን ከታቦተ ጽዮንና ከብዙ ሌዋዊያን ካህናት ጋር ሊቀ ካህን ሆኖ ከኢየሩሳሌም ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ አክሱም ተቀምጦ ኖረ፡፡ የኦሪትንም ሕግ እየዞረ ለኢትዮጵያ ሰዎች አስተማረ፡፡ ትውልዱም በአብርሃ ወአጽብሓና በአባ ሰላማ ዘመን እስከነበረው እንበረም የሚባለው ጻድቅ ድረስ ደረሰ፡፡ የእንበረምም ትውልድ ደገኛው ሕይወት ብነ በጽዮን ድረስ ደረሰ፡፡ ሕይወት ብነ በጽዮንም የደማስቆ ምድር ከሚሏት ከወለቃ ሀገር የመኮንን ልጅ የሆነችውን ወለተ ሳውልን አግብቶ አበይድላን ወለደ፡፡ አበ ይድላም በንጉሡ ድልዓዥን ዘመነ መንግሥት ለ150 ካህናት አለቃ ሆኖ በወለቃ ሀገር የክርስቶስን የወንጌል ሕግ እያስተማረ ብዙዎችን አጠመቀ፡፡ እስከ ሸዋ ምድር ድረስ እያስተማረ መጥቶ በሸዋ ምድር ተቀመጠ፡፡ ብዙ አብያተ ክርስቲያናትንም አሳነጸ፡፡ እጅግ አስደናቂ ተአምራትንም ያደርግ ነበር፡፡ ‹‹በሸዋ ጽላልሽ ተቀምጦ ሲያስተምርም በአንዲት ቀን እስከ ሁለት መቶ ሺህ ሕዝብ ያጠምቅ ነበር›› በማለት ገድለ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ይመሰክርለታል፡፡
አበይድላ በመጨረሻ በፈቃደ እግዚአብሔር ከሸዋ ጽላልሽ ምድረ ዞረሬ ሚስት አግቶ ሀበነ እግዚእን ወለደ፤ ሀበነ እግዚእም በኩረ ጽዮንን ወለደ፤ በኩረ ጽዮንም ሕዝበ ቀድስን ወለደ፤ እርሱም ነገደ እግዚእ የተባለ ነው፡፡ ሕዝበ ቀድስም ብርሃነ መስቀልን ወለደ፤ እርሱም ዐቃቢነ እግዚእ የተባለ ነው፡፡ ብርሃነ መስቀልም ሕይወት ብነን ወለደ፤ እርሱም ሴትን ወለደ፡፡ ሴትም ወረደ ምሕረትን ወለደ፡፡ ወረደ ምሕረትም ዘካርያስን ወለደ፡፡ ዘካርያስም የእነ አቡነ ተክለ ሃይማኖት አባት የሆኑ 6 ወንድማማች ልጆችን ወለደ፡፡ እነርሱም እንድርያስ፣ አርከሌድስ፣ ዘርዐ አብርሃም፣ ዘርዐ ዮሐንስ ወይም ጸጋ ዘአብ፣ ቀሲስ ዮሐንስና ቀሲስ ዮናስ ናቸው፡፡ እንድርያስም ሳሙኤል ዘወገግን ወለደ፤ አርከሌድስም ሕፃን ሞዐን ወለደ፤ ዘርዐ አብርሃምም ታላቁን አኖርዮስን ወለደ፤ ዘርዐ ዮሐንስ ወይም ጸጋ ዘአብም ተክለ ሃይማኖትን ወለደ፤ ቀሲስ ዮሐንስም ዜና ማርቆስን ወለደ፣ ቀሲስ ዮናስ ደግሞ የፈጠጋሩን ማትያስንና ገላውዲዮስን ወለዳቸው፡፡ ገላውዲዮስም የመሐግሉ ቀውስጦስን ወለደ፡፡ እነዚህ ደጋግ ቅዱሳን በእናታቸውም በኩል እንዲሁ በዝምድና የተሳሰሩ ናቸው፡፡ ማቴዎስ የተባለው ደገኛ ክርስቲያን የሸዋ ገዥ የነበረ ሲሆን አንድ ወንድ ልጅ መድኃኒነ እግዚእንና ሦስት ሴቶች ልጆችን ወለደ፡፡ ሶስቱ ሴቶች ልጆችም እምነ ጽዮን፣ ትቤ ጽዮንና ክርስቶስ ዘመዳ ይባላሉ፡፡ ሦስቱ እኅትማማቾችም ደጋጎቹን አባቶቻችንን ወለዱልን፡፡ እምነ ጽዮን የእነ ዜና ማርቆስን እናት ማርያም ዘመዳንና ወለደች፡፡ ትቤ ጽዮንም ሕፃን ሞዐን ወለደች፡፡ ክርስቶስ ዘመዳ ደግሞ ታላቁን አኖሬዎስን ወለደች፡፡ የፈጠጋሩ ገዥ መድኃኒነ እግዚእ ደግሞ የተክለ ሃይማኖትን እናት እግዚእ ኀረያን ወይም በሌላ ስሟ ሣራን ወለደ፡፡
አቡነ ተክለ ሃይማኖት ከልጅነታቸው ጀምሮ በወላጅ አባታቸው በካህኑ ቅዱስ ጸጋ ዘአብ ግብረ ዲቁናን ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንን ሲያጠኑ ቆይተው በ15 እና በ22 ዓመታቸው ከእስክንድርያው ሊቀ ጳጳስ ከአቡነ ቄርሎስ (ጌርሎስ) ዲቁናንና ቅስናን ተቀብለዋል፡፡ ብፁዕ ወቅዱስ አባታችን ቅድስት ቤተክርስቲያንን በወጣትነት ዕድሜያቸው ያገለግሉ እንደነበር በዚህ ይታወቀል፡፡
ከዕለታት በአንዱ ቀን አባታችን ከጓደኞቻቸው ጋር ለአደን ወደ ዱር ሄደው ሳለ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ተገልጦ ታያቸው፡፡ ቅዱስ አባታችንም ‹‹እንደዚህ ባለ ገናንነት የማይህ ጌታዬ ማነህ?›› ባሉት ጊዜ ቅዱስ ሚካኤል ‹‹ዘወትር የምጠብቅህ ካንተ የማልለይ እናትህንና አባትህንም ስላንተ ከውኃ ስጥመትና ከምርኮ ያዳንኳቸው እኔ ሚካኤል ነኝ፡፡ ከእንግዲህ አውሬ አዳኝ አትሁን፤ ሰውን ወደ እግዚአብሔር ለመመለስ ሰውን በትምህርት የምታድን ሁን እንጂ፡፡ እነሆ እግዚአብሔር ጽኑዕ ሥልጣን ሰጥቶሃልና፤ ሙት ታስነሣለህ፤ ድውያንን ትፈውሳለህ፤ አጋንንትም አንተን በመፍራት ይሸሻሉ፡፡ ስምህ ፍሥሐ ጽዮን አይሁን፤ ተክለ ሃይማኖት ይሁን እንጂ፡፡ ትርጓሜውም ተክለ አብ፥ ተክለ ወልድ፥ ተክለ መንፈስ ቅዱስ ማለት ነው›› አላቸው፡፡
ቅዱስ ሚካኤል ይህን ሲነግራቸው ጌታችን በሥጋ ከደቀ መዛሙርቱ ጋር እንደነበር ሆኖ መልከ መልካም ጎልማሳ መስሎ ታያቸው፡፡ ጌታችንም ‹‹ወዳጄ እንዴት ሰነበትክ? ቸር አለህን?›› አላቸው፡፡ አቡነ ተክለ ሃይማኖትም ‹‹ጌታዬ ሆይ አንተ ማነህ?›› ብለው ሲጠይቁት ጌታችንም ‹‹እኔ የዓለም መድኃኒት ኢየሱስ ነኝ፤ በናትህ ማኅፀን ፈጥሬህ ያከበርኩህ እኔ ነኝ፡፡ በተወለድክ በሦስተኛው ቀን አሐዱ አብ ቅዱስ አሐዱ ወልድ ቅዱስ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ ብለህ ታመሰግነኝ ዘንድ የምስጋና ሀብት ያሳደርኩብህ እኔ ነኝ፡፡ በርሃብ ዘመን በቤት የሚያሻው ምግብ ሁሉ ቅቤው፣ የስንዴው ዱቄት በእናት በአባትህ ቤት ይመላ ዘንድ በእጅህ ሀብተ በረከት ያሳደርኩብህ እኔ ነኝ፡፡ ያንን ሰው አንተን በተጣላ ጊዜ በነፋስ አውታር የሰቀለኩት በመዓት ጨንገር የገረፍኩት እኔ ነኝ፡፡ ውኃ ጠምቶህ በለመንከኝ ጊዜ ከደረቅ መሬት የጣፈጠ ውኃ ያመነጨሁልህ እኔ ነኝ፡፡ ከልጅነትህ ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ ብዙ ተአምራት እያደረግሁ በአንተ እጅ የታመሙትን ያዳንኳቸው እኔ ነኝ፡፡ ወደፊትም አደርግልሃለሁ›› አላቸው፡፡ ይህንን ብሎ በእጆቹ ባረካቸውና ‹‹ንሣእ
"ባሰማት ጊዜ"
ስሙ ገብርኤል የተባለ ለድንግል ነገራት መልካም ዜና
እንደምትወልደው ወልድን በድንግልና(፪)
ባሰማት ጊዜ ቃሉን ቅዱስ ገብርኤል በለዛ(፪)
ድንግል ቀረበች ወደእርሱ ፍጹም ትሕትናን ይዛ(፪)
ትጸንሻለሽ ሲላት መልአኩ ፋጹም በልቧ ሳትመካ
እንደቃልህ ይሁን አለቺው በቃሉ ተማርካ(፪)
አዝ---
የዓለም መድኃኒት ነውና ካንቺ የሚወለደው በመንፈስ ቅዱስ
ትሰይሚዋለሽ ስሙን ብለሽ ኢየሱስ(፪)
አዝ---
እፁብ ድንቅ ነው ሁልጊዜ ለድንግል ማርያም የተሰጣት ክብር
የአምላክ እናት መሆን መመረጥ ከሴቶች መካከል(፪)
አዝ---
ጸጋን የተመላሽ ድንግል ሆይ ይገባሻል አንቺ ክብርና ምስጋና
የክብር ባለቤት ሁልጊዜ ካንቺ ጋር ነውና(፪)
አዝ---
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
ታኅሣሥ ፳፪
ብሥራተ ገብርኤል
ታኅሣሥ ሃያ ሁለት በዚህች ዕለት ብርሃናዊው መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ለእመቤታችን አምላክን እንደምትወልድ ያበሰረበት መታሰቢያ ነው፡፡ ይኸውም ከዘጠኙ የጌታ ዓበይት በዓላት አንዱ ነው። ይኸውም ‹‹ልዑል እግዚአብሔር ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤልን ‹ሂድና ለጽዮን ልጅ ለድንግል የእግዚአብሔር የባሕርይ ልጅ ወደአንቺ መጥቶ ኃይለ ልዑል ወልድ ሥጋሽን ለብሶ ሰው ይሆናል፤ ይኸውም ካንቺ የሚወለደው ጽኑዕ ነው ብለህ ንገራት› አለው፡፡ ‹ደንቆሮዎች የሚሰሙበት፣ ድዳዎቸ የሚናገሩበት፣ ዕውራንም የሚያዩበት፣ ሙታን የሚነሡበት፣ ለምጻሞች የሚነጹበት፣ ሐንካሳዎች የሚሄዱበት፣ በጨለማ ውስጥ የነበሩ ሰዎች ብርሃን የሚያዩበት ጊዜ እነሆ ደረሰ ብለህ ንገራት› አለው፡፡
ቅዱስ ገብርኤልም ይህን ሰምቶ በግንባሩ ተደፍቶ ልዑል እግዚአብሔርን ‹ጌታ ሆይ! የምትነግረኝ ይደረግ ዘንድ እንደምን ይሆናል?› አለው፡፡ ጌታም ‹የጀመርኩትን ቸርነት ፈጸምኩ፣ የወይን ግንድ ይቆረጣል (ወልደ እግዚአብሔር ይሞታል)፣ ወይራም ከበለስ ጋር ይተከላል (መስቀል ይተከላል)፣ ቅጽሮችም ይቀጸራሉ (ምግባር ከሃይማኖት ጋር ይሠራል)፣ የኤልፍና የሌሚ ወገን ይነሣል፡፡ ገብርኤል ሆይ! ሄደህ ለዳዊት ልጅ ‹እግዚአብሔር ከአንቺ ጋር ነውና ደስ ይበልሽ› ብለህ አብሥራት› አለው፡፡ ‹ለዘለዓለም ነግሦ የሚኖረውን እነሆ ትፀንሳለሽ በላት› አለው፡፡ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤልም ይህን ሰምቶ ሰገደ፡፡ ልብሱንም በላዩ ይዞ በመስቀል ቀኝ ይወርድ ዘንድ ወደደ፡፡ ጌታም ‹መግባትህና መውጣትህ በፍቅር አንድነት ይሁን› አለው፡፡ ‹ዘካርያስን ረግመህ አንደበቱን እንዳሰርህ እርሷን እንዳታሳዝናት ይልቁንም አብዝተህ ደስ አሰኛት አንጂ› አለው፡፡ ቅዱስ ገብርኤልም ይህን ሰምቶ ፈጽሞ ደስ እያለው ሊባኖስ ከሚባል ተራራ እስኪሰማ ድረስ ክንፉን እያማታ ወረደ፡፡ በዚህም ጊዜ በዙሪያው ያሉ ሁሉ ‹ይህ የምንሰማው ምንድነው?› ይሉ ነበር፡፡ የተደረገበትንም ቦታ አላወቁትም ነበር፡፡››
እመቤታችንን በ3 ዓመቷ እናትና አባቷ ብፅዓት አድርገው ለእግዚአብሔር ሰጥተዋታልና ካህናትም በቤተ መቅደስ ከመካነ ደናግል አስገብተዋት በመልአኩ በቅዱስ ፋኑኤል አማካኝነት ኅብስት ሰማያዊ ጽዋዕ ሰማያዊ እየመጣላት ያንን እየተመገበች ቅዱሳን መላእክት እየጎበኟት 12 ዓመት ኖራለች፡፡ በ15 ዓመቷ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ለእመቤታችን ጌታችንን እንደምትወልድ በዚህች ዕለት አብሥሯታል፡፡ በመጀመሪያ እመቤታችን ውኃ ቀድታ ስትመለስ የጠተማ ውሻ እያለከለከ ሲመጣ ብታየው ለፍጥረት ሁሉ የምትራራ ናትና በወርቅ ጫማዋ ለዛ ለተጠማው ውሻ ውኃ ስታጠጣ አብሯት የነበሩ ሴቶች ‹‹ማድጋሽን አጎደልሺው፣ ቀድቼ እሞለዋለሁ እንዳትይ ጉድጓዱ ጥልቅ ነው መቅጃም የለሽም›› አሏት፡፡ ክብርት እመቤታችንም ‹‹ውሃ የሚገኘው ከወደላይ ነው እንጂ ከወደታች ነውን? ፍጥረቱን ያጠጣ ጌታ ይሞላልኛል›› አለቻቸው፡፡ ማድጋዋም በተአምራት ሞልቶ ተገኘ፡፡ ሴቶቹም ዳግመኛ ‹‹በዚህ ዘመን አምላክ ከድንግል ይወለዳል ይላሉ ካንቺ ይሆን?›› እያሉ ሲዘብቱባት ወዲያው ከወደኋላዋ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል መጥቶ ‹‹እነሆ ትጸንሻለሽ›› አላት፡፡ እመቤታችንም ዞር ብትል የተናገራትን አጣችው፡፡ በዚህም ጊዜ ‹‹አባቴን አዳምን እናቴን ሔዋንን ያሳተ ጠላት ይሆናል›› ብላ ሄደች፡፡
ዳግመኛም እመቤታችን ከቤት ደርሳ ማድጋዋን ስታስቀምጥ መልአኩ አሁንም በድምፅ ‹‹እነሆ ትጸንሻለሽ›› አላት፡፡ እመቤታችንም ይህን ጊዜ ‹‹ምነው ይህስ ነገር ደጋገመኝ እንዲህ ያለውን ነገር ቤተ መቅደስ ሄደው ሊረዱት ይገባል›› ብላ ወደ ቤተ መቅደስ ሄዳ ወርቅና ሐር እያስማማች ስትፈት መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል እሁድ ቀን በ3 ሰዓት በገሃድ ተገለጸላትና እጅ እየነሳ እየሰገደ አበሠራት፡፡ ‹‹የዕውነተኛ ንጉሥ እናቱ እመቤታችን ላንቺ ፍቅር አንድነት ይባል›› አላት፡፡ ዳግመኛም ‹‹አንቺ ከሴቶች ይልቅ ተለይተሸ ንዕድ ክብርት ነሽ›› አላት፡፡ አምላክን የወለደች በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ የጸናቸ ክብርት እመቤታችንም የብርሃናዊውን መአልክ የቅዱስ ገብርኤልን ቃል በሰማች ጊዜ ‹‹እንዲህ ያለውን ሰላምታ እንደምን ይቀበሏል! እንዴትስ መቀበል ይቻላል? እንጃ›› አለችው፡፡ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤልም ‹‹ማርያም ሆይ! መንፈስ ቅዱስ ያድርብሻል፣ ኃይለ ልዑል ወልድም ሥጋሽን ይለብሳልና አይዞሽ አትፍሪ›› አላት፡፡ ዳግመኛም ‹‹ይህ ካንቺ የሚወለደው ጽኑ ከሃሊ ነው፡፡ ስሙንም ኢየሱስ ትዪዋለሽ፣ እርሱ ታላቅ ይሆናል የልዑል ልጅም ይባላል፣ ጌታ አምላክም የአባቱን የዳዊትን ዙፋን ይሰጠዋል፣ በያዕቆብ ቤትም ላይ ለዘለላም ይነግሣል፣ ለመንግሥቱም መጨረሻ የለውም›› አላት፡፡ እመቤታችንም መልአኩን ‹‹ምድር ያለ ዘር ፍሬን አትሰጥምና እኔ ወንድ ስለማላውቅ ይህ እንዴት ይሆናል?›› አለችው፡፡ መልአኩም መልሶ ‹‹መንፈስ ቅዱስ በአንቺ ላይ ይመጣል፣ የልዑልም ኃይል ይጸልልሻል ስለዚህ ደግሞ ከአንቺ የሚወለደው ቅዱስ የእግዚአብሔር ልጅ ይባላል። እነሆም ዘመድሽ ኤልሳቤጥ እርሷ ደግሞ በእርጅናዋ ወንድ ልጅ ፀንሳለች፡፡ ለእርስዋም መካን ትባል ለነበረችው ይህ ስድስተኛ ወር ነው፣ ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር የለምና›› አላት፡፡ ክብርት እመቤታችንም ይህን ጊዜ ‹‹እነሆኝ የጌታ ባሪያ እንደ ቃልህ ይሁንልኝ›› አለችው፡፡ መልአኩም ከእርሷ ዘንድ ሄዶ ተሠወረ፡፡ አካላዊ ቃልም በማኅፀኗ አደረ፡፡ በዚያችም ቅጽበት የእመቤታችን የፊቷ መልክ ተለወጠ፣ እንደፀሐይም አሸበረቀ፡፡
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
‹‹እንዘ ትፈትል ወርቀ ወሜላተ ወሪዳ ምድረ ቆላ ገብርኤል መጽአ እንዘ ይረውጽ በሰረገላ ክንፎ ክንፎ ክንፎ ጸለላ ተፈስሒ ተፈስሒ ለድንግል ይቤላ፤
ትርጉም ፦ወደ ቆላው ምድር ወርዳ እመቤታችን ወርቅን ከሐር ጋር አስማምታ እየፈተለች ሳለች መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል በሰረገላ እየሮጠ መጣ፣ ክንፉንም እያማታ እየሰገደ ድንግል ሆይ ደስ ይበልሽ አላት››
"ተፈሥሒ ፍሥሒት ኦ ምልዕተ ጸጋ፤ ጸጋን የሞላብሽ ሆይ ደስ ይበልሽ" ሉቃ 1፡28
…ደስ የተሰኘህ ሆነህ ምሥራችን የተናገርክ መልአኩ ገብርኤል ሆይ የተሰጠህ ክብር ታላቅ ነው። ወደኛ የመጣ የጌታን ልደት ነገርኸን ለድንግል ማርያም ጸጋን የተመላሽ ሆይ እግዚአብሔር ካንቺ ጋር ነውና ደስ ይበልሽ ብለህ አበሰርኻት ። ቅድስት ሆይ ለምኝልን ።…
እንኳን አደረሳችሁ!
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
"የራማው ልዑል ገብርኤል"
የራማው ልዑል ገብርኤል (፪)
ተመላለስ መሐላችን ስምህን ጠርተን ና ስንልህ(፪)
ብርሃን ልብሱ እሳታዊ መልአክ
አንተ አማልደን ከመሐሪው አምላክ (፪)
አዝ….
የምስራች ነጋሪ ድንቅ ልደት አብሳሪ
የጽድቅ ፋና የምሕረት ጎዳና (፪)
አዝ….
ላመኑብህ ለተማጸኑህ
ፈጥኖ ደራሽ አለኝታቸው ነህ (፪)
አዝ….
የአናንያ የአዛርያ የሚሳኤል ከለላቸው
ከእሳት ነበልባል ያዳንካቸው (፪)
አዝ….
ምሰሶ አምዳችን መጠጊያችን
ቅዱስ ገብርኤል ጠባቂያችን (፪)
አዝ….
ዕለት ዕለት የምንማልድህ
ልጀችህን ይምራን መንፈስህ(፪)
አዝ....
©ዓምደ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
ታኅሣሥ ፲፱
ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል
ታኅሣሥ ዐስራ ዘጠኝ በዚህች ቀን ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ሠለስቱ ደቂቅን ከእሳት ያዳነበት ነው፡፡ ንጉሥ ናቡከደነፆር ከአባታቸው ከይሁዳው ንጉሥ ከኢዮአቄም ጋር የማረካቸው አናንያ፣ ሚሳኤልና አዛርያ እግዚአብሔር በዚህች ዕለት መልአኩን ልኮ ታላቅ ተአምር አድርጎላቸዋል፡፡ ንጉሥ ናቡከደነፆር እነዚህን ወጣቶች በቤተ መንግሥቱ ውስጥ ጥበብን እያስተማረ ካሳደጋቸው በኋላ በባቢሎን ሀገሮች ሁሉ ውስጥ ሾማቸው፡፡ ከዚህም በኋላ ንጉሡ የወርቅ ምስል በሠራ ጊዜ መኳንንቱንና በግዛቱ ውስጥ ያሉ ሁሉ ለዚያ ምስል እንዲሰግዱ አዘዘ፡፡ በዚህም ጊዜ ለጣዖቱ ባለመስገድ እግዚአብሔርን ብቻ በማምለክ የጸኑት እነዚህ ሦስት ወጣቶች ብቻ ነበሩ፡፡ ስለ እነርሱ በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ እንዲህ ተብሎ ነው የተጻፈው፡-
‹‹ንጉሡ ናቡከደነፆር ቁመቱ ስድሳ ክንድ ወርዱም ስድስት ክንድ የሆነውን የወርቁን ምስል አሠራ፤ በባቢሎንም አውራጃ በዱራ ሜዳ አቆመው፡፡ ንጉሡም ናቡከደነፆር መኳንንትንና ሹማምቶችን፥ አዛዦችንና አዛውንቶችን፥ በጅሮንዶችንና አማካሪዎችን፣ መጋቢዎችንም፣ አውራጃ ገዦችንም ሁሉ ይሰበስቡ ዘንድ፣ ንጉሡም ናቡከደነፆር ላቆመው ምስል ምረቃ ይመጡ ዘንድ ላከ፡፡ በዚያን ጊዜም መኳንንቱና ሹማምቶቹ፣ አዛዦቹና አዛውንቶቹ፣ በጅሮንዶቹና አማካሪዎቹ፣ መጋቢዎቹና አውራጃ ገዦቹ ሁሉ ንጉሡ ናቡከደነፆር ላቆመው ምስል ምረቃ ተሰበሰቡ፤ ናቡከደነፆርም ባቆመው ምስል ፊት ቆሙ፡፡ አዋጅ ነጋሪውም እየጮኸ እንዲህ አለ፡- ‹ወገኖችና አሕዛብ በልዩ ልዩ ቋንቋም የምትናገሩ ሆይ! የመለከትንና የእንቢልታን፣ የመሰንቆንና የክራርን፣ የበገናንና የዋሽንትን፣ የዘፈንንም ሁሉ ድምፅ በሰማችሁ ጊዜ፣ ተደፍታችሁ ንጉሡ ናቡከደነፆር ላቆመው ለወርቁ ምስል እንድትሰግዱ ታዝዛችኋል፡፡ ተደፍቶም የማይሰግድ በዚያን ጊዜ በሚነድድ እሳት እቶን ውስጥ ይጣላል፡፡› ስለዚህ በዚያን ጊዜ አሕዛብ ሁሉ የመለከቱንና የእንቢልታውን፣ የመሰንቆውንና የክራሩን፣ የበገናውንና የዘፈኑንም ሁሉ ድምፅ በሰሙ ጊዜ፣ ወገኖችና አሕዛብ በልዩ ልዩ ቋንቋም የተናገሩ ሁሉ ተደፉ፤ ንጉሡም ናቡከደነፆር ላቆመው ለወርቅ ምስል ሰገዱ፡፡
በዚያን ጊዜም ከለዳውያን ቀርበው አይሁድን ከሰሱ፡፡ ለንጉሡም ለናቡከደነፆር ተናገሩ እንዲህም አሉ ‹ንጉሥ ሆይ! ሺህ ዓመት ንገሥ፡፡ አንተ ንጉሥ ሆይ የመለከትንና የእንቢልታን፣ የመሰንቆንና የክራርን፣ የበገናንና የዋሽንትን፣ የዘፈንንም ሁሉ ድምፅ የሚሰማ ሰው ሁሉ ተደፍቶ ለወርቁ ምስል ይስገድ፤ ተደፍቶም የማይሰግድ በሚነድድ እሳት እቶን ውስጥ ይጣላል ብለህ አዘዝህ፡፡ በባቢሎን አውራጃ ሥራ ላይ የሾምሃቸው ሲድራቅና ሚሳቅ አብደናጎም የሚባሉ አይሁድ አሉ፤ ንጉሥ ሆይ! እነዚህ ሰዎች ትእዛዝህን እንቢ ብለዋል፤ አማልክትህን አያመልኩም፥ ላቆምኸውም ለወርቁ ምስል አይሰግዱም፡፡› ናቡከደነፆርም በብስጭትና በቍጣ ሲድራቅንና ሚሳቅን አብደናጎንም ያመጡ ዘንድ አዘዘ፤ እነዚህንም ሰዎች ወደ ንጉሡ ፊት አመጡአቸው፡፡ ናቡከደነፆርም ሲድራቅና ሚሳቅ አብደናጎም ሆይ! አምላኬን አለማምለካችሁ ላቆምሁትም ለወርቁ ምስል አለመስገዳችሁ እውነት ነውን? አሁንም የመለከቱንና የእንቢልታውን የመሰንቆውንና የክራሩን የበገናውንና የዋሽንቱን የዘፈኑንም ሁሉ ድምፅ በሰማችሁ ጊዜ ተደፍታችሁ ላሠራሁት ምስል ብትሰግዱ መልካም ነው፤ ባትሰግዱ ግን በዚያ ጊዜ በሚነድድ እሳት እቶን ውስጥ ትጣላላችሁ፤ ከእጄስ የሚያድናችሁ አምላክ ማን ነው?›› ብሎ ተናገራቸው፡፡ ሲድራቅና ሚሳቅ አብደናጎም መለሱ ንጉሡን ‹ናቡከደነፆር ሆይ! በዚህ ነገር እንመልስልህ ዘንድ አስፈላጊያችን አይደለም፡፡ የምናመልከው አምላካችን ከሚነድደው ከእሳቱ እቶን ያድነን ዘንድ ይችላል፤ ከእጅህም ያድነናል፡፡ ነገር ግን ንጉሥ ሆይ! እርሱ ባያድነን አማልክትህን እንዳናመልክ ላቆምኸውም ለወርቁ ምስል እንዳንሰግድለት እወቅ› አሉት፡፡
የዚያን ጊዜም ናቡከደነፆር በሲድራቅና በሚሳቅ በአብደናጎም ላይ ቍጣ ሞላበት፡፡ የፊቱም መልክ ተለወጠባቸው፡፡ እርሱም ተናገረ የእቶንም እሳት ይነድድ ከነበረው ይልቅ ሰባት እጥፍ አድርገው እንዲያነድዱት አዘዘ፡፡ ሲድራቅንና ሚሳቅንም አብደናጎንም ያስሩ ዘንድ ወደሚነድድም ወደ እቶን እሳት ይጥሉአቸው ዘንድ በሠራዊቱ ውስጥ ከነበሩት ኃያላን አዘዘ፡፡ የዚያን ጊዜም እነዚህ ሰዎች ከሰናፊላቸውና ከቀሚሳቸው ከመጐናጸፊያቸውም ከቀረውም ልብሳቸው ጋር ታስረው በሚነድድ በእቶን እሳት ውስጥ ተጣሉ፡፡ የንጉሡም ትእዛዝ አስቸኳይ ስለሆነ የእቶኑም እሳት እጅግ ስለሚነድድ፣ ሲድራቅንና ሚሳቅን አብደናጎንም የጣሉአቸውን ሰዎች የእሳቱ ወላፈን ገደላቸው፡፡ እነዚህም ሦስቱ ሰዎች ሲድራቅና ሚሳቅ አብደናጎም ታስረው በሚነድደው በእቶኑ እሳት ውስጥ ወደቁ፡፡ የዚያን ጊዜም ንጉሡ ናቡከደነፆር ተደነቀ ፈጥኖም ተነሣ፤ አማካሪዎቹንም ‹ሦስት ሰዎች አስረን በእሳት ውስጥ ጥለን አልነበረምን?› ብሎ ተናገራቸው፡፡ እነርሱም ‹ንጉሥ ሆይ! እውነት ነው› ብለው ለንጉሡ መለሱለት፡፡ እርሱም ‹እነሆ እኔ የተፈቱ በእሳቱም መካከል የሚመላለሱ አራት ሰዎች አያለሁ፤ ምንም አላቈሰላቸውም፤ የአራተኛውም መልክ የአማልክትን ልጅ ይመስላል› ብሎ መለሰ፡፡ የዚያን ጊዜም ናቡከደነፆር ወደሚነድደው ወደ እሳቱ እቶን በር ቀርቦ ‹እናንተ የልዑል አምላክ ባሪያዎች ሲድራቅና ሚሳቅ አብደናጎም! ኑ ውጡ› ብሎ ተናገራቸው፡፡ ሲድራቅና ሚሳቅም አብደናጎም ከእሳቱ መካከል ወጡ፡፡
መሳፍንቱና ሹማምቶቹም አዛዦቹና የንጉሡ አማካሪዎች ተሰብስበው እሳቱ በእነዚያ ሰዎች አካል ላይ ኃይል እንዳልነበረው፣ የራሳቸውም ጠጕር እንዳልተቃጠለች ሰናፊላቸውም እንዳልተለወጠ፣ የእሳቱም ሽታ እንዳልደረሰባቸው አዩ፡፡ ናቡከደነፆርም መልሶ ‹መልአኩን የላከ ከአምላካቸውም በቀር ማንም አምላክ እንዳያመልኩ ለእርሱም እንዳይሰግዱ ሰውነታቸውን አሳልፈው የሰጡትን የንጉሡንም ቃል የተላለፉትን በእርሱ የታመኑትን ባሪያዎቹን ያዳነ፣ የሲድራቅና የሚሳቅ የአብደናጎም አምላክ ይባረክ፡፡ እኔም እንደዚህ የሚያድን ሌላ አምላክ የለምና በሲድራቅና በሚሳቅ በአብደናጎም አምላክ ላይ የስድብን ነገር የሚናገር ወገንና ሕዝብ በልዩ ልዩም ቋንቋ የሚናገሩ ይቈረጣሉ፣ ቤቶቻቸውም የጕድፍ መጣያ ይደረጋሉ ብዬ አዝዣለሁ› አለ፡፡ የዚያን ጊዜም ንጉሡ ሲድራቅንና ሚሳቅን አብደናጎንም በባቢሎን አውራጃ ውስጥ ከፍ ከፍ አደረጋቸው፡፡›› ትንቢተ ዳንኤል 3፡1-30፡፡
አምላካችን ከቅዱስ ገብርኤል ረድኤት በረከት ያካፍለን ፤ የመልአኩ ፈጣን ምልጃ አይለየን!
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
#ተዘክሮተ_ሞት
«ለመተኛት ወደ አልጋህ ባመራህ በቀረብህ ጊዜ አልጋዬ፡ ምን አልባት በዚህ ሌሊት ለእኔ መቃብሬ ልትኾኚ ይኾን ይኾናል፤ በጊዜአዊው ዕንቅልፍ ፈንታ በዚህ ሌሊት ያኛው እንቅልፍ (ሞት) ይመጣብኝም እንደ ኾነ አላውቀውም በላት ።ስለዚህ ነጻ እግሮች እያሉህ ከመልካም ሥራ በኋላ ሩጥ፤ ከታሠሩ መፈታት በማይችሉበት ማሰሪያ ከመታሠራቸው በፊት፡፡ የእጆችህ ጣቶችም እስካሉህ ድረስ ሞት ከመምጣቱ በፊት በጸሎት ፊትህንና መላ ሰውነትህን በተእምርተ መስቀል አማትብ፡፡ ዐይኖች እስካሉህ ድረስ በአቧራ ከመሽፈናቸው በፊት በእንብዕ(በእንባ) ምላቸው።ሰው ሆይ ከዚህ ዓለም መለየትህን አስብ፣ እንዲህም በል፡- እነሆ የታዘዘ መልአክ ከበር ቆሞአል (ደርሶአል)፣ እኔንም ይከተለኛል። ለምን ሊል ዘሊል እኾናለሁ? መመለሻ የሌለው ዘለዓለማዊ መንገድ አለ፡፡መለኮት ደግነት የተነሣ የሰውን ልብ የሚገዛውና ነፍስን ወደ ሕይወት የሚመራት የመጀመሪያው ትምህርት ተዘክሮተ ሞት ነው።.ተዘክሮተ ሞት በሰይጣን እጅግ በብዙ ይጠላል፡፡ እርሱም ከሰው ተዘክሮን ለመንቀል በሙሉ ኃይሉ መሞከርን አይተዉም፡፡ የሚቻለውስ ቢኾን በምድራዊ ሕይወት አሳብ ተብትቦ ተዘክሮተ ሞትን ከሰው ልብ (አእምሮ) ለማስወገድ ምድራዊ መንግሥታትን ለሰው በሰጠው ነበር፡፡ አታላዩ ሰይጣን ተዘክሮተ ሞት በሰው ሁልጊዜም ካለ፣ አሳቡ ለአሁኑ ሕይወት መታለሎች የተጣበቀ ኾኖ እንደማይቀር አልያም የሰይጣን ማታለሎች ሰውን ሊቀርቡት እንደማይችሉ ያውቃል፡፡"
➥ማር ይስሐቅ ሶርያዊ
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox