በሳዑዲ አረቢያ ከሚኖሩ 7መቶሺህ ኢትዮጵያዊያን መካከል 4መቶ50ሺዎቹ መደበኛ ያልሆኑ ናቸዉ ተባለ፡፡
ከ2017 እስከ 2023 ባለዉ ጊዜ ዉስጥ ከ5መቶ61ሺህ በላይ ኢትዮጵያዊያን ወደ አገራቸዉ መመለሳቸዉም ተገልጿል፡፡
93ሺህ 5መቶ የሚሆኑ ዜጎች በ2022 በግዴታ ወደ አገራቸዉ ተመልሰዋል ነዉ የተባለዉ፡፡
በ2023 ደግሞ 43ሺህ የሚሆኑ ዜጎች በግዴታ ወደ አገራቸዉ መመለሳቸዉን ዘ ፍሪደም ፈንድ የተባለ ግብረሰናይ ድርጅት አስታዉቋል፡፡
የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር በበኩሉ፤1መቶ33 ሺህ የሚሆኑ ዜጎች ከሳዑዲ መመለሳቸዉን የገለጸ ሲሆን፤ 46 የሚሆኑት ከባድ ጉዳት የደረሰባቸዉ ነበሩ ብሏል፡፡
ህጻናትን እና የአዕምሮ ህሙማንን ጨምሮ 6ሺህ ኢትዮጵያዊያንም ወደ አገራቸዉ ተመልሰዋል ሲል ሚኒስቴሩ አስታዉቋል፡፡
ከሱዳን ከጦርነቱ መቀስቀስ በኋላ ወደ 47ሺህ 8መቶ ዜጎች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል ያለዉ ሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር፤ ከየመን ከ4ሺህ በላይ ዜጎቻችን ተመልሰዋል ብሏል፡፡
በሁለት ዙር በተደረገ ስራ 2መቶ80ሺህ ዜጎች ወደ አገር መመለሳቸዉንም ሰምተናል፡፡
@Yenetube @FikerAssefa
የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ ዕድገት ጉዳይ
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በትናትናው ዕለት ለ5 ምሁራን የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ ዕድገት መስጠቱን አስታውቋል፡፡የዩኒቨርሲቲው የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ ዕድገት ትምህርት ሚኒስቴር በቅርቡ ካሳለፈው ጊዜያዊ እግድ ጋር አይጋጭም ወይ የሚል ጥያቄን አስነስቷል፡፡
ሚኒስቴሩ ታህሳስ 1 ቀን 2017 ዓ.ም ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ ዕድገት እንዳይሰጡ በድጋሚ ውሳኔ ማሳለፉ ይታወሳል፡፡ትምህርት ሚኒስቴር በዕግዱ ላይ ከታህሳስ 1 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ በየትኛውም የከፍተኛ ትምህርት ተቋም የተሰጠ እና የሚሰጥ የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ ዕድገት ተቀባይነት እንደማይኖረውም ያትታል፡፡
የዕግዱ ምክንያትም ከጥቅምት 4/2013 ዓ.ም ጀምሮ በሥራ ላይ የነበረው "የአካዳሚክ ሠራተኞች የደረጃ ዕድገት መመሪያ" በመሻሻል ላይ በመሆኑ እንደሆነ ያነሳል፡፡የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በበኩሉ፤ የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ ዕድገቱን የሰጠው በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ''ስለ ራስገዝ ዩኒቨርሲቲ ለመደንገግ በወጣው'' አዋጅ ቁጥር 1294/2015 መሠረት መሆኑን ይገልጻል፡፡
EBC ጉዳዩን ለማጣራት አደረኩት ባለው ጥረት ዩኒቨርሲቲው ራስ ገዝ በመሆኑ ከላይ በተጠቀሰው አዋጅ መሰረት ዕድገቱን የመስጠት መብት እንዳለው ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ምላሽ አግኝቷል፡፡
Via EBC
@YeneTube @FikerAssefa
የሱማሊያ ውጭ ጉዳይ ሚንስትር አሕመድ ፊቂ፣ ሱማሊያ ለኢትዮጵያ የባሕር በር እንደምትሠጥ አሽራቅ ለተባለው የዓረብኛ ጋዜጣ መናገራቸውን የአገሪቱ ዜና ምንጮች ዘግበዋል።
ኾኖም ሱማሊያ ለኢትዮጵያ የምትሠጣት የባሕር በር ለንግድ አገልግሎት ብቻ የሚውል እንደሚኾን ፊቂ መግለጣቸውንም ዘገባዎቹ ጠቅሰዋል።ኢትዮጵያና ሱማሊያ አንካራ ላይ በደረሱበት ስምምነት መሠረት፣ በባሕር በር ዙሪያ የቴክኒክ ውይይት ለመጀመር መስማማታቸው ይታወሳል።
@YeneTube @FikerAssefa
ነዋሪዎች በሰሜን ወሎ ዞን በምግብ እጥረት ለተጎዱ ሕፃናት በቂ እርዳታ አልቀረበም አሉ!
በአማራ ክልል በሰሜን ወሎ ዞን ቡግና ወረዳ በ16 ቀበሌዎች በተከሰተው የምግብ እጥረት የተጎዱ ሕፃናትንና እናቶች ለመታደግ የተሰራጨው የአልሚ ምግብ ርዳታ በቂ እንዳልኾነ፣ ወላጆች፣ የቡግና ወረዳ ጤና ጽሕፈት ቤት ኃላፊና ሐኪሞች ለአሜሪካ ድምጽ ተናገሩ።
በመንግሥት ኃይሎችና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል ለአንድ ዓመት በዘለቀው ግጭት ምክኒያት ወረዳው ሙሉ ለሙሉ በፋኖ ታጣቂዎች ቁጥጥር ሥር እንደኾነ የተናገሩት የቡግና ወረዳ ጤና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ገብረመስቀል አለሙ፣ ቀድሞውኑ በአልሚ ምግብ ርዳታ ሲደገፍ የቆየውን ማኅበረሰብ ለከፋ ችግር እንደዳረገው ተናግረዋል።
የአሜሪካ ድምፅ ያነጋገራቸው ሦስት እናቶች፣ በጤና ሠራተኞቹና በሀገር ሽማግሌዎች አማካኝነት የሕፃናቱ መጎዳት በይፋ ከታወቀ በኋላ ካለፈው ሰኞ ጀምሮ የተሰራጨው የሕፃናት አልሚ ምግብ በቂ አይደለም ብለዋል። በቂ ርዳታ በአስቸኳይ ካልተከፋፈለ በሕፃናትና ነፍሰጡር እናቶች ላይ የታየው ከፍተኛ ጉዳት ወደ አዋቂዎቹም መዛመቱ እንደማይቀር አሳስበዋል።
የሰሜን ወሎ አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ማስተባበሪያ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አለሙ ይመር፣ ከ16 ቀበሌዎች ከተውጣጡ 18 የሀገር ሽማግሌዎች፣ የኃይማኖት አባቶችና የጤና ባለሞያዎች ጋራ በተደረገ ውይይት ርዳታው እንዲገባ ኃላፊነቱን በመውሰዳቸው ርዳታ መላክ ጀምረናል አኹንም እንቀጥላለን ብለዋል።
ከሀገር ሽማግሌዎቹ አንዱ ነበርኩ ያሉት ቄስ ገብረእግዚአብሔር ዝናቤ፣ ሕፃናቱ ከሞመታቸው በፊት ርዳታ እንዲታደል ባቀረቡት ልመና የአልሚ ምግብ መግባት መጀመሩን ገልጸው፣ ነገር ግን በቂ አይደለም ብለዋል።
Via VoA
@YeneTube @FikerAssefa
በካሬ ከ 78,246 ብር ጀምሮ የቤት ባለቤት ይሁኑ። እንዳያመልጦ ለ 15 ቀናት ለ 50 ቤቶች ብቻ የወጣ እድል ነው።
ከ 432,000ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ
ከ ስቱድዮ 56ካሬ- ባለ 4 መኝታ 177 ካሬ ድረስ
ባለ 1 መኝታ -69ካሬ,77ካሬ
ባለ 2 መኝታ-99ካሬ,104ካሬ
ባለ 3 መኝታ-139ካሬ,147.6ካሬ
ባለ 4 መኝታ-177ካሬ
በ 8% ቅደመ ክፍያ
60% የባንክ ብድር ጋር
ለ ቢሮ እና ሳይት ቀጠሮ
በ +251994670888 ይደውሉ።
“የቪድዮ ማስታወቂያ ከ500 ብር ጀምሮ
😃“
ከ 500-5000 ብር የተዘጋጁትን የስጦታ ካርዶች ሲወስዱ በውስጡ:-
✔️ለቤተሰብ ለጓደኛ እንዲሁም ሞዴሎች የሚሆን የቪድዮ እና የፎቶ መነሻ ስጦታ🎁
✔️ለ ጀማሪ ቢዝነስ ,ሱቆች, ካፌዎች, ድርጅቶች የገና giveaway እንዲሁም product photography እና ማስታወቂያ ማሰሪያ ስጦታ🎁
✔️ለ podcast ሰሪዎች, content creator, actor , music clip ሰሪዎችና ፎቶ ግራፈሮች የሚሆን የ studio rental ስጦታ ያገኛሉ።
ለራሶም ሆነ ለወዳጅዎ ካርዶቹን ይዘዙን። የነፃ ዴሊቨሪ አለን🤩።
ለተጨማሪ መረጃ
በቲክቶክ እና ኢንስታግራም Account @easyproduction1 ይመልከቱ።
በቴሌግራም Account @yabu721 or @M16192129
ወይም
📞0931719020
📞0923125196. ይደዉሉልን
በእስር ላይ የሚገኙት አቶ ክርስቲያን እና አቶ ዮሐንስ "ህመማቸው እንደባሰባቸው" ቤተሰቦቻቸው ተናገሩ!
በቃሊቲ ማረሚያ ቤት እስር ላይ የሚገኙት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባሉ አቶ ክርስቲያን ታደለ እና የአማራ ክልል ምክር ቤት አባሉ አቶ ዮሐንስ ቧያለው "ለከፍተኛ ሕመም" መዳረጋቸውን የቅርብ ቤተሰቦቻቸው ለቢቢሲ ተናገሩ።ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁ ቤተሰቦቻቸው እስረኞቹ ቀዶ ሕክምና ከተደረገላቸው በኋላ "የማያቋርጥ የደም መፍሰስ እንዳጋጠማቸው" ገልጸዋል።
ሁለቱ ፖለቲከኞች "በተደጋጋሚ አቤቱታ" ከሁለት ሳምንት በፊት ቀዶ ሕክምና ማድረጋቸውን ጠበቃቸው አቶ ሰለሞን ገዛኸኝ ለቢቢሲ ተናግረው ነበር።ከቀዶ ሕክምናው በኋላ ሁለቱ ግለሰቦቹ በሆስፒታል ይቆዩ ቢባልም "ያንን እምቢ ብለው በሰዓታት ልዩነት በማይመች መኪና ጭነው ወደ ማረሚያ ቤት መልሰዋቸዋል" ሲሉ የታሳሪዎቹ ቤተሰቦች ተናግረዋል።
አንድ የአቶ ክርስቲያን የቅርብ ቤተሰብ "ቁስሉም አልደረቀም እና ደግሞ ደም እየፈሰሳቸው ነው። ሐኪሞቹም ተናግረዋል፤ ደም መፍሰስ ሊያጋጥም እንደሚችል እና ይህ ሲያጋጥምም እንድታመጧቸው ብለው ነበር" ብለዋል።ነገር ግን ከቀዶ ሕክምናው በኋላ ወደ ሆስፒታል አለመወሰዳቸውን ገልጸዋል።
ሕክምናውን ተከትሎ ለሚከሰተው የደም መፍሰስ ማስታገሻ እንደተሰጣቸው ያስታወሱት የቤተሰብ አባላቱ "የተሰጣቸው የማስታገሻ መድኃኒትም አልቆባቸዋል። ሕመሙን ለማስታገስ ቶሎ ቶሎ እየወሰዱት ስለነበር" ሲሉ ለቢቢሲ ተናግረዋል።
የአቶ ዮሐንስ ቤተሰብ አባል፤ "ትላንት ማስታገሻ ይዘን ስንሄድ መግባት አትችሉም ተባልን፤ ለምንድን ነው ስንል? ሊቀየሩ ነው አሉን። እስከ ትናንት ግን እነሱ አይሄዱም ብለውን ነበር። ትናንት በድንገት ተነስተው ሊወጡ ስለሆነ ምንም ምግብ ማስገባት አትችሉም መድኃኒትም አይገባም ብለው ከለከሉን" ብልዋል።
የአቶ ክርስቲያንም የቤተሰብ አባል በተመሳሳይ "ትላንትና ምግብም ማስታገሻም ይዘን ስንሄድ የሚያስገባን ስለሌለ ተመለስን" ሲሉ ተናግረዋል።የፌደራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ባለፈው ሳምንት ሰኞ ታህሳስ 7/ 2017 ዓ.ም. ባወጣው መግለጫ፤ "ታራሚዎችን ከቃሊቲ ማረሚያ ቤት ገላን አካባቢ ወደ ሚገኘው እና በተለምዶ አባ ሳሙኤል ተብሎ ወደሚጠራው ማረሚያ ቤት እንደሚያዘዋውር አስታውቆ ነበር።
Via BBC
@YeneTube @FikerAssefa
ቅዳሜ'ለት በኢትዮጵያ ጉብኝት ያደረጉት የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን፣ ኢትዮጵያ የዕዳ ሽግሽግ እንዲደረግላትና ይህም በቀጣይ ሳምንታት መፍትሄ ሊያገኝ እንደሚገባ ድጋፋቸውን ሰጥተዋል።
ፕሬዝዳንት ማክሮን፣ ኢትዮጵያ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ በማድረጓ፣ አበዳሪዎች የአገሪቱን የሦስት ቢሊዮን ዩሮ ብድር የማሸጋሸግ ሂደት "በቀጣይ ሳምንታት" ውስጥ የማጠናቀቅ ሃሳብ እንዳላቸው ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ከዓለማቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይ ኤም ኤፍ) ጋር እያካሄደች ያለችውን ንግግር ፈረንሳይ እንደምትደግፍም ፕሬዝዳንት ማክሮን አስታውቀዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
በካሬ ከ 78,246 ብር ጀምሮ የቤት ባለቤት ይሁኑ። እንዳያመልጦ ለ 15 ቀናት ለ 50 ቤቶች ብቻ የወጣ እድል ነው።
ከ 432,000ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ
ከ ስቱድዮ 56ካሬ- ባለ 4 መኝታ 177 ካሬ ድረስ
ባለ 1 መኝታ -69ካሬ,77ካሬ
ባለ 2 መኝታ-99ካሬ,104ካሬ
ባለ 3 መኝታ-139ካሬ,147.6ካሬ
ባለ 4 መኝታ-177ካሬ
በ 8% ቅደመ ክፍያ
60% የባንክ ብድር ጋር
ለ ቢሮ እና ሳይት ቀጠሮ
በ +251994670888 ይደውሉ።
“የቪድዮ ማስታወቂያ ከ500 ብር ጀምሮ
😃“
ከ 500-5000 ብር የተዘጋጁትን የስጦታ ካርዶች ሲወስዱ በውስጡ:-
✔️ለቤተሰብ ለጓደኛ እንዲሁም ሞዴሎች የሚሆን የቪድዮ እና የፎቶ መነሻ ስጦታ🎁
✔️ለ ጀማሪ ቢዝነስ ,ሱቆች, ካፌዎች, ድርጅቶች የገና giveaway እንዲሁም product photography እና ማስታወቂያ ማሰሪያ ስጦታ🎁
✔️ለ podcast ሰሪዎች, content creator, actor , music clip ሰሪዎችና ፎቶ ግራፈሮች የሚሆን የ studio rental ስጦታ ያገኛሉ።
ለራሶም ሆነ ለወዳጅዎ ካርዶቹን ይዘዙን። የነፃ ዴሊቨሪ አለን🤩።
ለተጨማሪ መረጃ
በቲክቶክ እና ኢንስታግራም Account @easyproduction1 ይመልከቱ።
በቴሌግራም Account @yabu721 or @M16192129
ወይም
📞0931719020
📞0923125196. ይደዉሉልን
"በጸጥታ ችግር"ለሁለት ወራት እርዳታ ባልደረሰበት ቡግና ወረዳ በሀገር ሽማግሌዎች ስምምነት መደረጉን ተከትሎ የእህል እርዳታ መጓጓዝ መጀመሩ ተገለጸ!
በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን ቡግና ወረዳ በህጻናት መቀንጨርና በምግብ እጥረት ለተጎዱ ከ110 ሺህ በላይ ሰዎች ከሁለት ወራት በኋላ የርዳታ እህል መጓጓዝ መጀመሩን የዞኑ አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ማስተባበሪያ ጽሕፈት ቤት ለአዲስ ስታንዳርድ ገለጸ።
በተጨማሪም በላሊበላ ከተማ 34ሺህ ለሚሆኑ ሰዎች 5100 ኩንታል እርዳታ ለፌደራል መንግሥት መጠየቁን ጠቅሰው እስከዚህ ሰዓት ድረስ 1200 ኩንታል መግባቱን የዞኑ አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ማስተባበሪያ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አለሙ ይመር አመላክተዋል፡፡
እርዳታው መጓጓዝ የጀመረው በጸጥታ ችግር ምክንያት ላለፉት ሁለት ወራት እርዳታ መድረስ ባለመቻሉ በሀገር ሽማግሌዎች ስምምነት መደረጉን ተከትሎ መሆኑንም ገልጸዋል። ይህ በእንዲህ እያለ አዲስ አበባ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ በወረዳው የተከሰተውን የምግብ እጥረት ቀውስ የሚገልጹ ሪፖርቶችን እየተከታተለ መሆኑን ትናንት ታኅሣሥ 11 ቀን 2017 ዓ.ም አመልክቷል።
Via Addis Standard
@YeneTube @FikerAssefa
አሜሪካ አዲሱን የሶሪያ መሪ ለመያዝ መድባ የነበረውን የ10 ሚሊዮን ዶላር ሽልማት ሰረዘች!
አሜሪካ የሶርያውን መሪ አህመድ አል-ሻራ በቁጥጥር ስር ለማዋል ለመያዝ መድባው የነበረውን የ10 ሚሊዮን ዶላር ሽልማት ከከፍተኛ ዲፕሎማቶች እና ከሃያት ታህሪር አል ሻም (ኤችቲኤስ) ተወካዮች ጋር ውይይት ካደረገች በኋላ ሰረዘች።ረዳት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ባርባራ ሌፍ ከሻራ ጋር የተደረገው ውይይት "በጣም ውጤታማ ነበር" ካሉ በኋላ እርሱም "ለመወያየት ዝግጁ" ሆኗል ብለዋል።
የአሜሪካ ልዑካን ቡድን ዋና ከተማዋ ደማስቆ የደረሰው የኤች ቲ ኤስ ታጣቂዎች የበሽር አል አሳድን መንግሥት ከሁለት ሳምንት ባነሰ ጊዜ ውስጥ ካስወገዱ በኋላ ነዉ።ዋሽንግተን አሁንም አማፂ ቡድኑን በአሸባሪነት እንደ ፈረጀች ነው።የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ፣ዲፕሎማቶቹ በአሜሪካ የሚደገፍ "የሽግግር መርሆዎች" ላይ፣ ቀጠናዊ ሁኔታዎች እንዲሁም አይኤስን የመዋጋት አስፈላጊነት ላይ መወያየታቸውን አረጋግጠዋል።
ቃል አቀባዩ አክለውም፣ ባለሥልጣናቱ በአሳድ አገዛዝ ዘመን ስለጠፉት አሜሪካውያን ዜጎች፣ በ2012 በደማስቆ የተጠለፈውን ጋዜጠኛ ኦስቲን ቲስ ፣ እና በ2017 የጠፋውን ሳይኮቴራፒስት ማጅድ ካልማዝ በተመለከተ ተጨማሪ መረጃ እንደሚፈልጉ መግለጻቸውን አስታውቀዋል።
የአሜሪካ ኤምባሲ ቃል አቀባይ ቀደም ሲል ሌፍን ይሳተፉበታል የተባለ ጋዜጣዊ መግለጫ በ"ደህንነት ስጋት" ምክንያት መሰረዙን አስታውቋል።በኋላ ላይ ግን በተሰጠው አጭር መግለጫ ላይ፣ "በጎዳና ላይ የነበረው ከበራ" ለመዘግየቱ መንስኤ መሆኑን በመግለጽ፣ የደህንነት ስጋት የተባለውን አስተባብለዋል።
ጉብኝቱ ከአስር ዓመታት ወዲህ በደማስቆ ለመጀመሪያ ጊዜ የተደረገ መደበኛ የአሜሪካ ዲፕሎማሲያዊ ጉብኝት ነው።ይህ ጉብኝት በሶሪያ የአሳድ ከስልጣን መወገድን ተከትሎ የታየ ድንገታዊ ለውጥ ሲሆን፣ አዲስ ስልጣን የሚረከበውን መንግሥት የአረብ አገራት ድጋፍ ተጨምሮበት አሜሪካ እና አውሮፓ ተጽዕኖ ለማሳረፍ የወሰዱት እርምጃ ነው።
Via BBC
@YeneTube @FikerAssefa
ጤናወ በእጀወ በቤትወ የጤና በረከት የተለያዩ መፍትሄ ያጡ ችግሮች እናም በሽታወችን እንዴት አባቶች እና እናቶች ባቆዩነን ቅመማቅመም ቅጠል ስር ፍሬ እና ጥበብ መታከም መፈወስ ከችግራችን መውጣት እንዴት እንደምንችል እምንረዳበት የምንችለው ቻናል ነው ይቀላቀሉ በየቀኑ የምንለቃቸውን ጠቃሚ መረጃ ተካፋይ ይሑኑ ሸር ያድርጉ
👇
https://vm.tiktok.com/ZMhNYSvDS/ ለበለጠ መረጃ
0912718883
0917040506 በቴሌግራም በውስጥ መስመር የሚፈልጉትን ያስቀምጡ
👉አድራሻችን አዲስ አበባ አየር ጤና ካራቆሬ ወደመድኀኒአለም 200ሜትር ገባ ይበሉ
ቁጥር 2ባህርዳር ቀበሌ 11ዲያስፖራ በአሮየው
አስፓልት መስጊዱ ፊት ለፊት ያገኙናል ይምጡ
ይፈወሱ
https://www.tiktok.com/t/ZMhN2XcBE/
በማንኛውም አገልግሎት ውጤቱን እንዳዪ ክፍያ ይፈፅማሉ
🔷 የአያትን አክሲዮን የገዛ ሁሌም ትርፋማ
በ 2015 ዓ.ም 51% ትርፍ /Dividend/ ለባለክሲዮኖች አከፋፍለናል
በቀላል አማርኛ የ 1 ሚሊዮን ብር አክሲዮን የነበራቸው ባለአክሲዮኖች 510 ሺ ብር ትርፍ /Dividend/ አግኝተዋል
የ 5 ሚሊዮን ብር የገዙ 2.5 ሚሊዮን ብር አትርፈዋል
የአንድ አክሲዮን ዋጋ 100 ብር ነው
ዝቅተኛ መግዛት የሚቻለው የአክሲዮን መጠን 2500 ነው
ዝቅተኛ የአክሲዮን ዋጋ 262,500 ብር ፣ 5% የአገልግሎት ክፍያን ጨምሮ
ከፍተኛ የአክሲዮን መጠን ገደብ የለውም
40% ከፍለው ቀሪውን በሶስት ዓመት መጨረስ ይችላሉ
አክሲዮኑን ከገዙ ከአንደኛው ወር ጀምሮ የትርፍ ተካፋይ መሆን ይጀምራሉ
ለበለጠ መረጃ: በ 0967907669 ይደውሉ
አሜሪካ በሰሜን ወሎ ቡግና ወረዳ ለተከሰተው ድርቅ እና የምግብ እጥረት ምግብ እየተላከ መሆኑን አስታወቀች!
አዲስ አበባ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን ቡግና ወረዳ የተከሰተውን ድርቅ እና የምግብ እጥረት ተከትሎ እርዳታ ወደ ስፍራው እየተላከ መሆኑን አስታውቋል።
ኤምባሲው በኦፊሴላዊ የፌስቡክ ገፁ እንዳስታወቀው በወረዳው እንደተከሰተ ከሰሞኑ እየወጡ ያሉ ሪፖርቶች ላይ ክትትል አድርጓል።
"የኢትዮጵያ ህዝብን ለመደገፍ አጋሮቻችን ምግብ እና አልሚ ምግቦችን ወደተጠቁት ስፍራዎች እየላኩ ነው" ያለው ኤምባሲው ሁኔታውን በቀጣይም በመከታተል ችግሩን ለመቅረፍ እንደሚሰራ አስታውቋል።
@YeneTube @FikerAssefa
Elegance Furniture
🛋️ 3 + 2 + 1 + 1 (7) Seater Sofa
📲 0911258421 / 0911259321
☑️ 3 Years Warranty
🚚 Free Delivery
25 % Discount
“የገቢዎች ቢሮ ያሳለፈው ውሳኔ የኢንዱስትሪ ሰላምን እንዳያውክ እሰጋለሁ” -የኢትዮጵያ ሆቴልና ቱሪዝም ፌደሬሽን
የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የደሞዝ ግብር ማጭበርበርን ለመቅረፍ እንደ ሆቴሎች እና ካፌቴሪያዎች ባሉ የተመረጡ የንግድ ተቋማት ላይ “ዝቅተኛ የደመወዝ ተመን እና የሰራተኛ ብዛትን” በተመለከተ ያሳለፈው ውሳኔ የኢንዱስትሪ ሰላምን እንዳያውክ እሰጋለኹ ሲል የኢትዮጵያ ሆቴልና ቱሪዝም ፌደሬሽን አስታወቀ።
የፌደሬሽኑ ፕሬዝደንት ዶ/ር ፍትህ ወልደሰንበት የቢሮው ውሳኔ የአሠሪና ሠራተኛ አዋጁን መሠረት ያላደረገና ዝቅተኛ የደመወዝ ወለልም እንደሃገር ገና በሂደት ላይ ባለበት ወቅት የተወሰነ መሆኑን መግለጻቸውን ቪኦኤ ዘግቧል።"ውሳኔውን በተመለከተ ከንግድ ማህበረሰቡ ጋር በቂ ውይይት አልተደረገም" ያሉት ፕሬዝዳንቱ ዝቅተኛ የሠራተኛ ብዛትን በተመለከተ ንግድን በነጻነት ከትንሽ ተነስቶ ለማሳደግ አዳጋች እንደሚያደርገው ጠቁመዋል።
የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ሰውነት አየለ በበኩላቸው ከዚህ በፊት እንደ ምግብ እና መጠጥ ቤቶች ያሉት የንግድ ተቋማት ለሠራተኞቻቸው ስለሚከፍሉት ደመወዝ በአግባቡ እንደማይገልጹ ጠቅሰው የግብር ማጭበርበርን ለማስቀረት አዲስ አሰራር መዘርጋቱን አመልክተዋል።
በዚህም ቢሮው ለሆቴሎች፣ ለካፊቴሪያዎች፣ ለምግብ እና መጠጥ ቤቶች እንዲሁም ለሥጋ ቤቶች ዝቅተኛ የሰራተኛ ብዛት ተመን እና ዝቅተኛ የሰራተኞች ደመወዝ ወለል ማስቀመጡን ተናግረዋል።አክለውም ይህ አዲስ አሰራር አነስተኛ የንግድ ተቋማትን እንደማይመለከት ገልጸው የንግድ ሥርዓቱን የሚያውክ ነገር የለም ብለዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
በአሜሪካ ማዕቀብ ተጥሎባት የነበረች የሩስያ መርከብ ሞተሯ ላይ ካጋጠመ ፍንዳታ በኋላ ሰጠመች!
የሩስያ ዕቃ ጫኝ መርከብ ሆነችው ኡርሳ ሜጀር በሞተር ክፍል ውስጥ በደረሰ ፍንዳታ ምክንያት በስፔን እና በአልጄሪያ መካከል በሚገኘው የሜዲትራኒያን ባህር ውስጥ መስጠሟን የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ።የመርከቧን 14 አባላት በመታደግ ወደ ስፔን ካርቴጋና ወደብ መውሰድ ቢቻልም ግን ሁለቱ ጠፍተዋል ብሏል።
የሩስያ የዜና ወኪል ኢንተርፋክስ እንደዘገበው ከሆነ ኡርሳ ሜጀር ከ12 ቀናት በፊት ነበር ከሴንት ፒተርስበርግ ወደብ ጉዞ የጀመረችው።የመርከቧ ባለቤት በሩቅ ምሥራቅ ሩሲያ ወደምትገኘው ቭላዲቮስቶክ በመጓዝ ላይ እንደነበረች እና እያንዳንዳቸው 380 ቶን የሚመዝኑ ሁለት ክሬኖችን (የእቃ ማንሻ መሳሪያ) ጭና እንደነበር የመርከቧ ባለቤት ገልጿል። የመርከቧን መዳረሻ በገለልተኛ ወገን ማረጋገጥ አልተቻለም።
ኡርሳ ሜጀር ከመስጠሟ በፊት ሳልቫሜንቶ ማሪቲሞ የተባለው የስፔን የባህር ላይ የአደጋ ጊዜ ኤጀንሲ እንዳስታወቀው 14 ሰዎች በአደጋ ጊዜ ጀልባ ላይ ተገኝተው በሰላም ወደ ስፔን የተጓጓዙ ሲሆን በኋላ ላይ የደረሰው የሩሲያ የጦር መርከብ የነፍስ አድን ሥራውን መረከቡን አክለዋል።
ኡርሳ ማጀር በሜድ አካባቢ ሌላኛዋ ማዕቀብ ከተጣለበት ስፓርታ ከምትባል ከሩሲያ መርከብ ጋር በነበረችበት ወቅት ችግር ውስጥ ገብታ ሁለቱ መርከቦችም በእንግሊዝ ቻናል በኩል ታጅበው ሲያመሩ ታይተዋል።
የዩክሬን ወታደራዊ መረጃ (ኤችዩአር) በዚህ ወር መጀመሪያ ላይ እንደዘገበው ስፓርታ ከበሻር አል አሳድ ውድቀት በኋላ ወታደራዊ መሳሪያዎችን ከሶሪያ ለማውጣት መቀመጫውን ታርቱስ ወዳደረገው እና በሶሪያ የባህር ጠረፍ ወደሚገኘው የሩስያ የባህር ሃይል ጣቢያ እያመራች ነበር።
Via BBC
@YeneTube @FikerAssefa
ጤናወ በእጀወ በቤትወ የጤና በረከት የተለያዩ መፍትሄ ያጡ ችግሮች እናም በሽታወችን እንዴት አባቶች እና እናቶች ባቆዩነን ቅመማቅመም ቅጠል ስር ፍሬ እና ጥበብ መታከም መፈወስ ከችግራችን መውጣት እንዴት እንደምንችል እምንረዳበት የምንችለው ቻናል ነው ይቀላቀሉ በየቀኑ የምንለቃቸውን ጠቃሚ መረጃ ተካፋይ ይሑኑ ሸር ያድርጉ
👇
https://vm.tiktok.com/ZMhNYSvDS/ ለበለጠ መረጃ
0912718883
0917040506 በቴሌግራም በውስጥ መስመር የሚፈልጉትን ያስቀምጡ
👉አድራሻችን አዲስ አበባ አየር ጤና ካራቆሬ ወደመድኀኒአለም 200ሜትር ገባ ይበሉ
ቁጥር 2ባህርዳር ቀበሌ 11ዲያስፖራ በአሮየው
አስፓልት መስጊዱ ፊት ለፊት ያገኙናል ይምጡ
ይፈወሱ
https://www.tiktok.com/t/ZMhN2XcBE/
በማንኛውም አገልግሎት ውጤቱን እንዳዪ ክፍያ ይፈፅማሉ
🔷 የአያትን አክሲዮን የገዛ ሁሌም ትርፋማ
በ 2015 ዓ.ም 51% ትርፍ /Dividend/ ለባለክሲዮኖች አከፋፍለናል
በቀላል አማርኛ የ 1 ሚሊዮን ብር አክሲዮን የነበራቸው ባለአክሲዮኖች 510 ሺ ብር ትርፍ /Dividend/ አግኝተዋል
የ 5 ሚሊዮን ብር የገዙ 2.5 ሚሊዮን ብር አትርፈዋል
የአንድ አክሲዮን ዋጋ 100 ብር ነው
ዝቅተኛ መግዛት የሚቻለው የአክሲዮን መጠን 2500 ነው
ዝቅተኛ የአክሲዮን ዋጋ 262,500 ብር ፣ 5% የአገልግሎት ክፍያን ጨምሮ
ከፍተኛ የአክሲዮን መጠን ገደብ የለውም
40% ከፍለው ቀሪውን በሶስት ዓመት መጨረስ ይችላሉ
አክሲዮኑን ከገዙ ከአንደኛው ወር ጀምሮ የትርፍ ተካፋይ መሆን ይጀምራሉ
ለበለጠ መረጃ: በ 0967907669 ይደውሉ
የአሜሪካ ተዋጊ ጄት በቀይ ባህር ላይ 'በስህተት' ተመትቶ ወደቀ!
የአሜሪካው የጦር መርከብ በቀይ ባህር ላይ በስህተት የራሱን ተዋጊ ጄት መትቶ መጣሉን የአሜሪካ ጦር አስታወቀ።ሁለቱም የአሜሪካ የጦር ኃይል አባላት ጉዳት ሳይደርስባቸው መውጣት መቻላቸውን የጦሩ የማዕከላዊ ዕዝ ገልጿል።አሜሪካ በየመን ዋና ከተማ ሰንዓ በሚገኘው እና በኢራን በሚደገፉ የሁቲ ታጣቂዎች የሚተዳደረውን የሚሳኤል ማከማቻ እና ማዘዣ ጣቢያ ላይ ተከታታይ የአየር ድብደባ ካደረገች በኋላ አጋጣሚው መከሰቱ ተገልጿል።
የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ አክሎም በቀይ ባህር ላይ የሚገኙ በርካታ የሁቲ ሰው አልባ አውሮፕላኖችን እና ፀረ መርከብ ክሩዝ ሚሳዔሎችን መምታቱን አስታውቋል።ማዕከላዊ ዕዙ በሰጠው መግለጫ በቀይ ባህር ላይ በነበረ ተኩስ ወቅት አደጋው መከሰቱን አረጋግጧል።"የአሜሪካው ሃሪ ኤስ ትሩማን የጦር መርከብ አካል የሆነው የዩናይትድ ስቴትስ ጌቲስበርግ በስህተት ከመርከቡ ሲነሳ ነበረውን ኤፍ/ኤ-18 መትቶታል" ሲል በመግለጫው አስታውቋል።
የወደቀው አይሮፕላን በየመን ዘመቻ ውስጥ ስለመሳተፍ አለመሳተፉ የታወቀ ነገር የለም።በሰንዓ በሚገኙ ዒላማዎች ላይ የተፈጸመው ጥቃት "ሁቲዎች በአሜሪካ የባህር ኃይል መርከቦች እና በደቡብ ቀይ ባህር፣ ባብ አል-ማንደብ እና በኤደን ባህረ ሰላጤ ላይ ያሉ የንግድ መርከቦች ላይ የሚያደርሱትን ጥቃት ለማደናቀፍ እና ለማቀጨጭ ነው" ሲል የማዕከላዊ ኮማንዱ አስታውቋል።
የአሜሪካ ወታደራዊ ሃይል "ኤፍ/ኤ-18ን ጨምሮ የአሜሪካ አየር ኃይል እና የባህር ሃይሎችን" በመጠቀም "በርካታ የሁቲ ተሽከርካሪዎች ወይም ሰው አልባ አውሮፕላኖች እና በቀይ ባህር ላይ የሚገኙ ጸረ-መርከብ ክሩዝ ሚሳዔል" መምታቱን ተናግሯል።ሰሜን ምዕራብ የመንን የሚቆጣጠረው እና በኢራን የሚደገፈው አማፂው የሁቲ ቡድን ከፍልስጤማውያን ጎን መቆሙን በማስታወቅ የጋዛ ጦርነት መጀመርን ተከትሎ በእስራኤል እና በዓለም አቀፍ መርከቦች ላይ ጥቃት መሰንዘር ጀመረ።
ከህዳር 2023 ወዲህ እንኳን የሁቲ ሚሳዔል ጥቃቶች ሁለት መርከቦችን በቀይ ባህር ሲያሰጥሙ ሌሎች ላይ ጉዳት አድርሰዋል። ከእስራኤል፣ ዩናይትድ ኪንግደም ወይም እንግሊዝ ጋር የተገናኙ መርከቦች ላይ ብቻ እያነጣጠርን ነው ይላሉ።ባለፈው ታህሳስ ወር አሜሪካ፣ ፣ ዩናይትድ ኪንግደም እና ሌሎች 12 አገራት የቀይ ባህርን የመርከቦች እንቅስቃሴ ከጥቃት ለመከላከል 'ኦፕሬሽን ፕሮስፐሪቲ ጋርዲያን' የሚባል ዘመቻ አስተዋውቀዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
በአዲስ አበባ በስድስት ክፍለ ከተሞች የሥምና ንብረት ዝውውር ታገደ!
በአዲስ አበባ ከተማ ለመሬት ይዞታ ማረጋገጥ ሥራ ሲባል ለቀጣይ 5 ወራት በስድስት ክፍለ ከተሞች እና በተመረጡ ወረዳዎች የሥምና ንብረት ዝውውር መታገዱን የከተማዋ መሬት ይዞታ ምዝገባና መረጃ ኤጄንሲ አስታውቋል።ኤጄንሲው ከመሬት ይዞታ ጋር ተያይዞ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመፍታት በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የገለጸ ሲሆን፤ ለዚህም ዘመናዊ ሁለገብ ካዳስተር ግንባታ ስርዓት በመዲናዋ ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ለማድረግ ሥራ መጀመሩን አመልክቷል፡፡
አሁን ላይ ከአዲስ አበባ ጠቅላላ የቆዳ ስፋት ውስጥ 54 በመቶ ለሚሆነው የመሬት ይዞታ ማረጋገጥ ሥራ መሰራቱን ገልጿል።በተያዘው በጀት ዓመት ለመጨረሻ ጊዜ በ136 ቀጠናዎች የሚገኙ ይዞታዎችን አረጋግጦ ለመመዝገብ እየተሰራ መሆኑንም አመላክቷል።በዚህ መሠረትም የይዞታ ማረጋገጥ ሥራው በተመረጡ ስድስት ክፍለ ከተሞች በቀጣይ አምስት ወራት ውስጥ እንደሚከናወን ተጠቅሷል።
ክፍለ ከተሞችም የካ፣ ለሚ ኩራ፣ አቃቂ ቃሊቲ፣ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ፣ቦሌ እና ኮልፌ ቀራኒዮ መሆናቸው ተገልጿል።ለመሬት ይዞታ ማረጋገጥ ሥራው ሲባልም ምዝባ በሚካሄድባቸው የክ/ከተሞቹ ወረዳዎች እስከ ቀጣዩ ሚያዝያ ወር ድረስ የሥምና ንብረት ዝውውር መታገዱ ተገልጿል።ባለይዞታዎች ከታሕሣሥ 20 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 10 ቀናት የይዞታ ይረጋገጥልኝ ማመልከቻ እንዲያቀርቡም ጥሪ ቀርቧል።
Via Ahadu
@YeneTube @FikerAssefa
ጤናወ በእጀወ በቤትወ የጤና በረከት የተለያዩ መፍትሄ ያጡ ችግሮች እናም በሽታወችን እንዴት አባቶች እና እናቶች ባቆዩነን ቅመማቅመም ቅጠል ስር ፍሬ እና ጥበብ መታከም መፈወስ ከችግራችን መውጣት እንዴት እንደምንችል እምንረዳበት የምንችለው ቻናል ነው ይቀላቀሉ በየቀኑ የምንለቃቸውን ጠቃሚ መረጃ ተካፋይ ይሑኑ ሸር ያድርጉ
👇
https://vm.tiktok.com/ZMhNYSvDS/ ለበለጠ መረጃ
0912718883
0917040506 በቴሌግራም በውስጥ መስመር የሚፈልጉትን ያስቀምጡ
👉አድራሻችን አዲስ አበባ አየር ጤና ካራቆሬ ወደመድኀኒአለም 200ሜትር ገባ ይበሉ
ቁጥር 2ባህርዳር ቀበሌ 11ዲያስፖራ በአሮየው
አስፓልት መስጊዱ ፊት ለፊት ያገኙናል ይምጡ
ይፈወሱ
https://www.tiktok.com/t/ZMhN2XcBE/
በማንኛውም አገልግሎት ውጤቱን እንዳዪ ክፍያ ይፈፅማሉ
🔷 የአያትን አክሲዮን የገዛ ሁሌም ትርፋማ
በ 2015 ዓ.ም 51% ትርፍ /Dividend/ ለባለክሲዮኖች አከፋፍለናል
በቀላል አማርኛ የ 1 ሚሊዮን ብር አክሲዮን የነበራቸው ባለአክሲዮኖች 510 ሺ ብር ትርፍ /Dividend/ አግኝተዋል
የ 5 ሚሊዮን ብር የገዙ 2.5 ሚሊዮን ብር አትርፈዋል
የአንድ አክሲዮን ዋጋ 100 ብር ነው
ዝቅተኛ መግዛት የሚቻለው የአክሲዮን መጠን 2500 ነው
ዝቅተኛ የአክሲዮን ዋጋ 262,500 ብር ፣ 5% የአገልግሎት ክፍያን ጨምሮ
ከፍተኛ የአክሲዮን መጠን ገደብ የለውም
40% ከፍለው ቀሪውን በሶስት ዓመት መጨረስ ይችላሉ
አክሲዮኑን ከገዙ ከአንደኛው ወር ጀምሮ የትርፍ ተካፋይ መሆን ይጀምራሉ
ለበለጠ መረጃ: በ 0967907669 ይደውሉ
አትሌት ስለሺ ስህን አዲሱ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት በመሆን ተመርጠዋል።
ዛሬ ቀጥሎ በተካሄደው የሁለተኛ ቀን 28ኛው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ አትሌት ስለሺ ስህን ለቀጣይ አራት አመታት የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽንን በፕሬዚዳንትነት እንዲመሩ አብላጫውን ድምፅ ማግኘታቸው ታውቋል።
@YeneTube @FikerAssefa
ልማት ባንክ ባለፉት ጥቂት አመታት ብቻ ከ92 ቢሊየን ብር በላይ ለግሉ ዘርፍ ፈሰስ አድርጓል ሲሉ ፕሬዝዳንቷ ገለጹ!
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ አምራች ኢንዱስትሪውን ለመደገፍ ከ92 ቢሊየን ብር በላይ ለግሉ ዘርፍ ፈሰስ አድርጓል ሲሉ የባንኩ ፕሬዝዳንት እመቤት መለሰ (ዶ/ር) ገለጹ።ፕሬዝዳንቷ ይህንን የተናገሩት በአዳማ ከተማ ሀገር በቀል ኢኮኖሚ እና የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ፖሊሲ ማሻሻያ ትግበራ ለአምራች ኢንዱስትሪው ያመጣው መልካም ዕድል፣ ተግዳሮት እና መፍትሔዎች ላይ ያተኮረ የመንግሥትና የግል ዘርፉ የምክክር መድረክ ላይ ነው።
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፕሬዝዳንት እመቤት መለሰ (ዶ/ር) የባንኩ ምስረታ ብዙ ዓመታትን ቢያስቆጥርም በተለያዩ ምክንያቶች አስቸጋሪ ሁኔታዎች ማለፉን አንስተዋል፡፡ይሁን እንጂ “ባለፉት የለውጥ ዓመታት የአምራች ኢንዱስትሪውን ለመደገፍ ከ92 ቢሊየን ብር በላይ ለግሉ ዘርፍ ፈሰስ አድርጓል” ብለዋል፡፡በክልል ለሚገኙ አምራች ኢንዱስትሪዎች አስፈላጊው ድጋፍ እንደሚደረግ የገለፁት ፕሬዝዳንቷ በብድር የተሰጠው ገንዘብ ሳይመለስ ቀርቶ ለመንግሥት ተጨማሪ እዳ እንዳይሆን ከሁሉም ባለድርሻ አካላት ጋር እንሰራለን ብለዋል፡፡
ሌላኛው የምክክሩ ተሳታፊ የኢትዮጵያ መድሀኒትና ህክምና መገልገያ አምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ማህበር ፕሬዝዳንት ዶክተር ዳንኤል ዋቅቶሌ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው የውጭ ምንዛሬ እጥረት ችግርን መፍታት አስችሏል ሲሉ ተናግረዋል።በዚህም በሀገር ውስጥ አምራቾች የሚሸፈነው የመድሀኒት ፍላጎት አሽቆልቁሎ 8 በመቶ ደርሶ እንደነበር ገልጸው፤ ከማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው በኋላ ወደ 36 በመቶ አድጓል ማለታቸውን ከኢንደስትሪ ሚኒስትር ያገኘነው መረጃ ያሳያል።
@YeneTube @FikerAssefa
“የትግራይ ሰራዊት በዲዲአር ስም እንዲበተን እየተደረገ ነው” - በዶክተር ደብረ ጽዮን ገብረሚካኤል የሚመራው ህወሓት
በዶክተር ደብረ ጽዮን ገብረ ሚካኤል የሚመራ የህወሓት ቡድን መቐለ ከተማ በሰጡት መግለጫ፣ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር አመራሮች፣ ታጣቂዎችን ትጥቅ በማስፈታት እና በመልሶ ማዋሃድ ሥራ ስም፣ የትግራይ መሰረታዊ ጥያቄ ሳይመለስ የቀድሞ ተዋጊዎች እንዲበተኑ እየተደረገ ነው ሲል ክስ አሰማ።
የህወሓት አንዱ ክፋይ በመቐለ ከተማ፣ “የእምቢታ ዘመቻ” ብሎ የጠራው ስብሰባ ሲያጠናቅቅ፣ “ጊዜያዊ አስተዳደሩ እንዲፈፅም የተሰጠው ሥራ ሙሉ በሙሉ ወድቋል” በማለትም ገልጿል።
በሌላ በኩል የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ካቢኔ ለሦስት ቀናት ያካሔደውን ስብሰባ አስመልክቶ በአወጣው መግለጫ፣ “ክልሉን ወደ ግርግር እና የአመፅ ተግባር ለማስገባት የሚንቀሳቀሱ ላይ ጊዜያዊ አስተዳደሩ አይታገስም” ብሏል።
@YeneTube @FikerAssefa
በካሬ ከ 78,246 ብር ጀምሮ የቤት ባለቤት ይሁኑ። እንዳያመልጦ ለ 15 ቀናት ለ 50 ቤቶች ብቻ የወጣ እድል ነው።
ከ 432,000ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ
ከ ስቱድዮ 56ካሬ- ባለ 4 መኝታ 177 ካሬ ድረስ
ባለ 1 መኝታ -69ካሬ,77ካሬ
ባለ 2 መኝታ-99ካሬ,104ካሬ
ባለ 3 መኝታ-139ካሬ,147.6ካሬ
ባለ 4 መኝታ-177ካሬ
በ 8% ቅደመ ክፍያ
60% የባንክ ብድር ጋር
ለ ቢሮ እና ሳይት ቀጠሮ
በ +251994670888 ይደውሉ።
“የቪድዮ ማስታወቂያ ከ500 ብር ጀምሮ
😃“
ከ 500-5000 ብር የተዘጋጁትን የስጦታ ካርዶች ሲወስዱ በውስጡ:-
✔️ለቤተሰብ ለጓደኛ እንዲሁም ሞዴሎች የሚሆን የቪድዮ እና የፎቶ መነሻ ስጦታ🎁
✔️ለ ጀማሪ ቢዝነስ ,ሱቆች, ካፌዎች, ድርጅቶች የገና giveaway እንዲሁም product photography እና ማስታወቂያ ማሰሪያ ስጦታ🎁
✔️ለ podcast ሰሪዎች, content creator, actor , music clip ሰሪዎችና ፎቶ ግራፈሮች የሚሆን የ studio rental ስጦታ ያገኛሉ።
ለራሶም ሆነ ለወዳጅዎ ካርዶቹን ይዘዙን። የነፃ ዴሊቨሪ አለን🤩።
ለተጨማሪ መረጃ
በቲክቶክ እና ኢንስታግራም Account @easyproduction1 ይመልከቱ።
በቴሌግራም Account @yabu721 or @M16192129
ወይም
📞0931719020
📞0923125196. ይደዉሉልን
🥇 በHuluPay ላይ የቴሌግራም ኮከቦችን እንዴት መግዛት ይቻላል ⭐️💳
ለምን የቴሌግራም ኮከቦች ያስፈልጋሉ? 🤔
1️⃣ የቴሌግራም ኮከቦችን በቴሌግራም ውስጥ ለማንኛውም ዲጂታል ክፍያዎች መጠቀም ይችላሉ 💰
2️⃣ተለያዩ airdrop መተግበሪያዎች ውስጥ ለክፍያዎች ሊጠቀሙባቸው ይችላሉ 🎁
📲 ሁሉፔይን ለመጠቀም ሁሉፔይ ሚኒ አፕን
/channel/HuluPayOfficialBot/start?startapp=301624537 እዚህ ሊንክ ጋር ያገኛሉ 🔗።