በዚህ Channel ውስጥ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንን ዶግማ ፤ ቀኖና እና ትውፊት የጠበቁ ትምህርቶች ይተላለፉበታል፡፡ ለአስተያየት: ጥቆማና ጥያቄ በዚህ ያግኙን ☞ @Ethiopian_Orthodox_bot Buy ads: https://telega.io/c/Ethiopian_Orthodox
ነሐሴ ፯
ጽንሰታ ለእግዝእትነ ማርያም ድንግል ወላዲተ አምላክ
ጴጥርቃ እና ቴክታ የሚባሉ ደጋግ ሰዎች በኢየሩሳሌም በአንድነት ተጋብተው ይኖሩ ነበር፡፡ እነዚህም በእግዚአብሔር የሚያምኑ የተወደዱ ጻድቃን ሰዎች ነበሩ፡፡ እነዚህም ሰዎች በእግዚአብሄርም በሰውም ዘንድ የተመሰከረለላቸው ባለጸጎች ነበሩ፡፡ ነገር ግን መካን ስለነበሩ የሚወርሳቸው ልጅ አልነበራቸውም፡፡
አንድ ቀን ጴጥርቃ ቴክታን እንዲህ አላት፡- ‹‹እኅቴ ሆይ! ይህን ሁሉ የሰበሰብነውን ገንዘባችንን ምን እናደርገዋለን? ልጅ የለን የሚወርሰን አንቺም መካን ነሽ፣ እኔም ካንቺ በቀር ሌላ ሴት አላውቅም›› አላት፡፡ እርሷም ‹‹ወንድሜ ሆይ! አምላከ እስራኤል ለእኔ ልጅ ቢነሳኝ አንተም እንደኔው ሆነህ ትቀራለህን? ከሌላ ደርሰህ ውለድ እንጂ›› ብላ ብታሰናብተው ‹‹እንደዚህ ያለ ነገር እንኳንስ ላደርገው በልቦናዬም እንዳላስበው አምላከ እስራኤል ያውቃል›› አላት፡፡ እርሷም ‹‹አምላከ እስራኤል የሚያደርገውን የሚያውቅ የለም፣ ትላንትና ማታ በህልሜ ነጭ ጥጃ ከማኅፀኔ ስትወጣ ያችም ነጭ ጥጃ ሌላ ነጭ ጥጃ ስትወልድ እንዲሁ እስከ 7ት ትውልድ ሲዋለድ ሰባተኛይቱ ጨረቃን ስትወልድ፣ ጨረቃዋም ፀሐይን ስትወልድ አየሁ›› አለችው፡፡ እርሱም በጠዋት ከህልም ፈቺ ዘንድ ሄዶ የነገረችውን ሁሉ ነገረው፡፡ ያም ህልም ፈቺ ‹‹እግዚአብሔር በምሕረቱ አይቷችኋል በሳህሉ መግቧአችኋል፣ 7 አንስት ጥጆች መውለዳችሁ 7 ሴቶች ልጆችና የልጅ ልጆች ትወልዳላችሁ፣ ከቤታችሁ ሰባተኛይቱ ጨረቃ መውለዷ ከሰው የበለጠች ከመላእክትም የከበረች ደግ ፍጥረት ትወልዳላችሁ፤ የፀሐይ ነገር ግን አልታወቀኝም›› አለው፡፡ እርሱም የነገረውን ሁሉ ሄዶ ለሚስቱ ነገራት፡፡ እርሷም ‹‹እንጃ አምላከ እስራኤል የሚያደርገውን ማን ያውቃል!›› ብላ ዝም አለች፡፡ ከዚያም ፀንሳ ሴት ልጅ ወለደች፡፡ ስሟንም ሔሜን ብለው አወጡላት፤ ሔሜንም አድጋ ለአካለ መጠን ስትደርስ ባል አጋብተዋት ሴት ልጅ ወለደች፣ በስምንተኛ ቀኗም ዴርዲ ብለው ስም አወጡላት፡፡ ዴርዲም አድጋ እንዲሁ ሴት ወለደችና ቶና አለቻት፣ ቶናም እንዲሁ ሴት ልጅ ወልዳ ሲካር አለቻት፣ ሲካርም እንዲሁ ሴት ልጅ ወልዳ ሴትና አለቻት፣ ሴትናም እንዲሁ ሴት ልጅ ወልዳ ሔርሜላ አለቻት፣ ሔርሜላም እንዲሁ ሴት ልጅ ወልዳ ንጽህት ቅድስት ክብርት የምትሆን እመቤታችንን የወለደቻትን ቅድስት ሐናን ወለደች፡፡
ይኽችም ቅድስት ሐና በሥርዓት አድጋ ለአእምሮ ስትበቃና አካለ መጠን ስትደርስ ከቤተ መንግስት ወገን ከነቅዱስ ዳዊት ወገን ከሆነው ከቅዱስ ኢያቄም ጋር አጋቧት፡፡ እነዚህ ቅዱሳን ኢያቄምና ሐና በአንድነት ተጋብተው ሲኖሩ ልጅ አጡ፡፡ እነርሱም እጅግ ደጋግ ሰዎች ነበሩ፡፡ አንድ ልጅ እንኳ ስላልነበራቸው እጅግ ያዝኑ ነበር፡፡ ወደ ቤተ መቅደስ እየሄዱ እግዚአብሔር ልጅ ይሰጣቸው ዘንድ አጥብቀው ይለምኑት ነበር፡፡ መብዓ ይዘው ለሊቀ ካህኑ ሲሰጡት ሊቀ ካህኑም እንኳ ሳይቀር ‹‹እግዚአብሔር ብዙ ተባዙ ያለውን ሕግ በእናንተ ላይ እንዳይፈጸም አድርጎ ልጅ የከለከላችሁ ኃጢአተኛ ብትሆኑ ነውና መብዓችሁን አልቀበልም›› ብሎ በእጅጉ አሳዝኗቸዋል። በሊቀ ካህኑ እያዘኑና እየተከዙ ሲመለሱ ከድካማቸው ያርፉ ዘንድ ዛፍ ሥር ተቀመጠው ሳለ እርግቦች ጫጩቶቻቸውን ሲያጫውቱ ተመልክተው ‹‹ለእነዚህ ወፎች እንኳ ልጆችን የሰጠህ አምላክ ለእኛስ መች ይሆን ልጅ የምትሰጠን?›› ብለው እጅግ አምርረው አለቀሱ፡፡
ቅዱስ ኢያቄምና ቅድስት ሐና ሲያዝኑ ሲጸልዩ ውለው ከዘካርያስ ከሊቀ ካህናቱ ሄደው ‹‹አቤቱ ጌታችን ሆይ ወንድ ልጅ ብንወልድ ተምሮ ቤተ እግዚአብሔርን አገልግሎ እንዲኖር እንሰጣለን፤ ሴት ልጅም ብንወልድ ውኃ ቀድታ መሶብ ወርቅ ሰፍታ መጋረጃ ፈትላ ካህናትን አገልግላ እንድትኖር እንሰጣለን›› ብለው ስዕለት ገቡ፡፡ ዘካርያስም ‹‹እግዚአብሔር ጸሎታችሁን ይስማችሁ ስዕለታችሁን ይቀበልላችሁ የልቦናችሁን ሀሳብ ይፈጽምላችሁ›› ብሎ አሳረገላቸው፡፡ ከዚህም በኋላ ቅድስት ሐናና ቅዱስ ኢያቄም ዕለቱን ራእይ አይተው ነገር አግኝተው አደሩ፡፡ ራእዩስ እንዴት ነው ቢሉ ኢያቄም ‹‹ሰባቱ ሰማያት እንደ መጋረጃ ተገልጠው ከላይኛው ሰማይ ነጭ ወፍ ወርዶ በራሴ ላይ ሲቀመጥ አየሁ›› አላት፡፡ ‹‹ወፍ›› የተባለው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፤ ነጭነቱ ንጽሐ ባህሪው ነው፤ ‹‹ከላይኛው ሰማይ ነጭ ወፍ ወርዶ በራሴ ላይ ሲቀመጥ አየሁ›› ማለቱ የኢያቄምን (የሰውን) ባህርይ ባህርይ እንዳደረገው ዕወቅ ሲል ነው፡፡ ሰባቱ ሰማያት የተባሉ የጌታችን ልዩ ልዩ ባሕርይው ምልአቱ ስፍሃቱ ርቀቱ ልእልናው ናቸው፡፡ ቅድስት ሐናም ‹‹እኔም ደግሞ አየሁ እንጂ›› አለችው፡፡ ‹‹ምን አየሽ?›› ቢላት ‹‹ነጭ ርግብ መጥታ በራሴ ላይ ወርዳ በጆሮዬ ገብታ በማኅፀኔ ስትተኛ አየሁ›› አለችው፡፡ ‹‹ርግብ›› የተባለች እመቤታችን ድንግል ማርያም ናት፣ ነጭነቱ ንጽህናዋ ቅድስናዋ ድንግልናዋ ነው፡፡ ‹‹ነጭ ርግብ መጥታ በራሴ ላይ ተቀምጣ ከራሴ ወርዳ በጆሮዬ ገብታ በማኅፀኔ ስትተኛ አየሁ›› ማለቷ ብሥራተ ገብርኤልን በጆሮዋ ሰምታ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ጌታችንን መፀነሷን ነው፡፡ ይህንኑም ራእይ ያዩት ሐምሌ 30 ዕለት ነው፡፡ እነርሱም እንዲህ ያለ ራእይ ካየን ነገር ካገኘን ብለው ዕለቱን በሩካቤ ሥጋ አልተገናኙም ይልቁንም ፈቃደ እግዚአብሔር ቢሆን ብለው አዳምንና ሔዋንን ‹‹‹ብዙ ተባዙ ምድርንም ምሉአት› ብሎ ያበሰረ አምላክ ለእኛስ ይልክልን የለምን!›› ብለው ዕለቱን አልጋ ምንጣፍ ለይተው እስከ ሰባት ቀን ድረስ ለየብቻቸው ሰነበቱ፡፡ ነሐሴ በባተ በሰባተኛው ቀን ‹‹ከሰው የበለጠች ከመላእክት የከበረች ደግ ፍጥረት ትወልዳላችሁና ዛሬ በሩካቤ ሥጋ ተገናኙ ብሎሏችኋል ጌታ›› ብሎ መልአኩ ለሐና ነገራት፡፡ በፈቃደ እግዚአብሔር በብሥራተ መልአክ እመቤታችን እግዝእትነ ማርያም ተፀነሰች፡፡
እግዚአብሔር አምላክ አብርሃምንና ሳራን የተመለከተ አምላክ በኢያቄምና ሃና አማካኝነት ለዓለም ድኅነት ምክንያት የሆነችውንና ዓለም ሳይፈጠር በአምላክ ልቦና ታስባ ትኖር የነበረች የተነገረላት ትንቢት ሊፈጸም የአባት የእናቷ የቅድመ አያቶቿ ራእይ ሊተረጎም ጌታ የፈቀደበት ጊዜ ሲደርስ እመቤታችን እግዝእትነ ማርያም እሁድ እለት ነሐሴ 7 ቀን በ16 ዓ.ዓ ተፀነሰች፡፡
እመቤታችን ከተፀነሰች በኋላ አይሁድ ቀንተው ተነሱባቸው፡፡ ቅናቱ እንዴት ነው ቢሉ ሳሚናስ የሚባል የጦሊቅ ልጅ ከኤዶቅ ከአጎቱ ቤት ሄዶ ሞተ፡፡ እነርሱም እንቀብራለን ብለው ባልጋ ይዘው ሲሄዱ ከመንገድ አሳረፉት፡፡ ቅድስት ሐናም የአጎቷ ልጅ ነበርና ለማልቀስ ብትደርስ ዘመዶቿ ሁሉ ተሰብስበው ሲላቀሱ ቆዩአት፤ እርሷም አብራ እየዞረች ስታለቅስ ጥላዋ ቢያርፍበት መግነዝ ፍቱልኝ ሳይል ብድግ ብሎ ተነሥቶ ‹‹ስብሃት ለኪ ማርያም እሙ ለፀሐየ ጽድቅ ለአብ ሙሽራው ለወልድ ወላዲቱ ለመንፈስ ቅዱስ ጽርሃ ቤቱ ተፈስሂ ደስ ይበልሽ" ብሎ ሰገደላት፡፡ አይሁድም ይህ ተአምር ሲደረግ ከዚያው ነበሩና ‹‹ምነው ሳሚናስ ምን አየህ? ምን ትላለህ?›› ቢሉት እርሱም ‹‹ከዚህች ከሐና ማኅፀን የምትወለደው ሕፃን ‹ሰማይን ምድርን አየርን የፈጠረ አምላክን ትወልዳለች› እያሉ መላእክት ሁሉ ሲያመሰግኗት ሰማሁ›› አላቸው፡፡ ዳግመኛም ‹‹እኔንም ያነሣችኝ የፈወሰችኝ ያዳነችኝ እርሷ ናት›› አላቸው፡፡ አይሁድም ‹‹በል ተወው ሰማንህ›› ብለው ቅናት ጀመሩ፡፡ ቅድስት ሐና በእርጅናዋ ጊዜ መፀነሷን የተመለከቱ ዘመዶቿና ያገሯ ሰዎች ተገርመው እየመጡ ይጠይቋት ነበር፡፡ እመቤታችን ማርያም በፅን
ለአባ ሕርያቆስ ፤ለቅዱስ ኤፍሬም ፤ለቅዱስ ያሬድ ፤ ለአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ የተገለጸች ዕመቤታችን እኛንም በበረከት እና በረድኤት ትጎብኘን ፤ ከልጅዋ ከወዳጅዋ ከመድኃኔዓለም ዘንድ ታማልደን፤ ሃገራችንን ኢትዮጵያ ከጥፋት፣ ቤተክርስቲያንን ከመናፍቃን፣ ህዝቦቿን ከስደት ትጠብቅልን።
ጾሙን ጾመ ሥርየት፤ ጾመ መድኃኒት ያድርግልን- አሜን ፡፡
ልመናዋ ክብሯ የልጅዋም ቸርነት ከኹላቸን ጋራ ለዘላለም ጸንቶ ይኑር አሜን፡፡
ጸሎታ ለማርያም ወስእለታ ለሕዝበ ክርስትያን ይዕቀቦም እመዓተ ወልዳ።
ጸሎታ ለማርያም ወስእለታ ለሀገሪትነ ኢትዮጵያ ይዕቀባ እመዓተ ወልዳ።
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
የእሑድ ውዳሴ ማርያም ትርጓሜ
በዚህ ዕለት እመቤታችን ከወትሮው ይልቅ ቀደም ብላ መጥታለች፡፡ “ዛቲ ዕለት ተዓቢ እምኩሎን ዕለታት፤ ወውዳሲያቲሃኒ የዓብያ እምኵሉ ውዳሴያት - ከዕለታት ኹሉ ይህቺ ዕለት ታላቅ ናት፤ ከውዳሲያቱም ኹሉ የዚች ዕለት ውዳሴ ታላቅ ነው” አለችውና ባረከችው፡፡ እርሱም በቤተ መቅደስ ባሉ ንዋያት ማለትም፡- በመሶበ ወርቅ፣ በተቅዋመ ወርቅ፣ በማዕጠንተ ወርቅ፣ በበትረ አሮን እየመሰለ ሲያመሰግናት አድሯል፡፡
፩. ተሰመይኪ ፍቅርተ ኦ ቡርክት እምእንስት አንቲ ውእቱ ዳግሚት ቀመር እንተ ተሰመይ ቅድስተ ቅዱሳን ወዉስቴታ ጽላተ ኪዳን። ፲ቱ ቃላት እለ ተጽሕፍ በአፃብዒሁ ለእግዚአብሔር ቀዲሙ ዜነወነ በየዉጣ እንተ ይእቲ ቀዳሜ ስሙ ለመድኃኒነ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘተሰብአ እምኔኪ ዘእንበለ ውላጤ። ወኮነ ዓራቄ ለሐዲስ ኪዳን። በውኂዘ ደሙ ቅዱስ አንጽሐሙ ለማሃይማን ወለሕዝብ ዝጹሐን። ሰአሊ ለነ ቅድስት።
ንዕድ ክብርት ሆይ! ከሴቶች ተለይተሽ የሥላሴ ባለሟል ተባልሽ፡፡ ከተለዩ የተለየሽ፣ ከከበሩ የከበርሽ፣ ቅዱሳን ኪሩቤል የተሣሉብሽ፣ ቅዱሳን ካህናት የሚያመሰግኑሽ ኹለተኛ ክፍል አንቺ ነሽ /ዘጸ.፳፮፡፩-፴/፡፡
ሕግ የተጻፈባት ጽላት ያለብሽ የምትባዪ አንቺ ነሽ /ዘጸ.፴፪፡፲፭-፲፱/፡፡ ኪዳንም ያልኹት በእግዚአብሔር ጣቶች የተጻፉ (በግብር አምላካዊ የተገኙ) ዐሥሩ ቃላት ናቸው፡፡ ዐሥርቱ ቃላትን በጽላቱ ጽፎ እንዳኖረ ኹሉ ዋሕድ ቃለ እግዚአብሔርም በአፃብዐ መንፈስ ቅዱስ (ያለ ወንድ ዘር፣ በግብረ መንፈስ ቅዱስ) በማኅፀንሽ እንዲቀረጽ ኾኗልና የሙሴ ጽላት አንቺ ነሽ /ቅዳ.ማር. ቁ.፴፫/፡፡ ዐጤ ዘርዐ ያዕቆብም በነገረ ማርያም መጽሐፉ፡- “… ወማኅፀናሰ ለማርያም ድንግል በክልኤ ይትሜሰል በጽላት ዘተጽሕፈ ውስቴታ ዐሠርተ ቃላት፡፡ ወዐሠርተ ቃላት ቀዳሜ ስሙ ለወልዳ ውእቱ ዘውእቱ የውጣ ዘተሰምየ በኈልቄ ዐሠርተ ቃላት - … በኹለት ወገን ድንግል የምትኾን የማርያም ማኅፀንስ ዐሥሩ ቃላት በውስጧ በተጻፈ ጽላት ይመሰላል፡፡ ዐሥሩ ቃላትም የልጇ የኢየሱስ ክርስቶስ የመዠመርያ ስሙ ነው፤ ያውም የውጣ በዐሥሩ ቃላት የተጠራ ነው” ብሏል /ነገረ ማርያም በብሉይ ኪዳን፣ ክፍል ፩፣ ገጽ ፻፳፰፣ በመጋቤ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ/፡፡
ከአንቺ ሳይለወጥ ሰው ኾነን፡፡ ለኦሪት ሳይኾን ለወንጌል ሊቀ ካህናት ኾነን፡፡ ለምድረ ርስት ሳይኾን ለመንግሥተ ሰማያት አስታራቂ ኾነን፡፡ ሐዋርያው ጳውሎስ፡- “በውድ ልጁም፥ እንደ ጸጋው ባለ ጠግነት መጠን፥ በደሙ የተደረገ ቤዛነታችንን አገኘን፤ እርሱም የበደላችን ስርየት ነው” እንዲል በከበረ ደሙ ፈሳሽነት በዓለመ ሥጋ በዓለመ ነፍስ ያሉትን አዳናቸው /ኤፌ.፩፡፯/፡፡ ሊቁ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅም የኤፌሶንን መልእት በተረጐመበት በአንደኛው ድርሳኑ ላይ፡- “ከእግዚአብሔር ዘንድ ያገኘነው ሥርየተ ኃጢአት በርግጥ ታላቅ ነው፡፡ ተቀዳሚ ተከታይ በሌለው በልጁ ደም መኾኑ ግን ከምንም በላይ ታላቅ ነው” በማለት የእግዚአብሔር ከኅሊናት የሚያልፈውን የማዳን ምሥጢር (ፍቅር) በመደነቅ ተናግሯል፡፡
በከበረ ደሙ ፈሳሽነት በዓለመ ሥጋ በዓለመ ነፍስ ያሉትን ካዳነ ልጅሽ ጽንዕት በድንግልና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሣን ለምኚልን፡፡
ታቦት በወርቅ ልቡጥ እምኩለሄ ዘግቡር እምዕፅ ዘኢይትቅዝ ይትሜሰል ለነ ዘእግዚአብሔር ቃለ ዘኮነ ሰብአ ዘእንበለ ፍልጠት ወኢዉላጤ፡ መለኮት ንጹሕ ዘአልቦ ሙስና ዘዕሩይ ምስለ አብ ወቦቱ አብሠራ ለንጽሕት፡ ዘእንበለ ዘርእ ኮነ ከማነ በኪነ ጥበቡ ቅዱስ፡ ዘተሰብአ እምነኪ ዘንበለ ርኩስ፡ ደመረ መለኮቶ፡ ሰአሊ ለነ ቅድስት።
፪. ኹል ጊዜ ንጽሕት የምትኾኚ አምላክን የወለድሽ እመቤታችን ሆይ! ስለዚህ ነገር ኹላችን እናከብርሻለን፤ እናገንሻለንም፡፡ ሰውን ከሚወድ ሰው ከሚወደው ከርሱ ይቅርታን እናገኝ ዘንድ ኹል ጊዜ ዓይነ ልቦናችንን ወዳንቺ እንሰቅላለን፡፡ ሸምሸር ሰጢን ከሚባል ከማይነቅዝ (በአምልኮተ ጣዖት ከማይለወጥ) እንጨት የተቀረጸ በአፍአ በውስጥ በወርቅ የተለበጠ ታቦት አካላዊ ቃልን ይመስልልናል /ዘጸ.፳፭፡፱-፳/፡፡ ይህ ንጹሕ የሚኾን፣ መለወጥ የሌለበት እርሱ ባለመለወጡ አለመለወጧን ነገራት፤ ከአብ ዕሪና ባለመለየቱም አለማለየቷን ነገራት (አምላክ ወሰብእ ኾኖ እርሷም እም ወድንግል መኾኗን ነገራት)፡፡ ከጥበብ በሚበልጥ ጥበብም ዘር ምክንያት ሳይኾነው እንደ እኛ ሰው ኾነ፡፡ አበው፡- “ዓለሙን ከፈጠረበት ጥበብ ይልቅ ሰው ኾኖ ዓለሙን ያዳነበት ጥበብ ይበልጣል” የሚሉትም ስለዚሁ ነው፡፡ አደፍ ጉድፍ ሳያገኝሽ መለኮቱን አዋሕዶ ከሥጋሽ ሥጋ ከነፍስሽ ነፍስ ነሥቶ ሰው ኾነ፡፡ መለኮቱን አዋሕዶ ሰው ከኾነ ልጅሽ ጽንዕት በድንግልና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሣን ለምኝልን፡፡
መቅደስ ዘይኬልልዋ ኪሩቤል እለ ሥዑላን በሥዕለ እግዚአብሔር፡ ቃል ዘተሰብአ እምኔኪ ዘእንበለ ዉላጤ ኮነ ሠራዮ ኃጥአትነ ወደ ምሳሴ አበሳነ፡ ሰአሊ ለነ ቅድስት።
፫. እግዚአብሔር በፈጠራቸው በኪሩቤል አምሳል፤ ሙሴ የሣላቸው ኪሩቤል የሚጋርዱሽ መቅደሰ ሙሴ አንቺ ነሽ፡፡ አንድም እግዚአብሔር በፈጠራቸው በኪሩቤል አምሳል፣ ሰሎሞን የሣላቸው ኪሩቤል የሚጋርዱሽ መቅደሰ ሰሎሞን አንቺ ነሽ፡፡ ጌታ በማኅፀንሽ ያደረብሽ አማናዊቷ መቅደስ አንቺ ነሽ፡፡ ሳይለወጥ ካንቺ ሰው የኾነው አካላዊ ቃል በውስጥ በአፍአ በነፍስ በሥጋ ኃጢአታችንን የሚያስተሠርይልን ኾነ፡፡ ኃጢአታችንን ከሚያስተሠርይልን ልጅሽ ጽንዕት በድንግልና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሣን ለምኝልን፡፡
አንቲ ዉእቱ መሶበ ወርቅ ንጹሕ እንተ ዉስቴታ መና ኅቡእ፡ ኅብስት ዘወረደ እምሰማያት ወሀቤ ሕይወት ለኩሉ ዓለም፡ ሰአሊ ለነ ቅድስት።
፬. መና ያለብሽ መሶበ ወርቅ አንቺ ነሽ /ዘጸ.፲፮፡፴፫-፴፬/፡፡ ይኸውም መና የተባለው ከሰማይ የወረደና ፱ ወር ከ፭ ቀን በማኅፀንሽ የተሸከምሽው ነው፡፡ እርሱም “አበዊክሙሰ መና በልዑ በገዳም ወሞቱ - አባቶቻችሁ በምድረ በዳ መና በሉ፤ ሞቱም” እንዳለው ያይደለ፤ ይልቁንም ለሰው ኹሉ ሕይወት የሚያድል ኅብስት ነው /ዮሐ.፮፡፶/፡፡ ሊቁ ቅዱስ ያሬድም በአንቀጸ ብርሃን ላይ፡- “አስተማሰልናኪ ቅድስት ወብፅዕት ስብሕት ወቡርክት ክብርት ወልዕልት በመሶበ ወርቅ ዘውስቴታ ኅብስተ ሕይወት ዘወረደ እምሰማያት ወሃቤ ሕይወት ለኵሉ ዘየአምን ኪያሁ ወይበልዕ እምኔሁ በአሚን ወበልብ ሥሙር ምስለ እለ በየማኑ - የተለየሽና ደግ የኾንሽ የተመሰገንሽና የተባረክሽ የከበርሽና ከፍ ከፍ ያልሽ ሆይ! የሕይወት ኅብስት ባለበት በወርቅ መሶብ መሰልንሽ፡፡ የሕይወት ኅብስትም በቀኙ ካሉ ጻድቃን ጋር እርሱን ለሚያምን በሃይማኖትና ፈቃደኛ በኾነ ልብ ከእርሱ ለሚበላም ኹሉ ሕይወትን የሚሰጥ ከሰማይ የወረደ ነው” ብሏል /ቁ.፯/፡፡ ዳግመኛም አባ ጊዮርጊሥ ዘጋሥጫ፡- ኦ መሶብ ቤተ ልሔማዊት ዘወለደቶ ለኅብስተ ሰማይ ዘኢያብቌልዎ ዝናማት ወዘኢሐፀንዎ አየራት - ዝናማት ያላበቀሉትን አየራት ያላሳደጉትን የሰማዩን እንጀራ የወለድሽው ቤተ ልሔማዊት መሶብ ሆይ” በማለት መስክሯል /አርጋኖን ዘረቡዕ/፡፡ ከአባቶች አንዱም፡- “ድንግል ሆይ! በእውነቱ አንቺ ከታላላቅ ይልቅ ታላቅ ነሽ፡፡ ማኅደረ ቃለ አብ ሆይ! አንቺን ሊተካከል የሚችል ታላቅ ማን ነው? ድንግል ሆይ! ከየትኛው ፍጥረት ጋር አወዳድርሻለሁ? አንቺ ቀድሞ በወርቅ ካጌጠችው የሕጉ ታቦት ይልቅ በንጽሕና ያጌጥሽ ታላቅ ነሽ! እውነተኛውን መና የተሸከምሽ
፮. እርሱን ከወለድሽ በኋላ ማኅተመ ድንግልናሽ ሳይለወጥ ኑረሻልና የክርስቶስ እናቱ ተባልሽ፡፡ ድንቅ በሚያሰኝ ተዋሕዶ አማኑኤልን ወልደሸዋልና ባለመለወጥ አጸናሽ፡፡ ታላቁ የቤተ ክርስቲያን መምህር ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ለማንም ሴት ያልተሰጠ ለድንግል ማርያም ብቻ የተሰጠ ድንግልና ከእናትነት ጋር አስተባብራ ስለ መገኘቷ ሲገልጥ “ወሰቦሂ ወለደቶ ዐቀበ ድንግልና፣ ዘእንበለ ርኩስ ከመ በፀንሳ መንክር ትኩን መራሂተ ለሃይማኖት ዐባይ - ከድንግል ተወለደ፤ በወለደችውም ጊዜ ድንግልናዋ ያለመለወጥ አጸና፡፡ ድንቅ የሚኾን ፅንሷ ለደገኛው ሃይማኖት መሪ ትኾን ዘንድ” በማለት ቅድስት ድንግል ማርያም አምላክን ስትወልድው ማኅተመ ድንግልናዋ እንዳልተለወጠ ጌታም ሰው ሲኾን ባሕርየ መለኮቱ ላለመለወጡ፣ እርሷ ድንግል ወእም (ድንግልም እናትም) ስትባል እንደምትኖር አካላዊ ቃል ክርስቶስም አምላክ ወሰብእ (ሰው የኾነ አምላክ) ሲባል የሚኖር የመኾኑን የተዋሕዶ ልዩ ምሥጢርን ያወቅንባት የተረዳንባት እርሷ ብቻ መኾኗን አስተምሯል /ሃይ.አበ.፷፮፡፴፪/፡፡ እንዲህ ካለ ልጅሽ ፅንዕት በድንግልና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሣን ለምኚልን፡፡
፯. ከምድር እስከ ሰማይ ደርሳ፣ በላይዋ ዙፋን ተነጽፎባት፣ በዚያ ላይ ንጉሥ ተቀምጦባት፣ መላእክት ሲወጡባት ሲወርዱባት ያዕቆብ በፍኖት ሎዛ ያያት የወርቅ መሰላል አንቺ ነሽ /ዘፍ.፳፰፡፲-፳፪/፡፡ ሰው ከመኾኑ አስቀድሞ ሰውም ከኾነ በኋላ የማይመረመር እርሱን በተፈትሖ በማይታወቅ በማኅፀንሽ ችለሸዋልና እኛን ስለማዳን ከአንቺ ሰው ከኾነ ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ዘንድ ሰዋስው (አማላጅ) ኾንሽን፡፡ እኛን ስለማዳን ከአንቺ ሰው ከኾነ ልጅሽ ፅንዕት በድንግልና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሣን ለምኚልን፡፡
፰. ጽርሐ ንጽሕት ሆይ! እነሆ ጌታ የፈጠረውን ዓለም ኹሉ በቸርነቱ ብዛት ያድን ዘንድ ከአንቺ ተወለደ፡፡ ቸር ሰው ወዳጅ ነውና በአፍአ በውስጥ እናመስግነው፡፡ ቸር ሰው ወዳጅ ከኾነ ልጅሽ ፅንዕት በድንግልና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሣን ለምኚልን፡፡
፱. አደፍ ጉድፍ የሌለብሽ ድንግል ምልዕተ ክብር ሆይ! ደስ ይበልሽ፡፡ ከእናትሽ ማኅፀን ጀምሮ መንፈስ ቅዱስ ጠብቆሻልና የዓለም ኹሉ መክበሪያ ንጽሕት ጽዋዕ ነሽ (ከሥላሴ ለምንጠጣው ክብር ምክንያት አንቺ ነሽ)፡፡
እንደ ደብተራ ኦሪቷ ማለትም ሙሴና አሮን በቀዳማይ ሰዓተ ሌሊት አብርተው በቀዳማይ ሰዓተ መዓልት እንደሚያጠፏት ፋና ያይደለሽ የማትጠፊ ፋና ነሽ /ዘጸ.፳፭፡፴፩-፵/፡፡
እንደ ቀደመችው የኦሪት ቤተ መቅደስ ያይደለሽ የማትፈርሺ መቅደስ ነሽ /፩ኛ ነገ.፯፡፵፰-፶/፡፡ ሊቁ አባ ጊዮርጊሥ ዘጋሥጫም፡- “አንቲ ውእቱ መቅደስ ዘሐነጸ ሰሎሞን ወአስቀጸላ በሜላትሮን ወለበጠ ዳቤራ በውሳጥያተ መቅደስ፤ … - ሰሎሞን ያሠራት እንደ ዝናር እንደ ዐምድ ባለ ወርቅ የጠፈሯን ዙርያ ያስጌጣት፤ በመቅደስ ውስጥ ያለቺውን ቅድስተ ቅዱሳንዋን ዐውደ ምሕረቷን ግድግዳዋን በጥሩ ወርቅ ያስጌጣት፤ ቁመቱ ሃያ ክንድ፤ ክንፉ ዐሥራ አምስት ክንድ የሚኾን ኪሩብን በውስጧ ያሣለባት ቤተ መቅደስ አንቺ ነሽ” በማለት በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ የጸናች እመቤታችን ሰሎሞን ባሠራት የወርቅ ቤተ መቅደስ መስሎ ኹለንተናዋ በንጽሕና በቅድስና ያጌጠች የተዋበች መኾኗን አስተምሯል /አርጋኖን ዘዐርብ/፡፡ ዳሩ ግን እመቤታችን በንጽሕናዋ በቅድስናዋ በሰሎሞን ቤተ መቅደስ ብትመሰልም ሊቁ (ኤፍሬም) እንዳለው ክብሯ የላቀ ነው፤ የሕያው እግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ናትና የማትፈርስ መቅደስ ናት /መዝ.፹፮፡፩-፭/፡፡
የማትለወጥ የቅዱሳን ሃይማኖታቸው (ቅዱሳን የሚያምኑበት ክርስቶስን የወለድሽላቸው አንቺ) ነሽ፡፡ ድንግል ሆይ! በውስጥ በአፍአ በነፍስ በሥጋ ይቅር ይለን ዘንድ፣ ኃጢአታችንን ያስተሠርይልን ዘንድ ከልጅሽ ዘንድ አማልጅን፡፡ ኃጢአታችንን ከሚያስተሠርይልን ልጅሽ ፅንዕት በድንግልና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሣን ለምኚልን፡፡
አነሣሥቶ ላስጀመረን አስጀምሮ ላስፈጸመን ለእግዚአብሔር ክብር ምስጋና ይግባው አሜን!!!
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
የቅዳሜ ውዳሴ ማርያም ትርጓሜ
@Ethiopian_Orthodox
በዚህም ቀን እመቤታችን ትመጣለች፤ የብርሃን ድባብ ይዘረጋል፤ የብርሃን ዙፋን ይነጠፋል፡፡ ከዚያ ላይ ኹናም ሊቁን ባርካው ምስጋናዉን ጀምሯል፡፡
@Ethiopian_Orthodox
የማይቻለውን ቻልሽ፡፡ ምንም ምን የሚወስነው የሌለውን ወሰንሽ፡፡ ምልዕተ ክብር ሆይ! በክብረ ወሊድ ላይ ክብረ ድንግልናን ደርበሽ ብትገኚ ላንቺ የተሰጠሸ ክብር ፍጹም ነው፡፡ የአካላዊ ቃል ማደሪያ ኹነሻልና፣ ምዕመናንን ሰብስባ የያዘቻቸውና ለሥላሴ ሰጊድን የምታስተምሪላቸው (አንድነት ሦስትነት በጐላ በተረዳ ነገር የታወቀብሽ) ጴጥሮስ በናሕሰ ኢዮጴ ያያት የቤተ ወንጌል ሰፊ መጋጃ አንቺ ነሽ /ሐዋ.፲፡፱-፲፮/፡፡ ኢትዮጵያዊው ቄርሎስ አባ ጊዮርጊሥ ዘጋሥጫም፡- “ሰላም ለኪ መንጦላዕተ ገርዜን - የበፍታ መጋረጃ ሰላምታ ለአንቺ ይገባል” ብሏል /የአባ ጊዮርጊሥ የሰባቱ ጊዜያት የሃይማኖትና የጸሎት መጽሐፍ ትርጓሜ በመጋቤ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ፣ ገጽ ፻፷/፡፡
ሙሴ ያየውን ዓምደ እሳት የተሸከምሽ አንቺ ነሽ /ዘጸ.፲፫፡፳፪/፡፡ ይኸውም ዓምደ እሳት ያልኩት ሰው ኹኖ በማኅፀንሽ ያደረው ወልደ እግዚአብሔር ነው፡፡ ሰማይና ምድር ለፈጠረ ለእርሱ ማደሪያ ኾንሽው፡፡ ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን በማኅፀንሽ ቻልሽው፡፡ ሰማይና ምድር የማይወስኑትን ለመወሰን የታመንሽ ነሽ፡፡ ከምድር ወደ ሰማይ ለመውጣት መሰላል ኾንሽ፡፡ በመሰላል የላዩ ወደ ታች ይወርዱበታል፤ የታቹ ወደ ላይ ይወጡበታል፡፡ የላዩ ወደታች እንዲወርዱበት መለኮትም ከአንቺ ትስብእትን ተዋሕዷል፤ የታቹ ወደ ላይ እንዲወጡበትም ትስብእት ከመለኮት ጋራ ለመዋሐዱ ምክንያት ኾነሻል፡፡ ድንግል ሆይ! ክብርሽ ከፀሐይ ብርሃን ይበልጣል፡፡ ቅዱሳን፣ ሰብአ ሰገል /ማቴ.፪፡፪/፣ እነ በለዓም /ዘኅ.፳፬፡፲፯/፣ ሐዋርያት ደስ ብሏቸው ያዩት ኮከብ ካንቺ የተወለደ ምሥራቅ አንቺ ነሽ፡፡ ይኸውም በፃር፣ በጋር፣ በምጥ ትወልድ ዘንድ በሔዋን የፈረደባት ነው፡፡ አንቺ ግን ምልዕተ ክብር ሆይ! ደስ ይበልሽ የሚል ድምፅ ሰማሽ /ሉቃ.፩፡፳፰/፡፡ ሔዋን “በሕማም ለዲ” የሚል ድምፅ ሰምታ /ዘፍ.፫፡፲፮/ ምክንያተ ሞት ቃየልን አስገኘች /ዘፍ.፬፡፩-፰/፡፡ አንቺ ግን “ተፈሥሒ ኦ ምልዕተ ጸጋ” የሚል ደምፅ ሰምተሸ ፍጥረትን ኹሉ የሚገዛ ንጉሥን ወለድሽልን /ሉቃ.፩፡፴፩/፡፡ ሄሬኔዎስ የተባለ ሊቅም ይህንን አንቀጽ በረጐመበት ድርሳኑ እንዲህ ብሏል፡- “እነሆ ጌታ የራሱ ወደኾኑት በግልጥ (በለቢሰ ሥጋ) መጣ፡፡ ትእዛዙን ተላልፎ በዕፅ የሞተውን አዳም በዕፅ (በመስቀል) ላይ ታዝዞና ካሣውን ከፍሎ፣ ወደ ጥንተ ተፈጥሮው ይመልሰው ዘንድ በራሱ ጥበብ ከፍጥረቱ ተወለደ፡፡ ለአንድ ወንድ የታጨችው ድንግል በምክረ ከይሲ ያመጣችውን ያለመታዘዝ ኃይል የእውነት መልአክ ለአንድ ወንድ ለታጨችው ድንግል ባበሠራት ጊዜ ፈራረሰ፡፡ ቀዳማይቱ ሔዋን ከእግዚአብሔር እንድትርቅና ቃሉን እንድትቃወም በክፉ መልአክ እንደተታለለች ኹሉ፣ ዳግማይቱ ሔዋን ቅድስት ድንግል ማርያምም ደጉ መልአክ ይዞት የመጣው መልካሙን ዜና እንድትቀበለውና እግዚአብሔርን በከዊነ ቃሉ እንደምትወልደው አመነች፡፡ ቀዳማይቱ ሔዋን እግዚአብሔርን እንዳትታዘዘው ክፉ መልአክ አታለላት፤ ወደቀችም፡፡ ዳግማይቱ ሔዋን ቅድስት ድንግል ማርያም ግን እግዚአብሔርን እንድትታዘዝ ቅዱስ መልአክ አሳመናት፤ እርሷም ሔዋንን ረዳቻት፡፡ ነገደ አዳም በአንዲት ድንግል አለመታዘዝ ምክንያት ሞት ተፈረደበት፣ ኾኖም በሌላይቱ ድንግል መታዘዝ ምክንያት ዳነ፡፡ የፍጥረት በኵር የሚኾን አዳም የበደለው በደል የእግዚአብሔር በኵር በሚኾን በወልደ እግዚአብሔር መቀጣት ተፈወሰ፡፡ የእባቡ ተንኰል በርግቡ የዋኅነት ተዋጠ፤ ለሞት ሲዳርገን የነበረው ቁራኝነትም ተሰበረ፡፡”
ሰው ኾኖ ያዳነን መሐሪ ነው፤ ሰው ወዳጅ ነው፡፡ ድንግል ሆይ! በእንተዝ ንዌድስኪ - ስለዚህ ነገር መልአኩ “ቡርክት አንቲ እም አንስት” ብሎ እንዳመሰገነሽ እኛም “ተፈሥሒ ኦ ምልዕተ ጸጋ እግዚአብሔር ምስሌኪ- እግዚአብሔር ከሥጋሽ ሥጋ ከነፍስሽ ነፍሽ ነስቶ ካንቺ ጋራ አንድ ባሕርይ ኹኗልና (ተፈሥሒ) ደስ ይበልሽ” ብለን እናመሰግንሻለን፡፡ እንዲህ ካለ ልጅሽ ጽንዕት በድንግልና እመቤታቸን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሣን ለምኚልን፡፡
ይኽን ሲጨርስ በያዘችው መስቀለ ብርሃን ባርካው ታርጋለች፡፡ እርሱም እጅ ነሥቶ ይቀራል፡፡
አነሣሥቶ ላስጀመረን አስጀምሮ ላስፈጸመን ለእግዚአብሔር ክብር ምስጋና ይግባው አሜን፡፡
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
፮. ድንግል ማርያም በቤተ መቅደስ አሰምታ ትናገር ነበር፡፡ አረጋዊው ዮሴፍ በግብረ መንፈስ ቅዱስ እንደ ፀነሰች ሳያውቅ “ኦ ወለተ እስራኤል መኑ ቀረፀ አክናፈ ድንግልናኪ” ቢላት “እኔስ ምልዕተ ክብር ሆይ! እግዚአብሔር ከሥጋሽ ሥጋ ከነፍሽ ነፍስ ነሥቶ አንድ አካል ይኾናል ብሎ መልአኩ አክብሮ ከነገረኝ ነገር በቀር ምን ምን የማውቀው እንደ ሌለኝ እግዚአብሔር ያውቃል” ብላ አሰምታ ተናገረች፡፡ ሊቁ ቅዱስ ኤፍሬም “ዲያተሳሮን” በተባለ የወንጌል ትርጓሜ መጽሐፉ የእመቤታችንና የዮሴፍ ግንኝነት እንዲህ በማለት በጥልቀት ተንትኖታል፡- “የመሲሑ ልደት እንዲህ ነበር፡፡ እናቱ ማርያም ለዮሴፍ በታጨች ጊዜ ሳይገናኙ በግብረ መንፈስ ቅዱስ ፀንሳ ተገኘች /ማቴ.፩፡፲፰/፡፡ ወንጌላዊው ቅዱስ ማቴዎስ ይህንን ያለ ምክንያት አይናገረውም፡፡ አሕዛብ አማልክቶቻቸው እጅግ አሳፋሪ በኾነ ግንኝነት እኛ ከምናውቀው ተፈጥሮ ውጪ ልጅ ይወልዳሉ ብለው ስለሚያስቡ እንጂ፡፡ በመኾኑም እነዚህ አሕዛብ እንደሚያስቡት እመቤታችን ፀንሳ ተገኘች ተብሎ እንዳይታሰብ ወንጌላዊው “ሳይገናኙ በግብረ መንፈስ ቅዱስ ፀንሳ ተገኘች” አለ፡፡ የተወለደው በወንድ ዘር አይደለም፡፡ ማኅተመ ድንግናዋን ሳይለውጥ ገባ፤ አከበራት፤ ነፍስና ሥጋም ከእርሷ ነሥቶ ተዋሐደ፡፡
አስቀድማ ለወንድ መታጨቷ፣ ባል (ጠባቂ) እንዳላት መደረጓ፣ ቀጥሎም መፅነሷ ልጇ ወዳጇ በዳዊት በትረ ሥልጣን ስለሚገባና የዳዊት ሥልጣንን የሚይዝ ደግሞም በእናቱ ሳይኾን በአባቱ ስም ስለሚጠራ ነው /ሉቃ.፩፡፴፪/፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ክፉዎች የፀነሰችው በሴሰኝነት ነው ብለው እንዳያስቡ ነው፡፡ እጅግ ጻድቅ ለኾነው ለዮሴፍ የመታጨቷ ምክንያት ይህ ነበር፡፡ ዮሴፍ እመቤታችንን ፀንሳ ባያት ጊዜ እስክትወልድ ድረስ ተከባከባት፡፡ ከእርሷ ጋር በቤቱ ኖረ እንጂ አላባረራትም፡፡ ከማንምና ከምንም አስቀድሞ ከእርሷ የተፀነሰው በግብረ መንፈስ ቅዱስ እንጂ በዘርዐ ብእሲ እንዳልኾነ ምስክር ኾነ፡፡
እመቤታችንም ያለ ታራሽ ልጇን ወለደችው፡፡ ቀዳማይቱ ሔዋን አዳም ከማንም ጋር ሳይገናኝ እንደወለዳት አሁንም ዮሴፍና እመቤታችን በግብር ሳይተዋወቁ በግብረ መንፈስ ቅዱስ ወለደች፡፡ ሔዋን ነፍሰ ገዳዩን (ቃየልን) ወለደች፤ እመቤታችን ግን ወሀቤ ሕይወትን ወለደች፡፡ ቀዳማዪቷ ሔዋን የወንድሙን ደም የሚያፈስ ልጅን ወለደች፤ ዳግማዪቱ ሔዋን ግን ስለ ወንድሞቹ ደሙን የሚያፈስ ልጅን ወለደች፡፡ የቀዳማይቱ ሔዋን ልጅ (ቃየል) ምድር ተረግማ ኃይልዋን አልሰጥ ስላለችው ኰብላይና ተቅበዥባዥ ኾነ /ዘፍ.፬፡፩-፲፬/፤ የዳግማይቱ ሔዋን ልጅ ግን ያንን ርጋማን አስወገደው በመስቀል ላይም ጠርቆ አስወገደው /ቈላ.፪፡፲፬/፡፡ የእመቤታችን ፅንስ አዳምን ያለ ወንድ ዘር ከድንግል ምድር እንደተገኘ ዳግማዊ አዳምም ያለ ዘርዐ ብእሲ በድንግሊቱ ማኅፀን እንደተገኘ ያስተምረናል፡፡ ቀዳማዊ አዳም በበደለ ጊዜ ወደ እናቱ ማኅፀን (ወደ ምድር) ተመለሰ፤ ዳግመኛ ወደ እናቱ ማኅፀን ያልተመለሰው ዳግማዊ አዳም ግን ቀዳማዊውን እንደገና ከእናቱ ማኅፀን እንዲወለድ አደረገው፡፡
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከተራራማው ሀገር ወደ ቤቷ በሄደች በተመለሰች ጊዜ የፀነሰችው በግብረ መንፈስ ቅዱስ እንደኾነ ታስረዳው ነበር፤ ነገር ግን ከኅሊናት በላይ ስለኾነበት ነገሩ ረቀቀበት፡፡ ፊቷን ሲመለከታት ምንም ዓይነት የውሸት ምልክት አይታይባትም፤ ግን ደግሞ ሆዷ ገፍቷል፡፡ በመኾኑም ደግ ነውና ሊገልጥባት አልወደደም፡፡ ከዚሁ ጐን ለጐን ግን ከሌላ ወንድ ጋር ተገናኝታለች ብሎ ስላሰበ ወደ ቤቱ ሊወስዳት አልወደደም፡፡ በእነዚህ ኹለት ሐሳቦች እየተማታ ወደቤቱ ሊወስዳት እንደማይገባ ግን ደግሞ ነገሩንም ሊገልጥባት እንደማይገባ ወሰነ፡፡ ያን ጊዜ ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልአክ ለዮሴፍ በሕልም ታየው፡፡ በጣም በሚያደንቅ መንገድ መልአኩ “ኦ ዮሴፍ ወልደ ዳዊት - የዳዊት ልጅ ዮሴፍ ሆይ!” አለው፡፡ ይኸውም እግዚአብሔር ለቅድመ አያቱ ለዳዊት “እስመ እምፍሬ ከርሥከ አነብር ዲበ መንበርከ- ከባሕርይህ የተከፈለ ልጅህ ክርስቶስን በዙፋንህ አስቀምጣለሁ” ብሎ የማለለትን ቃል እንዲያስተውስ ነው /መዝ.፻፴፩፡፲፩/፡፡ መልአኩ ቀጠለ፤ እንዲህም አለው “ኢትፍራህ ነሢኦታ ለማርያም ፍኅርትከ እስመ ዘይትወለድ እምኔሃ እመንፈስ ቅዱስ ውእቱ - የዳዊት ልጅ ዮሴፍ ሆይ! ከካህናት እጅ እንደተቀበልህ ከእደ መንፈስ ቅዱስ መቀበልን አትፍራ፤ ከእርሷ የሚወለደው በግብረ መንፈስ ቅዱስ ነውና፡፡ ድንግል በድንግልና ፀንሳ በድንግልና እንድምትወልድ ከረቀቀብህ እነሆ “ናሁ ድንግል ትፀንስ ወትወልድ ወልደ” የሚለውን የነቢዩን ቃል አስታውስ /ኢሳ.፯፡፲፬/፡፡ ዳግመኛም ነቢዩ ዳንኤል “ተበትከ ዕብን ዓቢይ እምደብር ዘእንበለ እድ - ታላቅ ደንጊያ እጅ ሳይነካው ከተራራ ወረደ” ብሎ የተናገረውን ልብ በል /ዳን.፪፡፴፭/፡፡ ይህ የነቢዩ ዳንኤል ቃል ኢሳይያስ በአንድ ቦታ “ርእይዋ ለኰኩሕ ጽንዕት እንተ ወቀርክሙ ወአዘቅተ ዕምቅተ እንተ ከረይክሙ - ያለዘባችኋትን ጽኑ ዐለት እይዋት የቈፈራችሁትንም ጥልቅ ጕድጓድ አስተውሉ” ብሎ እንደተናገረው ያለ አይደለም ኢሳ.፶፩፡፩/፡፡ ምክንያቱም ኢሳይያስ የወንድና የሴትን ነገር አንሥቶ የተናገረ ሲኾን ነቢዩ ዳንኤል ግን “ዘእንበለ እድ - ያለ እጅ” ነው ያለው፡፡ ይኸውም ቀዳማዊ አዳም ለሔዋን አባቷም እናቷም እንደኾነ ኹሉ እመቤታችን ለጌታችን (በተዋሐደው ሥጋ) እናቱም አባቱም ነች፡፡
ዮሴፍ ጻድቅ ሰው ስለነበረ ነገሩን ሊገልጥባት አልወደደም፡፡ ደግነቱም (ጽድቁም) እንደ ሕጉ የኾነ ደግነት አይደለም፡፡ ሕጉ እንዲህ ያለ ነገርን ያደረገ ወንድ ወይም ሴት እስኪሞቱ ድረስ በድንጋይ ተወግሮ እንዲገደል ያዝዛልና /ዘዳ.፲፯፡፭፣፯ ፤ ዘዳ.፳፪፡፳፫-፳፬/፡፡ ዮሴፍ ግን በስዉር ሊተዋት (ሊለያት) አሰበ እንጂ ሊገልጥባት አላሰበም፡፡ ዮሴፍ ይህን የሚደርገው ነገሩ ረቅቆበት፣ ከሚያውቀው የተፈጥሮ ሂደትም ውጪ ስለኾነበት ነው፡፡ በመቀጠል የኾነው ኹሉ እግዚአብሔር እንዳደረገው ተገነዘበ፡፡ ነገር ግን እንዲህ ያለ ነገር አይቶም ሰምቶም ስለማያውቅ ግራ ተጋባ፡፡ በተቃራኒው ደግሞ እመቤታችንን ላለማመን ምንም የማይቻል ነበር፡፡ ምክንያም በጣም ብዙ አስረጂ ነገሮችን አስረድታዋለችና፡፡ የዘካርያስ ዲዳ መኾን፣ የኤልሳቤጥ መፀነስ፣ የመልአኩ ብሥራት፣ የብላቴናው ዮሐንስ በሐሴት መሞላትና መዝለል፣ የቀደሙ አበው ትንቢት እና ሌሎች ዮሴፍን ለማሳመን ድምጻቸውን ከፍ አድርገው ይነግሩት ነበር፡፡ በመኾኑም ነገሩን ሳይገልጥባት በስዉር ሊተዋት (ሊለያት) ወሰነ፡፡ እመቤታችን የፀነሰችው በግብረ መንፈስ ቅዱስ መኾኑን ቢያውቅ ኖሮ በስውር ሊተዋት ባላሰበ ነበር፡፡
@Ethiopian_Orthodox
፩. ከሴቶች ተለይተሸ መርገመ ሥጋ መርገመ ነፍስ ሌለብሽ በረከተ ሥጋ በረከተ ነፍስን እያማለድሽ የምታሰጭ ነሽ /ሉቃ.፩፡፳፰/፡፡ ቤዴ የተባለ ተርጓሜ መጻሕፍት ይህን አንቀጽ ሲተረጉመው፡- “የመጀመርያው የሰው ልጆች ስሕተት ከዲያብሎስ በእባብ አማካኝነት ወደ ሴት ተላከ፡፡ ሴቲቱም በትዕቢት መንፈስ ወደቀች፡፡ ዲያብሎስ በእባብ ገላ ተሰውሮ መጣና የመጀመርያዎቹ ወላጆቻችንን አታለላቸው፡፡ ኢመዋቲው ጸጋቸውን ገፈፈው፡፡ ስለኾነም ሞት በሴት ምክንያት ገብቷልና መድኃኒትም በሴት ምክንያት ይገባ ዘንድ ይገባው ነበር፡፡ ቀዳማይቱ ሔዋን ዲያብሎስ በእባብ ገላ ተሰውሮ አታለላት፡፡ ለሰውም ኹሉ የሞትን ጣዕም አቀመሰችው፡፡ ሌላይቱ ሔዋን ግን ከእግዚአብሔር ዘንድ በተላከ መልአክ የዓለም መድኃኒት የኾነው ክርስቶስን አስገኘች” በማለት እመቤታችን ከሴቶች ኹሉ የመለየቷን ምሥጢር በጥልቀት አስተምሯል፡፡
የማኅፀንሽም ፍሬ ኢየሱስ ክርስቶስ መርገመ ሥጋ መርገመ ነፍሰ የሌለበት በረከተ ሥጋ በረከተ ነፍስ የሚያድል የባሕርይ አምላክ ነው፡፡ የሚላን ሊቀ ጳጳስ የነበረውና አምብሮስ የተባለው ሊቅ ይህን አንቀጽ ሲተረጕም፡- “እመቤታችን አመነች እንጂ አልተጠራጠረችም፤ በመኾኑም የእምነቷን ፍሬ አገኘች፡፡ “ወብጽዕት አንቲ እንተ ተአምኒ ከመ ይከውን ቃለ ዘነገሩኪ እም ኀበ እግዚአብሔር - ከእግዚአብሔር አግኝተው የነገሩሽን ነገር እንዲደረግ የምታምኚ አንቺ ንዕድ ክብርት ነሽ” እንዲል /ሉቃ.፩፡፵፭/፡፡ እናንተ ከእግዚአብሔር አግኝተው የነገርዋችሁን ነገር እንዲደረግ የምታምኑም ንዑዳን ክቡራን ናችሁ፡፡ የሚያምኑ ነፍሳት አካላዊ ቃልን ይፀንሱታል፤ በግብራቸውም ይወልዱታል (ይገልጡታል)፡፡ እንግዲያውስ እግዚአብሔርን ከፍ ከፍ ታደርጉት ዘንድ እመቤታችንን ምሰልዋት፡፡ በፈጣሪያችሁ በመድኃኒታችሁ አምናችሁ ደስ ይላችሁ ዘንድ የእመቤታችንን ልቡና ገንዘብ አድርጉ /ሉቃ.፩፡፵፮-፵፯/፡፡ ምንም እንኳን ጌታችንን በሰውነቱ የምትወልደው (የወለደችው) እመቤታችን ብቻ ብትኾንም በእምነት በኵል ግን የኹሉም አማንያን ፍሬ ነውና” በማለት ይመክረናል፡፡
አምላክን የወለድሽ ድንግል ማርያም ሆይ! የጽድቅ ፀሐይ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ካንቺ ተወልዶም /ሚል.፬፡፪/ በክንፈ ረድኤቱ (በሥልጣኑ) አቀረበን፡፡ በሐዲስ ተፈጥሮ፣ በጥንተ ተፈጥሮ ፈጥሮናልና፡፡ ሊቁ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅም እንዲህ ይላል፡- “በግብረ መንፈስ ቅዱስ ከግብርናተ ዲያብሎስ ነጻ ወጣን፡፡ በግብረ መንፈስ ቅዱስ ውሉደ እግዚአብሔር ተባልን፡፡ ከምንም በላይ ግን ከኀጢአት ቀንበር ተላቅቀን በሐዲስ ተፈጥሮ ተፈጠርን፡፡ ሥርየተ ኀጢአትን ሰጠን፡፡ ከርኩሰት ኹሉ አነጻን፡፡ ከጸጋው የተነሣ ደቂቀ አዳም የነበርን መላእክት አደረገን፡፡ መላእክቱም ለእኛ በተደረገው ነገር ሐሴት አደረጉ፡፡ ወዮ! ገና ሰዎች ሳለን መላእክት መኾናችን እንደምን ይረቃል እንደምን ይደንቃል? ይህ ኹሉ የመንፈስ ቅዱስ ሥራ ነው” /Fr. Tadros Malaty, On the Book of Isaiah 40:31/፡፡ በሐዲስ ተፈጥሮ፣ በጥንተ ተፈጥሮ ከፈጠረን ልጅሽ ጽንዕት በድንግልና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሣን ለምኚልን፡፡
፪. አምላክን የወልድሽ እመቤታችን ሆይ! ፀሐይ ዘኢየዐርብ (የማይጠልቅ ፀሐይ) የተባለው የብርሃን ክርስቶስ እናቱ ነሽና በአፍኣ በውሰጥ በሥጋ በነፍስ አንቺን ብቻሽን እናከብርሻለን፤ እናገንሻለንም፡፡ ልዑላን ከሚባሉ መላእክት አንቺ ትበልጫለሽ፤ ትሑታን ከሚባሉ ከደቂቀ አዳምም አንቺ ትበልጫለሽ፡፡ ከኀሊናት ኹሉ በላይ ነሽ (ኅሊና የአንቺን ክብር ተናግሮ መጨረስ አይቻለውም)፡፡ ክብርሽን ገናንነትሽን መናገር የሚቻለው ማነው? አንቺንስ የሚመስል ማነው? ሊቁ አባ ሕርያቆስም፡- “ይህንም ባሰብኩ ጊዜ ኅሊናዬ የልጅሽን የባሕሩ ጥልቅነት ይዋኝ ዘንድ ይወዳል፤ የወዳጅሽ የመሠወሪያው ማዕበልም ያማታዋል” ይላል /ቅዳ.ማር.ቁ.፹፬/፡፡ መላእክት ያከብሩሻል፤ ያገኑሻልም፡፡ ሱራፌልም ያመሰግኑሻል፡፡ በኪሩቤል በሱራፌል አድሮ የሚኖረው እርሱ ሰው ኹኖ በማኅፀንሽ አድሯልና፡፡ ክብር የክብር ክብር ያለው እርሱ፤ ሰውን የሚወድ ሰውም የሚወደው እርሱ የእኛን ሞት ነሥቶ የእርሱን ሕይወት ለኛ ሰጥቶ ካባቱ ጋራ አስታረቀን፡፡ ሊቁ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅም በ “በእንተ ልደት” ድርሳኑ ላይ፡- “ስለዚህ ሥጋዬን ተዋሐደ! ወንጌልን ሲያስተምር እሰማው ዘንድ ሥጋዬን በተዋሕዶ ገንዘቡ አደረገው! ሥጋዬን ወስዶም መንፈሱን ሰጠኝ፡፡ ሰጠሁ፤ ተቀበልኩም፡፡ የእኔን ወስዶ የራሱን ስለ ሰጠኝም ሕይወትን ገንዘብ አደረግሁ፡፡ እኔን ለመቀደስ ሥጋዬን ተዋሐደ፤ የሚያድነኝ መንፈስ ቅዱስንም ሰጠኝ” ብሏል፡፡ ክብር የክብር ክብር ካለው ልጅሽ ጽንዕት በድንግልና እመቤታችን ጸጋዉን ክብሩን እንዳይነሣን ለምኚልን፡፡
፫. ድንግል ሆይ! የደናግል ኹሉ መመኪያቸው አንቺ ነሽ፡፡ ከእናንተ መካከል “መመኪያነቷ እንዴት ነው?” ብሎ የሚጠይቅ ሊኖር ይችላል፡፡ እኛም እንዲህ ብለን እንመልስለታለን፡-
፩ኛ) ሊቁ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንዲህ ሲል ይመልስልናል፡- “ወበከመ አውፅአ ብእሲ ብእሲተ ዘእንበለ ብእሲት ከማሁ አውፅአት ብእሲት ብእሴ ዘእንበለ ብእሲ ወሀሎ ዕዳ ላዕለ ትዝምደ አንስት፤ ወበእንተዝ ኮነት ፈዳዪተ ዕዳሃ ለሔዋን - ለወንዶች የሚከፈል ዕዳ በሴቶች ላይ ነበረ፤ ያለ እናት ሔዋን ተገኝታ ነበርና፡፡ ስለዚህም የሔዋንን ብድራት ለአዳም ትከፍለው ዘንድ ድንግል ያለ ዘርዐ ብእሲ (ያለ ወንድ ዘር) ክርስቶስን ወለደችው፡፡ አዳም ያለ እናት ሔዋንን ስላስገኘ እንዳይመካ ድንግል ያለ አባት ክርስቶስን ወለደችው፡፡ ድንቅ በሚኾን አንድነት ይህ አንድ የፍጥረት እኩልነት ይታወቅ ዘንድ” /ሃይ.አበ.፷፮፡፳፱/፤
፪ኛ) ቀድሞ ወንዶች ሴቶችን በእናንተ ምክንያት ከገነት ወጣን እያሉ ርስት አያካፍሏቸውም ነበር፡፡ ሐዋርያው ጳውሎስ፡- “ብእሲ ወብእሲት አሐደ እሙንቱ በክርስቶስ - ወንድም ሴትም የለም፤ ኹላችሁ በክርስቶስ ኢየሱስ አንድ ሰው ናችሁና” ብሎ እስኪያስተምር ድረስ /ገላ.፫፡፳፰/ በሔዋን ምክንያት ከገነት ብትወጡ በእመቤታችን ምክንያት ገነት መንግሥተ ሰማያት ገብታችሁ የለምን? ብለው የሚመኩ ኹነዋልና፤
፫ኛ) ደግሞ ለደናግላን አስበ ድንግልናቸውን (የድንግልናቸውን ዋጋ) ስለምታሰጣቸው ሊቁ “ምክሆን ለደናግል” ብሏታል፡፡
የዕለተ ሐሙስ ውዳሴ ማርያም ትርጓሜ በድምፅ፡፡👉mp3 format
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
ኹሉ ጋር ተድላ ደስታ ወዳለበት ገነት ገባ” ብሏል /ሃይ.አበ.፷፯፡፫-፭/፡፡
ከባሕርያችን መርገመ ሥጋን መርገመ ነፍስን የሚያጠፋልንን ጌታን ዘር ምክንያት ሳይኾናት ወለደችው፡፡ ስለዚህ ነገር “ሰውን የምትወድ ሰው የሚወድህ አቤቱ ክብር ላንተ ይገባል” እያልን እናመስግነው፡፡ “ኄር ዘበህላዌሁ ዘልማዱ ኂሩት - በባሕርይው ቸር የኾነ፤ ቸርነትን ማድረግም ልማዱ የኾነ” እያልን እናመስግነው፡፡ ኄር ዘበህላዌሁ ዘልማዱ ኂሩት ከሚባል ልጅሽ ጸንዕት በድንግልና ሥርጉት በቅድስና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሣን ለምኚልን፡፡
፫. ዘር ምክንያት ሳይኾናት አምላክን የወለደች ድንግል፣ የማኅፀንዋ ሥራ ምን ይረቅ? ምን ይጠልቅ? አንድም ለድንግል ለማኅፀኗ ሥራ አንክሮ ይገባል፡፡ ለዮሴፍ የነገረው መልአክ ሳይለወጥ ሰው የኾነ አካላዊ ቃል ከርሷ የሚወለድ በግብረ መንፈስ ቅደስ እንደኾነ መስክሯልና /ማቴ.፩፡፳/፡፡ ማርያም የዚህ ደስታ ዕፅፍ ድርብ የሚኾን ጌታን ወለደችው፡፡ ሴቶች ልጅ ትወልዳላችሁ ሲባሉ ደስ ይላቸዋል፤ ይልቁንም ወንድ ትወልዳላችሁ ሲሏቸው ደስ ይላቸዋል፡፡ እመቤታችን ግን ከዚሁ ኹሉ ያለፈ አምላክን ወልዷለችና ደስታዋ ዕፅፍ ድርብ ኾነላት፡፡ መልአኩ፡- “ልጅ ትወልጃለሽ፤ ስሙም አማኑኤል ይባላል” አላት፡፡ አማኑኤልም ማለት እግዚአብሔር ከሥጋችን ሥጋ ከነፍሳችን ነፍስ ነሥቶ ከኛ ጋራ አንድ ባሕርይ ኾነ ማለት ነው፡፡ ዳግመኛም ወገኖቹን ከኃጢአታቸው ፍዳ የሚያድናቸው መድኃኒት ይባላል አላት /ማቴ.፩፡፳፩/፡፡ በመኾኑም በክሂሎቱ (በከሃሊነቱ) ያድነን ዘንድ፣ ኃጢአታችንን ያስተሠርይልን ዘንድ (እስከ ዕለተ ምፅአት ድረስ ክብር ይግባውና) ሰው የኾነ እርሱ አምላክ እንደኾነ በተረዳ ነገር አወቅነው፡፡ አምላክ ብቻ ቢኾን ባልታመመ ነበርና፤ ሰውም ብቻ ቢኾን ባላደነን ነበርና፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅም ከዚህ ጋር አያይዞ ፡- “ፍቁራን ሆይ! ምንም እንኳን ለዚህ ክብር የተገባን ኾነን ባንገኝም አባታችን በከኀሊነቱ እንዲሁ ከኀጢአታችን አድኖናልና ይህን ክብር፣ ይህን ጸጋ በፍጹም ልናክፋፋው (ልናቆሽሸው) አይገባንም፡፡ ልጅነት እንዲሁ ሳይሰጠን ለምረረ ገሃነም የተገባን የቁጣ ልጆች ከነበርን፤ ይህ ከኅሊናት በላይ የኾነ ጸጋ ከተቀበልን በኋላማ ፍዳችን እንደምን የበዛ አይኾን? ልጆቼ! ይህን የምለው እንዲሁ ለመናገር ያህል አይደለም፡፡ ዳግም ከአብራከ መንፈስ ቅዱስ ከማኅፀነ ዮርዳኖስ ከተወለዱ በኋላ ብዙ ክርስቲያኖች በኀጢአት፣ በስንፍና፣ ለምግባርና ለትሩፋት ሳይሽቀዳደሙ ታክተው ስለምመለከት ነው እንጂ” ሲል ይመክረናል /St. John Chrysostom, Homily on the Gospel of St. Matthew, Homily IV/፡፡
ወዮ! ንዕድ ክብርት ከምትኾን ከእመቤታችን ይህ የአምላክ መወለድ ምን ይረቅ? ምን ይጠልቅ? ቃልን ወሰነችው፡፡ ለልደቱም ዘርዕ ምክንያት አልኾነውም፡፡ በመወለዱም ማኅተመ ድንግልናዋን አልለወጠውም፡፡ ከአብ አካል ዘእምአካል ባሕርይ ዘእም ባሕርይ ድካም ሳይሰማው የተወለደ እርሱ ፭ ሺሕ ከአምስት መቶ ዘመን ሲፈጸምም ከድንግል ሕማም ሴቶች የሚሰማቸውን ሕማም ሳይሰማት እርሱን ሕፃናትን የሚሰማቸው ሕማም ሳይሰማው ተወለደ እንጂ፡፡
ሰብአ ሰገል ሰገዱለት፡፡
Ø አምላክ ነውና አምላክ እንደኾነ ለማጠየቅ ዕጣን አመጡለት፡፡ ንጉሥ ነውና ንጉሥ እንደ ኾነ ለማጠየቅ ወርቅ አመጡለት፡፡ ማኀየዊ የሚኾን የሞቱ ምሳሌ ከርቤንም አመጡለት፡፡
Ø አንድም “ይኸን ወርቅ እንገብርላቸው የነበሩ ነገሥታት ቀድሞም ፍጡራን ኋላም ኀላፍያን ናቸው፤ አንተ ግን ቀድሞም ያልተፈጠርህ ኋላም የማታልፍ ነህ” ሲሉ ወርቅ አመጡለት፡፡ “ይኽን ዕጣን እናጥናቸው የነበሩ ጣዖታት ቀድሞም ፍጡራን ኋላም ኃላፊያን ናቸው፤ አንተ ግን ቀድሞም ያልተፈጠርህ ኋላም የማታልፍ ነህ” ሲሉ ዕጣን አመጡለት፡፡ “ምንም ቀድሞ ያልተፈጠርህ ኋላም የማታልፍ ብትኾን በሰውነትህ መራራ ሞትን ትቀምሳለህ” ሲሉ ከርቤ አመጡለት፡፡
Ø አንድም ወርቅ ጽሩይ ነውና “ጽሩየ ባሕርይ ነህ” ሲሉ ወርቅ አመጡለት፡፡ ዕጣን ምዑዝ ነውና “አንተም ምዑዘ ባሕርይ ነህ” ሲሉ ዕጣን አመጡለት፡፡ ዳግመኛም “ከርቤ የተሰበረውን ይጠግናል፤ የተለያየውን አንድ ደርጋል፡፡ አንተም ከማኀበረ መላእክት የተለየ አዳምን አንድ ታደርገዋለህ፤ ጽንዓ ነፍስ ሰጥተህ ታጸናዋለህ” ሲሉ ከርቤ አመጡለት፡፡
Ø አንድም ወርቅ ጽሩይ ነውና “ባንተ ያመኑ ምዕመናን ጽሩያነ ምግባር ወሃይማኖት ናቸው” ሲሉ ወርቅ አመጡለት፡፡ ዕጣን ምዑዝ ነውና “ባንተ ያመኑ ምእመናንም ምዑዛነ ምግባር ወሃይማኖት ናቸው” ሲሉ ዕጣን አመጡለት፡፡ ዳግመኛም በዕለተ ሞቱ ያቀምሱታልና ከርቤ አመጡለት፡፡ ቸርና ሰው ወዳጅ የኾነ አንድ እርሱ ብቻ ነው፡፡ ቸርና ሰው ወዳጅ ከኾነ ልጅሽ ጽንዕት በድንግልና ሥርጉት በቅድስና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሣን ለምኚልን፡፡
፬. ከአዳም ጎን አንድ ዐፅም መንሣቱ ምን ይረቅ? ምን ይጠልቅ? “በእምነት ዓይን ከማየት በቀር ይህ ከኅሊናት በላይ የኾነውን ድንቅ ነገር በቋንቋ መናገር አይቻለንም” /St. John Chrysostom, Homily 15 on Genesis/፡፡ ከእርሱ (ከአዳም) ሔዋንን ፈጠረ፡፡ ፍጥረትንም ኹሉ ከአዳምና ከሔዋን ፈጠረ፡፡ እንዲህም አድርጎ የአብ አካላዊ ቃል ለኵነተ ሥጋ (ለሕማም ለሞት) ተሰጠ፡፡ ከልዩ ድንግልም ሰው ኾነና አማኑኤልም ተባለ፡፡ “ኦ ለዝንቱ መንክር ልዑል ላዕለ ኵሉ ሕሊናት ብእሲት ምድራዊት ወለደቶ ለእግዚአብሔር ቃል ዘኮነ ሰብአ… - ከኅሊናት ኹሉ ለራቀ ለዚህ ድንቅ ምሥጢር አንክሮ ይገባል፤ ምድራዊት ሴት ሰው የኾነ እግዚአብሔር ቃልን ወለደችው፡፡ ድንግል ፈጣሪዋን ወለደችው፤ እርሱም እናቱን ፈጠረ፡፡ ከእርሷም እርሱ የፈጠረውን ሥጋ ተዋሐደ” /ሃይ.አበ.፵፯፡፪/፡፡
ስለዚህ ነገር ከልጅዋ ከወዳጅዋ ታማልደን ዘንድ ኹል ጊዜ እርስዋን እንለምን፡፡ በቅዱሳን ዘንድ ቸር ናትና እርሷን እንለምን፡፡ ለሊቃነ ጳጳሳት አስበ ጵጵስናችን (የጵጵስናችን ዋጋ) ይሰጠናል ብለው ደጅ የሚጠኑትን ወልዳላቸዋለችና ከልጅዋ ከወዳጅዋ ታማልደን ዘንድ ኹል ጊዜ እርስዋን እንለምን፡፡ ነቢያት አስበ ትንቢታችንን ይሰጠናል ብለው “ይወርዳል፤ ይወለዳል” ብለው ትንቢት የተናገሩለትን ወልዳላቸዋለችና ከልጅዋ ከወዳጅዋ ታማልደን ዘንድ ኹል ጊዜ እርስዋን እንለምን፡፡ ሐዋርያት አስበ ሰብከታችንን ይሰጠናል ብለው “ውስተ ኵሉ ምድር ወፅአ ነገሮሙ ወእስከ አጽናፈ ዓለም በጽሐ ነቢቦሙ - መምህራነ ሐዲስ ሐዋርያት ለምእመናነ ሐዲስ ወረደ ተወለደ ብለው አስተማሩ” እንዲል /መዝ.፲፰፡፬/ ጽንፍ እስከ ጽንፍ ዙረው ወረደ ተወለደ ብለው ያስተማሩለትን ወልዳላቸዋለችና ከልጅዋ ከወዳጅዋ ታማልደን ዘንድ ኹል ጊዜ እርስዋን እንለምን፡፡ ሰማዕታ ከዓላውያን ነገሥታት፣ ከዓላውያን መኳንንት ገብተው አስበ ትዕግሥታችንን ይሰጠናል ብለው መከራውን ታግሠው የተቀበሉለትን፣ ምዕመናን አስበ ተጋድሏቸውን ይሰጠናል ብለው ከፍትወታት ከእኩያት ኃጣውእ የተዋጉለት ኢየሱስ ክርስቶስን ወልዳቸዋችና ከልጅዋ ከወዳጅዋ ታማልደን ዘንድ ኹል ጊዜ እርስዋን እንለምን፡፡ ሰው ኹኖ አድኖናልና በጥበቡ እየሰፈረ የሚሰጠው፣ ዳግመኛም የጸጋው ብዛት የማይታወቅ የቸርቱን ብዛት መርምረን እንወቅ፡፡ ሰው ኹኖ ካዳነን ልጅሽ ጽንዕት በድንግልና ሥርጉት በቅድስና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እዳይነሣን ለምኚልን፡፡
የሐሙስ ውዳሴ ማርያም ትርጓሜ
ይህ ዕለት ለምስጋና አራተኛ ለፍጥረት አምስተኛ ቀን ነው፡፡ በዚህም ቀን እመቤታችን ትመጣለች፤ የብርሃን ድባብ ይዘረጋል፤ የብርሃን ዙፋን ይነጸፋል፡፡ ከዚያ ላይ ኹናም ሊቁን ባርካው ምስጋናዉን ጀምሯል፡፡ ከወትሮ ይልቅም ነቢያትንና ሐዋርያትን አስከትላ መጥታለች፡፡
@Ethiopian_Orthodox
ሰው ማይኾነው ሰው ኾኗልና ይህን ድንቅ ምሥጢር ኑ እዩ፡፡ ቃል ከሥጋ ጋር ቢዋሐድ ጥንት የሌለው መለኮት ፭ ሺሕ ከ፭፻ ዘመን ሲፈጸም ዘመን ተቀድሞት ወደ ኋላ ተገኘ፡፡ ቅድምና የሌለውም ሥጋ ቀዳማዊ አምላክ ተባለ፡፡ አንድም ጥንት (ቅድምና) የሌለው ሥጋ ቀዳማዊ አምላክ ተባለ፡፡ ዘመን የማይቆጠርለትም መለኮት ፲፪ ዓመት ኾነው /ሉቃ.፪፡፵፪/፤ ፴ ዓመት ሞላው ተብሎ ዘመን ተቆጠረለት /ሉቃ.፫፡፳፫/፡፡ አንድም አካላዊ ቃል በጎላ በተረዳ ሰው ኹኗልና በኵር ያልነበረ መለኮት በኵር ተባለ /ማቴ.፩፡፳፭/፡፡ ክብር የሌለውም ሥጋ ክቡር አምላክ ተባለ፡፡ በገዥነት የማይታወቅ ሥጋ በገዥነት ታወቀ፤ በተገዢ ሥጋ ታይቶ የማይታወቅ መለኮትም በተገዢ ሥጋ ታየ፡፡ ቅድመ ዓለም የነበረው፣ በማዕከለ ዓለም ያለው፣ መቼም መች የሚኖረው ኢየሱስ ከርስቶስ እንሰግድለትና እናመሰግነው ዘንድ ከአብ ከባሐርይ አባቱ ከመንፈስ ቅዱስ ከባሕርይ ሕይወቱ ጋራ አንድ ባሕርይ ነው፡፡ ከአብ ከባሕርይ አባቱ ከመንፈስ ቅዱስ ከባሕርይ ሕይወቱ ጋራ አንድ ባሕርይ ከሚኾን ልጅሽ ጽንዕት በድንግልና ሥርጉት በቅድስና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንደይነሣን ለምኚልን፡፡
፯. ነቢዩ ሕዝቅኤል የእርሷን ነገር “በድንቅ ቁልፍ የተቈለፈች ደጅ በምሥራቅ አየሁ” ብሎ ተናገረ /ሕዝ.፵፬፡፩-፪/፡፡ ከእግዚኣ ኃያላን በቀር ሳይከፍታት ገብቶ ሳይከፍታት የወጣ የለም፡፡ እግዚአ ኃያላን እሱ ሳይከፍታት ገብቶ ሳይከፍታት ወጣ እንጂ፡፡ እግዚአ ኃያላን ከሚባለው ልጅሽ ጽንዕት በድንግልና ሥርጉት በቅድስና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን አንዳነሣን ለምኚልን፡፡
፰. ኆኀትም (ድጅም) የተባለች መድኃኒታችንን ጌታን የወለደችልን ድንግል ናት፡፡ እሱን ከወለደችው በኋላ እንደ ቀድሞ ማኅተመ ደንግልናዋ ሳይለወጥ ኑራለቸና፡፡ ሊቁ ቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግም፡- “… አንተ መናገር የተሰጣቸውን ሠረገሎች ድምፅ የሰማህ ባለ ሞገስ ሆይ (ሕዝ.፫፡፲፫)! እንደዚሁም የክንፎቻቸውን ድምፅና የዚያን ሠረገላ ታላቅ እንቅስቃሴ የሰማህ ሆይ (ሕዝ.፲፡፭)! አንተ የኪሩቤልን መልክ መለወጥ ያየህ የበራልህ ነፍስ ሆይ! እንዲሁም እኒያ የእሳት ላንቃዎች በከፍታ ላይ የተቀመጠውን ሲያመሰግኑ የሰማህ ሕዝቅኤል ሆይ (ሕዝ.፩፡፬-፳፰) ና! አንተ የቡዝ ልጅ ሆይ (ሕዝ.፩፡፳፫) ና! የተጠቀለለውን የትንቢትህን ቃል ብራና አምጣልን፡፡ አንተ ቁምና እውነትን ተናገር፤ ሌሎቻችን ኹሉ ዝም እንበል፡፡ ካየኻቸው ራዕዮች መካከል ድንግል ማርያም ታይታህ እንደኾነ፤ ፍጥረት ኹሉ ውበቷን ያይ ዘንድ መልኳን ግለጥልን፡፡ በትንቢትህ ውስጥ የጌታህን እናት የሚመለከት አንዳች ነገር ካለ ይህ ለሚሰሙት እጅግ ውድ ስለኾነ ተነሣና አብራራልን፡፡ ይህም ያም (መናፍቅ) ከመውለዷ በኋላ ድንግል አልነበረችም በማለት ይናገራልና እውነት ድንግልናዋን አጥታ እንደኾነ እስኪ አንተ አስረዳን፡፡ ሕዝቅኤል ሆይ! ዛሬ የአንተ ተራ ነውና እስኪ ተናገር፡፡ ስለ እመቤታችን ማርያም ተናገርና ከንቱ ምርምሮችን ግታልን፡፡ እስከ አሁን በትንቢት ተነግሮ የነበረው ምን እንደነበር እንስማ፡፡ የማትመረመር ስለኾነችው ስለ ድንቅ እናታችን ይህ ነቢይ በትንቢቱ ውስጥ እንዲህ ተናግሮ ነበር፡- ‘ወደ ምሥራቅም ወደሚመለከተው በስተ ውጭ ወዳለው ወደ መቅደሱ በር አመጣኝ፤ ተዘግቶም ነበር። እግዚአብሔርም። ይህ በር ተዘግቶ ይኖራል እንጂ አይከፈትም፥ ሰውም አይገባበትም፤ የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር ገብቶበታልና ተዘግቶ ይኖራል።’ አንተ የመንፈስ ነቢይ ሆይ! ይህ ቃል ምን ማለት እንደኾነ እስኪ ገልጠህ አብራራልን፡፡ በትንቢት የተነገረው የተዘጋው በር ድንግል ማርያም ናት፡፡ ምክንያቱም መሲሑ ጌታ በእርሱ በኵል ወደ ዓለም መጥቶ ዝግ አድርጎ ትቶታልና፡፡ ጌታ በዚህ በር ሲገባ እንዳልከፈተው ዕብራዊ የኾነ ሕዝቅኤል ከእኛ ጋር አብሮ ይህንኑ ይመሰክራል፡፡ እግዚአብሔር እንደወደደው በመውለድ በር ወደ ዓለም ገባ፡፡ ያንንም በር በድንግልና ዘጋው፡፡ ነቢዩ በሩ ተዘግቶ ያየው ያ ቤተ መቅደስ ስለ ድንግልናና ስለማይለወጥ ድንግልናዋ የሚያሳየን ነው፡፡ ቅዱሱ መሲሑ (ክርስቶስ) ሲኾን ቤተ መቅደሱም ማርያም ናት፡፡ የተዘጋውም በር በእርሷ የሚኖረውና ተፈትሖ የሌለበት የድንግልዋ ማኅተም ነው” ብሏል /Jacob of Serug, Homily on the Perpetual Virginity of Mary, pp VII-X/፡፡
የማኅፀንሽ ፍሬ ኢየሱስ ክርስቶስ መርገመ ሥጋ መርገመ ነፍስ የሌለበት በረከተ ሥጋ በረከተ ነፍስ የሚያድል ነው፡፡ ለሰው ከማያዝን ከማይራራ፤ አንድም ለእርሱ ከሥላሴ ዘንድ ምሕረት ከሌለው፤ አንድም ኃጢአቱን ሸልጎ ከማይሠራ ከዲያብሎስ እጅ ያዳነን ጌታችንን የወለድሽው ሆይ! በደንግሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ ፍጽምት ነሽ፡፡ መርገም ሥጋ መርገመ ነፍስ የሌለብሽ /ኢሳ.፩፡፱/ በረከተ ሥጋ በረከተ ነፍስ እያማለድሽ የምታሰጭ ነሽ፡፡ ጌትነቱ እንደ ነገሥታት በጉልበት፣ እንደ ካህናት በሀብት፣ እንደ ጣዖታትም በሐሰት ባይደለ በክብር ባለቤት ዘንድ ባለሟልነትን አግኝተሸልና በዚህ ዓለም ከሚኖሩ ሰዎች ኹሉ ይልቅ ክብር ላንቺ ይገባል፡፡ አካላዊ ቃል መጥቶ ከሥጋሽ ሥጋ ከነፍስሽ ነፍስ ነሥቶ ሰው ኾነ፡፡ ሰው ሰውኛውንም ኖረ፡፡ መሐሪ፣ ይቅር ባይ፣ ሰው የሚወደው ሰው ወዳጅ ነውና በልዩ አመጣጡ መጥቶ አዳነን፡፡ “አኮ በተንባል ወአኮ በመልአክ አላ ለሊሁ እግዚእ መጸእ ወያድኅነነ - በአማላጅ አይደለም፤ በመልአክም አይደለም፡፡ እርሱ ራሱ፣ በራሱ ደም፣ በራሱ ሊቀ ካህንነት መጥቶ ያድናቸዋል እንጂ ” /ኢሳ.፷፫፡፱/ እንዲል እንደ ቀደመው በረድኤት ሳይኾን በኩነት (ሰው ኹኖ) መጥቶ አዳነን፡፡ አንድም አምስት ሺሕ ካምሰት መቶ ዘመን ሲፈጸም አንድ ሰዓት ስንኳ ሳያሳልፍ በጽኑ ቀጠሮው መጥሮ አዳነን፡፡ በጽኑ ቀጠሮ መጥቶ ካዳነን ልጅሽ ጽንዕት በድንግልና ሥርጉት በቅድስና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሣን ለምኚልን፡፡
አነሣሥቶ ላስጀመረን አስጀምሮ ላስፈጸመን ለልዑል እግዚአብሔር ክብር ምስጋና ይግባው አሜን፡፡
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
፩. ኵሉ ሠራዊተ ሰማያት ይብሉ ብፅዕት አንቲ ሰማይ ዳግሚት ዲበ ምድር - ከምድር በላይ ያለሽ ኹለተኛ ሰማይ ሆይ! በሦስቱ ሰማያት (በኢዮር፣ በራማ፣ በኤረር) ያሉ መላእክት ንዕድ ነሽ፤ ክብርት ነሽ ይላሉ፡፡ ማርያም የምሥራቅ ደጅ ናት፤ ከእርሷ የጽድቅ ፀሐይ ክርስቶስ ተኝቷልና፡፡ ማርያም ሙሽራዋ ንጹሕ የሚኾን ንጽሕት የሠርግ ቤት ናት፡፡ በሠርግ ቤት የመርዓዊና የመርዓት (የሙሽራና የሙሽሪት) ተዋሕዶ ይደረግበታል፡፡ በእመቤታችንም እንደ መርዓዊና እንደ መርዓት ተዋሕዶ፤ ትስብእትና መለኮት አንድ ኹነዋልና፡፡ በሠርግ አዝማደ መርዓዊና አዝማደ መርዓት አንድ እንዲኾኑባት በእመቤታችንም ምክንያት ሰውና መላእክት፣ ሰውና እግዚአብሔር፣ ነፍስና ሥጋ፣ ሕዝብና አሕዛብ አንድ ኹነዋልና እመቤታችን ንጽሕት የሠርግ ቤት ናት /ኤፌ.፪፡፲፭/፡፡ አባ ሕርያቆስ “አስተንፈሰ ወአጼነወ ወኢረከበ ዘከማኪ፤ ወሠምረ መዓዛ ዚኣኪ ወአፍቀረ ሥነኪ ወፈነወ ኀቤኪ ወልዶ ዘያፈቅር” እንዲል /ቅዳ.ማር.ቁ.፳፬/ አብ ከሰማይ ኾኖ አየ፤ ነገር ግን እንዳንች ያለ ባያገኝ ተቀዳሚ ተከታይ የሌለውን ልጁን ሰዶ ካንቺ ከሥጋሽ ሥጋ ከነፍስሽ ነፍስ ነሥቶ ሰው ኾነ፡፡ ተቀዳሚ ተከታይ ከሌለው ልጅሽ ጽንዕት በድንግልና ሥርጉት (ክብርት) በቅድስና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሣን ለምኚልን፡፡
እዚህ ጋር አንዳንድ ወገኖች የሚያነሡትን ጥያቄ መልሰን እንለፍ፡፡ “ልመናስ ከዚያ በኋላ ስንኳን በሷ (ከበቁ በኋላ) በሌሎችም የለባቸውም፡፡ በቀደመ ልመናዋ የምታስምር ስለ ኾነ እንዲህ አለ እንጂ” ስለተባለ ምሥጢሩን ሳይረዱ “ቅዱሳን በአጸደ ነፍስ አያማልዱም” ለማለት የሚጠቅሱት ወገኖች አሉ፡፡ የዚህ ኃይለ ቃል ትርጓሜ ግን ሊቁ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ የዕብራውያንን መልእክት በተረጐመበት በ፲፫ኛው ድርሳኑ ላይ፡- “ጻድቃን ይረክቡ ኵሎ በአሐቲ ተምኔቶሙ በአሐቲ ስእለት - ጻድቃን አንድ ጊዜ በለመኑት ልመና የሚሹትን ኹሉ ያገኛሉ” እንዳለው /ቁ.፻፶፱/ ቅዱሳኑ በአጸደ ሥጋ ሳሉ እግዚአብሔር አንድ ጊዜ “በስምሽ/ህ ለታረዙ ያለበሰ፣ ሕሙማንን የጐበኘ፣ ዝክርሽ/ህን የዘከረ…” እያለ በገባላቸው ቃል ኪዳን መሠረት በስማቸው የዘከረ፣ በስማቸው ሕሙማንን የጐበኘ፣ የመጸወተ እንደሚምርላቸው የሚያስረዳ ነው፡፡ ለምሳሌ፡- እግዚአብሔር፣ ዓለምን ዳግም በንፍር ውሃ የማያጠፋትና በየዕለቱ ቀስተ ደመናን የምንመለከተው ፡- “ቃል ኪዳኔንም ለእናንተ አቆማለሁ፤ ሥጋ ያለውም ኹሉ ዳግመኛ በጥፋት ውኃ አይጠፋም፤ ምድርንም ለማጥፋት ዳግመኛ የጥፋት ውኃ አይኾንም” ብሎ /ዘፍ.፱፡፲፩/ ለኖኅ አንድ ጊዜ በገባለት ቃል ኪዳን መሠረት እንጂ ኖኅ በየዕለቱ እንዲህ ስለሚለምን አይደለም፡፡ “አይለምንም” ሲባል ግን ክብሩን፣ ልዕልናውን፣ መንፈሳዊ ብቃቱን የሚያስረዳ እንጂ ማማለድ አይችልም ለማለት አይደለም፡፡ እንደውም ይህ ኃይለ ቃል ከማማለድ በላይ የኾነ ክብር እንደተሰጣቸው የሚያመለክት ነው፡፡ ምክንያቱም አንድ ጊዜ ለምኖ በየጊዜው የሚሹትን ማግኘት፤ ዕለት ዕለት እየለመኑ የሚሹትን ከማግኘት በላይ ልዕልናን፣ ክብርን፣ መንፈሳዊ ብቃትን ያሳያልና፡፡ አሁን ቅዱሳንን አማልዱን ስንላቸው አባ ሕርያቆስ በቅዳሴው ደጋግሞ እንደገለጸው ቃል ኪዳናችሁን አሳስቡልን ስንል ነው /ቅዳ.ማር. ቁ.፻፷፬-፻፸፩ ይመልከቱ/፡፡
፪. ንግባእኬ ኀበ ጥንተ ነገር - ወደ ቀደመው ነገር እንመለስ፡፡ አምላክን የወለድሽ እመቤታችን ሆይ! አንቺን ብቻሽን ትውልደ ሴም፣ ትውልደ ካም፣ ትውልደ ያፌት (ትውልድ ኹሉ) ያመሰግኑሻል /ሉቃ.፩፡፵፰/፡፡ ፱ ወር ከ፭ ቀን ማኅፀንሽን ዓለም አድርጐ የኖረብሽ ሀገረ እግዚአብሔር፣ መንግሥተ ሰማያት ሆይ! ነቢያት ላንቺ “ኢይትዐፀዉ አናቅጽኪ (በሮችሽ ኹል ጊዜ ይከፈታሉ - ንስሐ የሚገቡ ኃጥአንን ለመቀበል)፤ ወኢይጸልም ወርኅኪ (ጨረቃሽ አይቋረጥም)፤ ወኢየዐርብ ፀሐይኪ (ፀሐይሽ ከዚያ በኋላ አትጠልቅም - ፈጣሪሽ አያልፍም)፤ እስመ እግዚአብሔር ብርሃንኪ ለዓለም (ለዘለዓለም ብርሃንሽ እግዚአብሔር ነውና)” /ኢሳ.፷፡፲፩፣፳/፤ “ነኪር ነገሩ በእንቲአኪ ሀገረ እግዚአብሔር - የእግዚአብሔር ከተማ ሆይ! ስላንቺ የተነገረው ነገር ድንቅ (ልዩ) ነው” /መዝ.፹፮፡፫/ እያሉ ድንቅ ድንቅ ነገርን ተናገሩልሽ፡፡ በርግጥም ሰማይና ምድር የማይችሉትን አምላክ የአንቺን ማኅፀን ከተማ አድርጎ ፱ ወር ከ፭ ቀን መኖሩ፤ ያለ ዘር ያለ ሩካቤ አካላዊ ቃልን መፀነስሽ፤ በኅቱም ድንግልና መወለዱ፤ የድንግልና ጡቶችሽን ማጥባትሽ ድንቅ ነው፡፡
ደስ ብሏቸው የሚኖሩ የጻድቃን፣ የሰማዕታት፣ የመላእክት ማደሪያ ኹነሻልና የምድር ነገሥታት ይህን ዜናሽን ሰምተው፣ ጣዕመ መንግሥተ ሰማያትን ምረረ ገሃነምን ዐውቀው መንነው ይሄዳሉ፡፡ እነርሱ ብቻ አይደሉም፤ ሠራዊቶቻቸውም ጣዕመ መንግሥተ ሰማያትን ምረረ ገሃነምን ዐውቀው መንነው ይሄዳሉ፡፡ አንድም ብርሃን ልጅሽን አምነው ጸንተው ይኖራሉ፡፡ አምላክን የወለድሽ እመቤታችን ሆይ! አንቺን ብቻሽን ትውልደ ሴም፣ ትውልደ ካም፣ ትውልደ ያፌት ያመሰግኑሻል /ሉቃ.፩፡፵፰/፤ ካንቺ ለተወለደውም ይሰግዱለታል፤ “ዐቢይ እግዚአብሔር - እግዚአብሔር ታላቅ ነው” እያሉም ያከብሩታል፤ ያገኑታልም፡፡ “ዐቢይ እግዚአብሔር” እያሉ ከሚያከብሩት ከሚያገኑት ልጅሽ ጽንዕት በድንግልና ሥርጉት በቅድስና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሣን ለምኚልን፡፡
፫. “እንተ በአማን ንጹሕ ዝናም” የተባለ፣ የነፍሳትን ጥም ያበረደ የሕይወት ዝናም፣ የሕይወት ጠል፣ የሕይወት ውሃ ክርስቶስን ቋጥረሽ (በድንግልና ፀንሰሽ፣ በድንግልና ወልደሽ) የታየሽልን እውነተኛ ደመና አንቺ ነሽ፡፡ ኢትዮጵያዊው ቄርሎስ አባ ጊዮርጊሥ ዘጋሥጫም፡- “ንዑ እንከ ከመ ናልዕላ ለዛቲ ደመና ብርሃን እንተ ጾረቶ ለማየ ዝናም ንጹሕ- ንጹሑን የዝናም ውሃ የተሸከመችውን የብርሃን ደመና ኑ ከፍ ከፍ እናድርጋት” ብሎ ጋብዞናል /አርጋኖን ዘሠሉስ ፮፡፪/፡፡ ስትወልጂው ማኅተመ ድንግልናሽ አለመለወጡ፤ አካላዊ ቃል ሰው ሲኾን አምላክነቱ ላለመለወጡ፣ ድንግል ወእም (ድንግልም እናትም) ስትባዪ መኖርሽም ልጅሽ አምላክ ወሰብእ (ፍጹም አምላክ ፍጹም ሰው) ሲባል ለመኖሩ ምሳሌ ነውና አብ የልጁ ምልክት አደረገሽ፡፡ መንፈስ ቅዱስ ቢያድርብሽ፣ ኀይለ ልዑል ወልድም ሥጋሽን ቢለብስ፤ አንድም መንፈስ ቅዱስ ከሦስቱ ግብራት (ማለትም ከሩካቤ፣ ከዘር፣ ድንግልናን ከመለወጥ) ቢከለክልሽ፣ ኀይለ ልዑል ወልድም ከሦስቱ ግብራት ቢከልልሽ ለዘላለሙ የሚኖር አካላዊ ቃልን ወለድሽልን /ሃይ.አበ.፻፲፡፳፱/፡፡ እርሱም ሰው ኾኖ ከኃጢአት አንድም ከኃጢአታችን ፍዳ አዳነን፡፡
የዕለተ ማክሰኞ ውዳሴ ማርያም ትርጓሜ በድምፅ፡፡👉mp3 format
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
፯. ወደ ደብረ ሲና የወረደው፣ ለሙሴ ሕገ ኦሪትን የሠራ፣ የተራራውን ራስ በጨለማ በእሳት በጽጋግ በነፋስ (በዕበየ ግርማው) የሸፈነ፣ ፈርተው የቆሙትን ፈጥኖ በሚሰማ በረቂቅ ነጋሪት ድምጽ የገሠፀ እርሱ የሰው ልጆችን ለማዳን ፭ ሺሕ ፭፻ ዘመን ሲፈጸም ሰው ኾኖ የመጣው የአብ አካላዊ ቃል ነው፡፡ በሌላ አንቀጽም ይኸው ሊቅ፡- “እም ደብረ ሲና ወፅአ እሳት ወጽልመት ወእምኔኪ ወፅአ ለነ አምላክ ወሰብእ፡፡ እም ደብረ ሲና ወፅአ ድንጋፄ ወሀውከ ላዕለ አይሁድ ወእምኔኪ ወፅአ ሁከት ወድንጋፄ ዐቢይ ላዕለ አይሁድ ወሄሮድስ ወዲያብሎስ ምስለ አጋንንቲሁ - ከደብረ ሲና እሳት ጨለማ ወጣ፤ ከአንቺ ግን ሰው የኾነ አምላክ ተገኘልን፡፡ በደብረ ሲና በአይሁድ ላይ ድንጋፄ ሀውክ ተደረገ፤ በአንቺም በአይሁድ በሄሮድስ በዲያብሎስና በሠራዊቱ ላይ ጽኑ ድንጋፄ ተደረገ” ብሏል /ዘጸ.፳፡፲፰፣ ዕብ.፲፪፡፲፱፣ ሃይ.አበ.፵፯፡፱-፲/፡፡ እንዲህ ከተባለ ልጅሽ ጽንዕት በድንግልና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሣን ለምኚልን፡፡
፰. “ናሁ ድንግል ትፀንስ ወትወልድ ወልደ” ከሚለው የኢሳይያስ አንቀጽ /ኢሳ.፯፡፲፬/ ስትደርሺ “እኔ በኾንኩኝ” ሳትዪ፤ ይልቁንም “ምነው ከዘመኗ ደርሼ፣ ወጥቼ ወርጄ በድንግልና የምትወልደውን ድንግል ባገለገልኳት” ብለሽ በትሕትና የተናገርሽ ደብር ነባቢት ሆይ! ሰውን የሚወድ፣ ሰውም የሚወደው ጌታ ባሕርዩ ሳይለወጥ ካንቺ ከሥጋሸ ሥጋ ከነፍስሽ ነፍስ ነሥቶ ሰው ኾነ፡፡ እንደኛ የሚናገር ሥጋን ነሥቶም ሰው ኾነ፡፡ ጥበብን በሚገልጽ፣ ሥጋዌን በሚያስፈጽም በግብረ መንፈስ ቅዱስ አምላክ በማኅፀንዋ አደረና ፍጹም ሰው ኾነ፡፡ በቸርነቱና በይቅርታው ብዛት አዳምን ያድነው ዘንድ፣ ኃጢአቱንም ያስተሠርይለት ዘንድ፣ በሰማያዊ ቦታ በሰማያዊ መዓርግ ያኖረው ዘንድ /ኤፌ.፪፡፮/፣ ወደ ቀደመው ቦታው ወደ ቀደመው ክብሩ ይመልሰው ዘንድ ፍጹም ሰው ኾነ፡፡ በቸርነቱ በይቅርታው ብዛት አዳምን ወደ ቀደመው ቦታ ከመለሰው ልጅሽ ጽንዕት በድንግልና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሣን ለምኚልን፡፡
፱. የድንግል ክብሯ ሊናገሩት አይቻልም፡፡ ከእናንተ መካከል፡- “ይኸው እየተናርን አይደለምን?” የሚል ሊኖር ይችላል፡፡ እኛም እንዲህ ብለን እንመልስለታለን፡- “ለርሷ እንደሚገባ አድርጎ መናገር የሚቻለው የለም” ሲል ነው፡፡ “ለምን?” ጌታ መርጧታልና፡፡ አሁንም ከእናንተ መካከል፡- “ታድያ እርሱ ከመረጣትማ ምን ይደንቃል?” የሚል ሊኖር ይችላል፡፡ እኛም እንዲህ ብለን እንመልስለታለን፡- አባ ሕርያቆስ በቅዳሴ ማርያም ላይ፡ “በአማን ነጸረ እግዚአብሔር አብ እምሰማይ ምሥራቀ ወምዕራበ ሰሜነ ወደቡበ ወውስተ ኵሉ አጽናፍ አስተንፈሰ ወአጼነወ ወኢረከበ ከማኪ ወሠምረ መዐዛ ዚአኪ ወአፍቀረ ሥነኪ ወፈነወ ኀቤኪ ወልዶ ዘያፈቅር - እግዚአብሔር አብ በሰማይ ኾኖ ምሥራቅንና ምዕራብን ሰሜንንና ደቡብን ዳርቻዎችን ኹሉ በእውነት ተመለከተ፤ ተነፈሰ፤ አሻተተም፤ እንዳንቺ ያለ አላገኘም፡፡ የአንቺ መዐዛ ወደደ፤ የሚወደውን ልጁንም ወደ አንቺ ላከ” ብሎ እንደተናገረው እንድትመረጥ ኾና ተገኝታለችና ነው /ቅዳ.ማር.ቁ.፳፬/፡፡
ሐዋርያው “ማንም ሊቀርበው በማይችል ብርሃን ይኖራል” እንዲል /፩ኛ ጢሞ.፮፡፲፮/ በመመርመር ገንዘብ በማድረግ የሚቀርበው በሌለው ብርሃን ባሕርዩ አድሮ የሚኖረ እርሱ /ሃይ.አበ.፴፫፡፫/ ሰው ኾኖ በማኅፀንዋ አደረ /ዮሐ.፩፡፲፬/፡፡ ዘጠኝ ወር ከአምስተ ቀን በማኅጸንዋ ኖረ፡፡ ሰውም ከመኾኑ አስቀድሞ ሰውም ከኾነ በኋላ የማይመረመር እርሱን ማኅተመ ድንግልናዋ ሳይለወጥ ወለደችው፡፡ ሰውም ከመኾኑ አስቀድሞ ሰውም ከኾነ በኋላ ከማይመረመረው ልጅሽ ጽንዕት በድንግልና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሣን ለምኚልን፡፡
፲. ነቢዩ ዳንኤል ያየውና እጅ ሳይፈነቅለው ከረጅም ተራራ የወረደው ደንጊያ /ዳን.፬፡፩-፴፭/ ከአብ ዘንድ የወጣው አካላዊ ቃል ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡ ያ ድንጋይ የሰው እጅ ሳይነካው ከረዥሙ ተራራ እንደተፈነቀለ ኹሉ አካላዊ ቃል ኢየሱስ ክርስቶስም ከሰማየ ሰማያት ወርዶ ዘር ምክንያት ሳይኾነው ከድንግል ተወለደ፡፡ ዳንኤል በአምሳለ እብን (ደንጊያ) ካየው ልጅሽ ጽንዕት በድንግልና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሣን ለምኚልን፡፡
፲፩. ሐሩረ ፀሓይ ያልወደቀባት፣ ነፋስ ያልወዘወዛት፣ ለታብቁል (ታብቅል) ባለው ቃል ከልምላሜ፣ ከጽጌ፣ ከፍሬ የተገኘች ዐፅቀ ሠሉስ (የማግሰኞ ቅርንጫፍ) አንች ነሸ /ኩፋ.፪፡፲፪/፡፡ እንዲህ ማለቱ ነው፡- “በዕለተ ሠሉስ የተገኙ ቅጠሎች፣ ቅርንጫፎች ፀሐይ እንዳላጠወለጋቸው፣ ነፋስ እንዳልወዘወዛቸው ኹሉ አንቺም የኃጢአት ፀሐይ አልለወጠሽም፡፡ በሥጋሽ፣ በነፍስሽ፣ በኅሊናሽም ድንግል ነሽ እንጂ” /መጋቤ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ፣ ነገረ ማርያም በብሉይ ኪዳን፣ ክፍል ፩፣ ገጽ ፲/፡፡ አባ ጊዮርጊሥም፡- “በበደል ምሣር የማትቈረጪ፣ ከኀጢአት ዐውሎ ነፋስ የተነሣ የማትነዋወጪ፣ ዘወትር ፍጹም የምትለመልሚ፣ በዘመኑ ኹሉ የምታፈሪ፣ በወሮች ኹሉ የምትለቀሚ፣ ከዕፅዋት ኹሉ ይልቅ የምታምሪ እመቤቴ ማርያም ሆይ! የተባረክሽ ዕፅ ነሽ” ይላታል /እንዚራ ስብሐት፣ ገጽ ፲፬/፡፡ አምላክን የወለድሽ ንጽሕት፣ በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ ኅትምት የምትኾኝ ሆይ! ኢየሱስ ክርስቶስ እኛን ስለ ማዳን ሰው ኹኗልና (አካላዊ ቃልን ወልደሽልናልና) የሃይማኖትም (የክርስቶስም) ሙዳይ (መገኛ) ነሽ፡፡ (በልጅሽ ላመኑ) የአባቶቻችን የቀናች ሃይማኖታቸው ነሽ፡፡ እኛን ስለማዳን ሰው ከኾነ ልጅሽ ፅንዕት በድንግልና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሣን ለምኚልን፡፡
፲፪. የከበርሽ አምላክን የወለድሽ ሆይ! የማይመረመር ቃልን የወሰንሺው የብርሃን እናቱ አንች ነሽ፡፡ እርሱንም ከወለድሽው በኋላ ማኅተመ ድንግልናሽ ሳይለወጥ ኖረሻልና በአፍኣ በውስጥ በሥጋ በነፍስ ያከብሩሻል፤ ያገኑሻል፡፡ እንዲህ ካለ ልጅሽ ጽንዕት በድንግልና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሣን ለምኚልን፡፡
@Ethiopian_Orthodox
፲፫. ወዮ! ስለ አንቺ ድንቅ ኾኖ የሚነገረውን ነገር መናገር የሚቻለው ምን አንደበት ነው? ቅድመ ዓለም ያለ እናት ተወልዶ፣ ድኅረ ዓለም ያለ አባት እንደምን እንደወለደሽው መናገር የሚቻለው ምን አንደበት ነው? የአካላዊ ቃል እናቱ ንጽሕት ደንግል ሆይ! ኪሩቤል ለሚሸከሙት ለንጉሥ ማደሪያ ኾንሽ፡፡ ንዕድ ክብርት ሆይ! እኛም ክብርሽን ገናንነትሽን ዕፁብ ዕፁብ እያልን እናመሰግንሻለን /ሉቃ.፩፡፵፰/፡፡ የአካላዊ ቃል እናቱ መልካሟ ርግብ (ርግበ ኖኅ) ማርያም ሆይ! ስምሽን በትውልደ ሴም፣ በትውልደ ካም፣ በትውልደ ያፌት እንጠራለን፡፡ ሊቁ እመ አምላክን “መልካሟ ርግብ” አላት፡፡ ይኸውም የኖኅ ርግብ “የጥፋት ውሃ ጐደለ፤ የጥፋት ውሃ ተገታ፤ ከእንግዲህ ወዲህ ሰላም ነው” ስትል የምሥራቹን የዘይት ቅጠል ይዛ እንደታየች ኹሉ /ዘፍ.፰፡፲፩/ እመቤታችንም “የኀጢአት ውሃ ጐደለ፤ የመርገም ውሃ ተገታ፤ ከእንግዲህ ወዲህ ዘመነ ሰላም ነው” ስትል ዓመተ ፍዳ ዓመተ ኩነኔን ኣሳልፎ ዓመተ ምሕረትን የተካ፣ ለዓለሙ ኹሉ ታላቅ የምሥራች የኾነ፣ የዓለም መድኃኒት ክርስቶስን ወልዳልናለችና፡፡ እንዲህ ካለ ልጅሽ ጽንዕት በድንግልና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሣን ለምኚልን፡፡
የዕለተ ሰንበት ውዳሴ ማርያም ትርጓሜ በድምፅ፡፡👉mp3 format
እነሆ የየዕለቱን የውዳሴ ማርያም ትርጓሜ በድምጽ እናስቀምጣለን፡፡ ይከታተሉን!
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
መሶበ ወርቅ አንቺ ነሽ፡፡ መና የተባለውም መለኮት የተዋሐደው ሥጋው ነው” ብሏል፡፡ ኅብስተ ሕይወት ከሚባል ልጅሽ ጸንዕት በድንግልና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሣን ለምኚልን፡፡
፭. እንቲ ውእቱ ተቅዋም ዘወርቅ እንተ ፆርኪ ማኅቶተ ፀዳል ኩሎ ጊዜ። ዘውእቱ ብርሃኑ ለዓለም። ብርሃን ዘእምብርሃን ዘአልቦ ጥንት። አምላክ ዘእምአምላክ ዘበአማን። ዘተሰብአ እምኔኪ ዘእንበለ ውላጤ። ወበምጽአቱ አብርሃ ላዕሌነ ለእለ ንነብር ዉስተ ጽልመት ወጽላሎቱ ሞት። ወአርአትዐ እገሪነ ዉስተ ፍኖተ ሰላም በምሥጢረ ጥበቡ ቅዱስ። ሰአሊ ለነ ቅድስት።
ብርሃንነት ያለውን ፋና የተሸከምሽ የወርቅ ተቅዋም (መቅረዝ) አንቺ ነሽ /ዘጸ.፳፭፡፴፩-፵/፡፡ ይኸውም ፋና ለሰው ኹሉ ዕውቀትን የሚገልጽ ብርሃን ነው፡፡ ጥንት ከሌለው ከብርሃን የተገኘ ብርሃን ነው፡፡ ከባሕርይ አምላክ የተገኘ የባሕርይ አምላክ ነው፡፡ ሳይለወጥ ካንቺ ሰው የኾነው ነው፡፡ ሰውም በመኾኑም በድንቁርና በቀቢጸ ተስፋ ለምንኖር ለኛ አበራልን (ዕውቀትን ገልጸልን)፡፡ በጥበቡ ባደረገው ሥጋዌ እግረ ልቡናችንን ወደ ሕገ ወንጌል ጎዳና አቀናልን /ኢሳ.፱፡፩-፪፣ ማቴ.፬፡፲፬-፲፮/፡፡ ታላቁ የዜማ አባት ሊቁ ቅዱስ ያሬድም፡- “አንቲ ውእቱ ተቅዋም ዘወርቅ ዘኢገብራ እደ ኬንያ ዘሰብእ… - የብልሐተኛ እጅ ያልሠራት በውስጧም መብራት የሚያበሩባት የወርቅ መቅረዝ አንቺ ነሽ፤ ራሱ የአብ ብርሃን ያበራባታል እንጂ፡፡ ከብርሃን የተገኘ ብርሃን ወደ አንቺ መጥቶ አደረ፡፡ አምላክነቱም በዓለም ኹሉ አበራ፡፡ ጨለማን ከሰዎች ላይ አራቀ፡፡ እኔ የዓለም ብርሃን ነኝ፤ በብርሃኔ እመኑ፤ ብርሃን ሳለላችሁ ተመላለሱ ብሎ በሚያድን ቃሉ አዳነን” ብሏል /ቁ.፰፣ ዮሐ.፲፪፡፴፭፣ ፩ኛ ዮሐ.፩፡፭/፡፡ በጥበቡ ባደረገው ሥጋዌ እግረ ልቡናችንን ወደ ሕገ ወንጌል ጎዳና ከአቀናልን ልጅሽ ጽንዕት በድንግልና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሣን ለምኚልን፡፡
፮. አንቲ ውእቱ ማዕጠንት ዘወርቅ። እንተ ፆርኪ ፍሕመ እሳት። ብሩክ ዘነሥአ እመቅደስ ዘይሠሪ ኃጢአተ ወይደመሰስ ጌጋየ። ዝ ውእቱ ዘእግዚአብሔር ቃል ዘተሰብአ እምነኪ ዘአዕረገ ለአቡሁ ርእሶ ዕጣነ ወመሥዋዕተ ሥሙረ። ሰአሊ ለነ ቅድስት።
ቡሩክ አሮን ከቤተ መቅደስ ይዞሽ የወጣ እሳትነት ያለውን ፍሕም የተሸከምሽ ማዕጠንተ ወርቅ አንቺ ነሽ /ዘጸ.፴፡፩-፰/፡፡ ፍሕም የተባለውም በአፍኣ በውስጥ በሥጋ በነፍስ ኃጢአትን የሚያስተሠርይ ነው፡፡ ይኸውም ከአንቺ ሰው የኾነውና “ወአንከረ አብ እምዝንቱ መሥዋዕት - ከዚህ መሥዋዕት የተነሣ አብ አደነቀ” እንዲል /ሃይ.አበ.፷፰፡፳፫/ ለአባቱ ራሱን ያማረ የተወደደ መሥዋዕት አድረጎ ያቀረበ አካላዊ ቃል ነው /ኤፌ.፭፡፪/፡፡ ራሱን ያማረ የተወደደ መሥዋዕት አድርጎ ካቀረበ ልጅሽ ጽንዕት በድንግልና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሣን ለምኚልን፡፡
፯. ተፈሥሒ ኦ ማርያም ርግብ ሠናይት። ዘወለድኪ ለነ ዘእግዚአብሔር ቃለ። አንቲ ውእቱ ጽጌ መዓዛ ሠናይ እንተ ሠረፀት እምሥርወ ዕሤይ፡ ሰአሊ ለነ ቅድስት።
አካላዊ ቃልን የወልድሽልን መልካም ርግብ ማርያም ሆይ! ደስ ይበልሽ፡፡ ከእሴይ ሥር የወጣሽ መዓዛ ሠናይ አበባ አንቺ ነሽ፡፡ መዐዛ ሰናይ የተባለውም የቅዱሳን መዐዛ የሚኾን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው /መጽሐፈ ድጓ፣ ገጽ.፻፺፱/፡፡ መዐዛ ሠናይ ከተባለ ልጅሽ ጽንዕት በድንግልና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሣን ለምኚልን፡፡
፰. በትረ አሮን እንተ ሠረፀት ዘኢንበለ ተክል ወኢሠቀይዋ ማየ። ከማሃ አንቲኒ ኦ ወላዲተ ክርስቶስ አምላክነ ዘበአማን ዘእንበለ ዘርእ መጽአ ወአድኅነነ። ሰአሊ ለነ ቅድስት።
ሳይተክሏት የበቀለች፣ ውሃ ሳያጠጧትም የለመለመች ያበበች ፲፪ በኵረ ሎሚ ያፈራች የአሮን በትር ነበረች /ዘኁ.፲፯፡፩-፲/፡፡ ከቤተ መቅደስ ፲፪ ዓመት ኑረሽ፣ ዘር ምክንያት ሳይኾነው ሰው ኾኖ ያዳነን እውነተኛ አምላካችንን ክርስቶስን የወለድሽልን አንቺም እንደርሷ ነሽ /ኢሳ.፯፡፲፬/፡፡ አባ ጊዮርጊሥ ዘጋሥጫም በአርጋኖን ዘሰኑይ ላይ፡- “ዕፀ ከርካዕ እንከ እሰምየኪ እስመ ከርካዕ ሠናየ ይጸጊ፤ ወሠናየ ይፈሪ፤ ወሠናየ ይጼኑ፤ ወከመ በትር ይቡስ ዘቦ ላዕሌሁ ወፅአ ዑፃዌ ክህነት አሥረጸ አዕጹቀ ወአቊጸለ ከርካዕ ምዑዘ፤ ወከማሁ አንቲኒ ነበርኪ ውስተ ቤተ መቅደስ ዐሠርተ ወክልኤተ ክራማተ ወፀነስኪዮ ለኢሱስ ዘእንበለ ዘርዐ ብእሲ - እንግዲህ የሎሚ ዕንጨት ብዬ እጠራሻለሁ፡፡ ሎሚ መልካሙን ያብባል፤ መልካሙን ፍሬ ያፈራል፡፡ በጐ በጐ ይሸታልና ዕጣ እንደ ወጣበት ደረቅ በትር ሳይተከል በቤተ መቅደስ ለምልሞ፣ ቅንጣት አውጥቶ፣ አብቦ ተገኘ፡፡ ሽታው ያማረ የተወደደውን ሎሚ አፈራ፡፡ እንዲሁም አንቺ በቤተ መቅደስ ዐሥራ ኹለት ዓመት ተቀምጠሸ ያለ ወንድ ዘር መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ፀነስሺው” በማለት አብራርቶታል፡፡ ዳግመኛም ሊቁ ቅዱስ ያሬድ፡- “ሳይተክሏትና ውሃ ሳያጠጧት የለመለመች የአሮን በትር በቤተ መቅደስ ነበረች፡፡ ለካህናት ዝግጁ ያደረጋት ነበረች፡፡ አንቺም በቅድስናና በንጽሕና ጸንተሸ እንደ እርሷ በቤተ መቅደስ ኖርሽ፡፡ ከቤተ መቅደስም በክብር በታላቅ ደስታ ወጣሽ፡፡ በእውነት የሕይወት ፍሬ የኾነ ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ከአንቺ ተገኘ፡፡ ቅድስት ሆይ! ከመልአኩ እንደተረዳሽው ከወንድ ያለመገናኘት ልጅን አገኘሽ፡፡ መልአኩ መንፈስ ቅዱስ መጥቶ ያድርብሻል፤ የልዑል ኀይልም ይጸልልሻል ብሎ ነግሮሽ ነበርና” በማለት አማናዊቷ የአሮን በትር እርሷ መኾኗን አስተምሯል /ቁ.፲፩/፡፡ ሰው ኾኖ ካዳነን ልጅሽ ጽንዕት በድንግልና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሣን ለምኚልን፡፡
፱. ለኪ ይደሉ ዘእምኩሎሙ ቅዱሳን ተስአሊ ለነ ኦ ምልእተ ጸጋ አንቲ ተዐብዮ እምሊቃነ ጳጳሳት ወፈድፍደ ትከብሪ እምነቢያት ብኪ ግርማ ራእይ ዘየዐቢ እምግርማ ሱራፌል ወኪሩቤል። አንቲ በአማን ምክሐ ዘመድነ ወሰአሊት ሕይወተ ለነፍሳቲነ ሰአሊ ለነ ኅበ እግዚእነ ወመድኃኒነ ኢየሱስ ክርስቶስ። ያፅንዐነ በርትዕት ሃይማኖት ዉስተ አሚነ ዚአሁ። ይጽግወነ ሣህሎ ወምሕረቶ። ይሥረይ ኃጢአተነ በብዝኅ ምሕረቱ፡ ሰአሊ ለነ ቅድስት።
ምልዕተ ክብር ሆይ! ከቅዱሳን ኹሉ ይልቅ ትለምኚልን ዘንድ ላንቺ ይጋባል፡፡ ከሊቃነ ጳጳሳት አንቺ ትበልጫለሽ፡፡ ከመምህራን፣ ከሐዋርያት፣ ከ፸ አርድእትም አንቺ ትበልጫለሽ፡፡ ከሱራፌልና ከኪሩቤል ይልቅ የሚበልጥ የመወደድ የመፈራት ግርማ አለሽ፡፡ ሊቁ አባ ሕርያቆስም በቅዳሴው፡- “ኦ ሙኃዘ ፍስሐ! ፈድፋደ ብኪ ግርማ ራዕይ ዘየዐቢ እም ኪሩቤል እለ ብዙኃት አዕይንቲሆሙ ወሱራፌል ፮ ክነፊሆሙ - የደስታ (የጌታ) መገኛ የምትኾኚ እምቤታችን ሆይ! ዐይናቸው ብዙ ከሚኾን ከኪሩቤል፣ ክንፋቸው ስድስት ከሚኾን ከሱራፌል ይልቅ በምእመናን ዘንድ የመወደድ፣ በአጋንንት በአይሁድ በመናፍቃን ዘንድ የመፈራት፣ በሥላሴ ዘንድም የባለሟልነት መልክ አለሽ” ይላል /ቁ.፳፪/፡፡ በእውነት የባሕርያችን መመኪያ አንቺ ነሽ፡፡ ለሰውነታችን ሕይወትን የምታማልጅን አንቺ ነሽ፡፡ አንድነቱን ሦስተነቱን በማመን አጽንቶ ሥጋዌውን በማመን ያፀናን ዘንድ፣ “ጸጋሰ ሥርየተ ኃጢአት ይእቲ” እንዲል በቸርነቱ ብዛት ኃጢአታችንን ያስተሠርይልን ዘንድ ከጌታችን ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ዘንድ አማልጅን፡፡ ኃጢአታችንን ከሚያስተሠርይልን ልጅሽ ጽንዕት በድንግልና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሣን ለምኚልን፡፡
የዕለተ ቅዳሜ ውዳሴ ማርያም ትርጓሜ በድምፅ፡፡👉mp3 format
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
፩. ንጽሕት ነሽ፤ ብርህት ነሽ፡፡ በአፍአ በውስጥ ንጽሕት ነሽ፡፡ ሊቁ “ዲያተሳሮን” በተባለው የወንጌል ትርጓሜ መጽሐፉ የእመቤታችንን ንጽሕና ሲናገር፡- “የማርያም ሰውነት የምድር ላይ መቅደስ ነው፡፡ በዚሁ መቅደስም ከእግዚአብሔር ዘንድ የተላከ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል በኀጢአት፣ በሞትና በርግማን ፈንታ የበረከትን ዘር ሊዘራ መጣ፡፡ የኤልሳቤጥም ሰላምታ ይህንን አረጋገጠ፡፡… አንተና እናትህ ብቻ በማንኛውም ረገድ ንጹሐን ናችሁ፡፡ ጌታ ሆይ! በአንተ ውስጥ ምንም ነቅዕ የለም፤ በእናትህም ውስጥ ምንም ምልክት የለም” ብሏል /St. Ephrem the Syrian, Commentary on Tatian’s Diatesaron, pp 91-92/፡፡
ጌታን በማኽል እጅሽ የያዝሽው ሆይ! ምልዕተ ክብር ሆይ! (ተፈስሒ) ደስ ይበልሽ እያሉ ፍጥረት ኹሉ ከአንቺ ጋር ደስ ይላቸዋል፡፡ እግዚአብሔር ከሥጋሽ ሥጋ ከነፍስሽ ነፍስ ነሥቶ ከአንቺ ጋር አንድ ባሕርይ ቢኾን ባለሟልነትን አግኝተሻልና (ተፈስሒ) ደስ ይበልሽ፡፡ ግርምት ድንግል ሆይ! ክብርሽን ገናንነትሽን ዕፁብ ዕፁብ እያልን እናመሰግናለን (እናደንቃለን)፡፡ ከማኅፀንሽ ፍሬ የባሕርያችን ድኅነት ተገኝቷልና ከመልአኩ ጋር እንደ መልአኩ ምስጋና እናቀርባለን፡፡ የማኅፀንሽ ፍሬ ከአባቱ ጋር አስታርቆናልና እንደ መልአኩ ምስጋና እናቀርብልሻለን፡፡ ሊቁ ቅድም በጠቀስነው መጽሐፉ፡- “… መልአኩ ወደ አንዲት ድንግል ተላከ፡፡ ወደ እርሷ ገብቶም “እነሆ ድንግልናሽ ሳይነዋወጽ ትፀንሻለሽ፤ ወንድ ልጅም ትወልጃለሽ፤ ስሙንም ኢየሱስ ትዪዋለሽ” አላት/ሉቃ.፩፡፴፩//፡፡ ይኸውም በሥጋ ተገልጦ ሊመጣ ስላለው ስለ አካላዊ ቃል ሲናገር ነው፡፡ ሲነግራት “ስሙንም ኢየሱስ ትዪዋለሽ” አላት እንጂ “ኢየሱስ የተባለው” እንዳላላት ልብ በሉ፡፡ ይኸውም የሰው ልጆች ወልደ እግዚአብሔር በለበሰው ሥጋ የሚድኑበት ስም መኾኑን የሚያመለክት ነው፡፡ ምክንያቱም ኢየሱስ ማለት በዕብራይስጥ “መድኅን” ማለት ነውና፡፡ መልአኩ “ስሙንም ኢየሱስ ትዪዋለሽ” ሲላት መድኅን ትዪዋለሽ ማለቱ ነው፡፡ ለምን? ሕዝቡን ኹሉ ከኃጢአታቸው ያድናቸዋልና” ብሏል /ማቴ.፩፡፳፩/፡፡ ከአባቱ ጋር ካስታረቀን ልጅሽ ፅንዕት በድንግልና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሣን ለምኚልን፡፡
፪. አባ ሕርያቆስ፡- “እግዚአብሔር አብ በሰማይ ኾኖ ምሥራቅንና ምዕራብን ሰሜንና ደቡብን ዳርቻዎችንም ኹሉ በእውነት ተመለከተ፤ እንደ አንቺ ያለ አላገኘም፡፡ የአንቺን መዓዛ ወደደ፤ የሚወደው ልጁንም ወደ አንቺ ሰደደ” እንዲል /ቅዳ.ማር. ቁ.፳፬/ እንደ ሰርግ ቤት አደፍ ጉድፍ የሌለብሽ ኾነሽ ቢያገኝሽ መንፈስ ቅዱስ አድሮብሻልና፤ ኃይለ ልዑል ወልድም ሥጋሽን ለብሷልና አንድም መንፈስ ቅዱስ ከሦስቱ ግብራት ከልክሎሻልና ኃይለ ልዑል ወልድም ከሦስቱ ግብራት ከልሎሻልና ለዘለዓለሙ ጸንቶ የሚኖር አካላዊ ቃልን ወለድሽልን /ሃይ.አበ.፻፲፡፳፱/፡፡ ሰው ኾኖ ከኃጢአት አዳነን /ማቴ.፩፡፳፩/፡፡ ሰው ኾኖ ከኃጢአታችን ፍዳ ካዳነን ልጅሽ ፅንዕት በድንግልና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሣን ለምኚልን፡፡
፫. መድኃኒታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን በሥጋ ወልደሽልናልና ከዳዊት ሥር የተገኘሽ ባሕርይ አንቺ ነሽ /ሉቃ.፩፡፴፪/፡፡ ቅድመ ዓለም የነበረ፣ ከአብ ባሕርይ ዘእም ባሕርይ አካል ዘእም አካል የተወለደ፣ ተቀዳሚ ተከታይ (ታላቅም ታናሽም) የሌለው አካላዊ ቃል ባሕርዩን በሥጋ ሠወረ፡፡ ከአንቺም አርአያ ገብርን ነሣ /ፊል.፪፡፯/፡፡
ከእናንተ መካከል፡- “አካላዊ ቃል አርአያ ገብርን ነሥቶ (የባሪያን መልክ ይዞ) በሰውም ምሳሌ ኾኖ ራሱን ባዶ አደረገ ሲል ምን ማለት ነው?” ብሎ የሚጠይቅ ሊኖር ይችላል፡፡ እኛም እንዲህ ብለን እንመልስለታለን፡- ራሱን ባዶ አደረገ ሲል የእኛን ባሕርይ ገንዘብ ባደረገ ጊዜ ባሕርየ መለኮቱ ተለውጧል ማለት አይደለም፡፡ ባሕርየ መለኮቱን ትቶ መጣ ማለትም አይደለም፤ በፈቃዱ ደካማ ባሕርያችንን ገንዘብ አደረገ ማለት ነው እንጂ፡፡ ወልደ እግዚአብሔር ራሱን ባዶ ያደረገው በመቅድመ ወንጌል “ከጥንት ዠምሮ በባሕርያችን እስኪሠለጥን ድረስ ሰይጣን በተንኰል በሥጋ ከይሲ እንደተሠወረ፤ እኛም ከፍዳ መዳናችን ቃለ እግዚአብሔር በባሕርያችን በመሠወሩ ኾነ” ተብሎ እንደተጻፈ የእኛን ባዶነት በጸጋው ለመሙላት ነው፡፡ ሰው የኾነው እኛን አማልክት ዘበጸጋ ያደርገን ዘንድ ነው፡፡” የባሪያውን መልክ ይዞ በሰውም ምሳሌ ኾኖ ስለ እኛ ብሎ ራሱን ባዶ ካደረገ ልጅሽ ፅንዕት በድንግልና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሣን ለምኚልን፡፡
፬. አደፍ ጉድፍ ሳይኖርብሽ አምልክን የወለድሽው እመቤታችን ሆይ! በኃጢአት ብርድ የተያዘውን ዓለም ኃጢአቱን ያርቅለት ዘንድ ፀሐየ ጽድቅ ጌታ ከአንቺ ተወልዷልና፤ ነቢያት ይወርዳል ይወለዳል ብለው እንደተናገሩም ዘር ምክንያት ሳይኾንሽ፣ መለወጥ ሳያገኝሽ ወልደሸዋልና ከምድር በላይ ያለሽ ኹለተኛ ሰማይ አንቺ ነሽ፡፡ ኢትዮጲያዊው ቄርሎስም፡- “ኦ ሰማይ ዳግሚት ዘወለደቶ ለፀሐየ ጽድቅ ዘውእቱ ብርሃነ ቅዱሳን ዘሰደዶ ለጽልመት - ጨለማን ያሳደደውን (ያስወገደውን) የቅዱሳን ብርሃን የሚኾን አማናዊ ፀሐይን የወለደች ኹለተኛይቱ ሰማይ ሆይ! …” እያለ ያወድሳታል /አርጋኖን ዘረቡዕ/፡፡ ዘር ምክንያት ሳይኾንሽ ከወለድሽው ልጅሽ ፅንዕት በድንግልና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሣን ለምኚልን፡፡
@Ethiopian_Orthodox
፭. ከተለዩ የተለየሽ፣ ከከበሩ የከበርሽ በውስጧም ሕግ የተጻፈበት ኪዳን ያለብሽ የተሠወረ መና ያለበት መሶበ ወርቅ ያለብሽ ደብተራ (ድንኳን) አንቺ ነሽ /ዘጸ.፳፮፡፩-፴/፡፡ ይኸውም መና የተባለው ሰው ኾኖ በማኅፀንሽ ያደረው ወልደ እግዚአብሔር ነው፡፡ መተርጕማኑ ይህን የበለጠ ሲያብራሩት፡- “ድንኳኗ የእመቤታችን ምሳሌ፤ ቅድስት የነፍሷ፤ ቅዱሳን የሥጋዋ፤ ታቦቱ የመንፈስ ቅዱስ፤ ጽላት የልቡናዋ፤ ቃሉ በመንፈስ ቅዱስ የተገለጸላት ምሥጢር ምሳሌ ነው፡፡ አንድም ቅዱሳን የሥጋዋና የነፍሷ፤ ቅድስት የልቡናዋ፤ ታቦት የማኅፀኗ፤ ጽላት የትስብእት፤ ቃሉም የመለኮት ምሳሌ ነው” ይላሉ /ውዳሴ ማርያም ንባቡና ትርጓሜው፣ ገጽ ፻፸፬/፡፡ ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫም በአርጋኖን ዘሐሙስ ላይ፡- “ተፈሥሒ ኦ ደብተራ ብርሃን ማኅደሩ ለዐቢይ ሊቀ ካህናት - የታላቁ ሊቀ ካህናት ማደርያ የብርሃን ድንኳን ሆይ! ደስ ይበልሽ” በማለት የሊቀ ካህናት የባሕርይ አምላክ የክርስቶስ እናት አማናዊት ድንኳን መኾኗን አስተምሯል፡፡
አካላዊ ቃል ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ነሥቶ ሰው ኾነ፡፡ የክብር ባለቤት እርሱን በዚህ ዓለም ወለደችው፡፡ ለዘለዓለሙ ጸንቶ የሚኖር አካላዊ ቃል ሰው ኾኖ ከኃጢአታችን ፍዳ አድኖናልና ሰው ኾኖ ያዳነን የነባቢ በግዕ (የሚናገር በግ የክርስቶስ) እናቱ ደስ ይላታል /ዮሐ.፩፡፳፱/፡፡ ለዘለዓለሙ ጸንቶ የሚኖር አካላዊ ቃል ሰው ኾኖ ከኃጢአታችን ፍዳ ካዳነን ልጅሽ ፅንዕት በድንግልና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሣን ለምኚልን፡፡
የዕለተ አርብ ውዳሴ ማርያም ትርጓሜ በድምፅ፡፡👉mp3 format
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
የኾነው የተደረገው ኹሉ የእግዚአብሔር ድንቅ ሥራ መኾኑን አውቋል፡፡ ኾኖም ግን ሌሎች በዙርያ ያሉ ሰዎች ይህን ነገር ሊያምኑት ስለማይችሉ በስውር መተው የተሻለ የጽድቅ ሥራ መስሎ ታየው፡፡ ይኸውም በግብር እንዲገናኛት ሳይኾን እንዲያገለግላት፣ እንዲጠብቃት የሰጡት ካህናት ይህን የእግዚአብሔር ሥራ ሊያምኑት እንደማይችሉ ስለሚያውቅ ነው፡፡ “የመለኮታዊው ልጅ አባት ነኝ ብል ኃጢአት ነው” በማለት በስውር ሊተዋት አሰበ፡፡ ልጇ (ክርስቶስ) በድንግልና የተፀነሰ በድንግልናም የሚወለድ መኾኑን ቢያውቅም ይህን የሚጠረጥሩ ሰዎች እንዳይኖሩ ከእርሷ ተለይቶ መኖርን ፈራ፡፡ መልአኩም መጥቶ “ኢትፍራህ ነሢኦታ ለማርያም ፍኅርትከ - ማርያምን ለመውሰድ አትፍራ” አለው፡፡ ወንጌላዊው ማቴዎስም ከዚያ በኋላ በጽድቅ በንጽሕና ከእርሱ ጋር እንደኖረች ዮሴፍም እንደወሰዳት ይነግረናል፡፡ ለዚህም ነው ካህናት በኋላ ዘመን ሊቀ ካህናቱ ዘካርያስን እመቤታችን ድንግል ናት ስላለ ወግረው የገደሉት፡፡ ዳግመኛም ካህኑ ዘካርያስ ጌታችን እንደተናገረው በቤተ መቅደስ ውስጥ እንዲገደል ያደረጉት፡ ሕፃናት በሄሮድስ ትዕዛዝ በሚገደሉበት ሰዓት ልጁ ዮሐንስን በድንግልና ተፀንሶ በድንግልና ስለሚወለደው ክርስቶስ ምስክር እንዲሰጥ ወደ በረሐ እንዲሸሽ በማድረጉ ነው /ማቴ.፳፫፡፴፭/፡፡
አንዳንድ ልበ ስሑታን እመቤታችን ጌታን ከወለደች በኋላ ከዮሴፍ ጋር በግብር ተገናኝታለች ለሚሉን እንዲህ ብለን እንመልስላቸዋለን፡- “ያቺ ማኅደረ መለኮት የኾነች ድንግል፣ ያቺ መንፈስ ቅዱስ የጸለለባት እመቤት እንደምን ሟች ከኾነ ዕሩቅ ብእሲ ጋር ተመልሳ በግብር ትገናኛለች ተብሎ ይታሰባል? እንደምንስ ዳግም በምጥ በጋር ትወልድ ዘንድ በግብር ተዋውቃለች ተብሎ ይታሰባል? እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከሴቶች ኹሉ ተለይታ ንዕድ ክብርት መኾኗን መልአኩ ከተናገረ ከጥንት (ከእናቷ ማኅፀን) አንሥቶ ከመርገመ ሥጋ ከመርገመ ነፍስ ንጽሕት ነበረች ማለት ነው፡፡ ይህም ብቻ ሳይኾን በምጥ በጋር ከመውለድ የተለየች ናት ማለት ነው፡፡ ስለዚህ እመቤታችን ዳግመኛ ከዮሴፍ ጋር በግብር ተዋውቃ በምጥ በጋር ትወልዳለች ተብሎ ፈጽሞ ሊታሰብ አይገባውም፡፡ በሰብአ ትካት ጊዜ ከኖኅ ጋር ወደ መርከብ የገቡ እንስሳት ስንኳ ከግብር የተለዩ ከነበሩ አማኑኤልን በግብር በማኅፀኗ የተሸከመች እመቤታችንማ ፈጽማ እንዲህ በግብር ተዋውቃለች ተብሎ ሊታሰብ አይገባውም፡፡ ከመርከቡ ውስጥ ከኖኅ ጋር የነበሩ እንስሳት በግብር ያልተዋወቁት ኖኅ ከልክሏቸው ነው፤ እመቤታችን ግን ከዚህ ግብር የተለየችው በፈቃዷ ነው፡፡ በንጽሕና በቅድስና እንደወለደች ኹሉ ንጽሕናዋና ቅድስናዋም እንደዚያ ኾኖ እንዲዘልቅ ፈቃዷ ነበር፡፡
የአሮን ልጆች እግዚአብሔር ያላዘዘውን እሳት በእግዚአብሔር ፊት በማቅረባቸው በሞት ከተቀጡ /ዘሌ.፲፡፩-፪/ እመቤታችንማ እንዴት? ወይንን የሚነግዱ ሰዎች በወይኑ ላይ ውኃ ቢጨምሩበት ቅጣታቸው የበዛ ከኾነ እምቤታችንማ እንዴት? አንዳንድ ሰዎች የጌታ ወንድሞች ተብለው የሚጠሩ ልጆች ስላሉ እመቤታችን የወለደቻቸው ይመስላቸዋል፡፡ ነገር ግን ጌታችንም የዮሴፍ ልጅ መባሉን ሊያስተውሉ ይገባል፡፡ ይህም አይሁድ ብቻ ሳይኾን እመቤታችንም እንዲህ አድርጋ ትናገር ነበር፡፡ “እስመ ናሁ አቡከኒ ወአነኒ ሠራሕነ እንዘ ነሐሥሠከ- እነሆ አባትህና እኔ እየተጨነቅን ስንፈልግህ ነበርን” እንዲል /ሉቃ.፪፡፵፰/፡፡ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ዮሴፍ እመቤታችንን ወደ ቤቱ እንዲወስዳት የነገረው አንደኛው፡ በሐሰት ሊከሷት የሚችሉትን ስዎች ጥርጣሬ እንዳይኖራቸው ለማድረግ፤ በተለይ ደግሞ ከመልአኩ ፀንሳ ተገኘች ብለው ሊገድሏት ከሚችሉ ሰዎች ሊጠብቃት ነው፡፡ በእነዚህ ሰዎች ዘንድ አንድ የተለመደ ወሬ ነበር፡፡ ይኸውም “ድንግል በድንግልና ትወልዳለች፤ ድንግሊቱ በመውለዷ ምክንያትም ከተማይቱ ትጠፋለች፤ ክህነታችን ሀብተ ትንቢታችን ኹሉ ይወገዳል” የሚል ነው፡፡ ድንግል በድንግልና ፀንሳ በድንግልና እንድምትወልድ የተናገረው ኢሳይያስን በመጋዝ ተርትረው እንዲገደል ያደረጉት ለዚሁ ነበር /ኢሳ.፯፡፲፬/፡፡
ድንግሊቱ የበኵር ልጇን ወለደች፤ ነገር ግን ማኅተመ ድንግልናዋ አልተለወጠም፡፡ … የበኵር ልጇንም እስክትወልድ ድረስ (ዮሴፍ) በንጽሕና በቅድስና ከእርሷ ጋር ኖረ /ማቴ.፩፡፳፭/፡፡ ይህ ቃል የተነገረው ዮሴፍ እመቤታችንን ወደ ቤቱ ከወሰዳት በኋላ ነው፡፡ “ዮሴፍም ከእንቅልፉ ነቅቶ የጌታ መልአክ እንዳዘዘው አደረገ፤ እጮኛውንም ወሰደ” ብሎ ቀጥሎም “የበኵር ልጇንም እስክትወልድ ድረስ (በግብር) አላወቃትም” እንዲል /ማቴ.፩፡፳፬-፳፭/፡፡ በሌላ አገላለጽ ወደ ቤቱ ወሰዳት፤ ነገር ግን በግብር አልተዋወቁም ማለት ነው፡፡ ወደ ቤቱ የወሰዳት ከፀነሰች በኋላም ቢኾን እጮኛዋ ስለኾነ ነው፡፡ የበኵር ልጇንም እስክትወልድ ድረስ አላወቃትም ማለትም እንኳንስ በግብር ቀርቶ በሐሳቡም ከእመቤታችን ጋር ሌላ ነገር ለማድረግ አላሰበም ተብሎ ይተረጐማል፡፡ እስክትወልድ ድረስ ማለትም ሰዎች እመቤታችን የፀነሰችው በግብረ መንፈስ ቅዱስ እንጂ በዘርዐ ብእሲ እንዳልኾነ እንደተረዱ የሚያስገነዝብ ነው፡፡
ዳግመኛም የበኵር ልጇንም እስክትወልድ ድረስ አላወቃትም ማለት ምንም እንኳ እመቤታችንና ዮሴፍ በፈቃዳቸው በንጽሕና በቅድስና ለመኖር ቢያስቡም ጸጋ መንፈስ ቅዱስም ረድቶዋቸዋል ማለት ነው፡፡ ጌታችን ከተወለደ በኋላ ያለው ቅድስናቸው ግን የራሳቸው ነጻ ፈቃድ ነው፡፡
ወንጌላዊው ቅዱስ ማቴዎስ ጸጋ መንፈስ ቅዱስ በግብር እንዳይተዋወቁ ከልክሎዋቸው እንደነበርና ጌታ ከተወለደ በኋላ ግን በራሳቸው ምርጫ በንጽሕና በቅድስና እንደኖሩ ለመግለጽ “እስከ” በሚለው ቃል ነግሮናል፡፡ የበኵር ልጇን እስክትወልድ ድረስ በንጽሕና በቅድስና አብሯት ኖሯል፡፡ እንግዲህ እስከ የሚለው ቃል ስለተጠቀሰ ዮሴፍ ከዚያ በኋላ በግብር አውቋታል ተብሎ ድምዳሜ ሊወሰድ ይችላልን? እስከ የሚለው ቃል መጨረሻ የሌለው እስከ ነው፡፡ “ጌታ ጌታዬን፡- ጠላቶችህን የእግርህ መረገጫ እስካደርግልህ ድረስ በቀኜ ተቀመጥ አለው” ተብሎ ስለተጻፈ /መዝ.፻፲፡፩/ ጌታ ጠላቶቹ በእግሩ መረገጫ ከኾኑ በኋላ ይነሣል ማለት ነውን? … ከእናንተ መካከል “የጌታችን ወንድሞች እኮ ስማቸው በወንጌል የተጠቀሰ ነው!” የሚለኝ ቢኖር እኔም እንዲህ ብዬ እመልስለታለሁ “ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀሉ ሥር ለሚወደው ደቀ መዝሙር (ለዮሐንስ) የሰጣት ስለኾነ እነዚህ ልጆች ልጆቿ እንዳልኾኑ፣ ዮሴፍም ባሏ እንዳልኾነ ግልጽ ነው” /ዮሐ.፲፱፡፳፯/፡፡ እናትና አባትህን አክብር ብሎ ሕግን የሠራ ጌታ እንደምን እመቤታችንን ከልጆቿ አለያይቶ ለዮሐንስ ይሰጣታል ተብሎ ይታሰባል?” /St. Ephrem the Syrian, Commentary on Tatian’s Diatesaron, pp 60-64/፡፡
ቅድመ ዓለም የነበረ እርሱ ሰው ኹኗልና (ካንቺ ተወልዷልና) የእኛን ሥጋ ነሥቶ የርሱን ሕይወት ሰጥቶ ከርሱ ጋራ አስተካከለን፡፡ በቸርነቱ ብዛት እንድንመስለው አደረገን /ፊል.፫፡፲-፲፩/፡፡ ከብዙ ሴቶች አንቺ ትበልጫለሽ፡፡ ክብር የክብር ክብር ካላቸው ከብዙ ሴቶች አንቺ ትበልጫለሽ /ሉቃ.፩፡፳፰/፡፡ ንጉሥ በከተማው እንዲኖር ዘጠኝ ወር ካምስት ቀን ማኅፀንሽን ዓለም አንድርጎ ኖሮብሽልና አምላክን የወለድሽ ድንግል ማርያም ሆይ! ልዑል እግዚአብሔር የከተመብሽ ረቂቅ ከተማ ነሽ፡፡ በኪሩቤል በሱራፌል አድሮ የሚኖረው እርሱን በማኽል እጅሽ ይዘሽዋልና ልዑል እግዚአብሔር የከተመብሽ ረቂቅ ከተማ ነሽ፡፡ በቸርነቱ ብዛት ፍጥረቱን ኹሉ በዝናም አብቅሎ በፀሐይ አብስሎ የሚመግበው እርሱ ጡትሽን ይዞ ጠባ፡፡ አንድም ለሰውን (ለመንፈሳውያን) ኹሉ ሥጋውን ደሙን ሰጥቶ የሚመግበው እርሱ ጡትሽን ይዞ ጠባ፡፡ ይኸውም ፈጣሪያችን መድኃኒታችን ነው፡፡ እንሰግድለት እናመስግነውም ዘንድ በሐዲስ ተፈጥሮ በጥንተ ተፈጥሮ ፈጥሮናልና ለዘለዓለሙ ይጠብቀናል /ዮሐ.፮፡፴፯/፡፡ ሰጊድ (አምልኮ) ከሚገባው ልጅሽ ጽንዕት በድንግልና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሣን ለምኚልን፡፡
@Ethiopian_Orthodox
፬. ድንግል ማርያም ዕፍረተ ምዑዝ (መዓዛው የጣፈጠ) የተባለ ጌታችንን የወለደች ሙዳየ ዕፍረት (የሽቱ መኖርያ) /፩ኛ ሳሙ.፲፡፩ አንድምታው/፤ ዳግመኛም የማየ ሕይወት (የሕይወት ውኃ የክርስቶስ) ምንጭ ናት /መኃ. ፬፡፲፪ አንድምታው/፡፡ የማኅፀኗ ፍሬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሰውን ኹሉ አድኗልና፡፡ ከእኛ መርገመ ሥጋን መርገመ ነፍስን አጠፋልን፡፡ ሐዋርያው ጳውሎስ፡- “በመስቀሉ ደም ሰላም አድርጎ በምድር ወይም በሰማያት ያሉትን ኹሉ ለራሱ እንዲያስታርቅ ፈቅዶአልና” እንዲል /ቈላ.፩፡፲፱-፳/ በመካከል ኾኖ በመስቀሉ አስታረቀን፡፡ ልዩ በኾነ ትንሣኤውም ሰውን ዳግመኛ ወደ ገነት መለሰው፡፡ ከእናንተ መካከል፡- “ልዩ በኾነ ትንሣኤ ሲል ምን ማለቱ ነው?” ብሎ የሚጠይቅ ሊኖር ይችላል፡፡ እኛም እንዲህ ብለን እንመልስለታለን፡- ከእነ አልዓዛር ትንሣኤ የተለየ መኾኑን ለማሳየት ነው፡፡ ምክንያቱም፡-
፩ኛ) እነ አልዓዛር አስነሺ ይሻሉ፤ እርሱ ግን “ላኖራት ሥልጣን አለኝ፤ ደግሞም ላነሣት ሥልጣን አለኝ” ብሎ እንደተናገረ /ዮሐ.፲፡፲፰/ የተነሣው በገዛ ሥልጣኑ ነውና፡፡ በተለያየ ሥፍራ “አብ አንሥኦ (አብ አስነሣው)፤ መንፈስ ቅዱስ አንሥኦ (መንፈስ ቅዱስ አስነሣው)” ቢልም አንድ ነው፡፡ ምክንያቱም ዕሪናቸውን መናገር ነውና፡፡
፪ኛ) የእነ አልዓዛር ትንሣኤ በብሉይ ሥጋ ነው፤ የእርሱ ግን በሐዲስ ሥጋ ነው፡፡
፫ኛ) የእነ አልዓዛር ትንሣኤ ሞትን ያስከትላል፤ የእርሱ ግን ሞትን አያስከትልም፡፡
፬ኛ) የእነ አልዓዛር ትንሣኤ ትንሣኤ ዘጉባኤን ይጠብቃል፤ የእርሱ ግን አይጠብቅምና፡፡
አዳምን ዳግመኛ ወደ ገነት ከመለሰ ልጅሽ ጽንዕት በድንግልና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሣን ለምኚልን፡፡
፭. አንዳንድ ተረፈ ንስጥሮሳውያን እንደሚሉት ንጽሕት ድንግል ማርያም ላቲ ስብሐትና “ወላዲተ ሰብእ” አይደለችም፤ የታመነች አምላክን የወለደች ናት እንጂ፡፡ የመናፍቃን መዶሻ የተባለው፣ በተለይም የቅድስት ድንግል ማርያምን ወላዲተ አምላክነት የካደውን ንስጥሮስን የረታው ቅዱስ ቄርሎስ እሳተ መለኮት አምላክን ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን በማኅፀኗ የተሸከመች፣ በጀርባዋ ያዘለች፣ በዝናብ አብቅሎ በፀሐይ አብስሎ የፈጠረውን ፍጥረት የሚመግበው አማኑኤልን የድንግልና ጡቶቿን ወተት የመገበችውን የወላዲተ አምላክን ክብር ያልተረዱትን ንስጥሮሳውያን መናፍቃንን ሲወቅስ “ወለዛቲ እንተ መጠነዝ ዐባይ ጾረት መለኮተ እፎ ይከልእዋ እምክብራ ለወላዲተ አምላክ ወላዲተ አምላክኬ ቅድስት ድንግል - ይኸንን ያኽል ታላቅ ኾና መለኮትን የተሸከመችቱን የአምላክ እናት ክብርን እንደምን ይነፍጓታል፤ ይከለክሏታል፡፡ የአምላክ እናት ማለት ድንግል ማርያም ናታ” በማለት የተሰጣትን ክብር በማድነቅ አስተምሯል /ተረፈ ቄርሎስ/፡፡
እንዲህም ስለኾነ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የታመነች የምሕረት አማላጅ ናት፡፡ የዚህ ዓለም ሰዎች አማልዱኝ ቢባሉ ነገር አጽንተው ይመለሳሉ፤ እርሷ ግን “ማእምንት ሰአሊተ ምሕረት - የታመነች የምሕረት አማላጅ ናት” /ዮሐ.፪፡፩-፲፩/፡፡ ሰአሊተ ምሕረት ሆይ! ኃጢአታችንን ያስተሠርይልን ዘንድ ከልጅሽ ዘንድ አማልጅን፡፡ ኃጢአታችንን ከሚያስተሠርይልን ልጅሽ ጽንዕት በድንግልና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሣን ለምኚልን፡፡
የዓርብ ውዳሴ ማርያም ትርጓሜ
ይህ ዕለት ለምስጋና አምስተኛ ለፍጥረት ስድስተኛ ቀን ነው፡፡ በዚህም ቀን እመቤታችን ትመጣለች፤ የብርሃን ድባብ ይዘረጋል፤ የብርሃን ዙፋን ይነጸፋል፡፡ ከዚያ ላይ ኹናም ሊቁን ባርካው ምስጋናዉን ጀምሯል፡፡ ከወትሮ ይልቅም ደናግልን አስከትላ መጥታለች፡፡
@Ethiopian_Orthodox
፭. ተናግሮ የማያስቀር፣ ምሎ የማይከዳ እግዚአብሔር፡- “ከባሕርይህ የተከፈለ ልጅህ (ክርስቶስን) በዙፋንህ አስቀምጥልሃለሁ” ብሎ ለዳዊት በእውነት ማለለት /መዝ.፻፴፩፡፲፩/፡፡ ዳዊትም ክርስቶስ በሥጋ ከእርሱ እንዲወለድ ባመነ ጊዜ የአካላዊ ቃል ማደርያውን መርምሮ ያውቅ ዘንድ ወደደ፡፡ ቀኖናም ገባ፡፡ ከዚህም በኋላ “ናሁ ሰማዕናሁ በኤፍራታ ወረከብናሁ ውስተ ዖመ ገዳም - በኤፍራታ ተወልዶ፤ በጎል ተጥሎ፤ በጨርቅ ተጠቅልሎ በግዕዘ ሕፃናት ሲያቅስ ሰማነው” አለ /መዝ.፻፴፩፡፮/፡፡ ይህቺውም እኛን ስለማዳን ይወለድባት ዘንድ የመረጣት ቤተ ልሔም፣ ቤተ ኅብስት የተባለች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ናት፡፡ ከሰማይ የወረደው ኅብስት እርሱ ነውና /ዮሐ.፮፡፶፩/፡፡
ከነቢያት አንዱ የሚኾን ሚክያስም ዳግመኛ እንዲህ አላት፡- “አንቺም የኤፍራታ ዕፃ የምትኾኝ ቤተ ኅብስት ቤተ ልሔም እመቤታችን ሆይ! በይሁዳ ከነገሡ ነገሥታት ብትበልጭ እንጂ አታንሺም፡፡ እሥራኤል ዘነፍስን የሚጠብቅ ንጉሥ ባንቺ ይወለዳልና እንዲህ እንደኾንሽ አትቀሪም፡፡ ንጉሥ ይወለድብሻል፤ ቅዳሴ መላእክት ይሰማብሻል፤ የብርሃን ድንኳን ይተከልብሻል፤ መቶው ነገደ መላእክት ደጅ ይጠኑብሻል፡፡ አሕዛብ ይገብሩብሻል” ብሏታል /ሚክ.፭፡፪/፡፡ ጀሮም የተባለ ቅዱስ አባት ይህን አንቀጽ ሲተረጕም፡- “ከሰማይ የወረደ ኅብስት /ዮሐ.፮፡፶፩/ የተወለደብሽ ቤተ ኅብስት ሆይ! ሰላምታ ይገባሻል፡፡ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ የተወለደብሽ ምድረ ፍሬ፣ ምድረ ምውላድ (ኤፍራታ) ሆይ! ሰላምታ ይገባሻል፡፡ በዘመነ ብሉይ ሚክያስ ነቢይ ስለ አንቺ ሲናገር እንዲህ ብሎ ተናግሮ ነበርና፡- ‘ወአንቲኒ ቤተ ልሔም ምድረ ኤፍራታ ኢትቴሕቲ እም ነገሥተ ይሁዳ - አንቺም የኤፍራታ ዕፃ የምትኾኝ ቤተ ልሔም ከይሁዳ ገዢዎች ከቶ አታንሺም /ማቴ.፪፡፮/፡፡ ኢይወጽእ ምስፍና ወምልክና እምአባሉ ለይሁዳ - በትረ መንግሥት ከይሁዳ አይጠፋም እንዲል /ዘፍ.፵፱፡፲/ ከባሕርይ አባቱ ከአብ ጋር ቅድመ ዓለም የነበረ፣ ከዲያብሎስ አስቀድሞ ቀዳማዊ የኾነ እሥራኤል ዘነፍስን የሚጠብቅ ንጉሥ ከአንቺ ይወጣል (ይወለዳልና)” ብሏል /St. Jerome, Letter 108:10/፡፡
ወዮ! ከዛሬ ጀምሮ እስከ ዕለተ ምጽአት ድረስ ከአብ ከባሕርይ አባቱ ከመንፈስ ቅዱስ ከባሕርይ ሕይወቱ ጋራ ክብር ይግባውና በአንድ በመንፈስ ቅዱስ ተገልጾላቸው የክርስቶስን ነገር የተናገሩ ሚክያስና ዳዊት የተናገሩት ነገር ምን ይረቅ? ምን ይጠልቅ? አንድም ሚክያስና ዳዊት ለተናገሩት ነገር አንክሮ ይገባል፡፡ ከአብ ከባሕርይ አባቱ ከመንፈስ ቅዱስ ከባሕርይ ሕይወቱ ጋር ክብር ከሚገባው ልጅሽ ጽንዕት በድንግልና ሥርጉት በቅድስና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሣን ለምኚልን፡፡
፮. ለእሥራኤል የነገሠ ዳዊት ኢሎፍላውያን በጠላትነት በተነሡበት ጊዜ ከቤተ ልሔም ምንጭ ውሃ ይጠጣ ዘንድ ወደደ፡፡ ዳዊት ታመመ፤ ቢታመም ዘመዶቹ ቀሳ አወጡት፡፡ ኢሎፍላውያን ይህን ሰምተው ቤተ ልሔምን አልፈው ሰፈሩ፡፡ ዳዊትም “ከቤተ ልሔም ምንጭ ውሃ ማን ባመጣልኝ?” አለ፡፡ ከእናንተ መካከል፡- “ስለምን ከቤተ ልሔም የተቀዳ ውሀ ይጠጣ ዘንድ ወደደ?” የሚል ሊኖር ይችላል፡፡ እኛም እንዲህ ብለን እንመልስለታለን፡- ከላይ ለመግለጽ እንደሞከርነው ታምሞ ስለነበር የቤተ ልሔም ውሀ ደግሞ ማየ ፈውስ ናትና /፪ኛ ነገ.፳፫፡፲፭-፲፯፣ አንድምታውን ይመልከቱ/፡፡
ስለኾነም የጭፍራ አለቆች አዲኖን ኢያቡስቴ ኤልያናም አፋ አፋቸውን ታጥቀው፣ ዘገራቸውን ነጥቀው፣ ራዋታቸውን ጭነው “የማን ጌታ በውሃ ጥም ይሞታል?” ብለው ፈጥነው ተነሡ፡፡ በኢሎፍላውያን ከተማ ተዋጉለት፡፡ ይጠጣ ዘንድ የወደደውንም ውሀ አመጡለት፡፡ ብጹዕ ዳዊት ግን ስለ ርሱ ሰውታቸውን ለሞት አሳልፈው እንደ ሰጡ በየ ጊዜ የራዋቱን ውሀ አፈሰሰው፡፡ በማለፊያው ቀድተው የሰጡትን አልጠጣም፡፡ “የናንተን ደም መጠጣት ነው” ብሎ አፍሶታል፡፡ አንድም ውሀውን መሥዋዕት አድርጐ ለእግዚአብሔር አፈሰሰው፡፡ ከእናንተ መካከል፡- “ዳዊት ንጉሥ ሲኾን መሥዋዕት የሚኾን ላም በግ አጥቶ ነውን?” ብሎ የሚጠይቅ ሊኖር ይችላል፡፡ በፍጹም! እግዚአብሔር የወደዱትን ቢተዉለት ስለሚወድ ነው እንጂ /መዝ.፶፬፡፮፣ ዝኒ ከማሁ፣ ገጽ ፻፵፭/፡፡
ዳዊት የወደደውን ውሀ ስለ እግዚአብሔር ብሎ ስላፈሰሰውም ጽድቅ ኾኖ ተነገረለት፡፡ አዲኖን፣ ኢያቡስቴ፣ ኤልያና ስለ ዳዊት ብለው ጣዕመ ዓለምን እንደናቁ፤ ዳዊትም ስለነርሱ አንድም ስለ እግዚአብሔር ብሎ ጣዕመ ማይን እንደናቀ ሰማዕታት ጣዕመ ዓለምን ናቁ፡፡ አዲኖን፣ ኢያቡስቴ፣ ኤልያና ዳዊትን ብለው ደማቸውን እናፍስ እንዳሉ፤ ዳዊትም ውሀውን እንዳፈሰሰ፤ ሰማዕታት ስለ እግዚአብሔር ብለው ደማቸውን አፈሰሱ፡፡ አዲኖን፣ ኢያቡስቴ፣ ኤልያና ስለ ዳዊት ብለው መራራ ሞትን እንታገሥ እንዳሉ፡ ዳዊትም ጽምዓ ማይን ልታገሥ እንዳለ ሰማዕታት መራራ ሞትን ታገሡ፡፡ ቸር አባት ሆይ! እኛስ እንደ ሰማዕታት ከዓላውያን ነገሥታት፣ ከዓላውያን መኳንንት ገብተን መከራውን ታግሠን ተቀብለን፤ እንደ ምዕመናንም ከፍትወታት ከእኩያት ኃጣውእ ተዋግተን ድል ነሥተን መዳን አይቻለንምና እንደ ቸርነትህ ብዛት ይቅር በለን፡፡ ቸርና ይቅር ባይ ከሚባል ልጅሽ ጽንዕት በድንግልና ሥርጉት በቅድስና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሣ ለምኚልን፡፡
፯. ከሦስቱ አካል አንዱ አካል በእግረ አጋንንት መረገጣችንን መጠቅጠቃችንን አየና ባሕርዩን ዝቅ አድርጎ
ሰው ኹኖ በድንግል ማኅፀን አደረ /ኢሳ.፶፱፡፮/፡፡ ባሕየ መላእክትን ባሕይ አላደረገም፤ ባሕርየ ሰብእን ባሕርይ አድርጎ በድንግል ማኅፀን አደረ እንጂ /ዕብ.፪፡፲፮/፡፡ ከብቻዋ ከኃጢአት በቀርም እንደኛ ሰው ኾነ /ዕብ.፬፡፲፬/፡፡ ሚክያስና ዳዊት በቤተ ልሔም ይወለዳል ብለው እንደ ተናገሩ በቤተ ልሔም ተወለደ፡፡ “ይሙት ቤዛነ በትስብእቱ ወየሀበነ መድኃኒተ ዘከመ መለኮቱ” እንዲልም እንደ አምላክነቱ አዳነን እንደ ሰውነቱም ቤዛ ኾነን /ኤፌ.፩፡፯/፡፡ ዳግመኛም ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ፡- “እናንተ አስቀድሞ በሥጋ አሕዛብ የነበራችሁ፥ በሥጋ በእጅ የተገረዙ በተባሉት ያልተገረዙ የተባላችሁ፥ ይህን አስቡ፤ በዚያ ዘመን ከእስራኤል መንግሥት ርቃችሁ ለተስፋውም ቃል ኪዳን እንግዶች ኾናችሁ በዚህም ዓለም ተስፋን አጥታችሁ ከእግዚአብሔርም ተለይታችሁ ያለ ክርስቶስ ነበራችሁ። አሁን ግን እናንተ በፊት ርቃችሁ የነበራችሁ በክርስቶስ ኢየሱስ ኾናችሁ በክርስቶስ ደም ቀርባችኋል” /ኤፌ.፪፡፲፩-፲፫/ እንዲል ወገኖቹ ያልነበርን እኛን ወገኖቹ አደረገን፡፡ ወገኖቹ ካደረገን ልጅሽ ጽንዕት በድንግልና ሥርጉት በቅድስና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሣ ለምኚልን፡፡
ይኸን ሲጨርስ በያዘችው መስቀለ ብርሃን ባርካው ወደ ሰማይ ታርጋለች፡፡ እርሱም ተባርኮ እጅ ነሥቶ ይቀራል፡፡
አነሣሥቶ ላስጀመረን አስጀምሮም ላስጨረሰን ለልዑል እግዚአብሔር ክብር ምስጋና ይግባው አሜን!!!
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
፩. ነደ እሳት ሰፍሮባት፣ በነደ እሳት ተከባ፣ ጫፎቿ ሳይቃጠሉ ሙሴ በደብረ ሲና ያያት ዕፅ ድንግል ማርያምን ትመስላለች /ዘጸ.፫፡፩-፫/፡፡ አካላዊ ቃል ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ነሥቶ ሰው ኹኗልና፤ ባሕርየ (እሳተ) መለኮቱም አልለወጣትምና (አላቃጠላትምና) ሐመልማላዊቱ ዕፅ እመቤታችንን ትመስላለች፡፡ ዳግመኛም እርሱን ከወለደችው በኋላ ማኀተመ ድንግልናዋ አልተለወጠምና ሐመልማላዊቱ ዕፅ እመቤታችንን ትመስላለች፡፡ እርሱም ምንም ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷም ነፍስ ነስቶ ፍጹም ሰው ቢኾንም ባሕርየ መለኮቱ አልተለወጠምና እሳቱን ይመስላል፡፡ ሰውም ቢኾን ባሕርየ መለኮቱ አልተለወጠምና ሰው ኾኖ ያዳነን የባሕርይ አምላክ ነው፡፡ ሰው ኾኖ ካዳነን ልጅሽ ጽንዕት በድንግልና ሥርጉት በቅድስና እመቤታችን ጸጋዉን ክብሩን እንዳይነሣን ለምኚልን፡፡
፪. ይቅርታሽ (ምልጃሽ) ለኹላችን ይኾን ዘንድ አምላክን የወለድሽ እመቤታችን ሆይ! ኹላችን እናከብርሻለን፤ እናገንሻለን፡፡ ሔዋን ባደረገችው ዐመፅ በባሕርያችን ጸንቶ የነበረ መርገመ ሥጋ መርገመ ነፍስ በእርሷ ምክንያት የጠፋልን አምላክን የወለደች ድንግል ማርያም የኹላችን መመኪያ ናት፡፡ “ሔዋን ምን አደረገች?” ትለኝ እንደኾነም ዕፀ በለስን በልታለች እልሃለሁ፡፡ “ወአዘዞሙ ለኪሩቤል ወሱራፌል ዘውስተ እደዊሆሙ ሰይፈ እሳት እንተ ትትመያየጥ ከመ ይዕቀቡ ፍኖተ ዕፀ ሕይወት - ወደ ሕይወት ዛፍ የሚወስደውንም መንገድ ለመጠበቅ ኪሩቤልንና የምትገለባበጥ የነበልባል ሰይፍን በዔድን ገነት ምሥራቅ አስቀመጠ” እንዲል /ዘፍ.፫፡፳፬/ በሔዋን ምክንያት የገነት ደጅ ተዘጋ፡፡ “ወአግኃሦ ለሱራፊ ዘየዐቅብ ፍና ዕፀ ሕይወት፤ ወአእተተ እምእዴሁ ኵናተ እሳት - ” እንዲልም በድንግል ማርያም ምክንያት ዳግመኛ ተከፈተልን፡፡ ቅዱስ ያዕቆብ ዘስሩግም፡- “አዳምን እንዲሞት ያደረገች ያቺ ቀን ተለወጠች፡፡ እርሱም ከሞት የሚድንባት ሌላ ቀን መጣች፡፡ እባቧ ሳትኾን መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ይናገር ዘንድ ተነሣ፡፡ ሔዋን ሳትኾን ድንግል ማርያምም ቃሉን ትቀበል ዘንድ ተዘጋጀች፡፡ በተንኰል የሚያስተው ሳይኾን ሕይወትን የሚያውጀው ቃል ወጣ፡፡ በሞት ዛፍ መካከል የሞት ዕዳዋን በጻፈችው ሔዋን ፈንታ ልጇ (ማርያም) የአባቷን ዕዳ ኹሉ ከፈለች፡፡ ሔዋንና እባቡ በቅድስት ድንግል ማርያምና በቅዱስ ገብርኤል ተተኩ፡፡ ያ ከመጀመርያው የተበላሸው ነገር አሁን ተስተካከለ፡፡ የሔዋን ጀሮና ቀልብ አታላዩ በሚናገርበት ጊዜ እንደምን እንዳዘነበለ አስተውሉ፤ ያ በገነት ሲመለከታቸው የነበረው መልአክ አሁን በድንግል ማርያም ጀሮ የድኅነትን ተስፋ ሲያሰርጽና የእባቡን ከፉና መርዛማ ቃል ሲያጠፋ ደግሞ አስተውሉ፡፡ ሔዋን ያፈረሰችው ሕንፃ ገብርኤል ገነባው፡፡ በዔደን ገነት ውስጥ ኹና ሔዋን ያፈረሰችውን መሠረት ዳግሚት ሔዋን ቅድስት ድንግል ማርያም በዚህ ምድር ኹና ገነባችው፡፡ ከኹለት መልእክተኞች መልእክት የተቀበሉ ኹለት ደናግላን ኹለት ትውልድን ቀጠሉ፡፡ አንዱም የአንዱ ተቃራኒ ኾነ፡፡ በእባብ ምክንያት ሰይጣን ምሥጢርን ለሔዋን ላከ፡፡ በሌላ ቅዱስ መልአክ አማካኝነት ደግሞ ጌታ የምሥራቹን ወደ ቅድስት ድንግል ማርያም ላከ፡፡ እባብ ለሔዋን የሐሰትን ቃል ለሔዋን ስትናገር ቅዱስ ገብርኤል ግን የእውነትን ቃል ለቅድስት ድንግል ማርያም ተናገረ፡፡ እውነትን በሚናገር አንደበቱ የቀደመውን የእባብ ቃል አደሰው፡፡ እውነትን ተናገረና ሐሰቱን አስወገደው፡፡ አስቀድሞ ሐሰትን ከራሱ አንቅቶ ሰይጣን ሔዋንን በዔደን ገነት አታለላት፡፡ ይህንንም ታላቅ ስሕተት በጀሮዋ አልፎ እንዲሰማት ፈቀደች፡፡ አሁን ግን በመጀመርያዋ ድንግል ፈንታ ሌላ ድንግል ተመረጠች፡፡ በዚህች ድንግል ጀሮም ከአርያም የተላከ የእውነት ቃል ገባ፡፡ ሞት በገባበት በዚያ በር (ጀሮ) ሕይወት ገባ፡፡ ክፉው (ዲያብሎስ) ያጠበቀው ጽኑ የሞት ማሰርያም ተፈታ፡፡ ኀጢአትና ሞት ሠልጥነውበት በነበረ ቦታ ጸጋ ከመጠን ይልቅ በዝቶ ታየ፡፡ … እባብ የስሕተትን ዜማ ለሔዋን ዘመረላት፤ ሐሰትንም ረጨባት፡፡ በተፈጥሮዋ ገና ድንግል በምትኾን በሔዋን ላይ ክፉ ምክርና ስሕተት አፈሰሰባት፡፡ በመርዝ የተለወሰና ደምን የተጠማ ክፉ ምክር በአዳም ቤት ውስጥ አስገባ፡፡ ኃይለ ልዑል የላከው መልአክ ግን እነዚህን የክፋት ሰይፎች ለመቆራረጥ ክንፉን እያማታ እየበረረ መጣ፡፡ ለሰው ኹሉ የሚኾን የድኅነት ሰነድ ይዞ መጥቶም ለድንግሊቱ (ለማርያም) አበሠራት፡፡ ሰገደላት፡፡ ሕይወትን በውስጧ አሰረጸ፡፡ ሰላም ዐወጀ፡፡ በፍቅር ቀረባት፡፡ የቀድሞውን የሞት ዳባ በጣጠሰው፡፡ እባብ የገነባውን የማታለል ግንብ ዳግም ላይገነባ በወልደ እግዚአብሔር እንደሚናድ ነገራት፡፡ በእባብ የታጠረው የሞት ቅጽር በወልድ መውረድ እንደሚሰባበር ቀጠሮው እንደደረሰ ነግሮ የምሥራች አላት” በማለት ከማር የጣፈጠ ትምህርቱን እያነጻጸረ አስተምሯል፡፡
ከዕፀ ሕይወትም እንበላ ዘንድ አደለን፡፡ ይኸውም እኛን ስለ መውደድ ሰው ኾኖ ያዳነን የክርስቶስ ቅዱስ ሥጋውና ክቡር ደሙ ነው፡፡
ወዮ! ሰውን የሚወድ ሰውም የሚወደው እግዚአብሔር፣ ማኅደርም ኀዳሪም ያይደለ አካላዊ ቃል፣ ሳይለወጥ ቅድመ ዓለም የነበረ እግዚአብሔር ወልድ፣ ከአብ አንድነት ሳይለይ መጥቶ ንዕድ ክብርት ከምትኾን ከእመቤታችን ሰው ኾኗልና፤ እርሱንም ከወለደችው በኋላ እንደ ቀድሞ ማኅተመ ድንግልናዋ ሳይለወጥ ኑራለችና፤ ስለዚህም ነገር አምላክን የወለደች እንደኾነች በጎላ በተረዳ ነገር ታውቃለችና ለርሷ ድንቅ ኾኖ የሚነገረውን ነገር መናገር የሚቻለው ምን አንደበት ነው? መስማትስ የሚቻለው ምን ጆሮ ነው? ማወቅስ የሚቻለው ምን አእምሮ ነው? የእግዚአብሔር የጥበቡ ምላት ስፋትስ ምን ይረቅ? ምን ይጠልቅ? አንድም ለእግዚአብሔር ለጥበቡ ምላት ስፋት አንክሮ ይገባል፡፡ “በፀነስሽ ጊዜ ጭንቅሽን እጅግ አበዛለሁ፤ በጭንቅ ትወልጃለሽ፤ ፈቃድሽም ወደ ባልሽ ይሆናል፥ እርሱም ገዥሽ ይሆናል” /ዘፍ.፫፡፲፮/ ብሎ የፈረደባት ማኀፀን የሕይወት፣ የድኅነት መገኛ ኾነች፡፡ ዕንቆ ጳዝዮን የተባለ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅም፡- “እስመ ቀዳሚኒ ሔዋን ኮነት ድንግል ወአስሐታ ዲያብሎስ ለማርያምሂ ድንግል አብሠራ ገብርኤል ወባሕቱ ለሔዋንሰ አስሐታ ዲያብሎስ ወወለደት ቃየልሀ ዘውእቱ ምክንያተ ሞት ወማርያምሰ ሶበ አብሠራ መልአክ ወለደት ቃለ በሥጋ ዘውእቱ መራሔ ኵሉ ኀበ ሕይወት ዘለዓለም - ቀድሞም ሔዋን ድንግል ነበረችና ዲያብሎስ አሳታት እንጂ፤ ድንግል ማርያም ግን ገብርኤል አበሠራት፡፡ ነገር ግን ሔዋንን አሳታት፤ የሞት ምክንያት የሚኾን ቃየልን ወለደች፤ ማርያም ግን መልአክ ባበሠራት ጊዜ ኹሉን ወደ ዘለዓለም ሕይወት የሚመራ አካላዊ ቃልን በሥጋ ወለደች፡፡ የሔዋንን ልብላ ልብላ ማለቷ ዕፀ በለስ የሞት ምክንያት እንደኾነ አስረዳ፡፡ በዚያም አዳም ተድላ ደስታ ካለበት ከገነት ወጣ፡፡ ከድንግል የተወለደ አካላዊ ቃል ግን ዕፀ መስቀል የድኅነት ምክንያት እንደኾነ ገለጠ፡፡ በዚያም መስቀል ቀማኛ ወንበዴ የነበረው ሰው ከአባቱ ከአዳምና ከቀደሙ አባቶች
የዕለተ ረቡዕ ውዳሴ ማርያም ትርጓሜ በድምፅ፡፡👉mp3 format
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
ደስ ያለህ ባለ ምሥራች ገብርኤል ሆይ! ወደኛ የመጣ የጌታን ልደት ነግረኸናልና ላንተ የተሰጠ ክብር ፍጹም ነው፡፡ አንድም “ወነዋ ተወልደ ፍስሐ ዘይከውን ለክሙ ወለኩሉ ዓለም - እነሆ ለሕዝቡ ኹሉ የሚኾን ታላቅ ደስታ የምሥራች እነግራችኋለሁ” ብለህ /ሉቃ.፪፡፲/ የጌታን ልደት ለኖሎት (ለእረኞች) ነገርኻቸዋልና ለአንተ የተሰጠ ክብር ፍጹም ነው፡፡ “እግዚአብሔር ከሥጋሽ ሥጋ ከነፍስሽ ነፍስ ነሥቶ ካንቺ ጋራ አንድ ይሆናልና ደስ ይበልሽ” ብለህ /ሉቃ.፩፡፴/ ለእመቤታችን ነግረኻታልና ለአንተ የተሰጠ ክብር ፍጹም ነው፡፡ እንዲህ ካለ ልጅሽ ጽንዕት በድንግልና ሥርጉት በቅድስና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳነሣን ለምኚልን፡፡
፬. መንፈስ ቅዱስ ቢያድርብሽ፣ ኃይለ ልዑል ወልድም ሥጋሽን ቢለብስ ጸጋን አገኘሽ፡፡ መንፈሰ ቅዱስ ከሦስቱ ግብራት ቢከለክልሽ ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ ተብለው ከሚመሰገኑት ከሦስቱ አካላት አንዱን ቅዱስ ወለድሽልን፡፡ ሰውን ኹሉ የሚያድን እርሱም ሰው ኾኖ አዳነን፡፡ ሰው ኾኖ ካዳነን ልጅሽ ጽንዕት በድንግልና ሥርጉት በቅድስና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሣን ለምኚልን፡፡
፭. ቀድሞ ከነበሩት ጋር አንድ ኾኖ አንደበታችን የድንግልን ሥራ ያመሰግናል፡፡ ዛሬ ካሉት ጋር ኾኖም እመቤታችንን ያመሰግናል፡፡ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዳዊት አገር በዳዊት ባሕርይ ካርሷ ተወልዷልና፡፡ አሕዛብ ሆይ! ኑ እመቤታችንን እናመስግናት /ሃይ.አበ.፷፮፡፳/፡፡ እናትን ኹናለችና፤ ድንግልናም ደርባለችና ኑ እመቤታችንን እናመስግናት፡፡ አካላዊ ቃል ካንቺ ሰው የኾነ አደፍ ጉድፍ የሌለብሽ ድንግል ሆይ! ደስ ይበልሽ፡፡ አደፍ ጉድፍ የሌለብሽ ንጹሕ ሽቱ ዕቃ ሆይ! ደስ ይበልሽ፡፡ የሽቱን ዕቃ ጢስ እንዳይተንበት ትቢያ እንደይበንበት ቤት ሰፍተው፣ ሰቅለው፣ ተንከባክበው ያኖሩታል፡፡ እርሷንም “መንፈስ ቅዱስ ዐቀባ እምከርሠ እማ ከመ ኢትጌጊ - እንዳትበድል ድንግልን ከእናቷ ሆድ ጀምሮ የጠበቃት መንፈስ ቅዱስ እንዳትረክስም ያነጻት ለወልድ ዋሕድም ማደርያ ያደረጋት እርሱ ነው” ይላታልና /አርጋኖን ዘእሑድ፣ ቁ.፲፰/፡፡ ዐጤ ዘርዐ ያዕቆብም በነገረ ማርያም መጽሐፉ፡- “ንጽሕት ይእቲ እምኵሉ ትሕዝብት ወእምኵሉ ርስሐተ ኀጢአት - እርሷ (እመቤታችን) ከርስሐተ ኀጢአትና ከመጠራጠርም ኹሉ ንጽሕት ናት” ብሏል /ነገረ ማርያም በሐዲስ ኪዳን፣ ገጽ ፶፮-፶፯/፡፡
ስለ ቀደመ ሰው (ስለ አዳም) ዳግመኛ አዳም የተባለ የክርስቶስ እናቱ ነባቢት ገነት ሆይ! ደስ ይበልሽ፡፡ ከአባቱ ዕሪና (አንድነት) ያልተለየ ተቀዳሚ ተከታይ የሌለው እርሱን የወሰንሺው በፍጹም ጌጥ ያጌጠች ንጹሕ የሰርግ ቤት ሆይ! ደስ ይበልሽ፡፡ የሰርግን ቤት አስቀድመው በሐር ያንቆጠቁጡል፤ ያነጽፉታል፤ ይጎዘጉዙታል፤ ሽቱ ያረበርቡበታል፤ ሐረግ ወርድ ይሥሉበታል፡፡ እንደዚህም ኹሉ አስቀድመን እንደተናገርን መንፈስ ቅዱስ ድንግልን ከእናቷ ማኅፀን ጀምሮ ጠብቋታልና እንዳትረክስም አንጽቷታልና እንዲህ አለ፡፡ አንድም በየጊዜው የጸጋ ክብር ይጨመርላታልና፡፡
ባሕርየ መለኮቱ ያልለወጠሽ ዕፀ ጳጦስ ሆይ! ደስ ይበልሽ፡፡ (ዕፀ ጳጦስ ማለት በሀገራችን ደደሆ፣ እንጆሪ የምንለው ነው) /ዘጸ.፫፡፩-፫/፡፡ ቅዱስ ኤፍሬም የዚህን ግሩም ምሥጢር “ዲያተሳሮን” በተባለ መጽሐፉ ሲተነትነው ፡- “ፈጣሬ ዓለማት ቅዱስ እግዚአብሔር የወደቀውን ፍጥረቱ ወርዶ ያነሣው ዘንድ፣ ቆሽሾ የነበረው ሕንፃዉንም (ሰውንም) ይወለውለው ዘንድ ተገቢ ነበር፡፡ በመኾኑም ፈጣሪ ራሱ በሰው ልጆች ላይ ፈርዶት የነበረውን ፍርድ የባሕርይ ልጁ እንዲሸከመው ካደረገ (በእርግጥም አድርጐታልና) የሰው ልጅ ወደ ጥንተ ተፈጥሮው ይመለሳል ማለት ነው (በርግጥም ተመልሷል)፡፡ ይህ አካላዊ ቃል፣ በሰው መተላለፍ ምክንያት በቅለው የነበሩት እሾክንና አሜኬላን ያቃጥል ዘንድ የመጣ ነባቢ ፍሕም ነው /ዘፍ.፫፡፲፰፣ ኢሳ.፱፡፲፰/፡፡ መጥቶም በማኅፀነ ድንግል አደረ፤ አነጻው፤ የጭንቅና የርግማን ቦታ የነበረው ማኅፀን ቀደሰው /ዘፍ.፫፡፲፮/፡፡ ነቢየ እግዚአብሔር ሙሴ ያየው ነበልባል ሐመልማሉን አላጠፋውም፤ ይልቁንም እንዲለመልም አደረገው እንጂ /ዘጸ.፫፡፪-፫/፡፡ የነጠረ ወርቅ የሚመስል አካልም ወደ ነበልባሉ ገባ፤ ኾኖም አሁንም እሳቱ አልፈጀውም፡፡ ይኸውም በዘመኑ ፍጻሜ ሊመጣ ላለው ነባቢ እሳትና የድንግልን ማኅፀን አለምልሞ ቁጥቋጦውን እንደከደነውም እንደሚከድናት የሚያስረዳ ነው” ብሏል፡፡ ዳግመኛም አባ ጊዮርጊሥ ዘጋሥጫ የእሳተ መለኮት መምጣት ምክንያቱ ሲገልጽ፡- “… (ጌታችንም) የዓለምን ኃጢአት በትከሻው ተሸክሞ ወደ ዕፀ መስቀል ወጣ፡፡… ያን ጊዜ እግዚአብሔር እሾኽና አሜኬላ ይብቀልብህ ብሎ በረገመው ጊዜ በአዳም ሥጋ የበቀለ የኃጢአት እሾኽ ተቃጠለ” ብሏል /መጽሐፈ ምሥጢር ፲፱፡፳፩/፡፡
በኪሩቤል አድሮ የሚኖረው ሰማያዊ መለኮትን በሥጋ የተሸከምሽው ማኅደርም የተባልሽ እመቤትነትን ከገረድነት፣ እናትነትን ከድንግልና ጋር አስተባብረሽ የያዝሽ ሰማይ ሆይ! ደስ ይበልሽ፡፡ ስለዚህ ነገር፡- “አምላክ ለኾነ ለሥጋ ከሥላሴ ጋራ በአንድነት ምሥጋና ይገባዋል፤ በምድርም ዕርቅ ተወጠነ” እያልን ንጹሐን ከኾኑ መላእክት ጋር በፍጹም ደስታ ደስ ተሰኝተን እናመስግን፡፡ ክብር የክብር ክብር ያለው እርሱ አንቺን ለእናትነት መርጧልና ንጹሐን ከኾኑ መላእክት ጋር በፍጹም ደስታ ደስ ተሰኝተን እናመስግን /ሉቃ.፪፡፳/፡፡ አንቺን ለእናትነት ከመረጠ ልጅሽ ጽንዕት ሥርጉት በቅድስና በድንግልና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳነሳን ለምኚልን፡፡
፮. ከቅዱሳን ክብር የእመቤታችን ክብር ይበልጣል፡፡ አካላዊ ቃልን ለመቀበል በቅታ ተገኝታለችና፡፡መላእከት የሚፈሩትን፣ ትጉሃን በሰማያት የሚያመሰግኑትን ድንግል ማርያም በማኅፀንዋ ቻለችው፡፡ እንዲህም ከኾነ ከመላእክት ትበልጣለች፤ ከሱራፌልም ትበልጣለች፤ ከሦስቱ አካል ላንዱ ማደሪያ ኾኖለችና፡፡ ኢትዮጲያዊው ሊቅ አባ ጊዮርጊስም ይህን በኆኅተ ብርሃን መጽሐፉ ላይ ሲገልጽ “አንቲ ተዓብዪ እምኪሩቤል ወትፈደፍዲ እምሱራፌል፣ እምሱራፌል ወኪሩቤል በሠረገላ እሳት ይጸውርዎ ወበምጽንዐ እሳት ይጼንዑ መንበሮ፤ ወአንቲሰ ጾርኪዮ በከርሥኪ ወሐዘልኪዮ በዘባንኪ ወሐቀፍኪዮ በአብራክኪ ህየንተ ሠረገላ እሳተ አብራክኪ ኮነ ወህየንተ ምጽንዐቲሁ ዘእሳተ እደውኪ ኮና - ከኪሩቤል ይልቅ አንቺ ትበልጫለሽ፤ ከሱራፌልም ይልቅ አንቺ ትልቂያለሽ፤ ኪሩቤልና ሱራፌል በእሳት ሠረገላ ተሸክመውታልና፤ አንቺ ግን በማኅፀንሽ ወሰንሺው፤ በዠርባሽም አዘልሺው፤ በጉልበቶችሽም ዐቀፍሽው፤ ጉልበቶችሽም እንደ እሳት ሠረገላ ኾኑ፤ እጆችሽም እንደ እሳት አዕማድ ኾኑ” በማለት የተሰጣት ክብር ከኪሩቤል ከሱራፌል የበለጠ መኾኑን አስተምሯል፡፡
የነቢያት ሀገራቸው ኢየሩሳሌም ይህች ናት፡፡ መንግሥተ ሰማያትን የሚያወርሰን ከእርሷ በነሣው ሥጋ ምክንያት ነውና ደስ ብሏቸው የሚኖሩ የጻድቃን፣ የሰማዕታት፣ የመላእክት ማደሪያቸው ይህቺ ናት፡፡ በድንቁርና በቀቢፀ ተስፋ ለነበሩ ሰዎች ዕውቀት ተሰጣቸው፤ ክርስቶስ ተወለደላቸው /ኢሳ.፱፡፪/፡፡ ወንጌል ተጻፈላቸው /ሉቃ.፩፡፩-፬/፡፡ በቅዱሳን አድሮ የሚኖር እግዚአብሔር እኛን ለማዳን ሰው ኹኗዋልና በሞተ ሥጋ፣ በሞተ ነፍስ ለነበሩ ሰዎች ልጅነት ተሰጣቸው /ዮሐ.፩፡፲፫/፡፡ በኃጢአት በክሕደት ለነበሩ ሰዎች ሃይማኖት (አሚን) ተሰጣቸው /ማቴ.፬፡፲፬/፡፡ ተወዳጆች ሆይ! ይህን ድንቅ ምሥጢር ኑ እዩ፡፡ ስለ ተገለጸን ምሥጢር ምስጋና አቅርቡ፡፡ ከዚህ ቀደም ሰው ኾኖ የማያውቀው እንግዲህም ወዲህ
ረቡዕ ውዳሴ ማርያም ትርጓሜ
ምለስጋና ሦስተኛ፣ ለፍጥረት አራተኛ ቀን በሚኾን በዚህ ዕለት ከወትሮ ይልቅ መላእክትን አስከትላ እመቤታችን ትመጣለች፤ የብርሃን ድባብ ይዘረጋል፤ የብርሃን ምንጻፍ ይነጸፋል፡፡ ከዚያ ላይ ኾናም፡- “ሰላም ለከ ኦ ፍቁርየ ኤፍሬም” ትለዋለች፡፡ እሱም ታጥቆ እጅ ነሥቶ ይቆማል፡፡ ከባረከችው በኋላም ምስጋናዋን “ኵሉ ሠራዊተ ሰማያት ይብሉ ብፅዕት አንቲ…” ብሎ ይጀምራል፡፡
@Ethiopian_Orthodox
፲፬. እናትነትን ከአገልጋይነት ጋር /ሉቃ.፩፡፴፰/ ያለሽ እመቤታችን ሆይ! ደስ ይበልሽ፡፡ በክንድሽ የያዝሺውን (የታቀፍሽውን) መላእክት ያመሰግኑታልና፡፡ እሳታውያን የኾኑ ሱራፌልም ሳያቋርጡ ክንፋቸወን ዘርግተው፡- “የክብር ባለቤት ይህ ነው” ይላሉ፡፡ “በቸርነቱ በይቅርታው ብዛት የሰውን ኹሉ ኃጢአት ለማስተሥረይ ሰው የኾነ የክብር ባለቤት ይህ ነው” እያሉ በፍርሐት በረዐድ ኾነው ያመሰግኑታል፡፡ የሰውን ኃጢአት በቸርነቱ ብዛት ከሚያሰተሠርይ ልጅሽ ጽንዕት በድንግልና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሣን ለምኚልን፡፡
ይህን ሲጨርስ በያዘችው መስቀለ ብርሃን ባርካው ታርጋለች፡፡ እርሱም ተባርኮ እጅ ነሥቶ ይቀራል፡፡
አነሣሥቶ ላስጀመረን ፤ አስጀምሮም ላስፈጸመን ለልዑል እግዚአብሔር ክብር ምስጋና ይግባው አሜን።
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
ሙሴ ያየው ሐመልማል ነበልባሉን እንዳላጠፋው ኹሉ ጌታም ምንም እንኳን ከሥጋሽ ሥጋ ከነፍስሽም ነፍስ ነሥቶ ቢዋሐድም ባሕርየ መለኮቱ አልተለወጠምና ሙሴ በደብረ ሲና ያያት ዕፅ አንቺ ነሽ ፡፡ ሙሴ በአምሳለ ሐመልማል ወነበልባል ካየው ልጅሽ ጽንዕት በድንግልና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሣን ለምኚልን፡፡
@Ethiopian_Orthodox
፬. አንቲ ውእቱ ገራኅተ ዘኢተዘርዐ ውስቴታ ዘርዕ - ዘር ያልወደቀባት፣ ገበሬ ያልጣረባት ያልጋረባት፣ ለታብቁል (ታብቅል) ባለው ቃል ብቻ ከልምላሜ፣ ከጽጌ (ከአበባ)፣ ከፍሬ የተገኘች ገራኅተ ሠሉስ (የማክሰኞ እርሻ) አንቺ ነሽ፡፡ የወንድ ዘር ሳይወድቅብሽ ፍሬ ሕይወት (የሕይወት መገኛ) ጌታ በግብረ መንፈስ ቅዱስ ካንቺ ተወልዷልና፡፡ አረጋዊው ዮሴፍ በትሩፋተ ደሙ የዋጀሽ /ቅዳ.ማር. ቁ. ፻፳፰/፣ ዕንቁ የተባለው መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስንም ያገኘብሽ /ሃይ.አበ.፺፮፡፶፭/ የተቈለፈች ሣጥን አንቺ ነሽ፡፡ በዚህ አለ፣ በዚያ የለም የማይሉት ሙሉዕ በኵለሄ የኾነ አካላዊ ቃል በማኅፀንሽ አደረ /መዝ.፻፴፱፡፰/፤ በዚህ ዓለምም ማኅተመ ድንግልናሽ እንደተቈለፈ ወለድሽው /ሕዝ.፵፬፡፩-፪/፡፡ በዕንቁ ከተመሰለው ልጅሽ ጽንዕት በድንግልና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሣን ለምኚልን፡፡
፭. ሥጋዌውን ተልከው ለነቢያት ሲነግሩ የነበሩ፣ አሁን ደግሞ በአጭር ቁመት በጠባብ ደረት ተወስኖ አይተውት “ስብሐት ለእግዚአብሔር በሰማያት ወሰላም በምድር” ብለው በደስታ ያመሰገኑትን ጌታን የወለድሽው ሆይ! ደስ ይበልሽ፡፡
የነቢያት ዜና ትንቢታቸው ንጽሕት ሆይ! ደስ ይበልሽ፡፡ አባ ሕርያቆስም በቅዳሴው፡- “ኦ ድንግል አምሳል ወትነቢት ዘነቢያት- ነቢያት ትንቢት የተናገሩልሽ ምሳሌ የመሰሉልሽ…” ይላታል /ቅ.ማር.ቁ.፴፯/፡፡ እግዚአብሔር ከነፍስሽ ነፍስ ከሥጋሽ ሥጋ ነሥቶ ካንቺ ጋራ አንድ ባሕርይ ኾኗልና ደስ ይበልሽ፡፡ አንድም እግዚአብሔር በጸጋ ቢያድርብሽ ባለሟልነትን አግኝተሻልና ደስ ይበልሽ፡፡ የሰው ኹሉ ደስታ የሚኾን የመልአኩን ቃል እንደ ኒቆዲሞስ ሳትከራከሪ /ዮሐ.፫፡፬-፱/ እንደ ዘካርያስም ሳትጠራጠሪ /ሉቃ.፩፡፳/ አምነሻልና ደስ ይበልሽ /ሉቃ.፩፡፵፭/፡፡ ሃያውን ዓለም የፈጠረ ጌታ የወለድሽው ሆይ! ደስ ይበልሽ፡፡ሃያውን ዓለም ከፈጠረ ልጅሽ ጽንዕት በድንግልና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሣን ለምኝልን፡፡
፮. በእውነት ወላዲተ አምላክ ተብለሻልና ደስ ይበልሽ፡፡ አንድም በሚገባ ወላዲተ አምላክ ተብለሻልና ደስ ይበልሽ፡፡ አንድም ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ፡- “ብልህ ሸክላ ሠሪ የሚሠራውን የለዘበ ጭቃ በአገኘ ጊዜ ከእርሱ መልካም ዕቃ እንዲሠራ፤ እንደዚህም ጌታችን የዚህችን ድንግል ንጹሕ ሥጋዋን ንጽሕት ነፍሷን ባገኘ ጊዜ ነፍስ ያለችውን ሥጋ ሊዋሐደው ፈጠረ” /ሃይ.አበ.፷፮፡፲፬/ እንዲል በቅተሸ ብትገኚ ወላዲተ አምላክ ተብለሻልና ደስ ይበልሽ፡፡
የሔዋን ደኅንነቷ ሆይ! ደስ ይበለሽ፡፡ ሊቁ ያዕቆብ ዘሥሩግም እንዲህ ይላል፡- “የሕዝቦች ሴቶች ልጆች ሆይ! ከአባቶቻችሁ ስሕተት ነጻ ያወጣችሁን ቅረቡት፤ እርሱንም ማመስገን ተማሩ፡፡ ያ ሔዋን የዘጋችውን የማይናገር አፍ አሁን በእመቤታችን ማርያም ተከፍቷልና ለእኅታችሁ ምስጋናን ለመዘመር ቅረቡ፡፡ አሮጊቷ ሴት (ሔዋን) በምላሶቻችሁ ዙርያ የዝምታን ገመድ ቋጠረች፤ የድንግል ልጅ ግን ጮኻችሁ ታመሰግኑ ዘንድ እሥራታችሁን ፈታ…” /A Metrical Homily on Holy Ephrem, pp 47/፡፡ ከአባቶች አንዱም፡- “እንግዲህስ ሴቶች ኹሉ ሐሴት ያድርጉ፤ አሁን ሴቲቱ ዕፀ በለስን ሳይኾን ዕፀ ሕይወትን አስገኝታለችና፡፡ ዳግመኛም ደናግላን እናቶች ኹሉ በፌሽታ ይዝለሉ፤ ያለመታዘዝን ዕፅ በሴት ተፈውሷልና፡፡ እነሆ ክብሩ ከመላእክት ይልቅ የከበረ ኾኗልና ከእንግዲህ ወዲህ የሴትነት ጾታ የሞትና የውድቀት ምልክት መኾኑ ቀርቷል፡፡ ሔዋን ተፈወሰች፤ ድንግል ግን ከበረች፡፡ እነሆ ድንግሊቱ እናትም አገልጋይም፣ ደመናም ድንኳንም፣ ደግሞም የጌታ ታቦት ኾናለችና፡፡ እንግዲያውስ ኑ! አንቺ ከሴቶች መካከል ተለይተሸ የተባረክሽ ነሽ፤ የሔዋን መድኃኒቷ አንቺ ብቻ ነሽ፤ ዓለምን በደሙ የሚገዛትን ጌታ ያስገኘሽ አንቺ ብቻ ነሽ እያልን እናወድሳት” ብሏል፡፡
ፍጥረትን ኹሉ በፀሐይ አብስሎ በዝናብም አብቅሎ የሚመግበውን እርሱ ጡትሽን ይዘሽ አጥተሸዋልና ደስ ይበልሽ፡፡ አንድም ለመንፈሳውያን ኹሉ ሥጋውን ደሙን ሰጥቶ የሚመግበውን እርሱን ጡትሽን ይዘሽ አጥብተሸዋልና ደስ ይበልሽ፡፡
ተጠምቀው ሕያዋን ኾነው የሚኖሩበት ማየ ገቦ ከአንቺ ከተገኘ ከጌታ የተገኘ ነውና የሕያዋን የጻድቃን እናታቸው ንእድ ክብርት ሆይ! ደስ ይበልሽ፡፡ መቅድመ ተአምርም፡- “ሕይወትየ ይቤላ አዳም ለብእሲቱ አእሚሮ ከመ ትወጽእ እግዝእትነ ማርያም እምሐቌሁ ወእምከርሠ ብእሲቱ - አዳምም እመቤታችን ማርያም ከሱ አብራክ እንድትከፈል ከሔዋንም ማኅፀን እንድትወለድ ዐውቆ ሔዋንን ሕይወቴ ነሽ ይላት ነበር” ይላል /መቅድመ ተአምር ቁ. ፲/፡፡ ሊቁ ቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግም፡- “አዳም ያለ ሩካቤ ድንግል የኾነች ሔዋንን አስገኘ፤ የሕይወት እናት ብሎም ጠራት፡፡ በዚህም ነቢይ ኾነ፤ በኹለተኛ ልደት ከእርሷ የሚያበራ ሕይወት ይገለጣልና፤ በድንግልናዋም የእግዚአብሔር ልጅን ታስገኛለችና፡፡ በአዳም ትንቢት የእውነት ሕይወት የኾነው የጌታችንን መምጣት በምሳሌ ተናገረ፡፡ እናቱም ድንግል ማርያም ኾነች፡፡ ሔዋንን የሕያዋን ኹሉ እናት ብሎ ጠራት፤ ሕይወትን አስገኝታለችና፡፡ እርሱም ኢየሱስ የተባለው ጌታችን ነው” ይላል /Jacob of Serug, On the Virgin, pp 36/፡፡ አንድም “ነዋ ወልድኪ- እነሆ ልጅሽ” /ዮሐ.፲፱፡፳፮/ ባለ ጊዜ በዮሐንስ እኛን ለእርሷ መስጠቱ ነውና የሕያዋን ኹሉ እናታቸው ንዕድ ክብርት ሆይ! ደስ ይበልሽ፡፡ ለምኚልንና ትልምኝልን ዘንድ ዓይነ ሕሊናችንን ወደ አንቺ እንሰቅላለን፡፡
፯. ድንግል ሆይ! ንዕድ ክብርት ሆይ! ጌታን የወለድሽው ሆይ! እኛን ለማዳን ድንቅ የሚያሰኝ ተዋሕዶ በአንቺ ቢደረግ ንጉሥን ወለድሽልን፤ መንክር በአርያሙ የሚባል ጌታ በማኅፀንሽ አደረ፡፡ ነገር ግን በብዙ ኅብረ መልክእ፣ በብዙ ፆታ መልክእ ሃያ ኹለቱን ሥነ ፍጥረት የፈጠረ፣ ሀብተ መንፈስ ቅዱስን በብዙ ፆታ በብዙ ዕድል እንደየ ሰዉ የአእምሮ ስፋት የሃይማኖት ጽናት የሚያድል፣ ልዕልናውን ገናንነቱን በብዙ መንክር ራዕይ በብዙ ወገን (ለምሳሌ በፀሐይ፣ በቀላይ፣ …) የተመሰለ እርሱን የጌትነቱን ነገር ጠንቅቀን (ፈጽመን) መናገር አይቻለንምና ዝም እንበል፡፡ ዳግመኛም በብዙ ኅብረ ትንቢት (ለምሳሌ ናሁ ድንግል ትፀንስ ወትወልድ ወልደ ተብሎ) የተነገረ፣ በብዙ ኅብረ አምሳል (ለምሳሌ በአምሳለ ነበልባል ወሐመልማል፣ በአምሳለ ጠል ወፀምር፣ በአምሳለ አንበሳ፣ በአምሳለ እብን ቅውም) የተመሰለ የርሱን የሥጋዌውን ነገር ጠንቅቀን (ፈጽመን) መናገር አይቻለንምና ናርምም (ዝም እንበል)፡፡
ሥጋዌው በአምሳለ ነበልባል ወሐመልማል፣ በአምሳለ ጠል ወፀምር ከተመሰለ ልጅሽ ጽንዕት በድንግልና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሣን ለምኚልን፡፡