ethiopian_orthodox | Unsorted

Telegram-канал ethiopian_orthodox - የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

30344

በዚህ Channel ውስጥ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንን ዶግማ ፤ ቀኖና እና ትውፊት የጠበቁ ትምህርቶች ይተላለፉበታል፡፡ ለአስተያየት: ጥቆማና ጥያቄ በዚህ ያግኙን ☞ @Ethiopian_Orthodox_bot Buy ads: https://telega.io/c/Ethiopian_Orthodox

Subscribe to a channel

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

የትምህርት ዓይነቶች
ሐዋርያው ቅዱስ ያዕቆብ ምድራዊና ሰማያዊ፣ ሥጋዊና መንፈሳዊ በማለት ጥበብን በሁለት በመክፈል ጽፏል። ስለምድራዊ ጥበብ ሲናገር «ይህ ጥበብ ከላይ የሚወርድ አይደለም፣ ነገር ግን የምድር ነው፥ የሥጋም ነው» በማለት ሲገልጸው ሰማያዊውን ጥበብ ደግሞ «ላይኛይቱ ጥበብ ግን በመጀመሪያ ንጽሕት ናት፡ በኋላም ታራቂ፣ ገር፡ እሺ ባይ፥ ምሕረትና በጎ ፍሬ የሞላባት፥ ጥርጥርና ግብዝነት የሌለባት ናት፡፡›› በማለት ይገልጻታል። ያዕ3፥15(17) ጥበብ ለሁለት ወገን ተከፈለች ማለት ትምህርትም ለሁለት ይከፈላል። ምክንያቱም ጥበብ የሚገኝ ከትምህርት ነውና፡፡
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ደግሞ ትምህርትን ትምህርተ ክርስቶስና ትምህርተ ሰብእ (የሰው ትምህርት) በማለት ለሁለት ክፍለ አስረድቷል፡፡ ይህም «እንደ ክርስቶስ ትምህርት ሳይሆን፥ እንደ ሰው ወግና እንደ ዓላማዊ እንደ መጀመሪያ ትምህርት ባለ በፍልስፍና በከንቱም መታለል ማንም እንዳይማርካችሁ ተጠበቁ::» ባለው ይታወቃል።ቆላ2÷8
ስለዚህ መንፈሳዊውን ትምህርት የክርስቶስ ትምህርት፣ መንፈሳዊ፣ የቤተክህነት፣ ሰማያዊ፤ ጥንታዊ በማለት ስንጠራው ዘመናዊውን ትምህርት ደግሞ ዓለማዊ፣ ምድራዊ ፣ሰብአዊ፣ ወግ፣ ፍልስፍና፣ ሥጋዊ ትምህርት በማለት ልንጠራው እንችላለን፡፡
ከቤተ ክርስቲያን የጸሎት መጻሕፍት መካከል አንዱ የሆነው መስተብቁዕ መንፈሳዊውን ትምህርት «የመለኮት ትምህርት» በማለት ይጠራዋል፡፡ «ወሴሲ ልበነ በመለኮተ ትምህርት ወበለብዎ ዘእምኀቢከ» ፍችውም «በመለኮት ትምህርት ልቡናችንን መግብ፡ ከአንተ ዘንድ የሚገኘውንም ማስተዋል» ማለት ነው። (መስተብቁዕ በእንተ ዝናማት)
በአሁኑ ጊዜ ሥጋዊውን ትምህርት በሀገራችን ለማዳረስ ኃላፊነት የተሰጠው ክፍል በሚኒስቴሮች መሥሪያ ቤት የትምህርት ሚኒስቴር ሲሆን እውነተኛውን መንፈሳዊ ትምህርት ለዓለም እንድታዳርስ ከጌታችን ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ሙሉ ኃላፊነትና ትዕዛዝ የተቀበለች ቤተ ክርስቲያን ናት፡፡ ይሁን እንጂ ቤተ ክርስቲያን በሀገራችን ለመንፈሳዊውም ሆነ ለሥጋዊው ትምህርት መሠረት እንደ መሆኗ መጠን ዘመናዊውንም ትምህርት በሀገራችን ከማስፋፋት የቦዘነችበት ጊዜ የለም።
በሀራችን በኢትዮጵያ ዘመናዊ ትምህርት በማይታወቅበት ጊዜ እንኳን ቤተክርስቲያን መንፈሳዊ ትምህርቷን በአስደናቂ መልኩ ቀርጻ ከፍልስፍና (ከዘመናዊ ጥበብ) ጋር ጐን ለጐን ስታስተምር ቆይታለች።ከዚህም በተጨማሪ ለሀገርና ለአህጉር መኩሪያ የሆነ ብቁ ፊደል ቀርጻ ማስረከቧ ሳያንሳት የፊደላቱን ምሥጢር፣ መልክና ቅርጽ በማስለየት እስከዛሬ ድረስ ግንባር ቀደም ሚና እየተጫወተች ነው።ይህን ሁሉ የመረመረ ሰው ቤተ ክርስቲያን ለመንፈሳዊ ትምህርት ብቻ ሳይሆን ለሥጋዊ ትምህርት መሠረት መሆኗን ለማወቅ አይቸገርም፡፡
ሕንፃ ከማነጽ፣ ፍትሕት ከመፍታት፣ ከማጥመቅ፣ ከመቀደስ ይልቅ ቀዳሚው የቤተ ክርስቲያን ተልዕኮ ማስተማር ነው:: ማስተማርና ማሳመን ከሌለ እነዚህ ምሥጢራት በሙሉ ላላመነ ሰው የሚፈጸሙ አይደሉምና፡፡ እንዲያውም ቤተ ክርስቲያን የተመሠረተችው በትምህርተ ወንጌል ነው። «ሊቀ ማኅበር» የሚባል ኢየሱስ ክርስቶስ ሁለትም ሦስትም ሆነን በምንሰበሰብበት ጊዜ በመካከላችን ይገኛል፡፡ «ያዘዝኋችሁንም እንዲጠብቁ እያስተማራችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው እነሆም እኔ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ሁል ጊዜ ከእናንተ ጋር ነኝ» ማቴ28፥20፤18፥20 በማለት ከቃል ኪዳን ጋራ ቤተ ክርስቲያን በትምህርተ ወንጌል እንድትመሠረት የፈቀደ ራሱ ነውና፡፡
ስለዚህ ቤተ ክርስቲያን ማስተማር የዘወትር ሥራዋ ነው፡፡ ትምህርቷም የሕይወት ትምህርት ነው።ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ «እናት አባት ልጆቻቸውን የእነርሱ ለማድረግ ቢፈልጉ ለቤተ ክርስቲያን ይስጡ፡፡ ከደግ በቀር ክፉ ነገር አታስተምራቸውምና፡፡›› በማለት የቤተ ክርስቲያን ትምህርት ለልጆች ያለውን ጠቀሜታ አስረድቷል፡፡
የትምህርተ ወንጌልን አገልግሎት ቸል በማለት ለሌሎች መንፈሳዊ አገልግሎቶች ቅድሚያ የሚሰጡ የቤተ ክርስቲያን አካላት ቢኖሩ ዋናውን ጉዳይ ቸል ስላሉ ከዚህ ቀጥሎ ባለው የወንጌል ቃል ይገሠጻ።«በሕግ ያለውን ዋና ነገር ስለምትተዉ፡ ወዮላችሁ፤ ሌላውን ሳትተዉ ይህንን ልታደርጉ ይገባችሁ ነበር፡፡ እናንተ ዕውሮች መሪዎች ፡ ትንኝን የምታጠሩ ግመልንም የምትውጡ፡፡» ማቴ 23፥23
ዋናው የቤተ ክርስቲያን ተልዕኮ መንፈሳዊ ትምህርት ማስተማር ነውና።
ከቤተ ክርስቲያን ባሻገር ወላጆች ልጆቻቸውን «በተግሣጽና በምክር» የማሳደግ ኃላፊነት አለባቸው፡፡ ኤፌ6፥4 ሠለስቱ ምዕትም በሃይማኖተ አበው «ለልጆችህ አርምሞንና ጸጥታን አስተምራቸው፤ ሰነፍ አትሁን።›› በማለት ወላጆችን መክረዋል፡፡ ልጆቻችውን የማያስተምሩ ወላጆች ቅጣት እንደሚገባቸው ቅዱስ ባስልዮስ «ልጆችን መልካም ትምህርት ከማስተማር ቸል የሚሉ ወላጆች በሌላ በኩል ለልጆቻቸው ደግ ቢሆኑ በዚህ ብቻ ሊቀጡ ያስፈልጋቸዋል» በማለት ተናግሯል፡፡ አስቀድሞ እንደተገለጸው ሥጋዊና መንፈሳዊ ጥበባት በምድሪራችን ይገኛሉ፡፡ ሁለቱም በአቀራረባቸው፣ በዓላማቸውና በሚሰጡት ጠቀሜታ እጅግ ይለያያሉ። አንዳንድ ጊዜ የሚስማሙበት የጋራ ነጥብ ሲኖራቸው ብዙ ጊዜ ደግሞ እጅግ የሚቃረኑበት ቦታ አለ።ታዲያ ሰው አስቀድሞ መማር የሚኖርበት የትኛውን ትምህርት ነው?

ቀጣይ ምዕራፍ ዐሥር ክፍል ኹለት:
👉 «የትኛው ይቅደም»
👉«በሚገባ መማር»
👉«የትምህርት ጥቅም»
በሚል ይቀጥላል .....
ለጥያቄና አስተያየት @Ethiopian_Orthodox_bot ተጠቀሙ።

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

ሕይወተ ወራዙት(የወጣቶች ሕይወት)
 ምዕራፍ ዐሥር ክፍል አንድ
.................................................
➺ወጣቶችና ትምህርት

ትምህርት ዕድሜን አይወስንም። ለመማር ፍላጎት ያለው ሰው ሁሉ ለመማር ይችላል፡፡ ወጣቶች ግን ከሁሉ ይልቅ ባገኙት አጋጣሚ ተጠቅመው መማር ይኖርባቸዋል። ምክንያቱም ወጣትነት በሁሉም አቅጣጫ ለትምህርት ምቹ ወቅት ስለሆነ ነው።
በወጣትነት ዘመን ሰውነት እየጠነከረ የመሄዱን ያህል አእምሮ'ም እየሰፋና እየዳበረ ይሄዳል፡፡ መጽሐፍ ስለ ወጣቶች ሲናገር «በሠላሳ ዘመን ናላ ይመላል አእምሮ ይደላደላል» ይላል።(ሕዝቅኤል ትርጓሜ) ከዚህ ትርጓሜ ወጣትነት በራስ ቅል ውስጥ የሚገኝ የዕውቀት መገኛ (አንጐል) ወደ መጨረሻ የእድገት ደረጃው የሚደርስበት ጊዜ መሆኑን እንረዳለን፡፡ ስለዚህ ወጣቶች ለመማር ፈቃደኛ ከሆኑ ለማወቅ የተመቻቸ ተፈጥሮ አላቸው፡፡
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ «ልጅ ሳለሁ እንደ ልጅ እናገር ነበር፥ እንደ ልጅም አስብ ነበር፥ እንደ ልጅም እቆጥር ነበር፤ ጎልማሳ ሆኜ ግን የልጅነትን ጠባይ ሽሬአለሁ።» በማለት የተናገረው ቃል በልጅነት ዘመን ያለው ዐላዋቂነት በጎልማስነት ዘመን እንደሚሻርና በወጣትነት ዘመን ኣእምሮ እንደሚዳብር ያስረዳል፡፡ 1ቆሮ13:11 ይህ የዳበረ የወጣቶች አእምሮ ደግሞ የትምህርት ሂድትን ቀላል ያደርግላቸዋል፡፡
መጽሐፍ ጻድቃንን ከዕውቀት አንጻር በወጣት ሊመስላቸው ኃጥአንን ደግሞ በሕፃናት ይመስላቸዋል፡፡ ሕፃናት ፍትፍትና እሳት ለይተው እንደማያውቁ ኃጥአንም ክፉና በጎን ለይተው በማወቅ አይሠሩም:: ወጣቶች ግን ክፉና ደግን ለይተው እንደማያውቁ ጻድቃንም ጽድቅና ኃጢአትን ለይተው በማወቅ ይሠራሉ። ስለዚህ ወጣቶች ከዕውቀት አንጻር በጻድቃን ተመስለዋል፡፡ (ምሳ 1፣ 4 ትርጓሜ)

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

ስለ ወንድ «ወንድ ፀጉሩን ቢያስረዝም ነውር እንዲሆንበት፡ ሴት ግን ጠጉርዋን ብታስረዝም ክብር እንዲሆንላት ተፈጥሮ እንኳን አያስተምራችሁምን" በማለት ቅዱስ ጳውሎስ ተናግሯልና ወንድ ፀጉሩን ማስረዘም አይገባውም።ሠለስቱ ምዕትም ስለ ፀጉር በተናገሩበት በፍትሐ ነገሥት " ኢታስተርኢ ስእርተከ በአፍኣ» ብለዋል፡፡ ይህም ፀጉርህን ስበህ እስክታየው ድረስ አታሳድገው» ማለት ነው::
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ስእለት ስለ ነበረበትና አይሁድም ስለ እርሱ ያላቸውን የተዛባ አመለካከት አስተካክለው ሥርዓትና ሕግ ኣክባሪ መሆኑን እንዲያውቁ ለማድረግ ሁለት ጊዜ ፀጉሩን ተላጭቷል፡፡ የሐዋ21፥24፤ 18÷18 ሠለስቱ ምዕት ከዚህ ተነሥተው ወንዶች ይልቁኑም ካህናት ፀጉራቸውን እንዳያሳድጉ ሥርዓት ሠርተዋል።
ቅዱስ ጳውሎስ ስእለት ስለነበረበት ተላጨ እንጂ ተላጩ ወይም ጸጉራችሁን አሳጥሩ የሚል ሥርዓት የለም ማለት አይገባም።በእርግጥ ቅዱስ ጳውሎስ የተላጨው ለትሩፋት ብሎ ነው።ምክንያቱ ስእለት የነበረ ቢሆንም «የቅዱስ ጳውሎስ ሥራ ሥርዓት ለመሆን አያንስም።» በማለት አበው ሠለስቱ ምዕት ወንዶች ፀጉራቸውን እንዳያስረዝሙ ሥርዓት አድርገው ጠቅሰውታል፡፡
ወንዶች ይልቁኑም ካህናት ፀጉራቸውን አያሳድጉ የሚለው ትእዛዝ ናዝራውያንን አይመለከትም። በመጽሐፍ ቅዱስ እንደ መልከ ጼዴቅ፣ ሶምሶን፣ ነቢዩ ኤልያስና መጥምቁ ዮሐንስን የመሳሰሉት ናዝራውያን ጸጉራቸውን አይላጩም ነበር፡፡ ዘኁ6፥5፤ መሳ13÷5
ወንዶች ፀጉራችንን እንድናሳጥረው ብቻ ሳይሆን በምናሳጥረበት ጊዜም ጋሜ፣ ቁንጮ እያልን ጌጥና ልዩ ልዩ ቅርጽ እንዳናወጣ ታዘናል። አበው ወኢትኅድግ ላዕሊከ ሥርጋዊ እም ጸጉረ ርእስከ» ብለዋል። ይኽም «በፀጉርህ ላይ ጌጥ አትተው» ማለት ነው።
በሐዋርያት ዘመን የነበሩ ሴቶች ረጅም ፀጉራቸውን በመጠቀም እንደ ስጋጃ በመሥራትና ለጣዖት በመጋረድ ለባዕድ አምልኮ እስከ መጠቀም ደርሰው ነበር። ይህ የሚያሳየው ፀጉር ተገቢ ላልሆነ ልዩ ልዩ አላማ ሊውል መቻሉን ነው። ስለዚህ ወንዶች ፀጉራቸውን በማስረዘም ትኩረት ለመሳብና ለልዩ ልዩ ዓላማ ቢጠቀሙበት መጨረሻቸው ላያምር ይችላል፡፡
አቤሴሎም የተባለው የንጉሥ ዳዊት ልጅ ቆንጆ መልኩን ፀጉሩን ከማስረዘም ጋር አስተባብሮ የብዙዎችን ቀልብ ለመሳብ ችሎ ነበር። ይህንኑ ማራኪነት ደግሞ የገዛ አባቱን ከዙፋኑ ለማባረርና ብዙ ድምፅ ለማግኘት ተጠቅሞበታል።ሙከራው ለጊዜው የተሳካለት ቢመስልም በመጨረሻ ግን መጥፊያው የሆነው ወዶ ያስረዘመው የራሱ ፀጉር ነበር። መጽሐፍ ቅዱስ የአቤሴሎምን አሟሟት እንዲህ ይተርከዋል።«አቤሴሎም በበቅሎ ተቀምጦ ነበር ፣ በቅሎውም ብዙ ቅርንጫፍ ባለው ከታላቅ ዛፍ በታች ገባ፣ ራሱም (ፀጉሩም) በዛፉ ተያዘ ፤ በሰማይና በምድር መካከል ተንጠለጠለ።..... ኢዮአብም.... ሦስት ጦሮች በእጁ ወስደ፣ አቤሴሎምም ገና በዛፍ ላይ ተንጠልጥሎ ሕያው ሳለ በልቡ ላይ ተከላቸው ዐሥሩም የኢዮአብ ጋሻ ጃግሬዎች ከበቡት አቤሴሎምንም መትተው ገደሉት::» 20ሳሙ 18÷9-15
ከዚህ መንፈሳዊ ታሪክ በመነሣት ወጣት ወንዶችና ሴቶች ስለ ፀጉራቸው በሚገባ ማሰብና ሥርዓት ባለው መልኩ መያዝ ይኖርባቸዋል።ከዚህ አልፎ ግን ከዘመኑ ፋሽን ጋር እንደፈለጉ ፀጉራቸውን ቢለዋውጡ በኅብረተሰብ ዘንድ በብልሹ ስም ከመታወቅ አንሥቶ በልዩ ልዩ መንገድ ሳይጎዱበት አይቀርም።እንደ አለባበስ ሁሉ የፀጉር አያያዝም ስለማንነት አፍ አውጥቶ ይናገራልና።
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ" ሁሉ በእናንተ ዘንድ በአግባብና በሥርዓት ይሁን" በማለት መክሮናል። በክርስትና ሥርዓት የሌለው ነገር የለም።ነገር ግን አንዳንዶች ስለ አመጋገብ፣ አለባበስ፣ ፀጉር አበጣጠርና የመሳሰሉ ነገሮች የተሠሩትን ሥርዓቶችና መመሪያዎች ሲመለከቱ በሥርዓት መኖርን ያልለመዱ ከሆነ ነጻነት እንደማጣት፣ መብትን እንደመገፈፍና ብዙ አማራጮች እንደማጣት አድርገው ይቆጥሩት ይሆናል።ነገር ግን በመንፈሳዊ ዓይን ለሚመለከተው ደግሞ ምልከታው የተገላቢጦሽ ነው።ክርስቲያኖች በሥርዓት አየኖሩ ነገር ግን ስለ ፀጉር አበጣጠርና ስለ አለባበስ እጅግ ብዙ ከሥርዓት ውጭ አማራጭ እንዳለ ያውቃሉ። ጥያቄውንም የመንፈሳዊነት እንጂ የመብት ጉዳይ አለመሆኑን ይረዳሉ፡፡ ምክንያቱም ለፈጣሪ ስለ መገዛት ንቆ በመተው እንጂ እንደ ክርስቲያኖች ነጻ ፍጥረት ሊኖር እንደማይችል ያስተውላሉና።
ወጣቶች በሙሉ ለማንኛውም ነገር ከመንፈሳዊነት ሳይናወጹ ሊያገኙት የሚችሉት ብዙ አማራጭ መኖሩን ማወቅ ይገባቸዋል።ይልቁንም ብዙ ነገሮች በዓይነትም ሆነ በመጠን በብዛት በሚገኙበት በዚህ ዘመን የክርስትና ጎዳና ጠባብ አይደለችም። እንደ ዓለማዊ ነገሮች ሁሉ መንፈሳዊ ነገሮችም መሠረታቸውን ሳይለቁ ዘመናዊና ምቹ ሆነው በቀላሉ እንደሚገኙ ከማንም የተሠወረ አይደለም። ልዩነቱ የምርጫ ጉዳይ ብቻ ነው።ስለዚህ መንፈሳዊነት የኑሮ አማራጮችን ያጠባል ማለት አሮጌ አስተሳሰብና ጊዜ ያለፈበት ስለሆን በዘመናዊ አስተሳሰብ መለወጥ አለበት።

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

ስለ መጋጌጫ ነገሮች ምን ይባላል?
ሰዎች ልብስ የሚለብሱት በዋናነት ሰውነታቸውን ለመሸፈን ቢሆንም በሌላ ዘንድ አምሮ ለመታየት መርጦ መልበስም ተቆጥሮለታል፡፡ የጥንት ዕብራውያን የሚጠጋቸውን ሁሉ ለመማረክ አዘወትረው ሽቶ ይቀቡ፣ ቅባቶችንና መኳኳያዎችን ይጠቀሙ እንደ ነበር መጽሐፍ ቅዱስ ይመሰክራል።
ሆኖም በእግዚአብሔር ፊት ሞገስ የሚያመጣላቸውን ነገር ማድረግ የሚፈልጉ ወጣት ሴቶች ዋና ጌጣቸው «በእግዚአብሔር ፊት ዋጋው እጅግ የከበረ የዋህና ዝግተኛ መንፈስ» መሆን አለበት፡፡ በተጨማሪም ምንም ነገር ቢሆን በልክና እጅግ ባልተጋነነ መልኩ መሆን እንዳለበት አለመዘንጋት ይጠቅማል፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ «ነገርን ሁሉ በልክ» እንድናደርግ መክሮናል፡፡ 2ጢሞ4÷5
ሌላው ወጣት ሴቶች ሁሉ ማወቅ ያለባቸው ከጥቅማቸው ይልቅ ጉዳታቸው እንደሚያመዝን ነው።መዋቢያ ቅባቶች ጥሩውን ደም ግባት ሊያበላሹ ወይም መልከ ጥፉነትን የባሰ መጥፎ ሊያደርጉት ይችላሉ፡፡ በተጨማሪም መጋጌጫ ቅባቶች ከማሳመር በስተጀርባ የሚበልጠውን የተፈጥሮ የወጣትነትን የፊት ጥራት፣ ወዝንና ቁንጅናን የሚደብቅና የሚያበላሽ ጎጂ ጎን አላቸው::
ልጃገረዶች በመዋቢያ ቅባቶች ያለ ልክ መጠቀማቸው ወደ ደካማ ጎናቸው ትኩረትን ከመሳብ ያለፈ ጠቀሜታ የለውም።በተጨማሪም እንዲህ ማድረጋቸው በአንድ በኩል በሌሎች ዘንድ በመጥፎ እንዲተረጎምባቸው ሲያደረግ በሌላ በኩል ደግሞ ከጊዜ በኋላ በውጫዊ መልካቸው ባስተዋወቁት ወይም ባሳዩት ርካሽ አምሳል ጠባያቸው እንዲቀረጽ ተፅዕኖ ሊያደርግባቸው ይችላል።
ኩል፣ ቅባት፣ የጥፍርና የፀጉር ቀለም፣ እንሶሰላና የመሳሰሉትን ነገሮች በሚመለከት እንዲጠቀምባቸው በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የተጠቀሱ ነገሮች ባይኖሩም ጥሩ ጥሩ መመሪያዎች ግን ተሰጥተዋል፡፡ ሌሎች ቅዱሳት አዋልድ መጻሕፍትም የሚሻለውን መንገድ ሳይጠቁሙ አላለፉም።ለምሳሌ፦ የመልክዓ ማርያም ደራሲ ድንግል ማርያምን ሲያወድሱ «ሰላም ለአጽፍረ እግርኪ ዘኢፈቀዳ ለሥርጋዌ ጥምዓታተ ኅምር ምድራዊ » ብለዋል፡፡ ትርጓሜው «እንሶስላ መሞቅና ሌላ ምድራዊ ጌጥን ላልፈቀዱ የእግር ጥፍሮችሽ ሰላምታ ይገባል» ማለት ሲሆን ይህም አፍአዊ ጌጣጌጥን አለመሻት የሚያስመሰግን ቁጥብነትና ግብረ ገብነት በሆኑን ያስረዳል፡፡ ስለዚህ ልጃገረዶች ይህን በተመለከተ ሚዛናዊ ሆኖ መገኘት ይኖርባቸዋል፡፡ (መልክዐ ማርያም)
መጋጌጫን በተመለከተ ወላጆች ለልጆቻቸው ተጨማሪ መመሪያዎች የማወጣት ተገቢ የወላጅነት መብት አላቸው።አንድ ቤት ባለቤቶችን ከሚወክለው በላይ ልጆች ወላጆችን ይወክላሉ።በወላጆቻቸው ስም ይጠራሉና፡፡ ስለዚህ ልጆች የሚሠሩት ሥራ በሙሉ አሳዳጊዎቻቸው ምን ዓይነት ስብእና እንዳላቸው ሊናገር ይችላል፡፡ ከሁሉም በላይ ግን ክርስቲያን ነን እስካሉ ድረስ በስሙ የተጠሩበትን ኢየሱስ ክርስቶስንም ይወክላሉ፡፡ ስለሆነም ወጣቶች «አለባበሴና የሰውነቴ አቋም ከወላጆቼ ክብርና ማንነት ይልቁንም ከክርስቲያንነቴ ጋር ይስማማልን?› በማለት ራሳቸውን መጠየቅ አለባቸው። አንድ ቤት ፈርሶና ተላልጦ ቢታይ ባለቤቱን አንደሚያስነቅፍ የክርስቲያኖች ሕይወት ቤተ ክርስቲያንንና ወላጆቻቸውን ሊያስነቅፍ ይችላል፡፡ የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች አባል ለሆኑበት ሰንበት ትምህርት ቤት ደንብና ሥርዓት ተገዢ ቢሆኑና ባያምፁ እጅግ ተጠቃሚ ይሆናሉ፡፡ አንዳንድ ሰንበት ትምህርት ቤቶች ስለ አለባበስና ስለመሳሰሉት ሥነ ምግባራት ደንብ እንዳላቸው የታወቀ ነው።

ቀጣይ ምዕራፍ ዘጠኝ ክፍል ስድስት:
👉 ክርስቲያናዊ ፀጉር አያያዝ እንዴት ነው?
👉 ስለ <መልክ> ሊኖር የሚገባ ተገቢ አመለካከት
በሚል ይቀጥላል .....
ለጥያቄና አስተያየት @Ethiopian_Orthodox_bot ተጠቀሙ።

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

«ሴት የወንድ ልብስ አትልበስ› ሲል ሱሪ አትልበስ ማለቱ ብቻ ከሆነ ከሁለት ዓይነት ነገር (ቀለም) የተሠራ ልብስ አትልበስ›› ሲልስ ምን ማለቱ ነው? የሚል ጥያቄ ያስነሣል፡፡ እስኪ ንባቡን ቆም አድርገውና ከላይ እስከ ታች የለበስከው ልብስ ስንት ዓይነት ነገር (ቀለም) እንዳለው ቁጠረው:: ታዲያ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ያለው ይህን አለባበስህን ለመንቀፍ ነውን? አይደለም።«ከሁለት ዓይነት ነገር (ቀለም) የተሠራ ልብስ አትልበስ› ማለቱ ሁለት ዓይነት ሰብእና አትላበስ፡፡ በተጨማሪም «በአንድ ራስ ሁለት ምላስ› እንደሚባለው ቃሉና ሐሳቡ ተለዋዋጭ የሆነ ሁለት ዓይነት ሰው አትሁን ማለቱ ነው።ይህን የመሰለ «ከተልባ እግርና ከበግ ጠጉር በአንድነት የተሠራ ልብስ አትልበስ» የሚል ትእዛዝም አለ፡፡ ስለዚህ መጽሐፍ ቅዱስ አርእስትና ኅዳጉ እየታየ በሚገባ ይተረጎማል እንጂ በዘፈቀደ የሚነገር አይደለምና መጠንቀቅ ያሻል። ዘዳ22፥11፣ Ηሌ19:19
ይህ የመጽሐፍ ቅዱስ ቃል በዚህ መልኩ በመተርጎሙ ጠባብ አመለካከት ያላቸው እጅግ በጣም በርካታ ሴቶች ሱሪ ለመልበስ መግቢያ ያገኙ ይመስላቸው ይሆናል፡፡ ምክንያቱም አብዛኞቹ ሴቶች «ሴት የወንድ ልብስ አትልበስ› የሚለውን ቃል የሚረዱት "ሴት ሱሪ መልበስ አይገባት"እንደሚል ብቻ አድርገው በመሆኑ ነው።ከዚህ ቀደም «ሱሪ» የማይለብሱ ሆነው ይህን ትርጓሜ በማወቃቸው ብቻ «ሱሪ» ለመልበስ የሚነሣሡ ሴቶች እውነት አይነገረን ከተነገረን ግን ዋ! የሚል ዓላማ አንግቦ ሰልፍ የሚወጣን ሰነፍ ሰው ይመስላሉ፡፡
ከላይ የተጠቀሰው ቃል ትርጓሜውን በዚህ መልኩ በግልጽ ማስቀመጥ ያስፈለገበት ምክንያት የቃሉን ምሥጢራዊ ፍቺ ባለማወቅ ብዙዎች «ሱሪ» በሚለብሱ ሴቶች ላይ ያላቸው አመለካከት የተዛባ በመሆኑ አመለካከታቸውን ለማረም እንዲችሉ ነው።አንዲህ ዓይነት ሰዎች ፍርድና ትችት ስለሚያበዙ የእነርሱን አስተሳሰብ ለመገሠጽ ትርጓሜው ተጻፈ እንጂ ሴቶች ሱሪ ይልበሱ ለማለት እንዳልሆነ ልብ ማለት ይገባል።አሁንም ቢሆን ሴቶች ሱሪ አለመልበሳቸው በብዙ መንገድ ጠቃሚ መሆኑንና የመልካም ማንነታቸው መሆኑን መዘንጋት የለባቸውም። በማኅበረሳባችን ዘንድ ሱሪ የወንዶች ልብስ መሆኑ በአብዛኛው ሰው ዘንድ ታምኖ ሳለ ሴቶች ሱሪ ቢለብሱ አርአያን መለወጥ ስለሆነ ስሕተት ከመሆኑም ባሻገር ተረማማጅ (ተለዋዋጭ) ዐመልንና ባሉበት ነገር ያለመወሰንን ሁኔታ የሚያመለክት ነው።

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

"ማርያም አንቲ"
ማርያም አንቲ ደመና ሰማይ ዘአኃዝኪ ዝናመ(፪)
ተክላተ መሬት አዳም ወሔዋን ዘፈረዩ ብኪ ዳግመ(፪)

ከመሬት የተገኙ አዳምና ሔዋን ሕይወት ያገኙብሽ(፪)
ዝናምን የያዝሽ የሰማይ ደመና ማርያም አንቺ ነሽ(፪)
በማኅበረ ቅዱሳን መዘምራን

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

ግንቦት ፳፩
ደብረ ምጥማቅ


ከሠላሳ ሶስቱ የእመቤታችን በዓላት አንዱ ነው። ደብረ ምጥማቅ በግብፅ ሀገር በምኔተ ገምኑዲ አቅራቢያ የምትገኝ ቦታ ናት። እመቤታችን በስደት ሳለች ጌታ በዚህ ቦታ በስምሽ ዐብይ ቤተ ክርስቲያን ይታነጻል፤ ስሙንም ደብረ ምጥማቅ ይሉታል ብሎ ነግሯት ነበር። ይኸውም አልቀረ፤ በዚሁ ቦታ በእመቤታችን ስም ቤተክርስቲያን ታንጾ ስሙ ደብረ ምጥማቅ ተብሏል።

በዚህም ዕለት እመቤታችን ከፀሐይ ሰባት እጅ አብርታ ከጉልላቱ ላይ በመንበረ ብርሃን ተቀምጣ መላእክት ሊቃነ መላእክት ከበው ሲያመሰግኗት ነቢያት ሐዋርያት ጻድቃን ሰማዕታት እጅ ሲነሷት ታይታለች። “እንዘ ትበርቂ በደብረ ምጥማቅ ኃምሰ ዕለታተ” እንዳለ ደራሲ በልጇ የመለኮት ብርሃን አሸብርቃ መላእክት: ሊቃነ መላእክት: ኪሩቤል: ሱራፌል ከበዋት ነቢያት: ሐዋርያት: ሰማዕታት: ደናግላን: መነኮሳት ሄሮድስ ያስፈጃቸው ሕፃናት ይመጣሉ። ሱራፌል ማዕጠንት ይዘው በእያንዳንዱ እያመሰገኑ ያጥኑ ነበር። ከሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስ በነጭ ፈረስ ተከትሎ ቅዱስ መርቆርዮስ በጥቁር ፈረስ በየተራ እየመጡ ይሰግዱላታል።

ከፊቷ ብርሃን የተነሣ 5 ቀን ሌሊቱና ቀኑ አይታወቅም ነበር። በዚህ ጊዜ ልብሳቸውን ወደ ላይ ሲወረውሩላት የፈቀደችውን ተቀብላ ትልክላቸዋለች። ከዚያም ለበረከት ይካፈሉታል። ከተሰበሰቡትም እስኪ እገሌን አስነሺልን እያሉ ሲለምኗት አስነሥታ በሕይወተ ሥጋ ታሳያቸው ነበር። እንዲህ እየሆኑ በፍጹም ደስታ ሰንብተዋል። እስከ አምስት ቀንም ምዕመናኑን አረማውያኑንም አንድ ወገን አድርጋ ስትባርክ ሰንብታለች። ከዚህም በኋላ ምዕመናኑም አረማውያኑም በየዓመቱ እኚህን አምስት ዕለታት በደብረ ምጥማቅ ተሰብስበው የሚያከብሩ ሆነዋል። የበዓሉ መታሰቢያ ከግንቦት 21 እስከ 25 ቀን ነው።

ግንቦት 21 በደብረ ምጥማቅ በገሃድ ተገልጻ ታላቅ ተአምር ያደረገችበት፡፡

ግንቦት 22 በደብረ ምጥማቅ ለተሰበሰቡ ምእመናን በግልጽ በመታየት ትነጋገራቸው ነበር፡፡

ግንቦት 23 በደብረ ምጥማቅ ለተሰበሰቡ ምእመናን በግልጽ በመታየት ትነጋገራቸው ነበር፡፡

ግንቦት 24 እመቤታችን ተወዳጅ ልጇን ይዛ ከአረጋዊ ዮሴፍና ሰሎሜ ጋር በመሰደድ ግብፅ አገር የገባችበት ዕለት፡፡

ግንቦት 25 ተወዳጅ ልጇ የደረቁ በትሮችን ተክሎ በተአምራት ያለመለመበት ዕለት፡፡

በዚህ ዕለትም እናታችን፣ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በደብረ ምጥማቅ ለ5 ቀን በግልጽ መታየቷ የሞቱት መነሳታቸው ብርሃን መሆኑ ጨለማ መጥፋቱ የሰውን ልመና መቀበሏ ወዘተ ይነገራል። የቅድስት እናታችን ረድኤት በረከቷ አማላጅነቷ አይለየን፣ ጣዕሟን ፍቅሯን አይለይብን። የዓመት ሰው ይበለን፣ አሜን!
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
“ድንግል ሆይ በሁሉ አንደበት መመስገን የተገባሽ ስለሆነ በሰማይ ካሉ መላእክትና በምድር ከሚኖሩ ደቂቀ አዳም ሁል ጊዜ ምስጋና ይቀርብልሻል።” ቅዳሴ ማርያም

“ሰላም ለእለ ርእዩኪ ከመ ዐይነ ወለት ኀበ እማ፣
መዋዕል ኃምስ እስከ ይትፌጸማ፣
ማርያም ንግስት ዘደብረ ምጥማቅ ከተማ፣
ብፁዓት አዕይንት ዘነጸራኪ በግርማ፣
ወብፁዓት አእጋር ቅድሜኪ ዘቆማ።” እን ዐርኬ
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
ምንጭ፡ መዝገበ ታሪክ 2 ገጽ 87፣ መድብለ ታሪክ ገጽ 383

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

ምስባክ፦
ዐረገ እግዚአብሔር በይባቤ ፤
ወእግዚእነ በቃለ ቀርን፤
ዘምሩ ለአምላክነ ዘምሩ።

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

አፍአዊ ጌጥን መውደድ «አምልኮ ጣዖት ነው!» የሚባለው ለምንድር ነው?
መታበይ፣ መኩራራት፣ ማማረርና፣ ተስፋ መቁረጥን የመሳሰሉ ኃጢአቶች በሙሉ በአብዛኛው አፍአዊ ጌጽን ከመውደድ ይወለዳሉ:: ሰዎች ይህን ሲያገኙ እንደሚኮሩና ደስ እንደሚላቸው ሁሉ ያጡትም እንደ ሆነ በሕይወታቸው አንድ ታላቅ ነገርን እንዳጡ በመቁጠር ያለ መጠን ሲማረሩና ሲያዝኑ ይገኛሉ:: አልፎ ተፈርሞ በተገቢው መንገድ የሚሹትን አፋአዊ ጌጽ ካላገኙ በመስረቅ፣ በመዋሸትና ፍላጎታቸውን ሊያሟሉ ለሚችሉ ሀብታም ሰዎች በመገዛት ያሟሉታል።ይህ መገዛታቸው ልክ በማጣቱ ሐሳባቸው ይሟላላቸው ዘንድ ለዝሙት ከመንበርከክና ከመግደል አንሥቶ ለማንኛውም የኃጢአት ተግባር ወደ ኋላ አይመለሱም፡፡ ሊያገቡት የመረጡትንና ያጩትንም ሰው የጌጥ አምሮታቸውን ባለሟሟላቱ ብቻ እስከ መካድ የሚደርሱበት አጋጣሚ እጅግ ብዙ ነው:: በዚህ ምክንያት አፍአዊ ጌጽ መውደድን እንደ ጨካኝ ጌታ ስንቆጥረው ጌጽ ወዳጅዋን ሴት ደግሞ የሥጋና የዓለም ታማኝ ሎሌ እንላታለን፡፡ ለምን ቢባል ጌጥ በመውደዷ ብቻ የማትፈልገውን ኃጢአት ሁሉ ትሠራለችና፡፡
አንቺ ሴት እንደ ሌሎች ሴቶች ለማጌጥ አቅም በማጣትሽ ለምን ታዝኛለሽ? ፈጣሪሽ ለጌጣጌጥ በባርነት ከመገዛት ነጻ ስላወጣሽ ታዝኛለሽን? አንድ ሰው መዝገቡን ተግተሽ አንድትጠብቂ ቢያዝሽ እጅግ ታዝኚ ነበር፡፡ ከዚህ ይልቅ ግን የጌጣጌጥሽን ጉዳይ ለመሟላት የምታደርጊው ጥንቃቄና ዝግጅት ይከብዳል፡፡ ታዲያ ለጌጣጌጥ በመገዛት ራስሽን በጽኑ ማሠሪያ ለምን ታሥሪዋለሽ? ጠፍቶብሽ ከመደንገጥ፣ እዘረፋለሁ ከማለት፣ ግድ ለማያስፈልግ ነገር ከፍተኛ ባጀት ከመመደብ፣ ጊዜ ከማባከን፣ በጌጥ ምክንያት የሰው እጅ ከማየት፣ ወዘተ ነጻ እንደ መሆን ምንም አይገኝም:: ማጌጫ አጣሽ ማለት ከእነዚህ ሁሉ ክፉ ነገሮች ነጻ ወጣሽ ማለት ነውና፡፡
ጌጽ መውደድ ባርነት ብቻ ሳይሆን <ጣዖት አምልኮ> ም ነው።ነፍስ በጽኑ ፍቅር የታሠረችበት ከሆነ ሁሉም ነገር ወደ አምልኮት ይሄዳልና፡፡ ታዲያ አንቺ ያለ ጌጽ ምንም ነገር የማይሆንልሽ፣ ጌጥሽን ልጆችሽና አገልጋዮችሽ አንኳን ሊነኩት ሊያዩት የማታደርሻቸው ከሆነ፣ ለራስሽ እንኳን ልታጌጭበት የምትሳሽለት፣ ለሌላ ማዋስማ ፈጽሞ የማይታሰብ ነገር ከሆነብሽ ከዚህ የበለጠ «ጣዓት አምልኮ» ከወዴት ይመጣል? በቀን ዐሥር ጊዜ ሣጥን ከፍተሽ የምትመለከቺው፣ ዕጣን የምታጥኚው፣ ሽቶ የምትቀቢው፣ አጥፈሽ የምትዘረጊው፣ የምታናፍሽው፣ ብታውሺው እንኳን ጠባይሽን ዐውቀው «ያጅሪት ገንዘብ» እያሉ ያዋስሻቸው ሰዎች እንዳንቺ የሚጠነቀቁ ከሆነ ትንሽ ቢበላሽባቸው ደግሞ ጥፋታቸውን የማትታገሻቸው ከሆነ ያ ነገር ላንቺ «ጣዖት» ነው ቢባል ይበዛበታልን? በፍጹም አይበዛበትም:: ምክንያቱም መምለኪያነ ጣዖታት (ጣፆታትን የሚያመልኩ ሰዎች) ጣዖትን እንደሚንከባከቡት አንቺም ጌጣጌጥሽን የምትንከባከቢው እንደነርሱ ነውና።
በተመሳሳይ መልኩ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ለአፍአዊ ጌጽ የሚሳሱ ሰዎች ከጣዖት አምላኪ ጋር እንደሚቆጠሩ የቅዱስ ጳውሎስን ቃል ጠቅሶ ተናግሯል፡፡ «እስኩ ንግረኒ ኢኮነሁ ርቱዐ ቃለ ሐዋሪያ ሶበ ይሰምዮ ለስሱዕ ከመ መምልኬ ጣዖት» ይህም ወደ አማርኛ ሲመለስ «እስኪ ንገረኝ ሐዋሪያው ጣዖት የሚያመልኩትን በነቀፈበት አንቀጽ «አው ዐማፂ (ዐመፀኛም ቢሆን)» ብሎ በምንዝር ጌጥ (በትውዝፍት) እና በፍቅረ ንዋይ የታሠሩትን ሰዎች አያይዞ መንቀፉ የሚገባ አይደለምን? ጣዖት አምላኪዎች ጣዖታትን እንደሚያከብሯቸው «ከማሁ እሉሂ ያከብሩ አልባስ ወንዋየ፤ እንዲሁ እነዚህም ልብስንና ገንዘብን ያከብራሉና›› ማለት ነው:: ተግሣጽ ዘዮሐ አፈ.20
እስራኤላዊያን ጭቃ በመርገጥ ኖራ በመውቀጥ ለግብፅ ንጉሥ ይገዙ ነበር፡፡ እኅቶቻችንም ርጉም ሰይጣንን ለማስደሰት ለአፋዊ ጌጣጌጥ ብዙ ይጨነቃሉ፡፡ ከፈርዖን አገዛዝ ለአፋአዊ ጌጣጌጥ መገዛት ይከፋል።ያ ሥጋዊ ነውና፤ ለጌጣጌጥ መገዛት ግን በቀጥታ ለዲያብሎስ መገዛት ነው።ሆኖም እግዚአብሔር የራሔልን ዕንባ ተመልክቶ እስራኤላዊያንን እንደታደጋቸው እኛም ንስሐ ብንገባና ስለ ኃጢአታችንም መሪር ዕንባን ብናነባ የነፍሳችንን ኀዘን ተመልክቶ ለቁሳቁስ ከመገዛት ፈጣሪያችን ነጻ ያወጣናል፡፡ ዕንባችንን አይቶ የሚልክልን ጸጋም ሊቁ «ይፌኑ ለነ ቃሎ ወረድኤቶ ወፈሪሆተ ) ዚአሁ» እንዳለ «ቃሉን ትእዛዙን ፣ ረድኤቱን እርሱን መፍራትንና ሰውን ማፈርን ያሳድርብናል እንጂ ፤ ሙሴና አሮንን አይደለም፡፡» በዚህ ጊዜ በግብፅ ከተመሰለች ኃጢአት ሙሉ በሙሉ ነጻ እንወጣለን ፤ መልካምና ክፉንም ለይተን እናውቃለን፡፡
ቀጣይ ምዕራፍ ዘጠኝ ክፍል አምስት :
👉 «ሴት የወንድ ልብስ አትልበስ» ሲል ምን ማለቱ ነው?
👉 ሴቶች ሱሪ መልበስ ይችላሉ?
👉 ስለ መጋጌጫ ነገሮች ምን ይባላል?
በሚል ይቀጥላል .....
ለጥያቄና አስተያየት @Ethiopian_Orthodox_bot ተጠቀሙ።

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

ሕይወተ ወራዙት(የወጣቶች ሕይወት)
 ምዕራፍ ዘጠኝ ክፍል ዐራት
.................................................

➺አለባበስሽ ስለ አንቺ በደንብ ይናገራል!
አለባበስሽና ውጫዊ ቁመናሽ ከውስጥሽ ምን ዓይነት ሰው አንደ ሆንሽ መቶ በመቶ ባያስረዳም የቀረበ ግምት ለመስጠት ይረዳል፡፡ ሕፃን ሳለሽ አለባበስሽ ምን ዓይነት ሰው እንደሆንሽ ብዙም አይናገር ኖሮ ይሆናል፡፡ ልብሶችሽን የሚመርጡልሽና ፀጉርሽንም የሚያበጥሩልሽ አሳዳጊዎችሽ ናቸውና፡፡ እያደግሽ ስትሄጂ ግን ልብስ ስለ መምረጥ፣ ስለ ፀጉር አያያዝና ስለመሳሰሉት የራስሽን ምርጫ እንድትከተዪ ይተውሻል፡፡ ከዚያ ወዲያ የራስሽ ምርጫ መታየት ጀመረ ማለት ነው።ስለዚህ ቁመናሽና አለባበስሽ በውስጥሽ ምን ዓይነት ሰው እንደሆንሽ ማንጸባረቅ ጀምሯል፡፡ እስኪ ይህን ንባብ ገታ በማድረግ የሰውነትሽ አቋምና አለባበስስ ስለ አንቺ ምን እንደሚናገር ለአፍታ ቆም ብለሽ አስቢው።
አለባበስሽ በእርግጥ ስለ አንቺ ስለሚናገር ከአንድ ዓይነት ቡድን ወይም ክፍል ጋር ያስመድብሻል።ብዙ ሺህ ዓመታት ወደኋላ መለስ ብለን ብንመለከት ይህንን እውነታ ከመጽሐፍ ቅዱስ እንረዳለን፡፡ ለምሳሌ በነገሥት መጽሐፍ ውስጥ የንጉሥ አካዝያስ መልእክተኞች እርሱ ከላካቸው በኋላ አንድ ዓይነት ሰው ማግኘታቸውንና አርሱም በበኩሉ መልሶ መልእክት እንደላካቸው ተመልሰውም ለንጉሡ እንደተናገሩ ተጽፏል:: ንጉሡም « የሰውየው መልክ ምን ይመስላል» ብሎ ጠየቃቸው አለባበሱን በገለጹለት ጊዜ ወዲያውኑ «ኤልያስ ነው» አለ፡፡ እንዴት ዐወቀው ቢሉ ኤልያስ ነቢያት የሚለብሱትን ዓይነት ልብስ ይለብስ ስለነበረ ነው።2ነገ1÷2-6

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

ሚስቶች አለባበስን በተመለከተ የራሳቸውን ስሜት ብቻ ሳይሆን የባሎቻቸውንም ሁኔታ ከግምት ውስጥ ማስገባት እንዳለባቸው ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ተናግሯል።በሚስቶች ተገቢ ያልሆነ አለባበስ ባሎች የሚሰማቸውን ሲናገርም"ወሶበሂ ኢኀፈረ ነቢበ እንበይነ ዘእንበለ ዳእሙ ያት ሒዘበኪ በልቡ።
ወታመጽኢ ቅንአተ በርእስኪ፡፡ ወታኀጥኢ ኩሎ ተድላ በእንቲአሁ፡፡ ወባሕቱ ትጻልኢ፡ ወትሴስሊ እምኔሁ፡፡"ይህም «በማይገባ ልብስ አጊጠሽ ባየ ጊዜ ሕጌ ይፈርስብኛል ብሎ ሊናገርሽ ቢያፍር እንኳን በልቡ ይጠረጥርሻል፡፡ በሥራሽ ቅንአትን ታመጭበታለሽ፡፡ ስለ ቀናም ከእርሱ የምታገኚውን ተድላ ታጫለሽ፡፡ ትነቀፊያለሽ ስለዚህ ከባልሽ ተፋተሽ ትሔጃለሽ» ማለት ነው:: ዳግምኛም በልብስ ዘማ አጊጣ ስትወጣ ባያት ጊዜ ወደ ቤተ ክርስቲያን የምትሔድ እንኳን ቢሆን «ባይከለክላት እንኳን ይጠረጥራት የለምን? ከቤት ሳለች እንዲህ የማታጌጠው ለምንድር ነው? ምን አምሯት ይሆን?» ማለቱ አይቀርም።ይህም ቃል በግእዙ እንዲህ ይነበባል፡ «ወእምኒ ኢከልኣ አኮኑ እምተሐዘባ፡፡ ወይቤ ለምንት ኢትሠረገው ውስተ ቤት ወኢትሤነይ፡፡ ወምንትኑ መፍቅዳ፡፡» (ተግ.ዘዮሐ 28)
ሐ. እኔ እንዲህ የማጌጠው ባሌ ውጭ ውጭ እንዳይልብኝ ነው ! » በማለት ልብሰ ዘማ (የዘማዊያንን ልብስ) መልበስ አትለማመጂ፡፡ ከዚያ ይልቅ ቅዱስ ጴጥሮስ እንደ ተናገረው ‹ንጹሑን ኑሮሽን እየተመለከተ» ባልሽ ባንቺ እንዲማረክ አድርጊ፡፡ 1ጴጥ3፥1-6 ባልሽን በአለባበስሽ እንዲማረክ ማድረግ የበለጠ ሴሰኛ ማድረግ መሆኑን አታውቂምን? ባልሽ «ንጹሕ» ሰው ከሆነ የሚማረከው በ«ንጹሕ» አኗኗርሽ እንጂ በአለባበስሽ አይደለም።«ወእመሰ ተሠርገውኪ በዘዚአሁ ሠርጉ ወኮነ ምትኪ ዘማዌ የሐውር ኀበ ካልእት ማለትም «ባልሽ ሴሰኛ ከሆነ ግን ምንም በጌጦች ዓይነት ሁሉ ብታጌጪ ካንቺ ወደ ሌላ መሄዱ አይቀርም፡፡» ምክንያቱም በማጌጥ አንዷ ሴት አንዷ መብለጧ አይቀርምና፡፡ (ተግ.ዘዮሐ 28)
መ. ከወሊድ ጋር ተዛምዶ ያላቸውን አካላት የሚያጋልጥ ልብስ ለብሶ ወደ ገበያና ሥራ ቦታ መሄድ እጅግ ያሳፍራል፡፡ ለሥራም የሚመች አይደለም፡፡ ይልቁኑም ለክርስቲያኖች ሰውነትን እንደ ከብት የሚያስገምት ልብስ ለብሶ በመዋኛና በመታጠቢያ ስፍራዎች ወዲህና ወዲያ ማለት እንዴት ያስነውራል? ከዚህ ሁሉ ግን የሚያስወቅስው በልብሰ ዘማ አጊጦና ተገላልጦ ወደ ቤተ ክርስቲያን መግባት ነው። ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ «ቦኑ ትትቃወሚዮ ለቃለ ሐዋርያ ብፁዕ ጳውሎስ» በማለት እንደ ተናገረው ወደ ቤተ ክርሰቲያን የምትሔጂው «ራስዋን ሳትሸፍን ግን የምትጸልይ ወይም ትንቢት የምትናገር ሴት ራስዋን ታዋርዳለች» በማለት የተናገረውን ቅዱስ ጳውሎስን ለመቃወም ነውን? 1ቆሮ11፥5
ሠ. የማይገባ አለባበስ በክርስቲያኖች ዘንድ ቢታይ በማያምኑ ሰዎች ፈጣሪያቸውን ያሰድቡታል፡፡ ለምሳሌ፦ አንዲት ሴት እጅግ በጣም ከፍተኛ ዋጋ በሚያወጣ ልብስ ተሸልማ የሚበሉትና የሚጠጡትን አጥተው የተቸገሩ ድሆች ቢያይዋት ስለ ፈጣሪ የሚያስቡት ምንድር ነው? «እኛ እንዲህ ስንቸገር አንተ ሰብስበህ ለአንዲቱ ይህን ሁሉ ታሽክማታለህን? አንተንስ ፋንድያ ማጠን ነው!» አይሉትምን? እንዲህም ባይሉት ፈጣሪ የማይወዳቸው እየመሰላቸው ተስፋ መቁረጣቸው አይቀርም፡፡ አሕዛብንም ቢሆን ግብረ ገብነት የጎደለው አለባበሳችን ወደ ሃይማኖታችን እንዳይሳቡ ሊያደርጋቸው ይችላል።
ረ. አለባበስን በተመለከተ የራስን ስሜት፣ የትዳራችንን ሁኔታ፣ የድሆችንና የማያምኑ ሰዎችን ሕሊና ላለመጉዳት ከማሰብ በላይ ከፈጣሪ ሕግ ላለመውጣት ጥረት ብናደርግ አለባበሳችን በዘመናችን ሁሉ ብዙ እጅግ በጣም ተለዋዋጭ እንዳይሆን ለማድረግ ባልቸገረንም ነበር። ስለዚህ ልብስ ከፈጣሪ አይበልጥምና አለባበስን በተመለከተ «ፈጣሪዬ ከኔ የሚሻው ነገር ምንድር ነው?» እያሉ በአግባቡ መመላለስ ይገባል፡፡
ሰ. ሕይወት በእንቅሰቃሴ የተሞላች ናት፡፡ ከቤት ለአንድ ዓላማ ብለሽ ከወጣሽ በኋላ እግረ መንገድሽን ቤተ ክርስቲያንም ሆነ ሌላ ቦታ መድረስ ያስፈልግሽ ይሆናል፡፡ ታዲያ አለባበስሽ ማንኛውንም ነገር ከማድረግ የማያግድሽ ሁለገብ እንዲሆን ለምን አትጥሪም? ለአንቺም ቢሆን እኮ የምታከብሪያቸውን ሰዎች ስታዪና በእግዚአብሔር ፊት ለመቆም ወደ ቤተ ክርስቲያን ስትሄጂ በመሳቀቅ ከምታልቂ አንድ ፊቱን በእግዚአብሔርና በመልካም ሰዎች ዘንድ የተወደደ አንድ ወጥ የአለባበስ መንገድ ብትከተዪ መልካም ነው::
ሸ. ልብስ ስትለብሺ በእንቅስቃሴ ወቅት እንዴት እንደምትሆኚ አስቢ እንጂ እንደ ልብስ ማሳያ አሻንጉሊት ይመስል የሰቀሉብሽን ወይም ያምርብሻል ያሉሽን ሁሉ አትልበሺ፡፡ አንቺ እኮ! በመኪና ቁጭ ብለሽ የምትጓዢ፣ በቢሮ ቁጭ ብለሽ የምትጽፊ፣ አጎንብሰሽ የወደቀ የምታቀኚና ልብስ የምታጥቢ በአጠቃላይ በእንቅስቃሴ የተሞላ ሕይወት ያለሽ ፍጡር ነሽ፡፡ ታዲያ በነዚህ እንቅስቃሴዎችሽ ውስጥ አጭርና ጠባቃ ልብስ ብትለብሽ ለሌሎች እይታ የምታጋልጫቸውን ሕዋሳቶችሽንና ሊፈጠርብሽ የሚችለውን አንዳንድ መጥፎ ገጠመኝ ለምን አታስተውዪም። እኔ በግሌ አጭር ልብስ ለብሶ ማርዘም ላይቻል ሲጎትቱ ከመዋል ረጅሙን መርጦ መልበስ ይሻላል እላለሁ።
ቀ. አንዳንድ ወጣቶች ኋላ ቀር መስለው እንዳይታዩ በጣም አዲስ ከሆነው ፋሽን ጋር መራመድ እንደሚገባቸው አድርገው ያስባሉ።ምን ጊዜም ከመጠን ያለፈ «ወግ አጥባቂ» በመሆንና በጣም «ዘመናዊ» በመሆን መካከል አንድ አማካይ ቦታ ይኖራል፡፡ ይህን መሀከለኛነት ከያዝሽ ሁል ጊዜ ጥሩ አለባበስ ይኖርሻል፡፡ በየጊዜው ለሚመጣው የፋሽን ለውጥ ተገዥ ከመሆንም ትድኛለሽ፡፡
በተጨማሪም ስለ ፋሽን በጣም በመጨነቅሽ የምትጠቅሚው ማንን ነው? መልሱ ራስሽን ሳይሆን ፋሽኖችን የሚያቀርበውንና የሚያበረታታውን የንግዱን ዓለም ነው።እነርሱ አንድ ዋነኛ ዓላማ አላቸው፤ እርሱም ገንዘብ ማግኘት ነው።በእነርሱ ሥራ ውስጥ የሰይጣንን ሚና ከተመለከትሽ ደግሞ ዓላማው በብልሹ አለባበስ ምክንያት በዓለም ላይ የሥነ ምግባር ጉድለት እንዲንሰራፋ፣ ስለ እግዚአብሔር ማሰብ በቁሳዊ ነገር እንዲተካ ማድረግ ሆኖ ታገኝዋለሽ፡፡ ስለዚህ ሁልጊዜ ፋሽን ተከታይ ከሆንሽ አንቺ ምንም ሳትጠቀሚ ገንዘብሽን ጨምሮ የምታጫቸው ነገሮች በርካታ ናቸው::

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

ሰበር ዜና

የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ በዛሬው ዕለት ባደረገው ስብሰባ የሚከተለውን ውሳኔ አስተላልፏል፦

1. ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆርስን የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፤
2. ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስን የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽሕፈት ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅ፤
3. ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስን የሐዲያ ሀ/ስብከትን እንደያዙ የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ሊቀ ጳጳስ፤
4. ብፁዕ አቡነ ናትናኤል ዘኮሎራዶን የቅድስት ሀገር ኢየሩሳሌም ገዳማት ሊቀ ጳጳስ፤
5. ብፁዕ አቡነ ናትናኤልን ሜኒሶታን እንደያዙ የኮሎራዶ ሀ/ስብከትን እንዲመሩ፤
6. ብፁዕ አቡነ ሄኖክ የደቡብ አፍሪካ ሀ/ስብከት ሊቀ ጳ ጳስ፤
7. ብፁዕ አቡነ ዕንባቆምን የገዳማት መምሪያ ሊቀ ጳጳስ ሆነው እንዲመሩ፤
8. ብፁዕ አቡነ ሙሴ አውስትራልያን እንደያዙ የግቢ ቅዱስ ገብርኤልና የበዐታ ለማርያም ገዳም ሊቀ ጳጳስ ሆነው እንዲመሩ ወስኗል።
➼ የኢኦተቤ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ!
ግንቦት ፲፭ ቀን ፳፻፲፯ ዓ/ም

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

ሴቶች ሠላጤ የሌለው ሱሪ መልበሳቸው ደግሞ ለጊዜው ለእይታ ሲጋለጡና ወደ ደርብ (ሰገነት) ሲወጡ ለአካላቸው መከለያ እንዲሆን ነው።ምሥጢሩ ግን እንደ ወንዶች የምንዋጋበት ዐቅም የምንደፍርበት ልብ የለንም፡፡ የአካላችንም ቅርጽ ከወንዶች አካል ቅርጽ ልዩ ነው እንደ ማለት ነበር፡፡ ስለዚህ የሱሪያቸው ስም ትርጉም ባለው አጠራር «ልብ አልባ» ይባላል፡፡
የካህናትና የባላገሮች ሱሪና እጀ ጠባብም ሠላጤውን እንደ ወታደር አድርገው መስፋታቸው የተፈጥሮ አካላችን ቅርጹ ከእናንተ ጋር አንድ ነው ማለት ሲሆን፡ የእጅና የእግር ማስገቢያውን ደግሞ የሌላ ሰው እጅና እግር ደርቦ የሚያስገባ ያኽል ቦላሌ አያያ መስፋታቸው ለጊዜው ሲሠሩና ሲንቀሳቀሱ እንዳያልባቸው እንዲያናፍስላቸውና ቶሎ እንዳያልቅባቸው በማለት ነበር፡፡ ምሥጢሩ ግን የሌላውን ሰው እጅና እግር ደርቦ የሚያስገባ ያህል ሰፊ አድርገው መሥራታቸው አርሰን የምንመገበው አስተምረንና አማልደን የምናጸድቀው በተፈጥሮ ወንድማችን ለሆነ ሁሉ ነው እንጂ ለራሳችን ጥቅም ብቻ ስንል አይደለም ለማለት ነው። ሠላጤውንም እንደ ወታደር አድርገው መታየታቸው ስለ ሁላችሁ እንሥራ ብለን ለክህነት ራሳችንን ለየን አንጂ እንደ ወታደርም የጦር ሥራ ለመሥራት የምንችል ነን ለማለት ነው:: ስለዚህ ልብስ የሰው የሥራውና የተፈጥሮው ልዩነት መታወቂያ ነው እንጂ ነፋስና ብርድን መከላከያ ብቻ ወይም የፋሽን ገበያ ማሞቂያ አይደለም:: እንዲህ ከሆነ ክርስቲያኖች የልብሳቸውን አርአያ እንደፈለጉ ከመቀያየር ተቆጥበው በሥርዓትና በአግባቡ ማጌጥ አለባቸው።

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

ግንቦት ፲፪
ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ


በዚህችም ዕለት ቅድስት እናታችን ክርስቶስ ሠምራ ቃል ኪዳን የተቀበለችበት ነው፡፡ በሸዋ ከፍለ አገር በቡልጋ አውራጃ ልዩ ስሟ ቅዱስ ጌዬ የተባለች አገር ነበረች ይህችም የእናታችን ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ የትውልድ አገሯ ናት። በዚህም አገር በወርቅና በብር በሐር እና በልዩ ልዩ ልብስ በወንድና በሴት አገልጋዮች በፈረስና በበቅሎ የከበረ አንድ ስሙ የታወቀ ሰው ነበር። የዚህ ሰው ስሙ ቅዱስ ደረሳኒ ሲሆን የሚስቱም ስም ቅድስት ዕሌኒ ይባላል ሁለቱም ባልና ሚስቱ እግዚአብሔር የሚፈሩ ደጋግ ሰዎች ስለነበሩ በጎ ሥራቸው በዓለም ሁሉ የታወቀ ነበር። እሊህም ሰዎች በእግዚአብሔር ዘንድ የተመረጠችና የከበረችን ቅድስት ክርስቶስ ሠምራን ወልደው በደም ግባቷና በጠባይዋ እየተደሰቱ አሳደጓት ከዚያም የእግዚአብሔርን ሕግጋትና ሥርዓቶችንም ሁሉ አስተማሯት። ባደገችና ለአቅመ ሔዋን በደረሰች ጊዜ የንጉሥ ባለሟል የሆነ ትውልዱ፤ ነገዱ ከአባ ፃሠርጓ ወገን የሆነ ለኢየሱስ ሞዓ ልጅ ለሠምረ ጊዮርጊስ በሕግ አጋቧት። እሱም በዚህ ዓለም ገንዘብ በጣም የከበረ ከመሆኑም በላይ በይበልጥ መንፈስ ቅዱስ ያደረበት ሰው ነበረ። ከደም ግባቷ የተነሣ ሙሽራይቱ ማለት እናታችን ቅድስት ክርስቶስ ሠምራን እጅግ አድርጎ ወደዳት። አሟቷ ኢየሱስ ሞዐም ይህች ብላቴና "በታላቅ ቁም ነገር የተመረጠች ነች" በማለት ትንቢት ይናገርላታል ስለዚህ እንደ እመቤቱ አድርጐ ያከብራት ነበር። ከዚህም በኋላም ለሕጋዊ ባሏ ለሠምረ ጊዮርጊስ ዓሥራ አንድ ልጆች ወለደችለት ከነዚህም መካከል ዘጠኙ ወንዶች ሁለቱ ሴቶች ነበሩ። ልጆችዋንም ሕገ እግዚአብሔርን እያስተማረች በክብር በሥርዓት አሳደገቻቸው።

በዚያን ዘመን የእግዚአብሔር ባለሟል የሚሆን ዓፄ ገብረ መስቀል የሚባል የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ነበር። እርሱም ዝናዋን ሰምቶ ሥነ ምግባሯን ተመልክቶ ይልቁንም በሷ ላይ ያደረውን ኃይለ መንፈስ ቅዱስ እግዚአብሔር ስለገለጸለት እጅግ አድርጐ ይወዳትና ያከብራት ነበር። ከዕለታት ባንድ ቀን በጸሎትሽ አስቢኝ በማለት በራሱ በንጉሡ ቤተ መንግሥት ከሚያገለግሉ አገልጋዮች ወይም ሠራተኞች መካከል እንዲያገለግሏት 174 አገልጋዮች ላካላት። ዳግመኛም ፈረስና በቅሎ ከነሥራታቸው እንደዚሁም ለነሥታት ሚስቶች የሚገባ ከሐርና ከወርቅ የተሠራ ልብስና የወርቅ ጫማ ላከላት። ነገር ግን እሷ ይህን ሁሉ ክብር አልፈለገችም ይልቁንም ለዓላማየ ዕንቅፋት ወይም ከንቱ ውዳሴ ይሆንብኛል በዚያውስ ወርቁ ጌጡ ልብሱ ተሸጦ ለነዳያን ይመጸወታል ለቤተ ክርስቲያን መባዕ ይሰጣል እኒህን አገልጋዮች ግን ምን አደርጋቸዋለሁ በማለት ወደ እግዚአብሔር እያመለከተች ቆየች።

ከአገልጋዮችዋ መካከል ምግባሯ የከፋ የምታናድዳትና የምታበሳጫት አገልጋይ ነበረች። ከዕለታት በአንድኛው ቀን እናታችን ክርስቶስ ሠምራ በጣም ተበሳጨችና በዚያች አገልጋይ አፍ ውስጥ የእሳት ትንታግ ጨመረችባት።  ያም እሳት ትንታግ በአገልጋይዋ ጉረሮ ድረስ ዘለቀና ገደላት። በዚህን ጊዜ ቤተሰቦችዋ መጥተው የአገልጋይቱን አስከሬን ወደሌላ ክፍል ወሰዱት። ብፅዕት ክርስቶስ ሠምራም ደንግጣ ካለችበት ቤት ውስጥ ወደ ሌላው ክፍል ገባችና ወደ ሰማይ አቅንታ "ወይኔ ወዮልኝ ወዮታ አለብኝ የካህን ሚስት ስሆን ነፍስ ገዳይ ሆኛለሁና። ሰውስ ምን ይለኛል ለነፍሴስ ምን እመልስላታለሁ ከእግዲህ ከክርስቲያን ወገን ልቆጠር አይገባኝም በደሌንስ እንደምን አድርጌ ልሸሸሽጋት እችላለሁ" እያለች አለቀሰች።

ከዚህ በኋላ እንዲህ ስትል ለእግዚአብሔር ብፅዓት አደረገች "አቤቱ ይህችን በእኔ እጅ የሞተችውን አገልጋይ ነፍስዋን ከሥጋዋ አዋህደህ ብታሥነሣልኝ ልጆቼን ቤቴን ንብረቴን ትቼ ባለ ዘመኔ ሁሉ አንተን እከተላለሁ። አንተን ከመከተል ከቶ ወደኋላ አልልም። ለሰውነቴ ጌጥ ወይም ግርማ ሞገስ የሚሆናት ወይም የሚሞቃት ልብስ ከቶ አልለብስም ሥጋዬን የሚያረካ ምግብም አልመገብም። አቤቱ ጌታዬ ሆይ ጸሎቴን ስማኝ ልመናዬም በፊትህ ፈጥኖ ይድረስ አቤቱ ፊትህን ከኔ ከባሪያህ አትመልስ"። እንዲህ እንዲህ እያለች በልቅሶና በኀዘን ለብዙ ሰዓት ከጸለየች በኋላ ድካም ተሰማትና ዕረፍት አደረገች። ከዚህ በኋላ ቤተሰቦችዋ እስዋ ወዳለችበት ክፍል መጥተው "እመቤታችን ሆይ ሙታ የነበረችው አገልጋይሽ በእግዚአብሔር ኃይልና በአንቺ ጸሎት ተነሥታለችና ደስ ይበልሽ" አሏት። በዚህ ጊዜ ፈጥና ተነሥታ ደስ እያላት ሙታ የነበረችው አገልጋይ ካለችበት ቦታ ደረሰችና ሕይወት አገኘቻት ከዚያም ቃሏን ከፍ አድርጋ "ልመናዬን ቸል ያላለ ቸርነቱንም ከኔ ከባሪያው ያላራቀ ፈጣሪ ይክበር ይመስገን" ብላ በታላቅ ምስጋና እግዚአብሔር አመሰገነች።

ከዚህ በኋላ አስቀድሞ ከአፏ የወጣውን ከአንደበቷ የተነገረውን ቃል አስባ ልብሰ ምንኵስናዋን ማለት ቆቧን ቀሚሷን አጽፏን መታጠቂያዋን አዘጋጀች። ቤተሰቦቿና አገልጋዮቿም "እመቤታችን ሆይ ይህ የምታዘጋጂው የምናኔ ልብስ ለምንሽ ነው ወይስ ለማን ነው የምታዘጋጂው" አሏት። እርሷም " ሃይማኖት ያስተማሩኝ አባቴ ልብስ አልቆባቸዋል ሲሉ ሰምቼ ለሳቸው ነው የማዘጋጀው" አለቻቸው።

ከዚህም በኋላ ከዕለታት ባንደኛው ቀን እናታችን ክርስቶስ ሠምራ አገልጋዮቿን ወደ ቤተ ክርስቲያን እንሄድ ዘንድ ተዘጋጁ አለቻቸውና እነሱም አሺ በጎ ብለው አጅበዋት ወደቤተ ክርስቲያን ሄዱ። ከዚያም እንደደረሱ "በሉ እንዲህ እኔ ከዚህ ጥቂት እቆያለሁና እናንተ ወደ ቤታችሁ ተመለሱ ለኔ ይህች አንድዲት አገልጋይና ይህ ሕፃን ልጅ ብቻ ይበቁኛል አለቻቸው። በዚያኑ ጊዜ አገልጋዮቿ እጅ እየሱ ወይም እየተሰናበቱ ወደቤታቸው ተመለሱ። ከዚያም ከዳዊት መዝሙር "ልቤ ጽኑ ነው አቤቱ ልቤ ጽኑ ነው እግዚአብሔርን ፈጽሜ አመሰግነዋለሁ እግዚአብሔር የደህንነቴ መብራት ስለሆነ ምን ያስደነግጠኛል እግዚአብሔር የሕይወቴ መተማመኛ ነው ምንስ ያስፈራኛል የሚለውን እየጸለየች የሚያልፈን ዓለም በማያልፈው ዓለም ለመተካት ወይም ለመለወጥ አውጭኝ እግሬ ብላ ገሠገሠች። ያ በልስላሴና በእንክብካቤ የኖረ እግር ከመንገዱ ብዛት እንደዚሁም ከቅርቅፍቱና ከእንቅፋቱ የተነሣ ፈለግ ሲያወጣ ሥጋውን እየቆረጠች ስትጥለው ደሙ እንደጒርፍ ውሃ ይወርድ ነበር። ያች የተከተለቻት አገልጋይ ግን ከእመቤቷ እግር እየተቆረጠ የሚወድቀውን የአካል ቊራጭ እያነሳች በልብሷ ትቋጥረው ነበር። በዚህ ዓይነት ችግርና ፀሐይ ሐሩር የብዙ ጐዳና ጉዞ ተጉዛ ከአሰበችበት አገር ደረሰች። በደብረ ሊባኖስ አቅራቢያ ወይም አካባቢ ስትደርስ የራስ ፀጒራን ይዛው በነበረ ምላጭ ላጨች ልብሷንም አውልቃ ለነዳያን አከፋፈለች የያዘችውንም ገንዘብ በመንገድ ላይ ላገኘችው ሁሉ መፅውታ ጨረሰች። ከዚያም አስቀድማ ያዘጋጀችውን ልብስ ምንኵስና ማለት ቀሚስዋን አጥልቃ አጽፋን ተጐናጽፋ ቆቧን ደፍታ ደብረ ሊባኖስ ከሴቶች ገዳም ደረሰች። የገዳሙ መነኰሳትም በታላቅ ክብር ተቀብለው ወደበዓታቸው አስገቧት ...

እናታችን ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ለሳጥናኤል ምሕረት እንደለመነች፦ ከዕለታት በአንድኛው ቀን እናታችን ክርስቶስ ሠምራ ጓንጉት በምትባል ደሴት ውስጥ ዓርብ ዕለት ከቀኑ በስድስት ሰዓት ላይ ስለሰው ልጆች ስትጸልይ ሣለ። ዓለሙ ሁሉ ከንቱ እንደሆነና የሰውም ልጅ ሕይወት እንደጥላ ኃላፊ ጠፊ መሆኑን ፈጽማ ተመለከተች። ነቢዩ ዳዊት "ሰው ከንቱ ነገርን ይመስላል ዘመኑ ወይም ሕይወቱ እንደጥላ ያልፋል" ሲል ተናግሯልና። ዳግመኛም "ሰው ክብር እንኳ ቢሆን ሊኖር አይችልም እንደሚጠፋ ወይም ማስተዋል እንደሌለው እንስሶች መሰለ...

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅም ሥርዓተ መንግሥተ ሰማያትን በተናገረበት አንቀጽ ‹ሕፃናት ተወልደው እስከ ሰባትና አሥራ ሁለት ዓመታቸው ድረስ የሚያውቁት ዕውቀት ጻድቃን ከበቁ በኋላ እንደማያውቁት ዕውቀት ነው፡፡ እስከ ሃያና ሠላላ ዓመታቸው የሚያውቁት ዕውቀት ጸድቃን ከሞቱ በኋላ በገነት እንደሚያውቁት ዕውቀት ነው፡፡ እስከ ዓርባና ሃምሳ ዓመታቸው የሚያውቁት ዕውቀት ደግሞ ጻድቃን መንግሥተ ሰማያት ገብተው እንደሚያውቁት ዕውቀት ነው፡፡› በማለት በሃያዎቹና በሠላሳዎቹ ውስጥ የሚገኙ ወጣቶች ኸዕውቀት አንጻር በሞት ለሄዱና በገነት ላሉ ጻድቃን ምሳሌ እንደሚሆኑ አስረድቷል።(ዮሐ.አፈ.ተግ.8)
ይህ የወጣቶች ለጻድቃን ምሳሌ መሆን ወጣቶች ብሩህ አእምሮ እንዳላቸው የሚያመለክት ነው።ቀን ላለ በብርሃን መመላለስ ይሉሃል በወጣትነት መማር ነው።ወጣትነት ብሩህ ወቅት ነው። ኃላፊነቶች ያልበዙበት ሰው በመሆንህ ያለህን ነጻነት ለመማር ተጠቀምበት። ራስህን ጊዜው ባልሆነ የተቃራኒ ጾታ ግንኙ ነት ውስጥ ሳታስገባ ለመማር ጥረት አድርግ፡፡ በተጨማሪም ሌሎች ልዩ ልዩ ሱሶችና ልማዶች የወጣትነት ብሩህ አእምሮህን በአጉል ተስፋ እንደሚያጨልሙብህ አትጠራጠር።
ምንም እንኳን ሁሉም ወጣቶች ተመሳሳይ ዕድል ባይኖራቸው በሀገራችን ብዙ ወጣቶች ወላጆችና ትልልቅ ሰዎች ያሉባቸው ዓይነት ኃላፊነት የለባቸውም:: እንዲያውም አብዛኞቹ ወጣቶች በቤተሰቦቻቸው ትከሻ እየኖሩ እንክብካቤ የሚደረግላቸውና «የሚጦሩ» ናቸው፡፡ ስለዚህ እነዚህ ወጣቶች ከብዙ ኃላፊነት ነጻ መሆናቸውን ዐውቀው ዕድላቸውን ቢጠቀሙበት ለመማርና ዕውቀት ለመሰብሰብ ሰፊ ጊዜ ይኖራቸዋል። ሆኖም አብዛኞቹ ወጣቶች ያን ያህል ሰፊ ጊዜ እንደነበራቸው የሚያስተውሉት ጊዜው ካለፈ በኋላና ለመጠቀም የማይችሉበት ሁኔታ ውስጥ ሊገኙ መሆኑ እጅግ ያስቆጫቸዋል።
ትምህርት ትግልን ይጠይቃል፡፡ መታገሉን ብትሰለች ከትግሉ በኋላ የምታገኘውን ዘለቄታዊ ጥቅም ታጣለህ:: ስለዚህ ወጣት ከሆንክ ኋላ የምትቆጭበትና ከሰው የምታንስበት ጫወታና መዝናናት አታሎኽ ከመማር አትቦዝን። ለጊዜያዊ ደስታ ብለህ ዘለቄታዊ ጥቅምን ለምን ታጣለህ? መዝናናትና መደሰት ድሮም ነበሩ፣ የሚያልቁ ነገሮች አይደሉምና ወደፊትም ይኖራሉ፡፡ ስለዚህ በሌላ ጊዜ የምትደርስባቸው እነዚህ ነገሮች እንዳያዘናጉህ ተጠንቀቅ:: የወደፊት የሥጋህና የነፍስህ ዕጣ ምን ሊሆን እንደሚችል ከወዲሁ በጥንቃቄ አስብበት። ነቢዩ ኢሳይያስ «ወይስ ወሬ ማስተዋልን ለማን ይሰጣል?» ብሏልና ከወሬነት ለማያልፉ ነገሮች እየጓጓህ ትምህርትን ቸል እትበል፡፡ ኢሳ28÷9
ጠቢቡ ሰሎሞን ታካች ሰው ብትልከው «አንበሳ በመንገድ አለ» ይላል በማለት እንደተናገረው ላለ መማር ምክንያት አታብዛ። ምክንያት የሚያልቅ ነገር አይደለም። ለምንም ነገር ምክንያት ሊቀርብ ይችላል:። ከዚያ ይልቅ ለሰው የሚያዋጣው ምክንያትን በብርታት አሸንፎ ጠንክሮ መማር ነው፡፡ ብፁዕ አቡነ ዮሐንስ ቀዳማዊ አንዱን ወጣት ያለ ሥራ ስላዩት «ልጄ ለምን አትማርም?» ቢሉት እርሱም «አባታችን- ምን በልቼ?›› በማለት መለሰላቸው። ብፁዕነታቸውም ምክንያተኝነት እንደማይጠቅም በሚያስረዳ ቃል «ታዲያ አሁን እየደነቆርህ ያለኸው ምን እየበላህ ነው?›› በማለት መለሱለት ይባላል።
ላለመማር የትምህርት ፖሊስን፣ መምህራንን፣ ወላጆችን (ቤተሰብን)፣ ጾታን፣ የሥራ ጫናን፣ የጤና ሁኔታንና የመሳሰሉትን መኮነን ለማንም አልጠቀመም።የተሻለው መንገድ በራስ በኩል ያሉትን ድክመቶች አስወግዶ ተገቢውን ጥረት ማድረግ ብቻ ነው።ጥሮ በመማር መጠቀም እንጂ ቁጭ ብሎ ሌላውን ማማትና መተቸት ዐዋቂነት አይደለም።ስለዚህ በተቻለህ ሁሉ ጠንክረህ ተማር ከዐቅምህ በላይ የሆነውን ደግሞ ፈቃዱን አታውቅምና ለፈጣሪህ ተወው፡፡
እንኳን ከጨዋታና ከመዝናናት ይቅርና ከሥራም ቢሆን መቅደም ያለበት ትምህርት ነው።ዕውቀት ያልደገፈው ሥራ መሠረት እንደሌለው ቤት ነውና፡፡ ሥራ ያለህም ሰው ብትሆን የየዕለት መሠረታዊ ፍጆታህን ካገኘህ በኋላ ሐሳብህ ወደ ትምህርት ይሁን። ከተግባረ ሥጋም ሆነ ክተግባረ ነፍስ መቅደም ያለበት መማር ነውና፡፡
በራስ አነሣሽነት ከትምህርት ይልቅ ዋዛ ፈዛዛንና በልምድ የሚገኝ ዕለታዊ ተግባርን የመረጠ ሰው የኋላ ኋላ የሚያዝንበትና የሚያፍርበት ነገር ሳያጋጥመው አይቀርም:: ጠቢቡ ሰሎሞን ትምህርትን በልዩ ልዩ ምክንያት ሳይማር የቀረ ሰው ዘግየት ብሎ የሚሰማውን ስሜት እንዲህ በማለት ይገልጸዋል:- «በመጨረሻም ሥጋህና ሰውነትህ በጠፉ ጊዜ ታለቅሳለህ፡ ትላለህም፥ እንዴት ትምህርትን ጠላሁ ልቤም ዘለፋን ናቀ! የአስተማሪዎቼንም ቃል አልሰማሁም፡ ጀሮቼንም ወደ አስተማሪዎቼ አላዘነበልሁም።»ምሳ5:11-13
ይልቁንም ለመማር የሚያስችል ሁኔታ ተመቻችቶ ሳለ ለመሥራትና ንብረት ለማካበት መሽቀዳደም የከበረች ጥበብን ዋጋ ማሳጣት ነው፡፡ ከገንዘብ ተግሣጽ ይበልጣልና:: ተግሣጽ ደግሞ ጥበብም ትምህርትም ነው፡፡ ስለዚህ መጽሐፍ ቅዱስ «ተግሣጹን እንጂ ብርን አትቀበሉ፡ ከምዝምዝ ወርቅም ይልቅ ዕውቀትን ተቀበሉ፣ ጥበብ ከቀይ ዕንቁ ትበልጣለችና የከበረ ነገር ሁሉ አይተካከላትም፡፡» ምሳ8፥10-11 በማለት ትምህርት በገንዘብ እንደማይለካ ምስክርነቱን ይሰጣል፡፡ ሲራ6፥ 18-37

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

ስለ «መልክ» ሊኖር የሚገባ ተገቢ አመለካከት!
በኮረዳነት ወቅት የሚከሠቱ አካላዊ ለውጦች የስሜት ለውጦችን ሊያስከትሉ ይችላል፡፡ አንዲት ልጃገረድ አንድ ጊዜ በኃይልና በብርታት የተሞላች ጤናማ ወጣት የሆነች ይመስላትና በሌላ ቅጽበት ደግሞ ድክምክም ብላ ፍጹም ጤና እንደሌላት እንደሚሰማት ሁሉ ስለማንኛውም ነገር የሚሰማት ስሜትም በዚያው ልክ በጣም ተለዋዋጭ ሊሆንባት ይችላል፡፡ ከዚህ የተነሣ ብዙ ብሩህና የደስታ ወቅቶች በትካዜና በተስፋ መቁረጥ ተሞልተው ይታያል፡፡ አሁን የወደደችውን ከጥቂት ደቂቃ በኋላ ያለ ምንም ተጠቃሽ ምክንያት መሰልቸትና መጥላት ትጀምራለች።በዚህ ምክንያት የወሰነቻቸው ውሳኔዎችና የወሰደቻቸው እርምጃዎች የማይሽር ጸጸት ሊያስከትሉባት ይችላሉ፡፡
በዚህ ተለዋዋጭ ስሜት ላይ ነገሮች በሙሉ በሽማኔ መወርወሪያ ፍጥነት የሚቀያየሩበት ዘመናዊው የኢንዱስትሪ ዓለም ሲጨመርበት ወጣት ልጃገረዶችን ለከፍተኛ ጭንቀትና ግራ መጋባት ሊዳርጓቸው ይችላሉ።በእርግጥ ጤናማ መሆኗንና ወደፊት ምን ዓይነት ሰው እንደሚወጣት ሊያሳስባት ይችላልደበዚህ ያለመረጋጋት ሁኔታ በቀላሉ ላለመሸነፍ ብዙ ብቸኛና ዝምተኛ ወይም በጣም ትምክህተኛና እኔ ያልኩት ብቻ ይሁን ማለት አያዋጧትም::
ወጣት ልጃገረዶች ስለመልካቸው መሳሳትና መጨነቃቸው ከዘመነ ሔዋን ጀምሮ እንደ ነበር በመጻሕፍት ተገልጧል። ይሁን እንጂ የሴቶች ጠቅላላ የወደፊት ሕይወት በመልክ ላይ የተመረኮዘ ይመስል ሰለ ፊትና ቁመና ከመጠን በላይ መጨነቅ አይገባም፡፡ በዙሪያሽ የሚገኙና በብዙ መንገድ የምትቀኚባቸውን ታላላቅ ሰዎች አስተውለሽ ተመልከቻቸው። አብዛኞቹ ተራ መልክ ያላቸው አይደሉምን? ስለዚህ ወደፊት ለሚኖርሽ ደስተኛ ኑሮ እውነተኛ ቁልፉ የቁመና ማራኪነት አለመሆኑን ለምን አታስተውዪም?
አካላዊ ውበትን የተላበስሽ ልጃገረድም ብትሆኚም ሐቁ ከዚህ አይዘልም፡፡ ብዙ ቆንጆ ሴቶች በጣም ከንቱና ይልቁኑም የብልግና ኑሮ የሚኖሩ ሆነው እንደቀሩ መገንዘብ ይኖርብሻል፡፡ ይህ ኑሮ ኀዘንና «ምነው ባልተፈጠርኩ?» የሚያሰኝ ጸጸት የሞላበት እንደሆነ ግልጽ ነው።መልከ ጥፉ ሴት ከሆንሽ ብታስተውዪው ብዙ ቆንጆ ሴቶች ሕይወታቸው መና የቀረበት ፈተና ላንቺ እንደቀረልሽ ትረጃለሽ፡፡
ውስጣዊ ማንነት እንጂ ውጫዊ ቁመና ከንቱና ጠፊ መሆኑን ማወቅ ካቃተሽ ምንም ቆንጆ ብትሆኚ ትልቅ ጥበብ ጎሎሻል ማለት ነው።በዓለም ኣስቀያሚ ፍጥረት የሚባለው ደግሞ ጥበብ የጎደለው ነው።መጽሐፍ ቅዱስ «የወርቅ ቀለበት በእሪያ አፍንጫ እንደሆነ ከጥበብ የተለየች ቆንጆ ሴትም እንዲሁ ናት» ይላል፡፡ ምሳሌ 11÷22 በተጨማሪም «ውበት ሐሰት ነው፥ ደም ግባትም ከንቱ ነው፣ እግዚአብሔርን የምትፈራ ሴት ግን እርሷ ትመሰገናለች» የሚል ቃል ይገኛል።ምሳ31፥30 አንቺ ምን ያህል እግዚአብሔርን ትፈሪዋለሽ? በፆታሽና በቁመናሽ ምን ያህል ደስተኛ ነሽ? ያለሽን ሕዋሳት በሙሉ እግዚአብሔር ባሉበት ሁኔታ ዐውቆ እንደሰጠሽ አስበሽ በደስታ ተቀብለሻል? እንዲህ ከሆነ በጣም ቆንጆ ሴት ነሽ ማለት ነዋ!

ቀጣይ ምዕራፍ ዐሥር ክፍል አንድ:
👉 "ወጣቶችና ትምህርት "
👉"የትምህርት ዓይነቶች "
በሚል ይቀጥላል .....
ለጥያቄና አስተያየት @Ethiopian_Orthodox_bot ተጠቀሙ።

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

ሕይወተ ወራዙት(የወጣቶች ሕይወት)
 ምዕራፍ ዘጠኝ ክፍል ስድስት
.................................................

ክርስቲያናዊ ፀጉር አያያዝ እንዴት ነው?
ፀጉርን ማሳመር የሚችሉ ብዙ የፀጉር አያያዝ ዘዴዎች አሉ፡፡ ከእነዚያም ውስጥ ክርስቲያኖች ሊቀበሉት የማይገባ የፀጉር አያያዝ መንገድ አይጠፋምና መጠንቀቅ ያስፈልጋል፡፡ ለፀጉር አሠራር ደግሞ ማንኛውንም መንገድ ብከተል ምን አለበት? ማለት ጥሩ አይደለም፡፡ የሰው የልቦና ክፋት ከልክ ያለፈና ለመንፈሳዊነት ተፃራሪ የሆነ የፀጉር አያያዝን አስከትሏልና፡፡ ስለዚህ ሐዋርያት በተለያየ ስፍራ ስለ ፀጉር አያያዝ የሚበጅ መመሪያ አስተላልፈዋል፡፡
ለምሳሌ፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስና ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ ክርስቲያን ሴቶች ከልክ እንዳያልፉ ወይም ለፀጉር አያያዝ ከመጠን ያለፈ ትኩረት እንዳይሰጡ መምከር አስፈላጊ ሆኖ ስላገኙት «ለእናንተ ጠጉርን በመሸረብና ወርቅን በማንጠልጠል ወይም ልብስን በመጎናጸፍ በውጭ የሆነ ሽልማት አይሁላችሁ» በማለት ተመሳሳይነት ያለውን መልእክት ጽፈዋል።1ጴጥ3፥3፤ 1ጢሞ2፥10
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ እንደ ተናገረው ለሴት «ፀጉርዋ መጎናጸፊያ ሊሆን ተሰጥቶአታል» 1ቆሮ11:15 ስለዚህ ፀጉሯን ማስረዘም ተገቢ ነገር ነው:: ፀጉሯን «መቁረጥ ወይም መላጨት የሚያሳፍር» መስሎ ካልተሰማት መቁረጥ ወይም መላጨት መብቷ ነው:: ፀጉሯን ካስረዘመች ግን በጸሎት ጊዜ «ራሷን ትሸፍን» ወይም ትከናነብ፡፡ 1ቆሮ11÷6

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

ሴቶች «ሱሪ» መልበስ ይችላሉ?
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ስለ ወንድና ስለ ሴት ኣለባበስ ብዙ መግለጫዎች አሉ፡፡ ለምሳሌ ከወንዶች አልባሳት ተርታ ከተጠቀሱት ውስጥ መታጠቂያ፣ መደረቢያ፣ መጎናጸፊያ፣ ስናፊል፣ ቀሚስ፣ እጀ ጠባብ፣ ካባና ድግ ይገኙበታል፡፡ 1ሳሙ18፥4፤2፥19 ዳን3፥21 ምሳ31፥24፤ ዮሐ19፥23፥ ኢያ7:21 በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ከተጠቀሱት የሴቶች አልባሳት መካከል ደግሞ የሚከተሉት ይገኙበታል፡፡ እነርሱም: ልግም በገላ፣ መታጠቂያ፣ መጎናጸፊያ፤ ራስ ማሠሪያ፣ ቀጸላና ዓይነ ርግብ ናቸው:: ኢሳ3÷20-24
«ሱሪ» ግን በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ለወንዶች ይልቁንም ለካህናት ብቻ ተጠቅሶ እናገኘዋለን፡፡ ዘጸ39፥29 ያም ቢሆን በተለይ በሀገራችን አብዛኛው ማኅበረ ስብአ «ሱሪ»ን ያለ አንዳች ተደራቢ ነገር መልበስ የወንዶች መደበኛ አለባበስ አድርጎ መቀበሉን ማረጋገጫ አያስፈልገውም፡፡ ስለዚህ ተገቢ ያልሆነን አለባበስ መርምሮ እንኳን «ሱሪ» ይቅርና ቀሚስም ቢሆን አለመልበስ ለሴቶች የተገባ ነው። ወንዶችም ቢሆኑ ሱሪ ስለ ሆነ ብቻ ሳይሆን በልዩ ልዩ መንገድ መዝኖ ሊያደርጉት የማይገባ ከሆነ መተው ይጠበቅባቸዋል።
በተረፈ ሴቶች «ሱሪ» መልበሱን ካልተውት ሲብስ ነው እንጂ «ሱሪ» በመሆኑ ብቻ ለባሾቹን ከመተቸት መተው ይመረጣል። እንዲህ የተባለው «ሴቶች ሱሪ መልበስ አይተዉም» በማለት ተስፋ ከመቁረጥ የመነጨ ሳይሆን «ሱሪ» መልበስ እጅግም የሚነቅፉት ነገር ባለመሆኑ ነው:: ምክንያቱም እንደኛ አርአያን መለወጥ ከሚለው ምሥጢር ከመነሣት ካልሆነ በቀር ሱሪ በመሆኑ ብቻ «ሱሪ› መልበስን ለመንቀፍ በቂ መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሠረት አይኖረንም። ሁለተኛ ሁሉም ባይሆኑ አንዳንድ ሴቶች ሱሪ የሚለብሱበት የጤና መታወክን ጨምሮ አፍን የሚያሲዝ በቂ ምክንያት አላቸው።ሦስተኛ ደግሞ መሠረት በሌለው ነገር ለመተቸት መሞከር የሚጎዳው የሚለብሱትን ሳይሆን ሐሜተኞቹንና እንተቻለን ባዮቹን በመሆኑ ነው።

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

ሕይወተ ወራዙት(የወጣቶች ሕይወት)
 ምዕራፍ ዘጠኝ ክፍል አምስት
.................................................

«ሴት የወንድ ልብስ አትልበስ» ሲል ምን ማለቱ ነው?
መጽሐፍ ቅዱስ «ሴት የወንድ ልብስ አትልበስ ወንድም የሴትን ልብስ አይልበስ ይላል።» ዘዳ22፥5 ይህን የእግዚአብሔር ቃል «ሴት ሱሪ አትልበስ ማለቱ ነው» በማለት የሚፈቱት አንዳንዶች ኣሉ።ነገር ግን ይህ ቃል ምሥጢሩ ከዚህም በላይ ከፍ የሚልና «ሴት ወንድነትን አትላበስ ወንድ ደግሞ ሴትነትን አይላበስ ሁለቱም በተፈጠሩበት ጾታ ጸንተው ይገኙ» ማለትም ይሆናል፡፡ ምክንያቱም ሴትነታቸውን የሚያማርሩ «ዘር ላቀብል » እስከ ማለት የሚደርሱ እጅግ ብዙ «ወንዳ ገረድ» ሴቶች መኖራቸው ይታወቃል።ከወንዶችም ደግሞ «ዘር ልቀበል፣ ላምጥ፡ ልውለድ የሚሉ ወንዶች በርካታ ናቸው። ይህ ጎዳና «በአምላካችን በእግዚአብሔር ዘንድ የተጠላ ነውና» መጽሐፍ ቅዱስ ሴት የወንድን ወንድ ደግሞ የሴትን ልብስ አይልበስ ማለቱ እውነት ነው፡፡ ዘዳ 22፥5

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

ዐረገ በስብሀት ዐረገ በእልልታ :
ሞትን ድል አድርጎ የሠራዊት ጌታ።

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

ዕርገት

ከጌታችን ፱ቱ አበይት በዓላት ውስጥ አንዱ ዕርገት ነው፡፡

“እያዩት ወደሰማይ ዐረገ”(ሉቃ 24÷50 የሐዋ 1÷9)

ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትን ድል አድርጎ ከተነሳ በኋላ ለሰላሳ ዘጠኝ ቀናት ያህል ለሐዋርያቱ በተለያየ ጊዜ እየተገለጠ ለአገልግሎት ሲያዘጋጃቸው እና ስለ እግዚአብሔር መንግስት ምስጢር እያስተማራቸው ከቆየ በኋላ በ፵ኛው ቀን በሐዋርያቱ ፊት አርጓል። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ከምታከብራቸው የጌታችን አበይት በዓላት አንዱ ዕርገት ነው።

ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ በተነሣ በ፵ኛው ቀን ወደ ሰማይ አረገ ያረገበትም ቦታ ቢታንያ አጠገብ የሚገኘው ደብረ ዘይት የሚባለው ተራራ ነው። አሥራ አንዱ ሐዋርያትን እዚያ ድረስ ከወሰዳቸው በኋላ ባርኳቸው እያዩት ዐረገ። ደመና ከዓይናቸው ሰውራ ተቀበለችው። በእግዚአብሔርም ቀኝ ተቀመጠ። ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ቀደመ ክብሩ፤ በመለኮታዊ ክብሩ ወደ ሰማይ አርጎ በአባቱ ቀኝ ተቀመጧል። ጌታችን ያረገውም በለበሰው ሥጋ በመሆኑ እና ለሁለተኛ ጊዜ ለፍርድ በሚመጣበት ጊዜ ይህን ክብር እኛም እንድናገኝ ምሳሌ ሲሆነን ነው።

በሚመጡ ዘመናትም በክርስቶስ ኢየሱስ ለእኛ ባለው ቸርነት ከሁሉ የሚበልጠውን የጸጋውን ባለ ጠግነት ያሳይ ዘንድ፥ ከእርሱ ጋር አስነሣን በክርስቶስ ኢየሱስም በሰማያዊ ስፍራ ከእርሱ ጋር አስቀመጠን። ኤፌ . ፪፡፮ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ ዕርገቱ አስመልክቶ ከተናገራቸው ሦስት ነገሮች ውስጥ፦

#የመጀመሪያው፤ እኔም ከምድር ከፍ ከፍ ያልሁ እንደ ሆነ ሁሉን ወደ እኔ እስባለሁ። ዮሐ . ፲፪፡፴፪
#ሁለተኛው ደግሞ፤ ወላጆች እንደ ሌላቸው ልጆች አልተዋችሁም፤ ወደ እናንተ እመጣለሁ። ዮሐ .፲፬፡፲፰
#ሶስተኛው፤ እኔ ግን እውነት እነግራችኋለሁ፤ እኔ እንድሄድ ይሻላችኋል። እኔ ባልሄድ አጽናኙ ወደ እናንተ አይመጣምና፤ እኔ ብሄድ ግን እርሱን እልክላችኋለሁ። ዮሐ . ፲፮፡፯

የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ዕርገት ለእኛ ትልቅ ተስፋ ነው ስለዚህም ሐዋርያት ጌታችን ሲያርግ ወደ ሰማይ ትኩር ብለው ይመለከቱት እንደነበር እኛም በታላቅ ተስፋ የጌታን ነገር ልናስብ ይገባል። ነቢዩ ዳንኤል ስለ ጌታችን ዕርገት እና በአብ ቀኝ ስለመቀመጡ እንዲህ ሲል በትንቢት ተናግሮ ነበር፤ "በሌሊት ራእይ አየሁ፤ እነሆም፥ የሰው ልጅየሚመስል ከሰማይ ደመናት ጋር መጣ
በዘመናት ወደ ሸመገለውም ደረሰ፤ ወደ ፊቱም አቀረቡት። ወገኖችና አሕዛብ በልዩ ልዩ ቋንቋም የሚናገሩ ሁሉ ይገዙለት ዘንድ ግዛትና ክብር መንግሥትም ተሰጠው፤ ግዛቱም የማያልፍ የዘላለም ግዛት ነው፥መንግሥቱም የማይጠፋ ነው።" ዳን. ፯፡፲፫ - ፲፬ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ካረገ በኋላ በአብ ቀኝ ተቀመጠ ስንል ጌታ ከአብ ጋር እኩል ነው ማለታችን ነው።

ከ፬ቱ ወንጌላት ውስጥ ይህን የዕርገቱን ታሪክ የመዘገቡት የማርቆስ ወንጌልና የሉቃስ ወንጌል ናቸው። ከሳምንቱም በመጀመሪያው ቀን ማልዶ በተነሣ ጊዜ፥ አስቀድሞ ሰባት አጋንንት ላወጣላት ለመግደላዊት ማርያም ታየ። እርስዋ ሄዳ ከእርሱ ጋር ሆነው ለነበሩት ሲያዝኑና ሲያለቅሱ ሳሉ አወራችላቸው፤ እነርሱም ሕያው እንደ ሆነ ለእርሷም እንደታያት ሲሰሙ አላመኑም። ከዚህም በኋላ ከእነርሱ ለሁለቱ ወደ ባላገር ሲሄዱ በመንገድ በሌላ መልክ ተገለጠ፤ እነርሱም ሄደው ለሌሎቹ አወሩ፤ እነዚያንም ደግሞ አላመኑአቸውም። ኋላም በማዕድ ተቀምጠው ሳሉ ለአሥራ አንዱ ተገለጠ፥ ተነሥቶም ያዩትን ስላላመኑአቸው አለማመናቸውንና የልባቸውን ጥንካሬ ነቀፈ። እንዲህም አላቸው። "ወደ ዓለም ሁሉ ሂዱ ወንጌልንም ለፍጥረት ሁሉ ስበኩ። ያመነ የተጠመቀም ይድናል፥ ያላመነ ግን ይፈረድበታል። ያመኑትንም እነዚህ ምልክቶች ይከተሉአቸዋል፤ በስሜ አጋንንትን ያወጣሉ፤ በአዲስ ቋንቋ ይናገራሉ፤ እባቦችን ይይዛሉ፥ የሚገድልም ነገር ቢጠጡ አይጎዳቸውም፤ እጃቸውን በድውዮች ላይ ይጭናሉ እነርሱም ይድናሉ። ጌታ ኢየሱስም ከእነርሱ ጋር ከተናገረ በኋላ ወደ ሰማይ ዐረገ በእግዚአብሔርም ቀኝ ተቀመጠ።" ማር. ፲፮፡፱-፲፱ "እናንተም ለዚህ ምስክሮች ናችሁ። እነሆም፥ አባቴ የሰጠውን ተስፋ እኔ እልክላችኋለሁ፤ እናንተ ግን ከላይ ኃይል እስክትለብሱ ድረስ በኢየሩሳሌም ከተማ ቆዩ። እስከ ቢታንያም አወጣቸው እጆቹንም አንሥቶ ባረካቸው። ሲባርካቸውም ከእነርሱ ተለየወደ ሰማይም ዐረገ።" ሉቃ. ፳፬፡፵፰-፶፩

ቅዱስ ሉቃስ የሐዋርያት ሥራን ሲጽፍ ስለ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዕርገት አብራርቶ ጽፎታል። እንዲህ ሲል፦ ደግሞ አርባ ቀን እየታያቸው ስለ እግዚአብሔርም መንግሥት ነገር እየነገራቸው፥ በብዙ ማስረጃ ከሕማማቱ በኋላ ሕያው ሆኖ ለእነርሱ ራሱን አሳያቸው። ከእነርሱም ጋር አብሮ ሳለ ከኢየሩሳሌም እንዳይወጡ አዘዛቸው፥ ነገር ግን።" ከእኔ የሰማችሁትን አብ የሰጠውን የተስፋ ቃል ጠብቁ፤ ዮሐንስ በውኃ አጥምቆ ነበርና፥ እናንተ ግን ከጥቂት ቀን በኃላ በመንፈስ ቅዱስ ትጠመቃላችሁ" አለ። እነርሱም በተሰበሰቡ ጊዜ። "ጌታ ሆይ፥ በዚህ ወራት ለእስራኤል መንግሥትን ትመልሳለህን?" ብለው ጠየቁት። እርሱም "አብ በገዛ ሥልጣኑ ያደረገውን ወራትንና ዘመናትን ታውቁ ዘንድ ለእናንተ አልተሰጣችሁም፤ ነገር ግን መንፈስ ቅዱስ በእናንተ ላይ በወረደ ጊዜ ኃይልን ትቀበላላችሁ፥ በኢየሩሳሌምም በይሁዳም ሁሉ በሰማርያም እስከ ምድርዳርም ድረስ ምስክሮቼ ትሆናላችሁ" አለ። ይህንም ከተናገረ በኋላ እነርሱ እያዩት ከፍ ከፍ አለ፤ ደመናም ከዓይናቸው ሰውራ ተቀበለችው። እርሱም ሲሄድ ወደ ሰማይ ትኵር ብለው ሲመለከቱ ሳሉ፥ እነሆ፥ ነጫጭ ልብስ የለበሱ ሁለት ሰዎች በአጠገባቸው ቆሙ፤ "ደግሞ የገሊላ ሰዎች ሆይ፥ ወደ ሰማይ እየተመለከታችሁ ስለ ምን ቆማችኋል? ይህ ከእናንተ ወደሰማይ የወጣው ኢየሱስ ወደ ሰማይ ሲሄድ እንዳያችሁት፥ እንዲሁ ይመጣል" አሏቸው። ሐዋ. ፩፡፫-፲፩

ክርስቲያኖች በሰማያት ስፍራ ከጌታችን ከመድሃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር አብረው እንደሚቀመጡ የእርሱ ዕርገት ያረጋግጥልናል። ቅዱስ ጳውሎስም ስለ ጌታችን እርገት እንዲህ ሲል ይመክረናል፤ "እንግዲህ ከክርስቶስ ጋር ከተነሣችሁ፥ ክርስቶስ በእግዚአብሔር ቀኝ ተቀምጦ ባለበት በላይ ያለውን እሹ። በላይ ያለውን አስቡ እንጂ በምድር ያለውን አይደለም። ሞታችኋልና፥ ሕይወታችሁም በእግዚአብሔር ከክርስቶስ ጋር ተሰውሮአልና። ሕይወታችሁ የሆነ ክርስቶስ በሚገለጥበትጊዜ፥ በዚያን ጊዜ እናንተ ደግሞ ከእርሱ ጋር በክብር ትገለጣላችሁ።" ቆላ. ፫፡፩-፬

ኖርንም ሞትንም የክርስቶስ ነንና ዘላለማዊ ሕይወትን እንወርስ ዘንድ አምላካችን ይርዳን። ልዑል እግዚአብሔር በኑሮአችን ሁሉ ባርኮን፤ ቀድሶን፤ በእርሱ ፈቃድ እንድንኖር ይርዳን። የምንሻትን መንግስተ ሰማያትን ያወርሰን ዘንድ የእናቱ የድንግል ማርያም አማላጅነት፤ ስለ እርሱ ክብር ሲሉ ሕይወታቸውን ሰውተው ያለፉት ቅዱሳን ሰማዕታት ምልጃ እና ጸሎት አይለየን አሜን።

[በዲያቆን ንጋቱ አበበ]
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

በእርግጥ በነቢይነት መታወቅ ክብር ያለው ነገር ነው።ይሁን እንጂ ቀጥሎ የሚጠቀሰው የመጽሐፍ ቅዱስ ቃል ምሳሌ አለባበስ አንድን ሰው በወራዳና በተነወረ ተግባርም ሊያሳውቀው እንደሚችል ያሳያል።የይሁዳ ምራት ትዕማር የፈለገችውን ለማግኘት ዓላማ አድርጋ የመበለትነት ልብሷን አወለቀችና መጎናጸፊያና መሸፈኛ ለብሳ ከመንገድ ዳር ተቀመጠች።አማቷ ይሁዳ በዚያ መንገድ ሲያልፍ «ጋለሞታ መሰለችው ፊትዋን ሸፍና ነበርና» በማለት መጽሐፍ ቅዱስ ይተርካል፡፡ ትዕማርን አለባበሷ በጊዜው የነበሩትን ጋለሞታዎች አስመስሏት ነበር።ዘፍ38 ፥ 13-15
እንደ ቀድሞ ጊዜ ሁሉ ዛሬም ምንም እንኳን ያን ልብስ የሚለብሱ ሰዎች የሚያደርጉትን ባናደርግና የሚያምኑትንም ባናምን አለባበሳችን ግን እንደ እነርሱ ከሆነ ከእነርሱ ጋር በአንድ ሊያስመድበን ይችላል፡፡ ሌሎች ከአለባበሳችን ተነሥተው ስለ እኛ እንዲህ በማሰባቸውና በመገመታቸው ልንፈርድባቸው እንችላለንን? ሌሎች አሳባቸውን እንዲለውጡ ከማድረግና እኛ አለባበሳችንን ከማስተካከል የቱ ይቀላል? በቀላሉ ሲገለጽ አሳብን ከመቀየር ልብስን መቀየር አይቀልምን?
ልብስ የሕግ አስከባሪዎች (ፖሊሶች)፣ ፈሊጠኞችና የሥነ መንግሥት ሰዎች (ፖለቲከኞች)፣ የእሳት አደጋ ተከላካዮች ወይም የሕክምና ባለሙያዎችና የወታደሮች ብቻ መለያ አይደለም፡፡ በረከሰ ተግባር የተሰማሩ ሰዎችም በአለባበሳቸው ተለይተው ሊታወቁ ይችላሉ፡፡ ለምሳሌ፡ ብዙ ዝሙት አዳሪዎች የሚለብሱት አካልን የሚያጋልጥና ምንዝርን የሚያሳስብ ልብስ ይበልጥ ግልጽ በሆነ ሁኔታ የተሰማሩበትን ተግባር ያመለክታል፡፡ እንደ መልካሞቹ ሁሉ ግብረ ሰዶም ፈጻሚዎች፣ በዝርፊያ ተግባር የተሰማሩ ሰዎች፣ ወንበዴዎችና በልዩ ልዩ መጥፎ ተግባር የተሰማሩ ሰዎች ተለይተው የሚታወቁበትን የፋሽን ልብስ ይለብሳሉ። አንቺስ ከእነዚህ እንደ አንዱ ሆነሽ ለመታየት ትፈልጊያለሽ?
በማኅበረሰቡ ዘንድ የሚነቀፍ፣ ወይም መጥፎ ግብርን የሚያመለክት አለባበስ ብትከተይና ሥራ ለመቀጠር ወይም በቤተ ክርስቲያን ውስጥ መንፈሳዊ ተግባር ለማከናወን ወይም አንድ ዓይነት መንፈሳዊ አገልግሎት ለማግኘት በምትሞክሪበት ጊዜ ችግር ቢያጋጥምሽ ልትደነቂ ይገባል? እርግጠኛ ነኝ አለባበስሽ ዘወትር ግብረ ገብነት ይጎደለው ከሆነ የዚህ ዓይነት አንድ አጋጣሚ ሳይኖርሽ አይቀርም፡፡ ግን በማን ፈረድሽ? በናቁሽ፣ በተጸየፉሽ፣ መብትሽንና የመሰለሽን እንዳታደርጊ በከለከሉሽ፣ ባንጓጠጡሽና ፊት በነሡሽ ወይስ በራስሽ? እርግጥ ነው እንዲህ ማድረጋቸው ትክክል አይሆን ይሆናል ግን የችግሩ ዋና ምንጭ አንቺ መሆንሽን ለምን ትዘነጊዋለሽ?
በዚህ አንቀጽ ነውረኛ አለባበስ በእጅጉ ቢነቀፍና ስለአለባበስ ከልክ ያለፈ ጭንቀት እንደማያስፈልግ ቢጻፍም ስለ መልካም የአለባበስ ልማድ ለማስተማር ነው እንጂ በጥቅሉ ልብስን ለመኮነን አይደለም፡፡ በተገቢው መንገድ ከሆነ አንዲት ሴት በአለባበሷ ብቻ ሳይሆን በቤት አያያዟና በኑሮ'ዋ ሁለ ጠንቃቃ መሆን ያስፈልጋታል፡፡ ቤቷን ንጹሕና ስንዱ አድርጎ መያዝ፣ በእንቅልፍ፣ በአመጋገብና በሥራ ወቅት ሰዓት አክባሪ መሆን፣ ለግልፍተኝነት፣ አክብሮት ለጎደለውና ለሻካራ ንግግር አለመሸነፍ ይኖርባታል፡፡ እንዲህ ባደረገች ቁጥር ጸጥታ፣ ከጸጸት የመዳን፣ የመረጋጋትና የአሸናፊነት ስሜት ይሰማታል፡፡ ይህም የሚያጋጥማትን ሌሎች የስሜት ጫናዎች ቀላል ለማድረግ ይረዳታል፡፡
ሴት ልጅ ከአለባበሷ ጀምሮ ቸልተኛ፣ ሰነፍና ዝርክርክ ብትሆን ብዙ ልትጎዳ ትችላለች።ዝርክርክነት ቀላልና ብዙ ዋጋ የማያስወጣ ይመስላል። ይሁን እንጅ በሌሎች መንገዶች ብዙ ነገር ሊያስቀር ይችላል።አንዲት ሴት ልብሶቿ በውድ ዋጋ የተገዙና የዘመኑን ፋሽን የተከተሉ ባይሆኑም ንጹሕና በሥርዓት የተያዙ ከሆኑ ጠንቃቃ መሆኗን ያሳያሉ፡፡ እንዲህ ከሆነ ሌሎች ሰዎች በይበልጥ ያከብሯታል ፤ በእርሷም ላይ የበለጠ እምነት ያሳድራሉ፡፡

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

በ. ስለራሳቸው በጣም የሚኮሩ ሰዎች ኩራታቸውን የሚያሳዩት ብዙ ጊዜ ስለ አለባበሳቸው ከመጠን በላይ በመጨነቅ ነው፡፡ በልብሳቸው ወይም በመልካቸው ሁል ጊዜ «ሌሎችን አስንቀው» ለመታየት ይፈልጋሉ።ይህንንም ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ እንዲህ ሲል ገልጾታል፦ «ከመ ትዘኀሪ መትትመክሒ በላዕለ ብዙኃት አንስት ነዳያት ወትትዐበዪ በቅድመ አዕይንቲሆን ወትምስዊ አልባቢሆን ወታድውዪ ነፍሳቲሆን ወትወስኪዮን ንዴተ በዲበ ንዴቶን» ይህም አንቺ ሴት አጊጠሽ መውጣት የምትፈልጊው «ልብስ በሌላቸው በድሆች ላይ ልትመኪ፣ በፊታቸው ልትታበዪ፣ ልቡናቸውን በቅንአት እንደ ሰም ልታቀልጪ፣ ሰውነታቸውን በቅንአት ልታሳምሚና በኃዘናቸው ላይ ኃዘን ልታመጪባቸው ወደሽ ነው እንጂ በሌላ ምክንያት አይደለም።» ማለት ነው:: አንቺ ራስሽ «ዝንጥ» ያልሽ ጊዜ እንዲህ ዓይነት ስሜት ተሰምቶሽ አያውቅም? ተግ.ዮሐ28
ውድና ጌጠኛ ልብስ መልበስ ያኮራሻል? ይህ የሚያኮራሽና ከሌላው ሰው የበለጥሽ መስሎ የሚሰማሽ ከሆነ ሰነፍ ሴት ነሽ፡፡ አላዋቂ በመሆንሽም ታሳዝኛለሽ እንጂ አታስጎመጂም፡፡ ምክንያቱም እንኳን ዐዋቂው የሰው ልጅ ይቅርና ፈረስና በቅሎ እንኳን የሰው ያህል ዕውቀት ሳይኖራቸው በጣም የሚደሰቱት ጌጣጌጥ አድርገውላቸው ከሚነዷቸው ይልቅ አራግፈው ሲያቀሉላቸው ነው።ስለዚህ ዐዋቂ የሚባል የሰው ልጅ ወርቁን ሐሩን በራሱ ቢሸከመው በወገቡ፣ በደረቱ፣ በእጁና በጣቱ ቢያጠልቀው በአንገቱም ቢያንጠለጥለው ሊያፍር እንጂ ሊኮራ አይገባውም ነበር፡፡
ያደረገው የወርቅና የሐር ጌጥ ዕወቀትና ሕይወት የሌለው ፍጡር በመሆኑ ነው እንጂ ኩራት የሚገባው ለእርሱ ነበር። ለባሕርይው የማያሻው ነገር ከተጫነበት ሰው ይልቅ ጌጡ ቢከብር ምን ይደንቃል? በላዩ የተቀመጠበት ሳይኮራ ተሸካሚው የሰው ልጅ መኩራቱና መደሰቱ እጅግ የሚያሳዝንና ዐላዋቂነት ነው። ተመልካቾችም ስለዚህ ሽክም ምክንያት ሊያዝኑለት ሲገባቸው ቢቀኑበት ወይም ቢያከብሩት ቅዱስ ያዕቆብ ለወርቅና ለብር በመሳሳታቸው የነቀፋቸው ከንቱዎች ናቸውና አይመሰገኑም፡፡ ዐዋቂ ግን ሌላውን ባለው ወርቅና ብር ብዛት አያከብርም።ለራሱም ቢሆን በሀብቱ ብዛት እናደሚከበር አያስብም አይቀበለውምም፡፡
በሌላ አቅጣጫ ስንመለከተው ደግሞ አንዳንድ ጊዜ ስለ ልብስ «ግድ የለሽ» መሆንም ኩራትን ወይም ራስ ወዳድነትን ሊያሳይ ይችላል፡፡ በአለባበሱ የተዝረከረከው ግለሰብ ስለ አለባበሱ ግድ የለሽ የሆነው በስንፍና ምክንያት ሊሆን ቢችልም አለባበሱ በሌሎች ላይ ለሚያሳድረው ተጽዕኖ «ምን ቸገረኝ!» የሚል ዓይነት ዝንባሌ ያለው ሰው መሆኑን ሊጠቁም ይችላል፡፡
ተ. እኛ ራሳችንን ከምንመለከተው በላይ ሌሎች ሰዎች ይመለከቱናል፡፡ ታዲያ ሌሎች ሲመለከቱን መልካም ነገር ከእኛ እንዲያገኙ መጣር የለብንምን? ይህም ስለ ስሜታቸው እንደምንጠነቀቅላቸው የሚያሳይ መሆን አለበት፡፡ ብዙ ክርስቲያኖች ግን ነገረ ሥራቸው በሙሉ ወዳጆቻቸው ስለራሳቸው በሚያስቡበት ጊዜ እንዲሸማቀቁ የሚያደርግ ነው:: በዚህም ተግባራቸው «እያንዳንዳችን እንድናንጸው እርሱን ለመጥቀም ባልጀራችንን ደስ እናሰኝ» በማለት ሐዋርያው የተናገረውን ምክር ቀኑን ሙሉ ሲሽሩት ይውላሉ፡፡ ሮሜ 12÷2
ቸ. አንቺ ሴት እስኪ ነፍስሽን ትሕትና አስተምሪያት።ሁልጊዜ ደምቆና አሽብርቆ መታየት ብቻ ሳይሆን ተራና መናኛ ልብስን መልበስንም ተለማመጂ።«ሞትን የምታለብስና ወደ ሲኦል የምታወርድ አፍአዊ ጌጥን» ከልክ በላይ አትውደጂ:: ይህ በነፍስ እንደ ማጌጥ በእግዚአብሔር ፊት አያኮራሽምና፡፡ ለአፍአዊ ጌጥ የማትጓጓ ሴት ዘውድ ከደፋ ንጉሥ ትበልጣለች፡፡ እንዴት? ቢባል ሰው ሁሉ ለቁሳቁስ ሲገዛ እሷ አትገዛምና፡፡
ነ. አንዳንድ ሰዎች ስለ አለባበስ ባይሰበክ ይመርጣሉ።ብዙዎች ደግሞ «ለምን ስለ ሌላ ነገር አታስተምሩም? ከዚህ ይልቅ ብዙ አንገብጋቢ ርእሰ ጉዳይ የለምን?» ይላሉ።አርግጥ ቅድሚያ የሚሰጠው ነገር ይኖር ይሆናል፣ ሆኖም የአለባበስ ጉዳይም በክርስትና ዐቢይ ነገር ነው።ያ ባይሆን ኖሮ ሐዋርያትም ሆኑ ሊቃውንት ስለ አለባበስ ብዙ ባልጻፉ ነበር፡፡ ይህ ጉዳይ ተራ ነው የምትዪ ከሆነ አለባበስሽን በማስተካከል ተራነቱን አንቺ ራስሽ አስቀድመሽ ማሳየት ይገባሻል፡፡ ካልሆነ በጉዳዩ በየጊዜው ላለመገሠጽ ብለሽ ትምህርቱን ማናናቅሽ አስተዋይ አያደርግሽም።

ቀጣይ ምዕራፍ ዘጠኝ ክፍል ዐራት :
👉አለባበስሽ ስለ አንቺ በደንብ ይናገራል!
👉አፋዊ ጌጥን መውደድ "አምልኮ ጣዖት ነው!" የሚባለው ለምንድር ነው?
በሚል ይቀጥላል .....
ለጥያቄና አስተያየት @Ethiopian_Orthodox_bot ተጠቀሙ።

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

ሕይወተ ወራዙት(የወጣቶች ሕይወት)
 ምዕራፍ ዘጠኝ ክፍል ሦስት
.................................................

በአልባሳት በምታጌጪበት ጊዜ ልታስተውያቸው የሚገቡ ነገሮች!
ሀ. ወጣት በምትሆኚበት ጊዜ ስለ አለባበስሽና ስለ ውጫዊ ማንነትሽ የምትጨነቂው በአብዛኛው እኩዮችሽ ስለ አንቺ ምን እንደሚያስቡ በማሰብ ነው። በዚህ ጉዳይ ብዙ አትልፊ እነርሱ ራሳቸው በመለወጥ ላይ ያሉ ገና ታዳጊዎች መሆናቸውን መዘንጋት የለብሽም።ስለዚህ ዛሬ በአድራጎትሽ ቢደሰቱ ነገ በጭራሽ ላይደሰቱ ይልቁንም ነገሮች ሲገቧቸው ባሳደርሽባቸው ተጽዕኖ ሊያዝኑብሽም ይችላሉ፡፡
እኩዮችሽን ያስደስታል ብለሽ የምታደርጊው ነገር ወላጆችሽንና በአንቺ ግምት የምታከብሪያቸውን፣ የምታደንቂያቸውንና ከፍ አድርገሽ የምትመለከቻቸውን ሰዎች በእጅጉ ሊያሳዝናቸው ይችላል።ለምን ቢባል ከእኩዮችሽ ይልቅ አድራጎትሽ የሚያስከትለውን ቀውስ መመርመር ስለሚችሉ ነው።በወላጆችሽና እንደነዚህ ባሉ ሰዎች ዘንድ ዝቅ ተደርገሽ እንዳትታዪና እንደ ትልቅ ሴት እንድትቆጠሪ ከፈለግሽ ከአለባበስሽ ይልቅ ስለመልካም ሴትነትሽ ተጨነቂ፡፡
ለ. ሴቶች ያገቡ ወይም ያጩ ከሆነ ልብስ በሚለብሱበት ጊዜ ስለ ትዳራቸው በትኩረት ማሰብ ይኖርባቸዋል፡፡ ልብስ ከግብረ ዝሙት ጋር የጠበቀ ትስስር ስላለው ባሎች የሚስቶቻቸውን አለባበስ በጥንቃቄ ይከታተላሉ፡፡ ለአፋቸው ልበሺው «ያምርብሻል» ቢሉም እንኳን ሚስቶች ለባሎቻቸው ሕሊና መጠንቀቅ ይኖርባቸዋል፡፡ ይህን ቸል ብላ የምታልፍ ሴት የገዛ ትዳሯን በራሷ እጅ እያፈረስች መሆኗን ማወቅ አለባት።ምክንያቱም የሴቶች አለባበስ በወንዶች ስሜት ላይ ያለውን ሚና ወንዶች ከራሳቸው በመነሣት በሚገባ ስለሚያውቁ ያንቺ አለባበስ የሚያስከትለውን መዘዝ ለመገመት ለባልሽ በጣም ይቀለዋል።

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

«የሚገባ ልብስ»
ክርስቲያኖች ሊለብሱት የሚገባና የማይገባ የልብስ ዓይነት አለ፡፡ ለዚህም ቅዱስ ጳውሎስ «ሴቶች በሚገባ ልብስ ከእፍረትና ራስን ከመግዛት ጋር ሰውነታቸውን ይሸልሙ።› በማለት የተናገረው ቃል ምስክር ነው:: 1ጢሞ2፥10
የማይገባ ልብስ የሚባለው አካልን ለእይታ የሚያጋልጥና ፀረ ክርስትና መልእክት ያለው ልብስ ሁሉ ነው።በላዩ ላይ የዝሙት መልእክት ያለው ሥዕልና ጽሑፍ ያዘለ ከሆነ፡ ስስና ዘርዛራ ወይም ከገላ ጋር የሚጣበቅ ሆኖ ገላን የሚያሳይና ቅርጽን የሚያወጣ ከሆነ ወይም በማናቸውም መልኩ ክርስቲያናዊ ዓላማን የሚፃረር ከሆነ ክርስቲያኖች ሊለብሱት አይገባም።
የማይገባ አለባበስ የሚባለው የሴቶች ሱሪ መልበስ ብቻ አይደለም።ቀሚስም የማይገባ ልብስ ሆኖ የሚገኝበት ብዙ መንገድ አለ፡፡ ለምሳሌ እጅግ ቢያጥር ወይም ተሰንጥቆና ሳስቶ ሰውነትን ለእይታ ካጋለጠ ቀሚስ በመሆኑ ብቻ «የሚገባ ልብስ» ሊሆን አይችልም::
አንዲት ልጃገረድ ለአቅመ ሔዋን ስትደርስ በሰውነቷ ላይ የሚታየው ለውጥ ለአቅመ አዳም የደረሱ ወንዶችን በኃይል የሚማርክ ይሆናል፡፡ በዚህ ምክንያት ሴቶች በወንዶች በተደጋጋሚ ይፈተናሉ፡፡ አንቺም ወደ ትልቅ ሴትነት ስትቀርቢ ተመሳሳይ የሆነ ፈተና ያጋጥምሻል:: እውነተኛ የልብና የሕሊና ስላም ለማግኘትና ዘለቄታዊ ሰላምሽን የሚያደፈርሱ ችግሮች እንዳይደርሱብሽ የምትፈልጊ ከሆነ ራስሽን መቆጣጠርና ትክክኛ ለሆነው ነገር ጠንካራ አቋም ማሳየት ይጠበቅብሻል፡፡
ከወሊድ ጋር ተዛምዶ ያላቸውን የሰውነትሽን ክፍሎች ለማሳየት ቁምጣና አጣብቂኝ የሆኑ ጉርድ ቀሚሶችን፣ አጭር ቀሚስና ጠባብ ሹራቦችን፣ ስስና ዘርዛራ ልብስ፣ ጠባቃ ሱሪ፣ እየለበስሽ ሆን ብለሽ ትኩረት መሳብ ይገባሻልን? እንዲህ ያደረግሽ እንደሆነ የወጣት ሴቶች ፆር በሆነው የምንዝር ጌጥ ፍቅር (ትውዝፍት) ተይዘሻል ማለት ነው።በዚህ መቀጠልሽ ደግሞ የተቃራኒ ጾታዎችን ፍትወተ ሥጋ የመቀስቀስ ሚና ይጫወታል፡፡ ከዚያስ በኋላ ምን እንደሚከተል ታውቂያለሽ?
በዚህ ዓይነት አድራጎትሽ የተሳቡ ወንዶች የሚያቀርቡልሽን ፈተና ሁሉ ለመቋቋም ምን ያህል ችሎታ አለሽ? ፈተናው እንደ ስኳር በሚጣፍጥ ወይም ሥውር በሆነ ማባበልና ማታለል፣ በውዴታ፣ ገፋ ካለም በግዴታ ሊሆን ይችላል፡፡ ታዲያ ገና በማደግ ላይ ያለሽ ስትሆኚ ይህን ሁሉ እንዴት ችለሽ ታልፊዋለሽ? አካላዊ ዕድገት አሳይተሽ ይሆናል ፡ ነገር ግን ምን ያህል ለጋብቻና እናት ለመሆን የሚያስፈልገው የአእምሮና የስሜት ብስለት አለሽ? በአካል ማደግሽ ብቻ በቂ አይደለም::
ዕድገቱን የጨረሰ ነገር ግን ያልበሰለ አረንጓዴ ሙዝ አይተሽ ታውቂ ይሆናል፡፡ ይህ ሙዝ ከተቆረጠ በኋላ እንኳን ለመበላት ገና መብሰል አደሚያስፈልገው አታውቂምን? አንቺም እንዲሁ በአካል የደረስሽ ቢመስልሽም ይህን ለመሰለ ጾታዊ ግንኙነት ለመጀመር ገና መብሰል እንደሚቀርሽ ራስሽን አሳምኚው:: ብትጣደፊ ግን ጊዜው ሳይደርስ የጽጌሬዳን እንቡጥ ለመክፈት እንደ መሞከር ይሆንብሻል፡፡ ይህም ትርፉ አበባን ማበላሸትና ወደ ፊት ሊገኝ የሚችለውን ውበት መጉዳት ብቻ ነው::
ጋብቻ ማለት ሙሽራ መሆን ብቻ እንዳልሆነም አትዘንጊ የቤት አደራጅ፣ ምግብ አዘጋጅና ልብስ አጣቢ መሆንንም ያካትታል፡፡ እናት መሆንም ልጆችን ተንከባክቦ በማሳደግ ረገድ ከፍተኛ ትዕግሥትና ጽናት የሚጠይቅ ነው።ይህ ሁሉ ደግሞ በጥሩ ጊዜ ብቻ ሳይሆን በክፉ ጊዜም በሕመምና በጤንነት ጊዜ ሁሉ ጭምር ሳይቋረጥ መደረግ የሚያስፈልገው የሕይወት እንቅስቃሴ ነው::
ከዚህ በተጨማሪ ለጋብቻ ዝግጁ እንደሆንሽ ቢሰማሽ እንኳን ልታገቢው የምትፈልጊው ምን ዓይነት ባልን ነው? አንድ ወጣት ወንድ የተማረከው አንዲት ልጃገረድ በጾታ ግንኙነት በኩል ልትሰጠ ው በምትችለው እርካታ ላይ ብቻ በማተኮር ከሆነ ጥሩ ባል የሚሆን ይመስልሻል? ታዲያ ሰውን በአለባበስና በውጫዊ ውበት ለመማረክ ከመሞከር ይልቅ ውስጣዊ ማንነትሽን ተመልክቶ ማለትም በአእምሮሽና በልብሽ ውስጥ ያለውን አይቶ ዘላቂ ወዳጅነት እንዲመሠረት ብትፈልጊ በጣም የተሻለ አይመስልሽምን? ይህን ለማድረግ የምትችዪው ደግሞ ለአለባበስሽ ከመጠን በላይ ከመጨነቅ ይልቅ ሌሎችን የሚስቡ መልካም ጠባዮችን በማፍራት ነው። ማለትም በግልጽና በበሳል አነጋገር፣ ስለ ሕይወት ባለሽ ደስተኛና ጤናማ አመለካከት፣ እንደዚሁም ለታማኝነት፣ ለግብረ ገብነት፣ እግዚአብሔርን ለመፍራትና ለመሳሰሉ መልካም ነገሮች ያለሽን በጎ ፍላጎት በቃልና በሥራ ለማሳየት በመጣር ነው።
ከዚህ አልፈሽ የትዳር ዓላማ ሳይኖርሽ መረን በወጣ የዝሙት ተግባር ለመኖር አስበሽ አለባበስሽን ያበላሽሽ ከሆነ ዘግየት ብሎ ማዘንሽ አይቀርም፡፡ አለባበሳችን ኑሮአችንን ደስተኛ ወይም ኀዘን ያጠላበት ለማድረግ የሚጫወተው ሚና ከፍተኛ ነው።ደስተኛና መልካም ስብእና የሞላበት ኑሮ ለመኖር የሚደረግ ጥረት አለባበስን ቁጥብ ከማድረግ ይጀምራል፡፡ አስተውሎ መልበስ የመልካም ስብእና መገለጫ ሲሆን ስድ አለባበስ የሚፈጥረውን የስሜት መገለባበጥ መሠረት ያደረገ የአኗኗር መንገድን መከተል ከሰውነት ደረጃ ዝቅ ያደርጋል::
ስለዚህ ሆን ብለሽ ጥፋትን ዓላማ ያደረገ አለባበስ ከመልበስ ተጠንቀቂ! በአለባበስሽ አንድን ወንድ ብትማርኪ አንቺም ሆንሽ እርሱ አትደነቁም:: ምክንያቱም እርሱ በእንስሳዊ ጠባይ የሚማረክ ደካማ ሲሆን አንቺም ደግሞ በስሜት ብቻ እንጂ በውስጣዊ ማንነትሽ በአእምሮአቸው በሳል የሆኑ ሰዎችን መማረክ ያቃተሽ ደካማ ነሽና። ጎበዝ ከሆንሽ ከስሜት ይልቅ በበሳል አስተሳሰብና በጨዋነት የሚሳቡትን ሰዎች ለመማረክ ጨዋና ግብረ ገብነት ያለው ሰው ለምን አትሆኚም?
በወጣትነትሽ ለፈጣሪሽ ታማኝ ሁኚ! ለውጫዊና ለጊዜያዊ ደስታ ብለሽ መልካም ጠባያትን ንቀሽ አትጣያቸው:: ውስጣዊውን ንቀሽ ለሥጋዊና ለውጫዊ ነገሮች ተገዝተሽ መኖርሽ ከፈጣሪሽ ጋር በእጅጉ ያራርቅሻል።እርሱ እንዲህ ብሏልና «በውጭ የሆነ ሽልማት አይሁንላችሁ ነገር ግን በእግዚአብሔር ዘንድ ዋጋው እጅግ የከበረ የዋህና ዝግተኛ መንፈስ ያለውን የማይጠፋውን ልብስ ለብሶ የተሠወረ የልብ ሰው ይሁንላችሁ» 1ጴጥ3፥4 ስለዚህ ስለውስጣዊ ማንነትሽ እንጂ ስለውጫዊው ማንነትሽ ብዙም አትጨነቂ፡፡

ቀጣይ ምዕራፍ ዘጠኝ ክፍል ሦስት :
👉በአልባሳት በምታጌጪበት ጊዜ ልታስተውያቸው የሚገቡ ነገሮች በሚል ይቀጥላል....
ለጥያቄና አስተያየት @Ethiopian_Orthodox_bot ተጠቀሙ።

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

ሕይወተ ወራዙት(የወጣቶች ሕይወት)
 ምዕራፍ ዘጠኝ ክፍል ሁለት

.................................................
➺የልብስ ምሳሌነትና ምሥጢር

ልብስ የጸጋና የክብር ምሳሌ ነው። አዳምና ሔዋን ሕግ በጣሱ ጊዜ የእግዚአብሔር ክብር እንደራቃቸው ያወቁት ልብሳቸው በመገፈፉ ነው።ልብስ የክብር ምልክት ነውና፡፡ ዛሬ በቤተ ክርስቲያን የሚገኙ ንዋያተ ቅድሳትንና ምስጢራትን በሙሉ በመንጦላዕት እናከብራቸዋለን፡፡ (በመጋረጃ) እና በአልባሳት በመሸፈን እናከብራቸዋለን።
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ «ሐፍረትን ንቆ» ዕርቃኑን የተሰቀለው ራሱን እስከ መጨረሻው አዋርዶ፣ ተዋርዶ የነበረ አዳምን በልዕልና ስፍራ ማስቀመጡን ለማመልከት ነበር። በልብስ መሸፈን የክብር ምልክት ከሆነ መራቆት ደግሞ የውርደት ምሳሌ መሆኑ ግድ ነውና፡፡ እንዲሁም የእስራኤልን ውርደት ለማመልከት እግዚአብሔር ከነቢያት አንዱን ዕርቃኑን እንዲሄድ ያደረገበት ጊዜ ነበር፡፡
ይልቁንም ለኛ ለኢትዮጵያውያን እግዚአብሔር በጥበቡ ምሥጢር ያለው አለባበስ ያለበሰን መሆኑን «ፍኖተ አእምሮ» በተባለው መጽሐፋቸው እንዲህ ሲሉ ጽፈው ነበር:: « ብዙዎቻችን የአለባበሳችንን ምሥጢር ሳናውቅ ብንለብስም የፈጣሪ ፈቃድ ያለበት ነውና ምሥጢሩን ዐውቀን እናጽናው እንጂ አንለውጠው::»
ምሥጢሩም "የመኳንንትና የወታደር ሱሪና እጀ ጠባብ ሠላጤ ጫፉ እንደ ጦር ራሱ እንደ ልብ ሆኖ መስፋቱ ለጊዜው ሲሮጡ፣ ሲሄዱ፣ ሲቀመጡም ሆነ ሲነሡ የማያስቸግርና ልከኛ እንዲሆን ነው:: ምሳሌው ግን ቅዱ አንደ ጦር መሆኑ ልባችን ለድፍረት ሰውነታችን ለስለት የተመረጠ የጦር ሰዎች ነን ለማለት ነበር፡፡"

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

አለ ክቡር ዳዊት። ስለዚህም ሁሉ ነገር አቤቱ ማራቸው ይቅርም በላቸው መፃተኛዋ ባሪያህንም ኃጢአቷን አታስብባት እያለች ወደፈጣሪዋ መሪር ዕንባን አለቀሰች። ያን ጊዜ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ በታላቅ ግርማ ወደስዋ መጣ። በታላቅ ግርማ ሆኖ ባየችውም ጊዜ ደነገፀች ከእግሩ ሥርም ወደቀች። ከዚህ በኋላ ነውር በሌለባቸው ንዑዳት ክቡራንና ንጹሐን በሆነ እጆቹ አነሣት። ቀጥሎም "ወዳጄ ክርስቶስ ሠምራ አትደንግጭ ነገር ግን የልብሽን ሃሳብ ንገሪኝ" አላት። እስዋም "አቤቱ ባሪያህንስ በባለሟልነት ካሠለጠንካት አባታችን አዳምን በአርአያህና በአምሣልህ ስለምን ፈጠርከርው። በእንጨት መስቀልስ ላይ ለምን ተሰቀልክ ስለአዳምና ስለልጆቹ አይደለምን?" አለችው። "አዋን ስለነሱ ስል ተሰቅያለሁ" አላት። "እግዲያውስ መሰቀልህ ወይም የተሰቀልከው ስለነሱ ከሆነ ከአቤል ጀምሮ እስከ ዛሬ የሞቱን ከዛሬም በኋላ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ የሚሞቱትን አቤቱ ማራቸው ይቅርም በላቸው" አለችው። "አንተ ቸር ይቅር ባይ መዓትህ የራቀ ምሕረትህ የበዛ ነህና ከአንተ ሌላ አምላክ የሌለ እውነተኛ አምላክ ነህ ሁሉ ይቻልሃልና የሚሣንህ ነገር ከቶ የለምና ዓለም በጠቅላላዋ በእፍኝህ አትሞላም" በማለት እያለቀሰች ለመነችው። በዚያ ጊዜ ጌታ መልሶ "ወዳጄ ክርስቶስ ሠምራ ሆይ እስኪ አንቺ ራስሽ ፍረጅ አዳም ከነልጆቹ ከሠራው ኃጢአት እና እኔ በጰንጤናዊው በጲላጦስ ዘመን በቀያፋና በሐና አደባባይ በዕለተ ዓርብ ከተቀበልኩት ሕማማተ መስቀል ቢመዘን የትኛው ይመዝን ይመስልሻል?" አላት። ይህንም ባላት ጊዜ ደነገጠችና ከመሬት ላይ ወደቀች። በዚህ ጊዜ ቅዱሳት በሆኑ እጆቹ ከወደቀችበት አነሣትና "እንግዲህ ይህን ሁሉ መከራ የተቀበልኩ ለማን ወይም በማን ምክንያት ይመስልሻል" አላት።

ጌታም "ወዳጄ ክርስቶስ ሠምራ ሆይ እስኪ የልብሽን ሃሳብ ወይም ፍላጐትሽን ንገሪኝ" አላት። በዚህን ጊዜ "አቤቱ ፈጣሪየ ፈቃድህስ ቢሆን የአዳም ልጆች ከሥቃይ ከኵነኔ ይድኑ ዘንድ ዲያብሎስን ይቅር ትለው ወይም ትምረው ዘንድ እለምንሃለሁ። የኃጥእን መመለሱን እንጂ ጥፋቱን አትወድምና" አለችው። "የምለምንህ ወይም ማረው የምልህ ዲያብሎስን ወድጄው አይደለም ነገር ግን እርሱ ከተማረ በአዳም ልጆች ላይ ሥቃይና ኵነኔ ሊኖር አይችልም ብየ በመገመት እንጂ። የነሱ ሥጋ ሥጋየ እንደሆመኑ መጠን የኔም ሥጋ ሥጋህ ነውና" አለችው። ይህንም ባለችው ጊዜ ጌታ ፍግግ ብሎ "ወዳጄ ክርስቶስ ሠምራ ሆይ ሌሎች ካንቺ በፊት የነበሩ ካንቺም በኋላ የሚነሱ የማያስቡትን እጅግ የሚያስደንቅ ልመና አቀረብሽ" አላት። ይህንም ካለ በኋላ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ጠርቶ "ወዳጄ ክርስቶስ ሠምራ ዲያብሎስን ማርልኝ ስትል ልመና አቅርባለችና እሺ ካላት ታወጣው በንድ ወደሲዖል ይዘሃት ሂድ" ብሎ አዘዘው። በዚህ ጊዜ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል እሺ ብሎ ሰግዶ እጅ ነሥቶ ወደሲዖል ይዞአት ሄደ። አብረው በሚጓዙበትም ጊዜ "እንግዲህ ዲያብሎስ ከታረቀ ወይም ከተማረ የሰው ልጆች ሁሉ ያርፋሉ" እያለች ለመላእክት አለቃ ለቅዱስ ሚካኤል ታሳስበው ነበር። ይህን አምላክነትን ሲሻ ከክብሩ የተዋረደ ዲያብሎስ ምሕረት ለማግኘት ይሻ መስሏት ነበርና።

ከሲዖል አፋፍ በደረሱም ጊዜ የተመለከተችው ሥቃይ ተነግሮ የማያልቅ ነው ሰዎች ከሰዎች ጋር እንደውሻ ይናከሱ ነበር። የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል "ምሕረት የሚፈልግ ከሆነ እስኪ በይ ዲያብሎስ ብለሽ ጥሪው" አላት። በዚህ ጊዜ በመላእክት ቋንቋ ሦስት ጊዜ "ሣጥናኤል ሣጥናኤል ሣጥናኤል" በማለት ጠራችው። ዲያብሎስም "ከዚህ በብዙ ሠራዊት ላይ ነግሼ ከምኖርበት አገር ማን ነው እሱ የሚጠራኝ" እያለ በታላቅ ቃል አሰምቶ ተናገረ። ከዚህም በኋላ "ለብዙ ዘመን ስፈልግሽ ወይም ሳድንሽ ቆይቼ ነበር ዛሬ ግን ከምኖርበት ቤቴ ድረስ መጣሽን" አላት። እርሷም "ጌታ ይቅርታ አድርጓልሃልና ከዚህ ከሥቃይና ከመከራ ቦታ ከወገኖችህ ጋራ ና ፈጥነህ ውጣ" አለችው። ይህንም በለችው ጊዜ ልቡ እንደ እሳት ነደደ አፈፍ ብሎ ተረማምዶ በግራ እጁዋን ይዞ ከሲዖል ረግረግ ውስጥ ወረወራት። በዚያን ጊዜ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል የእሳት ሰይፍ ይዞ ከኋላ ከኋላዋ ይከተላት ነበርና ይህን ምሕረት የሌለው ዕቡይ ዲያብሎስ በያዘው ሰይፍ ቢቀጣው የሲዖል ደጃፍ ተከፈተች። በዚህ ሰዓት ታላቅ ጨኸትና ውካታ ወይም መደበላለቅ ሆነ በሲዖል ያሉ የሰዎች ነፍሳት እንደንብ ከበቧት ወይም ሠፈሩባት። በዚያን ጊዜ በቅዱስ ሚካኤል ክንፍና በስዋም በተሰጣት ክንፈ ረድኤት ከሲዖል የወጡት ነፍሳት ቁጥር ዓሥር ሺህ ያህል ነበር። እነዚህ ከመከራ ያመለጡ ከሥቃይ የወጡ ነፍሳትን ባየች ጊዜ እጅግ አድርጋ ተደሰተች ከደስታዋም ብዛት የተነሣ የእናቱን ጡት እየጠባ እንደሚዘል እምቦሳ ጥጃ በመካከላቸው ትዘል ነበር።

ከዚህም በኋላ ወደ ፈጣሪዋ ሄዳ "አቤቱ ፍርድህ ከቶ እንደዚህ ነውን?" እያለች አደነቀች። ጌታም "ወዳጄ ክርስቶስ ሠምራ ሆይ ዲያብሎስን ድል አድርገሽ ጥቂት ምርኮን አገኘሽን" አላት። እስዋም  "አዋ ጌታዬ በኃይልህና በቸርነትህ አገኘሁ" አለችው። ከዚህ በኋላ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱስ ሚካኤል ጠርቶ "እሊህን ነፍሳት ዓለም ሳይፈጠር ወደ አዘጋጀሁላት ወደ ክርስቶስ ሠምራ መኖሪያ ቦታ ውሰዳቸው" አለው። በዚህ ጊዜ "አቤቱ ፈጣሪየ የእኔ መኖሪያየ ወዴት ነው?" አለችው። ጌታም "መኖሪያሽ ከእናቴ ከድንግል ማርያም ጋራ ነው እነሆ በትረ ማርያም ብየ ሰየምኩሽ መቀመጫሽን ወይም ደረጃሽን ከእርስዋ ቀጥሎ ሁለተኛ አደረግሁልሽ የባለሟልነት ግርማ አጐናጸፍኩሽ አንቺን የሚወዱ ሁሉ የተመሰገኑ ናቸው" አላት። ይህንም ባላት ጊዜ ፈጽማ ደስ ተሰኘች ወደ ኋላዋም መለስ ብላ ብትመለከት ለዓይን የሚያንፀባርቁ ዓሥር አክሊላት አየች። በየአንዳንዳቸው አክሉል ላይ ዐራት ከዋክብት አሉ ባቸው የእሊህ ከዋክብት ቊጥራቸው ሲደመር አርባ ይሆናል። በዚህ ጊዜ ከስዋ ጋራ የነበረውን መልአክ "እሊህ በላያቸው ብርሃናውያን ከዋክብት ያሉባቸው አክሊላት ለማን የተዘጋጁ ናቸው ሰውነቴ እጅግ አድርጋ ወዳቸዋለችና" አለችው። የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤልም "ላንቺ ቢሆን ደስ አይልሽምን?" አላት። እርስዋም "አዎን ጌታየ ለኔ ቢሆን እወዳለሁ" አለችው። "እንግዲያስ ላንቺ የተዘጋጁ ናቸው" አላት። "በምን ሥራዬ ለኔ ተሰጡኝ" አለችው። "ዐሠርቱ ቃላት ኦሪትን ስድስቱን ቃላተ ወንጌል ጠብቀሽ ቤትሽን ጥለሽ ይህን ዓለም ንቀሽ አጥቅተሽ የክርስቶስን ቀምበር ተሸክመሽ ፈጣሪሽን ስለተከተልሽው ነው" አላት። ይህንንም በአላት ጊዜ እጅግ አድርጋ ተደሰተች ሁሉን ማድረግ የሚችል እግዚአብሔርንም ፈጽማ አመሰገነች።
ምንጭ፦ ገድለ ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ

የቅድስት እናታችን ረድኤት በረከቷ ይደርብን፣ በጸሎቷ ይማረን!

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

ለተክለ ሃይማኖት ጻድቅ

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

Читать полностью…
Subscribe to a channel