ethiopian_orthodox | Unsorted

Telegram-канал ethiopian_orthodox - የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

30344

በዚህ Channel ውስጥ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንን ዶግማ ፤ ቀኖና እና ትውፊት የጠበቁ ትምህርቶች ይተላለፉበታል፡፡ ለአስተያየት: ጥቆማና ጥያቄ በዚህ ያግኙን ☞ @Ethiopian_Orthodox_bot Buy ads: https://telega.io/c/Ethiopian_Orthodox

Subscribe to a channel

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

"ቅዱስ ላሊበላ"

በገርጂ ጊዮርጊስ የፍሬ ሃይማኖት ሰ/ት/ቤት መዘምራን

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

የምትፈልግ አይደለህም፤ ለጠፈራቸው መማገሪያ ገመድ የምትሻ አይደለህም፣ እንጨትንም ለማገር፣ ለምሰሶዋቸውም ገበታ፣ ለዙሪያቸውም ለማያያዣ ጭቃን የምትፈልግ አይደለህም፡፡ የቤተመቅደሶችን ፈቃድ ሁሉ ከአንድ ቋጥኝ ድንጋይ ትፈጽማለህና፡፡ የማሳይህ እኚህ የቤተ መቅደሶች አኗኗር ከምድር ልብ ውስጥ እስከዛሬ አለ፡፡ ከአሁን ጀምሮ በእጅህ እስኪገለጡም ድረስ በምድር ልብ ይኖራሉ፡፡ በሰው ልጅ ጥበብ ያይደለ በእኔ ሥልጣን ከምድር ልብ ውስጥ ታወጣቸው ዘንድ መረጥሁህ፡፡ ሕዝቦቼ ተወልጄ አድጌ ሞቼ ተቀብሬ ከሞትም የተነሳሁባትን ሀገር ለማየት ኢየሩሳሌም በመሄድ ግማሹም በበረሃ ይቀር ነበር አሁን ግን አንተ ኢየሩሳሌምን በሀገርህ ትሠራለህ፡፡ በማንም እጅ ዳግመኛ ሊሠሩ የማይችሉ ቤተ መቅደሶቼን እንዳሳየሁህ ትሠራለህ፡፡ አንተም እንዳሳየሁህ በልብህ ውስጥ አኑራቸው፡፡ ስትሠራቸውም እየልካቸው ይሁን፤ ከእርዝመታቸውም በላይ ቢሆን፣ ከወርዳቸውም በላይ ቢሆን፣ በመወጣጫቸውም ላይ ቢሆን አንዳች እንዳትጨምር፡፡ ያሳየሁህ እሊህ ዐሥሩ መቅደሶች ከአንዲት ቋጥኝ ድንጋይ ሲወጡ አይተሃልና….› እያለ ጌታችን ሲነግረው ጻዲቁ ንጉሥ “ይህ እንዴት ይሆናል?” በማለት ይጠይቃል፡፡ ጌታም እውነት እልሃለሁ እነዚህ ያሳየሁህ መቅደሶች በሰው ኃይል የሚሠሩ ሆነው አይደለም፤ ጀማሪያቸው ሠሪያቸውና ፈጻሚያቸው እኔ ነኝ ነገር ግን ኃይሌ በአንተ እጅ እንዲገለጽ ለምክንያት ተልከሃል፤ አንተ አነጽካቸው እየተባለ እስከ ዕለተ ምፅዓት ድረስ ስምህ ይጠራባቸዋል…›› እያለ ይቀጥላል የቅዱስ ላሊበላ ገድል፡፡ ቤተ መቅደሶቹንም ለመሥራት ቦታውን ያውቅ ዘንድ ሱባኤ ገብቶ ሳለ ዛሬ ቤተ ማርያም ካለችበት ቦታ ላይ ቅዱሳን መላእክት ሲወጡና ሲወርዱ ታይተውት በቦታው ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ መቅደሱን መሥራት ጀመረ፡፡ ዓሥሩን ቤተ መቅደሶች ሲሠራ እርሱ አንድ ክንድ ሠርቶ እንደሆነ ሌሊቱን አድሮ በቀጣዩ ቀን አሥር ክንድ ሆኖ ያገኘው ነበር፣ ቀንም በማይታወቁ ሰዎች አምሳል እየተገለጡ መላእክት ይራዱት ነበር፡፡

5. አንዳንድ ነገሮች ስለ ቅዱስ ላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት፡- ቅዱስ ላሊበላ ዓሥሩም ውቅር አብያተ ክርስቲያናት በጣም በሚያስገርም ሁኔታ በውስጥና በውጭ ያሉት ብዙ ቅርጾች ነገረ ድኅነትን በምሳሌ እንዲወክሉ አድርጎ ነው ያነጻቸው፡፡ የክርስቶስን መከራና በእርሱም የተገኘውን ፍጹም ዘላለማዊ ድኅነት በእያንዳንዱ ቤተ መቅደስ ውስጥ እንዴት አድርጎ በምሳሌ እንዳስቀመጠው እጅግ አስገራሚ ነው፡፡
በላስታ ቅዱስ ላሊበላና አካባቢው የሚገኙ ሌሎች አስደናቂ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት፡- ከአሥሩ የቅዱስ ላሊበላ አስደናቂ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት በተጨማሪ የቅዱስ ነአኵቶለአብና የቅዱስ ይምርሃነ ክርስቶስ አብያተ ክርስቲያናት እንዲሁም አሸተን ማርያም በዋናነት ሕዝበ ክርስቲያኑ የሚጐበኛቸው ውቅር አብያተ ክርስቲያናት ናቸው፡፡ በላሊበላና አካባቢው ግን እጅግ ጥንታዊና አስደናቂ የሆኑ በጣም በርካታ አብያተ ክርስቲያናት ይገኛሉ፡፡ ለምሳሌ ያህል ሣርዝና ሚካኤል፣ ብልባላ ቂርቆስ፣ ብልባላ ጊዮርጊስ፣ አርባዕቱ እንስሳ፣ ትርኩዛ ኪዳነምሕረት፣ ገነተ ማርያም፣ ቀንቀኒት ሚካኤል እነዚህ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት ሲሆኑ እንዲሁም ዋልድቢት ቅድስት ማርያም አንድነት ገዳም፣ አቡነ ዮሴፍ ገዳም፣ ገብረ ክርስቶስ ዋሻ ቤተክርስቲያን፣ ቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን፣ ቀደሊት ገብረ መንፈስ ቅዱስ፣ እመኪና መድኃኔዓለምና እመኪና ልደታ፣ ማውሬ እስጢፋኖስ፣ የቅዱስ ገብረ ማርያም ቤተክርስቲያን፣ ማይ ማርያም ቤተክርስቲያን፣ ተከዜ ኪዳነምሕረትና መድኃኔዓለም አንድነት ገዳም ከብዙ በጥቂቱ ይጠቀሳሉ፡፡ ከእነዚህም ውስጥ አንዳንዶቹ ከ485-536 ዓ.ም ባለው ጊዜ ውስጥ በዐፄ ካሌብ ዘመነ መንግሥት የታነጹ ናቸው፡፡ ሌሎቹንና በሰሜን ላስታ ያሉትን ደግሞ እነ ላሊበላና ይምርሃነ ክርስቶስ አንጸዋቸዋል፡፡

ቅዱስ ላሊበላ እኛ ከምናውቃቸው ከድንቅ ሥነ ሕንፃዎቹ ሥራ በተጨማሪ ከሺህ ዓመታት በፊት በሥዕል፣ በሥነ ጽሑፍ፣ በሃይማኖት፣ በኢኮኖሚ፣ በውጭ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙትና በመሳሰሉት ሁሉ እጅግ ከፍተኛ አስተዋፅኦ አድርጓል፡፡ ቅዱስ ላሊበላ ከሺህ ዓመታት በፊት አዳራሾችን፣ ፎቆችን፣ የውስጥ ለውስጥ መተላለፊያዎችን፣ የእንግዳ መቀበያዎችን፣ የሕፃናት ማሳደጊያዎችን፣ የሕሙማን መፈወሻዎችን፣ የሕንፃ መሳሪያዎችን፣ የትምህርት ማዕከሎችን፣ የመደጎሻ ቦታዎችን ያቋቋመ መሆኑን የብራና ገድሉ እንደሚናገር የደብሩ አባቶች ይገልጣሉ፡፡ ወደፊት ተርጎመው እንሚያቀርቡልን ተስፋ እናደርጋለን፡፡ ቅዱስ ላሊበላ ከዚህ በተጨማሪ የግእዝ ቋንቋን በጽሑፍ አበልፅጎ ያቆየ ባለውለታ ነው፡፡ ከላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት ውጭ ሌሎችንም በርካታ ቤተ መቅደሶች ሠርቷል፤ ከሀገራቸንም አልፎ በሱማሌ ሞቃዲሾ ላይ መቅደሰ ማርያም የተባለች ቤተክርስቲያን ሠርቷል፡፡ ክርስትናን ከግብፅ ምድር ጨርሰው ለማጥፋት ተንባላት በተነሡ ጊዜ ዓባይን ሊያግድባቸው ሲነሣ በብዙ ምልጃና ልመና ስለማራቸው በሀገሪቱ ውስጥ ክርስትና እስካሁን እንዲቆይ የራሱን ከፍተኛ አስተዋፅኦ አድርጓል፡፡ በአጠቃላይ ቅዱስ ላሊበላ ነቢይም ሆኖ፣ ሐዋርያም፣ ጻዲቅም፣ ሰማዕትም ሆኖ ጥበብ መንፈሳዊንና ጥበብ ሥጋዊን ከእግዚአብሔር ተሰጥቶት ንግሥናንና ክህነትን፣ ቅድስናንና ንጽሕናን በሚገባ አስተባብሮ በማያዝ እግዚአብሔርንም ሰውንም በቅንነት ሲያገለግል ኖሮ ሰኔ 12 ቀን 1197 ዓ.ም ከፈጣሪው ታላቅ ቃልኪዳን ተቀብሎ በዝማሬ መላእክት፣ በመዝሙረ ዳዊት ቅድስት ነፍሱ ከሥጋው ተለይታ ሰማያዊ ክብርን ወርሷል፡፡ ክቡር ሥጋውም ራሱ ባነጸው ቤተ ሚካኤል መቅደስ ሥር በክብር ዐርፏል፡፡

(ምንጭ፡- ገድለ ቅዱስ ላሊበላ፡- የቅዱስ ላሊበላ ደብር በ2003 ዓ.ም ያሳተመው፣ ስንክሳር ዘወርሃ ሰኔ)
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

ሰኔ ፲፪
ቅዱስ ላሊበላ
ቅዱስ ገብርኤል ወደ ሰማይ ነጥቆ ወስዶ ሰባቱ ሰማያትን ካሳየውና በጌታችን ፊት አቅርቦት ካስባረከው በኋላ ጌታችንም በቅዱስ ቃሉ ‹‹ሕዝቦቼ የመከራና የሥቃዬን ቦታ ለማየት ኢየሩሳሌም በመሄድ በመንገድ እየቀሩ ስለሆነ አሁን ግን አንተ በሀገረ ሮሀ ኢየሩሳሌምን ትሠራለህ›› በማለት የቤተ መቅደሶቹን አሠራር በዝርዝር የነገረው ጻድቁ ንጉሥ ቅዱስ ላሊበላ ዕረፍቱ ነው፡፡

ቅዱስ ላሊበላ ጌታችን የጠጣውን መራራ ሐሞት በማሰብ ሁልጊዜ ዓርብ ዓርብ ኮሶ ይጠጣ ነበር፡፡ ቅዱስ ገብርኤል ላሊበላን ኢየሩሳሌም ወስዶት በዚያ ያሉ ቅዱሳን መካናትን ሁሉ አሳይቶ አሳልሞታል፡፡ ወደ ሰማይም ነጥቆ ወስዶ ሰባቱ ሰማያትን ያሳየው ሲሆን በጌታችን ፊትም አቅርቦት አስባርኮታል፡፡ ጌታችንም ‹‹ሕዝቦቼ የመከራና የሥቃዬን ቦታ ለማየት ኢየሩሳሌም በመሔድ በመንገድ እየቀሩ ስለሆነ አሁን ግን አንተ በሀገረ ሮሀ ኢየሩሳሌምን ትሠራለህ›› በማለት የቤተ መቅደሶቹን አሠራር በዝርዝር ነግሮታል፡፡ ከነገሠም በኋላ ሱባኤ ገብቶ ቤተመቅደስ የሚሠራበትን ቦታ በጸሎት ሲጠይቅ ዛሬ ቤተ ማርያም ካለችበት ቦታ ላይ የብርሃን አምደ ወርቅ ተተክሎ መላእክት ሲወጡና ሲወርዱ ስላየ ቦታው እግዚአብሔር የፈቀደው መሆኑን አውቆ ሥራውን ጀመረ፡፡ ጌታችን ቀድሞ ‹‹እኔ ራሴ ነኝ እንጂ ቤተ መቅደሶቹን የምትሠራቸው አንተ አይደለህም፣ ነገር ግን በአንተ ስም እንዲጠራ ስለፈቀድኩ ሄደህ ሥራ›› ብሎ እንዳዘዘው ቅዱስ ገድሉ ይናገራል፡፡ ላሊበላ ዓሥሩን ቤተመቅደሶች ሲሠራ እርሱ አንድ ስንዝር ሠርቶ እንደሆነ ሌሊቱን ዓሥር ስንዝር ሆኖ ያገኘው ነበር፡፡ ቀንም ሲሠራ ቅዱሳን መላእክት በማይታወቁ ሰዎች አምሳል ሆነው ይራዱት ነበር፡፡ በመጨረሻም ጌታችን በገሃድ ተገልጦለት በቦታው ላይ እጅግ አስገራሚ ቃልኪዳኖችን ሰጥቶታል፡፡

ከ10ኛው እስከ 13ኛው መቶ ክፍለ ዘመን (920-1253 ዓ.ም ድረስ) በላስታ ቡግና ምድር የነገሡ የላስታ ቡግና ተወላጅ የሆኑ የኢትዮጵያ ቅዱሳን ነገሥታት የንግሥናቸው መጠሪያ ‹‹የዛጉዌ ሥርወ መንግሥት›› ወይም ‹‹የላስታ መንግሥት›› በመባል ይታወቃል፡፡

የላስታ ነገሥታት የዘር ሀረጋቸው ከንጉሥ ሰሎሞን ዘር ሲያያዝ የመጣ ነው፡፡ ከላስታ (ከዛጉዌ) ነገሥታት መካከል ቅዱስ ይምርሃነ ክርስቶስ፣ ቅዱስ ገብረ ማርያም፣ ቅዱስ ላሊበላና ቅዱስ ነአኵቶለአብ እነዚህ አራቱ ነገሥታት እንደ መልከጼዴቅ (ዘፍ 14፡18) ክህነትን ከንግሥና፣ ቅድስናን ከንጽሕና ጋር አንድ አድርገው በመያዝ እግዚአብሔርንም ሰውንም በቅድስና አገልግለው አልፈዋል፡፡ በንግሥናቸው ሀገራችንን በመልካም ሥራና በቅድስና ከማስተዳደራቸው በተጨማሪ ቅዱሳን ጻድቃን ሆነው እግዚአብሔርን በብዙ ድካም በመልካም ተጋድሎአቸው ያገለገሉና አገልግሎታቸውም ሆነ ቅድስናቸው በእግዚአብሔር ዘንድ ስለተመሰከረላቸው ጌታችን የሰጣቸውን ቃልኪዳን መሠረት በማድረግ ቅድስት ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያናችን የቅድስና ማዕረግ ሰጥታ፣ በስማቸው ቤተክርስቲያን አንጻ፣ ጽላት ቀርፃ በዓላቸውን እያከበረች መታሰቢያቸው ተጠብቆ ለዘለዓለም እንዲኖር አድርጋለች፡፡
እኛ ኢትዮጵያውያን የቅዱስ ላሊበላን እጅግ ድንቅ የሆኑ ሥራዎቹን ዓለም ከሚመለከትበት የተለየ መንፈሳዊ ዐይን ሊኖረን ይገባል፡፡ ስለዚህም የቅዱስ ላሊበላን የቅድስና ሕይወትና ከእግዚአብሔር ጋር ስለነበረው ግንኙነት ገድለ ቅዱስ ላሊበላን መነሻ በማድረግ ብዙ ነገሮችን ቀጥሎ እናያለን፡-
1. ቅዱስ ላሊበላ ከአባቱ ዣን ስዩምና ከእናቱ ኪርወርና ጌታችን በተወለደበት ዕለት ታኅሣሥ 29 ቀን 1101 ዓ.ም በላስታ ቡግና ወረዳ ልዩ ስሟ ሮሀ በተባለችው ሥፍራ ተወለደ፡፡ የልደቱን ነገር አስቀድሞ ቅዱስ ሚካኤል ለእናቱ ነግሯት ነበርና በተወለደ ጊዜ ብዙ ነጫጭ ንቦች መጥተው በሰውነቱ ላይ አርፈው እንደ ማር እየላሱት ስለታዩ እናቱ ‹‹ልጄን ንብ ዘበኛ ሆኖ ይጠብቅልኛል›› ስትል ስሙን ‹‹ላል ይበላል›› ብላዋለች፡፡ ላል በአገውኛ ንብ ማለት ነው፡፡ በጊዜ ብዛት በተለምዶ ነው ‹‹ላሊበላ›› ተብሎ መጠራት የተጀመረው፡፡ ንቦቹ ግን ሥጋዊ ንቦች ሳይሆኑ በንብ የተመሰሉ መላእክት ናቸው፡፡ ንጉሥ መሆኑን እያመለከቱ የሃይማኖትና የምግባር ማር ከእርሱ ይቀዳል ሲሉ በንብ ሠራዊት ተመስለው ሰውነቱን ላሱት፡፡ እንደ ዮሐንስና እንደ ኤርምያስም በእናቱ ማኅፀን ሳለ ነው መንፈስ ቅዱስ የሞላበት፡፡

ከዚህ ቀጥሎ በገድሉ ውስጥ የተጠቀሱ አንዳንድ አስደናቂ ነገሮችን እናያለን፡፡
2. ቅዱስ ላሊበላ ያነጻቸውን አብያተ ክርስቲያናት መመልከት ያለብን በቅርስነታቸውና በቱሪስት መስህብነታቸው ሳይሆን በመንፈስ ቅዱስ የተገኙ ብቸኛ መንፈሳዊ ሀብቶቻችን መሆናቸውን ነው፡- ስለ ቅዱስ ላሊበላ አብያተ ክርስቲያናት ከማንሳታችን በፊት በመጀመሪያ እውነተኛ የሕይወት ቃል የሆነውን መጽሐፍ ቅዱስን መመልከት የግድ ያስፈልጋል፡፡ ቅድስት ሀገራችን ኢትዮጵያ ቀድሞ በሕገ ልቡና ከዚያም በሕገ ኦሪት እግዚአብሔርን ስታመልክ ኖራለች፡፡ በሐዲስ ኪዳንም ሐዋርያቱ እንኳን ለስብከት ከኢየሩሳሌም ሳይወጡ ነው በ34 ዓ.ም በራሷ ሐዋርያ በጃንደረባው ባኮስ አማካኝነት በክርስቶስ ማመንንና ጥምቀትን ወደ ሀገሯ ያመጣችው፡፡ የዚህ ደግሞ ምስክሩ መጽሐፍ ቅዱስ ነው፡፡ 1ኛ ነገ 10፡1-13፣ ሐዋ 8፡26-40፡፡ በዚህ መረጃ መሠረት ኢትዮጵያውያን ከጥንት ጀምሮ እስከ ሰባተኛው መቶ ክፍለ ዘመን ድረስ ወደ ኢየሩሳሌም እየሔዱ ሃይማኖታዊ ጉዞ ያድርጉ ነበር፡፡

ከ7ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በኋላ ግን ከኢትዮጵያ ተነስቶ በሱዳን በግብፅ አድርጎ ወደ ኢየሩሳሌም በእግርና በእንስሳት ጉዞ ለማድረግ የመንገዱ አድካሚነትና በረሃማነት የሚባክነው ጊዜ እንዲሁም በኢየሩሳሌም ዙሪያ ተሻግሮም እስከ ግብፅና ሱዳን ድረስ የእስልምና ሃይማኖት ስለተጠናከረ ለኢትዮጵያውያን ክርስቲያኖች ወደ ኢየሩሳሌም ለመጓዝ አስቸጋሪ ስለሆነባቸው ለሃይማኖታዊ አምልኮና ስግደት ወደ ኢየሩሳሌም የሚያደርጉት ጉዞ ተቋረጠ፡፡ ይህ ሁኔታም ሲያያዝ እስከ ቅዱስ ላሊበላ ዘመን ደርሷል፡፡

ቅዱስ ላሊበላም የኢትዮጵያ ክርስቲያኖች ወደ ኢየሩሳሌም ያደርጉት የነበረው ጉዞ በመቋረጡ በእጅጉ እያዘነ ተግቶ ወደ እግዚአብሔር ይጸልይ ነበር፡፡ የኢየሩሳሌምንም አምሳያ የሆኑ አብያተ ክርስቲያናትን በሀገሩ ለመሥራት ይመኝ ነበር፡፡ ጥቂት ነገር ሲለምኑት አብዝቶ መስጠት ለእግዚአብሔር የባሕርይ ገንዘቡ ነውና ላሊበላ ምድራዊ ኢየሩሳሌምን በሀገሩ ለመሥራት ሲያስብ ልዑል እግዚአብሔር በጥበቡ እንደ ቅዱስ ጳውሎስ (2ኛ ቆሮ 12፡1-7) ወደ ሰማይ አሳርጎት ሰማያዊት ኢየሩሳሌምን አሳይቶታል፡፡ ጌታችንም ‹‹ሕዝቦቼ የመከራና የስቃዬን ቦታ ለማየት ኢየሩሳሌም በመሄድ በመንገድ እየቀሩ ስለሆነ አሁን ግን አንተ በሀገረ ሮሐ ኢየሩሳሌምን ትሠራለህ›› በማለት የቤተ መቅደሶቹን አሠራር ሁሉ በዝርዝር ነግሮታል፡፡ በሰማያዊት ኢየሩሳሌምም ምሳሌ በሀገሩ ላይ ወጥ ከሆኑ የዓለት ድንጋዮች መላእክት እየተራዱት ውቅር አብያተ ክርስቲያናትን እንዲያንጽ ነግሮታል፡፡
3. ጠላት ለክፉ ያሰበውን እግዚአብሔር ለበጎ ያደርገዋል፡- ወደኋላ ተመልሰን የቅዱስ ላሊበላን የልጅነት ሕይወቱን እናንሳ፡- ቅዱስ ላሊበላ እናትና አባቱ ከሞቱበት በኋላ ወደ ጎጃም በመሄድ ሥርዓተ ቤተክርስቲያንን፣ ብሉይና ሐዲስን በደንብ ተምሮ ከጨረሰ በኋላ ወደ ደብረ ሮሐ ተመልሶ መጥቶ ነግሦ ከነበረው ከወንድሙ ከገብረ ማርያም ዘንድ ተቀመጠ፡፡ ‹‹ከገብረ ማርያም ቀጥሎ የሚነግሠው ላሊበላ ነው›› ተብሎ ትንቢት ስለተነገ

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

ፈ በኋላ በግ ጠባቂው ያን ብላቴና ባሕራን ብሎ ሲጠራው በሰማ ጊዜ "ልጅህ ነውን?" ብሎ ጠየቀው። በግ ጠባቂውም "አዎን ይህ አሁን ጐልማሳ ሆኖ የምታየው ወጣት ገና ሕፃን ሆኖ ሳለ በሣጥን ተከቶ ከባሕር ውስጥ ተጥሎ አግኝቼው ወስጄ አሳድጌዋለሁና ልጄ ነው" አለው። ባለጸጋውም በባሕር ውስጥ የጣለው ሕፃን መሆኑንም ስላወቀ ይህንን ነገር በሰማ ጊዜ ፈጽሞ ደነገጠ፤ ይገድለውም ዘንድ ፈለገ፡፡

በበነጋውም መንገዱን ለመሄድ ሲዘጋጅ ልዩ ልዩ ምክንያት (ሰይጣናዊ ሃሳብ) በመፍጠር በግ ጠባቂውን "ወንድሜ ሆይ አንድ የማስቸግርህ ጉዳይ አለኝ ይኸውም በቤቴ የረሳሁት ነገር ስላለ ዕገሊት ወደ ምትባል ሀገር ሄዶ መልእክት ያደርስልኝ ዘንድ ይህን ብላቴና እንድትሰጠኝ ነው የድካሙንም ዋጋ ሃያ ወቄት ወርቅ እከፍላለሁ" አለው።
ያም በግ ጠባቂ ስለ ወርቁ ስጦታ ደስ በመሰኘት ያን ጐልማሳ ጠርቶ "ልጄ ባሕራን ሆይ ይህ ክቡር ሰው ለሥራ ጉዳይ ወደ ቤቱ ሊልክህ ይፈልጋልና መልእክቱን አድርስለት እግዚአብሔር በሰላም ያግባህ" ሲል ጠየቀው፡፡ ልጁም "እሺ መልካም ነው አባቴ ሆይ ያዘዝከኝን ሁሉ ለመፈጸም ዝግጁ ነኝ" አለው። ከዚህም በኋላ ያ ባለጸጋ "ይህችን የመልእክት ደብዳቤ ይዞ ወደ አንተ የመጣውን ስሙ ባሕራን የተባለውን መልእክቷ በደረሰችህ ጊዜ ፈጥነህ ግደለው ገድለህም ሬሣውን ከጉድጓድ ጣለው እኔ በሰላም ተመልሼ እስክመጣ ድረስ ማንም ማን ይህን ምሥጢር አይወቅ" የሚል ጽሑፍ ለሹሙ ጽፎ አዘጋጀ፡፡ እንዲሁም በሹሙና በእርሱ መካከል የሚተዋወቁበትን ማኅተም በደብዳቤው ላይ አትሞ ለባሕራን ሰጠው፡፡ ለመንገዱም የሚሆነው ስንቅ ሰጥቶ ላከው።

ባሕራንም መልእክቱን ለማድረስ ዘጠኝ ቀን ተጉዞ የአንድ ቀን ጎዳና ሲቀረው እነሆ ክቡር የሚሆን የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል በንጉስ ጭፍራ አምሳል በፈረስ ተቀምጦ ወደሱ ደረሰና ወዴት እንደሚሄድ ጠየቀው፡፡
ባሕራንም "ከአንድ ባለጸጋ ሰው የተጻፈ ደብዳቤ ይዤ እርሱን ለማድረስ ዕገሊት ወደምትባል አገር እሄዳለሁ" አለው። ንዑድ ክቡር የሚሆን ቅዱስ ሚካኤልም "እስኪ የመልእክቱን ደብዳቤ አሳየኝ?" አለው፡፡ ባሕራንም "ጌታዬ ለማንም አታሳይ ብሎኛል" አለው፡፡ መልአኩም "እሺ ያም ባይሆን እንደተጠቀለለ አሳየኝ" አለው፡፡ ባሕራንም አሳየው፡፡ ቅዱስ ሚካኤልም በሞቱ ደብዳቤ ላይ እፍ ቢልበት የሞቱን ትእዛዝ አጥፍቶ የሕይወት ትዕዛዝ ጽፎበታል፡፡ በደብዳቤው ላይ የተጻፈውን የሞት መልእክት ደምስሶ "ከእኔ ከባለጸጋ ዕገሌ የተጻፈ" ይልና "ይህን መልእክት ይዞ ለመጣሰው ዕገሊት የምት ባለዋን ልጄን አጋቡት (ዳሩለት) በዱር የተሰማራውን ከብቴን በቤት ያለውን ሀብቴን በጠቅላላው የሚንቀሳቀስና የማይንቀሳቀስ ንብረቴን በሙሉ አውርሼዋለሁና እኔ እስክመጣ ድረስ አትጠብቁ በሄድኩበት ሀገር የምቆይበት ጉዳይ አለኝና፤ በቤቴና በንብረቴ ላይ ሙሉ ሥልጣን ሰጥቼዋለሁና የወደደውን ያደርግ ዘንድ አትከልክሉት ስለዚህም በእኔና በአንተ መካከል የምንተዋወቅበትን ምልክት አድርጌበታለሁ" የሚል ጽሑፍ ጽፎ ሰጠውና "እንግዲህ ወደ ባለጸጋው ቤት ሂድና ይህን መልእክት አድርስ ነገሩ እንዳይገለጽብህ ከእኔ ጋር መገናኘታችንንና የመልእክቱን ጽሑፍ እንደለወጥኩልህ ለማንም አትንገር" ሲል አስጠነቀቀው፡፡ ባሕራንም "እሺ ጌታዬ እንዳዘዝከኝ አደርጋለሁ" ብሎ ጉዞውን ቀጠለና የዚያን የባለፀጋ ቤት እየጠየቀ ከደረሰበት በኋላ ደብዳቤውን ለሹሙ ሰጠው።

ያም ሹም ደብዳቤውን ተቀብሎ ሲያነብ የታተመበት ማኅተም ዕውነተኛ መሆኑን ከአረጋገጠ በኋላ እግዚአብሔር እንዳዘዘው በቤተ ክርስቲያን ደንብ የባለጸጋውን ልጅ በተክሊል አጋባው፣ የሠርጉንም በዓል እስከ ዐርባ ቀን ድረስ በታላቅ ደስታ አከበሩ። ከሠርጉም በዓል ፍጻሜ በኋላ ያ ባለጸጋ ሰው ከሄደበት አገር ወደ ሀገሩ ተመልሶ ገባና በቤቱ አካባቢ ሲደርስ የደስታና የዘፈን ድምፅ ስለሰማ "ይህ የምሰማው ድምፅ ምንድነው?" ሲል ጠየቀ፡፡ ሰዎቹም "ባሕራን የተባለ ጐበዝ ካንተ ዘንድ ልጄን ዳሩለት የሚል ትእዛዝ አምጥቶ ልጅህን አግብቶ በሠርጉ ምክንያት ይዘፍናሉ ይደሰታሉ እነሆ እየበሉና እየጠጡ በቀንና በሌሊት እየዘፈኑ ሲደሰቱ ዐርባ ቀን ሆኗቸዋል በመልእክትህም እንዳዘዝከው ገንዘብህን የወንድና የሴት ባሮችህን በጠቅላላው የሚንቀሳቀስና የማይንቀሳቀስ ንብረትህን ሁሉ በሙሉ አስረክበውታል" አሉት።

ያም ባለጸጋ ያህን ቃል በሰማ ጊዜ ከድንጋጤው የተነሳ በታላቅ ቃል በመጮኽ ከመሬት ላይ ተከስክሶ ሞተና ነፍሱን አጋንንት ተረክበው ወደ ሲኦል አወረዷት። ከዚህም በኋላ ባሕራን የተባለ ያ ጐልማሳ የቅዱስ ሚካኤልን በዓል በየወሩ እያከበረ ዝክሩን እየዘከረ ይኖር ጀመር። በዚያን ጊዜ በጉዞ ላይ ሳለ ተገልጾለት የሞቱን መልእክት ወደ ሕይወት የለወጠለት ቅዱስ ሚካኤል እንደሆነም አወቀ ተረዳ። ንዑድ ክቡር የሚሆን የመላእክት ሁሉ አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ያደረገው ተአምር ሊቆጥሩት የማይቻል ብዙ ስለሆነ በኛም ላይ ኃይለ ረድኤቱ አድሮብን ይኑር እስከ ዘላለሙ ድረስ አሜን።
+ + +

ቅድስት አፎምያ፡- ቅድስት አፎምያ ሀገሯ ኪልቅያ ነው፡፡ ባለቤቷ አስተራኒቆስ መስፍነ ኪልቅያ ነበረ፡፡ እርሷም በትዳር በነበረችባቸው ዘመናት እግዚአብሔርን ከሚወድ ባለቤቷ ጋር እግዚአብሔርን ስታገለግለው የኖረች ሴት ደገኛ ሴት ናት፡፡ በየወሩ በ29 ቀን የጌታችንን የልደቱን፣ ወር በገባ በ21 የእመቤታችንንና ወር በገባ በ12 የቅዱስ ሚካኤልን መታሰቢያ እያደረጉ ነዳያንን ይጎበኙ ነበር፡፡

ባለቤቷ አስተራኒቆስ ከዚህ ዓለም የሚያርፍበት ጊዜ እንደደረሰ ባወቀ ጊዜ ይሰጡት የነበረውን ምጽዋት እና የሦስቱን በዓላት መታሰቢያ ማድረግ እንዳታስታጉል ከአደራ ጋር አዘዛት፡፡ እርሷም የመልአኩን የቅዱስ ሚካኤልን ሥዕል ያሥልላት ዘንድ ባለቤቷን ጠይቃ አሠርቶ ሰጣት፡፡ በከበረ ቦታም አኖረችው፡፡ ባሏ ካረፈ በኋላ ያዘዛትን መንፈሳዊ ሥራ ከወትሮው አስበልጣ መሥራት ቀጠለች፡፡ ባሏም ታሞ ሞቶ ከሀብቷ ከንብረቷ እየሰጠች እየመጸወተች በጾም በጸሎት ተወስና ትኖር ነበር፡፡ ሰይጣን ለምቀኝነት አያርፍምና ደግ መነኩሴ መስሎ አጋንንትን መነኮሳይያት አስመስሎ መጥቶ ከደጅ ሆኖ አስጠራት፡፡ እርሷም "ከቤት ገብታችሁ በቅዱስ ሚካኤል ሥዕል ፊት ጸልዩልኝ" አለቻቸው፡፡ ሰይጣናቱም "እኛማ በነግህ ጸልየናል?" አሏት፡፡ ቀጥሎም ሰይጣን "...እንደው አንቺ ግን ይህ ሁሉ ጾም ጸሎት ምን ያደርገልሻል? ሀብትሽን ሰጥተሸ መጨረስሽስ ስለምንድን ነው? በዚያ ላይ አንቺ ስትደክሚ የሚደግፍሽ ስታረጂ የሚጦርሽ ልጅ የለሽም ሁለተኛ ማግባት ኃጢአት መስሎሻልን? እነ አብርሃም እነ ዳዊ ከብዙ ሴቶች ብዙ ልጆች ወልደው የለምን? አሁንም ቤት ሰሪ ጎመን ዘሪ ልጅ ያስፈልግሻልና ባል አግቢ፣ እሺ በይኝ" አላት፡፡
ቅድስት አፎምያም "አባ ቆብህ መልካም ነበር ንግግርህ ግን ክፉ ነው፣ አትጹሚ አትጸልዩ ያልከኝ ጌታ ምጽዋት አበድር እመስዋዕት ብሎ የለምን? ሁለተኛ ባል አግቢ ማለትንስ ከምን አገኘኸው? እርግቦች እንኳ ባሎቻቸው ከሞቱባቸው ከሌላ ወንድ አይቀርቡም ታዲያ ጥንቱን በንጽሕና ሊኖር የተፈጠረ ሰው ሁለተኛ አላገባም ቢል ዕዳ ፍዳ ሊሆንበት ነውን?" ብላ ሞገተችው፡፡

የሰው ልጆች ጠላት የሆነው ሰይጣንም በመልካም አገልግሎት ስትበረታ አይቷታልና ዝም ብሎ ሊተዋት አልወደደም፡፡ ከላይ እንዳየነው በመጀመሪያ ባል ሳታገባ ማገልገሏን ትታ ሌላ ባል አግብታ ልጅ ወልዳ እንድትኖር በብዙ ማባበል ጠየቃት፡፡ ባሏ መንግሥተ ሰማያትን ስለወረሰ ምንም ምጽዋት እንደማይሻ አስመስሎ ነገራት፡፡ ቅድስት አፎምያ ግ

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

3) መንፈሳዊ ትምህርት መንፈሳዊ ዓላማ ሲኖረው ሥጋዊ ትምህርት ደግሞ በአመዛኙ ሥጋዊ ዓላማ አለው፡፡ መንፈሳዊ ትምህርትን ከዓላማው ወጥቶ መብያና መጠጫ ቢያደርጉት ፈጣሪን ማስደሰት አይችልም፡፡ አልፎ ተርፎም እንደ ቅኔ ባለ መንፈሳዊ ትምህርት ፈጣሪን ለማመስገን መራቀቅ ሲገባ ፍጡርን ሲሹ እንደፈጣሪ ለማወደስ አልያም ደግሞ እንደ ዲያብሎስ ለመደምሰስ ቢጠቀሙበት ያለ ዓላማው ነውና ማስጠየቁ አይቀርም። ስለዚህ በተማሩት ትምህርት ከመጠየቅና ከመጐዳት በአግባቡ በሥራ ላይ በማዋል መጠቀም ያሻል።መኮትኮቻን መፍለጫ፡ መፍለጫን ደግሞ መኮትኮቻ ማድረግ ያለፋል እንጂ ምንም አይጠቅምም:: እንደዚሁም ሁሉ መንፈሳዊ ትምህርትን ያለ ዓላማው ቢያውሉት ያስጐዳል እንጂ አይጠቅምም።
4) ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ «የሰው ሕይወት በገንዘቡ ብዛት አይደለምና ተጠንቀቁ።» ሉቃ12፥15 በማለት አስተምሮአል:: የሰው ሕይወት በገንዘቡ ብዛት አይደለም ማለት ባለው ነገር መጠን አይደለም ማለት ነው:: ስለዚህ የሰው ሕይወት በጉልበቱ፣ በመልኩ፣ በወገኑ፣ በዕውቀቱ ልክ አይደለም፡፡ አንዳንድ ሰዎች ግን ዛሬ ዛሬ ሕይወት በትምህርት ልክ መስሏቸዋል። በዚህ ምክንያት በትምህርታቸው ማነስ ተስፋ በመቁረጥ በእጅጉ ያዝናሉ፡፡ በዚህ ጉዳይ ብዙ ከማዘን መማር የሚችሉበት መንገድ ካለ መማር የሌለ ከመሰላቸውም ምንም ሳይማሩ የተሻለ ኑሮ የሚኖሩትን ሰዎች በመመልከት እነርሱም እንደዚያ ከመኖር የሚያግዳቸው ነገር እንደሌለ በማመን ጠንክሮ መሥራት ይኖርባቸዋል:: ስለ ትምህርት ባለን የተዛባ አመለካከት የምንጐዳው እኛው ራሳችን ነን፡፡ «ያልተማረ ይታሰር ወይም ይገደል!» ተብሎ እስካልታወጀ ድረስ ጥሩ አስተሳሰብና ስብእና ካለህ የምትሠማራበት የሥራ መስክ ይለይ ይሆናል እንጂ ከተማረ ሰውም በተሻለ መልኩ ለመኖር ትችላለህ።ይህን መቀበል ካቃተህ ግን ትምህርት አምላኪ ከመሆንም ባሻገር ብትማርም እንኳን የትግል መንፈስ የለህምና ስኬታማ አትሆንም። ስለዚህ ያልተማረ ብትሆንም ሙሉ ሰውነት ይሰማህ እንጂ አትሸማቀቅ። አልተማርኩም ብሎ ተስፋ መቁረጥ ባልተማሩ ሰዎች ዘንድ አልፎ አልፎ የሚታይ የትምህርት አንጻራዊ ጉዳት ነው፡፡
5) ለማወቅ ብትጓጓና ጎበዝ ተማሪ ለመሆን ብትመኝ መልካም ነው፡፡ ምኞትህም ከግብ እስኪደርስ ጠንክረህ ተማር፡፡ ሕይወትን መና በሚያስቀሩ ልዩ ልዩ ዕፀዋቶች ታግዘህ ለመማር አትሞክር። አንዳንዶች ለጥናት ይረዳል በማለት ጫት ከመቃም አንሥቶ ዕውቀት ይገልጻሉ የተባሉትን ልዩ ልዩ ዕፀዋት በመጠቀም በጤናቸው፣ በጠባያቸውና በመሳሰሉት ማንነታቸው ላይ የማይሽር ጠባሳ አስቀምጠዋል፡፡ ለመማር አገዙኝ የምትላቸው እነዚህ ዕፀዋት ሱስ ወደ መሆን ይለወጡና የሠራህበትን ገንዘብ በሙሉ «ያስተማርነበት ነው!» በማለት እንደሚያስገብሩህ መዘንጋት የለብህም፡፡
6) ከተማርህ በኋላ በተማርከው የትምህርት ዘርፍ ተያያዥ የሆነ ሥራ ብታገኝ መልካም ነው።ይህ ግን ሊሳካም ላይሳካም የሚችል ነገር በመሆኑ በመስክህ ሥራ አላገኘኽም ማለት ሥራ ፈጽሞ የለም ማለት አይደለም፡፡ ማንኛውምን ሥራ ለመሥራት የተነሣሣ ልቡና ይኑርህ፡፡ ገቢ ባይኖረውም እንኳን የሥራ ልምድ የሚሆንህን መንገድና ዕድል ተጠቀምበት እንጂ አትናቀው፡፡መሥራትም ትምህርት ነውና ገቢ ባይኖረውም ከመቦዘን መሥራት በጣም ጠቃሚ ነው፡፡ ሥራ ስታጣ አስብና ፈጥረህ ሥራ እንጂ ሥራን ከመንግሥት ብቻ አትጠብቅ፡፡ እንዲህ ማድረግ ተስፋ ከመቁረጥ ያድንሃል፡፡ ተምረህ ሥራ ማጣትህ ካልተማረ ይልቅ ተስፋ ካስቆረጠህ መማርህም ያጠራጥራል፡፡ ምክንያቱም መማር ማለት በተሻለ መልኩ ማሰብ ማለት ነዋ!

ቀጣይ ምዕራፍ ዐሥራ አንድ ክፍል አንድ :
👉
«መልካም ስም» በሚል ይቀጥላል .....
ለጥያቄና አስተያየት @Ethiopian_Orthodox_bot ተጠቀሙ።

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

ሕይወተ ወራዙት (የወጣቶች ሕይወት)
 ምዕራፍ ዐሥር ክፍል ዐራት
.................................................

የትምህርት ተዛማጅ ጉዳቶች
1) ከላይ ከተጠቀሰው በተጨማሪ በዘመናዊ ትምህርት ምክንያት ሲከሠት የሚስተዋለው ጉዳት ሰዎች ለትምህርት ከሚሰጡት ጊዜ ጋር የተቆራኘ ነው፡፡ ይኸውም አንዳንድ ሰዎች ትምህርት ለሰው ከሚያስፈልጉት ነገሮች እንደ አንዱ ብቻ በነጠላ ሊታይ የሚገባው ነገር መሆኑን ይዘነጉታል፡፡ ለሚያስፈልጓቸው ሌሎች ተግባራት ማዋል ያለባቸውን ጊዜ በሙሉ ለትምህርት ብቻ በማዋል የኋላ ኋላ ሲጸጸቱ ይታያል፡፡ ለምሳሌ:- አንዲት ልጃገረድ ትምህርቷን ባለመመጠንዋ ምክንያት የመውለጃ ዕድሜዋ ቢያልፍባት ተምራ ያገኘችው ማዕረግ የተሳናትን ልጅ መውለድ ሊመልስላት ወይም ኑሮዋን ደስተኛና የተሟላ ሊያደርገው አይችልም:: ስለዚህ ጊዜን አስፈላጊ ለሆኑ ነገሮች ማብቃቃት እንጂ መላ ዕድሜን ለትምህርት ብቻ መስጠት ብልህ አያሰኝም፡፡
ትምህርት ሰው እራሱን ካልመጠነ በቀር ፍጻሜ የሌለው ነገር ነው:: አንድ ሰው በዓለም ላይ ያሉትን ነገሮች ጠቅሎ ሊያውቅ አይችልም። በአንድ ርእሰ ጉዳይ ግን የተሻለና ጠለቅ ያለ ዕውቀት ሊኖረው ይችላል፡፡ ሐዋርያው «ከዕውቀት ከፍለን እናውቃለን›› በማለት የተናገረው አንድ ሰው የሚያውቀው ጥቂት ነገርን ያውም በክፊል መሆኑን ለማስረዳት ነው። 1ቆሮ 13፥9

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

መንፈሳዊ ትምህርት ለበጎ ሥራ ያዘጋጃል።«የእግዚአብሔር ሰው ፍጹምና ለበጎ ሥራ የተዘጋጀ ይሆን ዘንድ» በማለት ቅዱስ ጳውሎስ የተናገረው ቃል ከላይ የተጠቀሰውን ሐሳብ ይደግፋል፡፡ 2ጢም3፥16 መንፈሳዊ ትምህርት ለበጎ ሥራ የሚያዘጋጅ፣ የሃይማኖት ሰው እንድንሆን የሚያደርግ በመሆኑ በነፍስም ሆነ በሥጋ እጅግ ጠቃሚ ነው፡፡ የመንፈሳዊን ትምህርት ጥቅም በአጭር ቃል ስናጠቃልለው «መዳን የሚገኝበት ጥበብ›› እንለዋለን፡፡ 2ጢሞ3፥15 ምክንያቱም ይህ ጥበብ ሰው የእምነትንና የምግባርን እርካብ እየረገጠ ወደ መንግሥተ ሰማያት ለመውጣት ስለሚያስችለው ነው፡፡ ከዚህ ሁሉ በላይ ደግሞ መንፈሳዊ ትምህርት ወደ አእምሮ የሚገበትን የዘመናዊ ትምህርት ዕንስ ሐሳቦችንና ማንኛውም ዓይነት ዕውቀቶችን ምን ያህል እውነተኛና ጠቃሚ እንደሆኑ ለመመዘን ይረዳል።መንፈሳዊ ትምህርት ከዘመናዊ ትምህርት መቅደም የሚኖርበትም ስለዚህ ነው፡፡ አንድ ሰው አስቀድሞ መንፈሳዊውን ትምህርት በሚገባ የተማረ ከሆነ ለወደፊት ሕይወቱ የሚበጀውንና ከእግዚአብሔር አንድነት እንዳይለይ የሚረዳውን ነገር ሁሉ ለይቶ ያውቃል።
«ሥራ» ተብለው ነገር ግን ከመንፈሳዊ ሕይወት ጋር ፍጹም የሚቃረኑ ብዙ መስኮች አሉ፡፡ አንድ ክርስቲያን አስቀድሞ መንፈሳዊ ግንዛቤ ካለው ከፈጣሪ አንድነት የሚለዩትን እነዚህን ነገሮች እየተማረና እያጠና ገንዘቡንና ጊዜውን አያባክንም። ለምሳሌ:- ቤተ ክርስቲያን ከመጽሐፍ ቅዱስ መረጃ በመጥቀስ «ዘፋኝነትን» ታወግዛለች፡፡ አንድ ሰው ደግሞ ደግሞ መንፈሳዊነትን መላበስ እየፈለገና የቤተ ክርስቲያን ልጅ ሆኖ ሳለ አንድን የሙዚቃ መሣሪያ አጨዋወትና ጥሩ ዘፋኝ ለመሆን የሚያስችል የድምጽ አወጣጥ ጥበብን ቢያጠና በሕይወቱ ብዙ ነገሮች አይቃወሱበትም? ምክንያቱም ሌላ ሥራ እንዳይሠራ ገንዘቡንና ጊዜውን አቃጥሎ ያገኘው ሙያ ቢኖር የሙዚቃ መሣሪያ መጫወትና ዘፋኝነት ነው፡፡ እንዳይተወው ደግሞ ምን ሠርቶ ይኑር? በዚሁ ሥራው ተሰማርቶ እንዳይኖር ደግሞ ከፈጣሪው ጋር ያለው ግን በእጅጉ ይበላሽበታል፡፡ ለዚህ ሁሉ ችግር መፍትሔ የሚሆነው በምን መልኩ ብንጓዝ እንደምንጠቀም ከወዲሁ ለይተን እንድናውቅ የሚረዳንን መንፈሳዊ ትምህርት አስቀድመን ብንማር ነው።
ብዙ ክርስቲያኖች ጥሩ መንፈሳዊ ሰው መሆን ያልቻሉት ከላይ የተጠቀሰው ዓይነት ውስብስብ ችግር ስላጋጠማቸው እንጂ መሆን ሳይፈልጉ ቀርተው አይደለም፡፡ እንዲህ ያለ ችግር ያጋጠማቸው ሰዎች ቀስ በቀስ ሥራቸውን በሌላ አማራጭ እየተከ ከፈጣሪ ጋር ያላቸውን ዘምድና ከማጠናከር ውጭ ባሉበት ሁኔታ ጥሩ መንፈሳዊ ሰው መሆን የሚችሉበት ምንም ዓይነት መንገድ
የለም።ከዚህ ሁሉ የሚከፋው ደግሞ «ካፈርኩ አይመልሰኝ» እንደሚባለው ሥራቸው በቅዱስ መጽሐፍ የተወገዘ ሆኖ ሳለ አንድ ጊዜ ስለገቡበት ብቻ ሥራቸውን መጽሐፍ ቅዱስ እንደማይቃወመው አድርገው ለማስረዳት የሚሞክሩ ሰዎች መኖራቸው ነው፡፡ ተሳስቻለሁ ! እኔ በሄድኩበት እንዳትሄዱ ብሎ ማስረዳት አንዱ መንፈሳዊነት ሆኖ ሳለ ሌሎችም ተጨምረው እንዲሳሳቱ «ሥራዬ ልክ ነው» ማለት «እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል» የሚል ዓይነት የምቀኝነት ሥራ ነው፡፡ አንተ ወጣት የምትማረው ትምህርትና የወደፊት የሥራ መሰማሪያህ በመንፈሳዊ ሕይወት ለአንድ ክርስቲያን መኖር እስከሚገባው ድረስ ዘልቆ ከመሄድ የሚያግድህ እንዳይሆንብህ ትጠነቀቃለህ? ከሆነ ደህና ካልሆነ ግን ለነፍስህ ምንም እንዳላሰብክላት እወቅ፡፡ ስለ ወደፊት መንፈሳዊ ማንነቱ ምንም የማያስብ ሰውስ እንዴት ክርስቲያን ሊባል ይችላል?

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

ሕይወተ ወራዙት(የወጣቶች ሕይወት)
 ምዕራፍ ዐሥር ክፍል ሦስት
.................................................

በትምህርት መኖር «ጥበቃ» ነው!
ቦዘኔ አእምሮ ብዙ ክፉ ሐሳቦችን ሲወልድ ይውላል።«ሥራ ፈት አእምሮ የሰይጣን ቤተ ሙከራ ነው» መባሉ ተገቢ ነው።ሰዎች ጊዜያቸውን ለመልካም ነገር ካልተጠቀሙበት ለክፉ ተግባር የሚያወሉት የተትረፈረፈ ጊዜ ይኖራቸዋል። በመልካም ተግባር! ወይም በመማር የተጠመዱ ከሆኑ ግን ክፉ ሐሳብ ቢፈጠርባቸው እንኳን ከጊዜ እጥረት የተነሣ ሳያከናውኑት ይቀራሉ፡፡
ለብዙ ወጣቶች የሥነ ምግባር ጉድለቶች ተጠቃሽ የሚሆነው ቦዘንተኝት ወይም ሥራ አጥነት ነው።የእነዚህ ሰዎች አእምሮ በሥራ ባለመጠመዱ ምክንያት ወደ ልዩ ልዩ ክፉ ጐዳና ይተማል፡፡ የአብዛኞቹ ሰካራሞች፣ የጫት ቃሚወች፣ የሲጃራ አጫሾች፣ የአደንዛዥ ዕፀዋትና መድኃኒት ሱሰኞች ሕይወት ቢፈተሽ ለሥራና ለትምህርት ግድ የለሾች መሆናቸውን መረዳት ይቻላል።ይህ ማለት ግን ከሠራተኞችና ከምሁራን ይህን በመስለ ርካሽ ተግባር የተመረዙ የሉም ማለት አይደለም።

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

ሐዋርያት ተባበሩ፤
በአዲስ ቋንቋ እየተናገሩ፤
ቃሉን አስተማሩ።

ካረገ በኋላ በአስረኛው ቀን፤
ወደ አለም ላከው ጰራቅሊጦስን።

በዝግ ቤት ውስጥ ቆዩ ቀኑን ሲጠብቁ፤
የተሰጣቸውን ተስፋውን እስኪያውቁ።

ቀኑም ደረሰና በሃምሳኛው እለት፤
ተሰብስበው ሳሉ በአንድነት ፀሎት፤
መንፈስ ቅዱስ ታየ በነደ እሳት።

ያ የተነገረው ያ የተስፋ ቃል፤
ወረደ ከሰማይ በእሳት አምሳል።

ጴጥሮስ አሳመነ ሶስት ሺ ነፍሳት፤
ያን ጊዜ ገሊላ በሰጠው ትምህርት።

ከሶስት አካል አንዱ መንፈስ ቅዱስን፤
ልኮ አናገራቸው ሁሉን በልሳን።

ሐዋርያት ተባበሩ፤
በአዲስ ቋንቋ እየተናገሩ፤
ቃሉን አስተማሩ።

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

መንፈስ ቅዱስ ጰራቅሊጦስ ስለተባለበትና ተስፋ በተሰጣቸው በኀምሳኛው ቀን ወርዶ ስለ ሠራው ሥራ እንዲህ በማለት ያብራራል። ‹‹ወመንፈስ ቅዱስኒ ኢተሰምየ ጰራቅሊጦስሃ ዘእንበለ አመ ይቤሎሙ እግዚእ ኢየሱስ ለአርዳኢሁ እፌኑ ለክሙ ካልአ ጰራቅሊጦስሃ። ጰራቅሊጦስ ብሂል ናዛዚ ብሂል በነገረ ጽርዕ ……መንፈስ ቅዱስም ጌታ ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን ሌላውን አጽናኝ እልክላችኋለሁ›› ከማለቱ በፊት ጰራቅሊጦስ አልተባለም ጰራቅሊጦስ ማለት በጽርዕ ቋንቋ አጽናኝ ማለት ነው ስለምን አጽናኝ ተባለ ደቀ መዛሙርቱ ወልድ ካረገበት ቀን ጀምሮ ጰራቅሊጦስ እስከ ወረደበት ቀን ድረስ ያለቅሱ ነበረና ስለዚህም ወልድ መንፈስ ቅዱስን ጰራቅሊጦስ አለው። የስሙ ትርጓሜ ግን አስቀድመን እንደተናገርነው አጽናኝ ማለት ነው። (ዮሐ. ፲፬፥፲፭)

በዓለ ጰራቅሊጦስ የሚከበረው ርደተ መንፈስ ቅዱስን መሠረት በማድረግ በመሆኑ ምክንያት ጸጋ መንፈስ ቅዱስ ለመቀበል ነው፤ በዕለቱም ኢየሩሳሌም በተባለችው ቤተክርስቲያን ስለመጽናት፤ ከግለኝነት ይልቅ መንፈሳዊ አንድነትን ስለማስቀደም እና ስለመጸለይ እንማራለን፡፡
በዓለ ትንሣኤውን በቸርነቱ በሰላም እንድናሳልፍ ፈቅዶ እስከ ዛሬ ድረስ ስለ ጠበቀን፣ አሁን ደግሞ በጾም፣ በጸሎት ሆነን እርሱን የምናመሰግንበትን ወቅት ስላመጣልን አምላካችን ልዑል እግዚአብሔር ስሙ ለዘለዓለሙ የተመሰገነ ይሁን፤ አሜን፡፡
ምንጮች፤

መዝገበ ታሪክ፣ ክፍል ፪፤ መምህር ኅሩይ ኤርምያስ፤ ፲፱፻፺፭ ዓ.ም፤ ገጽ ፹፬-፹፭፡፡

መጽሐፈ ስንክሳር ግንቦት ፲፰ ቀን፣ መጽሐፈ ምሥጢር፡፡

መጽሐፈ ግጻዌ፡፡

ማኅቶተ ዘመን፣ መምህር በሙሉ አስፋው፤ ፳፻፩ ዓ.ም፤ ገጽ ፻፺፭-፪፻፬፡፡


ወስብሐት ለእግዚአብሔር

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

የትምህርት ጥቅም
መማር የሚኖርብህ ልጅ በመሆንህ ተገደህ ወይም ምንም ምርጫ ስላጣህ መሆን የለበትም፡፡ ትምህርት ብዙ ጥቅም እንዳለው ዐውቀህ ከልብ በመነጨ ፍላጐትና ጥረት ብትማር ለወደፊት ኑሮኽ ምን ዓይነት ባልንጀራ ማፍራት እንዳለብህ፣ ምን ብትሠራ እንደምትጠቀምና በሕይወትህ ዙሪያ ለሚፈጠሩ የሕሊና ጥያቄዎች በቀላሉ መልስ እንድታገኝ ጥሩ መሠረት ይጥልልሃል።
ትምህርት ሌሎች ሰዎች ክዚህ በፊት የሠሩትን ወይም አሁን በመሥራት ላይ ያሉትን ነገሮች ለማወቅ ያስችላል፡፡ በሥራቸውም የተሳካላቸውንና ውድቀት ያስከተለባቸውን አካሄድ በመለየት በሙከራ ጊዜ ሳታጠፋና በእነርሱ ላይ የደረሰውም ውድቀት ሳይደርስብህ የትኛ ውን ጐዳና መከተል እንዳለብህ ለመወስን ይረዳሃል፡፡
ከልብ የተማረ ሰው ጊዜውን ጠብቆ መጠቀሙ አይቀርም።የተማረውን ትምህርት ለሌሎች ለማስተማር፤ የፈጠራ ሥራዎችን በመሥራት፣ ወይም ተምሮ ባገኘው ሙያ ምንደኛ ሆኖ በሚያገኘው ግቢ ራሱን ማስተዳደር ይችላል ። ከዚህም በተጨማሪ የሙያ ተሰጥኦቹን በመጠቀም ያለአግባብ የሚያወጣውን ወጪ መቀነስና ለራሱ የተመቻቸ ሁኔታን ሊፈጥር ይችላል፡፡ ለምሳሌ፡- የምግብ አዘጋጃጀት ትምህርትን የተከታተለ አንድ ሰው የሚፈልገውንና የሚስማማውን የምግብ ዓይነት በማዘጋጀት ጤናውን ለመጠበቅ ከመቻሉም በላይ መመገብያ ቤቶችን (ሆቴሎችን) በመጠቀም የሚያወጣውን ያልተመጣጠነ ወጪ በመቀነስ ራሱን ለመርዳት ይችላል፡፡ በተመሳሳይ ሁኔታ እንድ የቴክኒክ ሙያ ሥልጠና የወሰደ ሰው በዙሪያው ከሚገኙ ነገሮች በመጠቀምና ወጪ ሳያስፈልገው ልዩ ልዩ መገልገያዎችን ለራሱ ማበጀት ወይም የተበላሹ ንብረቶቹን ያለተጨማሪ ወጪ ራሱ ሊጠግናቸውና ሊያድሳቸው መቻሉም ከመማር የሚገኝ ጉልህ ጥቅም ተደርጐ ሊጠቀስ ይችላል፡፡
አንድ ሰው የተማረውን ትምህርት በቀጥታ በሥራ ላይ ለማዋል በማይችልበት ሁኔታ ውስጥ ቢገኝ እንኳን ትምህርት አይጠቅምም ለማለት አይቻልም፡፡ እንደዚህ ዓይነት ሰው ምንም እንኳን በተማረው ትምህርት በቀጥታ ገቢ አግኝቶ ተጠቃሚ ባይሆንም ትምህርቱ በሌላ አቅጣጫ ተጠቃሚ እንደሚያደርገው ማስተዋል ይገባል:: ምክንያቱም መማር ለመማር ከተዘጋጀንበት መደበኛ ትምህርት ውጭ በሂደቱ ትዕግሥትን፣ ትጋትን፣ ሐሳብን ሰብስቦ የመከታተል ችሎታን፣ መጠየቅንና የማንበብ ልምድን እንድናዳብር ከማድረጉም በላይ አእምሮአችን እንዲሰፋ ያደርጋል።የሠሩበት አካል እንደሚጠነክር ሁሉ የተማሩበትም አእምሮ መዳበሩ አይቀርም። ይህም በዋጋ ሊተመን የማይችል የትምህርት ሁለ ገብ ጥቅም ነው።
ቀጣይ ምዕራፍ ዐሥር ክፍል ሦስት :
👉«በትምህርት መኖር ጥበቃ ነው»
👉«የመንፈሳዊ ትምህርት ጥቅም »
👉«ትምህርት ጉዳት ይኖረዋል »
በሚል ይቀጥላል .....
ለጥያቄና አስተያየት @Ethiopian_Orthodox_bot ተጠቀሙ።

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

መንፈሳዊ ትምህርት እንደ ራት ሲሆን ሥጋዊ ትምህርት ግን እንደ ዳረጎት ነው:: ከእራትና ከዳረጐት ዳረጎትን የሚመርጥ ማንም የለም:: ዳረጐት እራት አይሆንምና፡፡ እንደዚሁም ሁሉ ጊዜያዊ እንጂ ዘለዓለማዊ ጥቅም የሌላት ሥጋዊ ጥበብ ከመንፈሳዊ ጥበብ መቅደም የለባትም፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ማንኛውም ሰው በሕይወት ዘመኑ ማስቀደም ያለበት ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ለመግባት የሚረዳውን ነገር መሆን እንዳለበት ሲገልጽ «አስቀድማችሁ የእግዚአብሔርን መንግሥት ጽድቁንም ፈልጉ ይህም ሁሉ ይጨመርላችኋል» በማለት ተናግሯል:: ማቴ6÷33
ሠለስቱ ምዕት ልጆችና ወጣቶች አስቀድመው ምን መማር እንዳለባቸው በትእዛዝ መልክ እንዲህ ብለዋል- «ቅድመ መሀርዎሙ ለውለድክሙ መጽሐፈ ሲራክ ወሰሎሞን ወመዝሙረ ዳዊት» ይህም «አስቀድማችሁ ለልጆቻችሁ የሲራክን የሰለሞንን መጻሕፍትና የዳዊትን መዝሙር አስተምሯቸው» ማለት ነው:: ይልቁንም «አስቀድማችሁ» እና «አስተምሯቸው» የሚሉት ቃላት ልጆች ከዘመናዊ ትምህርት አስቀድመው መንፈሳዊውን ትምህርት እንዲማሩ የማድረግ ኃላፊነት የወደቀው በወላጆች ላይ መሆኑን ይጠቁማሉ፡፡
ይህ የአበው ትዕዛዝ መንፈሳዊው ትምህርት ከሥጋዊው ትምህርት መቅደም እንዳለበት ብቻ ሳይሆን ከመንፈሳዊ መጻሕፍትም ለወጣቶች ከላይ የተጠቀሱት መጻሕፍት መቅደም እንዳለባቸው ያስረዳል።ምክንያቱም እነዚህ መጻሕፍት ወጣቶች በአእምሮ የበሰሉ እንዲሆኑ ከማድረጋቸውም በላይ ሥጋዊውንና መንፈሳዊውን ጥበብ አጣምረው ለመረዳት እንዲችሉ ያደርጓቸዋል፡፡
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎሰ ለሃይማኖት ልጁ ለጢሞቴዎስ በላከው መልእክቱ «ማንም ባልቴት ግን ልጆች ወይም የልጅ ልጆች ቢኖሩአት፥ እነርሱ አስቀድመው ለገዛ ቤተሰቦቻቸው እግዚአብሔርን መምሰል ያሳዩ ዘንድ ለወላጆቻቸውም ብድራትን ይመልሱላቸው ዘንድ ይማሩ» በማለት ልጆችና ወጣቶች አስቀድመው ምን መማር እንዳለባቸው በግልጽ ተናግሯል፡፡ መማር ያለባቸውም ተገልጦ ሊታይ የሚችል «እግዚአብሔርን መምሰል›› እና ወላጆቻቸውን በመጦር መንከባክብ ማለትም «ብድራትን መመለስ»መሆን እንደሚገባው አስረድቷል።ወላጆችን መርዳትና እግዚአብሔርን መምሰል የሚገኝበት ትምህርት መንፈሳዊ ትምህርት መሆኑ ግልጽ ነው።ይህን ተረድቶ መንፈሳዊውን ትምህርት አስቀድሞ መማር ምን ያህል እግዚአብሔርን እንደሚያስደስተው «ይህ በእግዚአብሔር ፊት መልካምና የተወደደ ነውና» በማለት ጨምሮ ገልጧል፡፡ 1ጢሞ5፡4
አንድ ክፉ ሱስ ከተጸናወተህ በኋላ ምንም እንኳን ጐጂነቱን በበቂ ሁኔታ ብታውቅ ካንተ ለማራቅ እጅግ ይቸግርሃል፡፡ እንደዚሁም ሁሉ ዓለማዊ ትምህርትን አስቀድመህ ተምረህ ከሃይማኖትህ ጋር የሚጣረሱትን ጽንሰ ሐሳቦች ከተለማመድካቸው በኋላ እነዚህን አስወግደህ ሃይማኖተኛ ለመሆን መቸገርህ አይቀርም።ዘመናዊ ትምህርት ለማመን ዳተኛ ያደርጋል፣ የሕሊና ሙግት ይፈጥራል፣ ጥያቄ እንድታበዛ ያደርጋል፤ ከማመን ይልቅ እንድትመራመር ይገፋፋሃል፡፡ እነዚህ ነገሮች ደግሞ በመንፈሳዊ እይታ መጠነኛ ጥቅም ሲኖራቸው የሚያመዝነው ግን ጉዳታቸው ነው፡፡ እንኳን ዘመናዊ አስተሳሰብና ትምህርት ወደ ውስጥህ ቀድሞ ገብቶ ይቅርና ትምህርተ ሃይማኖትን አስቀድመህ ከተማርክ በኋላ እንኳን ዘመናዊውን ትምህርት ስትማረው በመንፈሳዊነትህ ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ ያሳድርብሃል፡፡ ለዚህ ምስክር የሚሆኑ በመጀመሪያ በሃይማኖት ትምህርት ከተደላደሉ በኋላ በዘመናዊ ትምህርት መርሕና አስተሳሰብ ተውጠው ሃይማኖተኛ እንደነበሩ ይቅርና ስለሃይማኖት ሰምተው እንኳን ማወቃቸው የሚያጠራጥሩ በርካታ ሰዎች በዙሪያህ ይገኛሉ።ስለዚህ ከምንም በላይ የሚጠቅመው ትምህርተ ሃይማኖትን አስቀድሞ መማር ነው።

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

የትምህርት ዓይነቶች
ሐዋርያው ቅዱስ ያዕቆብ ምድራዊና ሰማያዊ፣ ሥጋዊና መንፈሳዊ በማለት ጥበብን በሁለት በመክፈል ጽፏል። ስለምድራዊ ጥበብ ሲናገር «ይህ ጥበብ ከላይ የሚወርድ አይደለም፣ ነገር ግን የምድር ነው፥ የሥጋም ነው» በማለት ሲገልጸው ሰማያዊውን ጥበብ ደግሞ «ላይኛይቱ ጥበብ ግን በመጀመሪያ ንጽሕት ናት፡ በኋላም ታራቂ፣ ገር፡ እሺ ባይ፥ ምሕረትና በጎ ፍሬ የሞላባት፥ ጥርጥርና ግብዝነት የሌለባት ናት፡፡›› በማለት ይገልጻታል። ያዕ3፥15(17) ጥበብ ለሁለት ወገን ተከፈለች ማለት ትምህርትም ለሁለት ይከፈላል። ምክንያቱም ጥበብ የሚገኝ ከትምህርት ነውና፡፡
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ደግሞ ትምህርትን ትምህርተ ክርስቶስና ትምህርተ ሰብእ (የሰው ትምህርት) በማለት ለሁለት ክፍለ አስረድቷል፡፡ ይህም «እንደ ክርስቶስ ትምህርት ሳይሆን፥ እንደ ሰው ወግና እንደ ዓላማዊ እንደ መጀመሪያ ትምህርት ባለ በፍልስፍና በከንቱም መታለል ማንም እንዳይማርካችሁ ተጠበቁ::» ባለው ይታወቃል።ቆላ2÷8
ስለዚህ መንፈሳዊውን ትምህርት የክርስቶስ ትምህርት፣ መንፈሳዊ፣ የቤተክህነት፣ ሰማያዊ፤ ጥንታዊ በማለት ስንጠራው ዘመናዊውን ትምህርት ደግሞ ዓለማዊ፣ ምድራዊ ፣ሰብአዊ፣ ወግ፣ ፍልስፍና፣ ሥጋዊ ትምህርት በማለት ልንጠራው እንችላለን፡፡
ከቤተ ክርስቲያን የጸሎት መጻሕፍት መካከል አንዱ የሆነው መስተብቁዕ መንፈሳዊውን ትምህርት «የመለኮት ትምህርት» በማለት ይጠራዋል፡፡ «ወሴሲ ልበነ በመለኮተ ትምህርት ወበለብዎ ዘእምኀቢከ» ፍችውም «በመለኮት ትምህርት ልቡናችንን መግብ፡ ከአንተ ዘንድ የሚገኘውንም ማስተዋል» ማለት ነው። (መስተብቁዕ በእንተ ዝናማት)
በአሁኑ ጊዜ ሥጋዊውን ትምህርት በሀገራችን ለማዳረስ ኃላፊነት የተሰጠው ክፍል በሚኒስቴሮች መሥሪያ ቤት የትምህርት ሚኒስቴር ሲሆን እውነተኛውን መንፈሳዊ ትምህርት ለዓለም እንድታዳርስ ከጌታችን ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ሙሉ ኃላፊነትና ትዕዛዝ የተቀበለች ቤተ ክርስቲያን ናት፡፡ ይሁን እንጂ ቤተ ክርስቲያን በሀገራችን ለመንፈሳዊውም ሆነ ለሥጋዊው ትምህርት መሠረት እንደ መሆኗ መጠን ዘመናዊውንም ትምህርት በሀገራችን ከማስፋፋት የቦዘነችበት ጊዜ የለም።
በሀራችን በኢትዮጵያ ዘመናዊ ትምህርት በማይታወቅበት ጊዜ እንኳን ቤተክርስቲያን መንፈሳዊ ትምህርቷን በአስደናቂ መልኩ ቀርጻ ከፍልስፍና (ከዘመናዊ ጥበብ) ጋር ጐን ለጐን ስታስተምር ቆይታለች።ከዚህም በተጨማሪ ለሀገርና ለአህጉር መኩሪያ የሆነ ብቁ ፊደል ቀርጻ ማስረከቧ ሳያንሳት የፊደላቱን ምሥጢር፣ መልክና ቅርጽ በማስለየት እስከዛሬ ድረስ ግንባር ቀደም ሚና እየተጫወተች ነው።ይህን ሁሉ የመረመረ ሰው ቤተ ክርስቲያን ለመንፈሳዊ ትምህርት ብቻ ሳይሆን ለሥጋዊ ትምህርት መሠረት መሆኗን ለማወቅ አይቸገርም፡፡
ሕንፃ ከማነጽ፣ ፍትሕት ከመፍታት፣ ከማጥመቅ፣ ከመቀደስ ይልቅ ቀዳሚው የቤተ ክርስቲያን ተልዕኮ ማስተማር ነው:: ማስተማርና ማሳመን ከሌለ እነዚህ ምሥጢራት በሙሉ ላላመነ ሰው የሚፈጸሙ አይደሉምና፡፡ እንዲያውም ቤተ ክርስቲያን የተመሠረተችው በትምህርተ ወንጌል ነው። «ሊቀ ማኅበር» የሚባል ኢየሱስ ክርስቶስ ሁለትም ሦስትም ሆነን በምንሰበሰብበት ጊዜ በመካከላችን ይገኛል፡፡ «ያዘዝኋችሁንም እንዲጠብቁ እያስተማራችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው እነሆም እኔ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ሁል ጊዜ ከእናንተ ጋር ነኝ» ማቴ28፥20፤18፥20 በማለት ከቃል ኪዳን ጋራ ቤተ ክርስቲያን በትምህርተ ወንጌል እንድትመሠረት የፈቀደ ራሱ ነውና፡፡
ስለዚህ ቤተ ክርስቲያን ማስተማር የዘወትር ሥራዋ ነው፡፡ ትምህርቷም የሕይወት ትምህርት ነው።ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ «እናት አባት ልጆቻቸውን የእነርሱ ለማድረግ ቢፈልጉ ለቤተ ክርስቲያን ይስጡ፡፡ ከደግ በቀር ክፉ ነገር አታስተምራቸውምና፡፡›› በማለት የቤተ ክርስቲያን ትምህርት ለልጆች ያለውን ጠቀሜታ አስረድቷል፡፡
የትምህርተ ወንጌልን አገልግሎት ቸል በማለት ለሌሎች መንፈሳዊ አገልግሎቶች ቅድሚያ የሚሰጡ የቤተ ክርስቲያን አካላት ቢኖሩ ዋናውን ጉዳይ ቸል ስላሉ ከዚህ ቀጥሎ ባለው የወንጌል ቃል ይገሠጻ።«በሕግ ያለውን ዋና ነገር ስለምትተዉ፡ ወዮላችሁ፤ ሌላውን ሳትተዉ ይህንን ልታደርጉ ይገባችሁ ነበር፡፡ እናንተ ዕውሮች መሪዎች ፡ ትንኝን የምታጠሩ ግመልንም የምትውጡ፡፡» ማቴ 23፥23
ዋናው የቤተ ክርስቲያን ተልዕኮ መንፈሳዊ ትምህርት ማስተማር ነውና።
ከቤተ ክርስቲያን ባሻገር ወላጆች ልጆቻቸውን «በተግሣጽና በምክር» የማሳደግ ኃላፊነት አለባቸው፡፡ ኤፌ6፥4 ሠለስቱ ምዕትም በሃይማኖተ አበው «ለልጆችህ አርምሞንና ጸጥታን አስተምራቸው፤ ሰነፍ አትሁን።›› በማለት ወላጆችን መክረዋል፡፡ ልጆቻችውን የማያስተምሩ ወላጆች ቅጣት እንደሚገባቸው ቅዱስ ባስልዮስ «ልጆችን መልካም ትምህርት ከማስተማር ቸል የሚሉ ወላጆች በሌላ በኩል ለልጆቻቸው ደግ ቢሆኑ በዚህ ብቻ ሊቀጡ ያስፈልጋቸዋል» በማለት ተናግሯል፡፡ አስቀድሞ እንደተገለጸው ሥጋዊና መንፈሳዊ ጥበባት በምድሪራችን ይገኛሉ፡፡ ሁለቱም በአቀራረባቸው፣ በዓላማቸውና በሚሰጡት ጠቀሜታ እጅግ ይለያያሉ። አንዳንድ ጊዜ የሚስማሙበት የጋራ ነጥብ ሲኖራቸው ብዙ ጊዜ ደግሞ እጅግ የሚቃረኑበት ቦታ አለ።ታዲያ ሰው አስቀድሞ መማር የሚኖርበት የትኛውን ትምህርት ነው?

ቀጣይ ምዕራፍ ዐሥር ክፍል ኹለት:
👉 «የትኛው ይቅደም»
👉«በሚገባ መማር»
👉«የትምህርት ጥቅም»
በሚል ይቀጥላል .....
ለጥያቄና አስተያየት @Ethiopian_Orthodox_bot ተጠቀሙ።

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

ረ ሊያጠፋው ምክንያት ይፈልግበት ነበር፡፡ ለዐፄ ገብረ ማርያም በእናትም በአባትም እኅት የምትሆነው ለላሊበላ ግን በአባት ብቻ እኅት የሆነችው ዮዲት ላሊበላን ለመግደል በማሰብ ቀን ከሌሊት አጋጣሚን ትጠብቅ ነበር፡፡ ቅዱስ ላሊበላም ጌታችን መራራ ሐሞት መጠጣቱንም እያሰበ ሁልጊዜ ዓርብ ዓርብ ከጾምና ጸሎት በኋላ መራራ ኮሶ ይጠጣ ነበርና ይህን አጋጣሚ በመጠቀም አንድ ቀን እንደጠማው አውቃ በጠላ ውስጥ መርዝ ጨምራ ሰጠችው፤ ቅዱስ ላሊበላም መርዝ የተቀላቀለበትን ጠላ ጠጣው፡፡ እርሱ ከመጠጣቱ በፊት ያገለግለው የነበረው ዲያቆን ቀምሶት ወዲያው ሲሞት አየ፡፡ ዲያቆኑ ያስመለሰውን የጠጣው ውሻም ወዲያው ሞተ፡፡ ቅዱስ ላሊበላም ይህን ሲመለከት በሐዘንና በፍጹም ፍቅር ሆኖ ‹‹አገልጋዬ ለእኔ የተዘጋጀውን መርዝ ጠጥቶ እንደሞተ ሁሉ እኔም መሞት ይገባኛል›› በማለት ያን መርዝ ስለወዳጁ ፍቅር ሲል ጠጥቶ ለመሞት ቆረጠና ጠጣው፡፡ ጌታችን በወንጌሉ ስለራሱ ‹‹ስለ በጐቹ ቤዛ ነፍሱን ለሞት አሳልፎ የሚሠጥ ከዚህ የሚበልጥ ፍቅር የለም›› (ዮሐ 15፡13) ብሎ የተናገረውን ቃል ቅዱስ ላሊበላም ስለ ወዳጁ ሞት ሲል ራሱን ለሞት አሳልፎ ሰጠ፡፡ ነገር ግን መርዙ እንኳን ሊጎዳው ይቅርና በሆዱ ውስጥ ከልጅነቱ ጀምሮ የነበረበትን የሆድ ሕመም ነቅሎ አወጣለት፡፡ በዚህም ጌታችን በወንጌሉ ‹‹የሚገድል መርዝም ብትጠጡ ምንም አትሆኑም›› (ማር 16፡18) ያለው ቃል ተፈጽሞለታል፡፡ መርዙ ለበጐ ሆኖለት ከሆዱም ውስጥ የነበረው ጥፍሮች ያሉት አውሬ መሰል ፍጡር ወጣለትና የሆድ ሕማሙ ፈጽሞ ተወው፡፡ ያን ጊዜም ቅዱስ ላሊበላ በወቅቱ ለሦስት ቀንም ያህል እንደሞተ ሆኖ የቆየ ቢመስልም ቅዱስ ገብርኤል ግን በመንፈስ ወደ ሰማይ ነጥቆ ወስዶ ሰባቱ ሰማያትን ያሳየው ሲሆን በጌታችን ፊትም አቅርቦት አስባርኮታል፡፡ ጌታችንም ቅብዓ መንግሥት ቀብቶት ትልቅ ቃልኪዳን ሰጥቶታል፡፡
ጻዲቁ ንጉሥ ቅዱስ ላሊበላ ቅድስናን ከንግሥና፣ ክህነትን ከንጽሕና፣ ጥበብ መንፈሳዊን ከጥበብ ሥጋዊ ጋር አንድ አድርጐ አስተባብሮ የያዘ በመንፈስ ቅዱስ የሚመራ፣ ቅዱሳን መላእክትም ይራዱት እንደነበርና ጌታችንም ትልቅ ቃልኪዳን እንደሰጠው ከቅዱስ ገድሉ ላይ እናገኛለን፡፡ ከጌታችን ዘንድ የተሰጠውንም ቃልኪዳን በሦስት ከፍሎ ማየት ይቻላል፡፡ በዚህም መሠረት፡-
1ኛ. መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ቅዱስ ላሊበላን እየመራው ከላስታ ወደ አክሱም ከዚያም ወደ ኢየሩሳሌም አድርሶ በዚያ የሚገኙትን ቅዱሳት መካናት ሁሉንም ካሳየው በኋላ ‹‹ወደ ሀገርህ ሮሐ ተመልሰህ በእነዚህ ምሳሌ ታንጻለህ›› ብሎታል፡፡ ወደ ሀገሩም ተመልሶ በአሽተን ማርያም ተራራ ላይ ሱባኤ ይዞ በጾም ጸሎት ተወስኖ ሳለ እግዚአብሔር የሚሠራቸውን መቅደሶች በግልጽ በራእይ አሳይቶታል፡፡

2ኛ. ከላይ እንዳየነው ለሞት ተብሎ የተሰጠው መርዝ ለሕይወት ሆኖለት በመሬት ላይ ወድቆ ሳለ በነፍስ መልአክ ነጥቆት እስከ ሰባተኛው ሰማይ ጽርሐ አርያም ድረስ ደርሶ በጌታ ፊት ቀርቦ ከጌታ ዘንድ ‹‹እኔ አከበርኩህ ቃሌ አይታበይም፣ ከአንድ ቋጥኝ እነዚያን በራእይ ያሳየሁህን አብያተ ክርስቲያናት ታንጻለህ›› የሚል ቃልኪዳን ተቀብሏል፡፡

3ኛ. ከኢየሩሳሌምም ተመልሶ የንግሥናውን ዙፋን ከቅዱስ ገብረ ማርያም ከተረከበ በኋላ በተሰጠው መንፈሳዊ ሀብትና ባየው ራእይ መሠረት አብያተ ክርስቲያናቱን አንጾ ከጨረሰ በኋላ በቀኝና በግራው ዓሥር ዓሥር ኪሎ የሚመዝን የዓለት ድንጋይ ተሸክሞ ለ7 ዓመት ሲጾም ሲጸልይ ጌታችን ተገልጦለት ‹‹…ያነጽካቸውን ቤተ መቅደሶች የተሳለመውን ኢየሩሳሌምን እንደተሳለመ አድርግለታለሁ›› የሚለውን የመጨረሻውን ቃልኪዳን ሰጥቶታል፡፡ (ይህን ቃልኪዳኑን መጨረሻ ላይ በዝርዝር እናየዋለን) እነዚህን ሦስት ዋና ዋና ቃልኪዳኖቹን በቅድሚያ ማንሳት የፈለኩበት ምክንያት ቀደም ብዬ እንደጠቀስኩት ስለ ቅዱስ ላሊበላ ድንቅ ሥራዎች ከማሰባችንም ሆነ ከመናገችን በፊት በቅድሚያ ስለ ራሱ ስለ ቅዱስ ላሊበላ የቅድስና ሕይወቱና ከእግዚአብሔር ጋር የነበረውን ግንኙነት ማወቁ የግድ አስፈላጊ መሆኑን ለመጠቆም ነው፡፡ አሁን አሁን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ሆን ተብሎ በማወቅም ይሁን ባለማወቅ ውቅር አብያተ ክርስቲያናቶቹ በቱሪስት መስህብነታቸው ብቻ እየታዩ የቅድስና ታሪካችንም እየተጨፈለቀና መንፈሳዊ እሴቶቻችንንም ለማጥፋትም ጥረት እየተደረገ ስለሆነ እውነተኛውን ነገር በደንብ ማወቅና በእጅጉ መጠንቀቅ ስላለብን ነው ይህን የማነሳው፡፡ ስለዚህ የቅዱስ ላለበላን የቅድስና ሕይወትና ከእግዚአብሔር ጋር የነበረውን ግንኙነት ስንረዳ እነዚያ እጅግ ድንቅ የሆኑ ሥራዎቹ በመንፈስ ቅዱስ ኃይልና በሰማያውያን መላእክት እርዳታ የተሠሩ መሆናቸውን እንረዳለን፤ እግዚአብሔርም ለእኛ የሰጠንን ድንቅ የምሕረትና የቃልኪዳን ስጦታዎቻችን መሆናቸውን እንረዳለን፡፡ ያንጊዜም ውቅር አብያተ ክርስቲያናቶቹን ዓለም ከሚመለከትበት የተለየ መንፈሳዊ ዐይን ይኖረናል፡፡ የቃልኪዳኑም ተጠቃሚዎች ለመሆን መንፈሳችን ይነሳሳል፡፡ በዚህ ደግሞ አሁን ያለውም ሆነ ወደፊት የሚመጣው ትውልድ ታሪኩን ከማጉደፍና ከጥፋት ይጠበቃል፣ አኩሪ ታሪኩንም ጠንቅቆ ለማወቅ መንፈሳዊ ቅናትም ስለሚያድርበት ራሱንም ከውጪው የባሕል ወረራና ጥቃት ይጠብቃል፡፡ በሀገራችን ያሉትን እጅግ ጥልቅ የሆኑ ሃይማኖታዊና ባሕላዊ ምሥጢሮችን ጠንቅቀው የተረዱት እነ ፕሮፌሰር ፓንክረስት ‹‹ክርስቶስ ከነጮች ይልቅ ለኢትዮጵያውያን ቅርበት አለው›› በማለት ምስክርነታቸውን እየሰጡ ባለበት ወቅት የዘመኑ የሀገራችን ወጣት ማንነቱን ጠንቅቆ ቢያውቀው ኖሮ የእነርሱን (የነጮቹን) ባሕል ለመከተል ባልዳዳው ከዘመናዊ ባርነትም ራሱን በጠበቀ ነበር፡፡

4.መድኃኔዓለም ክርስቶስ ለቅዱስ ላሊበላ ስለ ቤተመቅደሶቹ አሠራር በዝርዝር እንዳስረዳው፡- በተራ ቁጥር ሁለት ላይ ለመጥቀስ እንደተሞከረው በቅዱስ ገድሉ ላይ ከገጽ 117-127 ድረስ በጣም በስፋትና በዝርዝር እንደተጠቀሰው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱስ ላሊበላን እስከ ሰባተኛው ሰማይ ድረስ በመላእክት ተነጥቆ በፊቱ እንዲቆም ካደረገው በኋላ ቤተ መቅደሶቹን እንዴት እንደሚያንጽ ቃል በቃል ነግሮታል፡፡ እግዚአብሔር ለኖህ መርከቡን እንዴት እንደሚሠራ ከነልኬቱ ጭምር በዝርዝር እንደነገረው ሁሉ ለቅዱስ ላሊበላም ዝርዝር ሁኔታዎችን ጭምር እንዲህ በማለት ትእዛዝ ሰጥቶታል፡- ‹‹መልአኩም ክብሩ ከሰማያት ሁሉ ክብር ወደሚበልጥ ወደ ሰባተኛው ሰማይ አደረሰው፣ ቅዱስ ላሊበላም ይህንን አይቶ በግንባሩ ተደፋ፣ ከኪሩቤል ዘንድ ይነሳ የሚል ቃል ተሰማና አንዱ ሱራፌል መጥቶ አነሣው፡፡ ልቡንም አጽንቶ አቆመው…እግዚአብሔርም ተናገረው፡- ‹በምድር ላይ ቤተመቅደስ ትሠራልኝ ዘንድ የማሳይህን አስተውል፤ እዝነ ልቡናህንም ግለጥ፡፡ ከሰው ጋር ስለምኖር በሰማያት የምትኖር አባታችን እያሉ ከሚጠሩኝ በሃይማኖት ከተጐናፀፈኝ ስሜን ከሚያመሰግኑ ከመረጥኳቸው ከሕዝብ አንደበት በምመሰገንበት ገንዘብ እኔ ፈጥሬያቸዋለሁና፡፡

ከመጀመሪያይቱ ድንኳን ውስጥ በተሣለው ላይ ምስላቸው የተሠራ ከሚንቀሳቀሱ ከኪሩቤል አምሳል ለሙሴ እንደተናገርኩት አይደለም፡፡ ወዳጄ ሙሴ የመጀመሪያይቱን ድንኳን አርአያ በደብረ ሲና እንዳሳየሁት ድንኳንን እንደሠራ ሁሉ እንደሁ አንተም እንዳሳየሁህ ትሠራ ዘንድ ዕወቅ፣ አስተውል፣ ተጠንቀቅም፡፡ የማሳይህ ግን ለሙሴ እንዳሳየሁት አይደለም፤ መቅደሴን የምትሠራልኝም ሙሴ እንደሠራው አይደለም፤ ሙሴስ ከተፈተለ ልብስና ከእንጨት ድንኳን ሠራ፤ አንተ ግን ለምሰሶውም ሆነ ለመቀኑ ለመድረኩ እንጨትን

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

ነዋ ሚካኤል መልአከ ክሙ
ይስአል ለክሙ በእንተ ምሕረት
በዘማሪት መቅደስ ከበደ

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

ን ዳግመኛ ትዳር ላለመመሥረት ቃል ኪዳን እንደገባች ርግብንና ዖፈ መንጢጥን አብነት አድርጋ እነርሱ እንኳ በሕይወት ዘመናቸው ከአንድ ባል ውጪ ሌላ ባል እንደማያውቁ በመጥቀስ አሳቡን እንደማትቀበለው ገለጸችለት፡፡ ሰይጣንም አስመሳይ መሆኑ አላዋጣ ሲለው ማንነቱን ቀይሮ ሊያንቃት ቢሞክር የእግዚአብሔርንና የቅዱስ ሚካኤልን ስም ጠርታ አባረረችው፡፡ እርሱም ተመልሶ መጥቶ እንደሚያጠፋት ዝቶባት እንደአቧራ በኖ እንደ ጢስም ተኖ ጠፋ፡፡

በሰኔ ፲፪ ቀን የቅዱስ ሚካኤልን መታሰቢያ እያዘጋጀች ሳለች ሰይጣን ብርሃናዊ መልአክ መስሎ መጣ፡፡ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል እንደሆነ ገልጾ የመጀመሪያውን የመሰለ ከንቱ ምክሩን አሰማምሮ አቀረበላት፡፡ አሳቡንም የእግዚአብሔር ፈቃድና አሳብ እንደሆነ አድርጎ ለማሳመን ሞከረ፡፡ ሰይጣን አስቀድሞ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በገዳመ ቆሮንቶስ መጻሕፍትን እየጠቀሰ እንደተፈታተነው ሁሉ ቅድስት አፎምያንም ለማሳመንም አብርሃምን፣ ይስሐቅን፣ ያዕቆብን፣ ዳዊትን የመሳሰሉ ደጋግ አባቶችን ታሪክ እየጠቀሰ ወደ ትዳር እንድትገባ ደጋግሞ ወተወታት፡፡ ቅድስት አፎምያም በእግዚአብሔር ኃይል ጸንታ በቅዱስ ሚካኤልም ተራዳኢነት ታምና "የእግዚአብሔር መልአክ ከሆንክ መንፈሳዊ ማረጋገጫህ የሆነው የመስቀል ምልክት የታለ?" በማለት በምድራዊ ንጉሥና በጭፍራው መካከል የሚኖርን የጋራ መግባቢያ መንገድ ዋቢ አድርጋ ጠየቀችው፡፡ ለጊዜው "በእኛ በመላእክት ዘንድ እንዲህ አይደለም" ብሎ ሊሸነግላትና አቋሟን ሊያስቀይራት ሞከረ፡፡ ከቤቷ ያለ የቅዱስ ሚካኤል ሥዕል ላይ ያለውን ምልክት አብራርታ የእርሱ ግን ከዛ ጋር አንድነት እንደሌለው አረጋገጠችበት፡፡ በመቀጠልም ከቤቷ ላለው ለቅዱስ ሚካኤል ሥዕል እጅ እንዲነሣ ጠየቀችው፡፡ በዚህ ጊዜ መልኩ ወደ ትክክለኛ ሰይጣናዊ ማንነቱ ተለወጠና ጨለማ ለብሶ እየዛተ አነቃት፡፡ ቅድስት አፎምያም የከበረ መልአክ ቅዱስ ሚካኤልን "ድረስልኝ" እያለች በጠራችው ጊዜ መልአኩም ፈጥኖ በመድረስ ከሰይጣን እጅ አዳናት፡፡

የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤልም ለሰይጣኑ ተገቢውን ቅጣት ሰጥቶ ቅድስት አፎምያን ባረካት፡፡ የዕረፍት ቀኗ በዚህ ቀን መሆኑን ነግሮ ቤቷን እንድታዘጋጅ አዘዛት፡፡ የበዓሉን ዝግጅት አከናውና ሥጋ ወደሙን ተቀብላ ኤጲስ ቆጶሱንና ካህናቱን እንደየመዓርጋቸው ጠርታ በቤቷ አክብራ ተቀበለቻቸው፡፡ ለነዳያንና ለጾም አዳሪዎች በኤጲስ ቆጶሱና በካህናቱ እጅ ገንዘቧን መጽውታ መንገዷን አሳመረች፡፡ ስለ ኃጢአቷ እንዲጸልዩላት ተማፅና በፊታቸው ተንበርክካ ጸለየች፡፡ ባሏ ያሠራላትን የቅዱስ ሚካኤልን ሥዕል አቅፋ ስማ ከተማጸነች በኋላ ሰኔ ፲፪ ቀን በሰላም ዐረፈች፡፡

ምልጣን ዘሰኔ ሚካኤል
አመ ይሰቅልዎ አይሁድ ለእግዚእነ፤
ሚካኤል አርመመ ወገብርኤል ተደመ፤
ፀሐይ ፀልመ ወወርኅ ደመ ኮነ፤
ወሪዶ እመስቀሉ አብርሃ ለኵሉ፤

ትርጉም

አይሁድ ጌታችንን በሰቀሉት ጊዜ
ሚካኤል ዝም አለ ገብርኤልም ተደነቀ
ፀሐይ ጨለመ ጨረቃ ደም ኾነ
ከመስቀሉ ወርዶ ለኹሉ አበራ።
ቅዱስ ያሬድ

ከበዓሉ በረከትን ያሳትፈን
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

ሰኔ ፲፪
የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል አፎምያን ያዳነበት ዕለት ነው፡፡ ዳገመኛም ይኽች ዕለት የባሕራንን የሞት ደብዳቤ ቀዶ እርሱን ለታላቅ ክብር ያበቃባት ዕለት ናት፡፡

ሚካኤል ማለት በዕብራይስጥ ቋንቋ ሚ-መኑ' ካ-ከመ' ኤል- አምላክ ማለት ሲሆን በአንድነት ሲነበብ መኑ ከመ አምላክ (እንደ እግዚአብሔር ያለ ማን ነው) ማለት ነው፡፡ አንድም ለእግዚአብሔር አሸናፊ ድል አድራጊ የቸርነትና የርህራሄ መገኛ መዝገብ ማለት ነው፡፡

ይህ ታላቅ መልአክ ዮሐንስ ወንጌላዊ በራዕዩ ‹‹በእግዚአብሔር ፊት የሚቆሙትን ሰባቱን መላእክት አየሁ›› ብሎ ከተናገረላቸው መላእክት ውስጥ የሚመደብ ሲሆን የሰባቱም ሊቃነ መላእክት አለቃ እንዲሆን እግዚአብሔር መርጦ ሹሞታል፡፡ ይህ ታላቅ መልአክ ያደረጋቸው የሠራቸው እጅግ ብዙ የሆኑ ተአምራት አሉት፡፡ ስለዚህ ስለ ታላቁ መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ክብር፤ ጠባቂነትና አማላጅነት ከአባቶቻቸው የተማሩትን በኑሮአቸው ያዩትን አባቶቻችን ጽፈዋል፡፡ ስለ ቅዱስ ሚካኤል ከጻፉት አባቶች መካከል የተወሰኑትን ለመጥቀስ ያክል፡- ዮሐንስ አፈወርቅ፣ ኤዎስጣቴዎስ ዘአንፆኪያ፣ ቅዱስ መቃርዮስ፣ ቅዱስ ያሬድ፣ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ እና የእስክንድርያው ሊቀ ጳጳስ አባዲማቴዎስ ናቸው፡፡ እኛም የአባቶቻችንን አንደበት አንደበታችን አድርገን በኅዳር ፲፪ ክቡር ገናና የሆነ ቅዱስ ሚካኤል ካደረጋቸውና ከሠራቸው ብዙ ተአምራት ውስጥ የተወሰኑትን በመልአኩ ተረዳኢነት እንዲህ ብለን እንናገራለን አንጽፋለን፡፡
ጥንተ ነገሩ እንዲህ ነው፡- ንግስት ክሌዎፓትራ ‹‹ሳተርን›› ለሚባለው ጣዖት የሠራችው ቤተ ጣዖት በእስክንድርያ ነበር፡፡ ይህ ቤተ ጣዖት እስከ እስክንድርያው ፓትርያርክ እለ እስክንድሮስ /፫፻፲፪ - ፫፻፳፮/ ዘመን ድረስ ነበር፡፡ እለ እስክንድሮስ ሊያጠፋው ሲነሣ ሕዝቡ ከልቡ ገና የአምልኮ ጣዖት ስላልጣፋ "፲፰ ፓትርያርኮች ያልነኩትን አንተ ለምን ታፈርስብናለህ?" ብለው ተቃወሙት፡፡ እለ እስክንድሮስም ሕዝቡን መክሮና አስተምሮ የሳተርን በዓል ይውልበት በነበረው ዕለት የቅዱስ ሚካኤልን በዓል እንዲያከብሩ አውጆ ቤተ ጣዖቱንም በቅዱስ ሚካኤል ስም ሰይሞ ቤተክርስቲያን አደረገው፡፡

ሕዝቡ በየዓመቱ መሥዋዕት እየሠው ተረፈ መሥዋዕቱን እየተመገቡ እየዘፈኑ እያጨበጨቡ ያከብሩ ነበር፡፡ ታላቁ ጻድቅ ንጉሥ ቁስጠንጢኖስ "አብያተ ጣዖታት ይዘጉ አብያተ ክርስቲያናት ይከፈቱ" ብሎ ካወጀ በኋላ ሊቀ ጳጳሳት እለ እስክንድሮስ ቤተ ጣዖቱን አፍርሶ ከቦታው ላይ ቤተ ክርስቲያን ሠርቶ ታቦተ ሚካኤልን አግብቶ በዓሉን በደስታ በሐሴት አሳለፉት፡፡ እለ እስክንድሮስም ሕዝቡን የጣዖቱን በዓል ተው "ይህን የመላእክት አለቃ የቅዱስ ሚካኤልን በዓል አክብሩ" ብሎ በየዓመቱ በዚህ ቀን በዓል እንዲሆን ሥርዓት ሠራላቸው፡፡ ይህንንም የቅዱስ ሚካኤልን በዓል ከሚያከብሩ ምእመናንን አንዱ የባሕራን አባት ነበር፡፡
እርሱም እግዚአብሔርን እጅግ አድርጐ የሚፈራ ወር በገባ በየዐሥራ ሁለቱ ቀን የቅዱስ ሚካኤልን ዝክሩን የሚዘክርና ይልቁንም በኅዳር ዓሥራ ሁለትና በሰኔ ዓሥራ ሁለት ቀን በታላቅ ክብር የሚያከብር አንድ ሰው ነበር። ለዚህ እግዚአብሔርን ለሚፈራ ሰውም ርኅራኄ የሌለው በእርሱም ላይ ጥላቻ ያደረበት አንድ በለጸጋ ጐረቤት ነበረው፡፡ የቅዱስ ሚካኤልን በዓል በሚያከብርበት ጊዜ ሁሉ ይዘብትበት ይሳለቅበት ነበር። ይህ እግዚአብሔርን ለሚፈራ ሰውዬ በዚህ ዓይነት በጐ ሥራ ብዙ ጊዜ ከኖረ በኋላ ከዚህ ዓለም ድካም ያርፍ ዘንድ የሞቱ ጊዜ ቀረበ። ሚስቱንም ጠርቶ "በጐ ስራ ከመሥራት ለድኃ ከመመጽወት ቸል አትበይ የቅዱስ ሚካኤልንም በዓል በየወሩ ከማክበር አትቦዝኝ ይልቁንም በኅዳር ዓሥራ ሁለትና በሰኔ ዓሥራ ሁለት ቀን ከፍ ባለ ሥነ ሥርዓት እንድታከብሪ አደራ እልሻለው" አላት፡፡ በሚሞትበትም ጊዜ ሚስቱ ፀንሳ ነበር። ይህም ደገኛ ሰው በሰላም ዐረፈና ፍጹም መንግሥተ ሰማያትን ወረሰ።

ከዚህም በኋላ ሚስቱ የመውለጃዋ ጊዜ ተቃርቦ ነበርና ምጥ ይዟት በታላቅ ጭንቅ ላይ እንዳለች "አንተ የእግዚአብሔር መልአክ ሆይ በእኔ ላይ ይቅርታን አውርድ ከዝህ ከደረሰብኝም ጭንቅ ይገላግለኝ ዘንድ ስለኔ እግዚአብሔርን ለምንልኝ አንተ ከእግዚአብሔር ዘንድ ታላቅ ባለሟልነት ተሰጥቶሃልና" እያለች ለመነች። ይህንንም በምትልበት ጊዜ ያለችበት ቤት በብርሃን ተመላ ከጭንቋም ዳነችና መልኩ በጣም ያማረ ልጅ ወለደች። የእግዚአብሔር መልእክተኛ ቅዱስ ሚካኤልም ከሰማይ ወርዶ ያን ሕፃን ባረከውና "ቸርነት ርኅራኄ የሌለውን የዚህን ባለጸጋ ገንዘብና ሀብት እርሻውንም ሁሉ ይህ ሕፃን እንዲወርስ እግዚአብሔር አዟል" አለ። ያን ጊዜ ያ ባለጸጋ በሴትዮዋ ቤት መስኮት አጠገብ ሆኖ ሁኔታውን ሁሉ ይመለከት ነበርና ይህን ነገር በሰማ ጊዜ ልቡ በታላቅ ኅዘን ተነካ፤ ሕፃኑንም የሚገድልበትን ምክንያት ይፈልግ ጀመር፡፡ ነገር ግን እግዚአብሔር በቅዱስ ሚካኤል ጸሎት ብላቴናውን ከክፉ ነገር ሁሉ ይጠብቀው ነበር።

ብላቴናውም ዓሥር ዓመት በሆነው ጊዜ እናቱ በጣም ችግር ፀናባት፡፡ በዚህን ጊዜ እምነት የጐደለው ያ ባለጸጋ "አንቺ ችግረኛ ስለሆንሽ ይላከኝ ያገለግለኝ ዘንድ ልጅሽን ስጭኝና ምግቡንና ልብሱን ምንም ሳላጐድል ተንከባክቤ አኖረዋለው ለአንቺም ሃያ ወቄት ወርቅ እሰጥሻለው" አላት። ይህንንም ባላት ጊዜ ስለ ችግሯ በጣም በመደሰት ልጅዋን ሰጠችውና ሃያውን ወቄት ወርቅ ተቀበለች፡፡ ብላቴናውንም በወሰደ ጊዜ እንግዲህ ሃሳቤ ሁሉ ዛሬ ተፈጸመልኝ እያለ በጣም ደስታ ተሰማው፡፡ ከዚህ በኋላ በልጅ ቁመት ልክ ሳጥን አሠርቶ ሕፃኑን በሣጥኑ ውስጥ አግብቶ በላዩ ላይ ቆለፈበትና ሣጥኑን ወስዶ ከባሕር ጨመረው፤ እንዲሁም የሣጥኑን ቁልፍ መክፈቻ አብሮ ወረወረው። ነገር ግን በእግዚአብሔር ፈቃድ ያ ሣጥን ሳይሰጥም በባሕሩ ላይ እየተንሳፈፈ ከዚያች አገር ርቃ ወደምትገኝ የባሕር ወደብ ደረሰ።
በባሕሩ አካባቢ በጎቹን አሰማርቶ የሚጠብቅ አንድ ሰው ነበርና ያንን ሣጥን ባየው ጊዜ ከባሕሩ አወጣውና ወደ ቤቱ ወሰደው። እቤቱም በደረሰ ጊዜ "ይህን ሣጥን በምን እከፍተዋለሁ?" እያለ ሲያወጣ ሲያወርድ ተመልሶ ወደ ባሕሩ ይሄድ ዘንድ እግዚአብሔር አሳሰበው፤ በሄደም ጊዜ አንድ ዓሣ የሚያጠምድ ሰው አገኘና ዓሣ አጥማጁን "በኔ ስም መረብህን ወደ በሕር ጣልና የተሠገረው ዓሣ ለኔ ይሆናል ዋጋውን ግን እከፍልሃለው" አለው፡፡ ዓሣ አሥጋሪውም እንደ ተነጋገሩት መረብን ከባሕር ቢጥል ታላቅ ዓሣ ተያዘና ለሰውየው ሰጥቶት ዋጋውን ተቀበለ። እሱም ያንን ዓሣ ከቤተሰቦቹ ጋር ጠብሶ ይበላ ዘንድ በችኮላ ወደ ቤቱ ሄደና ያሣውን ሆድ ቢሰነጥቀው የዚያን የሣጥን ቁልፍ መክፈቻ አገኘ፡፡ በዚያን ጊዜ ይህ መክፈቻ የዚህ ሣጥን ቁልፍ መክፈቻ መሆን አለበት ሲል አሰበና ቁልፉን ለመክፈት ቢሞክር ወለል ብሎ ተከፈተ። በዚህም እየተደነቀ ሳለ ሣጥኑን ቢከፍተው ያ ባለ ፀጋ ሊገድለው ያሰበውን ሕፃን በሣጥኑ ውስጥ አገኘው። ባየውም ጊዜ እጅግ ተደስቶ በባሕር ውስጥ ስላገኘው ስሙን "ባሕራን" ብሎ ሰየመውና እንደ ልጁ አድርጐ ይንከባከበው ዘንድ ወሰነ፡፡
ከባሕራን ሀገር የበግ ጠባቂው አገር የዓሥር ቀን ጐዳና የሚያስኬድ ርቀት ነበረው። ከብዙ ዓመታት በኋላ ያ ባለ ጸጋ ሰው ለንግድ ከሀገሩ ወጣ፡፡ በጉዞውም ላይ ሳለ ፀሐይ ስትገባ ከዚያ የበግ ጠባቂው ዘንድ ደረሰ። በግ ጠባቂውንም "ወንድሜ ሆይ ባንተ ዘንድ የማድርበት ቢኖር ታሳድረኝ ዘንድ እለምንሃለው፣ ኪራዩንም እከፍልሃለው" ብሎ ጠየቀውና ያ በግ ጠባቂ ወደ ቤቱ አስገባው። ባለጸጋውም ገብቶ ጥቂት ካረ

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

ጠቃሚ ነገር በልክ ተምሮ መሥራት ነው፡፡ ብዙ ተምረው ምንም ሳይሠሩ ሕይወታቸው የሚያልፍ ሰዎች ቁጥር ጥቂት አይደለም፡፡ ስለዚህ ትምህርትን መመጠን ነገር ግን ሥራን ማብዛት ይገባል፡ ጠቢቡ ሰሎሞን «ብዙ መጻሕፍትን ማድረግ ፍጻሜ የለውም ፥ እጅግም ምርምር ሰውነትን ያደክማል›› በማለት የተናገረው ሰው የሚጠቀመው ብዙ በመማሩ ሳይሆን በልክ ተምሮ ብዙ ሲሠራ መሆኑን ለመጠቆም ብሎ ነው፡፡ መክ12፥12 በተጨማሪም ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በልክ ስለመኖር የሰጠው ምክር በልክ ስለ መማርም ሊጠቀስ ይችላል፡፡ 2ጢም4፥5
መንፈሳዊያን ሰዎች መንፈሳዊ ትምህርት ቤትን እንደ መካነ ገድል (ገድል መፈጸሚያ ቦታ) በመቁጠር መላ ዘመናቸውን በትምህርት ቤት ለማሳለፍ ይወስናሉ፡፡ ይህ ድርጊት የዓለምን ጥቀርሻ ሳይቀቡና ከዓለም ምንም ሳይፈልጉ ለመኖር የሚወሰን የምናኔ ኑሮ በመሆኑ ጊዜን እንደ ማባከን አይቆጠርም፡፡ ታውቆ የተወሰነ ውሳኔ በመሆኑም ምንም ዓይነት ጸጸት አያስከትልም፡
ሆኖም እንዲህ ያለ የምናኔ ሐሳብ የሌላቸው ሰዎች በመንፈሳዊ ትምህርትም ላይ ቢሆን ያለ አግባብ ጊዜ ማጥፋት የለባቸውም፡፡ ብዙ ተምሮ ምንም ሳያገለግሉ፣ የሚሹትንም ሳያገኙ እየተቆጩጬ ኖረው ከመሞት በመጠኑ ተምሮ የተማሩትንም በአግባቡ ተጠቅመውበት ማለፍ ይመረጣል፡፡ ቤተ ክርስቲያን ሕይወት የሚገኝበትን ጥልቅ መንፈሳዊ ትምህርቷን ለሰው ሁሉ እንዲዳረስ የበለጠ ጥረት ማድረግ አለባት።
እግረ መንገዴንም ሳልጠቁም የማላልፈው ነገር ቢኖር የሚመለከታቸው አካላት በሙሉ ቢያስቡበት ሰፋ ያለ ጊዜ የሚጠይቁት የንባብ፣የቅዳሴ፣ የዜማ፣ የአቋቋም፣ የቅኔና የመጻሕፍት ትርጓሜ ትምህርቶቿ አሁን ከሚወስዱት እጅግ በጣም ባነሰ ጊዜ ውስጥ መጠቃለል የሚችሉ መሆናቸውን ነው፡፡እስከሚሆን ድረስ ደግሞ የመንፈሳዊ ትምህርት ጥማት ያለባቸው ምእመናን ሁኔታዎች እስከ ፈቀዱላቸው ድረስ በግላቸውም ቢሆን እንኳን ትምህርተ ቤተ ክርስቲያንን ከማጥናት መቦዘን የለባቸውምደ
2) ሰው ምንም ቢማር ራሱን እንደ አዋቂ መቁጠር አይገባውም፡፡ አዋቂ እንደ ሆነ የሚሰማው ሰው በትዕቢት ይይዛል፡፡ «ማንም አንዳች ያወቀ ቢመስለው ሊያወቅ እንደሚገባው ገና አላወቀም።» 1ቆሮ8፥2 በማለት ቅዱስ ጳውሎስ ተናግሯል፡፡ መታወቅ ያለበትን ትህትናን ሳያውቃት ሰው አዋቂ ሊባል አይችልም፡፡ ትሕትና ደግሞ አዋቂ ነኝ አታሰኝም። በዚህ ዓለም ካሉት ነገሮች ከቁጥር የማይገባን ጥቂት ነገር አውቆ አዋቂ ነኝ ማለት እጅግ የሚያሳፍር ነው፡፡
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ «ዕውቀት ያስታብያል» 1ቆሮ8÷2 በማለት እንደተናገረው ዕውቀት ሲያስታብይ ፍቅር ግን ያንጻል፡፡ከዕውቀት ፍቅር በብዙ ይበልጣል፡፡ስለዚህ አንተ ብዙ ዕውቀት ቢኖርህ ትንሽ ፍቅር ያለው ሰው ይበልጥሃልና መታበይ አይገባህም፡፡
ሰው ሁሉ ከትዕቢት ለመዳን ያወቀውን ዕውቀት ከሌሎች ሰዎች እንዳገኘውና በዕውቀት ከርሱ የተሻሉ በርካታ ሰዎች እንዳሉ ቢያስብ በጣም ይጠቀማል። ከዚህም በላይ ዕውቀትን እንደ ገበቴ ውኃ ማፍሰስ (ማጥፋት) የሚቻለው ፈጣሪም እንዳለ ባይዘነጋ ጥሩ ነው፡፡ ከአንተ አስቀድሞ የነበሩ ብዙ አዋቂዎች እንደ ቀለም ቀንድ ተሰብረው ተቀብረዋል፡፡ ሌሎችም የትምህርት ማስረጃቸውን እያሳዩ የሚለምኑ ሆነዋል:: ከፊሎቹ ደግሞ አብደውና አእምሮአቸውን አጥተው የሚናገሩትን እንኳን አያውቁትም።ታዲያ አንተ ከእነዚህ እንደ አንዱ ባለመሆንህ ማመስገን ሲገባህ የምትኩራራው ከእግዚአብሔር እጅ የምታመልጥ ይመስልሃልን? ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ «ዕውቀትም ቢሆን ይሻራል» በማለት የተናገረውን ቃል አስበህ ዕውቀትን የሚስጥና የሚነሣ የሰማይን አምላክ አመስግን እንጂ አትታበይ፡፡ 1ቆሮ13÷9
ትዕቢት በእጅጉ ይጐዳል፡፡አንተ በዕውቀትህ የምትታበይ ሰው ትዕቢት መጉዳቷን እንኳን ሳታውቅ አዋቂ ነኝ እንዴት ትላለህ? በማወቅህ ምክንያት ሊፈጠሩ የሚችሉ ትዕቢትና ትምክህት የሚያመጡብህ ጉዳት ትምህርት ከሚሰጥህ ጥቅም በእጅጉ ይከፋል፡፡ ታዲያ ተምሮ ትዕቢተኛ ከመሆን ደንቁሮ ትሑት መሆን አይሻልም ትላለህን?
የአንድ የፈጠራ ሙያ ባለቤት ብትሆን እንኳን ልትመካ አትችልም፡፡ ምክንያቱም እርሱም ቢሆን መሠረቱን ማየት ከቻልክ የሌሎች መሆኑን ትገነዘባለህ:: በዙሪያ የምታያቸው ነገሮች በአብዛኞቹ የአንድ ሰው የፈጠራ ውጤት ሳይሆኑ የብዙ ሰዎች የሐሳብ ጥርቅም ውጤቶች ናቸው:: ወይም በአንድ ሰው ክተጀመሩ በኋላ በሌሎች ሰዎች እየዳበሩ አሁን የምታያቸውን አኽለዋል:: ለምሳሌ፡- መቀመሪያ (ኮምፒውተር)፣ ሰዓት፣ ስልክ፣ ነፋሰ ድምፅ (ሬዲዮ)፣ ነፋሰ ሥዕል (ቴሌቪዥን)፣ መብራትንና ሌሎችንም ነገሮች ብትመለከት ስለግኝታቸው አንድ መሠረት የጣለ ስው ቢጠቀስላቸውም አሁን ላሉበት ደረጃ የበቁት ግን የብዙ ሰዎች ሐሳብ ተጨምሮባቸው ነው፡፡ መሠረት ጣለ የተባለውም ሰው ከእርሱ በፊት የነበሩ ሰዎች ለግኝቱ መሠረት የሆነ ሐሳብ በሆነ መንገድ ባይለግሱት ኖሮ መሠረት የተባለውን ሐሳብ አንኳን ለማግኘት አይበቃም ነበር፡፡ ከዚህ ሁሉ በላይ ዕውቀት የባሕርይው የሆነ የዕውቀት ባለቤት አእምሮውንና የተገለገለባቸውን ቁሳቁሶች ባይፈጥርለት ኖሮ ማንም ሰው የፈጠራ ሙያ ባለቤት ባልሆነም ነበር፡፡ ታዲያ ይህን ሁሉ ያስተዋለ በፈጠራ ሙያው ፈጣሪን ማመስገን እን እንጂ መመካት አይገባውም፡፡የሚመካውን ግን ሐዋርያው እንዲህ ሲል ይገሥጻል:- «አንተ እንድትበልጥ ማን አድርጐሃል? ያልተቀበልከውስ ምን አለህ? የተቀበልህ ከሆንህ ግን እንዳልተቀበልህ የምትመካ ስለ ምንድር ነው?›› 1ቆሮ4÷7

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

ትምህርት ጉዳት ይኖረዋል?
ቅዱሳት መጻሕፍትና ትምህርቶቻቸው የተገኙት ከማይሳሳት ከእግዚአብሔር በመሆናቸው ፍጹምና እንከን የለሽ ናቸው:: ቅዱስ ዳዊትም «በምድር ላይ እንደ ተፈተነ ሰባት ጊዜ እንደ ተጣራ ብር የእግዚአብሔር ቃል የነጻ ቃል ነው::›› በማለት የመንፈሳዊ መጻሕፍትን ፍጹምነት መስክሯል። መዝ11፥6 በዚህ ምክንያት ቅዱሳት መጻሕፍትን ማሻሻል፣ በዙ ብሎ መቀነስና አንሰዋል በማለት ለመጨመር መሞከር ከባድ መንፈሳዊ ቅጣት ያስከትላል፡፡ራእ 22÷18-19 ፤ዘዳ4÷2
እነዚህን ቅዱሳት መጻሕፍት የሰው ልጅ በሚገባ ባለመማሩ ይጐዳል እንጂ እነርሱን በመማሩ የተነሣ የሚጐድልበትና የሚጐዳበት አንዳችም ነገር የለም:: ሰው ቅዱሳት መጻሕፍትን ተምሮ ከተጐዳችግሩ ያለው ከራሱ ወይም ከመምህሩ እንጂ ከቅዱሳት መጻሕፍቱ ሊሆን አይችልም። ችግር የሚፈጠረው በመንፈስ ቅዱስ አጋዥነት የተጻፈውን ቅዱስ መጽሐፍ በርኩስ መንፈስ አጋዥነትና በራስ ፈቃድ ተነሣሥቶ ለመተርጐም በሚሞከርበት ጊዜ ነው። 2ጴጥ1፥20-2፤ ሐዋ8፥30-31 መንፈሳዊ ትምህርት ዓላማውን ሳይለቅ በሚገባ ቢማሩት ምንም ዓይነት ጉዳት የሌለው ፍጹም ጠቃሚ ትምህርት ነው።
ዓለማዊ (ሥጋዊ) ትምህርት ግን ፍጹምነት የለውም፡፡ በየጊዜው በሚደረስባቸው አዳዲስ ግኝቶች የተነሣ በአቀራረጹ ብቻ ሳይሆን በመሠረታዊ ሐሳቡም ከጊዜ ወደ ጊዜ የመለዋወጥና እያደገ የመሄድ ባሕርይ አለው።ይህ ሂደት ዘመናዊ ትምህርት ምንም እንኳን ጥልቅ ቢመስልም ገና ዕድገቱን ሙሉ በሙሉ ያልጨረሰ እንጭጭ እንደሆነና ፍጹምነት እንደሚጎድለው ያሳያል። እስከ አሁንም ድረስ ወደ ሙሉ የዕውቀት ደረጃ ባለመድረሱ አዲስ ሐሳብ ሲገኝ ብቻ ጉዳታቸው የሚገለጥ ዛሬ ግን በጠቃሚነታቸው ብቻ ጐልተው የሚታወቁ ብዙ ስሕተቶችን አካቶ ይዟል።
የዘመናዊ ትምህርት ፅንሰ ሐሳቦች በሙሉ በቤተ ሙከራ ተፈትሸው የወጡ አይደሉም፡፡ ሙከራ ሊደረግባቸው የማይችሉ ብዙ የዘመናዊ ትምህርት ክፍሎች አሉ፡፡ እነዚህ በሙከራ ያልታዩ ይልቁንም በዕድል፣ በመላምትና በግምት የተገኙ ጭብጥ የሌላቸው ሐሳቦች (ሃይፖተቲካልስ) ጉድለታቸው እስኪታወቅ ድረስ የሰውን ልጅ በተሳሳተ አመለካከት ተቀርጾ እንዲያድግ በማድረግ፣ በማኅበራዊ ኑሮው፣ በጤናው፣ በምግባሩና በሃይማኖቱ ላይ ይህ ነው የማይባል አሉታዊ ተፅዕኖ ማሳደራቸው አይቀርም።ይህም የዘመናዊ ትምህርት ዋነኛና ቀጥተኛ ጉዳት ተደርጐ ይጠቀሳል። ሃይማኖት የሌላቸውና ለመንፈሳዊ ነገር ግድ የሌላቸው ሰዎች ዘመናዊ ትምህርት ጥቅም ብቻ እንጂ ጉዳት ያለው አይመስላቸውም፡፡ ነገር ግን ዘመናዊ ትምህርት በመንፈሳዊ ትምህርት ከተመዘነ በብዙ ጎዳና ሊጎዳ እንደሚችል መታዘብ ይቻላል።

ቀጣይ ምዕራፍ ዐሥር ክፍል ዐራት :
👉 «የትምህርት ተዛማጅ ጉዳቶች» በሚል ይቀጥላል .....
ለጥያቄና አስተያየት @Ethiopian_Orthodox_bot ተጠቀሙ።

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

አሳዛኝ ውጤቶችን በሚያስከትሉ በጾታ ብልግና፣ በአደንዛዥ ዕፅ ሱሰኝነት፣ በሌብነት፣ በቡድን ጸብና በመሳሰሉት ልዩ ልዩ የዓመፅ ተግባራት የተመረዙ ባልንጀሮችህን ጨምርሮ በርካታ ሰዎች በዙሪያህ ይገኛሉ፡፡ይህን ከመሳሰሉት ሰዎች ጋር መዋል ቅር ሳያሰኝህ አይቀርም፡፡ ምንም እንኳን ከነዚህ ሰዎች ጋር ያለህን ግንኙነት በቀላሉ ለማስቀረት ያስቸገረህ ቢሆንም ትምህርትህን በሚገባ ብትከታተል ግን እንዲህ ካሉ መጥፎ ሰዎች ጋር ያለህን የጠበቀ ግንኙነት ቀስ በቀስ ለመቅረፍ ትችላለህ፡፡ ለትምህርት ጥሩ ትኩረት በምትሰጥበት ጊዜ ሰፊ ጊዜህን ይይዝልሃል፡፡ ይህም ሥነ ሥርዓት ከጐደላቸው ሰዎች ጋር የሚኖርህን ግንኙነት ውስን ያደርገዋል፡፡ እንደዚህ ያሉ ሰዎች ፍላጐትህ ትምህርትህን በሚገባ መከታተል ብቻ መሆኑን ሲያዩ ከጊዜ በኋላ ሊተዉህ ይችላሉ፡፡ይህም ከትምህርት የምታገኘው «ጥበቃ» ነው።
መጽሐፈ መነኮሳት የማንበብ ልምድና ትምህርት በንጽሕና ተጠብቆ ለመኖር አጋዥ መሆናቸውን እንዲህ ሲል ይገልጻል:- «ፃማ ሥጋዊት ወአንብቦ መጻሕፍት አሞላካውያት የዐቅብዋ ለንጽሕና» በአማርኛ «በሥጋ መድከምና አምላካዊያት መጻሕፍትን ማንበብ ንጽሕናን ይጠብቋታል» ማለት ነው:: (ማር.ይስ.አን.ሣልስ.ምዕ 9)
የመንፈሳዊ ትምህርት ጥቅም
ያለንበት ዘመን ከየትኛውም ጊዜ ይልቅ የትምሀርት ጥቅም ጎልቶ የሚታይበት ዘመን ሆኗል። ከላይ በጥቂቱ የተገለጹት ዕሤቶች ከሥጋዊ ትምህርት የሚገኙ ናቸው። ሥጋዊ ትምህርት እንደዚህ የሚጠቅም ሆነ መንፈሳዊ ትምህርት ደግሞ እጅግ በተሻለ ሁኔታ እንደሚጠቅም ጥርጥር የለውም:: ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ማንኛውም ሥጋዊ ነገር ያለው ጠቀሜታ ከመንፈሳዊ ነገር ጠቀሜታ ጋር ሲነጻጸር እጅግ ጥቂት" እንደ ሆነ እንዲህ በማለት ይገልጻል፡፡ «ሰውነትን ለሥጋዊ ነገር ማስለመድ ለጥቂት ይጠቅማልና፤ እግዚአብሔርን መምሰል ግን የአሁንና የሚመጣው ሕይወት ተስፋ ስላለው ለነገር ሁሉ ይጠቅማል፡፡»1ጢሞ4፥8 ስለዚህ መንፈሳዊ ትምህርት የሚሰጠው ጠቀሜታ ከሥጋዊ ትምህርት እጅግ የላቀ ነው።
በስሕተታቸው ጸንተው የሚኖሩ ሰዎች ሥራዬ ትክክል ነው ብለው የሚያምኑ ወይም መሳሳታቸውን በውል ያልተረዱ ናቸው፡፡ ከዚህ ካለፈ ደግሞ ስሕተታቸውን ቢያውቁም ከዘለቄታዊ ጥቅም ይልቅ ለጊዜው የፍላጐታቸውን መሳካት የሚወዱ ከመሆን አይዘሉም።ካለማወቅ የተነሣ የተሳሳቱ ሰዎች መላልሰው ሥራቸውን ቢመረምሩትና በቂ ግንዛቤ እስኪያገኙ ድረስ ስለ ሥራቸውም አስከፊነት ቢማሩ ከስሕህተት ይታረማሉ፡፡መማር ከመሳሳት ያድናልና፡፡
የማይሳሳት የለም፤ ከስሕተት ሁሉ የሚከፋው ግን በሃይማኖታችን ላይ የምንፈጥረው ስሕተት ነው፡፡ ለምን ቢባል ጉዳቱ የነፍስ ስለሆነ ነው።ከዚህም ዓይነት ስሕተት ቢሆን መዳን የሚቻለው በመማር ነው። አለማወቅ ለሕህተት መንሥኤ ከሆነ መማርና ማወቅ ከስሕተት ለመዳን መፍትሔ መሆኑ ግድ ነው፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በትንሣኤ ላይ ባላቸው እምነት ችግር ለነበረባቸው ለሰዱቃውያን የስሕተታቸው መነሻ ምን እንደ ነበር ሲነግራቸው ‹‹መጻሕፍትንና የእግዚአብሔርን ኃይል አታውቁምና ትስታላችው» ብሏቸዋል።ማቴ22፥29 ስለዚህ ትምህርት ካሉት ዋና ዋና ጥቅሞች መካከል ‹‹ከስሕተት ለመዳን›› የሚለው በአንደኛነት ይጠቀሳል።
ከስሕተት ለመዳን ብቻ ሳይሆን ለማመንና እግዚአብሔርን ፈርቶ ለመኖርም ትምህርት ወሳኝ ነገር ነው፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ሳይማሩ ሃይማኖተኛ ሰው መሆን እጅግ አስቸጋሪ እንደ ሆነ «ባልሰሙትስ እንዴት ያምናሉ? ያለ ሰባኪስ እንዴት ይሰማሉ?›› በማለት ተናግሯል።ሮሜ10፥14 ቅዱስ ዳዊት ደግሞ «ልጆቼ ሆይ ስሙኝ እግዚአብሔርን መፍራት አስተምራችኋለሁ» መዝ33÷11 በማለት ማመን ከትምህርት እንደሚገኝ ተናግሯል፡፡ በዓይን ያላዩትን እግዚአብሔርን መፍራት ማመን ይባላል፡፡
ለማመን ብቻ ሳይሆን መልካም ሥራ ለመሥራትም መማር ያስፈልጋል፡፡ የማያውቁትን መሥራት ስለማያስቸግር ለመሥራት ማወቅ፣ ለማወቅ ደግሞ መማር ግድ ነው፡፡ ማወቅ ለመሥራት ብቻ ሳይሆን በሥራችን የትክክለኛለነት ስሜት እንዲስማንና ያለማቋረጥ በጉጉት እንድንሠራው ያግዘናል፡፡ በአጠቃላይ በመንፈሳዊም ሆነ በሥጋዊ ጐዳና የሚሠሩ ሥራዎችን ለማከናወን መማር ያስፈልጋል።ለዚህም ነቢዩ ኢሳይያስ «መልካም መሥራትን ተማሩ» በማለት የተናገረው ቃል በቂ ማስረጃ ነው፡፡ ኢሳ1፥17፤ 26፥9-10

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

ጾመ ድኅነት

ጾመ ድኅነት ስሙ እንደሚያመለክተው የመዳን ጾም ማለት ሲኾን፣ ይህም በብሉይ ኪዳኑ አጽዋማት በጾመ አስቴር እና በጾመ ዮዲት የተተካ የሐዲስ ኪዳን ጾም ነው፡፡

በብሉይ ኪዳን በሐማ ምክንያት በእስራኤል ላይ ታውጆ የነበረው ሞት በጾመ አስቴር እንደ ተሻረ ኹሉ፣ በሐዲስ ኪዳንም በዕለተ ረቡዕ በጌታችን ላይ በተፈጸመው ምክር የሰይጣን ሴራ ፈርሷልና በጾመ አስቴር ምትክ ረቡዕን እንጾማለን፡፡

እንደዚሁም በብሉይ ኪዳን በጾመ ዮዲት ምክንያት ሆሎሆርኒስ ድል እንደ ተደረገበት ኹሉ፣ በሐዲስ ኪዳንም መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዕለተ ዓርብ በመስቀል ላይ በከፈለው መሥዋዕትነት ዲያብሎስ ድል ተደርጓልና በጾመ ዮዲት ምትክ ዓርብን እንጾማለን፡፡
የእነዚህ የሁለቱ ቀናት (የረቡዕና ዓርብ) ጾም ጾመ ድኅነት ይባላል፡፡

ጾመ ድኅነት እንደ ጾመ ነነዌ፣ ዐቢይ ጾም እና ጾመ ሐዋርያት የበዓላትና የአጽዋማት ማውጫ ቀመርን ተከትሎ የሚመጣ ከሰባቱ አጽዋማት መካከል የሚመደብ ጾም ነው፡፡

ጾመ ድኅነት ከበዓለ ኀምሳ በስተቀር ዓመቱን ሙሉ የሚጾም ጾም ነው፡፡

ዕለተ ረቡዕ የጌታ ሞት የተመከረበት፤ ዓርብም አምላካችን የተሰቀለበት ዕለት ነውና በመስቀሉ መሥዋዕትነት ያገኘውን ድኅነት ዘወትር ማሰብ ስለሚገባን ሁልጊዜ እንድንጾማቸው በቅዱስ ሲኖዶስ ሥርዓት ተሠርቶልናል፡፡

በዚህ ዓመት ጾመ ድኅነት ሰኔ ፬(4) ቀን ይጀመራል፡፡

ወስብሐት ለእግዚአብሔር!

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

ጾመ ሐዋርያት
ሰኔ 2
ጾመ ሐዋርያት በወርኃ ሰኔ ስለሚጾም በምእመናን ዘንድ የሰኔ ጾም በመባል ይታወቃል፤ ከሰባቱ የዐዋጅ አጽዋማትም አንዱ ነው፡፡ ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስን ከተቀበሉ በኋላ ለስብከተ ወንጌል ከመሰማራታቸው በፊት የጾሙት ጾም ነው፡፡
ይህም ጾም ከበዓለ ኀምሳ በኋላ የሚጾም ነው፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ በተነሣ በአርባኛው ቀን ቅዱሳን ሐዋርያት በጸሎት ይተጉ ወደ ነበረበት ቤት በመሄድ ደቀመዛሙርቱን ይዟቸው ከቤት በመውጣት መንገድ ጀመረ፡፡ እርሱ ከፊት እየመራቸው እነርሱ እየተከተሉት ወደ ረጅሙና በረጃጅም ዛፎች ወደ ተሞላው ደብረ ዘይት ተራራ ይዟቸው ወጣ፡፡ ይህንንም እየነገራቸው ከምድር ወደ ሰማይ ከፍ፤ከፍ አለ፡፡ ነጭ የሆነች ብሩህ ደመናም አምላካችንን ተቀበለችው፡፡ከዓይናቸውም እየራቀ፤ከእይታቸው በርቀት ሳይሆን በርኅቀት ተሰወረባቸው፡፡ሐዋርያትም ኢየሱስ ክርስቶስን በጣም ይወዱት ስለነበር ሲለያቸው አዝነው አተኩረው ሰማዩን ለረጅም ሰዓት ተመለከቱ፡፡ ድንገትም ነጫጭ ልብስ የለበሱ ሁለት ቅዱሳን መላእክት በአጠገባቸው ቆመው ታዩአቸው፡፡መላእክትም ሐዋርያትን እንዲህ አሏቸው፤ ‹‹እናንተ የገሊላ ሰዎች ሆይ ወደ ሰማይ እያያችሁ ለምን  ቆማችኋል፡፡ ይህ ከእናንተ ወደ ሰማይ ያረገው ኢየሱስ ከእናንተ ወደ ሰማይ ሲያርግ እንዳያችሁት እንዲሁ ዳግመኛ ይመጣል›› አሏቸው፤ (ሐዋ. ፩፥፰-፲፩)፡፡ ሐዋርያትም የመላእክትን ማረጋጊያ ቃል ከሰሙ በኋላ  በኢየሩሳሌም ወደ ምትገኘው ቤተ መቅደስ በመሄድ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የነገራቸው እስኪፈጸም ድረስ ቀን ከሌሊት በአንድነት ሆነው እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ከመካከላቸው አድርገው በጾምና በጸሎት እየተጉ ቆዩ፡፡
የጾመ ሐዋርያት የጊዜ ቀመር ሥሌት በዓለ ጰራቅሊጦስ እንደ ገባ ባለው የመጀመሪያው ሰኞ ይውላል፡፡ በዚህም መሰረት የዘንድሮ ጾመ ሐዋርያት ሰኔ ፪(2) ይገባል። ጌታችን አምላካችን እና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመዋዕለ ሥጋዌው ደቀ መዛሙርቱን ይህን ጾም እንደሚጾሙት እንዲህ ተናግሮ ነበር፡፡ በዚያን ጊዜ የዮሐንስ ደቀ መዛሙርት ወደ እርሱ ቀርበው። ‹‹እኛና ፈሪሳውያን፥ ብዙ እንጾማለን፥ ደቀ መዛሙርትህስ ለምን አይጾሙም? አሉት›› (ማቴ.፱፥፲፬)።  ደቀ መዛሙርቱ ይህንን በጠየቁት ጊዜ ጌታችን እንዲህ ብሎ መልሶላቸው ነበር፡፡‹‹ኢየሱስም እንዲህ አላቸው፤ የሙሽራው ሚዜዎች ሙሽራው  ከእነርሱ ጋር ሳለ ሊያዝኑ አይችሉም፤ ነገር ግን ሙሽራው ከእነርሱ የሚወሰድበት ወራት ይመጣል፤ያንጊዜም ይጾማሉ›› (ማቴ.፱፥፲፭)፡፡
እኔ ሳለሁ አይጾሙም ማለቱ እርሱ ካልሞተና ካላረገ፤ መንፈስ ቅዱስም ካልተሰጣቸው በመንፈስ ቅዱስ ባልታደሰ ሰውነት ጾመው ድል መንሳት ስለማይቻላቸው ነው፡፡ ይህን ጾም የምንጾመው ሐዋርያት ጾመው ጸልየው ድል ያደረጉትን ዓለም እኛም የምናሸንፍበት ኃይል እንዲሰጠን ፈጣሪያችንን አምላከ ሐዋርያት ተለመነን እያልን ለመማጸን ነው፡፡
ይህን ጾም እንደ ሌሎቹ አጽዋማት ሁሉ እያንዳንዱ ምእመን ሊጾመው የሚገባ ቢሆንም በአሁኑ ሰዓት ግን አብዛኛው ምእመን ‹‹የቄስ ጾም›› ነው በማለት ከጾሙ ሽሽት ሲያደርጉ ይስተዋላል፡፡ ይህ ሥርዓተ ቤተክርስትያንን መሠረት ያደረገ ባለመሆኑ መስተካከል ይገባዋል፡፡
ሐዋርያትን አብነት በማድረግ ጾመን በረከትን ልናተርፍ ይገባናል፡፡
የአምላካችን የልዑል እግዚአብሔር ቸርነት፣
የእናታችን የቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነት፣
የቅዱሳን ሐዋርያት በረከት፣
የጻድቃን የሰማዕታት ጸሎት እና ምልጃ አይለየን፡፡

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር
አሜን፡፡

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

በዓለ ጰራቅሊጦስ

መንፈስ ቅዱስ ከሚጠራባቸው ስሞች አንዱ ጰራቅሊጦስ ናዛዚ መጽንዒ መስተፍሥሒ፤ የሚያጽናና፣ የሚመክር፣ የሚረዳ፣ የሚታደግ የሚል ትርጉም አለው፡፡ አጽናኝም የተባለው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ‹‹አብ በስሜ የሚልከው ግን መንፈስ ቅዱስ የሆነው አጽናኝ እርሱ ሁሉን ያስተምራችኋል፤ እኔም የነገርኋችሁን ሁሉ ያሳስባችኋ›› ብሎ ተናግሯል፡፡ በሌላም በኩል ደግሞ ‹‹እኔ ከአብ ዘንድ የምልክላችሁ ጰራቅሊጦስ እርሱም ከአብ የሚወጣ የእውነት መንፈስ በመጣ ጊዜ፥ እርሱ ስለ እኔ ይመሰክራል›› እንዲል። (ዮሐ.፲፬፥፳፮፤ ፲፭፥፲፮)

ጰራቅሊጦስ የሚለው የመንፈስ ቅዱስ ስም የሚያጽናና፣ የሚመክር፣ የሚረዳ፣ የሚታደግ መሆኑም ከማሳየት በላይ፤ ፍጹም አካል ያለው አምላክ እንደሆነ አመልካች ነው። ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ጰራቅሊጦስ ማለት መሪ፣ አጽናኝ፣ ረጂ ማለት መሆኑን በስፋት ካስተማሩ ሊቃውንት በቀዳሚነት ይነሳል። ጰራቅሊጦሰ የተባለው መንፈስ ቅዱስ እግዚአብሔር ነው። ሐዋርያዊት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በመንፈስ ቅዱስ ያላትን እምነቷን ስትገልጥ ‹‹ወነአምን በመንፈስ ቅዱስ እግዚእ ማኅየዊ ዘሠረፀ እም አብ ንሰግድ ሎቱ ወንሰብሖ ምስለ አብ ወወልድ››፤ በመንፈስ ቅዱስ እናምናለን እርሱም ጌታ ሕይወትን የሚሰጥ ከአብ የሠረፀ ከአብ ከወልድ ጋራ በአንድነት እንሰግድለታለን፣ እናመሰግነዋለን፤›› የሚል ነው።
እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ቅዱስ፤ የቅድስናም ምንጭ ነው። አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ‹‹ወስመ መንፈስ ቅዱስ ነቅዐ ቅድሳትየ፤ የመንፈስ ቅዱስም ስም የቅድስናየ መገኛ ነው›› በማለት ገልጾታል። (መጽሐፈ ምሥጢር)
ቅዱስ ባስልዮስም በቅዳሴው ‹‹ሃሌ ሉያ ቅዱስ መንፈስ ቅዱስ ጰራቅሊጦስ መጽንዒ ቅድመ ዓለም የነበረ ዓለምን አሳልፎ የሚኖር መንፈስ ቅዱስ ንጹሕ ክቡር ልዩ ነው›› በማለት አምላካዊ ስሙን ጠርቶ አመስግኖታል። ቅድስት ቤተ ክርስቲያንም ዕለት ዕለት በምታከናውነው ሥርዓተ ቅዳሴ ‹‹መንጽሒ ወመጽንዒ የሚሆን መንፈስ ቅዱስ ክቡር ምስጉን ነው›› እያለች የአምላክነት ስሙን ጠርታ ታመሰግነዋለች።
ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ሃይማኖት ሊያጸኑ ከሓድያንን ሊለዩ (ሊያወግዙ) ሲሰባሰቡ በመካከላቸው ተገኝቶ ውሳኔ ያስወስናቸው የነበረው እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ እንደሆነ ሲገልጹ ጰራቅሊጦስ የተባለ ስሙን ጠርተው እንዲህ ብለዋል፣ ‹‹ወሀሎ ምስሌሆሙ ኅብረ መንፈስ ቅዱስ …. ጰራቅሊጦስ የሚያነጻና የሚያጸና መንፈስ ቅዱስም በጉባኤያቸው ነበረ፡፡›› (መጽሐፈ ምሥጢር)
ጌታችን አምላካችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ካረገ በኋላ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም፣ ዐሥራ ሁለቱ ደቀ መዛሙርት፣ ሰባ ሁለቱ አርድእት እና ሠላሳ ስድስቱ ቅዱሳት አንስት በኢየሩሳሌም ከተማ በአንድነት ሆነው በጸሎት ይተጉ ነበር፡፡ ጌታችን በሚያርግበት ጊዜ ‹‹እነሆ አባቴ የሰጠውን ተስፋ እኔ እልክላችኋለሁ፤ እናንተ ግን ከላይ ኃይል እስክትለብሱ ድረስ በኢየሩሳሌም ከተማ ቆዩ፤›› ሲል ለሐዋርያቱ በሰጣቸው የተስፋ ቃል መሠረት በዐረገ በዐሥረኛው ቀን መንፈስ ቅዱስን ልኮላቸዋል (ሉቃ. ፳፬፥፵፱)፡፡ ሁሉም በአንድ ቦታ ተሰባስበው ሳሉ እንደ ዐውሎ ነፋስ ያለ ድምፅ ድንገት ከሰማይ ወርዶ የነበሩበትን ቤት ሞላው፡፡ ከዚያም የተከፋፈሉ የእሳት ላንቃዎች በሁሉም ላይ አረፉባቸው፡፡ በዚህ ጊዜ ሁላቸውም መንፈስ ቅዱስ ባደላቸው መጠን በየሀገሩ ቋንቋዎች ሁሉ ተናገሩ፡፡ (ሐዋ.፪፥፩-፬)

ጌታችን መንፈስ ቅዱስን ለሐዋርያት የላከበት ይህ ዐቢይ በዓል ዐሥራቱን፣ በኵራቱን፣ ቀዳምያቱን ካህናተ ኦሪት ስለሚቀበሉበት በብሉይ ኪዳን በዓለ ሠዊት ተብሎ ይከበር ነበር፡፡ በሐዲስ ኪዳን ደግሞ ቅዱሳን ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስን ስለ ተቀበሉበት በበዓለ ሠዊት ምትክ በዓለ ጰራቅሊጦስ ተብሎ ይከበራል፡፡ የበዓለ ትንሣኤ መነሻው የአይሁድ የፋሲካ በዓል ማለትም በግብጽ፣ እስራኤል ከሞት የዳኑበት የመታሰቢያ በዓል እንደ ሆነው ሁሉ፣ ለበዓለ ጰራቅሊጦስም መነሻው ይኸው የአይሁድ የፋሲካ በዓል ነው፡፡ የአይሁድ ፋሲካ ከተከበረ ከሰባት ሳምንታት በኋላ በኀምሳኛው ቀን የሩቆቹ ከከተሙበት ወጥተው፣ የቅርቦቹ ከተሰባሰቡበት ተገናኝተው ለበዓሉ ፍጻሜ የሚሆነውን በዓለ ሠዊት (የእሸት በዓል) ያከብሩ ነበር፡፡
ሐዋርያት በጽርሐ ጽዮን ተሰባስበው ሳሉ መንፈስ ቅዱስ በእሳት አምሳል ወርዶ ሰማያዊ ሀብትን፣ ዕውቀትና ጸጋን አድሏቸዋል፡፡ መንፈስ ቅዱስ ከወረደላቸው በኋላም በአእምሮ ጐልምሰዋል፤ ጥቡዓን (ቈራጦች)፣ ጽኑዓን ሆነዋል፤ ለስብከተ ወንጌል የሚፋጠኑበትንና ለሰማዕትነት የሚዘጋጁበትን ልቡና ታድለዋል፡፡ ቀድሞ ይናገሩት ከነበሩት ቋንቋ በተጨማሪ ፸፩ ቋንቋዎች ተገልጠውላቸው ምሥጢራትን በልዩ ልዩ ቋንቋ መተርጐም ጀምረዋል፡፡ ሐዋርያት በየሀገሩ ቋንቋ ሲናገሩ የሰሙ በዚያ የነበሩ ሰዎችም በሐዋርያት ተገረሙ፡፡ አንዳንድ የአይሁድ ወገኖች ግን በሐዋርያት ላይ ያዩት ክሥተት አዲስ ነገር ስለሆነባቸው ‹‹ጉሽ ጠጅ ጠጥተው ሰክረው የሆነ ያልሆነውን ይቀባጥራሉ›› እያሉ ሐዋርያትን ያሟቸው ነበር፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስም ይህንን ሐሳባቸውን በመንፈስ ቅዱስ አውቆ ‹‹ሰክረዋል የምትሉ እናንተ እንደምትጠራጠሩት አይደለም፡፡ ጊዜው ማለዳ፣ ሰዓቱም ገና ሦስት ሰዓት ነውና፡፡ ግን በነቢዩ ኢዩኤል ‹ከዚህም በኋላ እንዲህ ይሆናል፤ መንፈሴን በሥጋ ለባሽ ሁሉ ላይ አፈሳለሁ፤ ወንዶችና ሴቶች ልጆቻችሁም ትንቢት ይናገራሉ› ተብሎ የተነገረው ትንቢት ይፈጸም ዘንድ፣ ይህንን ድንቅ ተአምር ያደረገው እናንተ የሰቀላችሁት ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፤››በማለት ሰፊ ትምህርተ ወንጌል ሰጥቷቸዋል፡፡ (ኢዩ.፪፥፳፰)
በትምህርቱም ነቢያት ትንቢት የተናገሩለት፣ምሳሌ የመሰሉለት አምላክ ወልደ አምላክ ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ መነሣቱን፣ማረጉንና ዳግም በክብር በምስጋና መጥቶ በሕያዋንና በሙታን ላይ የሚፈረድ መሆኑን ሐዋርያት እንደሚመሰክሩ በአይሁድ ፊት አሰምቶ ተናገረ፡፡በቅዱስ ጴጥሮስ ትምህርት የተማረኩ አሕዛብም ‹‹ምን እናድርግ?››ብለው በጠየቁት ጊዜ ከክፋታቸው ተመልሰው፣ንስሓ ገብተው በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እንዲጠመቁ ነገሯቸዋል፡፡ በዚያችም ሰዓት ሦስት ሺህ ሕዝብ በኢየሱስ ክርስቶስ አምኖ ተጠምቋል፡፡(ሐዋ.፪፥፩-፵፩)
ቅዱሳን ሐዋርያት፤ ‹‹በዚህች ቀን በሦስት ሰዓት ኢየሱስ ክርስቶስ ጰራቅሊጦስን ልኮልናልና በላያችን ኃይልን ሞላ፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ በሕያዋንና በሙታን ይፈርድ ዘንድ ሥልጣን እንዳለው በአዲስ ቋንቋ ተናገርን፤›› በማለት በዕለቱ ያዩትንና የተደረገላቸውን፣ እንደዚሁም የበዓሉን ታላቅነት ከመሰከሩ በኋላ ይህንን በዓል ማክበር እንደሚገባ አዝዘዋል፤ በዚህ ወቅት መጾምና ማዘን ተገቢ አለመሆኑንም ተናግረዋል፡፡ (ዲድስቅልያ ፴፥፴፰-፴፱፤ ፴፩፥፷፱-፸)
ቅዱሳን ሐዋርያትም ‹‹ከአብ የሠረፀ የሁላችንም መጽናኛ የሚሆን ዓለሙንም ሁሉ ያዳነ ከአብና ከወልድ ጋር ህልው የሚሆን መንፈስ ቅዱስን ላከልን፡፡ መንፈስ ቅዱስ ጰራቅሊጦስም አንድ ነው›› ብለዋል። በሌላም ነቢዩ ዳዊት ስለመንፈስ ቅዱስ ‹‹መንፈስህን ከእኔ አታርቅ አለ፤ ዳግመኛም በሰውነቴ እውነተኛ መንፈስን አጽናልኝ፣ ከሁሉ በሆነ መንፈስ ቅዱስ አጽናኝ አለ›› በማለት አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ መንፈስ ቅዱስን ጰራቅሊጦስ አጽናኝ መካሪ መባሉን አስተምሯል። (መዝ. ፶፥ ፲-፲፪፤ መጽሐፈ ምሥጢር)
አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በበዓለ ኀምሳ ምንባብ ላይ እግዚአብሔር

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

በሚገባ መማር
ትምህርትን ሲከታተሉ በፍቅርና በሙሉ ኃይል ጥረት ከማድረግ ጋር ከሆነ ውጤቱ ያማረ ይሆናል። ብዙ ወጣቶች ለትምህርት የተነሣሣ ልብ ስለሌላቸው በሚገባ አይማሩም፡፡ በትምህርት ገበታቸው ላይ እንኳን የሚገኙት ሌላ ምክንያት ሲኖራቸው ወይም ደስ ሲላቸው ብቻ ነው። ማጥናቱንም ቢሆን የሚያከናውኑት ፈተና ለማለፍ ያህል ነው፡፡ ይህም ሊሆን የሚችለው በጣም ተግተዋል ከተባለ ነው።አንተስ የምታጠናው እንዴት ነው? ስልቹ ሰው የቆረሰውን እንጀራ ለመጉረስም ይታክታልና፡፡ ስልቹ ሰው አትሁን! ደግሞም «መልካም ሥራን ለመሥራት አንታክት›› ገላ6÷9፣2ተሰ3፡13 የሚለውን የእግዚአብሔር ቃል እንደ ስንቅ ብትይዘው ከመሰልቸት ያድንኃል፡፡
በምንም ምክንያት በሚያስተምርህ መምህር ጥላቻ እንዲያድርብህ ተጠንቀቅ፡፡ ይህ በትምህርትህ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ አለውና፡፡ ከመምህራን ጋር በፍቅር ለመኖር የምታደርገው ጥረት ባይሳካልህ እንኳን ተግቶ ከመማር ግን ተስፋ ሊያስቆርጥህ አይገባም።እንደ ምንም ተቸግረህና ለፍተህ ተማር! ጊዜ ጠብቆ የለፋበትን መስጠት የእግዚአብሔር ድርሻ ነውና ተግተህ መማርህን እንጂ ውጤትህን አታሰላስል፡፡
በሚገባ ብትማር ዕውቀት ካንተ ጋር ትሆናለች፣ ስትሰንፍ ደግሞ ትለይሃለች፡ ከጎበዝ ተማሪ እየቀዳህ (እየኮረጅህ) ለማለፍ አትሞክር፡፡ ይህ ለዘለቄታው የሚጠቅም አይደለምና፡፡ በዚህ ሁኔታ ካሰብክበት ለመድረስ አትችልም። ብትደርስም እንኳን የሚስጥህን ኃላፊነት በብቃት መወጣት አትችልም። በራስ የመተማመን ስሜትህ ይጠፋል። ደግሞም በኩረጃ ማለፍ ሁልጊዜ የሚሳካ ነገር አይደለም፤ ቢሳካም እንኳን ሌብነትንና ኃጢአትን መለማመድ ነው፡፡ ደግሞስ ራስህን ጐበዝ ማድረግ ካላወቅህበት ወደፊት ለሚያጋጥሙህ የሕይወት ጥያቄዎች ማን ሊያስኮርጅህ ይችላል? ለዚህ ችግር መፍትሔው ራስን ጐበዝ ማድረግ ብቻ ነውና ጠንክሮ መማር ይኖርብሃል፡፡
በመደበኛ ክፍለ ጊዜ የምትከታተለውን ትምህርት በሚገባ ካልተወጣኸው በኋላ ለመማር ቁጭት ቢያድርብህ እንኳን ብዙ እንቅልፋቶች ያጋጥሙሃል፡፡ በመጀመሪያ የምትፈልጋቸው ሥልጠናዎች እንተ ባለህ ውጤት በቀላሉ ላይገኙ ይችላሉ፡፡ ቢገኙም ብዙ ገንዘብ የሚያስወጡህ ሆነው ነው። ታዲያ መደበኛ ተማሪ እያለህ በሚገባ በመማር ዕድልህን ለምን አትጠቀምበትም? ተግተህ በመማርህ የምትጠቀመው አንተ ራስህ ነህ፡፡ «ሰው የሚዘራውን ሁሉ ያንኑ ደግሞ ያጭዳልና» የሚለው የመጽሐፍ ቅዱስ ቃል እንዲሁ የሚቀር አይደለምና፡፡ ገላ6፥7
ዕውቀት የሚገነባው ሌሎች ሰዎችን መሠረት በማድረግ ነው። ስለዚህ ከሌሎች ሰዎች ጋር ሳትነጋገር፣ የጻፉትን ሳታነብ፣ ወይም ትምህርትን ዓላማ አድርገህ ሲሠሩ ሳትከታተል ሌሎች ያገኙትን ዕውቀትና ልምድ ልትቀስም አትችልም፡፡ ይህን ሁሉ ለማድረግ ደግሞ በቂ ጊዜ ያስፈልግሃል:: ማወቅ የሚገባህን ነገሮች ሳታውቅ ከተቃራኒ ጾታ ጋር ወዳጅነት ብትፈጥር ምን እንደሚያስከትልብህ ታውቃለህ? ዕውቀት ከምትገበይባቸው ሰዎችና ነገሮች ጋር ያለህ ግንኙነት እንዲጠብ ወይም እንዲቋረጥ በማድረግ ትኩረትህ ወደ አንድ ፆታዊ አቅጣጫ ብቻ እንዲሆን ያደርግና በዕውቀት እንዳታድግ ትሆናለህ፡፡ ስለዚህ ይህን ከመሳሰለ አካሄድ ለጊዜው ብትቆጠብ እዕቀትን ከመራብ ትድናለህ:: ለሁሉም ጊዜ አለውና፡፡

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

ሕይወተ ወራዙት(የወጣቶች ሕይወት)
 ምዕራፍ ዐሥር ክፍል ሁለት
.................................................

የትኛው ይቅደም?
በዚህ ዘመን ለሚከሠቱ ልዩ ልዩ ወንጀሎች መበራከት መንሥኤው የዕውቀት ማነስ ሳይሆን የግብረ ገብነት መጉደል ነው፡፡ ይህንን ችግር በመጠኑም ቢሆን መንግሥት የተረዳው ይመስላል፡፡ ምክንያቱም እንደ ድሮው ሁሉ ዛሬም በየትምህርት ቤቱ የሥነ ዜጋ ትምህርት (ሲቪክ ኤጁኬሽን) እና የሥነ ምግባር ትምህርት መሰጠት ተጀምሯል፡፡ ይህም ቢሆን እግዚአብሔርን መፍራት አያሳድርምና ብቻውን ዓላማውን ሊመታ አይችልም፡፡
ሰው ሁሉ የመልካም ሥነ ምግባር ባለቤት እንዲሆን በመጀመሪያ እግዚአብሔርን መፍራት ይኖርበታል፡፡ እግዚአብሔርን መፍራት የሚገኘው ደግሞ ከመንፈሳዊ ትምህርት ነው፡፡ ቅዱስ ዳዊት «ልጆቼ ኑ ስሙኝ እግዚአብሔርን መፍራት አስተምራችኋለሁ» መዝ33፥11 በማለት የተናገረው ቃል ለዚህ ምስክር ነው፡፡ «ከእሾህ ወይን ከኩርንችትም በለስ» እንደማይለቀም ሁሉ ሰው ሁሉ እግዚአብሔርን እንዲፈራ ለማድረግ ዓላማ ይዞ ያልተቀረጸ ትምህርት ሁሉ እግዚአብሔርን ስለመፍራት ሊያስተምር አይችልም፡፡ ስለዚህ በጥሩ ሥነ ምግባር ተኮትኩቶ ለማደግ አስቀድሞ መንፈሳዊ ትምህርትን መማር ይገባል፡፡ «የጥበብ መጀመሪያ እግዚአብሔርን መፍራት ነውና›› ምሳ1÷7፤ መዝ110 ፥ 10

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅም ሥርዓተ መንግሥተ ሰማያትን በተናገረበት አንቀጽ ‹ሕፃናት ተወልደው እስከ ሰባትና አሥራ ሁለት ዓመታቸው ድረስ የሚያውቁት ዕውቀት ጻድቃን ከበቁ በኋላ እንደማያውቁት ዕውቀት ነው፡፡ እስከ ሃያና ሠላላ ዓመታቸው የሚያውቁት ዕውቀት ጸድቃን ከሞቱ በኋላ በገነት እንደሚያውቁት ዕውቀት ነው፡፡ እስከ ዓርባና ሃምሳ ዓመታቸው የሚያውቁት ዕውቀት ደግሞ ጻድቃን መንግሥተ ሰማያት ገብተው እንደሚያውቁት ዕውቀት ነው፡፡› በማለት በሃያዎቹና በሠላሳዎቹ ውስጥ የሚገኙ ወጣቶች ኸዕውቀት አንጻር በሞት ለሄዱና በገነት ላሉ ጻድቃን ምሳሌ እንደሚሆኑ አስረድቷል።(ዮሐ.አፈ.ተግ.8)
ይህ የወጣቶች ለጻድቃን ምሳሌ መሆን ወጣቶች ብሩህ አእምሮ እንዳላቸው የሚያመለክት ነው።ቀን ላለ በብርሃን መመላለስ ይሉሃል በወጣትነት መማር ነው።ወጣትነት ብሩህ ወቅት ነው። ኃላፊነቶች ያልበዙበት ሰው በመሆንህ ያለህን ነጻነት ለመማር ተጠቀምበት። ራስህን ጊዜው ባልሆነ የተቃራኒ ጾታ ግንኙ ነት ውስጥ ሳታስገባ ለመማር ጥረት አድርግ፡፡ በተጨማሪም ሌሎች ልዩ ልዩ ሱሶችና ልማዶች የወጣትነት ብሩህ አእምሮህን በአጉል ተስፋ እንደሚያጨልሙብህ አትጠራጠር።
ምንም እንኳን ሁሉም ወጣቶች ተመሳሳይ ዕድል ባይኖራቸው በሀገራችን ብዙ ወጣቶች ወላጆችና ትልልቅ ሰዎች ያሉባቸው ዓይነት ኃላፊነት የለባቸውም:: እንዲያውም አብዛኞቹ ወጣቶች በቤተሰቦቻቸው ትከሻ እየኖሩ እንክብካቤ የሚደረግላቸውና «የሚጦሩ» ናቸው፡፡ ስለዚህ እነዚህ ወጣቶች ከብዙ ኃላፊነት ነጻ መሆናቸውን ዐውቀው ዕድላቸውን ቢጠቀሙበት ለመማርና ዕውቀት ለመሰብሰብ ሰፊ ጊዜ ይኖራቸዋል። ሆኖም አብዛኞቹ ወጣቶች ያን ያህል ሰፊ ጊዜ እንደነበራቸው የሚያስተውሉት ጊዜው ካለፈ በኋላና ለመጠቀም የማይችሉበት ሁኔታ ውስጥ ሊገኙ መሆኑ እጅግ ያስቆጫቸዋል።
ትምህርት ትግልን ይጠይቃል፡፡ መታገሉን ብትሰለች ከትግሉ በኋላ የምታገኘውን ዘለቄታዊ ጥቅም ታጣለህ:: ስለዚህ ወጣት ከሆንክ ኋላ የምትቆጭበትና ከሰው የምታንስበት ጫወታና መዝናናት አታሎኽ ከመማር አትቦዝን። ለጊዜያዊ ደስታ ብለህ ዘለቄታዊ ጥቅምን ለምን ታጣለህ? መዝናናትና መደሰት ድሮም ነበሩ፣ የሚያልቁ ነገሮች አይደሉምና ወደፊትም ይኖራሉ፡፡ ስለዚህ በሌላ ጊዜ የምትደርስባቸው እነዚህ ነገሮች እንዳያዘናጉህ ተጠንቀቅ:: የወደፊት የሥጋህና የነፍስህ ዕጣ ምን ሊሆን እንደሚችል ከወዲሁ በጥንቃቄ አስብበት። ነቢዩ ኢሳይያስ «ወይስ ወሬ ማስተዋልን ለማን ይሰጣል?» ብሏልና ከወሬነት ለማያልፉ ነገሮች እየጓጓህ ትምህርትን ቸል እትበል፡፡ ኢሳ28÷9
ጠቢቡ ሰሎሞን ታካች ሰው ብትልከው «አንበሳ በመንገድ አለ» ይላል በማለት እንደተናገረው ላለ መማር ምክንያት አታብዛ። ምክንያት የሚያልቅ ነገር አይደለም። ለምንም ነገር ምክንያት ሊቀርብ ይችላል:። ከዚያ ይልቅ ለሰው የሚያዋጣው ምክንያትን በብርታት አሸንፎ ጠንክሮ መማር ነው፡፡ ብፁዕ አቡነ ዮሐንስ ቀዳማዊ አንዱን ወጣት ያለ ሥራ ስላዩት «ልጄ ለምን አትማርም?» ቢሉት እርሱም «አባታችን- ምን በልቼ?›› በማለት መለሰላቸው። ብፁዕነታቸውም ምክንያተኝነት እንደማይጠቅም በሚያስረዳ ቃል «ታዲያ አሁን እየደነቆርህ ያለኸው ምን እየበላህ ነው?›› በማለት መለሱለት ይባላል።
ላለመማር የትምህርት ፖሊስን፣ መምህራንን፣ ወላጆችን (ቤተሰብን)፣ ጾታን፣ የሥራ ጫናን፣ የጤና ሁኔታንና የመሳሰሉትን መኮነን ለማንም አልጠቀመም።የተሻለው መንገድ በራስ በኩል ያሉትን ድክመቶች አስወግዶ ተገቢውን ጥረት ማድረግ ብቻ ነው።ጥሮ በመማር መጠቀም እንጂ ቁጭ ብሎ ሌላውን ማማትና መተቸት ዐዋቂነት አይደለም።ስለዚህ በተቻለህ ሁሉ ጠንክረህ ተማር ከዐቅምህ በላይ የሆነውን ደግሞ ፈቃዱን አታውቅምና ለፈጣሪህ ተወው፡፡
እንኳን ከጨዋታና ከመዝናናት ይቅርና ከሥራም ቢሆን መቅደም ያለበት ትምህርት ነው።ዕውቀት ያልደገፈው ሥራ መሠረት እንደሌለው ቤት ነውና፡፡ ሥራ ያለህም ሰው ብትሆን የየዕለት መሠረታዊ ፍጆታህን ካገኘህ በኋላ ሐሳብህ ወደ ትምህርት ይሁን። ከተግባረ ሥጋም ሆነ ክተግባረ ነፍስ መቅደም ያለበት መማር ነውና፡፡
በራስ አነሣሽነት ከትምህርት ይልቅ ዋዛ ፈዛዛንና በልምድ የሚገኝ ዕለታዊ ተግባርን የመረጠ ሰው የኋላ ኋላ የሚያዝንበትና የሚያፍርበት ነገር ሳያጋጥመው አይቀርም:: ጠቢቡ ሰሎሞን ትምህርትን በልዩ ልዩ ምክንያት ሳይማር የቀረ ሰው ዘግየት ብሎ የሚሰማውን ስሜት እንዲህ በማለት ይገልጸዋል:- «በመጨረሻም ሥጋህና ሰውነትህ በጠፉ ጊዜ ታለቅሳለህ፡ ትላለህም፥ እንዴት ትምህርትን ጠላሁ ልቤም ዘለፋን ናቀ! የአስተማሪዎቼንም ቃል አልሰማሁም፡ ጀሮቼንም ወደ አስተማሪዎቼ አላዘነበልሁም።»ምሳ5:11-13
ይልቁንም ለመማር የሚያስችል ሁኔታ ተመቻችቶ ሳለ ለመሥራትና ንብረት ለማካበት መሽቀዳደም የከበረች ጥበብን ዋጋ ማሳጣት ነው፡፡ ከገንዘብ ተግሣጽ ይበልጣልና:: ተግሣጽ ደግሞ ጥበብም ትምህርትም ነው፡፡ ስለዚህ መጽሐፍ ቅዱስ «ተግሣጹን እንጂ ብርን አትቀበሉ፡ ከምዝምዝ ወርቅም ይልቅ ዕውቀትን ተቀበሉ፣ ጥበብ ከቀይ ዕንቁ ትበልጣለችና የከበረ ነገር ሁሉ አይተካከላትም፡፡» ምሳ8፥10-11 በማለት ትምህርት በገንዘብ እንደማይለካ ምስክርነቱን ይሰጣል፡፡ ሲራ6፥ 18-37

Читать полностью…
Subscribe to a channel