ethiopian_orthodox | Unsorted

Telegram-канал ethiopian_orthodox - የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

30344

በዚህ Channel ውስጥ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንን ዶግማ ፤ ቀኖና እና ትውፊት የጠበቁ ትምህርቶች ይተላለፉበታል፡፡ ለአስተያየት: ጥቆማና ጥያቄ በዚህ ያግኙን ☞ @Ethiopian_Orthodox_bot Buy ads: https://telega.io/c/Ethiopian_Orthodox

Subscribe to a channel

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

ታኅሣሥ ፲፱
ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል


ታኅሣሥ ዐስራ ዘጠኝ በዚህች ቀን ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ሠለስቱ ደቂቅን ከእሳት ያዳነበት ነው፡፡ ንጉሥ ናቡከደነፆር ከአባታቸው ከይሁዳው ንጉሥ ከኢዮአቄም ጋር የማረካቸው አናንያ፣ ሚሳኤልና አዛርያ እግዚአብሔር በዚህች ዕለት መልአኩን ልኮ ታላቅ ተአምር አድርጎላቸዋል፡፡ ንጉሥ ናቡከደነፆር እነዚህን ወጣቶች በቤተ መንግሥቱ ውስጥ ጥበብን እያስተማረ ካሳደጋቸው በኋላ በባቢሎን ሀገሮች ሁሉ ውስጥ ሾማቸው፡፡ ከዚህም በኋላ ንጉሡ የወርቅ ምስል በሠራ ጊዜ መኳንንቱንና በግዛቱ ውስጥ ያሉ ሁሉ ለዚያ ምስል እንዲሰግዱ አዘዘ፡፡ በዚህም ጊዜ ለጣዖቱ ባለመስገድ እግዚአብሔርን ብቻ በማምለክ የጸኑት እነዚህ ሦስት ወጣቶች ብቻ ነበሩ፡፡ ስለ እነርሱ በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ እንዲህ ተብሎ ነው የተጻፈው፡-
‹‹ንጉሡ ናቡከደነፆር ቁመቱ ስድሳ ክንድ ወርዱም ስድስት ክንድ የሆነውን የወርቁን ምስል አሠራ፤ በባቢሎንም አውራጃ በዱራ ሜዳ አቆመው፡፡ ንጉሡም ናቡከደነፆር መኳንንትንና ሹማምቶችን፥ አዛዦችንና አዛውንቶችን፥ በጅሮንዶችንና አማካሪዎችን፣ መጋቢዎችንም፣ አውራጃ ገዦችንም ሁሉ ይሰበስቡ ዘንድ፣ ንጉሡም ናቡከደነፆር ላቆመው ምስል ምረቃ ይመጡ ዘንድ ላከ፡፡ በዚያን ጊዜም መኳንንቱና ሹማምቶቹ፣ አዛዦቹና አዛውንቶቹ፣ በጅሮንዶቹና አማካሪዎቹ፣ መጋቢዎቹና አውራጃ ገዦቹ ሁሉ ንጉሡ ናቡከደነፆር ላቆመው ምስል ምረቃ ተሰበሰቡ፤ ናቡከደነፆርም ባቆመው ምስል ፊት ቆሙ፡፡ አዋጅ ነጋሪውም እየጮኸ እንዲህ አለ፡- ‹ወገኖችና አሕዛብ በልዩ ልዩ ቋንቋም የምትናገሩ ሆይ! የመለከትንና የእንቢልታን፣ የመሰንቆንና የክራርን፣ የበገናንና የዋሽንትን፣ የዘፈንንም ሁሉ ድምፅ በሰማችሁ ጊዜ፣ ተደፍታችሁ ንጉሡ ናቡከደነፆር ላቆመው ለወርቁ ምስል እንድትሰግዱ ታዝዛችኋል፡፡ ተደፍቶም የማይሰግድ በዚያን ጊዜ በሚነድድ እሳት እቶን ውስጥ ይጣላል፡፡› ስለዚህ በዚያን ጊዜ አሕዛብ ሁሉ የመለከቱንና የእንቢልታውን፣ የመሰንቆውንና የክራሩን፣ የበገናውንና የዘፈኑንም ሁሉ ድምፅ በሰሙ ጊዜ፣ ወገኖችና አሕዛብ በልዩ ልዩ ቋንቋም የተናገሩ ሁሉ ተደፉ፤ ንጉሡም ናቡከደነፆር ላቆመው ለወርቅ ምስል ሰገዱ፡፡

በዚያን ጊዜም ከለዳውያን ቀርበው አይሁድን ከሰሱ፡፡ ለንጉሡም ለናቡከደነፆር ተናገሩ እንዲህም አሉ ‹ንጉሥ ሆይ! ሺህ ዓመት ንገሥ፡፡ አንተ ንጉሥ ሆይ የመለከትንና የእንቢልታን፣ የመሰንቆንና የክራርን፣ የበገናንና የዋሽንትን፣ የዘፈንንም ሁሉ ድምፅ የሚሰማ ሰው ሁሉ ተደፍቶ ለወርቁ ምስል ይስገድ፤ ተደፍቶም የማይሰግድ በሚነድድ እሳት እቶን ውስጥ ይጣላል ብለህ አዘዝህ፡፡ በባቢሎን አውራጃ ሥራ ላይ የሾምሃቸው ሲድራቅና ሚሳቅ አብደናጎም የሚባሉ አይሁድ አሉ፤ ንጉሥ ሆይ! እነዚህ ሰዎች ትእዛዝህን እንቢ ብለዋል፤ አማልክትህን አያመልኩም፥ ላቆምኸውም ለወርቁ ምስል አይሰግዱም፡፡› ናቡከደነፆርም በብስጭትና በቍጣ ሲድራቅንና ሚሳቅን አብደናጎንም ያመጡ ዘንድ አዘዘ፤ እነዚህንም ሰዎች ወደ ንጉሡ ፊት አመጡአቸው፡፡ ናቡከደነፆርም ሲድራቅና ሚሳቅ አብደናጎም ሆይ! አምላኬን አለማምለካችሁ ላቆምሁትም ለወርቁ ምስል አለመስገዳችሁ እውነት ነውን? አሁንም የመለከቱንና የእንቢልታውን የመሰንቆውንና የክራሩን የበገናውንና የዋሽንቱን የዘፈኑንም ሁሉ ድምፅ በሰማችሁ ጊዜ ተደፍታችሁ ላሠራሁት ምስል ብትሰግዱ መልካም ነው፤ ባትሰግዱ ግን በዚያ ጊዜ በሚነድድ እሳት እቶን ውስጥ ትጣላላችሁ፤ ከእጄስ የሚያድናችሁ አምላክ ማን ነው?›› ብሎ ተናገራቸው፡፡ ሲድራቅና ሚሳቅ አብደናጎም መለሱ ንጉሡን ‹ናቡከደነፆር ሆይ! በዚህ ነገር እንመልስልህ ዘንድ አስፈላጊያችን አይደለም፡፡ የምናመልከው አምላካችን ከሚነድደው ከእሳቱ እቶን ያድነን ዘንድ ይችላል፤ ከእጅህም ያድነናል፡፡ ነገር ግን ንጉሥ ሆይ! እርሱ ባያድነን አማልክትህን እንዳናመልክ ላቆምኸውም ለወርቁ ምስል እንዳንሰግድለት እወቅ› አሉት፡፡

የዚያን ጊዜም ናቡከደነፆር በሲድራቅና በሚሳቅ በአብደናጎም ላይ ቍጣ ሞላበት፡፡ የፊቱም መልክ ተለወጠባቸው፡፡ እርሱም ተናገረ የእቶንም እሳት ይነድድ ከነበረው ይልቅ ሰባት እጥፍ አድርገው እንዲያነድዱት አዘዘ፡፡ ሲድራቅንና ሚሳቅንም አብደናጎንም ያስሩ ዘንድ ወደሚነድድም ወደ እቶን እሳት ይጥሉአቸው ዘንድ በሠራዊቱ ውስጥ ከነበሩት ኃያላን አዘዘ፡፡ የዚያን ጊዜም እነዚህ ሰዎች ከሰናፊላቸውና ከቀሚሳቸው ከመጐናጸፊያቸውም ከቀረውም ልብሳቸው ጋር ታስረው በሚነድድ በእቶን እሳት ውስጥ ተጣሉ፡፡ የንጉሡም ትእዛዝ አስቸኳይ ስለሆነ የእቶኑም እሳት እጅግ ስለሚነድድ፣ ሲድራቅንና ሚሳቅን አብደናጎንም የጣሉአቸውን ሰዎች የእሳቱ ወላፈን ገደላቸው፡፡ እነዚህም ሦስቱ ሰዎች ሲድራቅና ሚሳቅ አብደናጎም ታስረው በሚነድደው በእቶኑ እሳት ውስጥ ወደቁ፡፡ የዚያን ጊዜም ንጉሡ ናቡከደነፆር ተደነቀ ፈጥኖም ተነሣ፤ አማካሪዎቹንም ‹ሦስት ሰዎች አስረን በእሳት ውስጥ ጥለን አልነበረምን?› ብሎ ተናገራቸው፡፡ እነርሱም ‹ንጉሥ ሆይ! እውነት ነው› ብለው ለንጉሡ መለሱለት፡፡ እርሱም ‹እነሆ እኔ የተፈቱ በእሳቱም መካከል የሚመላለሱ አራት ሰዎች አያለሁ፤ ምንም አላቈሰላቸውም፤ የአራተኛውም መልክ የአማልክትን ልጅ ይመስላል› ብሎ መለሰ፡፡ የዚያን ጊዜም ናቡከደነፆር ወደሚነድደው ወደ እሳቱ እቶን በር ቀርቦ ‹እናንተ የልዑል አምላክ ባሪያዎች ሲድራቅና ሚሳቅ አብደናጎም! ኑ ውጡ› ብሎ ተናገራቸው፡፡ ሲድራቅና ሚሳቅም አብደናጎም ከእሳቱ መካከል ወጡ፡፡

መሳፍንቱና ሹማምቶቹም አዛዦቹና የንጉሡ አማካሪዎች ተሰብስበው እሳቱ በእነዚያ ሰዎች አካል ላይ ኃይል እንዳልነበረው፣ የራሳቸውም ጠጕር እንዳልተቃጠለች ሰናፊላቸውም እንዳልተለወጠ፣ የእሳቱም ሽታ እንዳልደረሰባቸው አዩ፡፡ ናቡከደነፆርም መልሶ ‹መልአኩን የላከ ከአምላካቸውም በቀር ማንም አምላክ እንዳያመልኩ ለእርሱም እንዳይሰግዱ ሰውነታቸውን አሳልፈው የሰጡትን የንጉሡንም ቃል የተላለፉትን በእርሱ የታመኑትን ባሪያዎቹን ያዳነ፣ የሲድራቅና የሚሳቅ የአብደናጎም አምላክ ይባረክ፡፡ እኔም እንደዚህ የሚያድን ሌላ አምላክ የለምና በሲድራቅና በሚሳቅ በአብደናጎም አምላክ ላይ የስድብን ነገር የሚናገር ወገንና ሕዝብ በልዩ ልዩም ቋንቋ የሚናገሩ ይቈረጣሉ፣ ቤቶቻቸውም የጕድፍ መጣያ ይደረጋሉ ብዬ አዝዣለሁ› አለ፡፡ የዚያን ጊዜም ንጉሡ ሲድራቅንና ሚሳቅን አብደናጎንም በባቢሎን አውራጃ ውስጥ ከፍ ከፍ አደረጋቸው፡፡›› ትንቢተ ዳንኤል 3፡1-30፡፡

አምላካችን ከቅዱስ ገብርኤል ረድኤት በረከት ያካፍለን ፤ የመልአኩ ፈጣን ምልጃ አይለየን!

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

#ተዘክሮተ_ሞት

«ለመተኛት ወደ አልጋህ ባመራህ በቀረብህ ጊዜ አልጋዬ፡ ምን አልባት በዚህ ሌሊት ለእኔ መቃብሬ ልትኾኚ ይኾን ይኾናል፤ በጊዜአዊው ዕንቅልፍ ፈንታ በዚህ ሌሊት ያኛው እንቅልፍ (ሞት) ይመጣብኝም እንደ ኾነ አላውቀውም በላት ።ስለዚህ ነጻ እግሮች እያሉህ ከመልካም ሥራ በኋላ ሩጥ፤ ከታሠሩ መፈታት በማይችሉበት ማሰሪያ ከመታሠራቸው በፊት፡፡ የእጆችህ ጣቶችም እስካሉህ ድረስ ሞት ከመምጣቱ በፊት በጸሎት ፊትህንና መላ ሰውነትህን በተእምርተ መስቀል አማትብ፡፡ ዐይኖች እስካሉህ ድረስ በአቧራ ከመሽፈናቸው በፊት በእንብዕ(በእንባ) ምላቸው።ሰው ሆይ ከዚህ ዓለም መለየትህን አስብ፣ እንዲህም በል፡- እነሆ የታዘዘ መልአክ ከበር ቆሞአል (ደርሶአል)፣ እኔንም ይከተለኛል። ለምን ሊል ዘሊል እኾናለሁ? መመለሻ የሌለው ዘለዓለማዊ መንገድ አለ፡፡መለኮት ደግነት የተነሣ የሰውን ልብ የሚገዛውና ነፍስን ወደ ሕይወት የሚመራት የመጀመሪያው ትምህርት ተዘክሮተ ሞት ነው።.ተዘክሮተ ሞት በሰይጣን እጅግ በብዙ ይጠላል፡፡ እርሱም ከሰው ተዘክሮን ለመንቀል በሙሉ ኃይሉ መሞከርን አይተዉም፡፡ የሚቻለውስ ቢኾን በምድራዊ ሕይወት አሳብ ተብትቦ ተዘክሮተ ሞትን ከሰው ልብ (አእምሮ) ለማስወገድ ምድራዊ መንግሥታትን ለሰው በሰጠው ነበር፡፡ አታላዩ ሰይጣን ተዘክሮተ ሞት በሰው ሁልጊዜም ካለ፣ አሳቡ ለአሁኑ ሕይወት መታለሎች የተጣበቀ ኾኖ እንደማይቀር አልያም የሰይጣን ማታለሎች ሰውን ሊቀርቡት እንደማይችሉ ያውቃል፡፡"

ማር ይስሐቅ ሶርያዊ

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

#ውዳሴ_ከንቱ

የሚጠቅም ውዳሴ (ውዳሴ ዘይረብሕ)
ቅድስት ቤተክርስቲያናችን መጽሐፍ ቅዱስን መሠረት በማድረግ ጎጂነቱን አውቃ የከለከለችው ከንቱ ምስጋና እንዳለ ሁሉ ተገቢ ነው ይጠቅማል ብላ የፈቀደችው ያዘዘችውም የምስጋና ዓይነት አለ፡፡ ይህ የምስጋና አይነት የተለየ ስያሜ ባይኖረውም ከውጤቱ በመነሳት ውዳሴ ዘይረብሕ (የሚረባ-ረብ ያለው ውዳሴ)፣ ውዳሴ ዘይበቊዕ (የሚጠቅም ውዳሴ) ልንለው እንችላለን፡፡
ለአምላካችን እግዚአብሔር ፤ ለቅዱሳን፤ በሥራቸው ሊመሰገኑ ለሚገባቸው ቅን ሰዎች፤ አንዳንዴም በምስጋና ልናበረታቸው ለሚገቡ ድኩማን የሚደረጉ ምስጋናዎች ከዚህ ዓይነቱ ምስጋና ውስጥ የሚመደቡ ናቸው፡፡
ለእግዚአብሔርና ለቅዱሳን የሚቀርቡ ምስጋናዎች አመስጋኙን ብቻ ሲጠቅሙ የቀሩት ደግሞ የሚጠቅሙበት ጎዳና ቢለያይም አመስጋኙንም ተመስጋኙንም የሚጠቅሙ ናቸው፡፡ ምስጋና አመስጋኙን ብቻ ሊጠቅም እንደሚችል የሚያሳይ በቅዳሴ ማርያም ላይ “ዘንተ ቅዳሴ ዘይቄድስ ካህን አኮ ማርያምሃ ዘይቄድስ አላ ውእቱ ይትቄደስ - ይህን ቅዳሴ የሚቀድስ ካህን ማርያምን የሚቀድሳት አይደለም ራሱ ይቀደሳል እንጂ” የሚል ንባብ ይገኛል፡፡ ከጥቅማቸው ከፍታ አንፃር ካየነው ደግሞ ለእግዚአብሔርና ለቅዱሳን የሚቀርብ ምሥጋና ዘርፈ ብዙ ጥቅም ያለው ሆኖ እናገኘዋለን፡፡ ራሱን የቻለ ሰፊ ሐሳብ በመሆኑም በዚህ ጽሑፍ የምንዳስሰው አይሆንም፡፡ ይልቁን ከሰዎች ጋር ባለን ማኅበራዊ ሕይወት ስለሚያጋጥሙንና ጥንቃቄ ስለሚፈልጉ ምስጋናዎች በጥቂቱ እንመለከታለን፡፡
መልካም ለሚሠሩና ቅን ለሆኑ ሠዎች ምስጋና እንደሚገባቸው በቅዱስ ዳዊት የመዝሙር መጽሐፍ “ወለራትዓን ይደልዎሙ ክብር - ለቅኖችም ምስጋና ይገባቸዋል” መዝ 33:1 ተብሎ የተጻፈ ሲሆን ልጁ ሰሎሞን ደግሞ መልካም ስለምትሠራ ልባም ሴት በጻፈበት የምሳሌ ክፍል “ልጆችዋ ይነሣሉ ምስጋናዋንም ይናገራሉ ባልዋ ደግሞ እንዲህ ብሎ ያመሰግናታል።መልካም ያደረጉ ብዙ ሴቶች አሉ አንቺ ግን ከሁሉ ትበልጫለሽ። ውበት ሐሰት ነው ደም ግባትም ከንቱ ነው እግዚአብሔርን የምትፈራ ሴት ግን እርስዋ ትመሰገናለች። ከእጅዋ ፍሬ ስጡአት ሥራዎችዋም በሸንጎ ያመስግኑአት።” ምሳ 31:28 በማለት ጽፏል፡፡ ከእነዚህ ጥቅሶች መልካም ለሚሠሩ ሁሉ ምስጋና የሚገባ መሆኑን ብንረዳም ጎን ለጎን ልናደርጋቸው የሚገቡ በቂ ጥንቃቄዎችም አሉ፡፡ ከእነዚህም መካከል፡-
፩- በመጠንና በተገባ ነገር ማመስገን
ምስጋናው ያልተመጠነና የተጋነነ ከሆነ በአንድ በኩል ተመስጋኙ በደንብ አንዲሠራ ከማድረግ ይልቅ በምስጋናው እየተደሰተ ተዘናግቶ እንዲኖር የሚያደርገው ሲሆን በሌላ መልኩ ደግሞ በውዳሴ ከንቱ እንዲወድቅ ምክንያት ሊሆን ይችላል፡፡ አመስጋኙም ለውድቀት ምክንያት በመሆኑ ከመቀጣት አይድንም፡፡
፪-ከጕሕሉት(ከሽንገላ) እና ከውሸት የፀዳ መሆን
ብዙ ሰዎች ዘመን የወለደውን ንጉስ የወደደውን ተከትለው በልባቸው ባያምኑበት እንኳ መስሎ ለማደር ብለው ሰዎችን ያመሰግናሉ፡፡ ተመስጋኙ ይህ ከልብ ነው፣ ይህ አይደለም ብሎ መለየት ባይችልም ልብና ኲላሊትን የሚመረምር አምላክ ይፈርድብኛል ብለን “በአፉሆሙ ይድህሩ ወበልቦሙ ይረግሙ - በአፋቸው ይመርቃሉ በልባቸውም ይረግማሉ፡፡” መዝ 62:4 ከተባሉት እንዳንቆጠር መጠንቀቅ ይገባናል፡፡
፫ ምስጋናን ሱስ እስኪሆን አለማስለመድ
ምስጋና ከተለመደ እንደሌሎቹ ልማዶች ሱስ ሊሆን ይችላል፡፡ አበው “ኀዲገ ልማድ ፅኑዕ ውእቱ - ልማድን መተው ከባድ ነው” እንዳሉ በውዳሴ ሱስ የተጠመደ ሰውም ከዚህ ልማድ መውጣት ሊከብደው ሲቀር ቅር ሊሰኝ አልፎም ለምን አልተመሰገንኩም ብሎ ሊቆጣ ይችላል፡፡ ሰው እንዲህ ካለ ክፉና አስተቺ ልማድ ውስጥ እንዲገባ ምክንያት መሆን ከባድ ፍርድ ያለበት በመሆኑ ሱስ እስኪሆንበት በነጋ ጠባ ሰውን ከማመስገን መጠበቅ ተገቢ ነው፡፡
በቅዱሳት መጻሕፍት መልካም ለሚሠሩና ቅን ለሆኑ ሰዎች ብቻ ሳይሆን ምስጋናው ለማይገባቸውና የእነርሱ ባልሆነ ነገር ሰዎችን ማመስገን ጠቃሚ ሆኖ የሚገኝበት ጊዜ እንዳለም ተጽፏል፡፡ በሥጋዊ ትምህርት ጎበዝ ያልሆነውን ተማሪ ጎበዝ በማለት ተነሳሽነቱ እንዲጨምርና እንዲሻሻል ማድረግ እንደሚቻል በመንፈሳዊ ሕይወቱ ያልበረታን ሰውንም በማመስገን ማበርታት እንዲሁ ይጠቅማል፡፡ ይህን በተመለከተ በመጽሐፈ መነኮሳት ላይ “ወድሶ ለሰብእ በዘኢኮነ ሎቱ ወድሶ ለሰብእ በዘኢኮነ ድልወቱ እስመ ወድሶ ለሰብእ ይወስክ ኃይለ - ሰውን የእርሱ ባልሆነና ባልተገባው ነገር አመስግነው ምስጋና ለሰው ኃይልን ይጨምራልና” ተብሎ ተጽፏል፡፡
ከላይ ስለተገለጡት ተገቢ ምክንያቶች ማመስገን በዚህ ጽሑፍ ተነግረው የማያልቁ እጅግ ብዙ ጥቅሞች አሉት፡፡ “ብጹዕ ሕዝብ ዘየአምር የብቦ - እልልታን (ምስጋናን) የሚያውቅ ሕዝብ ምስጉን ነው፡፡” መዝ 89:15 ተብሎ እንደተጻፈ ሰዎችን ለማመስገን መነሳት በራሱ የሚያስመሰግን ደግ ተግባር ነው፡፡ ቁጣው የራቀ ምሕረቱ የበዛ አምላክ “በወንድሙ ላይ የሚቆጣ ሁሉ ፍርድ ይገባዋል” ማቴ 5:22 ብሎ ካስተማረን ወንድሙን ያመሰገነ ምን ዓይነት ሽልማት ይገባው ይሆን? “ዘይፀርፍ ላዕለ እኁኁ ዘረፈኬ ላዕለ እግዚአብሔር ልዑል - በወንድሙ ላይ የተሳደበ በእግዚአብሔር ላይ ተሳደበ” ተብሎ ከተጻፈ ወንድሙን ያመሰገነ ምን ዓይነት ክብር ይጠብቀው ይሆን?
............. ✞✞✞ .............

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

"እናምናለን እኛ ሁለት ልደታትን"
ሐዋርያት አበው እንዳስተማሩን
ስለሰው ልጅ ድኅነት አምላክ ሰው መኾኑን
በስሙ የተጠራን እኛ እናምናለን
መለኮት ከሥጋ ተዋሕዷል ብለን

እናምናለን እኛ ኹለት ልደታትን
የአብ ልጅ ከድንግል ዳግም መወለዱን/፪/

ስግደት የሚገባው የአብ አካላዊ ቃል
ከክቡር ዙፋኑ ከሦስትነት ሳይጎድል
በዚህ ዓለም መጥቶ ሰው ሆኗል ከድንግል
ከአብ አንድነቱ ከቶ ሳይከፈል
አዝ---
ቃልም ሥጋ ሆኖ በእኛ ላይ አድሮ
ወልደ አብ ወልደ ማርያም በተዋሕዶ ከብሮ
ፍጹም የአምላክ ልጅ ፍጹም ሰውነቱ
ተገልጧል በድንግል በዳግም ልደቱ
  አዝ---

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

"ከንቱ ነኝ"
ሊቀ መዘምራን ይልማ ኃይሉ

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

ከሰዎች ማነው እንደ እኔ ትእዛዝህን ሻሪ/፪/ከአማልክትስ ማነው እንዳንተ መሐሪ /፪/

የኃጢአት ሸክም ከብዶብኝ ሲያስጨንቀኝ
ጠላቶች ከበው በእኔ ላይ ሲዝቱብኝ
ብቸኝነቴን አይተህ ስለደረስክልኝ
ተመስገን እንጂ ላንተ ሌላ ምን አለኝ

አዝ...../፪/

በደሌን አይተህ በቅፅበት ያላጠፋኸኝ
እንደ ጥፋቴ በቁጣ ያልተበቀልከኝ
ቸር እና የዋህ አምላክ እንዳንተማ አይገኝ /፪/

አዝ...../፪/

እንደ ሕዝቅያስ ጸሎቴን አምላክ ስማኝ
እንደ ዳዊትም ልመናዬን ተቀበለኝ
በዘመኔ እኩሌታ አምላኬ አትውሰደኝ
ወሰን በሌላት ፍቅርህ ታግሰህ ጠብቀኝ

አዝ...../፪/


@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

"የአርማንያ ሰማዕት |አርሴማ|"
ለሰማያዊ ክብር በወንጌል|፪| ያስጌጠሽ
ለቃሉ ምስክር አምላክ  የጠራሽ
የአርማንያ ሰማዕት|፪|  አርሴማ አንች ነሽ፣
 
          አዝ...........
የምሥጢር ዋሻ ነሽ የሰማይ ሙሽራ፣
በዓለማት ሁሉ ክብርሽ የሚያበራ።
ምግባር|፪| እና እምነትን አስተባብረሽ ይዘሽ፣
በመንግሥተ ሰማይ አክሊል ተቀዳጀሽ።
አዝ.........
በእውነት ቢያምርም የሰው ልጅ ውበቱ፣
ምግባር ከታጣበት በሰማይ አባቱ።
ያልሆነለት|፪| እሱ ውበት ሃይማኖቱ፣
ብለሽ ተናግረሻል ይቀራል በከንቱ።
አዝ.....
የጽናት ምስክር  ለቃለ ወንጌሉ ፣
ከሁሉ ይበልጣል  የፈጣሪ ኃይሉ።
ጸንተው|፪| ለሚኖሩ በሃይማኖታቸው ፣
አርሴማ እናታችን አብነት ሆንሻቸው።
አዝ........
ለሰማያዊ ክብር ስለሆንሽ ምክንያት፣
እኛ እንልሻለን የሁላችን  እናት።
ለምናምን|፪| ሁሉ በምልጃ ኪዳንሽ፣
ምሕረትን አሰጪን ለምነሽ ከአምላክሽ።

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

"በቤተ መቅደስህ ያሳደግከኝ"

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

ንጽህተ ንጹሀን ከዊና፣
ከመታቦት ዘዶር ዘሲና፣
ውስተ ቤተ መቅደስ፣
ነበረት(፪) በድንግልና፣
ሲሳይያ ኅብስተ መና፣
ወስቴሃኒ ስቴ ጽሞና።

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

ታኅሣሥ ፫
በዓታ ለእግዝእትነ ማርያም

"ልጄ ሆይ፥ ስሚ፤ እዪ፤ ጆሮሽንም አዘንብዪ፤ ወገንሽን፡ ያባትሽንም ቤት እርሺ፤ ንጉሥ ውበትሽን ወዷልና፥ እርሱ ጌታሽ ነውና።"  መዝ ፵፭፥፲

ታኅሣሥ ሦስት በዚህች ቀን አምላክን የወለደች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሦስት ዓመት ሲሆናት ወደ ቤተ መቅደስ የገባችበት ነው ። እርሷ ለእግዚአብሔር የስእለት ልጅ ነበረችና።

እናቷ ቅድስት ሐና ልጅ የሌላት ስለሆነች በቤተ እግዚአብሔር ውስጥ ከሴቶች ተለይታ ርቃ ትኖር ነበር ሽማግሌ ከሆነ ከኢያቄም ከባሏ ጋርም እጅግ የምታዝን ሆነች ። እግዚአብሔርም ኀዘናቸውን ሰማ ቅድስት ሐናም እንዲህ ብላ ለእግዚአብሔር ተሳለች የሰጠህኝን ፍሬ ለእግዚአብሔር አገልጋይ አደርገዋለሁ ።

ቅድስት ድንግል እመቤታችን ማርያምንም በወለደቻት ጊዜ ሦስት ዓመት በቤቷ ውስጥ አሳደገቻት ከዚህም በኋላ ከደናግል ጋር ትኖር ዘንድ ወደ ቤተ መቅደስ ወሰደቻት በቤተ መቅደስም ምግቧን ከመላእክት እጅ እየተቀበለች ዐሥራ ሁለት ዓመት ኖረች ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ዓለም መጥቶ ከእርሷ ሥጋን እስከ ነሣ ድረስ።

ከሴቶች ሁሉ የተመረጠች ይቺ ናት በቤተ መቅደስም በመኖር ዐሥራ ሁለት ዓመት ሲፈጸምላት እርሷ ለእግዚአብሔር የተሰጠች የስዕለት ልጅ ናትና ለሚጠብቃት ይሰጧት ዘንድ ካህናት እርስበርሳቸው ተማከሩ በሴቶች ላይ የሚደርስ በርሷ ላይም ይደርስባታል ብለው ስለፈሩ በቤተ መቅደስ ውስጥ ይተዋት ዘንድ ለእርሱ ትክክል መስሎ አልታያቸውም ስለዚህም ሊጠብቃት ለሚገባው በእርሷ ላይ እጮኛ ሊአኖሩ ወደዱ።

ከዚህም አስቀድሞ ሊቀ ካህናት ዘካርያስ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ልጄ ማርያም ሆይ አንቺ እንዳደግሽና ለአካለ መጠን እንደደረስሽ ዕወቂ ልትታጪ ትወጃለሽን እግዚአብሔርን የሚፈራ መልካም የሆነ የተባረከ ጐልማሳ እንፈልግልሽን ወይም በሕይወትሽ ዘመን ሁሉ በቤተ መቅደስ ተቀምጠሽ እግዚአብሔርን ልታገለግዪው የምትሺ ከሆነ በሴቶች ላይ የሚደርሰው በሚደርስብሽ ወራት ወደ ቤተ መቅደስ ደጅ ከመግባት ትጠበቂ ዘንድ በኦሪቱ የተጸፈውን የርግማን ሥርዓት በአንቺ ላይ እንሠራለን አላት ።

ቅድስት ድንግል እመቤታችን ማርያምም እነሆ እኔ የእግዚአብሔር አገልጋዩ በፊታችሁ ነኝ አባትና እናት የሉኝም ስሙ ቡሩክ ምስጉን ከሆነ ከእግዚአብሔር በታች በእናትና አባት ፈንታ እናንት ናችሁና የእግዚአብሔርን ትእዛዝ እንደምታውቁ አድርጉ ብላ መለሰች።

ካህናቱና ማኅበሩም ሁሉ ዘካርያስን ወደ ቤተ መቅደስ ገብተህ ስለዚች ብላቴና ማርያም ወደ እግዚአብሔር ጸልይ አሉት ዘካርያስም ገብቶ ሲጸልይ በዚያን ጊዜ የእግዚአብሔር መልአክ ተገለጠለትና እንዲህ አለው። ዘካርያስ ሆይ ወጥተህ ከዳዊት ወገን ሚስቶቻቸው የሞቱባቸውን ሁሉ ወንዶች ሰብስብ የየአንዳንዱንም በትር ከስሙ ጋር ውሰድ ወደ ቤተ መቅደስም በምሽት አግብተህ ወደ እግዚአብሔር ጸልይበት በነጋ ጊዜም በትሮቻቸውን አውጣ እግዚአብሔርም በበትሩ ላይ ምልክት ለገለጠልህ ለዚያ ሰው ማርያምን ተቀብሎ ሊጠብቃት ይገባዋል።

ካህኑ ዘካርያስም ወጥቶ አንድነት ለተሰበሰቡት ሕዝብ የእግዚአብሔር መልአክ የነገረውን ነገራቸው በዚያንም ጊዜ ከዳዊት ወገን ጐልማሳም ቢሆን ሽማግሌም ቢሆን ሚስቱ የሞተችበት ሁሉ በኢየሩሳሌም ወደአለ ቤተ መቅደስ ይሒድ እያሉ ዓዋጅን ዙረው የሚናገሩ በእስራኤል አገር ሁሉ ላከ ።

ከዳዊት ወገን የሆነ ጠራቢው ዮሴፍም በሰማ ጊዜ በትሩን ይዞ ከናዝሬት ወደ ኢየሩሳሌም ሔደ ካህኑ ዘካርያስም የሁሉንም በትሮች ተቀብሎ ስማቸውን በላያቸው ጻፈ ቁጥራቸውም አንድ ሽህ ዘጠኝ መቶ ሰማንያ አምስት ሆነ ዘካርያስም በትሮችን ወደ ቤተ መቅደስ አስገብቶ ወደ እግዚአብሔር ጸለየ እንዲሁም ሰዎች ሁሉ ከቤተ መቅደስ ውጭ ቁመው ይጸልዩ ነበር ዘካርያስም ጸሎቱን በፈፀመ ጊዜ ለየአንዳንዱ በትራቸውን አውጥቶ ሰጠ ጠራቢው ዮሴፍም በትሩን ሊቀበል በቀረበ ጊዜ ከእርሷ ነጭ ርግብ የመሰለች ተገለጠች እየበረረችም ሒዳ በጠራቢው ዮሴፍ ራስ ላይ ተቀመጠች ካህናቱና ሕዝቡ ሁሉ አይተው እጅግ አደነቁ ምስጉን የሆነ እግዚአብሔርንም አመሰገኑት ።

ዘካርያስም ዮሴፍን ዮሴፍ ሆይ ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልአክ እንደ ተናገረ ድንግል ማርያምን ወደ ቤትህ ወስደህ ጠብቃት አለው ዮሴፍም ቅድስት ድንግል ማርያምን ከካህናት እጅ ተቀበላት በእርሱም ዘንድ ኖረች ። ከዚህም በኋላ የመላእክት አለቃ ገብርኤል ስለ እግዚአብሔር ልጅ ከእርሷ ሰው ሁኖ ስለመወለዱ በዮሴፍ ቤት አበሠራት።

ሊቀ መላዕክት ቅዱስ ፋኑኤል
በዚችም ቀን የሊቀ መላእክት ፋኑኤል የበዓሉ መታሰቢያ ነው።

ይህም ታላቅ መልአክ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም እናት እና አባት ቅድስት ሐና እና ቅዱስ ኢያቄም እግዚአብሔር አምላክ ልጅ ይሰጣቸው ዘንድ ዘወትር ይማፀኑት ነበር፡፡ለእግዚአብሔር “ወንድ ልጅ ብንወልድ እርሱ ወጥቶ ወርዶ ያበላናል አንልም ያንተን ቤት ያገለግላል፤ ሴትም ብትሆን ጋግራ ታብላን ፈትላ ታልብሰን አንልም ሀርና ወርቅ እየፈተለች መሶበ ወርቅ እየሰፋች ቤተ መቅደስን ታገለግላለች እንጂ”  ብለው ስዕለትንም ተስለው ነበር፡፡

ለአብርሀም እና ለሳራ ይስሐቅን (ዘፍ. 21፥1-8)፣ ለሕልቃና እና ለሐና ነብዩ ሳሙኤልን (1ኛ ሳሙ. 1፥1-21) የሰጠ አምላክ ዛሬም የእነዚህን ቅዱሳን እንባቸውንና ልመናቸውን ሰምቶ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ሰጣቸው፡፡ እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በእናት እና አባቷ ቤት እስከ 3 ዓመት ድረስ ከቆየች በኋላ በስእለታቸው መሰረት ለቤተ መቅደስ ሰጡ፡፡ ቤተ መቅደስ ከደረሱ በኋላ ስእለታቸውን ለሊቀ ካህኑ ለዘካርያስ በሰጡት ወቅት ሊቀ ካህኑ እና ሌሎች የቤተ መቅደሱ አገልጋዮች (ካህናት) የምግቧ ነገር እንዴት ሊሆን ነው ብለው እጅግ ተጨነቁ፡፡ በዚህ ወቅት ከሰባቱ ሊቃነ መላዕክት አንዱ የሆነው መልዐኩ ቅዱስ ፋኑኤል ሰማያዊ ጽዋ አና ሰማያዊ ሕብስት ይዞ ረብቦ ታየ፡፡ ሊቀ ካህኑ ዘካርያስ ለኔ የመጣ ነው ብሎ ወደ መልአኩ ጠጋ ሲል፡፡ ያኔ ቅዱስ ፋኑኤል ወደ ላይ ከፍ አለ፡፡ የሊቀ ካህኑ ምክትል የነበረው ስምኦንም ሲቀርብ መልአኩ አሁንም ከፍ አለ፡፡ ከዛም ህፃኒቱን እስቲ ተጠጊ ብለዋት ስትጠጋው መልአኩ ቅዱስ ፋኑኤል ፈጥኖ ወርዶ አንድ ክንፉን አንጥፎ አንድ ክፉን ጋርዶ በሰው ቁመት ከመሬት ከፍ አድርጎ መግቧት አረገ፡፡ ይህም የሆነው እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ወደቤተ መቅደስ በገባችበት ዕለት ነው፡፡

ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በእናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነት ይማረን በረከቷም ከእኛ ጋር ይኑር ለዘላለሙ አሜን!

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

በዚያንም ጊዜ የአገር ሰዎች ስለ ቅዱስ መርቆሬዎስ እንዳይነሡበት ፈርቶ የቀጰዶቅያና የእስያ ክፍል ወደ ሆነች ወደ ቂሣርያ በብረት ማሠሪያ አሥሮ ላከው። በዚያም እንዲአሠቃዩት አዘዘ ከአሠቃዩትም በኋላ ንጉሥ ዳኬዎስ እንዳዘዘ ራሱን በሰይፍ ቆረጡትና ተጋድሎውን ፈጽሞ በመንግሥተ ሰማያት የሕይወት አክሊልን ተቀበለ።

የማይጠፋ ሰማያዊ አክሊልንም ተቀዳጅቶ ወደ ዘላለም ሕይወት ከገባ በኋላ በዓለሙ ሁሉ አብያተ ክርስተያናት ታነፁለት። እግዚአብሔርም ታላላቅ የሆኑ ድንቆች ተአምራትን በውስጣቸው ገለጠ።

ተአምር ዘቅዱስ መርቆሬዎስ - ፩

ከተአምራቱም አንዲቱ ዑልያኖስ በነገሠ ጊዜ ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ካደ። በዚያንም ወራት ቅዱስ ባስልዮስ የቂሣርያ ሊቀ ጳጳሳት ነበረ ተአምራቱ በተጻፉበት መጽሐፍ እንደተጻፈ ምእመናን በጽኑዕ ሥቃይ ዑልያኖስ ባሠቃየ ጊዜ መክሮ አስተምሮ ከስሕተቱ ይመልሰው ዘንድ ቅዱስ ባስልዮስ ወደርሱ መጣ።

ዑልያኖስም ቅዱስ ባስልዮስን በአየው ጊዜ ክብር ይግባውና ጌታችንን ሰደበ። ቅዱስ ባስልዮስንም አሠረው። በዚያ በእሥር ቤትም የቅዱስ መርቆሬዎስን ሥዕል አይቶ በፊቱ ቅዱስ ባስልዮስ ጸለየ ሥዕሉም ከቦታው ታጣ። ያን ጊዜ ወደ ዑልያኖስ ሒዷልና በጦርም ወግቶ ገደለውና ወዲያውኑ ወደቦታው ተመለሰ ከጦሩም አንደበት ደም ይንጠፈጠፍ ነበር። ቅዱስ ባስልዮስም ከሀዲ ዑልያኖስን እንደገደለው አውቆ እንዲህ ብሎ ተናገረ የክርስቶስ ምስክር ሆይ የእውነት ፀር የሆነ ዑልያኖስን ገደልከውን ያን ጊዜ አዎን እንደሚል ሥዕሉ ራሱን ዘንበል አደረገ ቅዱስ ባስልዮስም ደስ ብሎት እግዚአብሔርን አመሰገነ።

ተአምር ዘቅዱስ መርቆሬዎስ - ፪

የዚህም የቅዱስ መርቆሬዎስ ሌላው ተአምር ከምስር አገር ከመሳፍንት ወገን የሆነ አንድ የእስላም ወጣት ነበረ የእስላሞችንም ሕጋቸውንና መጻሕፍቶቻቸውን ተምሮአል። በአንዲትም ዕለት ወደ ባሕር ዳርቻ በመንገድ አልፎ ሲሔድ አንድ የተፈረደበትን ሰው አገኘ። አስቀድሞ እስላም የነበረ አሁን የክርስትና ጥምቀትን የተጠመቀ የንጉሥ ጭፍሮችም ይዘውታል። ሊአቃጥሉትም ጉድጓድን ምሰው በውስጡ ታላቅ እሳት አንድደው አዘጋጅተውለታል። ብዙዎች ሰዎችም ሲቃጠል ለማየት ተሰብስበው ነበር።

ያም የመስፍን ልጅ ወጣት እስላም ወደ ተፈረደበት ሰው ቀረብ ብሎ "አንተ ከሀዲ ሰው ወደ ሲኦል ለመግባት ለምን ትሮጣለህ በኋላም በገሀነም እሳት ውስጥ ለመኖር አንተ እግዚአብሔርን ባለ ልጅ ታደርገዋለህና ሦስት አማልክትንም የምታምን ነህና ክፉ ነገር ነውና ይህን ስድብ ትተህ እኔን ስማኝ" አለው ።

ያ የተፈረደበትም እንዲህ ብሎ መለሰለት "እኛ የክርስቲያን ወገኖች ሦስት አማልክትን የምናመልክ ከሀድያን አይደለንም። አንድ አምላክን እናመልካለን እንጂ ይኸውም አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ነው። ወልድ ከአባቱ ከእግዚአብሔር ልዩ አይደለም። የራሱ ቃሉ ነው እንጂ። መንፈስ ቅዱስም ሕይወቱ ነው። የሃይማኖታችን ምሥጢር ከአናንተ የተሠወረ ድንቅ ነው። ዛሬ ለአንተ ልብህ ጨለማ ነው በውስጡ የሃይማኖት ብርሃን አልበራም በኋላ ግን ልብህ በርቶልህ እንደ እኔ ስለ ክርስቶስ ስም በመጋደል መከራውን ትቀበላለህ።"

ያም ወጣት እስላም በሰማው ጊዜ እጅግ ተቆጣ ጫማውንም ከእግሮቹ አውልቆ አፉን ፊቱንና ራሱን ጸፋው። ይህ የምትለው ከእኔ ዘንድ አይደረግም እያለ አብዝቶ አሠቃየ። የተከበረው ሰማዕትም ይህን ያልኩህን አስበህ የምትጸጸትበት ጊዜ አለህ አለው።

በዚያንም ጊዜ ራሱን በሰይፍ ቆርጠው ሥጋውን ከእሳት ማንደጃ ውስጥ ጨመሩ ከዚህም በኋላ እሳቱ ከፍ ከፍ ብሎ እንደ ታላቅ አጥር ሆነ። የንጉሥም ወታደሮች እየጠበቁት ሦስት ቀን ኖረ። ከዚህም በኋላ ከቶ እሳት ምንም ሳይነካው እንደ ተፈተነ ወርቅ ሆኖ ሥጋውን አገኙት። ይህንንም ለንጉሥ ነገሩት። እርሱም እንዲቀብሩት አዘዘ።

ያ ወጣት እስላም ግን እያዘነ ወደ ቤቱ ገባ እርሱ ክርስቲያን እንደሚሆን ስለተናገረው ከኀዘኑ ብዛት የተነሣ የማይበላና የማይጠጣ ሆነ። እናቱና ወንድሞቹም ወደርሱ ተሰብስበው የማትበላ የማትጠጣ በአንተ ላይ የደረሰ ምንድን ነው አሉት። ክብር ይግባውና ለጌታችን ኢየሱስ ምስክር የሆነው የተናገረውን ነገራቸው። እነርሱም ይህ አሳች የተናገረውን ተወው በልብህ አታስበው እያሉ አጽናኑት። እርሱ ግን ከቶ ምንም አልተጽናናም።

በዚያም ወራት ወደሐሰተኛ ነቢያቸው መቃብር ለመሔድ የሚሹ ሰዎችን አይቶ ከእሳቸው ጋር መሔድ እፈልጋለሁ ብሎ ለአባቱ ነገረው። አባቱም እጅግ ደስ ብሎት የሚበቃውን ያህል የወርቅ ዲናር ሰጠው ለወዳጁም አደራ ብሎ ሰጠውና አብሮት ሔደ።

በሌሊትም ሲጓዙ እነሆ ብርሃን የለበሰ አረጋዊ መነኰስ ተገለጸለት በፊቱም ቁሞ ትድን ዘንድ ና ተከተለኝ አለው እንዲሁም ሁለተኛና ሦስተኛ ተገልጦ ተናገረው።

በደረሱም ጊዜ ሥራቸውን ፈጽመው ወደ አገራቸው ተመለሱ ሰባት ቀንም ያህል ተጓዙ። እነርሱም በሌሊት ሲጓዙ ስለ ሥጋዊ ግዳጅ ያ ወጣት ከገመል ላይ ወርዶ ለመጸዳዳት ዘወር አለ። ባልንጀሮቹም በበረሀ ውስጥ ትተውት ሔዱ ከእሳቸው ጋር የሚጓዝ መስሏቸዋልና በተነሣም ጊዜ ተቅበዘበዘ ወዴት እንደሚሔድ አላወቀምና አራዊትም እንዳይበሉት ፈርቶ ደነገጠ።

በዘያንም ጊዜ በምስር አገር በአባቱ ቤት አቅራቢያ ያለች የሰማዕት የቅዱሰ መርቆሬዎስን ቤተ ክርስቲያን አስታውሶ በልቡ እንዲህ አለ። ሰዎች ሁሉ በእርሷ ዘንድ እየተሳሉ ይፈጸምላቸዋል። በዚያንም ጊዜ የክርስቶስ ምስክር መርቆሬዎስ ሆይ በዚህ በረሀ ካሉ አራዊት አፍ በዛሬዋ ሌሊት ካዳንከኝና ያለ ጥፋት ካወጣኸኝ እኔ ክርስቲያን እሆናለሁ ብሎ ተሳለ።

ወዲያውኑ መልኩ የሚያምር ጎልማሳ የከበረ ልብስ የለበሰና የወርቅ መታጠቂያ በወገቡ የታጠቀ በፈረስ ተቀምጦ ወደርሱ መጣና አንተ ከወዴት ነህ እንዴት በዚህ በረሀ ውስጥ ጠፋህ አለው። ወጣቱም ስለ ሥጋ ግዳጅ ከገመል ላይ ወረድኩ ባልነጀሮቼ ትተውኝ ሔዱ አለው ባለ ፈረሱም ና በኋላዬ በፈረሱ ላይ ተፈናጠጥ አለው በዚያንም ጊዜ ወደ አየር በረረ በምስር አገር ወዳለች የቅዱስ መርቆሬዎስ ቤተ ክርስቲያን እንደ ዐይን ጥቅሻ አደረሰውና እንደተዘጋች ከውስጧ አስገባው። ከፈረሱም ላይ አውርዶ በዚያ አቆመው ወደ መጋረጃ ውስጥም ገብቶ ከእርሱ ተሠወረ።

የቤተ ክርስቲያኑም መጋቤ በሌሊት በመጣ ጊዜ ቤተ ክርስቲያኒቱን ከፍቶ ሲገባ ይህን ወጣት ከመካከል ቁሞ አገኘው። ደንግጦ ሊጮህ ፈለገ ጠቀሰውና ወደኔ ዝም ብለህ ና አለው ወደርሱም ሲቀርብ ይቺ ቦታ የማናት አለው የቤተ ክርስቲያኒቱ መጋቢም ይቺ በምስር አገር ያለች የቅዱስ መርቆሬዎስ ቤተ ክርስቲያን ናት። አንተን ግን ልቡ እንደ ጠፋ ሰው ስትናገር አይሃለሁ ከዚህ ምን አመጣህ አሁንም ንገረኝ አለው። ወጣቱም እንዲህ ብሎ መለሰለት ልቤ እንዴት አይጠፋ እኔ በዛሬው ሌሊት በእገሌ በረሀ ሳለሁ ፈረስ ላይ የተቀመጠ ሰው ተገለጠልኝና ከኋላው በፈረሱ አፈናጠጠኝ ከዚህም አድርሶ ተወኝ አለው።

መጋቢውም የዚያችን በረሀ ስም በሰማ ጊዜ አደነቀ እንዲህም አለው ልብህ ጠፍቷል በማለቴ መልካም የተናገርኩህ አይደለምን የምትናገረውን አታውቅምና የዚያ በረሀ መጠኑ የሃያ ሁለት ቀን ጉዞ የሚያስጉዝ ስለ ሆነ በእርግጥ አንተ ወንበዴ ነህ የቅዱስ ሰማዕት መርቆሬዎስ ኃይል ያለ ገመድ አሥሮሃል፣ እርሱ የዚህን ዓለም ክብር ንቆ የተወ፣ ክብር ይግባውና ስለ ክርስቶስ ስም ከሀዲዎች ጽኑ ሥቃይ አሠቃይተው የገደሉት፣ ክርስቶስም በመንግሥቱ ውስጥ የተቀበለው፣ በቦታዎችም ሁሉ አብያተ ክርስቲያናት ታነፁለት በውስጣቸውም እግዚአብሔርን ያመሰግኑታል። እርሱ

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

✞ንብ ሁኑ ዝንብ አትሁኑ!

አንዳንድ ሰዎች በቤተክርስቲያን ውስጥ በሚመለከቱት ትክክል ያልሆኑ ነገሮች እጅግ ሐፍረት እንደሚሰማቸው በማዘን ይነግሩኛል። ለነዚህ ሰዎች እንዲህ ብዬ እነግራቸዋለሁ:- ዝንብን “እዚህ አካባቢ አበቦች ይታዩሻል” ብላችሁ ጠይቋት።
ዝንቧም “ ስለ አበባዎች አላውቅም። ነገር ግን እዚያ ጋር ትልቅ የቆሻሻ ክምር አለ በዚያ የምትፈልጉትን አይነት የሚሸት ቆሻሻ ታገኛላችሁ” ብላ ትመልስላችኋለች። ካስፈለገ ስለ ቆሻሻው ዝርዝርና በቦታው ስለሚገኝ ንጹህ ያልሆነ ነገር በቂ ማብራሪያ ትሰጣችኋለች። ንብን ደግሞ “በዚህ አካባቢ ንጹሕ ያልሆነ ቆሻሻ ቦታ ታውቂያለሽ” ብላችሁ ብትጠይቋት “ ቆሻሻ? በጭራሽ! እዚህ አካባቢ አይቼም አላውቅም! ይህ ቦታ እጅግ ውብ በሆኑ ቆንጆ መዓዛ ባላቸው አበቦች የተሞላ ነው” ብላ ትመልስላችኋለች። በአትክልት ስፍራውና በሜዳው ስላሉ አበቦች ውበትና ዝርዝርም ትነግራችኋለች። አስተዋላችሁ? ዝንብ የምታውቀው ቆሻሻንና ቆሻሻ ያለበትን ቦታ ነው ንቢቱ ግን ውብ አበቦች እና ሰናይ መዓዛ ያለበትን ቦታ ነው የምታውቀው።
አንዳንድ ሰው እንደ ዝንብ ነው። አንዳንድ ሰው ደግሞ እንደ ንብ። እንደ ዝንብ የሚያስቡት በሁሉም አጋጣሚ የሚያዩት መጥፎውን ሲሆን በመጥፎው ሃሳብም ቀድመው የተሞሉ ናቸው። መልካም ቢኖር እንኳ አይታያቸውም። ንቦቹ ግን በሚመለከቱት ነገር ውስጥ ሁሉ መልካሙን ያያሉ። ስሑት የሆነ እና በጎ ሕሊና የሌለው ሰው ሁሉን ነገር ስሑት አድርጎ ያስባል። ሁሉንም ነገር በመጥፎ መንገድ ይመለከታል። በጎ ሕሊና ያለው ሰው ግን ምንም ዓይነት ነገር ቢመለከት ምንም አይነት ነገር ብትነግሩት መልካምና ቀና ሀሳብን እንደያዘ ይቀጥላል።

አንድ ጊዜ የሆነ የከፍተኛ ትምህርት ተማሪ ወደኔ በዓት መጣና በበሩ ላይ ባለው የመጥሪያ ብረት አንኳኳ። በወቅቱ በርግጥ ብዙ ደብዳቤዎችን እያነበብኩ ቢሆንም ምን እንደፈለገ ወጥቼ ለማየት ወሰንኩ። “ ምን ፈለግክ የኔልጅ?” አልኩት። “ የአባ ፓይሲዮስ በዓት ነው?” ሲል ጠየቀኝ። አክሎም “አባ ፓይሲዮስን ላገኛቸው እፈልጋለሁ” አለኝ። “በርግጥ የአባ ፓይሲዮስ በዓት ነው ነገር ግን አባ ፓይሲዮስ ሲጋራ ሊገዛ ወጥቷል” ስል መለስኩለት። “ የሆነ ሰው ሊረዱ ነው የሄዱት በርግጠኝነት” ሲል መለሰልኝ። “አይ ለራሱ ነው የሚገዛው ሲጋራውን” አልኩት። “የነበረውን በሙሉ አጭሶ ጨርሷቸዋል። ሲጋራ በጣም ነው የሚወደው። እኔን እዚህ ብቻዬን ትቶኝ ነው የሄደው መቼ እንደሚመለስ እንኳን አላውቅም። የሚቆይ ከሆነ እኔ ራሱ ጥዬ መሄዴ ነው” አልኩት። የተማሪው ዐይን እንባን አቅርሮ ውስጣዊ ስሜቱን አሳበቀበት። ነገር ግን አሁንም በበጎ ሕሊና እና በቀና ሀሳብ “አባ ፓይሲዮስን እንደኔ ያለነው ነን ያሰቃየናቸው” ሲለኝ “ ቆይ ለምን ልታገኘው ፈለግህ” አልኩት “ቡራኬ ልቀበል ነው” አለኝ “ አንተ ሞኝ ከእርሱ ምን አይነት ቡራኬ ነው የምትጠብቀው ለራሱ የተታለለ ሞኝ ነውኮ! እኔ በደንብ አውቀዋለሁ። በርሱ ውስጥ ምንም ጸጋ እግዚኣብሔር የለም። ይመለሳል ብለህ እሱን በመጠበቅ ጊዜህን አታባክን ጠጥቶም ሊሆን ይችላል የሚመጣው በጣም ጠጪም ነው በዛ ላይ” አልኩት። ይህንን ሁሉ እየነገርኩት ሁሉ ያ ወጣት ልጅ አሁንም መልካም ማሰቡንና በጎ ሕሊናውን አልጣለም። በመጨረሻም “ ይኸውልህ እኔ እስኪመጣ ጥቂት እጠብቀዋለሁ ምን ልንገርልህ ንገረኝና ሂድ” ስለው “ የምሰጣቸው ደብዳቤ አለ በዚያም ላይ ሲመጡ ቡራኬ ተቀብዬ ነው የምሄደው” ብሎ ከነገርኩት ከዚህ ሁሉ ቆሻሻ ውስጥ መልካም ነገር ብቻ እንዴት እንዳየ ተመለከታችሁ? ምንም ያህል መጥፎ ነገር ብነግረው በመልካም ሀሳብ ነበር የሚወስዳቸው። ስለ ሲጋራ እንኳ እየነገርኩት አይኑ እንባ አቅርሮ “የሆነ ሰው ሊረዱ ሄደው ነው” ብሎ ያስብ ነበር። ብዙ የተማሩና ታላላቅ ነገሮችን ያነበቡ ሰዎች እንኳ የዚህን ወጣት ተማሪ ያህል በጎ ሕሊና የላቸውም። መልካም ሀሳቡን በመጥፎ ስታጠፉበት ደግሞ ሌላ በጎ ሀሳብ ይፈጥርና በዚያም ተመስርቶ በጎ ድምዳሜ ላይ ይደርሳል። በርሱ በጣም ተደነቅሁ እንዲህ ያለ ነገር ሳይ የመጀመሪያዬ ነው።

ንብ እንሁን ዝንብ አንሁን!


ቤተ ክርስቲያን የኖህ መርከብ ናት በውስጧ ርግብም እባብም አለ። ቀና ልቡና ከሌለን እንዴት ከእባብ ጋር አብረን እናገለግላለን ብለን ከመርከቧ ይውረዱልን የሚል ትንቅንቅ ውስጥ መግባታችን አይቀርም። እንደ ዝንብ ካየን ብዙ መጥፎ ነገሮች ከፊት ለፊታችን ተደቅነው ቤተ እግዚአብሔር መመላለስ ሁሉ ልንጠላ እንችላለን። ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንደሚለው ወደ ኖህ መርከብ የገባ እባብ ሲወጣም እባብ ነው። ወደ ቤተክርስቲያን የገባ የእባብ ልብ ያለው ሰው ግን ሲወጣ ተለውጦ የጠቦት ልብ ይኖረዋል። ወደ ኖህ መርከብ የገባ ቀበሮ ከመርከቡ ሲወጣም ቀበሮ ነው። ቤተክርስቲያን የገባ የቀበሮ ልብ ያለው ሰው ግን ሲወጣ የበጎች ልብ ይዞ ነው የሚወጣው። ምናልባት እነዚህ ቀበሮዎችና እባቦች ቤተክርስቲያን ገብተው ያልተቀየሩት እኛ የሚቀይር ማንነት ስለሌለን ይሆናል። እግዚኣብሔር የነርሱን ድክመት ያሳየን እንድንጸልይላቸው ይሆናል።

ንብ እንሁን ዝንብ አንሁን!


ልቡናችን ካልነጻ መልካሙን እንኳ ብናይ አንዳች ክፉ ማግኘታችን አይቀርም። ምን የተቀደሰ ቦታ ብንቆም እንደደመና ከከበቡን ቅዱሳን ይልቅ ደካሞች ላይ ዐይናችን መሄዱ አይቀርም። እንደ ዝንብ ካየን ቆሻሻው ዙርያችን ሞልቷል። ዐይናችን ይቀየር ዘንድ ልባችን ይነጻ ዘንድ ከምንወቅሳቸውና ነውር ነቀፋ ከምናወጣላቸው በላይ እኛ የጌታችን ይቅርታ እና መሀሪነት የሚያስፈልገን ደካሞች ልንሆን እንችላለን። በነገር ሁሉ መልካሙን እንፈልግ። በቆሻሻ መሀል አበቦችን እንፈልግ። በበጎ ሕሊና በፊታችን እንደ ደመና የከበቡንን የጸኑትን ቅዱሳን በማሰብ በፊታችን ያለውን ሩጫ እንሩጥ!

ንብ እንሁን ዝንብ አንሁን!


(ከአባ ፓይሲዮስ መንፈሳዊ ምክር ሦሥተኛ መጽሐፍ የተገኘ)

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

መምህር ኢዮብ ይመኑ እባላለሁ!

በኢኦተቤ ሰባኬ ወንጌል ነኝ!

መምህራን በተለያዩ ቦታዎች እየተዘዋወርን ወንጌልን እናዳርሳለን! እርስዎ የማኅበረ ቅዱሳንን ዩቱዩብ ሰብስክራይብ በማድረግና በማጋራት ብቻ ወንጌልን ለዓለም ማድረስ እንደሚችሉ ያውቃሉ?

እኔ ዘመቻውን ተቀላቅያለሁ እናንተስ?

ዩ ቲዩብ፡- http://www.youtube.com/user/EOTCMK

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

"አይ ሞኝነቴ ሞቴን መርሳቴ"

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

"ላመስግንህ የእኔ ጌታ"
ቀሲስ ምንዳዬ ብርሃኑ

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

#ውዳሴ_ከንቱ

፪. እኛ ስለ ሰዎች
ምስጋና ከእኛ ስለ ሰዎች በሚቀርብበት ወቅትም ልናስተውላቸው የሚገቡ ነገሮች አሉ፡፡በእርግጥ ሰዎችን ማመስገንና እንዲመሰገኑ መፈለግ ከክርስቲያኖች የሚጠበቅ የበጎ ምግባር መገለጫ ነው፡፡
እንደ ዲያቢሎስ መመስገን ብቻ እንጂ ሰውን ማመስገንና ማበረታታት የማይፈልጉ ሰዎች አሉና፡፡ ነገር ግን የምስጋናውን ልክ የምናልፍ ከሆነ ለተመስጋኙ ጥቅም ከመሆን ይልቅ ፈተና የምንሆንበት ዕድል የሰፋ ነው፡፡በውዳሴ ከንቱ የወደቀ ከሆነም መሰናክል የሆንነው እኛ በመሆናችን እንቀጣለን፡፡ "ከእነዚህ ከታናናሾቹ አንዱን የሚያሰናክል ቢኖር የወፍጮ ድንጋይ በአንገቱ ታስሮ ከጥልቅ ቢጣል ይሻለው ነበር” ተብሎ ተጽፏልና፡፡ ማቴ 18÷6 ስለዚህም መመስገን የሚገባውን ሰው መለየትና መመስገን በሚገባው ልክ ማመስገን ከእኛ የሚጠበቅ ይሆናል ማለት ነው፡፡ ደግሞም “ከጠላት መሳም የወዳጅ ንክሻ ይሻላል” ተብሎ እንደ ተፃፈ ለሰዎች ከሚቀርብላቸው ምስጋና ይልቅ ወቀሳና ምክር ለመሻሻል ይጠቅማቸዋልና ማመስገን ብቻ ሣይሆን መውቀስና መምከር ተገቢ ነው፡፡ጌታችን የአይሁድ መምህር የሆነ ኒቆዲሞስን “አንተ የአይሁድ መምህር ስትሆን ይህን አታውቅምን?” ብሎ አለማወቁን ገስፆ መምህርነቱን አመስግኖ እንደ ተናገረው ዮሐ. 3÷10
፫. እኛ ስለ እኛ
ውዳሴ ከንቱ ሰዎች እኛን በሚያመሰግኑበት ወቅት ባለን አቀባበል ወይም እኛ ለሰዎች በምናቀርበው ምስጋና ልክ ብቻየ ሚመዘን አይደለም፡፡እኛ ስለ ራሳችን ባለን አስተያየትና በምናቀርበው ምስጋናም ጭምር እንጂ፡፡ በእርግጥ ለራስ ጥሩ አመለካከት መያዝና ራስን ማበረታታት ተገቢ ነው፡፡ይህ ሁኔታ ልክ ከሌለው ግን ለራሳችን ብቻ የምናዜም በውይይት መሃል እኛ ብቻ መነሳት የምንፈልግ ከእኛ ይልቅ ሌላ ሰው ቢነሣ ቅር የሚለን ገፍተንም ስለራሳችን ጥሩነት የምናወራ እንሆናለን፡፡ በቅዱስ መጽሐፍ “የሌላ ሰው አፍ ያመስግንህ ” ተብሎ መጻፉ ሰው በራሱ አንደበት መመስገን እንደሌለበት የሚያስረዳ ነው፡፡በወንጌልም የታዘዙትን ሁሉ በፈፀሙ ጊዜ አገልጋዮች ምን ማለት እንዳለባቸው የተቀመጠላቸው ትዕዛዝ “የማንጠቅም ባሪያዎች ነን በሉ” የሚል ነው ሉቃ. 17፡10 ፡፡ ይህም ሰው ከልክ አልፎ ለራሱ ቦታ እንዳይሰጥና በውዳሴ ከንቱ እንዳይወድቅ ለመጠበቅ የታዘዘ ነው፡፡ ርዕሳችን ውዳሴ ከንቱ በመሆኑ በማይጠቅም ውዳሴ ላይ ብቻ አተኮርን እንጂ የሚገቡና የሚጠቀቅሙ የታዘዙም ምስጋናዎች አሉ፡፡ “ የማይጠቅም ውዳሴ ” የሚለውን ርዕስ በራሱ የሚጠቅም ውዳሴ መኖሩን የሚጠቁም ነው፡፡

➥ቀጣይ:- የሚጠቅም ውዳሴ.....

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

"ስብከት"
የዘመነ ስብከት መጀመሪያ ሳምንት

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የበዓላት ቀኖና መሠረት ከህዳር ፲፭/15 እስከ ጌታችን ልደት (ታኅሣሥ ፳፰/፳፱-28/29) ድረስ ያለው ወቅት በዘመነ ብሉይ የነበሩ ቅዱሳን ነቢያት የጌታን ልደት በተስፋ እየጠበቁ የገቡትን ሱባኤ፣ የጾሟቸውን አጽዋማት በማሰብ ልዩ ልዩ ክብረ በዓላት ይከበራሉ። ለእያንዳንዱ በዓልም የተለየ የቅዱሳት መጻሕፍት ንባብና ትርጓሜ፣ የተለየ የምስጋና መዝሙር ይዘመራል። በጾመ ነቢያት ውስጥ ያሉት የመጨረሻዎቹ ሦስት ሳምንታት በተለየ መልኩ ይከበራሉ። ወቅቱም ትንቢተ ነቢያትን በማሰብ "ዘመነ ስብከት" ይባላል። የነቢያት የስብከታቸው ማዕከል የክርስቶስ ሰው የመሆን ተስፋ ነውና።

የዘመነ ስብከት የመጀመሪያው ሳምንት "ስብከት" ይባላል(ከታኅሣሥ ፯/7-፲፫/13)፤ ሁለተኛው ሳምንት "ብርሃን" ይባላል(ከታኅሣሥ ፲፬/14-፳/20)፤ ሦስተኛው ሳምንት "ኖላዊ" ይባላል(ከታኅሣሥ ፳፩/21-፳፯27)።

ስብከት
ስብከት ማለት በቁሙ "የምስራች፣ አዲስ ዜና መንገርን" የሚመለከት ሲሆን ዋናው ምሥጢር ግን ከነገረ ድኅነት (ከመዳን ትምሕርት) ጋር የተገናኘ ነው።

በዚህ ዕለት (ሳምንት) ሁሉም ነቢያት ከነ ትንቢታቸው ይታሰባሉ። ይህም ከታሕሳስ ፯/7 እስከ ፲፫/13 ያለውን ይይዛል። ይሕስ እንደ ምን ነው ቢሉ፦ እግዚአብሔር አዳምን በ፯/7 ሃብታት አክብሮ በገነት ቢያኖረው "አትብላ" የተባለውን ዕፀ በለስ በላ። በዚህም ከፈጣሪው ተጣልቶ በሞተ ሥጋ ሞተ ነፍስ፣ በርደተ መቃብር፣ ርደተ ገሃነም ተፈረደበት። በኋላ ግን ንስሃ ስለ ገባ "ከ፭/5 ቀን ተኩል (፶፻፭፻/5500 ዘመን) በኋላ ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንሃለሁ" የሚል ቃል ኪዳንን ሰጠው።

ከዚህ በኋላ ለ፶፻፭፻/5500 ዘመናት ጊዜ ወደ ታች ይቆጠር ጀመር። ስለ እግዚአብሔር ሰው መሆንና ዓለምን ማዳንም ትንቢት ይነገር፣ ሱባኤ ይቆጠር፣ ምሳሌም ይመሰል ገባ።

ከአዳም እስከ ሙሴ (ዘመነ አበው) ምሳሌያት ይበዛሉ። ከሙሴ እስከ ዳዊት (ዘመነ መሣፍንት) ምሳሌያቱ እየጐሉ መጥተዋል:: ከልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት እስከ ቅዱስ ሚልክያስ ድረስ (በዘመነ ነቢያት/ነገሥት) ግን ትንቢቶች ስለ ክርስቶስና ስለ ማደሪያ እናቱ እንደ ጐርፍ ፈስሰዋል።

ነቢያትም የመሲህን መምጣት እየጠበቁ በጾም፣ በጸሎትና በትሕርምት ኑረዋል። እንባቸውንም አፍስሰው ቅድመ እግዚአብሔር ደርሶላቸዋል። መድኅን ክርስቶስም ተወልዶ አድኗቸዋል።

በዘመነ ስብከት የመጀመሪያው ሰንበት (እሑድ) በኦሪተ ሙሴ፣ በነቢያትም አስቀድሞ ስለ አካላዊ ቃል ኢየሱስ ክርስቶስ ሰው መሆን ትንቢት ተነግሮ፣ ምሳሌ ተመስሎ፣ ሱባዔ ተቆጥሮ እንደ ነበር ይነገራል፤ ይሰበካልም፡፡
"እምኦሪተ ሙሴ እስከ ነቢያት ሰበኩ ምጽአቶ ንህነ ነአምን ስብከቶ ፣ ከኦሪተ ሙሴ አንስቶ እስከ ነቢያት የወልደ እግዚአብሔርን መምጣት ሰበኩ አስተማሩ እኛም ሙሴና ነቢያት የሰበኩት ስብከት አምነን እንቀበላለን" እንዳለ (ቅዱስ ያሬድ )
በተጨማሪም በዚህ ሳምንት ከአብርሃም እስከ ዳዊት ባለው ትውልድ ውስጥ ስለ ክርስቶስ ሰው መሆን የተሰበከው ስብከት ይታሰባል፡፡
የነቢያት ስብከት: በዚህ ዕለት ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሙሴ በሕግ ነቢያትም በትንቢት እንደ ጻፉለት የሚናገረው ወንጌል ይነበባል (ዮሐ 1፡44)፡፡ ነቢየ እግዚአብሔር ዳዊትም ‹‹ፈኑ እዴከ እም አርያም » እጅህን ከአርያም ላክ አድነኝም› (መዝ 143፡7) በማለት ስለክርስቶስ ማዳን በትንቢት መነጽር ተመልክቶ የዘመረው የመዝሙር ክፍል እንዲሁ ይሰበካል፡፡ ከዐበይት ነቢያት አንዱ የሆነው ነቢየ እግዚአብሔር ኢሳይያስም ‹‹ሰማዮችን ቀደህ ምነው ብትወርድ! ተራሮችም ምነው ቢናወጡ›› (ኢሳ 64፡1) ብሎ ስለክርስቶስ ከሰማየ ሰማያት መውረድ፣ ከድንግል ማርያምም መወለድ የተናገረውን ትንቢት ቤተክርስቲያን ትሰብካለች፡፡
የቤተክርስቲያናችን ስብከት: ብርሃነ ዓለም ቅዱስ ጳውሎስ በመልእክቱ “እኛስ የተሰቀለውን ክርስቶስን እንሰብካለን” (2ኛ ቆሮ 4፡5) እንዳለው ቤተክርስቲያን በተለይ በዘመነ ስብከት ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለሰው ልጆች የሰጠውንና የፈጸመውን የማዳን ተስፋ ትሰብካለች፡፡ ቅዱስ ያሬድም በመዝሙሩ “ከዓለም በፊት የነበረውንና መድኃኒት የሆነውን ወልድን እንሰብካለን” እንዳለ ቤተክርስቲያናችን ፣ በጊዜውም አለጊዜውም፣ በችግርም በደስታም ስለ ኃጢአታችን የሞተውንና አምላክ ወልደ አምላክ ክርስቶስን ትሰብካለች።

አምላካችን እግዚአብሔር ከአባቶቻችን በረከት ያድለን፣ አሜን!

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

#ውዳሴ_ከንቱ

ውዳሴ ከንቱ የሚለው ቃል የማይረባ የማይጠቅም ውዳሴ የሚል ትርጓሜ ያለውሲሆን ውዳሴ ብጡል (የተናቀ፤ተርታ) ውዳሴ ተብሎም ይጠራል፡፡የቃሉ ትርጉም በዚህ መልኩ የሚፈታ ይሁን እንጂ “ የማይጠቅም “ ከመሆን አልፎ ሰውን ሊጎዳ የሚችል ነገር በመሆኑ የቤተክርስቲያናችን መጻሕፍት አጥብቀን ልንሸሸው እንዲሚገባ ያስተምራሉ፡፡
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እግሩ ስር ተቀምጣ ቃላት ታዳምጥ የነበረችውን የማርታ እህት ማርያምን “ማርያምስ የማይቀሟትን በጎ ዕድል መረጠች ” ሉቃ10÷42 ብሎ ያመሰገነበትን ቃል አበው ሲተረጉሙ “ መማር ውዳሴ ከንቱ የለውም “ አላውቅም ማለት ነውና፡፡ ስለዚህም አጋንንት የማይቀሟትን (ዋጋዋን ) የማያስቀሩባትን መማርን መረጠች ማለት ነው ብለው መተርጎማቸው ‹‹ውዳሴከንቱ›› የሰውን የልፋት ዋጋ በምድራዊ ክብር የሚያስቀር ከንቱ ነገር መሆኑን ያስረዳል፡፡ አበው ከውዳሴ ከንቱ እንድንጠበቅ ማስተማራቸው የመልካም ስራችን ዋጋ ሰዎች በሚያቀርቡልን የምስጋና ስጦታ ምክንያት በምድር እንዳይቀርብን በማሰብ ነው፡፡ በወንጌልም ጌታ ከሰዎች ምስጋና በመሻት መልካም ሥራቸውን በሰው ፊት ስላደረጉ ፈሪሳውያን ሲናገር “እሙንቱሰ ነሥኡ እሴቶሙ… እነዚህስ ዋጋቸውን ተቀብለዋል” ማቴ6÷2 በማለት ከሰው የተቀበሉት ምስጋና ሰማያዊ ዋጋቸውን እንዳሳጣቸው አስተምሯል፡፡
እንዲህ ስንል ግን በሰው የተመሰገነ ሁሉ ውዳሴ ከንቱ ሆኖበታል ያልተመሰገነ ደግሞ አልሆነበትም ማለትም አይደለም፡፡ በልቦናው የመመስገን መሻት ኖሮት መልካም ሥራ የሠራ ነገር ግን በለስ ያልቀናው ያልተመሰገነ ሰው ሊሰርቅ ሄዶ አጥር ፀንቶበት፣ ውሻ ጮሆበት፣ጠባቂ ነቅቶበት የተመለሰ ሰውን ይመስላል፡፡ መሻቱ በልቦናው ስላለ ሰዎች ባያመሰግኑትም ቅሉ ለመመስገን በመሻት አስቀድሞ ወድቋልና ከሰው ውዳሴ ሳይፈልግ የሠራ ሰውም ሰው ቢያመሰግነው እንኳ አይሻውምና በውዳሴ ከንቱ ወደቀ አያሰኝም፡፡ ይህም ውዳሴ ከንቱ ኃይል አግኝቶ ሰውን የሚጥለው የተዘጋጀ ልቦና ሲኖረው መሆኑን እንገነዘባለን፡፡
➥ውዳሴ ከንቱ በሦስት ዓይነት መንገድ ሲቀርብ እንደ አቀራረቡና አቀባበሉም ሰዎችን ሊጎዳ ይችላል፡፡
፩. ሰዎች ስለ እኛ
ውዳሴ ከሰዎች ለእኛ በሚቀርብበት ወቅት የሚያመሰግነን ሰው ማን ነው? ምስጋናውስ ለእኛ የሚገባን ነውን? የሚሉትን ጥያቄዎች ራሳችንን መጠየቅ ከጉዳት ይጠብቀናል፡፡ የሚያመሰግነን ሰው ማነው? የሚለውን ማሰባችን ተወዳጅነትን ለማትረፍና በአፀፋ ለማመስገን ከሚመጡ ሰዎች ሲጠብቀን ምስጋናው ለእኔ ይገባልን? የሚለውን ማሰብ ደግሞ ምስጋናውን ይገባናል ብሎ ከመቀበል ይጠብቀናል፡፡ በወንጌል ጌታችን “ ቸር መምህር ሆይ “ ብሎ የቀረበው ሰው መመስገንንና ተወዳጅነትን ለማትረፍ ሲሉ ምስጋና ከሚያቀርቡ ሰዎች የሚመደብ ነው፡፡ (ማር 10÷17) ምስጋናን “ለእኔ የሚገባ ነውን?” ብሎ መርምሮ መቀበልን የተማርነው ከቅዱሳን እናቶቻችንና ከቅዱሳን አባቶቻችን ነው፡፡
ክብር ይግባትና በሚገባት ግብር የተመሰገነች እመቤታችን “እፎኑ ከመ ዝኑ እንጋ አምኃ ይትአምኁ - እንዲህ ያለውን ሰላምታ እንዴት ይቀበሉታል?” ሉቃ 1÷29 ማለቷ ቅዱሳን በሚገባቸው ገንዘብ ቢመሰገኑ እንኳ (በትሕትና ) አይገባንም እንደሚሉ የሚያስረዳ ነው፡፡
በትንሣኤ ዘጉባኤም “ተርቤ አብልታችሁኛልና፣ ተጠምቼ አጠጥታችሁኛልና ….” ተብለው የሚመሰገኑ ቅዱሳን “መቼ ተርበህ አበላንህ?፣መቼ ተጠምተህ አጠጣንህ?.....” ሲሉ ሠርተው እንዳልሰሩ ሆነው በትሕትና እንዲመልሱ ተጽፏል፡፡ ማቴ 25÷44
አቡነ ተክለሃማኖትም ከብዙ ትሩፋትና ተጋድሎ በኋላ “አሌ ሊተ ወይ ሊተ ለዘኢገበርኩ ምንተ - ወዮ ለኔ ምንም ላልሠራሁት” እያሉ ምርር ብለው ማልቀሳቸውን ገድላቸው ዘግቦታል፡፡
እኛም ምንም እንኳ ከእነርሱ መዐርገ ትሕትና ደርሰን አይገባንም ማለት ባንችል በብሩህ ፊት ሆነን ውዳሴን እያጣጣሙ ከመቀበል መለየት ይገባናል፡፡ይልቁንም ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ እንዳሉት በምንመሰገንበት ወቅት የከፉ ኃጢአቶቻችንን እያሰብን ራሳችንን መገሰጽ ይገባናል፡፡

፪.እኛ ስለሰዎች ........ይቀጥላል .....

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

✝️እግዚአብሔር ርኅሩኅና መሐሪ ነው፡፡

"እግዚአብሔር ርኅሩኅና መሓሪ ነው፥ ከቍጣ የራቀ፥ ምሕረቱም ብዙ ነው፡፡" መዝ 144(145)÷8

ስለ እግዚአብሔር ርኅሩኅነትና መሓሪነት ማወቅ ለመንፈሳዊ ሕይወታችን ቁልፍ ነው፡፡ እኛ ሰዎች በደል የማያጣን ነን፡፡ ድካም የማይለየን ነን፡፡ ርኅሩኅነቱን ስንረዳ ሳናውቅ በስህተት አውቀን በድፍረት ለሰራነው ኃጢአት እንደሚምረን እንረዳለን፡፡

በመንገድ ስንሄድ መኪና ሰው ገጭቶ እናያለን፡፡ ሹፌሩ መግጨት ፈልጎ ነው ሰው የሚገጨው ? አይደለም፡፡ መቼም ማንም ሰው ሆን ብሎ ሰው አይገጭም፡፡ አንዳንዶቻችን እንደዚህ ነን፡፡ ሆን ብለን ኃጢአት ማድረግ አንፈልግም፡፡ ግን ደግሞ ስጋችን ደካማ ስለሆነ ሳንፈልግ እናደርጋለን፡፡ፈልጎ ማድረግና ሳይፈልጉ ማድረግ ይለያያል፡፡ ሆን ብሎ ሰው ያልገጨ ሹፌር እንዴት እንሚሆን አይታችሁታል? በሰራው ስህተት ከልቡ ያዝናል፡፡ እግዚአብሔርን ሆን ብለን መበደል የማንፈልግ ሰዎች አለን፡፡እርሱን ደስ ለማሰኘት ጠዋት ስንወጣ ሰላም አውለኝ ብለን ተማጽነነው ወደ ተግባራችን የምንወጣ ሰዎች አለን፡፡ እንዲህ ያልነው እግዚአብሔርንም እንዳንበድለው ፈልገን ጭምር ነው፡፡

በተሳሳትነው ነገር እስከ ተጸጸትን ድረስ አምላካችን እንደሚራራልን መረዳት አለብን፤ ውኃ ውስጥ ገብቶ እየሰመጠ እየሰመጠ እንደሚሄድ ሰው አንዳንዶቻችን ግን ሁሌ እየበደልኩት እንዴት ይቅር ይለኛል? በሚል አነገጋገር ውስጥ እየሰመጥንና እየሰመጥን ስንሄድ እንገኛለን፡፡እግዚአብሔር ርኅሩኅ ነው ፡፡ ርኅሩኅነቱን ስናስብ እየሰመጥን ካለንበት (ሁሌ እየበደልኩት ይቅር አይለኝም ከሚል አባባል) ያወጣናል፡፡

ከእጃችሁ አምልጦ የተሰበረ ብርጭቆ ተመልሶ ብርጭቆ መሆን እንደማይችል እኛም ይቅር እንደማንባልና እንደ ብርጭቆው ተስፋ የሌለን አድርገን ማሰብ የለብንም፡፡ ርኅሩኅ ነውና ይራራልናል ፤ መሐሪ ነውና ይምረናል፡፡መልሰን በእግዚአብሔር ፊት በመቅረብ፡- 'አባት ሆይ ማረን 'ልንል ይገባል እንጂ የጤና ችግር ኖሮበት ሰው ፊት እንደማይቀርብ እንዲሁ ፊቱ መቅረብ መተው የለብንም፡፡

ሰዎች ሰውን መጉዳት ሲፈልጉ ከሚያደርጉት ነገር አንዱ ስለ ጠሉት ሰው የተዛባ ነገር ማስወራት ነው፡፡ ጠላት ዲያብሎስም እኛ እግዚአብሔርን በበደልን ጊዜ እግዚአብሔር ይቅር እንደማይለንና ፊቱ መቅረብ እንደማንችል ይነግረናል፡፡ እግዚአብሔር ግን ርኅሩኅና መሐሪ መሆኑን ስናውቅ ግን አሉባልታውን ወደ ጎን ትተን ፊቱ በመቅረብ ማረን የምንልበት አዲስ ምዕራፍ እንከፍታለን፡፡

እናት ያለቀሰ ልጅዋን እያሻሸች እንደምታጽናና እግዚአብሔር ርኅሩኅና መሐሪ ነው የሚለው ቃል እጅግ የሚያጽናና ነው፡፡ በተጨማሪም እግዚአብሔር ለቁጣ የዘገየ(የማይቸኩል)፣ ምሕረቱም ብዙ እንደሆነ ቃሉ ይነግረናል፡፡

ወንጀል ሰርተሃል ተብሎ ፍርድ ቤት በየቀጠሮው ሲመላለስ የከረመ ሰው እስራት የማያሰጥህ ነው ተብሎ መዝገቡ ሲዘጋለት እየተደሰተ ወደ ቤቱ እንደሚመለስ ሰው የእግዚአብሔር ርኅሩኅነት፣ መሐሪነት፣ ከቁጣ የዘገየና ምሕረቱ ብዙ መሆኑን ስንሰማ የተጨነቀች ነፍሳችንን ደስ በጣም ደስ ያሰኛታል፡፡ነፍሳችን የሰማችው ቃል(ስለ ርኅሩኅነቱና መሐሪነቱ) እንደ ማግኔት እየሳበ ሁልጊዜም ከፊቱ እንድትቀርብና እንድትጸልይ ያደርጋታል፡፡

ርኅሩኅና መሐሪ አምላካችን ሆይ እናመሰግንሃለን ::

ወስብሐት ለእግዚአብሔር! አሜን፡፡

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

ታኅሣሥ ፮

ቅድስት አርሴማ ድንግል
እናታችን ቅድስት አርሴማን በምን እንመስላታለን? እርሷ በአድማስ ላይ ተቀምጦ እንደሚያበራ እንቁ ናትና ክብሯ ብዙ ነው:: መድኃኒታችን ክርስቶስ በወንጌል እንዳለው "በተራራ ላይ ያለች ከተማ ልትሠወር አይቻላትምና" (ማቴ. 5:11) የሰማዕቷ ሕይወት በፊታችን እንደ ብርሃን ተገልጦ ይታያል::
*ቅድስት አርሴማ እንደ ልጅ ወላጆቿን በመታዘዝ ደስ ያሰኘች ቡርክት ናት::
*ቅድስት አርሴማ ይህ ቀረሽ የማይሏት ውብ ናት::
*ቅድስት አርሴማ ድንግል ናት::
*ቅድስት አርሴማ ባሕታዊት ጻድቅ ናት::
*ቅድስት አርሴማ ኃያል ሰማዕት ናት::
➺ይህስ እንደ ምን ነው ቢሉ:
+አበው በትውፊት እንደ ነገሩን ከሆነ ቅዱሱ ጐርጐርዮስ የታላቁዋ ሰማዕት ቅድስት አርሴማ ትልቅ ወንድም ነው:: በዜና ሰማዕታት ተጽፎ እንደሚገኘው በዚያ የመከራ ዘመን ቅዱስ ጐርጐርዮስ ሦስት ኃላፊነቶች ነበሩበት:-
1.ቅድስት አርሴማን ጨምሮ ደናግሉን ማጽናት
2.ትምሕርተ ቤተ ክርስቲያንን በሚገባ ማጥናት
3.የሚመጣውን መከራ ለመቀበል ራሱን ማዘጋጀት::
+ቅዱሱ 3ቱንም ኃላፊነቶች በሚገባ በመወጣቱ ከራሱ አልፎ ለሌሎቹ አርአያ መሆን ቻለ:: ያቺን ንጽሕት አርበኛ ቅድስት አርሴማንም አጽንቶ የደናግሉ መሪ አደረጋት:: መከራው ገፍቶ እስከ መጣበት ጊዜ በአንድ የደናግል ገዳም ውስጥ ሆነው ይጸልዩ: ይጾሙ: ገዳማዊ ሥራንም ይሠሩ ነበር::
+ለዚህም ነው ቅድስት አርሴማና ቅዱስ ጐርጐርዮስ ጻድቃን የምንላቸው:: በሁዋላ ግን ማሕደረ ሰይጣን ዲዮቅልጢያኖስ በመልኩዋ ተማርኮ ቅድስት አርሴማን ካላገባሁ በማለቱ ቅዱስ ጐርጐርዮስ ድንግሏን አርሴማን ጨምሮ ክርስቲያኖችን ይዞ ወደ አርማንያ ተሰደደ::
+በአርማንያም በአንድ ገዳም ውስጥ ተደብቀው በጾምና በጸሎት ለጥቂት ጊዜ ቆዩ:: ነገር ግን ረሃብ ፈጃቸው:: የሚላስ የሚቀመስ ነገር በአካባቢው ባለ መኖሩ ቅዱስ ጐርጐርዮስ ወደ ከተማ ለመውጣት ተገደደ::
+በዚያም በድርጣድስ ቤተ መንግስት ውስጥ ባርነት ተቀጠረ:: በሚያገኛት ገንዘብም ወገኖቹን ይረዳ ነበር:: መከራው ግን አለቀቃቸውም:: ርጉም ዲዮቅልጢያኖስ ቅዱሳኑ ወደ አርማንያ መሔዳቸውን ስለ ሰማ ይዞ እንዲልክለት ድርጣድስን ላከው::
+ድርጣድስ ግን ቅድስት አርሴማን ባያት ጊዜ ከውበቷ የተነሳ መታገስ ባለመቻሉ "ካላገባሁሽ" አላት:: ድንግሊቱ ግን "እኔ የክርስቶስ ሙሽራ ነኝ: አይሆንም" አለችው:: ሊያስፈራራት ሞከረ:: ዐይኗ እያየ ደናግሉን ጨፈጨፋቸው::
+አልሳካልህ ቢለው በአደባባይ በግድ ሊያገባት ቢሞክር እጁን ጠምዝዛ በሰው ሁሉ ፊት መሬት ላይ ጣለችው:: እጅግ ስላፈረ አስገረፋት: አሰቃያት: ዐይኗንም አወጣ:: በመጨረሻም አንገቷን አስቆርጦ ከሰማዕታቱ ጋር ተራራ ላይ ጣላት::
+ከነገር ሁሉ በሁዋላ ድርጣድስና ባለሟሎቹ ለአደን በሔዱበት ርኩስ መንፈስ ወደ አውሬነት (እሪያነት) ቀየራቸው::
+የንጉሡ እንስሳ (አውሬ) መሆን በአርማንያ ታላቅ ድንጋጤን ፈጠረ:: የንጉሡ እህት ስታለቅስ በራዕይ "ለእመ ኢያዕረግምዎ ለጐርጐርዮስ አልብክሙ ድኂን-ጐርጐርዮስን ከተቀበረበት ካላወጣችሁት አትድኑም" አላቸው:: ወዲያውም ቆፍረው አወጡት::
+ቅዱሱ እንደ ወጣ ዕረፍትን አልፈለገም:: ለ15 ዓመታት ቀባሪ አጥቶ የተበተነውን የቅድስት አርሴማንና የሰማዕታቱን አጽም ሰብስቦ በክብር አኖረው::
ድርጣድስና ባለሟሎቹንም ወደ በርሃ ሒዶ ፈወሳቸው::
+የሰማዕቷ ቅድስት አርሴማ አጽም በ14ኛው መቶ ክ/ዘመን ከሌሎች ሰማዕታት አጽም ጋር ኢትዮዽያ እንደ መጣ አባቶቻችን በትውፊት ነግረውናል:: ለዚህም ይመስላል ቡርክቷ እናታችን ከሌሎች ሃገራት ለይታ ለኢትዮዽያውያን ልዩ ፍቅር ያላት:: በዋናው ገዳሟ (ወሎ /ኩላማሶ/ : ስባ : ውስጥ የሚገኝ ነው) ጨምሮ ስሟ በተራበት ሁሉ ኃይልን ታደርጋለችና::
+ነገር ግን ወንድሞቼና እሕቶቼ በቅድስቷ እናታችን ስም የሚነግዱ ሥጋውያን ሰዎች በዝተዋልና እንጠንቀቅ:: የሰማዕቷ ክብር ብዙ ነውና በሕልም ላይ ብቻ አንታመን:: አባ እንጦንስ እንዳሉት "በሕልሙ የሚታመን ሰው ከንቱ ነውና::" (መዝ. 75:5)
+በዚህ ዕለት ከሰማዕቷ ጋር የመንፈስ እናቷን ቅድስት አጋታን ልናስባት ይገባናል:: ይህች እናት እመ-ምኔት ስትሆን ቅድስት አርሴማን ታስተምራት: ታጸናት: ከጐኗም ትቆምላት ነበር:: ረሃቧን: ጥሟን: ስደቷን: መከራዋንም ሁሉ አብራት ተሳትፋለች:: በፍጻሜውም አብራት ተሰይፋለች::

ይህች ዕለት ለቅድስት አርሴማና ለተከታዮቿ ሰማዕታት የፍለሰትና የቅዳሴ ቤት መታሰቢያ ናት።

©ስንክሳር

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

#ዘፋኝነት
በዘመናችን የሥልጣኔ፣ የፍልስፍና የዘመናዊነት መገለጫ ዘፋኝነት የሚመስላቸው በርካታ ሰዎች አይጠፉም፡፡ በተለይም ‹‹ዘመናዊ›› ነን ብለው ራሳቸውን በሚቆጥሩ ሰዎች ዘፈን የማይዘፍን ወይም የማያዳምጥ ኋላ ቀር ተደርጎ ይታሰባል፡፡ አበው ‹‹ሳይርቅ በቅርቡ ሳይደርቅ በቅጠሉ›› እንዲሉ የተሰጥኦ ውድድር በሚል ሰበብ በትውልዱ ላይ የዘፋኝነት መንፈስ በውስጡ አስርጸዋል፡፡ ከዚህ ከተሳሳተ ድርጊታቸው እንዲታረሙ ለማስገንዘብና የዘፋኝነት ሱስ ተጸናውቶን ከእግዚአብሔር መንግሥት እንዳይለየን ለማስተማር ይህን ርዕሰ ጉዳይ ማንሳት አስፈልጓል፡፡
ዘፈን ምንድን ነው?የሚል ጥያቄ ለምናቀርብ ዘፈን ማለት ዝላይ፣ እስክስታ፣ በቅኔና በግጥም ከልዩ ልዩ መሣሪያ ጋር እየተቀነባበረ የሚቀርብ የደስታ ምልክት ነው ፡፡ በዘፈን ላይ ጥናት አድርገናል የሚሉ አንዳንዶች ደግሞ ‹‹የመንፈስ እርካታ›› ‹‹የሕይወት ቅመም›› እያሉ ለሥጋቸው መደሰቻ የሚመች ትርጉም ሲሰጡትም ይደመጣሉ፡፡
መዝሙር ከዘፈን ጋር ያለውን ልዩነት ምን እንደሆነ መለየት እንድንችል መዝሙር ፈጣሪያችን እግዚአብሔርን፤እናቱ ቅድስት ድንግል ማርያምና ቅዱሳንን የምናመሰግንበት፤ጸጋ እግዚአብሔር የሚያሰጥ፤ ሰማያዊ መንግሥቱን እንድንወርስ የሚያሳስብ ነው፡፡ ዘፈን ደግሞ በተቃራኒው ፈቃደ ሥጋን የሚያነሳሳ፤ ከእግዚአብሔር መንግሥት የሚለይ እኩይ ተግባር ነው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ዘፈን ቅዱስ ጳውሎስ የሥጋ ፈቃዳት ብሎ ከዘረዘራቸው የሚመደብ ነው፡፡ ለዲያብሎስና ጭፍሮቹ አጋንንት የሚቀርብ መስዋዕት እንደሆነም ከዚህ በታች መጽሐፍ ቅዱስን ዋቤ አድርገን እናያዋለን፡፡
የሥጋ ፈቃድ ነው
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ገላቲያ ለሚኖሩ ክርስቲያኖች በላከው መልእክቱ ‹‹የሥጋ ሥራም የተገለጠ ነው እርሱም ዝሙት ርኩሰት መዳራት ጣዖትን ማምለክ ምዋርት ጥል ክርክር ቅንዓት ቁጣ አድመኝነት መለያየት መናፍቅነት ምቀኝነት መግደል ስካር ዘፋኝነት ይህንም የሚመስል ነው›› በማለት ዘፋኝነት ከሥጋ ፈቃዳት አንዱና ዋነኛው እንደሆነ ተናግሯል ፡፡
የዲያብሎስ መሥዋዕት ነው
ዘፈን ዲያብሎስና ሠራዊቱን ለማስደሰት የሚቀርብ መሥዋዕት ነው፡፡ ለእግዚአብሔር አምላካችን የሚቀርበው መስዋዕት ምስጋና ሲሆን፤ የዲያብሎስ ፈቃድ የሚፈጽሙ ሰዎች ደግሞ የሚያቀርቡ መስዋዕት ዘፈን ነው፡፡ ሕዝበ እስራኤል በእግዚአብሔር ቸርነት በሙሴ መሪነት ከግብጽ ባርነት ከወጡ በኋላ ከፈርዖን የግፍ አገዛዝ ያጣቸውን እግዚአብሔርን በመርሳት ለአምላካቸው በሰገዱበት እግራቸው ለጣዖት ሰግደዋል፡፡ እግዚአብሔርን ባመሰገኑበት አንደበታቸው ለዲያብሎስ ዘፍነዋል፡፡ ከሰማይ መና ወርዶላቸው እንዳልተመገቡ ለዲያብሎስ የቀረበ መስዋዕት በልተዋል፡፡ በዚህ ክፉ ሥራቸው እግዚአብሔር አምላካቸውን አሳዝነዋል፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ ለዲያብሎስ ያቀረቡት የዘፈን መሥዋዕት እንዲህ በማለት ገልጾታል ‹‹ሕዝቡም ሊበሉ ሊጠጡም ተቀመጡ ሊዘፍኑም ተነሡ ተብሎ እንደ ተጻፈ ከእነርሱ አንዳንዶቹ እንዳደረጉት ጣዖትን የምታመልኩ አትሁኑ ›› /ዘጸ. 321-7/፡፡ ነብየ እግዚአብሔር ኢሳይያስም አጋንንት ዘፈን እንደሚስማማቸው ‹‹በዚያም አጋንንት ይዘፍናሉ ›› ብሎ በግልጽ ዘፈኝነት የአጋንንት ሥራ መሆኑን ተናግሯል፡፡ ከዚህ አንጻር የምንዘፍን ሰዎች ለዲያብሎስና ለተከታዮቹ አጋንንት መሥዋዕት እያቀረብን እንደሆነ አስተውለን ይሆን?
ዘፈኝነት የሚያስከትለው ችግር ከክብር ማሳነስ ነው፡፡ የያዕቆብ ልጅ ዲና የአሕዛብ ሴቶች ዘፈንና ጨዋታ ልታይ ሔዳ የኤሞር ልጅ ሴኬም ከእሷ ጋር በመተኛት ከክብር አሳንሳ እንድትመለስ አድርጓታል፡፡ ሊቀ ነቢያት ሙሴም ይህን ታሪክ መግልጽ አስቀምጦታል፡፡ ‹‹ለያዕቆብ የወለደችለት የልያ ልጅ ዲናም የዚያን አገር ሴቶች ልጆችን ለማየት ወጣች፡፡ የአገሩ አለቃ የኤዊያዊ ሰው የኤሞር ልጅ ሴኬም አያት ወሰዳትም ከእርሷም ጋር ተኛ አስነወራትም ›› ብዙዎች ዘፈን የሚያመጣውን ጣጣ ባለማወቅ ለመዝናናት በሚል ሰበብ ከቤታቸውን ወጥተው ድንግልናቸውን በማጣት ከክብር አንሰው ይመለሳሉ፡፡ ላልተፈለገ እርግዝና ተጋልጠው ከዓላማቸው ተሰነካክለው ይቀራሉ፤ በራሳቸው መንገድ ባመጡ ኃጢአት እግዚአብሔርን ያማርራሉ፡፡
ሐዋርያው ቅዱስ ያዕቆብ በዘፈን ምክንያት ከሚመጣ ኃጢአት ራሳችንን እንድንጠብቅ እንዲህ ይለናል ‹‹ከእናንተ መከራን የሚቀበል ማንም ቢኖር እርሱ ይጸልይ፤ ደስ የሚለውም ማንም ቢኖር እርሱ ይዘምር ›› በማለት ይመክረናል፡፡
ከዚህ መልእክት ልንወስደው የሚገባን ዓብይ ቁም ነገር በዘፈን ምክንያት ከሚመጡ የኃጢአት ሥራዎች ራሳችንን በመጠበቅ እንዳለብን ነው፡፡ ዘፋኝነት እግዚአብሔርን የሚያስቀይም፣ ሰዎችኝ ወደ ኃጢአት የሚጋብዝ፣ ከመንግሥተ ሰማያት በአፍአ የሚያደርግ ተግባር ነው፡፡ በመሆኑም ዘፋኝነት ሥራችን የሆነ ሰዎች እግዚአብሔር በሰጠን አንደበት እንዘምርበት፤ ዘፈን በመስማት ራሳችንን ለኃጢአት ያጋለጥን ሰዎች ንስሐ ገብተን መዝሙር እናዳምጥ! አምላካችንን ልዑል እግዚአብሔር የዘፋኝነት መንፈስ ከውስጣችን ያስወግድልን፡፡ በዘፈን ምክንያት ከምንሠራው ኃጢአት ይጠብቀን፡፡ አሜን!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

"ገባሬ መንክራት"
ገባሬ መንክራት ሰማዕት ሰማዕት መርቆሬዎስ
ተራድአነ  በገሃድ ተራድአነ በገሃድ
አዝ......
ለአረማዊ ወጣት መድኃኒት የሆንከው
ከአራዊት ጠብቀህ ከሞት የታደግከው
ካለመኖር ወደመኖር የመለስከው
ተራዳን በሃይማኖት ሆነን ለደከምነው
አዝ....
ዛሬም በእኛ ዘመን እንደ ዑልያኖስ
ጣኦት የሚያመልኩ የወጡ  ከመንፈስ
ከርስት እንዳይለዩን እደር በእኛ መሐል
ጥበብ ኃይል ሁነን መርቆሬዎስ ኃያል
አዝ....
የሮማዊ ሰማዕት የጳጳሳት ደስታ
የእግዚአብሔር አገልጋይ የኢትዮጵያ አለኝታ
ከእስር ቤት ወጥቶ ሥዕልህ  በተአምር
ዑልያኖስን ገድሎ ተመለሰ በክብር
አዝ.....
የአብ ወዳጁ  የእግዚአብሔር  አገልጋይ
ልመናችንን  አድርስ ወደአምላክ አዶናይ
በሞት እንዳንጠፋ በሕይወት ጠብቀን
በአንተ ተማጽነናል  ኪዳንህን አምነን
አዝ.....

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

መርቆሬዎስ ለተማፀነበት ሁሉ ይማልዳልና ድንቆች የሆኑ ታላላቅ ተአምራትንም ያደርጋልና።

ያም ወጣት መጋቢውን መልኩ እንዴት ነው ምን ይመስላል አለው መጋቢውም አካሉ አንተን ይመስላል አለው ይህንንም ብሎ ወደ ሥዕሉ ወስዶ ገልጦ አሳየው ወጣቱም በእገሌ በረሀ የታየኝ በእውነት ይህ ነው። በፈረሱም ላይ አፈናጥጦ ወደዚህ ያደረሰኝ ይህ ነው። እነሆ ታጥቋት በወገቡ ላይ ያየኋት የወርቅ መታጠቂያው ይቺ ናት። ስማኝ ልንገርህ እኔ በዚች አገር የምኖር አባቴም ስሙ ረጋ የሚባል መስፍን የሆነ እስላም የሆንኩ ሰው ነኝ። ክርስቲያንም ለመሆን ይች ምልክት ትበቃኛለች አሁንም በቦታ ውስጥ ሠውረኝ ለማንም ሥራዬን አትግለጥ። የክርስትና ትምህርትን አስተምሮ የእግዚአብሔርን መንገድ የሚመራኝን አምጣልኝ አለው። እርሱም ያለውን ሁሉ አደረገለት የክርስትና ጥምቀትንም አጠመቀው።

ከዚህም በኋላ ወደ ነቢያቸው መቃብር የሔዱ እሊያ እስላሞች በአንድ ወራቸው ደረሱ። ዘመዶቻቸውም ሊቀበሏቸው ወጡ። ይህን ወጣት የመስፍን ልጅ ግን አላገኙትም። አባቱም አደራ ያስጠበቀውን ወዳጁን በጠየቀው ጊዜ እርሱም በበረሀ ውስጥ ቀርቶ እንደ ጠፋ እያለቀሰ ነገረው አባቱም በሰማ ጊዜ ልብሱን ቀዶ አለቀሰ እንዲሁም ቤተሰቦቹ ሁሉም አርባ ቀኖች ያህል አለቀሱለት።

ከዚህም በኋላ በጥዋት ከቤተ ክርስቲያን ሲወጣ ይህን ክርስቲያን የሆነውን ወጣት አንድ እስላም አየው። ወደ ወላጆቹም ሒዶ እንዲህ ብሎ ነገራቸው ልጃችሁ በበረሀ ውስጥ የሞተ ከሆነ በመርቆሬዎስ ቤተ ክርስቲያን ደጅ ያየሁት እርሱን ባልመሰለኝ ነበር፤ እስቲ ሒዳችሁ አረጋግጡ። በሰሙም ጊዜ በስውር ሒደው ፈለጉት አግኝተውትም ይዘው ወሰዱት። እንዲህም አሉት በወገኖቻችን መካከል ልታሳፍረን ይህ የሠራኸው ምንድን ነው አሉት። እርሱም እኔ በሕያው እግዚአብሔር ልጅ በጌታዬና በፈጣሪዬ ኢየሱስ ክርስቶስ የማምን ክርስቲያን ነኝ ብሎ መለሰላቸው።

ይህንንም ሲል ታላቅ ሥቃይን አሠቃይተው ከጨለመ ጉድጓድ ውስጥ ጣሉት። ሽንታቸውን በላዩ እየደፉ የቤት ጥራጊም እያፈሰሱበት ያለ መብልና ያለ መጠጥ በዚያ ሰባት ቀንና ሌሊት ኖረ። እናቱ ግን ቀንም ሌሊትም በላዩ የምታለቅስ ሆነች ከልቅሶዋም ብዛት የተነሣ ከጉድጓድ አውጥተው እኛ ወደማናይህ ቦታ ሒድ አሉት። ወዲያውኑ ወደ አስቄጥስ ገዳም ሒዶ በዚያ እያገለገለና እየተጋደለ ሁለት ዓመት ኖረ።

ከዚህም በኋላ በላዩ የትንቢት ጸጋ ያደረበት አንድ መነኰስ ወደ ምስር ከተማ ሒደህ ሃይማኖትህን ከምትገልጽ በቀር በዚህ መኖር ለአንተ አይጠቅምህም አለው። ወዲያውኑ ተነሥቶ ወደ ምስር ከተማ ሔደ።

አባቱም በአየው ጊዜ ሐኪም ወደ ሚባል ንጉሥ ወስዶ ይህ ልጃችን ነበር የእስልምና ሃይማኖትን ትቶ ወደ ክርስቲያን ሃይማኖት ገብቷል አለው። ንጉሡም ስለአንተ የሚናገሩት ዕውነት ነውን አለው። እርሱም በበረሀ ውስጥ ሳለ በሌሊት ቅዱስ መርቆሬዎስ እንደ ተገለጸለትና ከእርሱ ጋር በፈረስ እንዳስቀመጠው፣ በምስር አገር ወዳለች ቤተ ክርስቲያኑ የሃያ ሁለት ቀን መንገድ እንደ ዐይን ጥቅሻ አድርሶ ከውስጥዋ እንዳስገባው፣ ሥዕሉንም አይቶ ያመጣው እርሱ መሆኑን እንደ ተረዳ ለንጉሡ ነገረው።

ንጉሡም በሰማ ጊዜ እጅግ አደነቀ። ታላቅ ፍርሀትም አደረበት አደርግልህ ዘንድ የምትሻውን ለምነኝ አለው። እርሱም በቅዱስ መርቆሬዎስ ስም ዳግመኛም በመላእክት አለቃ በቅዱስ ሚካኤል ስም ቤተ ክርስቲያን እንድሠራ ታዝልኝ ዘንድ እሻለሁ አለው።

ንጉሡም በአስቸኳይ እንዲታነፁለት አዘዘለት። በውስጣቸውም ታላላቅ የሆኑ ድንቆች ተአምራት ተገለጡ። እርሱም አበ ምኔት ሁኖ ወደርሱ ብዙዎች መነኰሳት ተሰበሰቡ። ሁለት ድርሳናትንም ደረሰ። ከሀዲያንንም አስተምሮ ወደ ቀናች ሃይማኖት መለሳቸው እግዚአብሔርንም አገልግሎ በሰላም አረፈ ። ለዚህም መነኰስ የክርስትና ጥምቀትን በተቀበለ ጊዜ ያወጡለት ስም ዮሐንስ ነው።

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱስ መርቆሬዎስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

©ስንክሳር

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

ኅዳር ፳
ቅዱስ መርቆሬዎስ ሰማዕት (ፒሉፓዴር)

ኅዳር ሃያ አምስት በዚች ቀን የስሙ ትርጓሜ መርቆሬዎስ የሆነ ፒሉፓዴር በሰማዕትነት አረፈ። መርቆሬዎስም ማለት የአብ ወዳጅ ማለት ነው በሁለተኛ ትርጓሜ የኢየሱስ ክርስቶስ አገልጋይ ማለት ነው።

ይህም ቅዱስ አስሊጥ ከምትባል አገር ነው እርሷም የአባቱና የአያቱ አገር ናት እርሱ ግን ተወልዶ ያደገው በሮሜ ከተማ ነው። የአባቱና የአያቱ ሥራቸው አውሬ ማደን ነበር በአንዲት ዕለትም እንደልማዳቸው ለማደን ወጡ ከገጸ ከለባት ወገንም ሁለት ወንዶች ተገናኙአቸውና የቅዱስ መርቆሬዎስን አያት በሉት። ሁለተኛም አባቱን ሊበሉት ፈለጉ ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልአክም ከለከላቸው፤ ከእርሱ የሚወጣ መልካም ፍሬ ስለአለ አትንኩት አላቸው።

ከዚህም በኋላ የእግዚአብሔር መልአክ ዙሪያቸውን በእሳት ከበባቸው። በተቸገሩ ጊዜም ወደ ቅዱስ መርቆሬዎስ አባት መጥተው ሰገዱለት። በዚያንም ጊዜ እግዚአብሔር ፍጥረታቸውን ወደገራምነት ለወጠውና እንደ በጎች የዋሆች ሆኑ። አብረውትም ወደ መንደር ገቡ።

ከዚህም በኋላ ቅዱስ መርቆሬዎስ በተወለደ ጊዜ ስሙን ፒሉፓዴር ብለው ጠሩት። የውሻ መልክ ያላቸውም በእነርሱ ዘንድ ብዙ ዘመናት የሚኖሩ ሆኑ ከዚህም በኋላ ክርስቲያኖች ሆኑ። የቅዱስ መርቆሬዎስ ወላጆች አስቀድሞ አረማውያን ነበሩና የክርስትና ጥምቀትንም ጸጋ በተቀበሉ ጊዜ የቅዱስ መርቆሬዎስን አባት ኖኅ ብለው ሰየሙት። እናቱንም ታቦት አሏት። ፒሉፓዴርንም መርቆሬዎስ ብለው ሰየሙት።

የውሻ መልክ ያላቸው ግን የእግዚአብሔር መልአክ በተገለጸላቸው ጊዜ እንደ ነገራቸው ለቅዱስ መርቆሬዎስ አባት የሚታዘዙና የሚያገለግሉ ሆኑ። ንጉሡም የኖኅንና የውሻ መልክ ያላቸውን ዜና በሰማ ጊዜ ወደርሱ አስቀረባቸው በዚያንም ጊዜ እግዚአብሔር በንጉሡ ፊት የቀድሞ ፍጥረታቸውን መልሶላቸው ንጉሡ ያቀረባቸውን ሁሉንም አራዊት አጠፏቸው።

ንጉሡም ይህን በአየ ጊዜ እጅግ ፈራ፤ የአራዊትንም ተፈጥሮአቸውን ያርቅ ዘንድ ወደ እግዚአብሔር እንዲማልድ የቅዱስ መርቆሬዎስን አባት ለመነው። እርሱም በለመነ ጊዜ ክብር ይግባውና ጌታችን ተፈጥሮአቸውን መልሶላቸው ገራሞች ሆኑ።

ከዚህም በኋላ የቅዱስ መርቆሬዎስን አባት ንጉሡ ወስዶ ገዥና የሠራዊት አለቃ አድርጎ ሾመው። የውሻ አርአያ ያላቸውም ይታዘዙለት ነበር። ከእርሳቸውም የተነሣ ሁሉም ይፈሩ ነበር።

ከዚህም በኋላ የቅዱስ መርቆሬዎስን አባት የሾመውን ንጉሥ ይወጋ ዘንድ ከሀዲ ንጉሥ ተነሣ። ንጉሡም ከጦር ሠራዊት ጋር የቅዱስ መርቆሬዎስን አባት ወደ ጦርነት ላከው። ከሀዲው ንጉሥ ግን እነዚያን የውሻ አርአያ ያላቸውን አባብለውና ሸንግለው ወደርሱ ያመጧቸው ዘንድ ወታደሮችን ላከ። በአመጧቸውም ጊዜ ሃይማኖታቸውን ይለውጡ ዘንድ አብዝቶ ሸነገላቸው፤ ባልሰሙትም ጊዜ ሊአሠቃያቸው ጀመረ አንዱ አምልጦ ሸሽቶ ወደ ጌታው ሔደ። ሁለተኛውም በሰማዕትነት ሞተ።

ከጦር ሜዳ የቅዱስ መርቆሬዎስ አባት በተመለሰ ጊዜ ሚስቱንና ልጁን ፈለጋቸው ግን አላገኛቸውም። ንጉሡ የሱ ወገኖች ድል እንደሆኑ በሰማ ጊዜ የቅዱስ መርቆሬዎስ አባት መኰንኑ የሞተ መስሎት ነበርና የቅዱስ መርቆሬዎስን እናት ወስዶ ሊአገባት ፈለገ። ከንጉሥ ወታደሮችም አንዱ ንጉሡ ያሰበውን በጽሙና ነገራት። እርሷም ይህንኑ ወታደር ከሀገር ውስጥ በሥውር ያወጣት ዘንድ ለመነችውና ከልጇ ከብፁዕ መርቆሬዎስ ጋር ወጥታ ወደ ሌላ አገር ሔደች።

ንጉሡም ከእርሱ የሆነውን የመኰንኑም የመርቆሬዎስን አባት ሚስቱን ለማግባት ማሰቡን እንዳይነግሩት አዘዘ። የውሻ መልኮች ያላቸው ከእርሱ ጋር እንዳሉ የተቆጣም እንደሆነ እንደሚአመጣቸውና አገሮችን ያጠፋሉ ብሎ ይጠራጠራልና ስለዚህ እጅግ ይፈራዋል።

ከዚህም በኋላ ደግሞ በንጉሡ ላይ ጦርነት ተነሣ። የቅዱስ መርቆሬዎስም አባት ወደ ጦርነቱ ወጣ በእግዚአብሔርም ፈቃድ ይዘው ማረኩት። ወደ ሮሜውም ንጉሥ አቀረቡት ንጉሡም ክርስቲያን ነበርና የተማረከው መኰንን ክርስቲያን መሆኑን በአወቀ ጊዜ አልገደለውም። በክብር አኖረው እንጂ እጅግም ወደደውና ከጥቂት ቀኖች በኋላ በመርዶሳውያን አገሮች ሁሉ ላይ ገዥ አድርጎ ሾመው።

ክብር ይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ፈቃድ ሚስቱና ልጁ መርቆሬዎስ ወዳሉበት አገር ደረሰ። ሚስቱም በቤተ ክርስቲያን ደጃፍ በአየችው ጊዜ ባሏ አንደሆነ አወቀችው። እርሱ ግን አላወቃትም።

በአንዲትም ዕለት እርሱና ጭፍሮቹ ከእንግዳ ማረፊያ ቤት በወጡ ጊዜ ልጅዋን መርቆሬዎስን ወስዳ ያማሩ ልብሶችን አልብሳ ሒዶ ከመኰንኑ ፈረስ ላይ እንዲቀመጥ አዘዘችው። እርሱም አባቱ ነው። በተቀመጠ ጊዜም ጭፍሮች ይዘው ወደ መኰንኑ ፊት አቀረቡት መኰንኑም ልጁ እንደሆነ አላወቀምና በእርሱ ላይ ተቆጣ።

የመርቆሬዎስም እናት መጥታ ጌታዬ ሆይ እኛ መጻተኞች ነን አንተም መጻተኛ እንደሆንክ በአወቅሁ ጊዜ ልጅህ ሁኖ ልጄ ከአንተ ጋር እንዲሆን አሰብኩ አለችው። እርሱም ጠየቃት እንዴት እንደተሰደደችም መረመራት እርሷም ሚስቱ እንደሆነች ነገረችው በዚያንም ጊዜ አወቃት ልጁን መርቆሬዎስንም አወቀው እጅግም ደስ ብሏቸው እግዚአብሔርን አመሰገኑት ያንንም የእንግዳ ማረፊያ ቤት ቤተ ክርስቲያን አደረጉት እግዚአብሔርንም እያመሰገኑ በአንድነት ኖሩ።

ከዚህም በኋላ አባቱና እናቱ በሞቱ ጊዜ ንጉሡ ቅዱስ መርቆሬዎስን ወስዶ በአባቱ ፈንታ በመርዶሳውያን አገር ላይ ሾመው። ቅዱስ መርቆሬዎስም መኰንንነትን በተሾመ ጊዜ ያ ገጸ ከልብ ከርሱ ጋር ነበር ወደ ጦርነትም አብሮት የሚወጣ ሆነ።

ለመዋጋትም በሚሻ ጊዜ የቀድሞ የአራዊት የሆነ ተፈጥሮውን እግዚአብሔር ይመልስለት ነበር ማንም ሊቋቋመው የሚችል የለም። ለቅዱስ መርቆሬዎስም ታላቅ የድል አድራጊነት ኃይል ተሰጠው ዜናውም በሁሉ ቦታ ተሰማ ከቤተ መንግሥት ሰዎችም ከፍ ከፍ አለ።

እንዲህም ሆነ ያን ጊዜ በዚያን ወራት በሮሜ አገር ጣዖትን የሚያመልክ ዳኬዎስ የሚባል ንጉሥ አለ። ጠላቶቹም የበርበር ሰዎች ተነሡበት። እርሱም ከእርሳቸው ጋር ሊዋጋ ሠራዊቱን ሰብስቦ ወጣ። እነርሱ ግን እንደ ባሕር አሸዋ ብዙ ነበሩ ብዛታቸውንም በአየ ጊዜ ደንግጦ እጅግ ፈራ። ቅዱስ መርቆሬዎስም እግዚአብሔር ያጠፋቸው ዘንድ በእጃችንም አሳልፎ ሊሰጣቸው አለውና አትፍራ አለው።

ከዚህም በኋላ ቅዱስ መርቆሬዎስ የእግዚአብሔርን መልአክ በውጊያው ውስጥ አየው የተሳለ ሰይፍም በእጁ ውስጥ አለ ያቺንም ሰይፍ ሰጠውና እንዲህ አለው ጠላቶችህን ድል በአደረግህ ጊዜ ፈጣሪህ እግዚአብሔርን አስበው።

ጠላቶቹንም ድል አድርጎ በሰላም ተመለሰ መልአኩም ዳግመኛ ተገልጦለት ለምን የፈጣሪህን የእግዚአብሔርን ስም መጥራት ረሳህ አለው።

ጦርነቱም ከተፈጸመ በኋላ ንጉሥ ዳኬዎስ ለጣዖታቱ ዕጣን በማሳረግ በዓልን ሊያደርግ ወደደ። ቅዱስ መርቆሬዎስም ለበዓል ማክበር አብሮት አልወጣም ወደ ቤቱ ሔደ እንጂ። ሰዎችም ቅዱስ መርቆሬዎስ እንዳልመጣና ዕጣንን በማሳረግም እንዳልተባበረ አስረዱት።

በዚያንም ጊዜ ንጉሥ መልእክተኞችን ልኮ ቅዱስ መርቆሬዎስን ወደርሱ አስመጣው። በመዘግየቱም አድንቆ ለአማልክት ዕጣን ለማሳረግ ከእኔ ጋር ያልመጣህ የእኔን ፍቅር እንዴት ተውህ አለው። በዚያንም ጊዜ ትጥቁንና ልብሱን ወረወረለትና ንጉሡን እንዲህ አለው። እኔ ክብር ይግባውና ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስን አልክደውም ለረከሱ ጣዖታትም አልሰግድም።

ንጉሥ ዳኬዎስም ይህን በሰማ ጊዜ እጅግ ተቆጣ። እርጥብ በሆኑ የሽመል በትሮች እንዲደበድቡት አዘዘ። ሁለተኛም ከላም ቆዳ በተሠራ ጅራፍ ይገርፉት ዘንድ አዘዘ ንጉሡ እንዳዘዘ ይህን ሁሉ አደረጉበት።

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

"እናታችን ጽዮን"
እናታችን ጽዮን ይድረስሽ ምስጋና፤
መጠጊያ ማረፊያ ጥላችን ነሽና።

ከገነት ብንወጣ ማረፊያ ሆንሽን፤
የምሕረት ደመና ውኃ ሰጠሽን፤
የሕይወት እንጀራ አመጣሽልን፤
በአስራትም በአደራም ለአንቺ ተሰጠን።
አዝ
የኤልሳቤጥ አጽናኝ የጭንቅ ቀን ደራሽ፤
የኃጢአታችን ብዛት ዳገት ሳይሆንብሽ፤
ምሥራችን ደስታን ይዘሽልን መጣሽ፤
ማርያም ስንልሽ ደረስሽልን ፈጥነሽ።
አዝ
ውለታሽ ብዙ ነው ከልብ የማይጠፋ፤
ስምሽ መጽናኛ ነው አዝኖ ለተከፋ፤
በእንተ ማርያም ብሎ ለለመነ፤
የሰማይ የምድርም ማንም አልጨከነ።
አዝ
በትራችን አንች ነሽ የምትደግፊን፤
ባሕረ እሳትን የምታሳልፊን፤
ጽርሐ ሥላሴ ነሽ ማኅደረ መለኮት፤
ሁልጊዜ አንጠግብሽም እንላለን ብጽእት።
አዝ

©በማኅበረ ቅዱሳን መዘምራን

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

ኅዳር ፳፩
ጽዮን ማርያም


ኅዳር ሃያ አንድ በዚች ቀን የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም የበዓሏ መታሰቢያ ነው።

“ታቦተ ጽዮን” የሚለውንም ስያሜ ያገኘችው ጽዮን ተብላ በምትጠራው የእስራኤል ከተማ ስም ነው፡፡ ጽዮን ማለት ተፀወነ፡ ተጠጋ፣ ተማጠነ ማለት ነው፡፡ ክቡረ ዳዊትም ጽዮንን አምባ፣ መጠጊያ አድርጎ ብዙ ጠላቶቹን ተዋግቶ አሸንፎ ድልን ተጎናጽፏል።

ጽዮን የተባለችው የታላቁ የዳዊት ከተማ የተገፉና የተበደሉ ሕዝቦች ሁሉ እውነተኛ ፍርድ ለማግኘት፣ ተሰብስበው የሚሰነብቱባት ከተማ ስለነበረች፣ ጽላተ ሙሴም በዚያ ስለነበረች በርሷ ተማጽነውም ችግራቸው ሰለሚቃለል ታቦቷ “ታቦተ ጽዮን” ተብላለች፡፡

ታቦተ ጽዮን ብዙ ጊዜ "ጽላተ ኪዳን፣ ታቦተ ሕጉ" እየተባለች ትጠራለች። "ጽሌ" ማለት "ሰሌዳ" እንደ ማለት ሲሆን "ጽላት" ደግሞ በብዙ ቁጥር ነው። "ኪዳን" ደግሞ በፈጣሪና በሰው ልጆች መካከል ያለ "ውል - ስምምነት" ነው።

"ታቦት" ማለት "ማሕደር-ማደሪያ" እንደ ማለት ነው። ሕጉ የተጻፈባቸውን ሰላድው "ጽላት" ስንላቸው የጽላቱ ማደሪያ ደግሞ "ታቦት" ይባላል። ጽላት (ታቦትን) ያመጣ ፈጣሪ ነው። በሐዲስ ኪዳንም ምሥጢርና ሐተታ ቢኖረውም 2 ቦታ ላይ ስለ ታቦት ተጠቅሶ እናገኛለን። (2ቆሮ.6፥16 ፣ ራዕይ.11፥19)

የአምላክ ማደሪያ ቅድስት ድንግል ማርያም በቃል ኪዳን ታቦት ትመሰላለች ይኽቺም ፦
✿ የእግዚአብሔር የጌትነቱ መግለጫ የኾነችው፤
✿ በፍልስጥኤም ይመለክ የነበረ ጣዖትን ቀጥቅጣ ያጠፋች፤
✿ በድፍረት ሊነካት የሞከረ ኦዛን የቀሰፈች፤
✿ በታላቅ ክብር ወደ ሀገሯ ስትመለስ ነቢየ እግዚአብሔር ዳዊት በታላቅ መንፈሳዊ ደስታ በፊቷ የዘመረላት ፤
✿ ልጁ ሰሎሞንም ታላቅ ቤተ መቅደስ ሠርቶ በክብር ያኖራት ናት፡፡

ጌታ የታቦቷን አሠራር ሲነግረው "ሽምሽር ስጢን ከሚባል ከማይነቅዝ እንጨት ቀርጸኽ አብጅ ከታች እንደ ዙፋን አራት እግር አውጣለት ሞላልነቱን ኹለት ክንድ ከስንዝር ቁመቱ ክንድ ከስንዝር ወርዱን ክንድ ከስንዝር ኹለት ክንድ ከስንዝር ምስሃል ለዚኽ ቁመት የለውም አራት ቀለበት ኹለት ሙሎጊያ አበጅለት አፍአውን ውስጡን በንጹሕ ወርቅ ለብጠው በምስማኩና በምስማኩ ኹለቱን ኪሩቤል እንደሚናተፉ አውራ ዶሮዎች አንገታቸውን ደፋ አድርገኽ በላይ ሣልበት ዙሪያውን ፈለግ አውጣለት ብጽብጽ ወርቅ አፍስበት ጽላቶቹን በውስጡ አኑር" ብሎታል፡፡
ይኸውም ምሳሌ
✅ታቦት ፡- የእመቤታችን
✅ወርቅ፡- የንጽሕናዋ የቅድስናዋ
✅ታቹ መቀመጫው ፡- የንጽሓት እንስት
✅ላዩ መግጠሚያው ፡- የንጹሓን አበው
✅ግራ ቀኙ ፡- የሐና የኢያቄም
✅ወደ ውስጥ የገባችው:-የድንግል ማርያም ያቺ በመኻከላቸወም እንደኾነች እመቤታችንም ከሐና ከኤያቂም ለመገኘቷ ምሳሌ ነው።
✅ኹለት ክንድ ከስንዝር:- ከአዳም እስከ ኖኅ ባለው ዘመን 2260 ዘመን ይመስላል ይኸውም በኖኅ ዘመን አርአያ ድንግል ታቦተ ኖኅ ለመገኘቷ ምሳሌ፡፡
✅አንድ ክንድ ከስንዝር ቁመቱ :- ከኖኅ እስከ  ሙሴ ባለው ዘመን ይመስላል ይኸውም 1600 ዘመን ነው። በዚህ ዘመን አርአያ  ድንግል ጽላተ ሙሴ  ለመገኘቷ ምሳሌ ነው፡፡
✅አንድ ክንድ ከስንዝር ወርዱ:- ከሙሴ እስከ  እመቤታችን ባለው ዘመን ይመስላል ይኽውም 1640 ዘመን ይኾናል ይኽ በኾነ አርአያ ድንግል ታቦተ ኖኅ አርአያ ድንግል ጽላተ ሙሴ ምሳሌዎቿ የሚሆኑ አማናዊት ድንግል ማርያም ለመገኘቷ ምሳሌ ነው፡፡
✅አራቱ ቀለበት:- የአራት ወገን ንጽሕናዋ  ምሳሌ ይኸውም ከርእይ /ኃጢአትን ከማየት/፤ ከሰሚዕ/ኃጢአትን ከመስማት/ ፤ ከገሲስ/በእጅ ዳሰሶ ኃጢአትን ከመሥራት እና ከአጼንዎ /የኃጢአት መዐዛን ከማሽተት/ እመቤታችን ከነዚኽ ኹሉ ተጠብቃለችና
✅ኹለቱ ቀለበት:- የፍቅረ እግዚአብሔርና  የፍቅረ ቢጽ ምሳሌ
✅ኹለቱ ሥዕለ ኪሩቤል:- የጠባቂ መልአክ  የቅዱስ ሚካኤልና የአብሳሪ መልአክ የቅዱስ ገብርኤል ምሳሌ ናቸው ይኽውም የብሉይ ሊቀ ካህናት በዓመት አንድ ቀን ገብቶ ከኹለቱ ኪሩቤል መካከል ቃል ሰምቶ ይወጣ ነበር ቅድስት ድንግል ማርያም በሊቀ መላእክት በቅዱስ ሚካኤል ተጠብቃ ከቅዱስ ገብርኤል ቃል ሰምታ አካላዊ ቃልን በግብረ መንፈስ ቅዱስ ያለ ዘር ያለ ሩካቤ ፀንሳ ተገኝታለችና።

ሊቁ ቅዱስ ያዕቆብ ዘስሩግ ይኽንን መንፈሳዊ ምስጢር በጥልቅት በመመርመር ድንግል ማርያምን ፡-
👉በምስጢር የተመላች ታቦት
👉 እሳትን የተመላች ታቦት
👉የቅዱስ ቃል ታቦት
👉የቃል ኪዳን ታቦት በማለት ገልጿታል፡፡

ኅዳር 21 ቀን የሚከበረውም የእመቤታችን ምሳሌዎች የተገለጡበት እና የተለያዩ ሥራዎች የተሰሩበት ዕለት ስለሆነ ነው፡፡ እነዚህም፡-

1. ነቢዩ ዘካርያስ ሁለንተናው ወርቅ የሆነ፣ የዘይት ማሰሮ በራሱ ላይ የነበረበትንና ሰባት መብራቶች ያሉትን መቅረዝ ሲያበራ ያየበት ዕለት ነው፡፡ ዘካ. 4፤1-2። ዘካርያስ ያየው ብርሃን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ምሳሌ ነው፡፡ ዮሐ. 8፤12፡፡ ይህ ብርሃን የታየባትና የተገለጠባት መቅረዝ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ምሳሌ ናት፡፡ ብርሃን መቅረዝ እንዲያዝና እንዲገለጥ መድኃኔዓለም ክርስቶስ ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ተወልዶ ተገልጦልናል፡፡ ጨለማ ዓለምን አብርቷል፡፡ ብርሃን ክርስቶስን ወልዳለችና እርሷም እመ ብርሃን / የብርሃን እናት/ ትባላለች፡፡

2. ታቦተ ጽዮን ዳጎንን ገልብጣ በመጣል ኃይሏን የገለጠችበት ዕለት ነው፡፡ በፍልስጥኤማውያን ተማርካ ቤተ ጣዖት ወስደው ከጣዖታቸው ከዳጎን በታች አስቀምጠዋት ነበር፡፡ ታቦተ ጽዮን ግን በላይዋ ያለውን ዳጎንን ገልብጣ ጥላ እርሷ ከላይ ተቀመጠች፡፡ በታቦት የሚገለጠው የእግዚአብሔር ኃይል ነው፡፡ ምክንያቱም በታቦቱ ላይ ያለው ሕገ እግዚአብሔርና ስመ እግዚአብሔር ነው፡፡ የእግዚአብሔር ስም የጸና ክንድ ነውና ሁሉን ያሸንፋል። ስለዚህ ምንም እንኳ ለጊዜው ስትማረክ ደካማ ብትመስልም መማረኳ ግን ኃይሏን ለመግለጥ፣ ለአሕዛብ የጣዖትን ከንቱነት የታቦትን ክቡርነት ለመግለጥ ነበር፡፡

3. ቀዳማዊ ምኒልክ ታቦቱን ይዞ አክሱም የገባበት፣ ንግሥት ሳባ ታላቅ በዓል አድርጋ የተቀበለችበት፣

4. አብረሃ ወአጽብሐ በአክሱም ከተማ 12 ቤተ መቅደስ ያለው ቤተ ክርስቲያን በአስደናቂ ሁኔታ ሠርተው ከጨረሱ በኋላ ቅዳሴ ቤቱን ያከበሩበት፣ እንዲሁም

5. በ9ኛው መ/ክ/ዘመን ዮዲት ክርስትና ለማጥፋት በተነሳች ጊዜ በእርሷ ምክንያት ታቦተ ጽዮን ወደ ዝዋይ ሐይቅ የተሰደደችበት፡፡ በኋላም የሰላሙ ዘመን ሲመጣ ተመልሳ አክሱም የገባችበት በዚሁ በኅዳር 21 ስለሆነ በእነዚህ በተደራራቢ ታሪኮች ምክንያት በየዓመቱ በደመቀ ሁኔታ ይከበራል “ኅዳር ጽዮን በአክሱም ጽዮን” የሚባለውም ለዚህ ነው፡፡

የእመቤታችን ልመናዋ ክብሯ አማላጅነቷም ከእኛ ከህዝበ ክርስቲያን ጋር ለዘለዓለም ጸንቶ ይኑር! አሜን!

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

ፈቃዴ ነው


ፈቃዴ ነው የሰውን ነገር ላልናገር/፪/
የእኔ ተሸፍኖ ከቆሙኩኝ በክብር
ፈቃዴ ነው የሰውን ነገር ላልናገር
አዝ.....

ሕይወቴ በሙሉ በኃጢአት ተሞልታ
አምላኬ ከማረኝ በፍቅሩ ዝምታ
የሰው በደል ላላይ በእውነት ምያለሁ
እኔን ከታገሠኝ ፍቅር ተምሬያለሁ/፪/
አዝ.....

በዐይኔ ፊት ተጋርዶ ያለውን ምሶሶ
እያየ ካለፈኝ በምሕረት ታግሦ
የሰው በደል ላላይ በእውነት ምያለሁ
እኔን ከታገሠኝ ፍቅር ተምሬያለሁ /፪/
አዝ.....

አንተ ቀራጩ ሰው ያለህ አቀርቅረህ
በምሕረት ተመለስክ ከእኔ ይልቅ ድነህ
በአንተ ላይ ስጠቁም የእኔን ጸሎት ትቼ የመዳኑ ሰዐት አለፉ ቀኖቼ/፪/
አዝ.....

ተቆጥሮ የማያልቅ ኃጢአቴ ተጠርቶ
በሞትና በደል በኃጢአት ሸፍኖ
ሰው አርጎ አቁሞኝ በሰው ፊት ጌታዬ
በማንም አልፈርድም ኃጢአተኛ ብዬ
በማንም አልፈርድም በደለኛ ብዬ
አዝ.....


ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ


@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…
Subscribe to a channel