tikvahethiopia | Unsorted

Telegram-канал tikvahethiopia - TIKVAH-ETHIOPIA

1250829

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ ነው። ሰውነትን አስቀድመው ግለሰብን፣ ህዝብና ሀገርን የሚያከብሩ፣ ሚዛናዊ አመለካከትን ያዳበሩ፣ ከጥላቻ አመለካከት የነፁ ኢትዮጵያውያን ቤት ነው። መልዕክት መቀበያ @officialtikvahethiopiaBOT @tikvahuniversity @tikvahethAfaanOromoo @tikvahethmagazine @tikvahethsport #ኢትዮጵያ

Subscribe to a channel

TIKVAH-ETHIOPIA

#Humanity❤️

ይህ የሆነው በአሜሪካ ሀገር ሚኒሶታ ነው።

በሚኒሶታ በሚገኝ #ፈጣን_መንገድ ላይ አንድ አሽከርካሪ መንገድ ስቶ ወጥቶ ከመብራት ፖል ጋር ተጋጭቶ እዛው መኪና ውስጥ እያለ መኪናው በከፍተኛ እሳት መያያዝና መንደድ ይጀምራል።

በመንገዱ ሲጓዙ የነበሩ አሽከርካሪዎች ይህን አይተው አላለፉም።

መኪናቸውን አቁመው ከሚነደው መኪና ውስጥ አሽከርካሪውን ለማውጣትና ለማዳን ርብርብ ጀመሩ።

ከእሳት ነበልባል ጋር #እየታገሉ ፤ በሹፌሩ በር በኩል ያለውን መስታወት ሰብረው ከብዙ እልህ አስጨራሽ ትግል በኃላ አሽከርካሪውን በእሳት ተያይዞ ከሚነደው መኪና ውስጥ በህይወት አወጡት።

በኃላም ወደ ሆስፒታል እንዲወሰድ አደረጉ።

አሽከርካሪው ላይ ምንም አይነት የከፋ ጉዳት አልደረሰበትም ተብሏል።

ከከፍተኛ እሳት ጋር ተጋፍጠው የሰው ህይወት ለማትረፍ ርብርብ ሲያደርጉ ከነበሩት አንዱ ከድር ቶላ ይባላል። (ጥቁር ጁንስ ሱሪ በነጭ ጫማ ያደረገው)

ወደ ስራ እየሄደ በነበረበት ሰዓት ነው ይህ ክስተት ያጋጠመው።

ከድር የነፍስ አድን ስራውን ፥ " በህይወቴ እጅግ በጣም አስፈሪው ቅጽበት ነበር። ይህንን መቼም ቢሆን አልረሳውም ሁሌም ቢሆን አስታውሰዋለሁ " ሲል አስረድቷል።

አሽከርካሪው በህይወት እንዲተርፍ ቦታው ላይ የነበሩ ሁሉም ሰዎች ላደረጉት ፍጹም #ሰብዓዊ ተግባርና ርብርብ ፈጣሪን አመስግኗል።

የነበረውን የህይወት አድን ርብርብ የሚያሳይ ቪድዮ ከድር ቶላ መኪና ላይ በነበረ የዳሽቦርድ ካሜራ የተቀረጸ ነው።

Video Credit : Kadir Tolla / ከድር ቶላ

#TikvahFamily

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" ከቤተክርስቲያን ጋር የሚያገናኘው ምንም ነገር የለም " - መምህር ዶ/ር አካለወልድ ተሰማ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ፤ የቀሲስ በላይ መኮንን ጉዳይ ከቤተክርስቲያኗ ጋር ምንም የሚያገናኘው ነገር የለም ብላለች።

" ምንም እንኳን ቤተክርስቲያኗ ውስጥ በከፍተኛ ኃላፊነት የሚገለግሉ ቢሆንም ተጭበርብሯል ከተባለው ሰነድ ጋር ግን ቤተክርስቲያኗን የሚያገናኘው ምንም ነገር የለም " ነው ያለችው።

የቀሲስ በላይን ጉዳይ በተመለከተ የመንበረ ፓቲሪያርክ ህዝብ ግንኙነት የሚዲያ ክፍል ዋና ኃላፊ  መምህር ዶ/ር አካለወልድ ተሰማ ለዶቼ ቨለ ሬድዮ ጣቢያ ቃላቸውን ሰጥተው ነበር።

መምህር ዶ/ር አካለወልድ ፥ " ሊቀአዕላፍ በላይ መኮንን በህግ ጥላ ስር በዋሉበት ጉዳይ ላይ ቤተክርስቲያን ጉዳዩን የመከታተል ጥረት ላይ ትገኛለች " ብለዋል።

" እስካሁን በተደረገው ክትትል ግን በህግ ጥላ ስር የዋሉበት ጉዳይ ከቤተክርስቲያናችን ጋር የሚያገናኘው ምንም ጉዳይ እንደሌለና በግል ህይወታቸው ውስጥ የገጠማቸው ነገር እንደሆነ ነው የተረዳነው " ሲሉ ገልጸዋል።

በቀጣይ ግን ጉዳዩ የቤተክርስቲያንን የሚጎዳ ነገር አለወይ ? ለሚለው በህግ ክፍል በኩል ማጣራት እንዲደረግ ትዕዛዝ መተላለፉን ለሬድዮ ጣቢያው በሰጡት ቃል አመልክተዋል።

ቀሲስ በላይ መኮንን ከአፍሪካ ኅብረት ኦፊሳላዊ የክፍያ ሰነድ ጋር ተመሳስለው የተዘጋጁ የተለያዩ ሐሰተኛ የክፍያ ሰነዶችን በመጠቀም ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የአፍሪካ ኅብረት የባንክ ሒሳብ ወደ ሌላ የባንክ ሒሳብ #ከ6_ሚሊዮን_ዶላር_በላይ (367 ሚሊዮን ብር የሚሆን) ለማዘዋወር ሲሞክሩ በቁጥጥር ሥር መዋላቸው ይታወሳል።

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#RoseWood

የቤትዎን ካቢኔት ሲያዙን ፦
✔️ በ አርኪቴክት ባለሞያ ለክተን እና ዲዛይን አደርገን
✔️ ካሉበት አድራሻ ዴሊቨር አድረገን
✔️ካቢኔት ከነግራናይት እና ሲንክ በጥንቃቄ ገጥመን ለመገልገል ዝግጁ የሆነ ካቢኔት በአጭር ጊዜ እናስረክባለን ።

ሮዝዉድ ፈርኒቸር ፦ 0905848586

ኣድራሻ ፦📍4ኪሎ ኣምባሳደር ሞል 2ኛ ፎቅ 
                 📍 እንቁላል ፋብሪካ ሩፋኤል

ቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇
/channel/R0seWood

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#ሊዝ #አዲስአበባ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ መሬትን በሊዝ ለማስተላለፍ 2ኛ ዙር ጨረታ አውጥቷል።

መሬትን በሊዝ የማስተላለፍ ተግባር ለአራት ዓመታት ከተቋረጠ በኋላ ግንቦት 5 ቀን 2015 ዓ.ም መጀመሩ ይታወሳል፡፡

2ኛው ዙር የመሬት ሊዝ ጨረታም ረቡዕ ሚያዝያ 9 ቀን 2016 ዓ.ም መውጣቱን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከቢሮና ከአዲስ ልሳን ጋዜጣ መረጃውን አግኝቷል።

በከተማዋ መሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ መረጃ መሠረት፣ በ2ኛው ዙር ጨረታ 243 መሬት (ቦታ) የተዘጋጀ ሲሆን፣ እነዚህ ቦታዎችም በአስር ክፍለ ከተሞች የሚገኙ ናቸው፡፡

በአራዳ ክ/ከተማ (ፒያሳ) በዓድዋ ድል መታሰቢያ አካባቢ በኮሪደር ልማት ምክንያት የፀዱ ቦታዎችን ጨምሮ ፦
- በንፋስ ስልክ ላፍቶ፣
- በኮልፌ ቀራንዮ፣
- በአራዳ፣
- በአቃቂ ቃሊቲ፣
- በየካ፣
- በቦሌ፣
- በአዲስ ከተማ፣
- በቂርቆስ፣
- በጉለሌ እና በልደታ ክፍለ ከተሞች የሚገኙ ለተለያዩ አገልግሎቶች የተዘጋጁ የልማት ቦታዎች በ2ኛው ዙር ጨረታ በሊዝ ሊተላለፉ እንደቀረቡ ታውቋል።

ከዚህ ቀደም አልሚዎች ተጫርተው አሸናፊ ከሆኑ በኋላ በሚተላለፉ የተለያዩ ቦታዎች ላይ “የይገባኛል” ጥያቄዎች ይነሱባቸው እንደነበር ነበር።

አሁን ለመተላለፍ የተዘጋጁ ቦታዎች ግን ከሶስተኛ ወገን ጥያቄ ነፃ መሆናቸውን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ ገልጿል።

ተጫራቾች የጨረታ ሰነዳቸውን ሚያዝያ 22 ቀን 2016 ዓ.ም ከቀኑ 11፡30 ሰዓት ድረስ ለም ሆቴል አካባቢ ኤም.ኤ (MA) ህንፃ ላይ በሚገኘው በከተማዋ መሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ ለዚህ በተዘጋጀ የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት እንዳለባቸው ተመላክቷል፡፡

ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ሚያዝያ 24 ቀን 2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡ዐዐ ሰዓት ጀምሮ በ9 ተከታታይ የስራ ቀናት በቦሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር አዳራሽ የሚከፈት ሆኖ፣ ዝርዝሩ በውስጥ ማስታወቂያ ይገለፃል ተብሏል፡፡

ተጫራቾች ቦታውን በአካል ቀርበው ለመመልከት ከፈለጉ በ16/8/16 ዓ.ም እና በ18/8/16 ዓ.ም ከጠዋቱ በ3፡00 እና ከሰዓት በ8 ሰዓት ለጨረታ የተዘጋጁ ቦታዎች የሚገኙበት ከፍለ ከተማ የመሬት ልማትና አስተዳደር ጽህፈት ቤት ድረስ በመቅረብ ለዚህ ስራ በሚመደቡ አስጎብኚዎች አማካኝነት መመልከት እንደሚችሉ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከአዲስ አበባ የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮና / ከአዲስ ልሳን ጋዜጣ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።

ዝርዝር የጨረታውን መረጃ ከታች (በቀጣይ ፖስት) እናያይዛለን።

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

“ ... ‘ ልጄ በአጋቾች እየተሰቃየች ነው። ገንዘብ ካላክሽ ልጅሽን እንገድላታለን ’ አሉኝ። አጋቾቹ 300 ሺሕ ብር ጠየቁኝ ” - እንባ የሚተናነቃቸው እናት

የ20 ዓመት ሴት ልጃቸው በሳዑዲ አረቢያ እና የመን ድንበር በደላሎች እንደታገተችባቸው፣ አጋቾቹ የጠየቁት ገንዘብ ሰሞኑን ካልተላከላቸው እንደሚገድሏት ማስጠንቀቂያ መስጠታቸውን፣ አጋቾቹ ይህን ያሉት ከአንድ ቀን በፊት መሆኑን የታጋቿ እናት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

እያለቀሱ ቃላቸውን የሰጡት እኚሁ እናት፣ “ ‘ልጄ በአጋቾች እየተሰቃየች ነው። ገንዘብ ካላክሽ ልጅሽን እንገድላታለን’ አሉኝ። አጋቾቹ 300 ሺሕ ብር ጠየቁኝ። ይህን ገንዘብ ለመላክ አቅሙ የለኝም። እባካችሁ ወገኖቼ ልጄን አድኑልኝ ” ሲሉ በውስጥም በውጪም ላሉ ወገኖች የእርዳታ ጥሪ አቅርበዋል።

አክለውም፣ “ ልጄም ‘እማዬ ገንዘቡን ካላክሽ ይገድሉኛልና እባክሽ ከዚህ ጉድ አውጪኝ’ አለችኝ። አጋቾቹም ‘ልጅሽ ያለችው በሳዑዲና የመን ድንበር ራጎ ነው’ የልጅሽን ደህንነት የምትፈልጊ ከሆነ ገንዘቡን ላኪ’ ብለው ስልኩን ዘጉት። ልጄን በሕይወት ላጣት ነው። እባካችሁ ወገን ድረሱልኝ ” ሲሉ ተማጸነዋል።

ልጃቸው ይህ ችግር የገጠማት ሕይወቷን ለመለወጥ ወደ ሳዑዲ አረቢያ #እየተሰደደች በነበረበት ወቅት መሆኑን ገለጸው፣ “ የቀን ሥራ እየሰራሁ ነው ያስተማርኳት። የልጄ ደህንነት አስጨንቆኛል። ወላጆች፣ እህት ወንድም ያላች ሁሉ፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ ሆይ እጃችሁን ዘርጉልኝ ” ሲሉ ተማጽነዋል።

የወጣቷን ቤተሰብ መርዳት ለምትፈልጉ በታጋቿ ወንድም መስፍን መኮንን ባዬ ንግድ ባንክ አካውንት 1000264883893 ዳግፋችሁን መላክ ትችላላችሁ።

የታጋቿ ቤተሰብ በስልክ ማነጋገር ለምትፈልጉ በ0945592726 ፍቅር ምስጋንን ማግኘት ይቻላል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ፥ ስለጉዳዩ ያነጋገራቸው አንድ ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁ ወደ ሳዑዲ የሚሄዱ ኢትዮጵያዊያንን ደህንነት በተመለከተ በሳዑዲ አስተባባሪ በሰጡት ቃል ፣ “ራጎ ረግረጋማና ከባድ ምሽግ ነው። ደላሎች ተጓዦችን አግተው ከ250 ሺሕ ብር ጀምሮ ይጠይቃሉ ” ብለዋል።

እኝሁ አካል አክለውም ፣ #በርካታ_ኢትዮጵዊያን ስደተኞች “ #ራጎ ” በሌሎች አካባቢዎች በስቃይ እንደሚገኙ፣ ወጣቱ  ከእነዚህ ወገኖች ትሞህርት ወስዶ በእንዲህ አይነት መንገድ ወደ ሳዑዲ አረቢያ ከመሰደድ እንዲቆጠብ አስገንዝበዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#ኮሬ

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፤ በኮሬ ዞን በተፈጸመ ጥቃት 3 ታዳጊ ልጆችን ጨምሮ 4 ሰዎች ተገደሉ።

ጥቃቱ የተፈጸመው ትላንት በጎርካ ወረዳ ፤ " ቆቦ ቀበሌ " ነው ተብሏል።

የኮሬ ዞን አስተዳደር ባወጣው መግለጫ ፥ ለንጹሐን አርሶ አደሮች ሞት ምክንያት ለሆነው ጥቃት " በምዕራብ ጉጂ ዞን ታጥቀው የሚንቀሳቀሱ ጽንፈኛ እና ፀረ-ሰላም " ሲል የጠራቸውን አካላት ተጠያቂ አድርጓል።

እንደ አካባቢው ነዋሪዎች ገለጻ ጥቃት ከደረሰባቸው ነዋሪዎች መካከል አንድ የ14 ዓመት ታዳጊ የሚገኝበት ሲሆን ሁለቱ ደግሞ እድሜያቸው ከ17 እስከ 19 ባለው ውስጥ ይገመታል።

አንድ ነዋሪ ፤ ታጣቂዎቹ ቀደም ብለው ማታ ላይ ገብተው ቦታ ይዘው እንደነበርና 7 ክላሽ የታጠቁ ሰዎች እንደሆኑ ገልጸዋል።

" ሟቾቹ ከብት ሊያግዱ ይዘው እየሄዱ እያለ፤ ከብት የሚታገድበት ቆላ የሚባል ቦታ ሲደርሱ እዚያ ጋር ነው ተኩስ የጀመሩት " ሲሉ አስረድተዋል።

ታጣቂዎቹ ጥቃት ከፈጸሙ በኋላ አራቱ ታዳጊዎች እያገዱ የነበሯቸውን ከብቶች ለመውሰድ ቢሞክሩም ተኩሱን ሰምተው በመጡ የአካባቢው ነዋሪዎች እንዲመለሱ ተደርገዋል።

የዞኑ አስተዳደር ባወጣው መግለጫ ፥ የኮሬ ሕዝብ በሚያዝያ ወር ብቻ ብዙ ሞቶችን ማስተናገዱን ገልጿል።

ምን ያህል የሚለውን በቁጥር አልገለጸም።

ነዋሪዎች ግን ከመጋቢት ወር ጀምሮ ቢያንስ አራት ጊዜ በተፈጸሙ ጥቃቶች ነዋሪዎች መገደላቸውን ገልጸዋል።

መረጃው የቢቢሲ አማርኛ አገልግሎት ነው።

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

አስደሳች ዜና ከሳፋሪኮም !

🎁 ልዩ ልዩ የኢንተርኔት ጥቅሎችን ከ M-PESA ሳፋሪኮም APP ላይ በመግዛት 50% ተጨማሪ ዳታ አግኝተን በነጻ ከሳፋሪኮም ወደ ሳፋሪኮም እንደዋወል! 🤳 ዳታ እንግዛ! በነጻ እንደዋወል!

🔗የM-PESA ሳፋሪኮም መተግበሪያ በዚህ ሊንክ እናዉርድ: https://play.google.com/store/apps/details?id=et.safaricom.mpesa.lifestyle

ስለ አገልግሎታችን ማንኛውንም ጥያቄ ወይም መረጃ  በቴሌግራም   ቻናላችን /channel/Safaricom_Ethiopia_PLC 24/7 ማግኘት ይቻላል!

የሳፋሪኮም ኢትዮጵያን ትክክለኛ መረጃዎችን በቀላሉ ለማግኘት ቀጥሎ በሚገኙት ይፋዊ የማህበራዊ ሚዲያዎች እንዲከታተሉ  እንጋብዛለን።

👉Facebook: https://www.facebook.com/SafaricomET
👉Twitter:
https://x.com/SafaricomET?t=y2XAHAhPNvFeZqXa2YE6aQ&s=08
👉Instagram: https://www.instagram.com/safaricomet?igsh=MWJtcjJrMzNhMzVsNg==
👉 YouTube: safaricomethiopia2751?si=w2o8uz61oHeZM9gm" rel="nofollow">https://youtube.com/@safaricomethiopia2751?si=w2o8uz61oHeZM9gm

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#RoseWood

የቤትዎን ካቢኔት ሲያዙን ፦
✔️ በ አርኪቴክት ባለሞያ ለክተን እና ዲዛይን አደርገን
✔️ ካሉበት አድራሻ ዴሊቨር አድረገን
✔️ካቢኔት ከነግራናይት እና ሲንክ በጥንቃቄ ገጥመን ለመገልገል ዝግጁ የሆነ ካቢኔት በአጭር ጊዜ እናስረክባለን ።

ሮዝዉድ ፈርኒቸር ፦ 0905848586

ኣድራሻ ፦📍4ኪሎ ኣምባሳደር ሞል 2ኛ ፎቅ 
                 📍 እንቁላል ፋብሪካ ሩፋኤል

ቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇
/channel/R0seWood

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#Update

' ቲክቶክ ' አሜሪካ ውስጥ ከታገድኩኝ " የ170 ሚሊዮን አሜሪካውያን የመናገርና ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት ይረገጣል " አለ።

ይህን ያለው የአሜሪካ የተወካዮች ምክር ቤት መተግበሪያው ከቻይና ካልተፋታ እንዲታገድ ረቂቅ ህግ ካጸደቁ በኃላ ነው።

የ 'ቲክቶክ' ቃል አቀባይ መተገበሪያው እንዲታገድ የሚለውን ረቂቅ ህግ አውግዘዋል።

" ከታገደ ፦
- የ170 ሚሊዮን አሜሪካውያንን የመናገር መብት ይረግጣል፣
- 7 ሚሊዮን ንግዶች እንዲጠፉ ይሆናል፣
- ለአሜሪካ ኢኮኖሚ በዓመት የሚገባውን 24 ቢሊዮን ዶላር ያሳጣል " ብለዋል።

አክለው ፤ " ባይትዳንስ የቻይና ወይም የሌላ አገር ወኪል አይደለም " ሲሉ ገልጸዋል።  " የቻይና ኩባንያ እንዳልሆነም በተደጋጋሚ ተናግረናል " ሲሉ አክለዋል።

ጉዳዩን የሚከታተሉ አካላት ግን ' ቲክቶክ ' ከቻይና ተፋቶ ድርሻው ለአሜሪካ ሰዎች ካልተሸጠ የጊዜ ጉዳይ ነው እንጂ #የመታገዱ ነገር አይቀሬ ነው ብለዋል።

ትላንት የአሜሪካ የተወካዮች ምክር ቤት ' ቲክቶክ ' በመላው ሀገሪቱ እንዲታገድ የሚያደርግ ረቂቅ ህግ አጽድቋል።

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

🔥ከባድ ትንቅንቅ የማያጣው የየኤፍ ኤ ካፕ ጨዋታዎች ወደ ሜዳ ተመልሰዋል🔥

Coventry vs Manchester United እሁድ ሚያዚያ 13 ከሰዓት 11፡30 ይፋለማሉ!

🔥 ማን ዩናይትድ ወደ  ፍፃሜ መቀጥል ይችላል?

👉 ዛሬውኑ ደንበኝነትዎን ያራዝሙ። ጨዋታዎችን ከትንታኔ ፣ ከተጫዋች ብቃት እስከ ቡድን ወኔ በሱፐርስፖርት ይከታተሉ!

የዲኤስቲቪ አገልግሎቶችን ለማግኘት ከታች ያለውን ሊንክ ይጫኑ!
👇
https://mydstv.onelink.me/vGln/eth2

#FACupAllOnDStv #ሁሉምያለውእኛጋርነው #DStvEthiopia #DStvSelfServiceET

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#AU #Fraud #CBE

ቀሲስ በላይ መኮንን ከአፍሪካ ኅብረት ኦፊሳላዊ የክፍያ ሰነድ ጋር ተመሳስለው የተዘጋጁ የተለያዩ ሐሰተኛ የክፍያ ሰነዶችን በመጠቀም ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የአፍሪካ ኅብረት የባንክ ሒሳብ ወደ ሌላ የባንክ ሒሳብ #ከ6_ሚሊዮን_ዶላር_በላይ (367 ሚሊዮን ብር) ለማዘዋወር ሲሞክሩ ነው በቁጥጥር ሥር ውለዋል።

ፍድር ቤት ቀርበውም ለፖሊስ ተጨማሪ ቀን ተሰጥቷል።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዜዳንት አቶ አቤ ሳኖ ምን አሉ ?

" በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ካለው የአፍሪካ ህብረት ሒሳብ የወጣ ገንዘብ የለም።

አንድ ሰው ሀሰተኛ ሰነዶችን ተጠቅሞ ለማውጣት ቢሞክርም እዛው በቦታው ላይ ተይዟል።

የማጭበርበር ሃሳብና ገንዘብ ለመውሰድ ጥረት ቢደረግም ማክሸፍ ችለናል። ይህንን የሞከሩት ሰዎች በፖሊስ ቁጥጥር ስር ናቸው። እኔ የማውቀው ይህን ብቻ ነው።

በመሰረቱ ጥሬ ገንዘብ በውጭ ምንዛሪ ሊሰጥ አይችልም። አጭበርባሪው መጥቶ  ሲጠይቅ ይህን እንኳን አያውቅም ነበር።

ሰውዬው እዚህ ሀገር የዶላር አካውንት ከሌለው ገንዘቡ ቢተላለፍም የትም ውስጥ ሊገባ አይችልም።

አጭበርባሪዎች በየቀኑ ነው ወደ ባንካችን የሚመጡት ፤ ባንክ ስለምንሰራ ይህ የተለመደ ነው። ነገር ን ሁሌም የማጭበርበር ድርጊቶቹ ከመሳካታቸው በፊት እንደርስባቸዋለን። ለፍርድም እናቀርባቸዋለን።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፥ የደንበኞቹን ሒሳቦች የመጠበቅ ኃላፊነት አለበት ያንን እያደረግን ነው። የአፍሪካ ህብረት እስካሁን ድረስ በይፋ ቅሬታ አላቀረበብንም። "

ስማቸው እንዲገለጽ ያልፈለጉ የአፍሪካ ኅብረት ምንጭ ምን አሉ ?

"የእኛ ሒሳብ ላይ መሰል ማጭበርበር ሲያጋጥም ይህ ለሶስተኛ ጊዜ ነው።

አሁን ላይ ማጭበርበሩ #በተከበሩ_ሰዎች አማካኝነት እየተሞከረ ነው። ይህ ደግሞ በጣም አስጨንቆናል። አንድ ቀን ባለስልጣናት ተመሳሳይ ነገር ላለማድረጋቸው ምንም አይነት ዋስትና የለንም።

እምነት እያጣን ነው። ስለዚህ ኢትዮጵያ ውስጥ ለደሞዝ አነስተኛ መጠን ያለው ፎሬክስ (የውጭ ምንዛሬ) ለመያዝ ወስነናል።

ይህን መሰሉ ሁኔታ የድርጅቱን ገንዘብ በውጭ ማቆየት እንድናስብ እያስገደደን ነው። "

https://telegra.ph/The-Reporter-04-21 #ሪፖርተር_ጋዜጣ

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#ኢትዮጵያ #ባንኮች

የአገሪቱ ባንኮች ከአሠራር ጋር በተያያዙ ክፍተቶች በተለያዩ ሥልቶች ለሚፈጸሙ የማጭበርበር ድርጊቶች በከፍተኛ ደረጃ ተጋላጭ እየሆኑ መምጣታቸውን ፣ ይህ ሁኔታም በቀጣይ የአጭርና የመካከለኛ ጊዜ ውስጥ የበለጠ እንደሚጨምር የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አስታውቋል።

ብሔራዊ ባንክ የአገሪቱ የፋይናንስ ዘርፍ ጤናማነትን በመገምገም አንድ ሪፖርት ይፋ አድርጓል።

ሪፖርቱ ምን ይላል ?

➡️ የአገሪቱ ባንኮች በበይነ መረብ ማጭበርበርያ ሥልቶች፣ ከባንኮች የውስጥ ሠራተኞችና ከሦስተኛ ወገን በሚደርሱባቸው የምዝበራ ድርጊቶች በከፍተኛ ደረጃ እየተጋለጡ ናቸው።

➡️ ባለፈው አንድ ዓመት ውስጥ ማለትም እስከ ሰኔ ወር 2015 ዓ.ም. ድረስ ባለው ጊዜ ውስጥ ብቻ በሐሰተኛ ሰነዶችና በሌሎች የማጭበርበር ድርጊቶች ባንኮች 1 ቢሊዮን ብር አጥተዋል። የተመዘበሩት የገንዘብ መጠንም ከቀዳሚው ዓመት በእጥፍ ጨምሯል።

➡️ የባንክ ማጭበርበሮች በአንድ ዓመት ውስጥ ብቻ ወደ 1 ቢሊዮን ብር ሲደርሱ፣ ከአምናው በእጥፍ አድጓል። እነዚህ ጉዳዮች የተከሰቱት በዋናነት ፦
° ሐሰተኛ የገንዘብ ኖቶችንና ቼኮችን በመጠቀም ገንዘብ በማጭበርበር፣
° ያልተፈቀደ የባንክ ዋስትና በማቅረብ፣
° የተሰረቁ የኤቲኤም ካርዶችን በመጠቀም ገንዘብ በማውጣት ድርጊት
° በሐሰተኛ የስልክ ጥሪዎችና አጭር የጽሑፍ መልዕክቶችን በመጠቀም ነው። በተጠቀሱት የማጭበርበሪያ ሥልቶችም 20 ባንኮች ጉዳት ደርሶባቸዋል። በሰኔ ወር 2015 መጨረሻ ላይ 3 ባንኮች 200 ሚሊዮን ብር ተዘርፈዋል።

➡️ ባንኮች አዳዲስ ምርቶችንና አገልግሎቶችን ሲተዋወቁ በአሠራር ክፍተቶች ሳቢያ በከፍተኛ ደረጃ ለአደጋ እየተጋለጡ ናቸው።

➡️ ባንኮች ከአሠራር ጋር የተያያዙ አደጋዎችን ለመከላከልና የመጭበርበር ተጋላጭነታቸውን ለመቀነስ፣ ውጤታማ የቁጥጥር ሥልቶችንና አሠራርችን በመተግበር ላይ ሊያተኩሩ ይገባል።

ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የ #ሪፖርተርጋዜጣ ነው።

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#SsellaPortFashion

ጫማዎች ፣ የሴቶች እና የወንዶች መዋብያ እቃዎች፣ የኤሌክትሮኒክስ አቃዎች መርጠው ይሸምቱ። ያለተጨማሪ ክፍያ እንልክሎታለን፣ ጥራት ያለው አገልግሎት እንሰጣለን።

ስልክ ፦ 0964341513 / 0919998383

የመረጡትን እቃ ይህን በመጫን ይላኩልን 👉 @businesslidu & @businesslidu2

ተጨማሪ ጫማዎችን ለመምረጥ እንዲውም ዋጋቸውን ለማወቅ ከታች ያለውን link ትጭነው join በማድረግ ይመልከቱ👇
/channel/+HSaoqnlQCrc1NjI8

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#እንድታውቁት #AddisAbaba

ነገ መንገድ ይዘጋል።

ነገ ሚያዚያ 13 ቀን 2016 ዓ/ም በአዲስ አበባ መነሻና መድረሻውን መስቀል አደባባይ ያደረገ ሩጫ ይካሄዳል።

ሩጫው የ2016 " የኢትዮጵያ ታምርት " የጎዳና ላይ የ10 ኪሎ ሜትር የሩጫ ውድድር ነው።

የአዲስ አበባን ዋና ዋና መንገዶችን የሚያካልል እንደሆነም ታውቋል።

መነሻው መስቀል አደባባይ ከዛም በለገሃር ፣ ሜክሲኮ አደባባይ ፣ ቡልጋሪያ ማዞሪያ ፣ ቄራ ፣ ጎተራ ማሳለጫ ፣ አጎና ሲኒማ ፣ ጥላሁን አደባባይ አድርጎ መዳረሻውን መስቀል አደባባይ ያደርጋል።

ይህን ተከትሎ ሩጫው ተጀምሮ እስኪያልቅ የሚዘጉ መንገዶች እንዳሉ የአዲስ አበባ ፖሊስ አሳውቋል።

በዚህ መሰረት ፦

- ከመገናኛ ወደ መስቀል የሚወስደው መንገድ ኡራኤል አደባባይ
- ⁠ከኦሎምፒያ አደባባይ ወደ መስቀል
- ከመስቀል ፍላዎር አደባባይ ወደ አጎና መስቀለኛ
- ከጎርጎሪዎስ አደባባይ ወደ ጎተራ
- ከጎተራ ሼል ወደ ጎተራ
- ከማሞ ማቋረጫ ወደ ጎተራ
- ከጎፋ ገብርኤል ወደ ጎፋ ማዞሪያ
- ከአልማዝዬ ሜዳ ወደ ቄራ በረት
- ከመካኒሳ አቦ አደባባይ ወደ ሳር ቤት አደባባይ
- ከካርል አደባባይ ወደ ሳር ቤት አደባባይ
- ከልደታ ፀበል ወደ ኤዩ መብራት
- ከቡልጋሪያ ማዞሪያ ወደኤዩ መብራት
- ከኦርቢስ መታጠፊያ/ጮራጋዝ/ መስቀለኛ ወደ ሲጋራ ፋብርካ
- ከጠማማ ፎቅ ወደ ጥይት ፋብርካ
- ከላንድ ማርክ ሆስፒታል ወደ ገነት መብራት
- ከከፍተኛ ፍ/ቤት /ባልቻ ሆስፒታል/ ወደ ሜክሲኮ አደባባይ
- ከአረቄ ፋብርካ ወደ ሜክሲኮ አደባባይ
- ከሠንጋ ተራ 40/60 መስቀለኛ ወደ ሠንጋ ተራ መብራት
- ከበድሉ ህንፃ ወደ ቴሌ ባር
- ከብሔራዊ ቲያትር መብራት ወደ ለገሃር መብራት
- ከሀራምቤ መብራት ወደ ሳንጆሴፍ መብራት
- ⁠ከብ/ቤተመንግስት ወደ መስቀል አደባባይ
- ⁠ከኢንተርኮንትኔታል ሆቴል ወደ ባምቢስ የሚወስዱ መንገዶች ከማለዳው 11:00 ሰዓት ጀምሮ ሩጫው እስኪጠናቀቅ ድረስ ለተሽከርካሪ ዝግ ይሆናሉ።

#AddisAbabaPolice #እንድታውቁት

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#Ethiopia #IMF

ኢትዮጵያ ከIMF ብድር ለማግኘት የብርን የመግዛት አቅም ለማዳከም ትስማማለች ? ሌላ አማራጭ የለም ?

የምጣኔ ሃብቱ ባለሞያ አቶ ያሬድ ኃይለመስቀል ፦

" devaluation የሚቀር አይመስለኝም። በምን ያህል ደረጃ devalue ይደረጋል የሚለው ጥያቄ ነው እንጂ devalue ሳይደረግ IMF / World Bank ገንዘብ ይሰጣል ብዬ እንደ ራሴ አልገምትም።

አማራጭ ፖሊስ በራሱ መጥፎ አልነበረም። ቅደም ተከተሉን አለማስተካከል ነው ትልቁ ስህተት። ለምሳሌ ከሌሎች መጀመር ይቻል ነበር።

liberalization ሊቀድም ይችል ነበር ከdevaluation ፤ liberalization ሲደረግ አዲስ ካፒታል ወደ ሀገር ውስጥ እንዲገባ ማድረግ ይቻላል።

በዚህ ሂደት ካፒታል / ዶላር ይገኝ ነበር። ይህ ደግሞ የዶላርም ይሁን የሌላ ውጪ አሳሳቢ አይሆንም ነበር። እዳንም መቀነስ ይቻላል። አሁን ግን እዳ ይጨምራል።

ለምሳሌ ፦ የዛሬ 7 ዓመት ለባቡር ወይም ለሌላ የተበደርነው ዶላር ቢኖር መንግሥት ይጠበቅበት የነበረው 22 ብር ቀረጥ ሰብስቦ ወደ 21 ዶላር ቀይሮ መስጠት ነበር አሁን 56 እና 57 ታክስ መሰብሰብ አለበት።

የኑሮው ውድነት ?

ካለንበት ችግር በመነሳት የብር የመግዛት አቅም እንዲዳከም ቢወሰን በዋጋ ንረት ላይ በኑሮው መወደደ ላይ የሚያደርሰው ተፅእኖ ከባድ ነው።

ብዙ ነገር imported inflation የሚባለው ነዳጅ 39 ብር ነበር አሁን ከ70 በላይ ሆኗል ፤ ማዳበሪያውም ፣ ስንዴውም ፣ መኪናውም በብዛት 21 ቢሊዮን ዶላር የሚገመት እቃ ወደ ሀገር ይገባል 3 - 4 ቢሊዮን የሚገመት export ታደርጋለች ይሄ ልዩነት ላይ ያለው 17 ቢሊዮን ብር የሚመጣውን እቃ ዋጋ ሊጨምረው ይችላል። ይሄ በእያንዳንዱ ቦታ ተበታትኖ በየሰዉ ኑሮ ላይ ተፅእኖ ያደርጋል።

inflation አሁን ትንሽ ረገብ አለ ቢባልም ከፍተኛ ነው። እንደገና ከፍ ሊል ይችላል።

ካፒታል ያላቸው ሰዎች ምንም ችግር የለባቸውም። ለምሳሌ ነጋዴ እቃ ቢወደድም ቢረክስም ችግር የለበትም የገዛበት ላይ ጨምሮ ነው የሚሸጠው ምናልባት ብዙ ላይሸጥ ይችላል ያ ሊጎዳው ይችላል።

ቁርጥ ያለ ገቢ ያለው ሰው ሊጎዳ ይችላል። ለምሳሌ የዛሬ 7 ዓመት 22 ሺህ ብር ደመወዝ የሚከፈለው ሰው 1000 ዶላር አካባቢ ነው አሁን ግን 450 ነው የሚያገኘው ስለዚህ ደመወዙ 50% ቅናሽ አድርጓል። በሌላ በኩል የመኖሪያ፣ የምግብ ዋጋ ጨምሯል።

ብዙ አማራጭ ያለ አይመስለኝም ከ devalue አንጻር። ያለውን ብር መቀበል ነው። አልያም ብሩን አልፈልግም ብሎ ሌላ አማራጭ መፈለግ ነው። ወይም የሚባለውን አድርጎ የሚያስከትለውን ችግር መፍትሄ መፈለግ ነው። "

ይህ የምጣኔ ሃብት ባለሞያ አስተያየት የተወሰደው ከሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬድዮ መሆኑን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ይገልጻል።

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#ሊዝ #አዲስአበባ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ ፤ በአራዳ ክፍለ ከተማ (ፒያሳ) በዓድዋ ድል መታሰቢያ አካባቢ በኮሪደር ልማት ምክንያት የፀዱ ቦታዎችን ጨምሮ በአጠቃላይ በ10 ክፍለ ከተሞች የሚገኙ ለተለያዩ የልማት ስራዎች የሚውሉ ቦታዎችን በጨረታ አወዳድሮ በሊዝ ለማስተላለፍ እንደሚፈልግ አሳውቋል።

ለ1 የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 2,300.00 (ሁለት ሺ ሶስት መቶ ብር) በቴሌ ብር መክፈል የግድ እንደሆነ ተነግሯል።

የጨረታው ሰነድ እስከ ሚያዚያ 24/2016 ዓ/ም ድረስ እየተሸጠ እንደሚቆይም ታውቋል።

አንድ ተጫራች በአንድ የጨረታ ዙር ከአንድ ቦታ በላይ መጫረት አይችልም ተብሏል። ከአንድ በላይ ቦታ ተጫርቶ ከተገኘም ተጫራቹ ከጨረታ ውጪ እንደሚሆን ተገልጿል።

🔵 ከላይ ሙሉ የጨረታው ዝርዝር መረጃ የተያያዘ ሲሆን በአራዳ ክፍለ ከተማ ከተራ ቁጥር 5 - 13 ወረዳ 01 በሚል የተገለፁ ቦታዎች ትክክለኛ መገኛ " ወረዳ 05 " መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ ገልጿል።

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#SamiTech

አዳዲስ ላፕቶፕች  ከአንድ ዓመት ዋስትና ጋር!!
@samcomptech

በአገልግሎት አሰጣጣችን ላይ እና  በዕቃዎቻችን ጥራት ላይ  ደንበኞቻችን ምስክሮቻችን ናቸው። ዛሬም ብዛትንም ጥራትንም ሳንቀንስ እያስተናገድን እንገኛለን። ለቢሮዎች፣ ለተማሪዎች ፣ ለዲዛይን ባለሙያዎች ፣ ለጌመሮች ወ.ዘ.ተ

አቅምን ካገናዘቡ እስከ ቅንጡ ላፕቶፖች ይህ ቀረ ሳይሉ የሚያገኙበትን ሱቃችንን ይጎብኙ። የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ ባሉበት ሆነው ይዘዙን እናደርሳለን።

የዕቃዎች ዋጋ፣ ዓይነት እና አድራሻ ለማግኘት ይሄን 👉 @samcomptech ተጭነው በቴሌግራምው ማየት ይችላሉ። @sww2844 0928442662 / 0940141114

https://maps.app.goo.gl/H3PM1NrTcQ4SWkK17

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

በአዲስ አበባ ከተማ የ2ኛው ዙር የመሬት ሊዝ ጨረታ

የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ በአራዳ ክ/ ከተማ (ፒያሳ) በዓድዋ ድል መታሰቢያ አካባቢ በኮሪደር ልማት ምክንያት የፀዱ ቦታዎችን ጨምሮ ፦
- በንፋስ ስልክ ላፍቶ፣
- በኮልፌ ቀራንዮ፣
- በአራዳ፣
- በአቃቂ ቃሊቲ፣
- በየካ፣
- በቦሌ፣
- በአዲስ ከተማ፣
- በቂርቆስ፣
- በጉለሌ
- በልደታ ክፍለ ከተሞች የሚገኙ ለተለያዩ አገልግሎቶች የተዘጋጁ የልማት ቦታዎችን በጨረታ አወዳድሮ በሊዝ ማስተላለፍ እንደሚፈልግ አሳውቋል።

(ዝርዝር የጨረታው መረጃ በPDF ተያይዟል - ይመልከቱ)

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ይህ የጨረታ መረጃ ባለቤት አዲስ ልሳን መሆኑን ያሳውቃል።

#TikvahFamilyAddisAbaba

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#Hawassa

ዛሬ ከሀዋሳ ከተማ ከዩኒቨርስቲው ፊት ለፊት በተለምዶ " ፍየል ገበያ " አካባቢ አንድ ወጣት ሞቶ ተገኝቷል።

የሟችን ማንነት ማወቅ ያልቻሉት በአካባቢው ላይ የነበሩ ሰዎች ተደናግጠው ሲመለከቱ ነበር።

በአካባቢዉ የተፈጠረውን ግርግር ተከትሎ ቦታው ላይ የደረሰው የከተማው ፖሊስ ቦታው የገበያ ግርግር ያለበት ከመሆኑ የተነሳ አስክሬኑን ፎቶ ከሚያነሱ ግለሰቦች ሲጠብቅ ነበር።

በስፍራዉ የተገኘዉ የቲክቫህ ኢትዮጵያ የሀዋሳ ቤተሰብ አባል ሁኔታውን ለማጣራት ባደረገዉ ጥረት የአካባቢዉ ሰዎች ግራ በሚያጋባ ሁኔታ ድንገት ሞቶ እንዳዩትና ከዚህ በፊት አይተዉት እንደማያውቁ ገልጸዋል።

በሌላ በኩል ስለሁኔታዉ የጠየቅናቸዉ በቦታዉ የደረሱ የፖሊስ ቡድን አባላት በበኩላቸዉ ጉዳዩን የማጣራት ስራ እንደተጀመረ በመግለፅ ለጊዜዉ ለህዝብ የሚሰጥ መረጃ እንደሌላቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከመሸ የሲዳማ ክልል ጸጥታ ቢሮ ኮሙዩኒኬሽን ስለ ጉዳዩ ጠይቋል።

በዚህም ሟች የዩኒቨርስቲ ተማሪ እንዳልነበር አረጋግጧል።

ይሁንና በሟች አስክሬን ላይ ጉዳት ስለማይታይ የሀዋሳ ሪፈራል ሆስፒታል ተወስዶ ከተመረመረ በኋላ ለተጨማሪ ምርመራ ወደ አዲስ አበባ እንዲሄድ መወሰኑን ገልጿል።

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#Update

የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ በተቋሙ በማህተም ተደግፎ ስለተለጠፈው " የምግብ በጀት እጥረት አጋጥሞናል ስለዚህ የሜኑ ማሻሻያ አድርገናል " የሚለውን ማስታወቂያ በተመለከተ መግለጫ አውጥቷል።

ተቋሙ በመግለጫው ምን አለ ?

- " ከዚህ ቀደምም ቢሆን በየወቅቱና እንዳስፈላጊነቱ ' የምግብ ሜኑ ማሻሻያ ' ሲደረግ ነበር። "

- " አንዳንድ ኃላፊነት የማይሰማቸው የማህበራዊ ትስስር ገጾች እንዲሁም የሚድያ ተቋማት ዩኒቨርሲቲው ያደረገውን የምግብ ማሻሻያ ሜኑ አስመልክቶ ተጨባጭነት የሌለውን መረጃ በማሰራጨት የተቋሙን በጎ ገጽታ ለማጠልሸት እና የፖለቲካ መጠቀሚያ ለማድረግ እየተንቀሳቀሱ ነው። "

🔴 የትኞቹ ማህበራዊ ትስስር ገጾችና ሚዲያዎች ተጨባጭነት የሌለው መረጃ እንዳሰራጩ በግልጽ ስም አልጠቀሰም።

- " ከወራት በፊት የተደረገ የሜኑ ማሻሻያ ለማሳወቅ ማስታወቂያ ወጥቷል። ይህም የቀን ስህተት የነበረበት መሆኑን እና ' አዲስ የተደረገ የምግብ ሜኑ ማሻሻያ ' እንደሌለ እንገልጻለን። "

- " ኃላፊነት በማይሰማቸው የማህበራዊ ትስስር ገጾች እንዲሁም የሚድያ ተቋማት ' ዩኒቨርሲቲው በምግብ እጥረት ምክንያት ተማሪዎችን ሊበትን ነው '  እየተባለ የሚሰራጨው ሀሰተኛ መረጃ በተቋሙ ዘንድ በፍጹም ተቀባይነት የለውም። "

🔴 የትኛው የማህበራዊ ትስስር ገጽ እና ሚዲያ ተማሪዎች ሊበተኑ ነው ብሎ እንዳሰራጨ ስም አልጠቀሰም።

- " ለተማሪዎቻችን ከምንጊዜውም በላይ የተቋሙ አቅም በሚፈቅደው መጠን ጥራት ያለውን ምግብ በበቂ ሁኔታ በማቅረብ የመማር ማስተማር ሥራው እንዳይስተጓጎል አበክረን እንሰራለን። "

- " ለተማሪዎቹ ወቅቱ በሚፈቅደው አግባብ ጥራቱን የጠበቀ ምግብ ለማቅረብ የሜኑ ማሻሻያ ከማድረግ ያለፈ በተማሪ ምገባ ላይ አንዳች ጉዳት  አይፈጽምም። "

- " አንዳንድ ኃላፊነት የጎደላቸው የማህበራዊ ትስስር ገጾች እና መገናኛ ብዙሃን ተቋሙን የፖለቲካ መጠቀሚያ ለማድረግ በዩኒቨርሲቲው ላይ የከፈቱትና እየከፈቱ የሚገኙት የገጽታ ማጠልሸት ድርጊት በፍጹም ተቀባይነት የሌለውም፤ በህግ አግባብ ያስጠይቃል። "

🔴 እዚህም ጋር የትኞቹ እንደሆኑ በግልጽ ስም አልተጠቀሰም።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ፤ ከሰሞኑን በወላይታ ሶዶ እና በዲላ ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ የተለጠፉትን ማህተም ያረፈባቸውን ተመሳሳይ ይዘት ስላላቸው ማስታወቂያዎች በተመለከተ መረጃ ማጋራቱ ይታወሳል።

ተቋማቱ ውስጥ የተለጠፉ ማስታወቂያዎች ፥ " እንደ ሀገር የምግብ በጀት እጥረት አጋጥሞናል። የምግብ ጥሬ ዕቃ ዋጋም በየቀኑ ከመጨመሩ ጋር በተያያዘ የተማሪዎች የምግብ በጀታቸው ሙሉ በሙሉ ካለቀ ወራት ተቆጥሯል " ይላል።

ይቀጥልና ፥ " ተቋሟችን የሚያደርገው ድጎማ ተማሪዎቻችን ትምህርታቸውን አቋርጠው እንዳይወጡ ባሉን የምግብ ጥሬ እቃዎች አገልግሎት እየሰጠን ነው " ሲል ይገልጻል።

የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ማስታወቂያ ደግሞ " ባሉን የምግብ ጥሬ ዕቃዎች አገልግሎት እየሰጠን ቢሆንም በአሁን ሰዓት እጅግ በጣም #እየከበደ ስለሆነ የሜኑ ማሻሻያ ለማድረግ ተገደናል " ይላል።

ይህ በተመለከተ የዲላ ዩኒቨርሲቲ የምርምር እና ቴክኖሎጂ ምክትል ፕሬዝደንት ዶ/ር ሀብታሙ ተመስገን ፥ ማስታወቂያውን ሆነ ሀሳቡን #እንደማያዉቁት በመግለጽ " ማን ይህን ሀሳብ እንዳመጣ እንዲሁም ማስታወቂያ እስከ መለጠፍ ድረስ እንደደረሰ እናጣራለን " የሚል ምላሽ ነው የሰጡት።

የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲው ምክትል ፕሬዝደንት ዶ/ር አክብር ጩፋ ደግሞ ፤ " ሶሻል ሚዲያ ላይ  መረጃው ሲንሸራሸር እያየን ነው " ካሉ በኃላ ሁኔታዉን ለማጣራት #ማኔጅመንቱ ስብሰባ እንደሚቀመጥ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸው ነበር።

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#Mekelle

በመቐለ የሚገኘው " ፍሬምናጦስ የአረጋውያን የአእምሮ ህሙማን የህፃናት እንክብካቤ ማእከል " በእሳት ቃጠሎ አደጋ ምክንያት ከፍተኛ ወድመት አጋጥሞታል። 

አደጋው ያጋጠመው ሚያዝያ 7/ 2016 ዓ.ም ሲሆን ለበጎ አድራጊዎች ሁሉ የእርዳታ ጥሪ ተማጽኖ አቅርቧል።

የምግባረ ሰናይ ድርጅቱን የተለያዩ በጎ አድራጊዎች ሲረዱት ቆይተዋል።

የሚያዘያ 7ቱ የእሳት አደጋ ከአጋዦቹ አንዱ የሆነው መስፍን ኢንዳስትሪያል ኢንጅነሪንግ ሚሊዮን ብሮች በመስጠት ባሰራው አዳራሽ ነው የደረሰው።

በተነሳው ቃጠሎም አዳራሹ ሙሉ በሙሉ ሲወድም በተረጂዎች ማደሪያ ፣ መመገብያና ፣ መስሪያ ክፍሎች ወድመት ደርሷል።

በከፍተኛ ውጪ የተሰራው አዳራሽ ሚያዝያ 6/2016 ዓ.ም. የተመረቀ ሲሆን በነጋታው  ሚያዝያ 7/2016 ዓ.ም ከቀኑ 10:00 ሰዓት ነው በእሳት ሙሉ በሙሉ የወደመው።

የአደጋው መንስኤ በኤሌክትሪክ ማስተላለፍያ በተነሳ ቃጠሎ ነው ተብሏል።

ያጋጠመው ቃጠሎ ከፍተኛ የነበረ ቢሆንም በህዝብና በመቐለ የእሳት አደጋ መከላከያ ብርጌድ የተቀናጀ ርብርብ በማእከሉ በሚገኙ አቅመ ደካሞች የህይወት ማጣት አደጋ  አልደረሰም።

ምግባረ ሰናይ ድርጅቱ በእሳት አደጋ ቃጠሎ ምክንያት የመኝታ፣ መመግብያ ክፍሎቻቸው የተቃጠለባቸው የሚንከባከባችው አቅሞ ደካሞች ሜዳ ላይ ተጥለው እንደሚገኙ በመጠቆም በአገር ውስጥና በውጭ የሚገኙ ሰብአውያን ሁሉ እንዲረዱት ጥሪ አቅርበዋል።    

መርዳት የሚፈልጉ ወገኖች ፍሬምናጦስ  የአረጋውያን የእአምሮ ህሙማንና የህፃናት እንክብካቤ ማእከል በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000622132404 ሂሳብ ቁጥር መጠቀም ይችላሉ።

#TikvahFamilyMekelle

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#SamiTech

አዳዲስ ላፕቶፕች  ከአንድ ዓመት ዋስትና ጋር!!
@samcomptech

በአገልግሎት አሰጣጣችን ላይ እና  በዕቃዎቻችን ጥራት ላይ  ደንበኞቻችን ምስክሮቻችን ናቸው። ዛሬም ብዛትንም ጥራትንም ሳንቀንስ እያስተናገድን እንገኛለን። ለቢሮዎች፣ ለተማሪዎች ፣ ለዲዛይን ባለሙያዎች ፣ ለጌመሮች ወ.ዘ.ተ

አቅምን ካገናዘቡ እስከ ቅንጡ ላፕቶፖች ይህ ቀረ ሳይሉ የሚያገኙበትን ሱቃችንን ይጎብኙ። የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ ባሉበት ሆነው ይዘዙን እናደርሳለን።

የዕቃዎች ዋጋ፣ ዓይነት እና አድራሻ ለማግኘት ይሄን 👉 @samcomptech ተጭነው በቴሌግራምው ማየት ይችላሉ። @sww2844 0928442662 / 0940141114

https://maps.app.goo.gl/H3PM1NrTcQ4SWkK17

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

🍲 " የምግብ በጀት እጥረት አጋጥሞናል " 🍲

ሰሞኑን በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ከተማሪ የምግብ አገልግሎት ጋር ተያይዞ ፤ " የምግብ በጀት እጥረት ገጥሞናል ያለውን ብሉ " አይነት ማስታዎቂያዎች መለጠፋቸውን ተከትሎ በበርካቶችን አነጋግሯል።

ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ የተለጠፉ ማስታወቂያዎች ምንድነው የሚሉት ?

- " እንደ ሀገር የምግብ በጀት እጥረት አጋጥሞናል። የምግብ ጥሬ ዕቃ ዋጋም በየቀኑ #ከመጨመሩ ጋር በተያያዘ የተማሪዎች የምግብ በጀታቸው ሙሉ በሙሉ ካለቀ ወራት ተቆጥሯል። "

- " ተቋማችን የሚያደርገው ድጎማ ተማሪዎቻችን ትምህርታቸውን አቋርጠው እንዳይወጡ ባሉን የምግብ ጥሬ እቃዎች አገልግሎት እየሰጠን ቢሆንም በአሁን ሰዓት እጅግ በጣም #እየከበደ ስለሆነ የሜኑ ማሻሻያ ለማድረግ ተገደናል። "

- " ከአሁን በኃላ የተሻሻለው ሜኑ ተግባራዊ ይሆናል። "

- " በተወሰኑ በስቶራችን ውስጥ ባሉ የምግብ ጥሬ ዕቃዎች እና በአትክልት የምግብ አገልግሎት እየሰጠን ነው። በአስቸኳይ የምግብ ጥሬ ዕቃ ግዥ አቅርቦት እንዲሟላ ጠይቀናል እስከዛ ታገሱ። "

... ይላሉ ማስታወቂያዎቹ።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ፥ በዲላ እንዲሁም በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲዎች ካሉ የቤተሰቡ አባላት ማህተም ያረፈባቸውን ማስታወቂያዎች ተልኮለት ተመልክቷል።

ይህ ነገር የቤተሰብ የጭንቀት ምንጭ ከመሆኑ በላይ ፦

° ዩኒቨርሲቲን የሚያክል እጅግ ትልቅ ተቋም እንዴት መጭውን የዋጋ ንረት እንዲሁም የዓመቱ የምግብ ወጪ ያላገናዘበ በጀት ይይዛል ?

° ለረጅም ዓመታት ለተማሪ በቀን የሚመደበው ገንዘብ አነስተኛ ሆኖ ሳለ እንዴት ይህ ሊፈጠር ቻለ ? የሚሉና ሌሎች ነቀፌታዎች ተሰምተዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ፤ " የምግብ በጀት እጥረት ገጥሞናል " የሚል ማስታወቂያ ከተለጠፈባቸው ተቋማት አንዱ ወደሆነው ዲላ ዩኒቨርሲቲ ደውሏል።

▪️የተከሰተው ችግር ምንድነው ❓

▪️በዚህ አይነት ሁኔታ ተማሪዎች ከመጎዳታቸው በላይ ወላጆችንስ አያስጨንቅም ወይ ❓ ... ሲል ለዩኒቨርስቲው የምርምር እና ቴክኖሎጂ ምክትል ፕሬዝደንት ዶ/ር ሀብታሙ ተመስገን ጥያቄ አቅርቧል።

ዶ/ር ሀብታሙ ፤ ማስታወቂያውንም ሆነ ሀሳቡን እንደማያዉቁት በመግለጽ " ማን ይህን ሀሳብ እንዳመጣ እንዲሁም ማስታወቂያ እስከ መለጠፍ ድረስ እንደደረሰ እናጣራለን " ብለዋል።

" ተማሪዎች ሆኑ ወላጆች ምንም የሚያሳስባቸዉ ነገር ሊኖር አይገባም " ያሉ ሲሆን ዩኒቨርሲቲዉም ሆነ እርሳቸዉ የሚመሩት የተማሪዎችን ጉዳይ የሚመለከት ቢሮ ችግሩ እንደሌለበት ገልጸዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ በተመሳሳይ ማስታወቂያ ወደ ተለጠፈበት የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ደውሏል።

የዩኒቨርሲቲው ምክትል ፕሬዝደንት ዶ/ር አክብር ጩፋ ፥ " ሶሻል ሚዲያ ላይ መረጃው ሲንሸራሸር እያየን ነው " ብለዋል።

" ሁኔታዉን ለማጣራት #ማኔጅመንቱ ስብሰባ ይቀመጣል። የስብሰባዉን ወጤት የተመለከተ መረጃ በፍጥነት አደርሳችኋለሁ " ሲሉ ገልጸዋል።

NB. ከላይ ተየያያዙት ማስታወቂያዎች ማህተም ያረፈባቸው ናቸው።

መረጃው በሀዋሳው የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ተዘጋጅቶ ነው የተላከው።

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#ATTENTION🚨

" አንዳንድ ወጣት ሴቶች ከቫይረሱ በላይ #እርግዝናን_ይፈራሉ "

ስለኤች አይቪ/ኤድስ ስርጭት የሚሰጠው የግንዛቤ ፈጠራ ሥራ ከጊዜ ወደጊዜ እየተቀዛቀዘ መሆኑን በጤና ሚኒስቴር የኤች አይቪ ኤድስ መከላከልና መቆጣጠር ገልጿል።

ችግሮች ከመባባሳቸው በፊት ትኩረት ሰጥቶ መሥራት እንደሚገባ አሳስቧል።

ቫይረሱ ኢትዮጵያ መግባቱ ከተረጋገጠበት ጊዜ አንስቶ በተሰራው እንቅስቃሴ ብዙ ለውጦች መመዝገባቸውን አስታውሷል።

ይሁን እንጂ የተመዘገቡት ለውጦች በተወሰነ ደረጃም ቢሆን መዘናጋት እንደፈጠሩ ፤ የሚዲያዎች ተሳትፎም መቀዛቀዙን ጠቁሟል።

በአሁኑ ወቅት ኤች አይ ቪ ቫይረስን በተመለከተ እየተሠሩ ያሉ ሥራዎች ትኩረት የሚሹና በይበልጥ ተጋላጭ የሆኑ የማኅበረሰብ ክፍሎች ላይ ብቻ ትኩረት ያደረጉ ናቸው ብሏል።

እነዚህም ፦
- ሴተኛ አዳሪዎች፣
- አደንዛዥ እፅ የሚጠቀሙ ሰዎች፣
- የረጅም ርቀት አሽከርካሪዎች፣
- አፍላ ወጣቶች በተለይ (ከማኅበራዊ ሚዲያ ጋር በተያያዘ)፣
- የቀን ሠራተኞች፣
- ከማኅበራዊ ችግሮች ጋር ተያይዞ ተጋላጭ የሆኑት እንደሆኑ አመልክቷል።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ የስርጭት መጠኑ ከ1 በመቶ በላይ ቢሆንም ከቦታ ቦታ በፆታ፣ በኅብረተሰብ ክፍል፣ በገጠርና በከተማ ከፍተኛ ልዩነት አለው ብሏል።

በከተሞች ያለው ስርጭት በገጠር ካለው በሰባት እጥፍ እንደሚበልጥም ጠቁሟል።

ይህንን ልዩነት መሠረት ያደረገ አጠቃላይ ማኅበረሰቡን ተደራሽ የሚያደርግ የግንዛቤ ፈጠራ ሥራ እየተከናወነ አይደለም ብሏል።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ ፦
° የመጠጥ ቤቶች ፣
° የጫት ቤቶች
° በሺሻ ቤቶች መስፋፋት ሌላ ተግዳሮቶች እየሆኑ መምጣታቸውን ገልጿል።

" አንዳንድ ወጣት ሴቶች ከቫይረሱ በላይ እርግዝናን ይፈራሉ። የወጣቶች አዲስ የመያዝ ምጣኔ ጨመረ ባይባልም እየቀነሰ አይደለም፤ ይህ በራሱ ችግር ለመኖሩ አመላካች ነው "ም ብሏል።

በተለይ በወጣቶች በኩል ሁሉን አቀፍ ሥራ ባለመሠራቱ እንደ ሀገር ዋጋ ሊያስከፍሉ የሚችሉ አጋላጭ ባሕሪያት እየተስተዋሉ መሆኑን አመልክቷል።

የኤች አይ ቪ ቫይረስን በተመለከተ ጠንካራ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎችን እንደሀገር ማከናወን እንደሚጠበቅ አሳስቧል። #ኢፕድ

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#ቀነኒሳ_በቀለ👏

አንጋፋው የኢትዮጵያ አትሌት ቀነኒሳ በቀለ በ41 ዓመቱ ዛሬ በለንደን የተካሄደ የማራቶን ውድድርን በ2ኛነት አጠናቋል።

በርካቶች ለአትሌቱን ትጋት ፣ ጥንካሬና ቁርጠኝነት አድናቆት እያጎረፉ ይገኛሉ።

አንጋፋው አትሌት ቀነኒሳ በቀለ የለንደን ማራቶን ውድድርን 2 ሰዓት ከ4 ደቂቃ ከ15 ሰከንድ በመግባት ነው ሁለተኛ ደረጃን ይዞ ያጠናቀቀው።

የዓለም አትሌቲክስም አትሌቱ ላሳየው ድንቅ ብቃት አድናቆቱን ችሯል።

የዛሬው ማራቶን የገባበት ሰዓት ከ2019 ወዲህ ከ40 ዓመት በላይ በሆናቸው አትሌቶች ዘንድ የተመዘገበ የመጀመሪያው እንደሆነም ጠቁሟል።

@tikvahethsport @tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

ባለፈው ማክሰኞ ሚያዚያ 8 ቀሲስ በላይ መኮንን በቁጥጥር ስር ውለዋል።

ቀሲስ በላይ መኮንን በ ' አፍሪካ ኅብረት ' ቅጥር ግቢ ውስጥ በሚገኘው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅርንጫፍ በአካል በመቅረብና ከአፍሪካ ኅብረት ኦፊሳላዊ የክፍያ ሰነድ ጋር ተመሳስለው የተዘጋጁ የተለያዩ ሐሰተኛ የክፍያ ሰነዶችን በመጠቀም ከአፍሪካ ኅብረት የባንክ ሒሳብ ወደ ሌላ የባንክ ሒሳብ ከ6 ሚሊዮን ዶላር በላይ (367 ሚሊዮን ብር) ለማዘዋወር ሲሞክሩ ነው በቁጥጥር ሥር የዋሉት።

የቀረበውን ሐሰተኛ የክፍያ ሰነድ የተጠራጠሩት የባንኩ ሠራተኞች ለአፍሪካ ኅብረት የሥራ ኃላፊዎች ስልክ በመደወል ለባንኩ ስለቀረቡት የክፍያ ሰነዶች እና #እንዲከፈል ስለተጠየቀው የገንዘብ መጠን በማሳወቅ የክፍያ ትዕዛዙን ትክክለኛነት እንደጠየቁ ለማወቅ ተችሏል።

የአፍሪካ ኅብረት የሥራ ኃላፊዎች የተጠቀሰውን የክፍያ ሰነድ ምንም እንደማያውቁትና ኅብረቱም የተባለውን የክፍያ ትዕዛዝ እንዳልሰጠ አሳውቀዋል።

ይህን ተከትሎ የክፍያ ሰነዱን ይዘው ከ6 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገንዘብ ለማዘዋወር በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የአፍሪካ ኅብረት ቅርንጫፍ በአካል የተገኙት ቀሲስ በላይ፣ የኅብረቱ የፀጥታ ሠራተኞች በቁጥጥር ሥር ካዋሉዋቸው በኋላ ለፌዴራል ፖሊስ አስረክበዋቸዋል፡፡

የፌዴራል ፖሊስ ተጠርጣሪውን ቀሲስ በላይ ሐሙስ ሚያዝያ 10 ቀን 2016 ዓ.ም. ለፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ አራዳ ምድብ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት አቅርቧቸዋል።

ፌደራል ፖሊስ ለፍርድ ቤት ምን አለ ?

- ቀሲስ በላይ ሐሰተኛ የክፍያ ሰነዶችን በመያዝ በአፍሪካ ኅብረት ቅጥር ግቢ ውስጥ በሚገኘው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅርንጫፍ በአካል እንደቀረቡ ገልጿል።

- ለ3 ግለሰቦችና ለ1 የግል ድርጅት የባንክ ሒሳቦች በድምሩ 6 ሚሊዮን 50 ሺሕ ዶላር ሊያዘዋውሩ ሲሉ በአፍሪካ ኅብረት የፀጥታ ሠራተኞች ተይዘው ለፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ተላልፈው እንደሰጡ ተናግሯል።

- የተጠረጠሩበትን የወንጀል ድርጊት ለችሎቱ በማስረዳት ተጨማሪ ምርመራ ለማከናወን የ14 ቀን ጊዜ እንዲሰጠው ጠይቋል።

ተጠርጣሪ ቀሲስ በላይ ምን አሉ ?

የተባለውን ድርጊት እንደፈጸሙ ያመኑ ቢሆንም ፣ በወንጀል ድርጊት እንዳልተሳተፉ በመግለጽ ችሎቱ የዋስትና መብት እንዲፈቀድላቸው ጠይቀዋል።

ፍርድ ቤት ምን አለ ?

የግራ ቀኝ ክርክር ካዳመጠ በኋላ ተጠርጣሪው ያቀረቡትን የዋስትና ጥያቄ በማለፍ፣ ለፖሊስ የ7 ቀናት የምርመራ ማጣሪያ ጊዜ ፈቅዷል።

ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የሪፖርተር ጋዜጣ ነው።

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" ... የት እንኳን እንዳለ አላውቅም። #መገደሉን በተመለከተም ገድዬዋለሁ ያለውን መጠየቅ ነው የሚሻለው " - አባ ገዳ ጎበና ሆላ

የቱልማ አባ ገዳ ጎበና ሆላ ኢሬሶ የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት (OLA) አባል የሆነ ልጃቸው መገደሉን ከማኅበራዊ ሚዲያ መስማታቸውን ተናገሩ።

ከ1 ሳምንት በፊት በኦሮሚያ ክልል ፣ የምዕራብ አርሲ ዞን ኮሚዩኒኬሽን የ ‘ ሸኔ ’ ቡድን አባል ነው የተባለውን የአባ ገዳ ጎበና ልጅ " ሰላማዊ ሰዎችን ለመግደል ሲንቀሳቀስ እርምጃ ተወስዶበታል " ብሎ ነበር።

ኮሚኒኬሽኑ " የኦሮሞ ልጆችን ሕይወት ሲቀጥፍ የነበረው የአባ ገዳ ጎበና ሆላ ልጅ (ፎሌ ጎበና) ላይ በምዕራብ አርሲ ዞን ገደብ አሳሳ ወረዳ ውስጥ የሰላማዊ ሰዎችን ሕይወት ለመቅጠፍ ሲንቀሳቀስ እርምጃ ተወስዶበታል  " ነው ብሎ የነበረው።

ይህንን ጉዳይ በተመለከተ አባ ገዳ ጎበና ሆላ ለቢቢሲ አፋን ኦሮሞ ቃላቸውን ሰጥተው ነበር።

አባ ገዳ ጎበና ሆላ ምን አሉ ?

- የልጃቸውን የመገደል ዜና የሰሙት በማህበራዊ ሚዲያ እንደሆነ እና እስካሁን ምንም ማረጋገጫ እንዳላገኙ ገልጸዋል።

- የልጃቸውን ሞት ባያረጋግጡም በእርግጥ ልጃቸው መንግሥት ኦነግ-ሸኔ ብሎ የሚጠራው የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ታጣቂ ቡድን አባል መሆኑን #አረጋግጠዋል።

- ልጃቸው ፎሌ ጎበና ዕድሜው ወደ 33 ዓመት እየተጠጋ መሆኑን እና ከልጃቸው ጋር ከተያዩ 6 ዓመታት ማለፉን ገልጸዋል።

- " ከ6 ዓመታት በኋላ ነው ለመጀመሪያ ጊዜ ከቀናት በፊት ፎቶ ግራፉን ማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ሲዘዋወር የተመለከትኩት " ብለዋል።

- " የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት (OLA) ውስጥ እንዳለ አውቃለሁ ፤ ነገር ግን ምንም ግንኙነት የለንም። የት እንዳለም አላውቅም። መገደሉን በተመለከተም ገድዬዋለሁ ያለውን መጠየቅ ነው የሚሻለው " ብለዋል።

- ልጃቸው ሰላማዊ ሰዎች እየዞረ እንደሚገድል በመንግሥት የቀረበበትን ክስ በተመለከተ ፥ ምንም የሚያውቁት ነገር እንደሌለ ገልጸዋል።

- " እኔ አባ ገዳ ነኝ አልዋሽም ፤ ከልጄ ጋር ምንም ዓይነት ግንኙነት የለኝም። ስልክ አንደዋወልም። ከ6 ዓመት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው ፎቶግራፉን እንኳ የተመለከትኩት " ብለዋል።

የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት አባል የሆነው እና የአባ ገዳው 7ኛ ልጃቸው የሆነው ፎሌ ጎበና ከቤት የወጣው የ26 ዓመት ወጣት ሳለ እንደነበረ አባቱ ገልጸዋል።

ከዚህ ጋር በተያያዘ አባ ገዳ ጎበና ልጃቸው ወደ ትጥቅ እንቅስቃሴ መግባቱን ተከትሎ ከዚህ ቀደም የመንግሥት ፀጥታ ኃይሎች በተደጋጋሚ መኖሪያ ቤታቸው ላይ ብርበራ ማድረጋቸውን ሲናገሩ ነበር።

ከጥቂት ወራት በፊት አባ ገዳ ጎበና ያለ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ ቤታቸው ላይ ብርበራ በተደረገበት ወቅት ከወላጅ አባታቸው የወረሱት የጦር መሳሪያ መወሰዱን እና ክስተቱን ተከትሎ በቤተሰብ አባላት ላይ ከፍተኛ መደናገጥ መፈጠሩን ተናግረው ነበር።

መረጃው የቢቢሲ አፋን ኦሮሞ ነው።

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#TikTok #USAHouse

የአሜሪካ የተወካዮች ምክር ቤት ተሰብስቦ ለዩክሬን ፣ ለእስራኤል እና ለሌሎች የባህር ማዶ የአሜሪካ አጋሮች የ95 ቢሊዮን ዶላር (5,419,427,000,000 ብር) የእርዳታ ጥቅል/ፓኬጅ ረቂቅ ሕግ አጽድቋል።

" ቲክቶክ " በአሜሪካ እንዲታገድም ድምጽ ሰጥቷል።

የተወካዮች ምክር ቤቱ በመጀመሪያ ድምፅ የሰጠው በ " #ቲክቶክ " ጉዳይ ሲሆን ባለቤትነቱ የባይትዳንስ የሆነው መተግበሪያ ለአሜሪካ ኩባንያ ካልተሸጠና ከቻይና ጋር ያለውን ግንኙነት ካላቋረጠ በመላው አሜሪካ ውጤታማ በሆነ መንገድ #ለማገድ 360 ለ 58 በሆነ ድምጽ ረቂቅ ሕግ #አጽድቋል።

" ቲክቶክ " በአሜሪካ ከ170 ሚሊዮን በላይ ተጠቃሚዎች አሉት።

በመቀጠል ምክር ቤቱ ፦

➡️ ለዩክሬን 60.8 ቢሊዮን ዶላር (3,422,796,000,000 ብር)፤

➡️ ለእስራኤል 26.4 ቢሊዮን ዶላር  (1,483,211,600,000 ብር)፤

➡️ ለታይዋን እና ለኢንዶ ፓስፊክ ሀገራት  ' ቻይናን ለሚጋፈጡ ' የ8 ቢሊዮን ዶላር (456,372,800,000 ብር) የእርዳታ ድጋፍ በድምሩ የ95 ቢሊዮን ዶላር ጥቅል እርዳታ ረቂቅ ሕግ አጽድቋል።

የምክር ቤቱ አባላት የዩክሬን ድጋፍ ሲጸድቅ ፤ " ዩክሬን !! " እያሉ በመጮህ የሀገሪቱን ባንዲራ ሲያውለበልቡ ታይተዋል።

@thiqahEth @tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" በትጥቅ ትግል ውስጥ ያሉ ወገኖቻችን አሁንም ሳይመሽ ቶሎ ወደ ድርድሩ እንዲገቡ በትህትና እንጠይቃለን " - ፕ/ር መስፍን አርአያ

የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን በሌላ መንገድ እየታገሉ ይገኛሉ ያላቸው አካላት ወደ ምክክር መድረኩ እንዲገቡ ጥሪ አቀረበ።

ኮሚሽኑ ከዚህ ቀደም ተደጋጋሚ ጥሪ ማቅረቡ ይታወሳል።

አሁንም " ወደ ምክክር መድረኩ ኑ " ያለው ኮሚሽኑ ፤ ለታጠቁ አካላት ተገቢውን የጥበቃ ዋስትና በኮሚሽኑ እንደሚያመቻች ገልጿል።

ይህ የተሰማው በምክክር ጉባዔው የሚሳተፉ የኦሮሚያ ክልል ማህበረሰብ ተወካዮች የማጠቃለያ ልየታ መድረክ በሻሸመኔ ከተማ በተካሄደበት ወቅት ነው።

" በትጥቅ ትግል ያሉ ወገኖቻችን አሁንም ሳይመሽ ቶሎ ወደ #ድርድሩ እንዲገቡ በትህትና እንጠይቃለን " ያሉት ዋና ኮሚሽነር ፕ/ር መስፍን አርአያ " የሚያዋጣን ይሄ ነው ፤ በየታች ድረስ ሄደን ያገኘነው ህዝባችን ሰላምን እንደሚፈልግ ነው የገለጸለን  " ብለዋል።

ምክትል ዋና ኮሚሽነር ዶክተር ሒሩት ገብረስላሴ በበኩላቸው ፥ እንዲህ አይነት ምክክር ትልቅ ታሪካዊ አጋጣሚ መሆኑን ጠቅሰዋል።

" ይህን አጋጣሚ በአገሪቱ የሚገኙ ሁሉም የማህበረሰብ ክፍሎች ሊጠቀሙበት ይገባል " ብለዋል።

" በተለይ በትጥቅ ትግል ውስጥ ያሉ አካላት ወደ መድረኩ ሊመጡና ሀሳባቸውን ሊገልጹ ይገባል ፤ እነሱ መጥተው በሚሳተፉበት ጊዜ ኮሚሽኑ ተገቢውን #የዋስትና_ጥበቃ /safe space/ የሚያመቻች ይሆናል " ሲሉ ተናግረዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን ከዶቼቨለ ሬድዮ ማግኘቱን ይገልጻል።

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#Ethiopia

ኢትዮጵያ ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) ብድር ለማግኘት ድርድር ላይ ናት።

እንደ ሮይተርስ ዘገባ ከ2020 ጀምሮ ምንም ፈንድ ያላገኘችው ኢትዮጵያ ብድር እንዲለቀቅላት ከIMF ተከታታይ ድርድሮች እያካሄደች ነው።

ከIMF 3.5 ቢሊዮን ዶላር ብድር እንደጠየቀች ተነግሯል።

ድርጅቱ ብደሩን ለመስጠት ኢትዮጵያ ብር ከዶላር አንጻር ያለው የመግዛት አቅም #እንዲዳከም ማድረግ እንዳለባት እንደጠየቀ ተጠቁሟል።

ግን ይህ እንደቅድመ ሁኔታ ይቀመጥ አይቀመጥ ድርጅቱ ማረጋገጫ አልሰጠም። ነገር ግን ተለዋዋጭ የሆነ የገበያ ሁኔታ የሚወስን የውጭ ምንዛሬ ተመን መኖር  እንዳለበት እንደሚያምን ሮይተርስ አስነብቧል።

ምንም እንኳን እየተካሄዱ ባሉ ተከታታይ ድርድሮች በኢትዮጵያ እና IMF መካከል ልዩነቶች ቢኖሩም ስምምነት ላይ የመድረስ #ተስፋ_እንዳለ የIMF የኢትዮጵያ ልዑክ አልቫሮ ፒርስ ተናግረዋል።

ፒስርስ ፥ " አሁንም ልዩነቶች ቢኖሩም ድርድር ግን ቀጥሏል። አስቸጋሪ ነግሮች ቢኖሩም ስምምነት ላይ የመድረሱ ተስፋ አለ " ብለዋል።

የኢትዮጵያን #የኢኮኖሚ_ሪፎርም_መደገፍ ላይ በአብዛኛው ስምምነት እንዳለ ነው የተሰማው።

ከዶላር አንጻር የብርን የመግዛት አቅም ማዳከም ከፍተኛ በሆነ የዋጋ ንረት እየተፈተነች ላለችው ኢትዮጵያ ይበልጥ ፈተና ሊሆንባት ይችላል።

ግን ደግሞ IMF የግዴታ ያ ካልተደረገ ብድር አለቀም ካለ ኢትዮጵያ በከፍተኛ ውጭ ምንዛሬ እጥረት ውስጥ የምትገኝ በመሆኑ ሌላ አማራጭ ላይኖራት ይችላል የሚሉ አሉ።

ከቀናት በፊት የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ ዶ/ር ኢዮብ ተካልኝ እና የብሄራዊ ባንክ ገዢው ማሞ ምህረቱ በተገኙበት ከIMF ኃላፊ ክሪስታሊያ ጆርጂያ ጋር ተገናኝተው መክረው ነበር።

ምክክሩ IMF በኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን ሪፎርም በሚደግፍበት መንገድ ላይ ያተኮረ እንደሆነ ተጠቅሷል። ዝርዝር ጉዳዩ ግን አይታወቅም።

መረጃው የሮይተርስ ነው።

@tikvahethiopia

Читать полностью…
Subscribe to a channel