በዚህ Channel ውስጥ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንን ዶግማ ፤ ቀኖና እና ትውፊት የጠበቁ ትምህርቶች ይተላለፉበታል፡፡ ለአስተያየት: ጥቆማና ጥያቄ በዚህ ያግኙን ☞ @Ethiopian_Orthodox_bot Buy ads: https://telega.io/c/Ethiopian_Orthodox
የካቲት ፲፮
ኪዳነ ምሕረት
የካቲት ዐሥራ ስድስት በዚችም ዕለት የክርስቲያን ወገኖች ሁሉም አምላክን ለወለደች ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በዓልን ያደርጋሉ። በዚች ዕለት መታሰቢያዋን ለሚያደርግ ስሟን ለሚጠራ ለድኆችና ለችግረኞች እስከ ቀዝቃዛ ውኃ ለሚሰጥ የክብር ባለቤት ከሆነ ከተወደደ ልጅዋ ከጌታችንና ከመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የምሕረት ቃል ኪዳንን ተቀብላለችና።
ይህችም የከበረች እመቤታችን ልጅዋ ንጹሕ ሥጋዋን ተዋሕዶ ከብቻዋ ኃጢአት በቀር የሰውነትን ሥራ ፈጽሞ ስለእኛ መዳን ወዶ ያደረገውን መከራ ተቀብሎ ሙቶ ተነሥቶ ከዐረገና በአባቱ ዕሪና ከተቀመጠ በኋላ እርሷን እናቱን ማርያምን በደቀ መዝሙሩ ዮሐንስ ዘንድ ትቷት ነበር እነሆ ልጅሽ እርሱንም እነሆዋት እናትህ ብሎ አደራ እንዳስጠበቀው።
ከዚያንም ጊዜ ጀምራ እመቤታችን ማርያም ትጸልይ ዘንድ ያለ ማቋረጥ ወደ ልጅዋ መቃብር ሁል ጊዜ ስትሔድ ኖረች ይኸውም ጎልጎታ ነው።
አይሁድም በአዩዋት ጊዜ ቍጣንና ቅናትን ተመልተው በድንጊያ ሊወግሩዋት ወደዱ እግዚአብሔርም ከዓይናቸው ሠወራት ከዚህም በኋላ ዳግመኛ መጥታ በዚያ እንዳትጸልይ ተማክረው ከመቃብሩ ዘንድ ጠባቂዎችን አኖሩ እርሷ ግን በየዕለቱ መሔድን አላቋረጠችም ጠባቆችም አያይዋትም የልጅዋ የጌትነቱ መጋረጃ ሠውርዋታልና መላእክትም መጥተው ያገለግሏታል ጌታችንም ዘወትር ይጐበኛታል የምትሻውንም ይፈጽምላት ነበር።
ከዚህም በኋላ መላእክት ወደ ሰማይ አሳረጓትና የጻድቃንን ማደሪያዎች አሳዩዋት አብርሃም ይስሐቅ ያዕቆብም ወዳሉበት አደረሱዋት ከአዳም ጀምሮ እስከዚያ ዕለት በአካለ ነፍስ ያሉ አባቶች ሁሉ አንቺን ከሥጋችን ሥጋን ከዐፅማችን ዐፅምን ለፈጠረልን ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን የአምላክ ልጅ ከአንቺ ሰው በመሆኑ በአንቺ ድህነት አግኝተናል ከጥፋትም የሕይወት ወደብ ሆነሽልናልና እያሉ ሰገዱላት።
ከዚያም ወደ ተወደደ ልጅዋ የእሳት መጋረጃ ወደተተከለበት ወደ ጌትነቱ ዙፉን አደረሷት ጌታችንም እጇን ይዞ ወደ ውስጠኛው መጋረጃ አስገብቶ ከጌትነቱ ዙፋን ላይ አውጥቶ ከእርሱ ጋር አስቀመጣት ያዘጋጀላትንም ዐይን ያላየው ጆሮ ያልሰማው በሰው ልቡና ያልታሰበ ተድላ ደስታን ሁሉ ነገራት።
ከጌትነቱ ዙፋንም በታች የእስራኤል ንጉሥ አባቷ ዳዊትን የነቢያትና የመላእክት ኅበር እንደ ግድግዳ ከበውት በመሰንቆ ሲያመሰግን አየችው እንዲህም ይላል "ልጄ ስሚ በጆሮሽም አድምጪ ወገንሽን የአባትሽንም ወገን እርሺ ንጉሥ ደም ግባትሽን ወዷልና እርሱም ጌታሽ ነውና።"
ዳግመኛም የሥቃይን ቦታ ያሳዩዋት ዘንድ መላእክት ከዚያ ውሰዷት ለሰይጣንና ለሠራዊቱ በእርሱ ጐዳና ለሚጓዙ ሁሉ ወደተዘጋጀ ወደጨለማው ዳርቻ አደረሷት እመቤታችን ማርያምም ወዮልኝ ወደዚያ እንዳይመጡ ለሰው ልጆች ማን በነገራቸው አለች መልአኩም አመቤቴ ቡርክት ማርያም ሆይ እግዚአብሔር ከአንቺ ጋር ይኖራልና ለአንቺም ከአንቺ በኋላም በቃል ኪዳንሽ ለሚታመኑ አትፍሪ አላት ከዚህም በኋላ ወደ ቦታዋ መለሷት።
ከዚያንም ጊዜ ጀምራ እመቤታችን ድንግል ማርያም ስለ ኃጥአን እጅግ እያዘነች ኖረች እንደ ዛሬይቱም የካቲት ዐሥራ ስድስት ቀን በጎልጎታ ቦታ ቁማ ወደ ልጇ እንዲህ ብላ ለመነች ልጄ ሆይ በእግዚአብሔር አባትህ በክርስቶስ ስምህ ከአንተ ጋርም ህልው በሆነ አጽናኝ መንፈስ ቅዱስ አማፅንሃለሁ ዓለም ሁሉ ሊሸከምህ የማይችል ሲሆን ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን በተሸከመችህ ማሕፀኔ አማፅንሃለሁ ልጄ ሆይ ያለ ሕማም ያለ ድካም ከእኔ በመውጣትህ በመወለድህ በአሳደጉህ ጡቶቼ በሳሙህ ከንፈሮቼ በአቀፉህ እጆቼ ከአንተ ጋር በተመላለሱ እግሮቼ አማፅንሃለሁ ። በውስጡ በተኛህበት በረት በተጠቀለልክበት ጨርቅ አማፅንሃለሁ የምወድህ ልጄ ሆይ በልቡናዬ ያለውን ሁሉ ትፈጽም ዘንድ የልመናዬን ቃል ሰምተህ ወደእኔ ትመጣ ዘንድ ወዳንተ ፈጽሜ እማልድሃለሁ።
የብርሃን እናቱ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም እንዲህ ብላ በጸለየች ጊዜ እነሆ ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወረደ ከእርሱም ጋር አእላፍት መላእክት አሉ በዙሪያውም ሁነው ያመሰግኑታል እርሱም እናቴ ማርያም ሆይ ምን ላድርግልሽ አላት እመቤታችንም ለተወዳጅ ልጅዋ እንዲህ ብላ መለሰችለት ልጄ ወዳጄ ሆይ ጌታዬና ፈጣሪዬ አለኝታዬና መጠጊያዬ በእናቴ ማሕፀንም ሳለሁ ባንተ ጸናሁ አንተም ጠበቅኸኝ ሁልጊዜም ስም አጠራሬ አንተ ነህ።
አሁንም ጸሎቴንና ልመናዬን ስማኝ ቃሌንም አድምጥ እኔ እናትህ እኔም አገልጋይህ የምለምንህ ይህ ነው መታሰቢያዬን ለሚያደርጉ በስሜ አቢያተ ክርስቲያን ለሚሠሩ ወይም የተራቆተውን ለሚያለብሱ የተራበውን ለሚያጠግቡ የተጠማውንም ለሚያጠጡ የታመመውን ለሚጐበኙ ያዘነውን ለሚያረጋጉ የተከዘውንም ደስ ለሚያሰኙ ወይም ምስጋናዬን ለሚጽፉ ልጆቹንም በስሜ ለሚሰይም በበዓሌም ቀን በማኅሌት ለሚያመሰግን አቤቱ ዐይን ያላየውን ጆሮ ያልሰማውን በሰውም ልቡና ያልታሰበውን በጎ ዋጋ ስጣቸው በአማላጅነቴም የሚታመነውን ሁሉ ከሲኦል ነጻ አድርገው ከአንተ ጋር የደረሰብኝን ረኃቡንና ጥማቱን መከራውን ሁሉ አስብ አለችው።
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም እንዳልሽው ይሁንልሽ የሰጠሁሽም ቃል ኪዳን እንዳይታበል በራሴ ማልኩልሽ አላት።
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእመቤታችን ድንግል ማርያም በጸሎቷ ይማረን በረከቷም ከእኛ ጋር ይኑር ለዘላለሙ አሜን።
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
ከላይ የተጠቀሰው ቃል በገዛ ፈቃድ በንጽሕና መኖርን የሚያመለክት እንጂ አካልን ስለ መቁረጥ የተነገረ አይደለም፡፡ አካል ቢኖርም ሥራውን ካልሠሩበት የሌለ ያህል ነውና ‹ጃንደረባ› በማለት የተናገረው ስለዚህ ነው:: ንዑስ መሌሊትን (ኀፍረተ አካልን) መቁረጥ ግን ከመንግሥተ ሰማያት ያወጣል፤ ከክህነትም ያሽራል፡፡
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ መላ ዘመንን በድንግልና መኖር የፈቃድ ኑሮ መሆኑን ለማመልከት «ስለ ደናግልም የጌታ ትእዛዝ የለኝም» ይበል እንጂ መልካም ምክርና ለጽናት ምላሌ የሚሆን ድንግልናዊ ኑሮ ግን አለው፡፡ ስለዚህ «ሰው ሁሉ እንደ እኔ ሊሆን እወዳለሁ» በማለት ተናግሯል። 1ቆሮ7፥7
ሐዋርያው ከሕይወቱ ምሳሌነት በተጨማሪ ምክሮቹ በመሉ በድንግልና መኖርን የሚያበረታቱ ነበሩ «…ከጌታ ምሕረትን የተቀበልኩ እንደ መሆኔ ምክር እመክራለሁ» ካለ በኋላ «እንግዲህ ስለ አሁኑ ችግር ይህ መልካም ይመስለኛል ሰው እንዲህ ሆኖ ቢኖር መልካም ነው› በማለት በዘመኑ ካለው ችግር የተነሣ በድንግልና መኖር መልካም መሆኑን አስረድቷል፡፡ 1ቆሮ7፥25-26
ሐዋርያው «ስለ አሁኑ ችግር» በማለት የተናገረው ቃል ሊሠመርበት የሚገባ ነው፡፡ ሐዋርያው በነበረበት ዘመን ድንግልናዊ ኑሮን ከመንፈሳዊ ጠቀሜታው ባሻገር ክጋብቻ ኑሮ ይልቅ የተሻለ የሚያደጉት ብዙ ነገሮች ነበሩ፡፡ ይህ እኛ ያለንበት ዘመን ደግሞ ከዚያን ጊዜ ይልቅ ድንግልናዊ ኑሮን የተሻለ የሚያደርጉት ችግሮች በመጠንም ሆነ በዓይነት የበረከቱበት ወቅት ነው:: ስለዚህ ምንም እንኳን መላ ዘመንን በድንግልና መኖር አስቸጋሪ መስሎ ቢታይም እስከ ጋብቻ ድረስ እንኳን ድንግልናን ጠብቆ መቆየት ከድንግልናዊ ኑሮ ጥቅሞች እንድንጋራ የሚያደርግ ነው::
«ድንግል በክልኤ»
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም «ድንግል በክልኤ» እየተባለ በቅዱሳት መጻሕፍት ተነግሮላታል፡፡ ስለ ድንግልናዋ ትንቢት ተነግሯል ምሳሌም ተመስሏል:: ይህም በሁለት ወገን ማለትም በሥጋና በነፍስ ድንግል መሆኗን ለማመልከት ነው:: የደናግልም ሁሉ መመኪያቸው እርሷ ናት፡፡
እመቤታችን ቅድመ ፀኒስ፣ ጊዜ ፀኒስ፣ ድኅረ ፀኒስ ድንግል ናት:: ቅድመ ወሊድ፣ ጊዜ ወሊድ፣ ድኅረ ወሊድም ድንግል ናት፡፡ ቅዱሳንን ሁሉ ስለ ድንግልኗ ምስጋናና ክብር ያለ ማቋረጥ እንዲናገሩ ያደረገ ይህ ንጽሕናዋ ነው፡፡ ‹‹ስብሐተ ድንግልናኪ ወትረ ይነግር አፉየ› እንዲል:: (መልክዐ ማርያም)
የእመቤታችንን ድንግልና «ድንግልና» በመባሉ ብቻ ካልሆነ በቀር የፍጡራን ድንግልና በምንም አይመሳሰለውም፡፡ ስለ እመቤታችን ድንግልና ለመናገር ሌላ ትልቅ ጥራዝ ያለው መጽሐፍ መጻፍ ያስፈልጋል:: ስለድንግልና ለመናገር ስንፈልግ ስለ እርስዋ ከተጻፉት መንፈሳዊ ድርሰቶች አስረጅ አድርገን ብዙ ብንጠቅስም በድንግልና ፍጽምት ከመሆኗ የተነሣ የፍጡራንን ድንግልና ሕጹጽነት ለማየት እንዲረዳን ነው እንጂ ለማመሳሰል አይደለም፡፡
የእመቤታችንን ድንግልና የመላእክትም ንጽሕና አይደርስበትም፡፡ ለዚህም ማስረጃው የተአምረ ማርያም መቅድም እንዲህ ሲል ያሰፈረው ቃል ነው:: «ለመኑ ተውህቦ ተደንግሎ እለ እምውሉደ ሰብእ፣ ለመላእክትኒ ኢተክህሎሙ ተደንግሎ ሕሊና እስመ አበሱ በፍትወት ወወረዱ ምድረ በመዋዕል ዘቀዳሚ» በአማርኛ «ሥጋዊ ምኞትን የማሸነፍ ዕድል ለማን ተሰጠው? ኃጢአትን ከማሰብ መጠበቅ ለመላእክት እንኳን አልተቻላቸውም፤ በቀደመው ዘመን ያልተሰጣቸውን ሽተው በፈጸሙት በደል ከሰማይ ወደ ምድር ወርደዋልና።» (መቅድመ ተአምረ ማርያም)
ደናግላንና አለባበሳቸው!
ለዐቅመ ሔዋን የደረሱና ያልደረሱ፣ ደናግላን የሆኑና ያልሆኑ ሴቶች ተለይተው የሚታወቁበት የፀጉር አሠራር፣ አለጫጨትና የአለባበስ ሁኔታ በየሀገሩ ይገኛል:: በድሮ ጊዜ ደናግለ እስራኤል ለፍሬ -እልደረስንም ሲሉ ወርቅ እንደ አበባ የፈነዳበት ነጭ ሐር ለብሰው ይታዩ ነበር።
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ስለ አለባበስ በሚገባ ካስተማረ በኋላ ትምህርቱ ደናግልንን ብቻ የሚመለከት ለመሰላቸው ሰዎች ‹ወአኮ ዘእቤ በእንተ ደናግል ባሕቲቶን› ማለትም «ይህን ያልኩት ስለ ደናግል ብቻ አይደለም» በማለት ደናግላን ብቻ ሳይሆኑ ሁሉም ሴቶች በሚገባ መንገድ ብቻ ማጌጥ እንዳለባቸው ይገልጻል:: ተግ.ዮሐ28
አለባበስ በዝሙት ለመውደቅ የሚዳርግበት ሁኔታ ሰፊ ስለሆነ በይበለጥ ደናግል አለባበሳቸው ተገቢ መሆን አለበት፡፡ ደናግላን የተለየ አለባበስ እንደ ነበራቸው መጽሐፍ ቅዱስም ይመሰክራል፡፡ ትዕማር ድንግል በነበረችበት ጊዜ ‹‹ብዙ ኅብር ያለውን ልብስ ለብሳ ነበር እንዲህ ያለውን ልብስ የንገሡ ልጆች ደናግሉ ይለብሱት ነበርና።» ነገር ግን በተደፈረችና ክብሯን ባጣች ጊዜ «ብዙ ኅብር ያለውን ልብስዋን ተርትሪ› እየጮኸች ሄደች:: 2ሳሙ13÷18-19
ድንጋሌ ሥጋ አንድ ጊዜ ጠፋ በኋላ ሊመለስ ይችላል?
በግዘፍ ያለ ድንጋሌ ሥጋ አንድ ብቻ ነው፡፡ ይህ ድንጋሌ ሥጋ. በሩካቤም ሆነ ያለ ሩካቤም የሚጠፋበት ጊዜ አለ፡፡ ድንጋሌ ሥጋን የሚያጠፋው ሩካቤ በመንፈሳዊው ሕግ የተደገፈ ሕጋዊ ሩካቤ ወይም ሕገ ወጥ ሩካቤ ሊሆን ይችላል:: በአጠቃላይ ድንጋሌ ሥጋ በልዩ ልዩ መንገድ ሊማስን ይችላል:: አንድ ጊዜ ጨርሶ የጠፋ ዓይን እግዚአብሔር ከሃሊነቱን ለማሳየት ሲፈቅድ ብቻ ካልሆነ በቀር ለበራ እንደማይችል ድንጋሌ ሥጋም አንድ ጊዜ ከተገሠሠ እንዲሁ ነውና አይመለስም፡፡ ድንጋሌ ሥጋ ዓይን መባሉን ከዚህ በላይ ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ‹ከመ ብንተ ዓይን» ያለውን በመጥቀስ ተመልክተናል፡፡
ከላይ እንደ ተገለጸው በንስሐ ተመልሶ የሚገኘው የነፍስ ድንግልና እንጂ የሥጋ ድንግልና አይደለም፡፡ መጽሐፈ መነኮሳት «ንስሐሰ ትሬስዮ ለዘአበሰ ከመ ዘኢአበሰ ለዘማዊ ድንግለ›› ፡ «ንስሐ ግን የበደለን እንዳልበደለ ዘማዊን እንደ ድንግል ታድርገዋለች::> በማለት የተናገረው ስለ ነፍስ ድንግልና እንጂ ስለ ድንጋለ ሥጋ አይደለም፡፡ አንድ ሰው ድንጋሌ ሥጋውን አንድ ጊዜ ካጣ በኋላ እንደ ገና በንስሐ ያገኘዋል ለማለትም አይደለም:: በተጨማሪም «እንደ ድንግል» ታደርገዋለች ይላል እንጂ ቁርጥ በሆነ ቃል «ድንግል ታደርገዋለች» አለማለቱን ልብ ማለት ያስፈልጋል:: ስለዚህ ስለ ድንጋሌ ሥጋ በመጀመሪያ መጠንቀቅ እንጂ ከሄደ በኋላ «ድንግል ብሆንስ?›› ማለት አጉል ተስፋ ነው፡፡ እንዲህ ሲባል ግን የእግዚአሔርን ከሃሊነት መጠራጠር ሳይሆን ያለ አግባብ ተስፋ ማድረ ግን ለመንቀፍ መሆኑን መረዳት ያስፈልጋል፡፡
የንጽሕና መርከባችን እንዳይሰበር መጠንቀቅ ያሻል:: «ብርሌ ከነቃ አይሆንም ዕቃ» እንደ ተባለው ድንጋሌ ሥጋም አንድ ጊዜ ከተወሰደ እንደ ተሰበረ የሸክላ ዕቃና እንደ ሞተ ሰው ነው:: እነዚህ ተመልሰው ይረባሉ፣ ይጠቅማሉ እንደማይባሉ ድንጋሌ ሥጋም እንዲሁ ነውና ይመለሳል አይባልም:: መዝ30፥12
የኃጢአት መጥፎነቷ ይታወቅ ዘንድ ኃጢአት ከሠራን በኋላ ቢያንስ በአንድ ነገር እንቀጣለን:: ወይም አንድ ነገር እናጣለን፡፡ ዝሙት ምክንያት ድንጋሌ ሥጋ አንዴ ከተወገደ በኋላ የማይመለስበትም አንዱ ምክንያት ይህ ነው:: ንጉሥ ዳዊት ባመነዘረ ጊዜ ምንም እንኳን ንስሐ ቢገባ በዝሙት የጸነሰው ልጁ ሊፈወስለት አለመቻሉ ኃጢአት ቢያንስ በአንድ ጐዳና ሳትጐዳ እንደ ማትቀር ያመለከታል:: 2ሳሙ12፥13-14
አንዳንድ ነገሮች አንድ ጊዜ ካመለጡ በኋላ በንስሐ እንኳን መልሶ ማግኘት የማይቻልበት ሁኔታ መኖሩን ማወቅ ያስፈልጋል:: ለምሳሌ:- ዔሳው ብኩርናውን ባቃለላት ጊዜ ከሱ ወደ ታናሽ ወንድሙ ወደ ያዕቆብ ተዛውራለች:: በኋላ ግን ምንም ክልብ ቢፈልጋት መልሶ ለማግኘት አለመቻሉን ቅዱስ ጳውሎስ ሲገለጽ እንዲህ ብሏል<ሴሰኛ ም የሚሆን እንዳይገኝ፥ ወይም ስለ አንድ መብል በኩርነቱን እንደሸጠ እንደ ዔሳው ለዚህ ዓለም የሚመች ስው እንዳይሆን ተጠንቀቁ:: ከዚያ በኋላ እንኳን በረከቱን ሊወርስ በወደደ ጊዜ እንደተጣለ ታወቃላችሁና፣ በእንባ ምንም ተግቶ ቢፈልገው ለንስሐ ስፍራ አላገኘምና> ዕብ12÷16-17 ድንግልናም አንድ ጊዜ ከተወገደ እንደ ፈሰስ ውኃ ነው።
የኃጢአት ቁስል በንስሐ መድኃኒት መፈወስ ቢችልም ትራት (ጠባሳ) ሳይተው ግን አይቀርም:: ስለዚህ እድናለሁ ብሎ በእሳት መጠበስ እንደማይገባ ንስሐ አለ ብሎም መበደል አይገባም፡፡ ኃጢአት የሚጥለው ጠባሳ ባይኖር ኖሮ ምንም ያልበደለና በድሎ በንስሐ የተመለሰ ሰው ልዩነት ባልኖራቸውም ነበር። በዝሙት የተሰነካከለ ሰው በንስሐ አማካይነት ምንም ካልተሰነካከለው ሰው ጋር በድንጋሌ ነፍስ መተካከል ቢችልም በድንጋሌ ሥጋ መበለጡ አይቀርም፡፡ ተሰብሮ በተጠገነና ምንም ባልተሰበረ ሰው መኻል ያለው ልዩነት ይህ ነውና፡፡
በንስሐ ከተመለስኩ ወዲህ እግዚአብሔር ድንጋሌ ሥጋዬን ቢመልስልኝ ምን አለበት? ማለት ተገቢ ሐሳብ አይደለም፡፡ በመጀመሪያ እግዚአብሔርን መፈታተን ነው፡፡ በሁለተኛ ደረጃ ለዚያ ነገር ሳይበቁ በጎን ነገር ከመመኘት አልፎ ይገባኛል ማለት የትዕቢት ሐሳብ ነው፡፡ ሌላው ይህን ሐሳብ የተለየ የሚያደርገው ደግሞ መጀመሪያ የተሰጠንን ከጣልን በኋላ መመኘታችን ነው፡፡ ራስ አጥፊ ረስ ተቆጭ መሆን አይሆንም? እንደ ሥራዬ ድንጋሌ ሥጋን ብቻ ሳይሆን ሌላም ማጣት ይገባኝ ነበር የሚል ሰው በእግዚአብሔር ዘንድ እንዴት የተወደደ ነው? በአንጻሩ ደግሞ «የኔ ውድቀት እንሌላው ሰው አልነበረም!» በማለት
ሕይወተ ወራዙት(የወጣቶች ሕይወት)
ምዕራፍ ስምንት
...............................................
ድንግልና ምንድር ነው?
ድንግል የሚለው ቃል «ተደንገለ፤ ተጠበቀ» ከሚለው የግእዝ ግሥ የተገኘ ሲሆን ትርጉሙ «መጠበቅ» ማለት ነው፡፡ እንደ አገባቡም ፍቺው ሊለያይ ይችላል፡፡ ለምሳሌ:- ድንግል የሚለውን ቃል ለዕቃ የሰጠን እንደ ሆነ ገና ከማምረቻ የወጣ፣ ምንም ያልተሠራበት፣ ያላደፈ ያልጎደፈ፣ ያላረጀ ያላፈጀ፣ ያልተቀላቀለ ማለት ይሆናል፡፡ ድንግል መሬት ሲባል ደግሞ ለምነቱ እንደ ተጠበቀ ያለ፣ ለእርሻ ያልዋለ ወይም ያልታረሰ፣ ያልተቆፈረ፣ ዘር ያላረፈበት እንደ ተፈጠረ ያለ መሬት ማለት ነው፡፡
ድንግል የሚለው ቃል ለሰው ሲነገር ደግሞ ወንድ የማታውቅ (ከወንድ ጋር ሩከቤ ፈጽማ የማታወቅ)፣ ጥብቅ፣ ልጃገረድ ሴት ወይም ሴትን በምንጣፍ ተገናኝቶ የማያውቅ ወንድ ማለት ይሆናል፡፡ በተጨማሪም የተፈጥሮ ንጽሕናቸውን የጠበቁ ንጽሐ ጠባይ ያላደፈባቸው ወንድና ሴት ማለት ነው:: ዘፍ24፥16፣ ራእይ14፥4
ብዙ ጊዜ ይህ ቃል ሲፈታና በዐረፍተ ነገርም ሲገባ የምንመለከተው የመጨረሻውን አስተያየት በመያዝ ወንዶችና ሴቶች የሰው ልጆችን ወክሎ ነው፡፡ ስለዚህ ከላይ በተሰጠው ትንታኔ መሠረት ድንግልና ንዑስ ሕዋስን ወይም አካልን ብቻ ሳይሆን አንድ ድርጊት መፈጸም አለመፈጸሙን የሚያመለክት ቃል ይሆናል ማለት ነው፡፡
በተጨማሪም ይህ ቃል ለመንግሥታት፣ ለሕዝብ፣ ለሀገር፣ ለምእመናን ምሳሌ በመሆን በመጽሐፍ ቅዱስ ብዙ ጊዜ ተጠቅሷል፡፡ ኢሳ 23÷12 ፣37÷22፣47÷1፣አሞ 5÷2፣ኤር 18÷13፣2ኛ ቆሮ 11÷2
ድንግልናና ማኅተመ ድንግልና
በሰው ልጆች ዘንድ ሩካቤ ካለ ዘር መቀበል፣ ማቀበልና ሰስሎተ ድንግልና (የድንግልና መወገድ) መኖሩ የታወቀ ነው:: ሆኖም ይኽ ስለ ታወቀ ብቻ ሩካቤ ከተፈጸመ ማኅተመ ድንግልና አይኖርም ድንጋሌ ሥጋ ካለ ደግሞ ሩካቤ አልተፈጸመም በማለት ድምዳሜ ላይ መድረስ አይቻልም፡፡ ምክንያቱም ብዙ ጊዜ ሩካቤ አድርገው ድንጋሌ ሥጋቸው ያልተወገደ እንደውም ማኅተመ ድንግልናቸው ሳይገሠሥ እስከ መፅነስ የደረሱ ብዙ ሴቶች ስላሉ ለዚህ ምስክር ናቸው። ከዚህም በተጨማሪ ተፈጥሮአዊ ጽንዐ ድንግልናቸው በሩካቤ ብቻ ሊገሠሥ የማይቻል እየሆነ በቀዶ ጥገና ሕክምና ማኅተመ ድንግልናቸው እንዲወገድ የሚደረግላቸው ብዙ ሴቶች አሉ፡፡
ይህ ከሆነ ድንግል የሚለው ቃል ብቻውን የአንዲት ሴትን ትክክለኛ ድንግልነት ላይገልጽ ይችላል ማለት ነው፡፡ የሚገልጽ ቢሆን ኖሮ ያለ ምንም ተጨማሪ ቃላት ለእመቤታችን በተነገረ ነበር፡፡ ነገር ግን ስለ እመቤታችን አምላክን መፅነስና መውለድ ሲነገር በድንግልና ፀንሳ ወለደችው ከማለት በተጨማሪ «ያለ ሩካቤ፣ ያለ ዘር፣ ያለ ሰስሎተ ድንግልና›› ፀንሳ ወለደችው ማለት በብዙ መጻሕፍት የተለመደ አገላለጽ ነው፡፡ ለምሳሌ፡- «ወይእቲ ንጽሕት እምነ ሠለስቱ ግብራት ዘውእቶሙ ዘርዕ፣ ወሩካቤ፣ ወስስሎተ ድንግልና እለ ሥሩዓን በዕጓለ እመ ሕያው ወእሙራን ቦሙ» - «እርሷም በሰው ልጆች ዘንድ ከታወቁት ከሦስቱ ግብራት የተጠበቀች ናት እነርሱም ሩካቤ ዘር መቀበልና፣ የድንግልና መወገድ ናቸው፡፡» ይላል፡፡ (ትርጓሜ ውዳሴ ማርያም) ስለዚህ ሩካቤና ሰስሎተ ድንግልና የተለያዩና ራሳቸውን የቻሉ ተግባራት ተደርገው መታየት አለባቸው። አንዲትን ሴት ማኅተመ ድንግልና ስላላት ብቻ «ሩካቤ አድርጋ አታውቅም» ወይም ሩካቤ ስላደረገች «ማኅተመ ድንግልና ሊኖራት አይችልም» ብሎ ድምዳሜ ላይ መድረስ አለመቻሉን እንረዳለን፡፡ እመቤታችን ግን «ድንግል» የሚለው ቃል ከሚገልጸው በላይ «ፍጽምት» መሆኗን ተያይዘው በተጠቀሱት ተጨማሪ ቃላት እንረዳለን፡፡ ድንግል ማርያም በሕሊናዋም በሥጋዋም ፍጹም ድንግል የሆነች «ምክሐ ደናግል>> ናት፡፡
ማኅተመ ድንግልና በሩካቤ ሥጋ ጊዜ የሚጠፋ እንደ መሆኑ መጠን በቀጥታ በሥጋ ድንግል ከመሆንና ካለመሆን ጋር መዛመዱ ግልጽ ቢሆንም አንዳንድ ጊዜ ግን ከላይ ከተጠቀሰው በተጨማሪ ማኅተመ ድንግልናን «ከድንግልነት» ጋር ለይተን ለመመልከት የምንገደድበት ሁናቴ ይኖራል፡፡
ለምሳሌ ወንዶች እንደ ሴቶች ተጨባጭና ጉልህ የድንግልና ምልክት ስለሌላቸው ከሴት ጋር ሩካቤ ፈጽመው የማያውቁ ሆነው ሳለ ደናግል አይደሉም ለማለት አይቻልም:: እንደዚሁም ሁሉ ሩካቤን ፈጽመው የማያውቁ ሴቶች ሲወለዱ ጀምሮ ማኅተመ ድንግልና የሌላቸው ሊሆኑ ይችላሉ:: ወይም ከጊዜ በኋላ በክባድ የአካል እንቅስቃሴ፣ በአደጋ፣ በሕክምና ወይም በዕድሜ ብዛት ምክንያት ማኀተመ ድንግልና ሊፈርስባቸው ይችላል:: እንዲህ ያሉ ሴቶች ማኅተመ ድንግልናቸውን ቢያጡም ሩካቤ ፈጽመው እስካላወቁ ድረስ ደናግል መባላቸው የተጠበቀ ነው:: ምክንያቱም ድንግልናና ማኅተመ ድንግልና በእንዲህ ዓይነት ሁኔታ ተለያይተው ስለሚታዩ ነው::
በሌላ አቅጣጫ ስንመለከት ወንዶች ሩካቤ ፈጽመው ሳለ እንደ ሴቶች የሚገሠሥ ማኅተመ ድንግልና ስለሌላቸው ድንግልናቸው አልፈረሰም እንደማይባል ሁሉ ሴቶች ሩካቤ ሥጋ እየፈጸሙ በልዩ ልዩ ምክንያት ማኅተመ ድንግልናቸው ባይገሠሥም መደበኛ ሩካቤ እስከ ፈጸሙ ድረስ ደናግል ሊባሉ አይችሉም:: ለምሳሌ:- የሚያይ የሚመስል ዓይን እያላቸው በመፍዘዙ ምክንያት የማያዩ ሰዎች የዓይን ምልክታቸው (ዓይን የሚባው ሕዋስ ወይም መልክ) ጨርሶ ስላልጠፋ ብቻ ዓይን አላቸው ይባላልን? እንደዚሁም ሁሉ ሩካቤ ፈጽመው ሳለ ማኀተመ ድንግልናቸው ባለመጥፋቱ ብቻ ደናግል ሊባሉ አይቻልም፡፡
አንዲትን ሴት ድንግል የሚያሰኛት ሥራዋና ዝንባሌዋ ብቻ ነው:: ማኅተመ ድንግልናዋ ስላልተወገደ ብቻ ወይም እርሷ ድንግል መሆን ስለምትፈልግ ወይም «ጳጳስ››ም ሆነ «ባሕታዊ» ጸሎት ስለ ደገመላት ድንግል መሆን አትችልም:: ከዚህ በታች የተጠቀሰው ኃይለ ቃል ይህንን ሐሳብ የሚያጎላ ነው፡፡ ‹‹ወኢያንብር ዕደ ላዕለ ድንግል አላ ምሥጢራ ባሕቲታ ትሬስያ ድንግለ›› የዚህ ዐረፍተ ነገር ትርጓሜ ‹‹ድንግል ናት ብሎ በአንብሮተ ዕድ አይሹማት (ድንግልና) ሾሜሻለው አይበላት:: ፈቃዷ ብቻ ድንግል ያደርጋታል እንጂ የሰው ፈቃድ ድንግል አያደርጋትምና፡፡» የሚል ነው፡፡ (ፍትሐ ነገሥት መንፈሳዊ)
የማኅተመ ድንግልና ስያሜዎች
ማኅተመ ድንግልና ሴት ከወንድ ጋር ሩካቤ አድርጋ አለማወቋን የሚያስረዳ የሥራዋ መገለጫ የእኗኗሯ መታወቂያ ልዩ የተፈጥሮ ምልክትና የድንግልናዊ ኑሮዋ ዘውድ ነው:: ይህ መለኮታዊ ማኅተም በሴቶች አፈ ማኅፀን ቀለበት በሚመስል ስስ ሥጋነት በጉልህ ይታወቃል፡፡ ድንግልና ጥቅሙን፣ ምሥጢሩን፤ ምሳሌውን የሚያመለክቱ ልዩ ልዩ ስያሜዎች አሉት:: በተለያዩ ቅዱሳት መጻሕፍት የተጠቀሱት እነዚህ የድንግልና መጠሪያዎች በርካታ ቢሆኑም ሦስት ያህሉ ብቻ ከዚህ በታች ተዘርዝረዋል::
ሀ. ማኅተመ ድንግልና «ክንፈ ድንግልና» ተብሎ ይጠራል፡፡ በዚህ ዓለም ያለ ስጋት ለመንቀሳቀስ የሚያስችል የንጽሕና ክንፍ ነውና፡፡ አረጋዊው ቅዱስ ዮሴፍ «ኦ ወለተ እስራኤል መኑ ቀረጸ አክናፈ ድንግልናኪ› በማለት የተናገረው ቃለ መጠይቅ ከላይ መኅተመ ድንግልና ‹ክንፈ ድንግልና (የድንግልና ክንፍ)» ይባላል በሚል ለተገለጸው ሐሳብ ብቁ ማስረጃ ይሆናል፡፡ ከዚህ ዐረፍተ ነገር እንጻር ለተመለከተው ድንግልናቸውን ያልጠበቁ ሰዎች በሙሉ ክንፍ የሌላትን ወፍ ይመስላሉ::
ለ. «ሕጓን ወሰደው› እንዲሉ ድንግልና ‹‹ሕግ›› ይባላል:: ሕግ የተባለበት ምክንያት «አታመንዝር» የሚለውን የመጽሐፍ ቅዱስ ሕግ መፈጸምና - አለመፈጸምን የሚያስታውቅ የሕግ ምልክት በመሆኑ ነው፡፡
#ምሥጢረ ንስሓ
ንስሓ ሰውና እግዚአብሔር የሚታረቁበት፣ የእግዚአብሔር ምሕረት፣ ይቅርታና ሰላም የሚገኝበት፣ ስርየተ ኃጢአት፣ ጸጋና በረከትን የምናገኝበት ምሥጢር ነው። ከሰባቱ ምሥጢራተ ቤተክርስቲያንም አንዱ ነው። አፈጻጸሙም መናዘዝ በሚችል ሥልጣነ ክህነት ባለው ካህን አማካኝነት ተነሳሒው የበደለውን በደል ተጸጽቶ በመናዘዝ ላጠፋው ጥፋት ተገቢውን ቀኖና የሚቀበልበት ነው። ንስሓ የሰው ልጆች ከአማናዊው ድኅነት ተካፋይ እንዲሆኑ እግዚአብሔር ያዘጋጀልን የጽድቅ በር ነው። ራስን ወቅሶ፣ ስሕተትን አምኖ፣ ዳግም ላለመፈጸም ወስኖ እና ተናዝዞ ወደ እግዚአብሔር መመለስ ነው።
“ንስሓ ካልገባችሁ ሁላችሁ ትጠፋላችሁ” (ሉቃ.13፣3) ተብሎ የተነገረው ንስሓ ከጥፋት ለመዳን ዋናው መንገድ መሆኑን የሚያመለክት ነው። “ንስሓ ግቡ፤ ኃጢአታችሁ ይሰረይላችሁ ዘንድ” (ሐዋ.2፣28) በማለት ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ ያስተማረው የሚያስገነዝበን ይህን ነው። ከኃጢአት ብንናዘዝ ኃጢአታችንን ይቅር ሊለን፣ ከዐመፃችንም ሊያድነን የታመነ ነው” (1ኛዮሐ.1፣8) የተባለው ንስሓ ከአምላካችን የምንታረቅበት በመሆኑ ነው።
በንስሓ ጊዜ መሥዋዕትነትና መንፈሳዊ ትግል ያስፈልጋል። “ከኃጢአት እየተጋደላችሁ ገና ደምን እስከ ማፍሰስ አልተቃወማችሁም (ዕብ.12፣4) እንዲል። ንስሓ እየገቡ ከሰይጣንና ከፈቃደ ሥጋ ጋር ታግሎ ለማሸነፍ መወሰን አማናዊውን ሰላም ያስገኛል። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በአንዳንድ ቦታዎችና በተወሰኑ ግለሰቦች ሲፈጸም የሚታየው ከሥርዓተ ቤተክርስቲያን ተቃራኒ ተግባር ነው። ሰውን የሚያዘናጋ፣ መንፈሳዊ ተጋድሎን ዋጋ የሚያሳጣ ነው። ተነሳሕያን ይህን ተረድተው ሥርዓተ ቤተክርስቲያን የሚያዝዘውን መፈጸም ይኖርባቸዋል። ምክንያቱም ከጸጋ እግዚአብሔር ያርቃልና። ንስሓ ምሥጢር መሆኑንም እንድንዘነጋ ያደርገናልና። ምሥጢረ ንስሓ በአንድ ካህንና በአንድ ተነሳሒ ምእመን አማካኝነት የሚፈጸም ምሥጢር ነው።
በንስሓና በምሥጢረ ንስሓ መካከል መጠነኛ ልዩነት አለ። ንስሓ የምንለው ከመጸጸት ጀምሮ ለካህኑ እስከ መናዘዝ ያለውን ሒደት ነው። ምሥጢረ ንስሓ የምንለው ግን በካህኑ የሚታይ አገልግሎት ቀኖና በመስጠት፣ በመናዘዝ፣ በመምከር፣ ንስሓውን በአግባቡ ሲፈጽም ሥጋ ደሙን እንዲቀበል በማድረግ፣ የመንጻቱ ማረጋገጫ የሚሆነውን ጸሎተ ፍትሐት በማድረስ፣ ማየ ምንዝህ በመርጨት የሚገለጥ ነው። የተነሳሒው ኃጢአት ሲሰረይ በዓይን አይታይም። ምሥጢር ከሚያሰኘው ጉዳይ አንዱም ይህ ነው። ንስሓ ከሚደገሙ ምሥጢራት አንዱ መሆኑም ሰዎች ኃጢአት መሥራት ስለሚደጋግሙ ደጋግመው ንስሓ በመግባት የድኅነት ተካፋይ እንዲሆኑ ነው።
ይህን ታላቅ ምሥጢር አንዳንድ “አጥማቂ ነን ባዮች” በዓመት ሁለት ወይም ሦስት ጊዜ በቀጠሮ ሲያከናውኑ ይታያል። ድርጊቱ ከሥርዓተ ቤተክርስቲያን ውጭ ነው። ለንስሓም ቀጠሮ አይሰጥም።መቼ
እንደምንሞት ስለማናውቅ ተዘጋጅተን መጠበቅ እንጅ ለንስሓ ቀጠሮ ተቀብሎ መቀመጥ አይገባም። ዕለት ዕለት የሠራነውን ኃጢአት ለንስሓ አባታችን በመናዘዝ ንጹሕ ሆነንና ተዘጋጅተን መጠበቅ ይኖርብናል እንጂ። ንስሓ ክህነት በሌለው ሰው ሊፈጸም የማይገባ ድንቅ ምሥጢር ነው። “ለማንም እንዳትናገር ተጠንቀቅ፤ ነገር ግን ራስህን ለካህን አሳይ” (ማቴ.8፣2) ተብሎ የተነገረውም ለዚህ ነው። በዚህ ዓይነት መንገድ ሲፈጸም የኖረውን ምሥጢረ ንስሓ ስመ ክርስትናን በወረቀት ጽፎ በማቃጠል “ኃጢአትህ ተሰረየልህ” እያሉ ማታለል በተነሳሕያኑም፣ በምሥጢሩም መቀለድ ነው። ድኅነትን ገንዘብ ማድረግ ከፈለግን አታላዮች ከሚፈጽሙት ኢ-ክርስቲያናዊ ድርጊት በመጠበቅ ቤተክርስቲያን የሠራችውን ቀኖና መፈጸም ይገባል።
“ኃጢአታቸውን ይቅር ያላችኋቸው ይሰረይላቸዋል፤ ይቅር ያላላችኋቸው ግን አይሰረይላቸውም” (ዮሐ.20፣23 የተባለው የሚፈጸመው በሥርዓት ነው። አስቀድመን እንደተመለከትነው ስርየተ ኃጢአት የሚገኘው ስምን በወረቀት ጽፎ ሰብስቦ በማቃጠል ሳይሆን ሥልጣነ ክህነት ያላቸው አባቶች በሚሰጡት ቀኖና አማካኝነት ነው። ከቤተክርስቲያን አስተምህሮ የተለየ የንስሓ አፈጻጸም የለም። ንስሓ ጸጸት ብቻ ሳይሆን መናዘዝም ያስፈልገዋል። በፈጸመው ኃጢአት ንስሓ ገብቶ ቀኖና አልተቀበለም እንጂ መጸጸትማ ይሁዳም ተጸጽቶ ነበር።
ንስሓ ራሱን የቻለ ጥምቀት አለው። ለዚህ ነው ሥልጣነ ክህነት ባለው አባት እንዲፈጸም ቤተክርስቲያን ሥርዓት የሠራችው። “እኔስ ለንስሓ በውሃ አጠምቃችኋለሁ” (ማቴ. 3፣11) የተባለው ሳይፈጸም የክርስትና ስምን በወረቀት ጽፎ በማቃጠል ስርየት እንደሚገኝ ቤተክርስቲያን ስላላስተማረችን የድርጊቱ ፈጻሚዎችም፣ በዚህ መንገድ ንስሓ ለመግባት የሚፈልጉ ተነሳሕያንም መጠንቀቅ ይኖርባቸዋል።
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
“አካሔድህን አስተካክል”
“ከአፍቃሪያችን ክርስቶስ ያገኘነው ስጦታ እንዲህ ነው ተብሎ በቃላት መግለጥ የሚቻል አይደለም፡፡ እንዴት ያልን እንደሆነ እኛ በኀጢአት እየተንፏቀቅን I'mባለንበት ወራት እርሱ በምሕረቱ ጐብኝቶናልና፡፡ ኀጢአት ሸክም በሆነችብን ጊዜ እርሱ በእኛ ቦታ ተገብቶ ተሸክሞልናልና፡፡ በዚህ የማይለካ ፍቅሩ ከዲያብሎስ አገዛዝ ወደ መንግሥቱ አፈለሰን /ቈላ.1፡14/፡፡ እኛው ራሳችን ርቀን እርሱ ራሱ አቀረበን፡፡ እኛ ራሳችን በድለን እርሱ ካሠልን፡፡ ተወዳጆች ሆይ! ይህን ሁልጊዜ ከልቡናችን አናውጣ፡፡ የተሠጠንን ነጻ ሥጦታ አንዘንጋ፡፡ከምን እንደወጣን አንርሳ፡፡
ሰው ሆይ! የተጠራኸው ወደ ዘለዓለም ሕይወት ነው፡፡ የተጋበዝከው ወደ ልጁ መንግሥት ነው፡፡ ታድያ አንተእዚህ ስለምን ታንጠራራለህ? ስለምን እዚህ ትቀመጣለህ? ስለምን እዚህ
ትንፏቀቃለህ? ስለ ሥጋህ ድሎት ብዙ ዋጋን ትከፍላለህ፡፡ ታድያ ስለ ነፍስህስ ትንሽ አይገድህምን? ወደ ሕይወት ተጠርተህ ሳለ ስለምን ወደ ሞት ትሮጣለህ? ቢያስፈለግ ይህ
ያገኘኸው ስጦታ ላለማቆሸሽ ብዙ መሥዋዕትነትን መክፈል በተገባኽ ነበር፡፡ ብዙ ሰይፍን መታገሥ በተገባህ ነበር፡፡ ወደ እሳት እንኳ ብትጣል ስለ ድኅነተ ነፍስህ መቋቋም ይገባህ ነበር፡፡
ወዳጄ ሆይ! እስኪ ንገረኝ! የመንግሥተ ሰማያት ዜጋ ለመሆን ተጠርተህ ሳለ ራስህን የዚህ ዓለም ዜጋ ማድረግህ ስለምንድነው? እንደምን ያለ ስንፍና እንደያዘህስ ታስተውላለህን? ይህን
ዓለም የመውደደህ ምስጢር ምቾትን መሻትህ ያሳያል፡፡ በዚህ ዓለም በምቾት መኖርን የሚሻሰው ደግሞ ክርስቲያን መሆን፣ ክርስቲያን ተብሎ መጠራት፣ ክርስቶስን መስሎ መመላለስ
ምቾት ሳይሆን እስር ቤት መስሎ ይታየዋል፡፡ ሁላችንም ወደዚሁ ቈጥ ካስገባን ሰነባብተናል፡፡ ከዚህች ዓለም ጋር የተወዳጀ ግን ምንም ክርስቲያን ቢባልም ምንም በአርባና በሰማንያ ቀኑ የሥላሴን ልጅነት ቢያገኝም ክርስቲያን ክርስቲያን መሽተቱ እየጠፋ ይሔዳል፡፡በዚኽ ዓለም ወጥመድ ተቀፍድዶ ይያዛል፡፡
ወዳጄ ሆይ! ይህን አድምጥና ፍርሐትና ረዓድ ይያዝህ!!! ምንም በቤተ መንግሥት
ብትኖርም፣ ምንም በተሽቆጠቆጠ መኖርያ ቤት ብትኖርም እንደተመቸህ አድርገህ
አትንገረኝ፡፡ አንተ የምትኖርበት ኑሮ ለእኔ ወኅኒ ቤት ነው፤ ያውም ሊፈርስ የተቃረበ ቤት!!!
ይኽ ቤትህ ክረምት ሲመጣ ይፈርሳል፡፡ ክረምት (የመጨረሻይቱ ቀን) ስትመጣ ቤትህ ይፈርሳል፡፡ ክረምት ስላልኩህ ደግሞ “ለሁሉም ሰው ክረምት ከሆነበት እኔ ከማን እለያለሁ” ብለህ አታስብ፤ ይህቺ ቀን ለሁሉም ክረምት አትሆንምና፡፡ ዳግመኛም እግዚአብሔር ሌሊትና
ቀን ብሎ ጠርቷታልና፡፡ ሌሊት የምትሆንባቸው ለኀጥአን ነው፤ ቀን የምትሆንላቸው ደግሞ ለጻድቃን ነው፡፡ እኔም ክረምት ብዬ መናገሬ ከዚህ አንጻር ነው፡፡ ሁላችንም ክረምት ሲመጣ
መብረር እንችል ዘንድ በበጋው ላይ ካላደግን የገዛ እናቶቻችን እንኳ ቢሆኑ ትተዉን ይሔዳሉ እንጂ በዚያ ሰዓት እኛን መሸከም (ማዳን) አይቻላቸውም፡፡ የገዛ እናቶቻችን እንኳ በረሃብ እንሞት ዘንድ ትተዉን ይሔዳሉ፡፡ ቈጡ (ቤቱ) በላያችን ላይ ሲፈርስ እኛን መታደግ አይቻላቸውም ፡፡ እግዚአብሔር ቤቱን ሲያፈርሰው፣ አሮጌው እንደ አዲስ ሲያደርገው፣ እያንዳንዱ እንዳልነበረ ሲሆን እኛን መርዳት የሚችል አንድ ስንኳ አይገኝም፡፡ የዚያን ጊዜ ጌታን በአየር ላይ መገናኘት የማይችሉቱ፣ የመንፈስ ክንፍ ተሰጥቶአቸው መብረር የማይችሉቱ ቤቱ በላያቸው ላይ ይፈርስባቸዋል፡፡ ስቃይ የስቃይም ስቃይ ይሆንባቸዋል፡፡ ስቃዩ
የስቃይ ስቃይ ነው ማለቴ ከ እስከ የሚባል ስለሌለው ነው፤ ለዘለዓለም ስቃይ ስለሆነ ነው፡፡ ክረምት ብዬ መጥራቴ ስለዚሁ ነው፤ ኧረ እንደውም ከክረምት የባሰ ነው፡፡ እንዴት ያልከኝ እንደሆነ በዚሁ፡ክረምት ላይ የሚዘንበው ውኃ አይደለምና፤ እሳት እንጂ፡፡ በዚሁ ክረምት ዙርያህ ጨለማ የሚሆነው ከደመና ብዛት የተነሣ አይደለምና፤ ጽኑ ጨለማ እንጂ፡፡ የብርሃን
ጭላንጭል የሌለው ጨለማ እንጂ፡፡ እዚህ የሚገቡት ሰዎች ተድላ መንግሥትን ማየት
አይቻላቸውም፤ ሰማያትን ማየት አይቻላቸውም፡፡ ከመቃብር ውስጥ የባሰ ጨለማ ይውጣቸዋል እንጂ፡፡
ወዳጄ ሆይ! አሁንስ አትርድምን? ወዴት እየሔድክ እንደሆነ አታስተውልምን? ፊትህንስ ወደ ልጁ መንግሥት አታደርግምን?”… አካሔድህን አስተካክል…
(ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ )
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
"ሞትማ ለመዋቲ ይገባል"
ሞትማ ለመዋቲ ይገባል(፪){፪}
የድንግል አሟሟት እጅጉን ይደንቃል{፪}
ለልጇ ስትነግር ሞት እንደምትፈራ{፪}
ወሰዷት በሐሴት መላእክተ ሐራ{፪}
ጭንቀቱ ሳይገጥማት ሳታስብ ድንገት{፪}
እንደ እንቅልፍ ወሰዳት ያ መልአከ ሞት{፪}
አዝ =
ይገርማል ይደንቃል የድንግል ፍልሰታ{፪}
በምስጋና አረገች ከልጇ ተጠርታ
በይባቤ አረገች ከልጇ ተጠርታ
እያሸበሸቡ መላእክተ ሰማይ{፪}
ወስደው አቀረቧት ከልጇ መንበር ላይ{፪}
አዝ =
ሱባኤ እንደገቡ እንደ ሐዋርያት{፪}
እኔም ከቤት ወጣሁ አንቺኑ በመሻት{፪}
ትንሳኤሽን በክብር እንዳሳየሻቸው{፪}
እኔንም ለዚህ አብቂኝ ብርሃንሽን እንዳየው{፪}
©በሊቀ መዘምራን ኪነጥበብ ወ/ቂርቆስ
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
ጥር ፳፩
በዓለ አስተርዕዮ ማርያም
ጥር ሀያ አንድ በዚህች ቀን አምላክን ለወለደች ለእመቤታችን ለከበረች ድንግል ማርያም የእረፍቷ በዓል መታሰቢያ ነው።ያን ጊዜ እመቤታችን በልጇ በጌታችን በፈጣሪያችንና በመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በከበረ መቃብሩ ቦታ ትፀልይ ነበረ ከዚህም ዓለም እንደምትለይ መንፈስ ቅዱስ ነገራት። ከዚህም በኋላ ከደብረ ዘይት ደናግል መጡ ጌታችን ነግሯቸዋልና እርሷም ነገረቻቸው።
በዚያንም ጊዜ እመቤታችን እንዲህ ብላ ፀለየች፦ "ልጄ ወዳጄ ጌታዬና ፈጣሪዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ልመናዬን ተቀብለህ ደቀ መዝሙርህን ዮሐንስን በዚች ሰዓት አምጣው።እንዲሁም ህያዋን እንደሆኑ ሐዋርያትን ሁሉንም ነፍሳቸውንም የለየሀቸውን አምጣቸው አንተ የህያዋንና የሙታን አምላክ ነህና ላንተም ምስጋና ይሁን ለዘለዓለሙ አሜን።"
በዚያንም ጊዜ በመንፈስ ቅዱስ ትእዛዝ ከኤፌሶን አገር ዮሐንስን ደመና ተሸክማ ወደ እመቤታችን ማርያም አደረሰችው ሰገደላትና በፊቷ ቁሞ እንዲህ አላት "ሰላምታ ይገባሻል ጌታችንን ፈጣሪያችንንና መድኃኒታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን የወለድሺው ፀጋን የተመላሽ ደስ ይበልሽ አንቺ ከዚህ ዓለም ተለይተሽ በክብር በምስጋና ወደ ዘለዓለም ህይወት ትሄጃለሽና። ይህም ስሙ ክቡር ምስጉን የሆነ ጌታችንና ፈጣሪያችን ድንቆች ተአምራቶችን በአንቺ ላይ ከገለጠ በኋላ ነው።"
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም ይህን በሰማች ጊዜ እጅግ ደስ አላት እግዚአብሔርንም እንዲህ ብላ አመሰገነችው "ፈጣሪዬ ጌታዬ ላንተ ምስጋና ይሁን አንተ የለመንኩህን ሰጥተኸኛልና አሁንም ነፍሴን ተቀብለው ወደ ሰማይ ወደ አንተ ሊያሳርጓት ከሚመጡ መላእክቶችህ ጋር በመምጣትህ የምለምንህን ሁሉ ስጠኝ።"
በዚያንም ጊዜ ከሰማይ እንዲህ የሚል ቃል መጣ "እነሆ አሁን መላእክት ይደርሳሉ ሐዋርያትም ሁሉ ከምድር ዳርቻ በደመና ተጭነው ለሰማይና ለምድር ጌታ ለኢየሱስ ክርስቶስ እናቱ ወደ ሆነች ወደ ቅድስት ድንግል ይደርሳሉ።"
ወዲያውኑ ሁሉም ሐዋርያት የሞቱትም ከመቃብራቸው ተነስተው ወደ እመቤታችን ደርሰው ሰገዱላት "አምላካችን ከአንቺ የተወለደ ፀጋን የተመላሽ ሆይ ደስ ይበልሽ። እርሱ ከዚህ ዓለም ለይቶ ቃል ኪዳን እንደሰጠሽ በክብር በምስጋና ከርሱ ጋር ያሳርግሻልና" አሏት።
በዚያንም ጊዜ እመቤታችን በአልጋዋ ላይ ተቀመጠች ሐዋርያትንም እንዲህ አለቻቸው "ፈጣሪዬ ፈጣሪያችሁ ኢየሱስ ክርስቶስ እንደሚመጣ እናንተንም እንዳየኋችሁ እንደማየው አሁን አወቅሁ ከዚህ ከስጋዬም ወጥቼ ወደዘለዓለም ህይወት እሄዳለሁ ነገር ግን ትነግሩኝ ዘንድ እሻለሁ ከዚህም ዓለም እንደምለይ ከወዴት አወቃችሁ?"
ጴጥሮስና ሐዋርያት ሁሉም "ወዳንቺ እንመጣ ዘንድ መንፈስ ቅዱስ አዘዘን በደመና ላይም በተጫንን ጊዜ ወዳንቺ እንደ አይን ጥቅሻ ፈጥነን ደረስን።" አሏት።
እመቤታችን ማርያምም ይህን ነገር ከሐዋርያት በሰማች ጊዜ ድምጿን ከፍ አድርጋ እንዲህ አለች "ጌታዬና ፈጣሪዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ክቡር ምስጉን የሆነ ስምህን ፈፅሜ አመሰግናለሁ።የእኔን የአገልጋይህን መከራ ተመልክተህ ድንቅ ኃይልህን አድርገህልኛልና ከእንግዲህ ወዲያ ትውልድ ሁሉ ያከብሩኛል ያመሰግኑኛል።"
ፀሎቷንና ምስጋናዋን ስትጨርስ ሐዋርያትን እንዲህ አለቻቸው "እጣን አምጥታችሁ በማጠን የጌታዬን ኢየሱስ ክርስቶስን ስሙን ጥሩት" እነርሱም እንዳዘዘቻቸው አደረጉ። በዚያንም ጊዜ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እልፍ አእላፍት መላእክት አጅበው እያመሰገኑት መጣና አረጋጋት ያዘጋጀላትንም ተድላ ደስታ ነገራት በዚያንም ብዙዎች ድንቆች ተአምራቶች ተደረጉ እውሮች አይተዋልና፣አንካሶች ቀንተው ሄደዋልና ደንቆሮዎች ሰምተዋልና ለምፃሞች ነፁ አጋንንትም ከሰዎች ወጥተው ሄዱ ዲዳዎች ተናገሩ በሽታና ደዌ ያለበት ሁሉ ዳነ እመቤታችን ድንግል ማርያም ወዳለችበት ቤት በቀረቡ ጊዜ ከደዌያቸው ይፈወሳሉና።
ከዚህም በኋላ እመቤታችን ተወዳጅ ልጇን እንዲህ አለችው "በአየር ውስጥ ተበትነው ከሚኖሩ ከሚያስደነግጡ ግሩማን መላእክት የተነሳ ከእሳት ባህርም እፈራለሁ" ጌታችንም "ከእናንተ ለማንም በአለሁ ላይ ስልጣን የለውም" አላት።
ከስጋዋም የምትለይበት ጊዜ ሲደርስ ሐዋርያትና ደናግል ትባርካቸው ዘንድ እያለቀሱ ለመኗት እጇን በላያቸው ዘርግታ ባረከቻቸው በዚያንም ጊዜ ጌታችን ንፅህት ነፍሷን ከስጋዋ ለይቶ በመለኮታዊ እጆቹ ይዞ በብርሀን ልብስ አጎናፅፎ ወደ ከፍተኛ መኖሪያ ከእርሱ ጋር አሳረጋት ስጋዋን ግን እንደሚገባ ገንዘው ወደ ጌቴሴማኒ ተሸክመው እንዲወስዷት ሐዋርያትን አዘዛቸው።
ነፍሷ ከስጋዋ ከመውጣቷ በፊት በሰው አንደበት ይህ ነው ተብሎ የማይነገር ብርሀንን እያየች ነበር የክብር ባለቤት ጌታችን ክርስቶስም "እንግዲህ ስጋሽን ተድላ ወዳለበት ገነት አፈልሳለሁ። ዳግመኛም ስጋሽን ከነፍስሽ ጋር አዋህጄ አስነስቼ መላእክት በውስጡ በፊትሽ ሆነው በሚያመሰግኑበት ተመሳሳይ በሌለው ተድላ ደስታ በአለበት ማደሪያ አኖርሻለሁ" አላት።
እመቤታችንም እንዲህ አለች "አቤቱ በረቀቀ ጥበብህ ይህን ሁሉ የሰራህ አመሰግንሀለሁ ሁለተኛም ልመናዬን ትሰማ ዘንድ እለምንሀለሁ በስሜ ወደ አንተ የሚለምነውን ሁሉ ልመናውን ተቀበለው በመከራም ውስጥ ሆኖ ስሜን ጠርቶ ወዳንተ የሚለምነውን ከመከራው ሁሉ አድነው በሰማይም በምድርም በስራው ላይ ሁሉ አንተ ከሀሊ ነህና መታሰቢያዬን በውስጧ የሚያደርጉትን ቦታ ሁሉ ባርክ በእኔ ስም የሚያቀርቡትን የሁሉንም መስዋእታቸውን ተቀበል።"
ጌታችንም እንዲህ ብሎ መለሰላት "የለመንሽኝን ሁሉ አደርግልሻለሁ ደስ ይበልሽ ከእኔ ከአባቴ ከመንፈስ ቅዱስ ዘንድ ፀጋ ክብር ባለሟልነት ተሰጥቶሻልና ስምሽንም ጠርቶ የሚለምን ሁሉ በዚህም ዓለም በሚመጣውም አለም አይጠፋም።"
እመቤታችንም ካረፈች በኃላ ጌታችን እንዳዘዘ ወደ ጌቴሴማኒ ሊወስዷት ሀዋርያት ገንዘው ተሸከሟት። አይሁድም በሰሙ ጊዜ ስጋዋን ሊያቃጥሉ ወጡ ከእነርሱም አንዱ ከምድር ላይ ይጥላት ዘንድ የእመቤታችንን አልጋዋን ያዘ ያን ጊዜ ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልአክ እጆቹን በእሳት ሰይፍ ቀጣውና እጆቹ በአልጋዋ ላይ ተንጠለጠሉ።
ያን ጊዜ በጌታችን አምኖ ወደ እመቤታችን እያለቀሰ እንዲህ ብሎ ለመነ "የእውነተኛ አምላክ የጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ እናት አንቺ በእውነት ድንግል የሆንሽ በእኔ ላይ ይቅርታ ታደርጊ ዘንድ እለምንሻለሁ" በሐዋርያትም ልመና እጆቹ ተመልሰው እንደቀድሞው ደኅነኞች ሆኑ።
በቀበሩዋትም ጊዜ ከዚያ ሶስት ቀን ኖሩ እረፍቷም የሆነው እሁድ ቀን በጥር ወር በሀያ አንድ በዚች ቀን ነበረ ጌታችንም ብርሀናውያን መላእክትን ላከ እነርሱም ስጋዋን ከመቃብር ወስደው በገነት ውስጥ በእፀ ህይወት ስር አኖሩዋት።
ሐዋርያ ቶማስ ግን ያን ጊዜ አልነበረም በደመና ላይ ተጭኖ እርሱ ሲመጣ መላእክት ሲያሳርጓት እመቤታችንን አገኛት መላእክትም ለአምላክ እናት ለእመቤታችን ድንግል ማርያም ና እጅ ንሳ አሉት እርሱም ሰገደላትና ተሳለማት ከእርሷም ተባረከ ከዚህም በኃላ ወደ ሐዋርያት ደረሰ ። እነርሱም እመቤታችንን ማርያምን እንደ አረፈችና እንደ ቀበርዋትም ነገሩት ቶማስም ስጋዋን እስከማይ አላምንም አላቸው።
ስለሆነም በተደጋጋሚ እየተፈጸሙባት የሚገኙትን እነዚህን እኩይ ተግባራት ከዚህ በላይ በዝምታና በትዕግስት ማለፍ መንፈሳዊ ተልዕኮዋን በአግባቡ እንዳትወጣ የሚያደርጋት ከመሆኑም በላይ መብቷን በእጅጉ የሚጋፋ፣ጥንታዊያን አባቶች ለሥርዓተ አምልኮ መፈጸሚያ ሲጠቀሙባቸው የነበሩና በትውልድ ቅብብሎሽ አሁን ያለው ትውልድ የተረከባቸው ንዋያተ ቅድሳቶቿን አደጋ ላይ የሚጥል ሁኔታ ከመፈጠሩም በላይ በሥርዓተ አምልኮዋ ላይ በማላገጥ በምዕመናን ዘንድ ቁጣ እንዲቀሰቀስ የሚያደርጉ በርካታ ተግባራት እየተፈጸሙ በመምጣታቸው ምክንያት እነዚህ እኩይና ጸብ አጫሪ ተግባራት ሕጋዊ እልባት እንዲያገኙ ማድረግ የግድ የሚልበት ደረጃ ላይ ደርሳለች።
ስለሆነም ቅድስት ቤተክርስቲያናችን ጉዳዩን በልዩ ሁኔታ ማጥናት፣መከታተልና ሕግን መሰረት ያደረገ መፍትሔ እንዲያገኙ ማድግ አስፈላጊ ሆኖ ስላገኘችው ወቅታዊ ሁኔታውን በዝርዝር በማጥናት ተቋማዊ እልባት የሚያገኝበትን መንገድ የሚያጠና ኮሚቴ ተቋቁሞ ወደ ሥራ እንዲገባ ያደረገች ሲሆን የቤተ ክርስቲያናችን የሕግ አገልግሎት መምሪያም በሕግ አግባብ ተጠያቂነትን በማረጋገጥ ፍትሕ ማግኘት የሚቻልበትን ሁኔታ ለመፍጠር አስፈላጊውን መረጃ በማሰባሰብና በማደራጀት ክስ መመስረት የሚያስችለውን ሁኔታ በማመቻቸት ወደ ተግባር ለመለወጥ በዝግጅት ላይ ይገኛል።
ከዚህ ጎን ለጎንም ከፍ ሲል እንደተገለጸው በጠቅላይ ቤተክህነት ከሚገኙ መምሪያዎች መካከል ጉዳዩ በቀጥታ የሚመለከታቸውን መምሪያዎች በማካተት የተቋቋመው ኮሚቴም ዝርዝር ጥናቶችን በሚገባ በማጥናትና ችግሮቹን ለይቶ ከመፍትሔ ሀሳብ ጋር በአጭር ጊዜ ውስጥ በማቅረብ በቤተክርስቲያኒቱ ማዕከላዊ አስተዳደር አማካኝነት ተቋማዊ አቋም የሚወሰድበትና በቅዱስ ሲኖዶስ ደረጃ የማያዳግም መፍትሔ የሚሰጥበትን ሁኔታ ለማመቻቸት የሚያስችል ሥራ በመሥራት ላይ መሆኑን እየገለጸች በሁለቱም ዘርፎች የተገኙ ውጤቶችን በተመለከተ በተከታታይ ለሕዝበ ክርስቲያኑ እንዲገለጽ የምታደርግ መሆኑን ከወዲሁ እያስታወቀች በጉዳዩ ዙሪያ ሙያዊ ድጋፍ ለመስጠት ፈቃደኛ የሆኑ ምዕመናንና ምዕመናት በተቋቋመው ኮሚቴ አማካኝነት የሚደረግላቸውን ጥሪ ተቀብለው ለቤተክርስቲያናችን መብት መከበር የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ እናት ቤተክርስቲያን ጥሪዋን ታቀርባለች።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን
መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት
አዲስአበባ -ኢትዮጵያ
ጥር ፲፯ቀን ፳፻ ፲ወ፯ ዓ.ም
@Ethiopian_Orthodox
"ቂርቆስ አንጌቤናይ"
ቂርቆስ ሕጻን አንጌቤናይ (፪)
አንጌቤናይ ወልደ አንጌቤናይት(፪)
ገና በሦስት ዓመት ወንጌልን ሰብከኻል
ስለ ጌታ ፍቅር ቆመህ መስክረሃል
እኔ ክርስቲያን ነኝ ብለህ ስትናገር
ቅድቲቷ እናትህ ተደስታ ነበር
አዝ= = = = =
ስለ ክርስትና መከራ ቢያበዙ
ጦርና ጋሻውን ሰይፍንም ቢመዙ
በእምነትህ ጸናህ ያለመደራደር
ከንጉሥ ፊት ስትቆም አስረውህ የፊጥኝ
አዝ= = = = =
ነበልባለ እሳትን በአንተ ላይ ቢያነዱ
ውኃው የሚያጓራ እንደ ነጎድጓዱ
ቅድስቲቷ እናትህ ኢየሉጣም ፈርታ
ጸለይክላት ቂርቆስ ልቧ እንዲበረታ
አዝ= = = = =
እኔ ቅርንጫፍ ነኝ እናትህን ብትላት
ስለ እናትህ ብለህ ጽናትን አድላት
ብለህ በለመንከው በጸለይከው ጸሎት
ዳግም እናትህን በእምነት ወለድካት
አዝ= = = = =
ከእሳት ነጎድጓድ ድምጹ ከሚያስፈራው
ከሚንተከተከው ፍል ውኃ ከሆነው
ከእናትህ ጋራ ብትገቡ ከእሳቱ
ገብርኤል ሲመጣ ሁሉም ሆነ ከንቱ
አዝ= = = = =
መዳንህን አይቶ ንጉሡ አፈረ
ፍጹም በመናደድ ልብሱን ተረተረ
ወታደሩን ጠርቶ አንገትህን ሰየፈው
ከቅዱሳን ሕብረት ነፍስህን ደመረው
©በመካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤ/ክ ውሉደ ብርሃን ሰ/ት/ቤት መዘምራን
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
ዳግመኛም ከጥዋት እስከ ማታ ከሥቃይ መሣሪያዎች ውስጥ ጨምረው አዋሏቸው ግን ማሠቃየት ተሳናቸው። ከዚህም በኋላ ከማምጠቂያው ውስጥ ጨምረው መገዙአቸውና አመድ እስከሆኑ ከቅባትና ከጨው ጋር በብረት ምጣድ ውስጥ ቆሉአቸው ጌታችንም ከሞት አስነሥቶ አዳናቸው።
ወደ መኰንኑም በገቡ ጊዜ እንዲህ አላቸው በእውነት ከሙታን ተለይታችሁ የተነሣችሁ ከሆነ ይህ ጫማዬ ከእግሬ ወጥቶ እንደ ቀድሞው ሕያው እንዲሆን አድርጉ ሕፃን ቂርቆስም በጸለየ ጊዜ ያ ጫማ ታለቅ በሬ ሆነ ከአንገቱም ፍየል ወጣ።
በዚያንም ሰዓት ለዐሥራ አንድ ሽህ አራት ሰዎች በሬውንና ፍየሉን አርደው ምሳ እንዲያደርጉላቸው መኰንኑ አዘዘ እንዲህም አለ ይህ በቅቷቸው ከጠገቡ ከዚህም ሌላ ምግብ ካልፈለጉ የተሠራው ሁሉ ዕውነተኛ ነዋሪ ነው። ከዚህም በኋላ አርደው ምሳ አደረጉላቸውና ከፍየሉ ሥጋ ስድስት እንቅብ ከበሬው ሥጋ አራት እንቅብ አተረፉ መኰንኑም የተረፈውን ሥጋ አይቶ ወደ ባሕር እንዲጥሉት አዘዘ።
መኰንኑም ቢያፍር የሕፃኑን ምላስ ይቆርጡ ዘንድ አዘዘ ጌታችንም ምላሱን መለሰለት ዳግመኛም በታላቅ ጋን ውኃ እፍልተው ሕፃን ቂርቆስንና እናቱን ኢየሉጣን ይጨምሩአቸው ዘንድ አዘዘ እናቱም አይታ ፈረች። ልጅዋም ወደ እግዚአብሔር በጸለየላት ጊዜ አምላካዊ ኃይልን አሳደረባትና ከልጅዋ ጋር ወደ ጋኑ ገባች። እንደ ውርጭም ቀዝቀዛ ሆነ ደግሞም በውስጡ መንኰራኲር ወዳለበት የብረት ምጣድ እንዲጨምሩአቸውና ሥጋቸው እሰከሚቦጫጨቅ እንዲስቡአቸው አዘዘ የእግዚአብሔርም መልአክ በሕይወት አወጣቸው።
መኰንኑም እነርሱን ማሸነፍ በተሳነው ጌዜ ቸብቸቧቸውን በሰይፍ ይቆርጡ ዘንድ አዘዘ በዚያን ጊዜ ለስም አጠራሩ ስግደት የሚገባው የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወረደ ሕፃን ቂርቆስንም የምትሻውን ለምነኝ አለው።
ሕፃኑም ሥጋዬ በምድር አይቀበር ስሜን ለሚጠራ መታሰቢያዬን ለሚያደርግ ቤተ ክርስቲያኔን ለሚሠራ የተጋድሎዬን መጽሐፍ ለሚጽፍና ለሚያጽፍ ወይም ለሚያነበው ለቤተ ክርስቲያኔ መባ ለሚያገባ በውስጧም ለሚጸልይ ለሁሉም ፍላጎታቸውን ስጣቸው ኃጢአታቸውንም ይቅር በል ስሜም በሚጠራበት በዚያች ቦታ የከብት ዕልቂት አይምጣ በሰውም ላይ እባር ቸነፈር በእህልም ላይ ድርቅ የውኃም ማነስ አይሁን።
መድኃኒታችንም የለመንከኝን ሁሉ እሰጥሃለሁ አንተም በቀኜ ትኖራለህ ሥጋህንም ኤልያስ በዐረገበት ሠረገላ ውስጥ አኖራለሁ አለው ሕፃን ቂርቆስም በሰማ ጊዜ እጅግ ደስ ብሎት ጌታችንን አመሰገነው። ከዚህም በኋላ በሌሊቱ እኩሌታም ከእናቱ ጋር አንገቱን ተቆረጠ መድኃኒታችንም በማይጠፋ አክሊል ጋረደው ነፍሶቻቸውንም በታላቅ ክብር ከእርሱ ጋር አሳደገ።
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
"አቡነ አረጋዊ"
ጽድቅህ ጠርቶናል አባትነትህ
በቅድስና ያማረ ሕይወትህ
ጌጥ ውበታችን አባ አረጋዊ
መናኝ መነኩሴ መልአክ ምድራዊ (፪)
ተቃኝተህ ስላደግክ በመንፈስ ቅዱስ
ወደ ፅርዕ ተጓዝክ ወደ አባ ጳኩሚስ
ተዘጋጅተህ ነበር ለችግር ፈተና
ዘሚካኤል አለህ ሰጥቶህ ምንኩስና (፪)
ለኢትዮጵያ ምእመናን አባት ተብለሃል
ወንጌል በማስተማር ብዙ አትርፈሃል
መጻሕፍት ተርጉመህ ያበረከትክ ለአበው
የአንተስ ትሩፋት እፁብ ነው ድንቅ ነው (፪)
የዓለም ጨው ሆነህ አጣፈጥካት ምድርን
በልባችን ሳልካት ቤተ ክርስቲያንን
ደብረ ሀሌ ሉያ ደብረ ዳሞ ቅድስት
የፈውስ ቦታ ናት መካነ ትኅርምት (፪)
ልክ እንደ አባቶችህ አስተዋይ ስለሆንክ
ገና ወጣት ሳለህ አረጋዊ ተባልክ
የሥጋን ሞት ሳታይ ተሰውረህ ከምድር
ብሔረ ሕያዋን ተቀላቀልክ በክብር (፪)
©በቦሌ ደብረ ገነት ቅ/ጊዮርጊስ እና ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ በፍሬ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት መዘምራን
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
ጥር ፲፬
ጻድቁ አቡነ አረጋዊ (ዘሚካኤል)
ጥር አሥራ አራት በዚህች ቀን ታላቁና የከበረው አባታችን አቡነ አረጋዊ (ዘሚካኤል) የተወለዱበት እና ወደ ደብረ ዳሞ የወጡበት ነው።
እኚህ አባት ከ9 ቅዱሳን አባቶች አንዱ ሲሆኑ አባታቸው ይስሐቅ የሮም ንጉስ ነበሩ፡፡ እናታቸው ንግስት እደና ይባሉ ነበር፡፡ የመጀመሪያ ስማቸው ዘሚካኤል ነው፡፡ ጥበብ መንፈሳ ሲማሩ አድገው ወደ እስክንድርያ ገዳም ገቡ፡፡ አበምኔቱ አባ ጳኩሚስ በፈቃደ እግዚአብሔር የመጡ መሆናቸውን አውቀው መዓረገ ምንኩስና ሰጥተዋቸዋል፡፡
የንጉሳዊ የቅንጦት ኑሮ ንቀው ትተው ገዳም ገብተው በምንኩስና ተወስነዋል፡፡ አባታችን በተጋድሏቸውም ከአባ እንጦንስ፣ ከአባ ጳውሊ እና ከአባ መቃርስ ቀጥሎ በአራተኛ ማዕረግ አበ መነኮሳት ሆነው ተመርጠዋል።
በገዳመ ዳውናስ 7 ዓመት ከቆዩ በኋላ ወደ ሮም ተመልሰው ሲያስተምሩ የሀገራችን ኢትዮጵያን ዜና ሰምተው ለመምጣት በ480 ዓ.ም ከአባ ፍሬምናጦስ በኋላ መንገድ ጀመሩ፡፡ ቅዱስ ሚካኤልም በክንፉ ተሸክሞ አክሱም አድርሷቸዋል፡፡
ተመልሰውም ሄደው ስለ ቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ መስክረዋል፡፡ ሐዋርያ ሳይላክላት በሃይማኖት በምግባር ጸንታ ትኖራለች ብለው ለሰባቱ ዘመዶቻቸው አበው መነኮሳት ነገሯቸው፡፡ ስምንቱም ጓዛቸውን ጠቅልለው በሮም ነግሶ የነበሩ ይስሐቅን (አባ ገሪማን) ጨምረው ንጉስ አልአሜዳ በነገሰ በአምስተኛ ዓመት ማለትም በ480 ዓ.ም ወደ ኢትዮጵያ ዘጠኝ ሆነው መጥተዋል፡፡
አባ አረጋዊ እናታቸው ቅድስት እድናን ደቀ መዝሙራቸውን ማትያስን አስከትለው እግረ መንገዳቸውን እያስተማሩና ድውያንን እየፈወሱ ደብረ ዳሞ ደረሰዋል፡፡
ከእግረ ደብር ሆነው አሁን ይህን ተራራ በምን ልወጣው እችላለሁ እያሉ ሲያወጡ ሲያወርዱ በንግግሩ ሐሰት የሌለበት አምላካችን በነቢዩ ዳዊት ላይ አድሮ በመዝሙር 90/91፥11-16 ላይ “በመንገድህ ሁሉ ይጠብቁህ ዘንድ መላእክቱን ስለ አንተ ያዝዛቸዋልና፤ እግርህም በድንጋይ እንዳትሰናከል በእጆቻቸው ያነሡሃል። በተኵላና በእባብ ላይ ትጫማለህ፤ አንበሳውንና ዘንዶውን ትረግጣለህ። እንዳለው የታዘዘ ዘንዶ መጥቶ ስደሳ ክንድ በሚያህል ጅራቱ ጠምጥሞ ቅዱስ ሚካኤል ሰይፈ እሳት ይዞ እየጠበቃቸው ከተራራው አናት አድርሷቸዋል፡፡
ወዲያው ሃሌ ሉያ ለአብ ሃሌ ሉያ ለወልድ ሃሌ ሉያ ለመንፈስ ቅዱስ ብለው አመስግነዋል፡፡ ቦታውም ደብረ ሃሌ ሉያ ተብሏል፡፡ በዚያ ዕለት ግማሽ ህብስት በልተው ጠገቡ፤ ከዚያ በኋላ ግን ምድራዊ ሕብስት አልተመገቡም፡፡ በሰንበተ ክርስታያን ከቅዳሴ በኋላ ሕብስተ ሰማያዊ እያመጡላቸው ይመገቡ ነበር እንጂ፡፡ ኋላም ዜና ጽድቃቸውን ሰምተው ከስድስት ሺህ ያላነሱ ደቀ መዛሙርት ተሰብስበውላቸዋል፡፡
ዘጠና ዘጠኝ አመት ሲሞላቸው ጌታ በመንፈቀ ሌሊት ተገልጾ ምድራዊ መንግስትህን ትተህ ስላገለገልከኝ ህልፈት ሽረት የሌለባት ሰማያዊ መንግስቴን አወርሰሃለሁ ብሎ ቃልኪዳን ሰጣቸው፡፡ በስምህ የተማጸነውን እስከ አስራ አምስት ትውልድ ድረስ እምርልሃለሁ አንተም ከሞት ገጽ ትሰወራለህ ብሎ ተስፋቸውን ነገራቸው፡፡ እሳቸው መነኮሳቱን ሰብስበው ከእንግዲህ በሥጋ አታዩኝም ብለው ነግረዋቸው አበምኔት ሾመውላቸው በደብረ ዳሞ ተራራ በስተምስራቅ አቅጣጫ ተሰውረዋል፡፡
የጻድቁ አባታችን ረድኤት በረከታቸው እንዲሁም አማላጅነታቸው አይለየን!
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
በቀጣይ ምዕራፍ ስምንት ክፍል ሁለት:
<<
👉እስከ ጋብቻ ጊዜ ድረስ መደንገል
👉በድንግልና መኖር የማይቻል ነገር ነው?
👉መታጨት፣ ማጨትና ማግባት በድንግልና ሊደረጉ ይገባል!
👉ከጋብቻ በፊት ድንግልናን መጣል የበለጠ <<ሴሰኛ>> ያደርጋል!
👉ድንግልናና ስርዓተ ተክሊል
👉<<ድንግል>> ልባል እችላለሁን?
>>
ለአስተያየትና ጥያቄዎቻችሁ @Ethiopian_Orthodox_bot ተጠቀሙ።
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
ሰበብ አስባብ እያበዛ በራሱ ተነሣሽነት ዝሙት እንዳልፈጸሙ በመናገር ድንግል መሆን እንደ ነበረባቸው ወይም እንደ ሆኑ እንደሚናገሩ ሰዎች እግዚአብሔር የሚያፍርባቸው ስዎች የሉም።
ለሌሎች ሰዎች ያልተደረገ ገቢረ ተአምር እንዲደረግልን ማለት በራሳችን ስሕተት ያጠፋነውን ድንጋሌ ሥጋ እንዲመለስልን የምንሻ እኛ ከእነሱ የተለየ በጎ ሥራ ምን ሠርተን ነው? ይህ ሐሳብ በእውነት የትዕቢት ሐሳብ ነው በዚህ መልኩ በትዕቢት ማሰብ እንደማይገባ ደግሞ «እንደ ባለ አእምሮ እንዲያስብ እንጂ ማሰብ ከሚገባው አልፎ በትዕቢት እንዳያስብ በመካከላችሁ ላለው ለእያንዳንዱ በተሰጠኝ ፀጋ እናገራለሁ::» ሮሜ12፥3 በማለት ሐዋርያው ምክር ለግሷል፡፡
መደንገል እስከ መቼ?
ድንግልናን ስለመጠበቅ ሲነሣ ብዙ ጥያቄዎች በሕሊና መውጣትና መውረዳቸው አይቀርም፡፡ ከእነሱም ውስጥ አንዱ እስከ መቼ? የሚል ነው:: የዚህ ጥያቄ መልስ እንደ ሰዉ የአኗኗር ዘይቤ ይለያያል:፡ ለአንዱ ጋብቻውን እስኪፈጽም ድረስ ሲሆን ለሌላው ደግሞ ለዘለዓለም ይሆናል፡፡ ይህም ማለት ለሚመነኩሱ ሰዎች እስከ ዕድሜያቸው ፍጻሜ ድረስ ማለት ነው::
እስከ ዕድሜ ልክ መደንገል
ድንግልናቸውን እስከ ሞት ድረስ መጠበቅ የሚኖርባቸው በድንግልና የመነኮሱ መነኮሳት ናቸው:: ምንኩስና ከሴት ርቆ እስክ ሕይወት ፍጻሜ ለመኖር የሚደረግ ውሳኔ ነውና፡፡በእርግጥ ምንኩስና ድንግሌ ሥጋ ያላቸው ሰዎች ብቻ የሚጓዙበት ጐዳና አይደለም:: ባለ ትዳር የነበሩ ወይም ሳያገበ ለዝሙት ተጋልጠው ድንጋሌ ሥጋቸውን ያጡ ብዙ ሰዎችም በንስሐ ተመልሰው ይኖሩበታል:: ይህም ቢሆን እንደ ቀላል የሚታይ ውሳኔ አይደለም:: ነገር ግን ምንኩስና የዓለምን ኑሮ እንደ ልብ ኖረውት ሲስለች ብቻ የሚገባበት አድርጐ ማሰብ ስሕተት ነው፡፡
ምንኩስና በድንግልና ሲሆን ብዙ ጸጋና ክብር ያመጣል፡፡ በቤተ ክርስቲያን ከመመንኮስ በተጨማሪ የግድ ድንግል ሆኖ መገኘትን የሚጠይቁ ብዙ ታላላቅ መንፈሳዊ የሹመት ደረጃዎችና የአኗኗር ዘይቤዎች ይገኛሉ፡፡
በድንግልና መመንኮስ ጣዕመ ዓለምን ሳይቀምሱ በመሆኑ ከምንኩስናም በኋላ ለሚኖሩት የንጽሕና ኑሮ አጋዥነት ይኖረዋል፡፡ ምክንያቱም ከመነኮሱበት ዓላማ ጋር የማይስማማ በልቡናቸው የሚቀር የዓለማዊ ኑሮ አሻራ ባለመኖሩ ነው:: «ያላዩት አገር አያናፍቅም» ይባል የለ?
በእርግጥ ይህን የመሰለ የምናኔ ኑሮ ለመኖር ስጦታ ያስፈልጋል፡፡ «ነገር ግን ለእያንዳንዱ ከእግዚአብሔር ዘንድ ስጦታ አለው፥ አንዱ እንደዚህ ሁለተኛውም እንደዚያ› በማለት ቅዱስ ጳውሎስ እንደተናገረው መመንኮስ የተሰጠው ይኖራል፡ ማግባትም የተሰጠው ይኖራል:: 1ቆሮ7÷27
ምንም እንኳን በጋብቻም ሆነ በምንኩስና መኖር ሁለቱም የእግዚአብሔር ስጦታዎች ቢሆኑም በጋብቻ መኖር ለሁሉ የተሰጠ ሲሆን ምንኩስና ግን መመረጥና መታደል የሚጠይቅ ነው:: ይህን በተመለከተ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ «ይህ ነገር ለተሰጣቸው እንጂ ለሁሉ አይደለም....ሊቀበለው የሚችል ይቀበለው::» በማለት ተናግሯል:: ማቴ19፥11
«ለአባታችን ለቅዱስ ጴጥሮስ የመንግሥተ ሰማያት መክፈቻ፣ ለዮሐንስ ደግሞ ድንግልና፥ ለአባታችን ለጳውሎስም የቤተ ክርስቲያን ብርሃኗ እርሱ ነውና መልእክታትን አብዝቶ መጻፍ ተሰጠው› በማለት ሥርዓተ ቅዳሴ በስም ለተጠቀሱት ሐዋርያት የመንግሥተ ሰማያት መክፈቻ! በድንግልና መኖርና መልእክታትን መጻፍ ለእያንዳንዳቸው እንደ ተሰጣቸው ይገልጻል:: ከዚህም በድንግልና መኖር ለጥቂቶች የሚሰጥ ጸጋ መሆኑን መረዳት ይቻላል፡፡
ሰው ሁሉ በተሰጠው ጸጋ መኖር ይገባዋል፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውለስ በድንግልና መኖር (ምንኩስና) የተሰጠው በድንግልና ጋብቻም የተሰጠው በትዳሩ ጸንቶ እንዲኖር «ወንድሞች ሆይ እያንዳንዱ በተጠራበት እንደዚህ ሆኖ በእግዚአብሔር ዘንድ ይኑር፡፡» በማለት መክሯል:: 1ቆሮ7÷24
ድንግልናን በሕይወት ዘመን በሙሉ ጠብቆ በምንኩስና መኖር ከስጦታነቱ በተጨማሪ በፈቃደኝነት ሊደረግ የሚገባው ነገር ነው እንጃ. የሚገደዱበት ተግባር አይደለም፡፡ ሐዋረያው ድንግልናዊ ኑሮ ውዴታ እንጂ ትእዛዝ አለመሆኑን ሲገልጽ ‹‹ስለ ደናግልም የጌታ ትእዛዝ የለኝም» በማለት ተናግሯል::
በድንግልና ተወስኖ ለመኖርም ሆነ ወደ ጋብቻ ለመሄድ የድንግልና መኖር አስፈላጊ በመሆኑ ድንግልናን ጠብቆ ለመኖር ስጦታችን የትኛው እንደሆነ ማወቅም አያስፈልገንም፡ በድንግልና ኖረን ከመነኮስን እሰይ ያሰኛል፡ ካገባንም ይበል የሚያሰኝ ነውና ድንግልናን ክወዲሁ ጠብቆ መኖር ይገባል፡፡
እስከ ጋብቻ ድረስ ድንግልናውን ጠብቆ ኖሮ ያገባ ሰው ሐዋርያው እንደተናገረው መልካም አደረገ:: 1ቆሮ7÷38 የታዘዘውን በሚገባ ፈጽሟልና ክበጎ ባርያዎች ጋር ይቆጠራል:: ያላገባ ወይም መላ ዘመኑን በድንግልና ለመኖር የወሰነ ደግሞ ከታዘዘው በላይ የትሩፋት ሥራ ሠርቷልና የተሻለ አደረገ፡፡ 1ቆሮ7÷38
በጎ ሎሌን ጌታው ሸማ አጥበህ፤ ማገር ቆርጠህ ና ብሎ ያዘዋል:: እርሱ ግን ጌታዬ አይችልም በማለት አዝኖልኝ ነው እንጂ
ዓሣን ለወጥ፣ ለማገር ደግሞ ልጥ ጨምሬ ይዤ ብሄድ ይከፋልን? ብሎ ልብሱን ካጠበና ማገሩን ከቆረጠ በኋላ ዓሣውንና ልጡን ጨምሮ ይመለሳል:: እንደዚሁ ሁሉ መነኮሳትም የፈጣሪ ታማኝ ባሪያዎች ናቸው:: ስለዚህ ፈጣሪ ሚስት አግብታችሁ፣ አሥራት፣ በኩራቱንና ቀዳምያቱን አውጥታችሁ፣ ሥጋውን ደሙን በሚገባ ተቀብላችሁ ኑሩ ቢላቸው ሚስት ማግባትን ተዉ፡ ይህንንም ያደረጉት ባሕሪያቸው ደካማ ነውና አይቻላቸውም ብሎ ፈጣሪያችን አዝኖልን ነው እንጂ ከሕገ ሥጋ ሕገ ነፍስ፣ ከሕገ እንስሳ ሕገ መላእክት እንደሚበልጥ የታወቀ አይደለምን? በማለት ስለ እግዚአብሔር ፍቅር ብለው በበጎ ፈቃደኝነት ነው እንጂ ተገደው አይደለም:: በዚህ ሥራቸው የተሻለ አድርገዋልና እንደ ታማኝ ሎሌ ይመሰገናሉ አንጂ አይነቀፉም:: ማቴ13፥4-8 (ትርጓሜ)
መላ ዘመንን ከሴት ርቆ ንጽሕ ጠብቆ በድንግልና መኖር በግዴታ ወይም በትእዛዝ የሚደረግ ሳይሆን ከፍቅረ እግዚአብሔር የተነሣ በፈቃደኝነት የሚደረግ መሆኑን «በእናት ማሕፀን ጃንደረቦች ሆነው የተወለዱ አሉ፥ ሰውም የሰለባቸው ጃንደረቦች አሉ፥ ስለ መንግሥተ ሰማያትም ራሳቸውን የሰለቡ ጃንደረቦች አሉ» በማለት ጌታችን የተናገረው ቃል ያስረዳል:: ማቴ 19÷12
«በእናት ማሕፀን ጃንደረቦች ሆነው የተወለዱ አለ› ማለት አንደ ኤርምያስ እና ዮሐንስ መጥምቅ ከማሕፀን ጀምሮ በምናኔ ለምንኩስናና ለድንግልዊ ኑሮ ተመርጠው የተለዩ አሉ ማለት ነው፡፡ “በሆድ ሳልሠራህ አውቄሃለሁ፥ ከማሕፀንም ሳትወጣ ቀድሼሃለሁ› እንዳለው ማለት ነው:: ኤር1፥5
«ሰውም የሰለባቸው ጃንደረቦች አሉ» ማለት መምህራን መክረውና አስተምረው ንጹሐን ያደረጓቸው ለድንግልናዊ ኑሮ ያበቋቸው አሉ ማለት ነው:: ለምሳሌ:- ሙሴ ኢያሱን፣ ኤልያስ ደግሞ ኤልሳዕን ቀርጸው ለዚህ ዓይነት የመዓርግ ኑሮ አብቅተዋቸዋል፡፡
«ስለ መንግሥተ ሰማያትም ራሳቸውን የሰለቡ ጃንደረቦች አሉ» ማለት ፈጣሪያችን አይችሉትም በማለት አዝኖልን ነው እንጂ ሳያገቡ መኖር የተሻለ ነው በማለት በራሳቸው ፈቃድ ድንግልናቸውን ጠብቀው ከሴት ርቀው መንግሥተ ሰማያትን የሚጠባበቁ አሉ ማለት ነው፡፡
እንደ ድንግልና ሁሉ በጋብቻም “አታመንዝር» የሚለው ሕግ ይጠበቃል እንጂ አይፈርስም። ስለዚህ እስከ ጋብቻ በንጽሕና ተጠብቆ ከሚኖርበት የድንግልና ሕግ ወደ ጥንድነት የሚተላለፉበት ጋብቻም ሕግ›› ይባላል፡፡ ብዙ መንፈሳዊ መጻሕፍት ባለትዳር ወይም ያገባ ለማለት «ሕጋዊ» የሚሉት በዚህ ምክንያት ነው::
ሐ. ድንጋሌ ሥጋ ዓይን ይባላል ወይም በ«ዓይን›› ይመስላል:: ለዚህም ምስክሩ ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ «መሀሮሙ ለደናግል ለእለ እያውሰቡ ከመ ይዕቀቡ ድንግልናሆሙ ከመ ብንተ ዓይን›› በማለት የተናገረው ቃል ነው:: ይህም ወደ አማርኛ ሲተረጎም
«ድንግልናቸውን እንደ ዓይን ብሌን ይጠብቁ ዘንድ ላላገቡ ደናግል ምክራቸው፣ አስተምራቸው፡፡>>ማለት ነው:: ድንግልና ለምን «ዓይን› እንደ ተባለ የሚያውቅ ማን ነው? ድንግልና የአንድን ሰው ማንነት እስከ መወሰን ወይም ገልጦ እስከ ማሳየት የሚደርስ መሠረታዊ ምሥጢር እንድትይዝ ሆና በመፈጠሯ አይደለምን? ዓይን ታያለች እርሷም ትታያለች፡፡ አንቺ ሴት ከጋብቻሽ በፊት ድንግልናሽን ያጠፋሽው ከሆነ ስታገቢ ባልሽን በምን ታይዋለሽ? ድንግልና «ዓይን› ተብላለችና፡፡ ባልም ቢሆን ድንግልናውን ጠብቆ ካልኖረ ረቂቅ መነጽር (ድንግልና) የለውምና ሚስቱን በምኑ ያያታል ? ዛሬ ዛሬ ብዙ ባልና ሚስቶች በጥቃቅን አለመግባባቶች ለአንድ ቀን እንኳን ተያይተው የማያውቁ ያህል የሚሆኑትና የሚኳረፉት ምናልባት ድንግልናን መጠበቅ ስለ ቀረ ይሆን? በማለት መጠየቅ አስተዋይነት ነው፡፡ ምክንያቱም ድንግልና ባልና ሚስት በተለየ መልኩ የሚተያዩበት የማይመረመር «ዓይን»ነውና፡፡
ድንግልና ሁሉን አርቆ የሚያሳይ ከፍተኛ ቦታ ነው:: የኑሮ ደረጃቸውን በድንግልና ሆነው መርምረውና ተመልክተው ያገቡ ሰዎች አይጸጸቱም: ማለትም አንድ ስው ደረጃው ማግባትም ይሁን መመንኮስ በሚገባ ለይቶ ማወቅ የሚችለው ንጽሕናውን ጠብቆ ለመኖር ከቻለ ብቻ ነው:: ድንግልና የንጽሕናን ቅባት የተኳለ አጥርቶ የሚመለከት የሰውነት መብራት ነውና፡፡
መጽሐፍ ቅዱስ «የሰውነት መብራት ዓይን ናት፡፡ እንግዲህ ዓይንህ ጤናማ ብትሆን ሰውነትህ ሁሉ ብሩህ ይሆናል፡፡ ዓይንህ ግን ታማሚ ብትሆን ሰውነትህ : ሁሉ የጨለመ ይሆናል» ይላል:: ማቴ6፡22-23 እንደዚሁም ሁሉ በዓይን የተመሰለች ድንግልናም በሕገ ወጥነት በዝሙት ሥሪ ከጠፋች አንድ ሰው ሰውነቱ ሁሉ እንደጨለመበት ለያምን ይገባዋል፡፡ ምክንያቱም ድንግልና ሃይማኖትና ምግባር መሠረታቸውን ለቀው እንዳይናጉ የሚያደርግ ጽኑ መሠረት ነውና፡፡ ማለትም አመለካከት፣ አነጋገርና አሠራር ሚዛናቸውን እንዳልሳቱ ከድንግልና አጠባበቅ አንጻር መናገር ይቻላል፡፡ ስለዚህ ድንግልና «ዓይን› ቢባል ያንሰዋል እንጂ አይበዛበትም፡፡
ብዙ ጊዜ ደንግልና ለሴቶች የሚነገረው በጉልህ ምልክት የሚታወቀው በእነርሱ ስለሆነ ነው:: ነገር ግን ድንግልና ለወንዶችም ተጠቃሽ መሆኑን መጽሐፍ ቅዱስ «ከሴቶች ጋር ያልረከሱ እነዚህ ናቸው፣ ድንግሎች ናቸው::» በማለት ከትቦ ይዟል:: ራእይ14፥4 በመሆኑም ድንግልናን የመጠበቅ ጥቅምም ሆነ ያለ መጠበቅ ጉዳት በማስተዋል ለተመለከተው በወንድም ሆነ በሴት በኩል ያለው ፋይዳ ተመጣጣኝ ነው:: ስለዚህ በዚህ ርእስ ሥር በጎላው ለመናገር ሴቶች ይጠቀሱ እንጂ ልዩ ማመልክቻ እስክ ሌለ ድረስ የሚወሳው ሁሉ ወንዶችንም ያጠቃልላል፡፡
የድንግልና ዓይነቶች
ድንግልናን በሁለት ወገን ከፍሎ ማየት ይቻላል፡፡ በሁለት ወገን ድንግል መሆኗን ለመግለጽ ስለ እመቤታችን ስለ ድንግል ማርያም ‹‹ድንግል በክልኤ» ተብሎ የተነገረው ቃል ለእክፋፈሉ በዋቢነት ይጠቀሳል::
የመጀመሪያው የድንግልና ዓይነት ድንጋሌ ሥጋ ሲሆን ሁለተኛው ዓይነት ደግሞ ድንጋሌ ነፍስ ነው፡፡ ድንጋሌ ነፍስ በሌላ መንገድ ድንጋሌ ሕሊና ይባላል። «ድንግል በሕሊናኪ ወድንግል በሥጋኪ» * «በሐሳብሽ ድንግል ነሽ በሥጋሽም ድንግል ነሽ› እንዲል፡፡ (ጸሎተ በሰላመ ገብርኤል መልአክ)
ድንጋሌ ሥጋ ለድንጋሌ ነፍስ መገለጫ፣ ጥላ ወይም አምሳል ነው:: ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ «እስመ ድንጋሌ ሥጋስ አርአያ ወጽላሎት ለእንታክቲ» ብሏልና፡፡ በእውነት «ድንግልና» የምትባለው ግን ድንጋሌ ነፍስ ናት፡፡ ለዚህም ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ «ወባሕቱ ድንግልናስ አማናዊት ድንጋሌ ነፍስ ይእቲ» በማለት አስረጅ የሚሆን ቃል ተናግሯል፡፡ «ነገር ግን አማናዊት ድንግልና የምትባለው ድንጋሌ ነፍስ ናት» ማለት ነው:: ዮሐ.ተግ28 ከላይ እንደ ተጠቀሰው ድንጋሌ ሥጋ በግዘፍ የሚታይ በገሢሥ የሚታወቅ ሲሆን ድንግሌ ነፍስ ግን ረቂቅ ነው፡፡
ነፍስ ግን ድንግልናዋ በብዙ ጐዳና ነው፡፡ ከቅጥነተ ድንግልናዋ (ከድንግልናዋ ረቂቅነት የተነሣሣ) አንድ ጊዜ በኃጢአት ተግባርና ሐሳብ የተወሰደባት ድንግልና በንስሐ ይመለስላታል:: ስለዚህ ድንጋሌ ነፍስ በኃጢአት ይወገዳል በንስሐ ደግሞ ይመለሳል ማለት ነው፡፡
የነፍስን ድንግልና የሚያጠፋው የኃጢአት ሥራና ሐሳብ ብቻ ነው:: ኃጢአት ካልሆነ በቀር የሥጋን ድንግልና እስክ ማጥፋት የደረሰ ጽኑ ተግባር እንኳን ቢሆን የነፍስን ድንግልና ሊያጠፋ አይችልም፡፡ ለምሳሌ፦ በቅዱስ ጋብቻ የተወሰኑ ባልና ሚስት በሚፈጽሙት ሩካቤ. ድንጋሌ ሥጋቸው ሲጠፋ የነፍስ ድንግልናቸው ግን አይወገድም። ምክንያቱም ሕጋዊ ባለትዳሮች ሩካቢያቸው ኃጢአት ባለመሆኑ ነው:: ይህን ሲያስረዳ ቅዱስ ዮሐንስ እፈ ወርቅ እንዲህ ብሏል:- «ወሶበኒ ባቲ ምት ድንግልት ይእቲ ተደንግሎ መንክረ» ይህም ማለት ባልም ብታገባ ድንቅ በሚሆን ድንጋሌ ነፍስ ድንግል ናት ማለት ነው፡፡ ዮሐ.ተግ.28
በተጨማሪም ከላይ የተጠቀሰውን ሐሳብ በሌላ አገባብ ብንመለከተው ይኽን ሐቅ እንረዳለን፡፡ ክህነትን አጽንቶ ዲያቆን ሆኖ ለመኖር ድንግልናን መጠበቅ ግድ መሆኑ ለማንም የተሠወረ አይደለም፡፡ ስለዚህ አንድ ዲያቆን ሕገ ወጥ በሆነ መንገድ ድንጋሌ ሥጋውን ሲያፈርስ ክህነቱን እያፈረሰ መሆኑ ግልጽ ነው:: ነገር ግን በተገቢ መንገድ ጋብቻ ፈጽሞ ሩካቤ በማድረጉ ምክንያት ድንጋሌ ሥጋውን ሲያጣ ክህነቱን ግን አያጣም:: ምክንያቱም ሕጋዊ ሩካቤ የነፍስን ድንግልና ስለማያጠፋና ስለማያረክስ ነው፡፡
ድንጋሌ ነፍስ የሌለው ሰው የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርስም:: ይህም ማለት የነፍስን ድንግልና የሚያጠፋው ኃጢአት ብቻ በመሆኑ ኃጢአቱን በንስሐ ያላራቀ ወይም ንስሐ ያልገባ ሰው ወደ መንግሥተ ሰማያት አይገባም ማለት ነው፡፡ ዮሐንስ ወንጌላዊ በራእይ መጽሐፉ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት መግባት የሚችሉት የነፍስ ድንግልና ያላቸው ብቻ መሆናቸውን ሲገልጽ:- «ከሴቶች ጋር ያልረከሱ እነዚህ ናቸው ድንግሎች ናቸውና፡፡ በጉ ወደሚሄድበት የሚከተሉ እነዚህ ናቸው፡፡ ለእግዚአብሔርና ለበጉ በኩራት እንዲሆኑ ክሰዎች የተዋጁ አነዚህ ናቸው::› ይላል፡፡ ራእይ14፥4
በተጨማሪም ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ድንጋሌ ነፍስ ወደ መንግሥተ ሰማያት ለመግባት ዋና ነገር መሆኑን ሲናገር እንዲህ ብሏል፦ «እስመ ድንጋሌ ነፍስ ይሬሲ ሱታፌ ምስለ ክርስቶስ ወያበውእ ውስተ መንግሥተ ሰማያት» ይህም በአማርኛ «ድንጋሌ ነፍስ ከመርዓዊ (ከሙሽራ) ክርስቶስ ጋራ አንድ ያደርጋል:: ወደ መንግሥተ ሰማያትም ያገባልና» ማለት ነው:: ዮሐ.ተግ.2
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
ይፍቱኝ አባቴ
የዓለም ወንጀለኛ በደለኛ ነኝ
ይፍቱኝ መምህሬ ይፍቱኝ ይባርኩኝ
ይፍቱኝ አባቴ ይፍቱኝ ይባርኩኝ
እናንተ ደካሞች ሸክም የከበዳችሁ
ኑ ብሎናልና እንዳሳርፋችሁ(፪)
አምላኬ ይቅር ባይ መሆኑን አውቃለሁ
አበስኩ ገበርኩ ብዬ ቀርቤአለሁ(፪)
አዝ---
ጴጥሮስ አስተምሯል ስለ ንስሐማ
ዮሐንስም ሰብኳል ስለ ንስሐማ
ልብ ያለው ልብ ያድርግ ጆሮ ያለው ይስማ(፪)
ያለፈው ጥፋቴ በደሌ እንዲፋቅ
አምላኬን በእንባ ይቅርታ ልጠይቅ(፪)
አዝ---
ስለ በደሌማ ስለኃጢአቴ
ንስሐዬን ይስጡኝ የንስሐ አባቴ(፪)
የማሰር የመፍታት ሥልጣን በሰጠዎ
ከኃጢአት ማሰሪያ ይፍቱኝ በአምላክዎ(፪)
አዝ---
በምድር ያሰሩት ታስሯል በሰማይ
በምድር የፈቱት ተፈትቷል በሰማይ(፪)
አዝ---
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
"አድኅነነ እግዚኦ"
አድኅነነ እግዚኦ አድኅነነ አምላክነ /፪/
ዘአድኃንካ ለነነዌ ሀገር በትንብልና ትንብልና ሣህልከ/፪/
አድነን ጌታ ሆይ አድነን አምላካችን/፪/
ያዳንካት ሀገረ ነነዌን በይቅርታህ በአምላካዊ ይቅርታህ/፪/
©በማኅበረ ቅዱሳን መዘምራን
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
ጾመ ሰብአ ነነዌ
የካቲት ፫-፭/፳፻፲፯ | 3 - 5/2017
‹‹ጾመ ሰብአ ነነዌ፤ የነነዌ ሰዎች ጾም›› የሦስት ቀን ጾም የጾሙት በነነዌ ይኖሩ የነበሩ ሰዎች ናቸው፡፡ ከተማዋም (ነነዌ) በጤግሮስ ወንዝ ዳርቻ የምትገኝ ስትኾን መሥራቿም ናምሩድ ነው (ዘፍ.፲፥፲፩-፲፪)፡፡ ጥንታዊቷ የነነዌ ከተማ ለአሦር መነሻ የሆነች፤ እጅግ ሰፊና ያማረች፤ የቅጥሯ ርዝመትም ፲፪ ኪሎ ሜትር የሚሸፈን ነበር፡፡ በከተማዋ ንጉሡ ሰናክሬም ብዙ ሕንጻዎችን ገንብቶ ነበር (ዮናስ ፬፥፲፩)፡፡
በዚያ ዘመን የነበሩ የነነዌ ሰዎች ኃጢአታቸው በዝቶ እግዚአብሔር ሊያጠፋቸው ሲል ዮናስ የስሙ ትርጓሜ ‹ርግብ› የሆነ በዳግማዊ ኢዮርብዓም ዘመነ መንግሥት የነበረ ነቢይን ቸርነትና ምሕረቱ የማያልቅበት እግዚአብሔር መክሮ፣ ዘክሮ እንዲመልሳቸውና ንስሐ እንዲገቡ ነቢዩ ዮናስን ወደ ነነዌ ሕዝብ ላከው (ሉቃ.፲፩፥፴)፡፡ ይህ ነቢይ መኖሪያው በገሊላ በጋትሔፌር ድንበር ከተማ ነበረ፤ አባቱም አማቴ ይባላል፡፡ በዚያን ጊዜ ኢዮርብዓም ሶርያውያንን አባሮ የእስራኤልን ድንበር እንዲመልስ ነቢዩ ዮናስ ትንቢትን ተናገረ (፪ኛነገ.፲፬፥፳፭፤ ዮናስ ፩፥፩)፡፡ ነቢዩ ኤልያስ ያስነሣው የሰራጵታዋ መበለት ሕፃን ነቢዩ ዮናስ እንደ ሆነ የቤተ ክርስቲያን ታሪክ ያስረዳል (፩ኛነገ.፲፯፥፲፱)፡፡ መድኃኒታችን ክርስቶስም የዮናስን ከዓሣ ሆድ መውጣት የራሱ ትንሣኤ ምሳሌ አድርጎ ነግሮናል (ማቴ.፲፪፥፲፱-፵፪፤ ሉቃ.፲፩፥፴-፴፪)፡፡
እግዚአብሔር አምላክም ‹‹ሔደህ በነነዌ ላይ ስበክ›› ባለው ጊዜ ነቢዩ ዮናስ ‹‹አንተ መሐሪ ነህ፤ ልትጠፉ ነው ብዬ ተናግሬ ብትምራቸው ሐሰተኛ ነቢይ እባላለሁ›› ብሎ ላለመታዘዝ እስራኤልን ለቆ በመርከብ ወደ ተርሴስ ሸሸ፡፡ እግዚአብሔርም ታላቅ ነፋስን አስነሥቶ መርከቧ በማዕበል እንድትመታ አደረገ፡፡ ከዮናስ ጋር በመርከቧ ተሳፍረው የነበሩ ነጋድያንም ያላቸውን ሀብት ወደ ባሕሩ መጣል ሲጀምሩ ነቢዩ ዮናስ ጥፋቱን ተገንዝቦ ‹‹ማዕበሉ በእኔ ምክንያት የመጣ ስለሆነ ንብረታችሁን ሳይሆን እኔን ወደ ባሕር ጣሉኝ›› ብሎ ተማጸናቸው፡፡ እነርሱም ‹‹ስለዚህ ሰው ነፍስ እንዳንጠፋ፣ ንጹሕም ደም በእኛ ላይ እንዳይደረግብን አይሆንም›› አሉ፡፡ ወደ ባሕሩ ለመጣል ዕጣ በተጣጣሉ ጊዜም ዕጣው በዮናስ ላይ ስለ ወጣ ነጋድያኑ ዮናስን ወደ ባሕሩ ጣሉት፡፡ ወዲያውኑ ከእግዚአብሔር ዘንድ የታዘዘ ታላቅ ዓሣ አንበሪ ዮናስን በአፉ ተቀብሎ ሦስት ቀንና ሦስት ሌሊት አሳድሮ ወደ ነነዌ አደረሰው፡፡ እግዚአብሔር የቅል ተክልን ምሳሌ በማድረግ ቅጠሉ በመድረቁ ዮናስ ባዘነ ጊዜ ‹‹አንተ ላልደከምክበት እና በአንድ ቀን በቅሎ ላደገ ቅል ስታዝን እነሆ በታላቂቱ ነነዌ ከተማ ያሉ ከአንድ መቶ ሃያ ሺሕ በላይ ሕዝብና እንስሳቱ የእጄ ፍጥረቶች ስለ ሆኑ ያሳዝኑኛል›› በማለት ነቢዩ ዮናስም ውሸታም ላለመባል መኮብለሉ ስሕተት መሆኑን አስረድቶታል፡፡
ዮናስም ነነዌ መሬት ላይ መድረሱን ባወቀ ጊዜ ከእግዚአብሔር መሸሽ አለመቻሉን ተረዳ፤ የነነዌ ሰዎችንም ‹‹ንስሐ ግቡ›› እያለ መስበክ ጀመረ፡፡ የነነዌ ሰዎችም ንስሐ በገቡ ጊዜ እግዚአብሔር ይቅር ብሎ ከጥፋት አድኗቸዋል፡፡ ሐሰት እንዳይባልም እሳቱ እንደ ደመና ሆኖ ከላይ ታይቶአል፡፡ የታላላቁ ዛፍ ቅጠል እስኪጠወልግ ድረስ አድርቆ ለሕዝቡ አሳይቷቸዋል፡፡ ንስሐቸው በከንቱ እንዳልቀረ አስረድቷቸዋል (ትንቢተ ዮናስ)፡፡ ታኅሣሥ ፭ ቀን የሚነበበው የመጽሐፈ ስንክሳር ክፍል ‹‹ወበልዐ አሐደ ኀምለ›› በማለት ንስሐ ያልገቡ አንድ አገር ያህል ሰዎች በእሳቱ እንደ ጠፉ ይነግረናል፡፡
ጾመ ነነዌ የሦስት ቀን ሱባኤ ነው፤ በሦስት ቀናት ጾምና ጸሎት ንስሐ የገቡ የነነዌ ሰዎች ከጥፋት እንደ ዳኑ ሁሉ፣ በብሉይ ኪዳን አስቴር ሦስት ቀን ጾማ፣ ጸልያ በእስራኤል ላይ የመጣውን መቅሠፍት እንዲመለስ አድርጋለች (አስ.፬፥፲፭-፲፮)፡፡ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም ከበዓል ስትመለስ ሕፃኑ ልጇ ኢየሱስ ክርስቶስ መንገድ ላይ ጠፍቶአት ከሦስት ቀን ፍለጋ በኋላ በቤተ መቅደስ አግኝታዋለች (ሉቃ.፪፥፵፮)፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ለሄሮድስ በሰጠው ምላሽ መልስ ሦስት ቀን የሱባኤ ፍጻሜ መሆኑን ገልጿል (ሉቃ.፲፫፥፴፪)፡፡
ጾመ ነነዌ የእግዚአብሔርን ቸርነትና መሐሪነት የምናስታውስበት ጾም ነው፡፡ ይኸውም እኛ ፍጡራኑ በበደልን ጊዜ ፈጽሞ ከማጥፋት ይልቅ ምክንያት ፈልጎ እንድንድን ያደርገናል፡፡ ዮናስ ለስብከት ፈቃደኛ ባይሆን እንኳን እግዚአብሔር በተለየ ጥበቡ እንዲሔድ አድርጎታል፡፡ በእርግጥ እግዚአብሔር ሌላ የሚልከው ነቢይ አጥቶም አይደለም፤ እርሱንም ጭምር ሊያስተምረው ስለ ፈለገ እንጂ፡፡ የነነዌ ሰዎች የተነሳሕያን ምሳሌ ናቸው፡፡ ይህም ማለት ሰው ጥፋቱን አምኖ ንስሐ ከገባ እግዚአብሔር ይቅር ማለቱን አይተውም፡፡ ለዚህም ነው ዮናስን ‹‹አንተ ላልደከምክበት እና በአንድ ቀን በቅሎ ላደገ ቅል ስታዝን እነሆ በታላቂቱ ነነዌ ከተማ ያሉ ከአንድ መቶ ሃያ ሺሕ በላይ ሕዝብና እንስሳቱ የእጄ ፍጥረቶች ስለ ሆኑ ያሳዝኑኛል›› ያለው፡፡
ቀደምት የቤተ ክርስቲያን አባቶቻችን ይህን እና ሌሎች አጽዋማትን እንድንጾም የወሰኑልን ያለ ምክንያት አይደለም፡፡ ሕጉ የተዘጋጀልን እንደ ነነዌ ሰዎች እኛም ጾመን፣ ጸልየን ከኃጢአታችን እንነጻ ዘንድ ነው፡፡ ዛሬ ዓለማችን በኃጢአት ማዕበል እየተናወጠች ባለችበት ወቅት እኛም እንደ ነነዌ ሰዎች ከበደላችን ብንመለስ እና ንስሐ ብንገባ ቸሩ ፈጣሪያችን እግዚአብሔር ይቅርታና ምሕረት የባሕርይ ገንዘቡ ስለ ሆነ ‹‹ወደ እኔ ተመለሱ፤ እኔም ይቅር እላችኋለሁ፤›› ይለናል፡፡
ስለሆነም በነቢዩ ዮናስ ላይ የተደረጉ ተአምራትንና ካለመታዘዝ የሚመጣ ቅጣት ቀላል አለመሆኑን በማስተዋል፣ ለነነዌ ሰዎች የወረደውን ምሕረት በመገንዘብ ለእግዚአብሔርም ሆነ ለሃይማኖት አባቶች እና ለወላጆቻችን መታዘዝ ይገባናል፡፡ ስንጾምም እግዚአብሔር አምላካችን መዓቱን በምሕረት፣ ቍጣውን በትዕግሥት መልሶ በኃጢአት ለጠፋው ዓለም ይቅርታውን ይልካል፡፡ በመጾማችን ራሳችን ከመዓትና ከመቅሠፍት ከመዳናችን ባሻገር በእኛ በደል ምክንያት አገራችን፣ ዕፀዋቱና እንስሳቱም ሳይቀር ከድርቅና ከቸነፈር ይተርፋሉና፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
"የእግዚአብሔር አገልጋይ - ዑራኤል"
መራሔ ብርሐን ረድኤትህ የበዛ
ወደ ግብጽ ስትሄድ ድንግል ልጇን ይዛ
አብረህ የተራዳህ መልአከ ልዑል
የእግዚአብሔር አገልጋይ ቅዱሥ ዑራኤል
አበው ሰብአ ሰገል ዑራኤል
ከምሥራቅ ሲመጡ ዑራኤል
ኮከቡን የመራህ ዑራኤል
አምሐ እንዲሠጡ ዑራኤል
ሕይወቴን አቅናልኝ ዑራኤል
ከኃጢአት አውጣና ዑራኤል
በብርሐን ምራኝ በጽድቅ ጎዳና
አዝ=
ፈጥነህ የምትደርስ ዑራኤል
ሥምህን ለጠራ ዑራኤል
ጽዋዕ ልቦና ዑራኤል
ያጠጣህ ለዕዝራ ዑራኤል
ጥበብ መንፈሣዊ ዑራኤል
በውስጤ እንዲዘራ ዑራኤል
ብርሐናዊው መልአክ ልቦናዬን አብራ
አዝ=
ለሔኖክ የገለጥህ ዑራኤል
የረቀቀን ምሥጢር ዑራኤል
በገጸ ሠማይ ላይ ዑራኤል
የፊደላት ቁጥር ዑራኤል
ማስተዋል አግኝቼ ዑራኤል
በፍቅር እንድሞላ ዑራኤል
ምልጃህ አይለየኝ ይሁነኝ ከለላ
አዝ=
አምላክ ሥለሰው ልጅ ዑራኤል
ቀራንዮ ሲሰዋ ዑራኤል
ደመ መለኮቱን ዑራኤል
በብርሐን ጽዋ ዑራኤል
ተቀብለኽ ረጭተህ ዑራኤል
ዓለምን የቀደስህ ዑራኤል
ለምስጋና አንቃኝ በነግህና በሰርክ
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
ስጋዋንም ያሳዩት ዘንድ ወደ መቃብሯ ባደረሱት ጊዜ በመቃብር ውስጥ ስጋዋን አላገኙም ደንግጠውም አደነቁ ያን ጊዜ ከመላእክት ጋር ወደ ሰማይ ስታርግ እመቤታችንን እንዳገኛት ቶማስ ነገራቸው። ሐዋርያትም ይህን በሰሙ ጊዜ የእመቤታችንን እርገቷን ስላላዩ እጅግ አዘኑ ስጋዋን በምድር ውስጥ ይተው ዘንድ እንዳልወደደ መንፈስ ቅዱስ አስገነዘባቸው። ከዚህም በኋላ አንድ ጊዜ ደግሞ እርሷን ያሳያቸው ዘንድ እንዳለው ጌታችን ቃል ኪዳን በማድረግ ተስፋ ሰጣቸው እነርሱም እስከ ነሐሴ አስራ ስድስት በተስፋ ኖሩ።
የእመቤታችንም የእድሜዋ ዘመን ስልሳ አራት ዓመት ነው፤ በአባትና እናቷ ቤት ሶስት ዓመት ከሰባት ወር ፣ በቤተ መቅደስም አስራ ሁለት ዓመት ፣ በዮሴፍም ቤት ሰላሳ አራት ዓመት ከሶስት ወር ፣ ከጌታ እርገት በኃላ በወንጌላዊ ዮሀንስ ቤት አስራ አራት ዓመት ነው።
የእመቤታችን ፍቅሯ፤ በረከቷ ፤ አማላጅነቷ በእኛ በምናምን ክርስቲያኖች ላይ እጥፍ ድርብ ሆኖ ይደርብን! የአስራት ሐገሯን ኢትዮጵያን ከፈተና ትጠብቅልን! አሜን!
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
"ጊዮርጊስ በዚያች ቀን"
ጊዮርጊስ በዚያች ቀን ከፈተናው አንፃር
ስለሃይማኖቱ የታየው ምን ነበር
ያመነውን አምላክ አላውቀውም እንዲል
በሥልጣን በገንዘብ እርሱን ለመሸንገል
የዱዲያኖስ ጭፍሮች ነገር ሲያሴሩበት
ልቡናው ምን አለ ሲቀርብ ለመሥዋዕት
ስገድ ባሉት ጊዜ ሰው ለሠራው ምስል
ትዝ አለው ጊዮርጊስ የአምላኩ ሕያው ቃል
ከሠለስቱ ደቂቅ ከዳንኤል ጋር
በእሳት ነበልባል ውስጥ ተአምር ሲሠራ
ቂርቆስ ኢየሉጣን ከመቃጠል ዋጅቶ
ያቀዘቀዘውን ፍሉን ውኃ አጥፍቶ
አስታውሷል ጊዮርጊስ ያንን ኃያል ጌታ
መስቀል መሸከሙን በዚያች ጎሎጎታ
ጴጥሮስና ጳውሎስ አባቶቹን መስሎ
ሞትን አሸነፈ በእምነት ተጋድሎ
እንድንጸና በእምነት ይህችን ዓለም ንቀን
በሰማዕቱ ምልጃ አምላክ ይጠብቀን
©በማኅበረ ቅዱሳን መዘምራን
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
ጥር ፲፰
ዝርወተ አፅሙ ለቅዱስ ጊዮርጊስ
ጥር ዐስራ ስምንት በዚች ቀን የሰማዕታት አለቃ የቅዱስ ጊዮርጊስ አፅሙ ተቃጥሎ ተደቁሶ የተበተነበት ነው፡፡
ይኸውም ሰባ ነገሥታት ማሰቃየት በሰለቻቸው ጊዜ ቅዱስ ጊዮርጊስን እንደ መጭመቂያ ሆኖ ከተሠራ የስቃይ መሣሪያ ላይ አውጥተው ሰውነቱን እንዲሰነጥቁት ንጉሥ ዱድያኖስ አዘዘ፡፡ አንጀቱ ሁሉ ወጥቶ ከምድር ላይ እስኪዘረግፉት ድረስ እንዲህ አደረጉበት፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከስቃይ ብዛት የተነሳ ነፍሱ ከሥጋው ተለየች ሥጋውንም በሙሉ በእሳት አቃጠሉት አመድም ሆነ፡፡
ከሐዲው ንጉሥ ዱዲያኖስ የተቃጠለውን የሥጋውን አመድ አፍሰው በቀፎ አድርገው ይድራስ ወደሚባል ተራራ ወስደው ምዕመናን ራሩን አመዱን እንኳን እንዳያገኙት በነፋስ እንዲዘሩት አዘዘ፡፡ ደብረ ይድራስ ማለት ምድረ በዳ ማለት ነው፡፡ ወታደሮቹም የሥጋውን አመድ በተራራ ላይ ነስንሰው የተመለሱበት፣ የሥጋው አመድ ያረፈበት ዕፅዋት ሁሉ ጊዮርጊስ ጊዮርጊስ ያሉበት፣ ጌታችን ከመላእክት ጋር ተገልጦ አራቱን የምድር ነፋሳትንም የቅዱስ ጊዮርጊስ የሥጋውን ትቢያ እንዲሰበስብ አዝዞ "የኔ ሆይ! የመረጥኩህ ወዳጄ ጊዮርጊስ ከሞት ተነሥ አትፍራ፤ እኔ አዝዤሀለሁና" ሲል ኀያሉን ሰማዕት ቅዱስ ጊዮርጊስ ጠራው። ያን ጊዜ ልዑል ንዑድ ጊዮርጊስም ከጫጉላ ቤት እንደሚወጣ ሙሽራ ምንም ሕማም ሳይኖርበት ተነሣ።
መድኃኒታችንም ባረከው። "አትፍራ፤ ይኸንን ከሀዲ ንጉሥም እስክታሳፍረው ድረስ እኔ አጸናሀለሁ። 'ከእንዲህስ ወዲህ አምላኩ ከእጃችን ሊያድነው አይችልም' እንዳይሉ እነዚህን ከሐድያን ነገሥታትና የረከሱ ጣዖታቸውን ታሳፍራቸው ዘንድ ተነሣና ወደ አገር ውጣ፤ ሰላሜ ለዘለዓለም ከአንተ ጋር ይሁን።" አለው፤ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ይህን ተናግሮ ሳመው። በፍጹም ምስጋናም ወደ ሰማይ ዐረገ። ቅዱስ ጊዮርጊስ ከጌታችን ይህንንም ቃል ኪዳን የተቀበለበት ቀን ነው፡፡
አምላካችን ከሊቀ ሰማዕት ቅዱስ ጊዮርጊስ ረድኤት በረከት ይክፈለን! ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን እንዲሁም ሐገራችን ኢትዮጵያን ሰማዕቱ ከፈተና ይጠብቅልን! አሜን!
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
የቤተክርስቲያንን መብትና ጥቅም ለማስከበር እና የሕግ ተጠያቂነትን ለማረጋገጥ በጥብቅ እየተሰራ ነው።
ጥንታዊት፣ታሪካዊትና ዓለም አቀፋዊት የሆነችው የኢትዮጵያ ኦርቶዶከስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መንፈሳዊ አገልግሎቷን ለማስፋፋት በምታደርጋቸው እንቅስቃሴዎች ሁሉ የሌሎችን መብትና ጥቅም ባለመንካት በትዕግሥትና በማስተዋል የምትጓዝ አገራዊ ኃላፊነት የሚሰማት ሰላምን አብዝታ የምትሰብክ መንፈሳዊት ተቋም መሆኗ ይታወቃል።
ቤተክርስቲያናችን ሥርዓተ አምልኮቷን ለማስፋፋት በተጓዘችባቸው አያሌ ዓመታት አገራችን ኢትዮጵያ የራሷ ፊደላትና የራሷ የቀን አቆጣጠር ባለቤት እንድትሆን ያስቻለች፣በሊቃውንቶቿ የመጠቀ እውቀት አማካኝነት የሥነ ጥበብ፣የሥነ ስዕል፣የዕጽዋትና የጠፈር ምርምርና ጥናቶችን በማከናወን ተጨባጭ ውጤቶችን ለዓለም ያበረከተች ጥንታዊት ተቋም ስለመሆኗም አያሌ ማስረጃዎችን ማቅረብ ይቻላል።
ይሁን እንጂ ይህች ለአገረ መንግስት መመስረትና መጽናት፣ለእውቀት መስፋፋት፣ ለአብሮነት መጎልበት፣ ትውልድን በሥነ ምግባር ቀርጻ ፍቅርና አንድነትን በተግባር የሰበከች እናት ቤተክርስቲያን ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በተለያዩ አካላት መብትና ጥቅሟን የሚነኩ፣በአስተምህሮቿ፣በዕምነቷ፣በንዋያተ ቅድሳቶቿ ላይ መሰረታቸውን ያደረጉና ትዕግስቷን የሚፈታተኑ ክብርና ሉአላዊነቷን የሚዳፈሩ እኩይ የትንኮሳ ተግባራት እየተፈጸመባት ይገኛል።
ጥር ፲፭
ቅዱስ ቂርቆስና እናቱ ቅድስት ኢየሉጣ
ጥር ዐሥራ አምስት በዚህች ዕለት የከበረ ሕፃን ቂርቆስ :እናቱ ብፅዕት ኢየሉጣ ዳግመኛ ለከበረ ሕፃን ቂርቆስ ማኅበር የሆኑ ዐሥራ አንድ ሺህ አራት ሰዎች በሰማዕትነት ሞቱ።
በዚያንም ወራት የክብር ባለቤት የሆነ ክርስቶስን በሚያምኑ የክርስቲያን ወገኖች ላይ ታላቅ መከራና ስደት ሆነ። ስሟ ኢየሉጣ የሚባል አንዲት ሴት ነበረች እርሷም ከታናሽነቷ ጀምራ ደግ ናት ስደትም እንደሆነ በሰማች ጊዜ መኰንኑን ከመፍራት የተነሣ ሕፃኗን ይዛ ከሮም ከተማ ተሰዳ የኪልቅያ አውራጃ ከሆነ ከጠርሴስ ደርሳ ከዚያም በሀገሮች ውስጥ እየተዘዋወረች ተቀመጠች።
ወደዚያች አገርም ያ ከእርሱ የሸሸችው መኰንን እለእስክንድሮስ መጣ ጭፍሮቹም ክርስቲያኖችን ፈለጓቸው። ይቺንም ቅድስት ኢየሉጣን አግኝተው ያዝዋትና ወደ መኰንኑ አደረሷት የክርስቲያን ወገንም እንደሆነች ነገሩት።
መኰንኑም ሴትዮ ተናገሪ ከወዴት ሕዝብ ወገን ነሽ ነገድሽ ምንድን ነው ሀገርሽስ ወዴት ነው አላት። የከበረች ኢየሉጣም እንዲህ ብላ መለሰችለት የአንጌቤን ሰው ለሆንኩ ለእኔ ወገኖቼ ለኢቆንዮን አገር አለቆች የሆኑ ኤሳውሮሳውያን ናቸው እኔም በአንተ ምክንያት ሸሽቼ ነበር እነሆ ዛሬ ግን በእጅህ ውስጥ ነኝ አለችው።
መኰንኑም በእጄ ውስጥ እንደተገኘሽ ታውቂያለሽን አላት አሁንም የሚሻልሽን ምረጪ ስምሽንም ተናገሪ እኔንም እሺ በይኝና ለአማልክት ሠዊ የከበረች ኢየሉጣም ለረከሱ አማልክት እኔ አልሰዋም አለችው መኰንኑም ስምሽን ስጪ ተናገሪ አላት እርሷም የኔ ስም ክርስቲያን መባል ነው አለችው። መኰንኑም ይህስ ስንፍና ነው የሚጠቅምሽ አይደለም እንዳትሞቺ ስምሽን ስጪ ተናገሪ አላት። የከበረች ኢየሉጣም የኔ ስም ክርስቲያን መባል እንደሆነ ነገርኩህ ሞት የሚሽረው በሰዎች ዘንድ የምጠራበትን ከፈለግህ ስሜ ኢየሉጣ ነው ብላ መለሰችለት።
መኰንኑም ጽኑ የሆኑ ሥቃዮችን በላይሽ ሳይመጣ ተነሥተሽ መሥዋዕትን ለአማልክት አቅርቢ አላት። የከበረች ኢየሉጣም ዕወነት ነገርን ለመሥራት የምትሻ ከሆነ ዕድሜው ሦስት ዓመት የሆነ ሕፃን ልጅ ይፈልጉ ዘንድ ወደ ሀገሩ መንደር ላክ ወዳንተም ያምጡትና የምንገዛለትንና የምናመልከውን እርሱ ይንገረን አለችው።
ያን ጊዜም የሦስት ዓመት ልጅ ይፈልጉ ዘንድ መኰንኑ ወታደሮችን ላከ የሀገር ሰዎችም ልጆቻቸውን ሠውረዋልና አላገኙም ከዚያም ከከተማው ቅጽር ውጭ በፀሐይ መውጫ ወዳለው በረሀ በኩል ወጡ የቅድስት ኢየሉጣንም ልጅ አገኙት ይህ ሕፃን የስንት ዓመት ልጅ ነው ብለው ስለርሱ ጠየቁ ሰዎችም ይህ ሕፃን የሦስት ዓመት ሲሆን የክርስቲያናዊት መበለት ልጅ ነው አሏቸው።
ያንንም ሕፃን ይዘው ወደ መኰንኑ ወሰዱት መኰንኑም መልኩ የሚያምርና ደም ግባት ያለው እንደሆነ በአየው ጊዜ ደስ የምትል ደስተኛ ሕፃን ሰላምታ ይገባሃል አለው። ሕፃኑም እኔን ደስተኛ ማለትህ መልካም ተናገርክ ላንተ ግን ደስታ የለህም እግዚአብሔር ለዝንጉዎች ደስታ የላቸውም ብሏልና ብሎ መለሰለት መኰንኑም ሕፃኑን ሳልጠይቅህ ይህን ያህል ትመልስልኛለህን አለው። ሕፃኑም ገና ከዚህ የሚበዛ ነገርን እመልስልሃለሁ አለው።
መኰንኑም ሕፃኑን ስምህ ማን ነው አለው ከንጹሕ ዐዘቅትና ከማይለወጥ ከማይጠፋ ውኃ የተገኘ ሕፃን ስሜ ክርስቲያን መባል ነው ብሎ መለሰለት። መኰንኑም ዳግመኛ እንዳትሞት ስምህን ንገረኝ አለው የከበረ ሕፃንም ስሜ ክርስቲያን መባል እንደሆነ ነገርኩህ ሞክሼ ስም የምትሻ ከሆነ እናቴ የሰየመችኝ ቂርቆስ ነው።
መኰንኑም ሕፃን ቂርቆስን እሺ በለኝና ለአማልክት ሠዋ በሥጋህም ስታድግ እሾምሃለሁ በብዙ ወርቅና ብርም አከብርሃለሁ አለው። ሕፃኑም የሰይጣን መልእክተኛ ለዕውነትም ጠላቷ የሆንክ ከእኔ ራቅ አለው።
መኰንኑም ሰምቶ ተቆጣ ደሙ እንደ ውኃ እስከሚፈስ ቆዳውን እንዲጨምቁትና እንዲገፉት አዘዘ። የከበረች ኢየሉጣም የልጅዋን ትዕግሥት ባየች ጊዜ እግዚአብሔርን አመሰገነችው።
ከዚህም በኋላ መኰንኑ ጨውና ሰናፍጭ አምጡ አለ የሁለቱንም አፍንጮቻቸውን ከፍተው ያንን ጨውና ሰናፍጭ እንዲጨምሩባቸው አዘዘ ያን ጊዜ ሕፃኑ ትእዛዝህ ለጕረሮዬ ጣፋጭ ሆነ ከማርና ከስኳርም ለአፌ ጣመኝ ብሎ ጮኸ።
ሁለተኛም መኰንኑ እንዲህ ብሎ አዘዘ የረዘሙና የተሳሉ በእሳትም እንደ ፍም የጋሉ ዐሥራ አራት የብረት ችንካሮች አምጡ ሰባቱን በእናቱ አካላት ውስጥ ጨምሩ በሕፃኑም ሁለት በጆሮዎቹ ሁለት በዐይኖቹ ሁለት በአፉና በአፍንጫው አንድ በልቡ ጨምሩ እንዲህ ሲጨመርበት ጆሮዎቹ እንዲአሩ ዐይኖቹም ይጠፉ ዘንድ አንደበቱም ይቃጠል ዘንድ ወደ ልቡም ጽኑ ሕማም ገብቶ እርሱ ከዚህ ዓለም በሞት እንዲለይ ለእናቱም እንዲሁ አድርጉ ችንካሮችም በቅዱሳኑ በሥጋቸው ሁሉ ተጨመሩ።
የክብር ባለቤት በሆነ በጌታችን ትእዛዝ የብረቶቹ ግለት ጠፍቶ እንደ በረዶ ቀዘቀዘ ጤነኞችም ሆኑ መኰንኑም ወደ ወህኒ ወስዳችሁ በዚያ አሥራችሁ ዝጉባቸው አለ።
ከዚህም በኋላ መኰንኑ የሥቃይ መሣሪያ ይሠራ ዘንድ አንዳዝዘው ብረትን የሚያቀልጥ ሰው አምጡልኝ አለ። በአመጡለትም ጊዜ ሰይጣኑ ወደ መኰንኑ ልብ ገብቶ አንደበቱን ዘጋውና መናገር ተሳነው ሕፃኑ ፈጥኖ አክሊልን ለመቀበል እንደሚተጋ ሰይጣን ስለ አወቀ ስለዚህ ዘጋው።
ከዚህም በኋላ ሕፃኑ ሠራተኛውን ጠርቶ እኔንና እናቴን የሚያሠቃዩበትን የሥቃይ መሣሪያ መሥራት ትችላለህን ይህ መኰንን ግን ምንም የሚያውቀው ነገር የለም አለው ሠራተኛውም እንደምትሻው በል ንገረኝ እንደምታዝዘኝ እኔ መሥራት እችላለሁ አለው።
ሕፃን ቂርቆስም ሊአዝዝ ጀመረ እንዲህም አለ ሁለት መላጫዎች ስፋታቸው አራት ክንድ የሆነ ለእኔና ለእናቴ ሥራ። ዳግመኛም የሚያስጨንቅ ራስን የሚመታና የሚሰብር አንገትንም የሚያሥር የሚዝቅም ሹካ ዐይንንም የሚያወልቅ አካልንም የሚበሳሳ አፍንጫንም የሚያጣምምና የሚሰብር ጆሮንም የሚልጥ ሕዋሳትን የሚፈታና የሚለያይ እንደ ልጓም ሁኖ ምላስን የሚቆርጥ በሰውነትም ውስጥ ገብቶ የሚንቀሳቀስ ቆላፋ ጉጠትን ጐኖችንም የሚፍቅና የሚቆለምም አስጨናቂ የሆነ ጉልበቶችንና ጭኖችን የሚሰብር ጅማቶችንም የሚቆራርጥ ሥሮችንም የሚመዝ በዚችም አስጨናቂ መሣሪያ ጅማቶችን የሚታታ አድርግ።
ዳግመኛም በላም አምሳል ሰፊ መቀመጫ ከናስ ሥራ ሦስት ቀዳዳዎችንም በዚያ መቀመጫ ውስጥ ቅደድ። በቁመቴም ልክ ሦስት ችንካሮችን ሥራ የችንካሮቹንም ራስ ከናስ አድርገህ በውስጡ ከሚጠሩት ዘንድ ፈጽሞ የማይለይ ልዩ ሦስት ብለህ ጻፍ።
ዳግመኛም ጠምዝዞ ወደ ላይ የሚያወጣ ሁለት መሣሪያ ሁለት መጋዞችን ሁለት የብረት ምጣዶችን ሥራ አሁንም አንድ ታላቅ ጋን ሠርተህ በውስጡ አንገትን የሚጠመዝዝና የሚሠነጥቅ ተሽከርካሪ መሣሪያ አድርግ።
በውስጥ የተሸሸገ የሆድ ዕቃን የሚመረምር እጅን ከብረት ሥራ እኔ የጻዕር ስቃይን የምሠቃይበት ይህ ነው አለ። ብረት ሠሪውም ሰምቶ እጅግ አደነቀ የሚረዱትንም ከሀገር ውስጥ መቶ ሠራተኞችን ሰብስቦ መሥራት ጀመረ በአርባ ቀንም ጨረሰ።
ከዚህም በኋላ መኰንኑ እለእስክንድሮስ ቂርቆስንና እናቱን ወደ አደባባይ ያመጡአቸው ዘንድ አዘዘ ያን ጊዜ አንደበቱ ተፈትቶ ነበርና እንዲህም አለ ሕፃኑንና እናቱን ከቆዳቸው ጋር ራሳቸውን ላጩአቸውና በላያቸው የእሳት ፍሞችን ጨምሩ እርር ብለው እንዲቃጠሉ ዳግመኛም አራት ችንካሮችን ከትከሻዎቹ እስከ ተረከዙ ድረስ እንዲተክሉበት አዘዘ የእግዚአብሔርም መልአክ መጥቶ ሥቃዮችን ከርሱ አራቀ።
"እንዘ ስውር"
እንዘ ስውር እምኔነ ይእዜሰ ክሱተ ኮነ(፪)
ተአምረ ወመንክረ ገብረ መድኃኒ በቃና ዘገሊላ ከብካብ ኮነ ማየ ረሰየ ወይነ(፪)
©በማኅበረ ቅዱሳን መዘምራን
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox