tikvahethiopia | Unsorted

Telegram-канал tikvahethiopia - TIKVAH-ETHIOPIA

1527734

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው። @tikvahuniversity @tikvahethAfaanOromoo @tikvahethmagazine @tikvahethsport @tikvahethiopiatigrigna #ኢትዮጵያ

Subscribe to a channel

TIKVAH-ETHIOPIA

" በካቢኔ ደረጃ ውይይት የተደረገበት እና ውሳኔ የተሰጠው ቢሆንም ለእኛ በውሳኔው ዙሪያ ከጤና ቢሮ ደብዳቤ አልደረሰንም " - የጤና መድህን አገልግሎት

የማኅበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን አገልግሎትን ለማስፈጸም በወጣው አዋጅ 1273/2014 መሰረት ምዝገባ እና እድሳት የሚጀመርበት ቀን እንዲሁም የአባልነትም ሆነ የመዋጮ ክፍያ የሚተመነው በ ክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮች መሆኑ ይታወቃል።

ሁሉም ሰው ተመሳሳይ የሆነ የጤና መድህን ክፍያ ከሚከፍል ነጋዴው እንደ ትርፉ ሌላም ሰው እንደ ኑሮ ደረጃው እና አቅሙ እንዲያዋጣ የሚያስችል አሰራር ለመዘርጋት በጥናት ላይ መሆኑን የኢትዮጵያ የጤና መድህን አገልግሎት ከዚህ ቀደም ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ማሳወቁ ይታወሳል።

አገልግሎቱ በሰጠን ቃል " ይህ ዓይነቱ አሰራር ከሌሎች ሃገሮች የተገኘ ተሞክሮ ነው ይህንን ተግባራዊ ለሚያደርጉ አካላት ሥልጠና ተሰጥቷል፣ መመሪያዎች ተዘጋጅተው ለክልሎች በመሰራጨት ላይ ነቸው ተግባራዊ ይሆናል " ብለው ነበር።

ይህንንም ተግባራዊ ለማድረግ የአዲስ አበባ ጤና ቢሮ ለማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን አገልግሎት የሚሰበሰብ የአባልነት ክፍያ ባጠናው አዲስ ጥናት መሰረት በሁሉም ሴክተር መስሪያ ቤቶች ማስከፈል እንዲችል ሰርኩላር እንዲጻፍለት የአዲስ አበባ ፋይናንስ ቢሮን በደብዳቤ ጠይቋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የተመለከተው ደብዳቤ እና በፋይናንስ ቢሮ ለ ገቢዎች ቢሮ በ 07/11/17 ዓም የተጻፈው ደብዳቤ ማንኛውም በማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን መታቀፍ የሚችል ነዋሪ በአባልነት ተመዝግቦ የጤና አገልግሎት ማግኘት እንደሚገባው እንዲሁም ሁሉም የንግድ ማህበረሰብ አባል መሆን እንዳለበት አዋጁን በመጥቀስ ያብራራል።

ፋይናንስ ቢሮ የጻፈው ደብዳቤ ለማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን አገልግሎት ከአባላት የሚሰበሰበው ገንዘብ ፍትሃዊነት ላይ ችግር ያለበት መሆኑን የአዲስ አበባ ጤና ቢሮ ማሳወቁን ይገልጻል።

ይህንን የፍትሃዊነት ችግር ለመቅረፍም ፋይናስ ቢሮ " ከአባላት የሚሰበሰበው ገንዘብ የፍትሃዊነት ችግር ያለበት በመሆኑ በተጠናው ጥናት መሰረት ለማስከፈል የአዋጁን አስገዳጅነት በመረዳት የሚመለከታቸው ሴክተር መ/ቤቶች ለማህበረሰብ ጤና መድን የሚውል ገንዘብ መሰብሰብ እንዲቻል በቢሮአቹ በኩል ሰርኩላር እንዲተላለፍ " በሚል ከጤና ቢሮ ሐምሌ 4 ቀን 2017 ዓ.ም በተጻፈ ደብዳቤ መጠየቁን ገልጿል።

የጤና ቢሮን ጥያቄ የተቀበለው ፋይናንስ ቢሮም የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አገልግሎት የሚሰበሰበው ክፍያ በአዲሱ ጥናት መሰረት እንዲሆን እና በሁሉም ሴክተር መስሪያ ቤቶች መሰብሰብ እንዲቻል በ 07/11/17 ለአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ በደብዳቤ ጠይቋል።

ቢሮው በደብዳቤው " ሁሉም የማህበረሰብ ክፍል የሚመለከተው ስለሆነ በቢሮአቹ በኩል የክሊራንስ ጥያቄ ሲቀርብ በአዋጁ መሰረት ጤና ቢሮ ባጠናው የዋጋ አከፋፈል ጥናት መሰረት መጀመሪያ ክፍያውን ፈጽመው ለመክፈላቸው መረጃ እንዲሆን የከፈሉበትን መረጃ ፎቶ ኮፒ እንዲያቀርቡላችሁ እንድታደርጉ የተለመደውን ትብብር እንድታደርጉ እንጠይቃለን " ብሏል።

በአፈጻጸሙ መሰረትም የክሊራንስ ጥያቄ የሚያቀርብ የንግዱ ማህበረሰብ አባል የክሊራንስ ደብዳቤ ከማግኘቱ በፊት ለማህበረሰብ አቀፍ  የጤና መድህን አገልግሎት በአዲሱ ተመን መሰረት ክፍያ የፈጸመብትን መረጃ ፎቶ ኮፒ እንዲያቀርብ የሚገደድ ይሆናል።

ገቢዎች ቢሮ ጥያቄውን በመቀበል ለሁሉም የግብር ከፋይ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች አሰራሩ ተግባራዊ እንዲሆን በቢሮው ሃላፊ አቶ ቢኒያም ምክሩ በተፈረመ ደብዳቤ አሳውቋል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባስቀመጠዉ አቅጣጫ መሰረት የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን ደንብ ቁጥር 86/2009 አንቀጽ 6 ንዑስ አንቀፅ 7 በንግድ የሚተዳደሩ ነጋዴዎች ዓመታዊ ገቢያቸዉን መነሻ በማድረግ የሚያዋጡት አመታዊ መዋጮ የሀ፣ ለ፣ ሐ ግብር ክፋዮች ደረጃ ተክትሎ እንደገቢያቸው መጠን የሚከፍሉበት ሁኔታ ተጠንቶ ተግባራዊ ሊደረግ እንደሚችል ያስቀምጣል፡፡

ተጠንቶ ተግባራዊ በሆነው ጥናት መሰረትም :-

- የደረጃ "ሀ" ግብር ከፋይ የመዋጮ መጠን 10,500 (አስር ሺ አምስት መቶ ብር)

- የደረጃ "ለ" ግብር ከፋይ የመዋጮ መጠን 6,900 (ስድስት ሺ ዘጠኝ መቶ ብር)

- የደረጃ "ሐ" ግብር ከፋይ የመዋጮ መጠን 2000 (ሁለት ሺ ብር ) እንዲሆን ተወስኗል።

በዚህም መሰረት አመታዊ ግብሩን የፈጸመ የንግዱ ማህበረሰብ አባል የክሊራንስ ጥያቄ ለገቢዎች ቢሮ በሚያቀርብበት ወቅት እንደ ግብር ደረጃ ምድቡ በክፍለ ከተማው የማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን አገልግሎት አካውንት ክፍያ የፈጸመበትን መረጃ ማቅረብ ይጠበቅበታል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከአዲስ አበባ ጤና መድህን አገልግሎት ስለጉዳዩ ጠይቆ "በካቢኔ ደረጃ ውይይት የተደረገበት እና ውሳኔ የተሰጠው ቢሆንም ለእኛ በውሳኔው ዙሪያ ከጤና ቢሮ ደብዳቤ አልደረሰንም" የሚል ምላሽ አግኝቷል።

ከአዲስ አበባ ጤና ቢሮ የቢሮውን ሃላፊ ዶ/ር ዮሃንስ ጫላን በጉዳዩ ላይ ምላሻቸውን ለማካተት ተደጋጋሚ ሙከራ ብናደርግም ስልካቸውን ለማንሳት ፈቃደኛ አልሆኑም።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamliyAA

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

🙏ስለአብሮነትዎ ምስጋና!!

🎊 የ2017 በጀት ዓመት እና የሶስት ዓመት መሪ የዕድገት ስትራቴጂያችንን በስኬት ማጠናቀቃችንን በማስመልከት ካበረከትንልዎ የ1 ጊ.ባ ዳታ፣ የ15 ደቂቃ የሀገር ውስጥ ጥሪ እና የ25 የጽሑፍ መልዕክት ስጦታዎች በተጨማሪ የቴሌብር ሱፐርአፕ ተጠቃሚ በመሆንዎ ተጨማሪ የ1 ጊባ ዳታ ስጦታ አበርክተናል!

🎁 ስጦታውን እስከ ሐምሌ 20/2017 ዓ.ም ድረስ ከሌሊት 6:00 እስከ ምሽት 12:00 ሰዓት መጠቀም ይችላሉ።

ስለአብሮነታችሁ ከልብ እናመሰግናለን!

#Ethiotelecom #telebirr #DigitalEthiopia #DigitalAfrica #RealizingDigitalEthiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

የትምህርት ቤት ክፍያዎን በቀላሉ በፀሐይ ባንክ በኩል ይክፈሉ!

እጅግ ዘመናዊ የሆነው የፀሐይ ኢ-ስኩል ሲስተም በሚሰጣቸው ዘርፈ ብዙ ጥቅሞች ተጠቃሚ ይሁኑ!

ወቅቱ ትምህርት ቤቶች የተማሪዎች ምዝገባ የሚያደርጉበት ነው፡፡ ፀሐይ ባንክ የትምህርት ቤቶችን ምዝገባ እና ሌሎች ሥራዎችን የሚያቀላጥፍ ምርጥ መላ ይዞ መጥቷል፡፡

አሁኑኑ አቅራቢያዎ ወደሚገኝ የፀሐይ ባንክ ቅርንጫፍ በመሔድ የፀሐይ ኢ-ስኩል ሲስተም ተጠቃሚ ይሁኑ!

ሥራዎትን ያቀላጥፉ! ከባንካችን ጋር በመስራት የሚያገኙትን ጥቅም ያሳድጉ!

ፀሐይ ባንክ
ለሁሉ!


የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቁሉ 👇 /channel/tsehaybanksc

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#እንድታውቁት

ሐምሌ18 እና ሐምሌ 19 ቀን 2017 ዓ.ም ከጨለንቆ እስከ ቀርሳ ከተማ ባሉት ከተሞች ዋና መንገድ ላይ ከባድ ተሽከርካሪ ማለፍ ክልክል መሆኑ ተገልጿል።

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#Oromia

በተደጋጋሚ የትራፊክ አደጋ በሚደርስበትና የሰው ህይወት በሚቀጠፍበት " ሰብስቤ ዋሻ " አካባቢ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ10 ወገኖቻችን ህይወት አለፈ።

ዛሬ በባሌ ዞን አዳባ ወረዳ " ዶልፊን " የህዝብ ማመላለሻ መኪና ተሳፋሪዎችን ጭኖ ከዲንሾ ወደ አዳባ በመጓዝ ላይ እያለ " ሰብስቤ ዋሻ " አከባቢ ተገልብጦ የ10 ሰው ህይወት አልፏል። 6 ሰዎችም ክፉኛ ተጎድተዋል።

የወረዳው የትራፊክ ደኅንነት ጽ/ቤት " የአደጋው መንስኤ የመኪናው መሪ በማስቸገሩ ነው " ብለዋል። #OBN

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#Update

" ቀሪዎቹ 2 አስክሬኖች ተገኝተዉ የ5ቱም ስርዐተ ቀብር ተፈፅሟል " - የደቡብ አሪ ዞን አስተዳዳሪ

በአሪ ዞን ደቡብ አሪ ወረዳ ኮመር ቀበሌ ሀምሌ 13/2017 ዓ/ም በተከሰተ የመሬት መንሸራተት አደጋ ሕይወታቸውን ያጡ 5 የአንድ ቤተሰብ አባላት አስክሬን ፍለጋ በማሽንና በሰዉ ሃይል ሲካሄድ ቆይቶ የ3 ሰዎችን አስክሬን ትላንት የተገኘ ሲሆን የቀሪዎቹ 2 ሰዎችም አስክሬን ዛሬ ተገኝቶ የቀብር ስነ ስርዓት እንደተፈፀመላቸዉ የወረዳዉ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ግዛዉ ሃይሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

በመሬት ናዳዉና በከፍተኛ ስጋት ዉስጥ ናቸዉ ተብለዉ ከተለዩ አከባቢዎች ከ1,019 የሚሆኑ ነዋሪዎች ተፈናቅለዉ በድንኳንና በሃይማኖት ተቋማት ተጠልለው ይገኛሉ ያሉት አስተዳዳሪዉ " ቀጣይ ትኩረታችን የተጎዱትን ማገዝና ተፈናቃዮችን መልሶ የማቋቋም ስራ ይሆናል " ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamliyHawassa

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#DStvEthiopia

4 ቡድን ፣ 6 ፍልሚያዎች!

ማንቼስተር ዩናይትድ ፣ ኤቨርተን ፣ ቦርንማውዝ እና ዌስትሃም የሚሳተፉበት የፕሪምየር ሊግ ሰመር ሲሪስ!

🗓 ከሐምሌ 19 - ሐምሌ 27

⚽️ የዲኤስቲቪ ደንበኞች በነፃ DStv Streamን በመጠቀም ጨዋታዎን የትም ይሁን የት ሆናችሁ በስልክዎ ይከታተሉ!

ዛሬውኑ ዲኤስቲቪ ያስገቡ ፣ ደንበኝነትዎን ያራዝሙ!
⬇️
https://mydstv.onelink.me/vGln/xepsjmo7

ደንብና ሁኔታዎች ተፈፃሚነት አላቸው!

#እናያለንገና👀 #ሁሉምያለውእኛጋርነው

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#Update

" አቶ ሃፍቱ ኪሮስ ከዞኑ ተነስተው የክልሉ ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ሀላፊ ሆነው ተሹመዋል " - የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር 

➡️ " ጥያቄያችን ለግለሰቦች ስልጣን ስለመስጠትና መንሳት አይደለም። ጥያቄያችን ስለ ህዝብ ተጠቃሚነትና ተሳትፎ ነው ። ስለሆነም የተሰጠኝ ኃላፊነት አልቀበለውም "  - የትግራይ ደቡባዊ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ሃፍቱ ኪሮስ

ሀምሌ 15/2017 ዓ.ም በጊዚያዊ አስተዳደሩ ትእዛዝ በፀጥታ ኃይል በመታገዝ ከኃላፊነታቸው ከተነሱት አመራሮች አንዱ የሆኑት ሃፍቱ ኪሮስ በማህበራዊ የትስስር ገፅ በተሰራጨው ደብዳቤ ከዞን አስተዳዳሪነት ተነስተው ወደ ክልል ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊነት መሾማቸው ያትታል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ በፕሬዚዳንት ታደሰ ወረደ (ሌ/ጀነራል) ተፅፎ በማህበራዊ የትስስር ገፆች ሲዘዋወር የተስተዋለው ደብዳቤ ትክክለኝነት አረጋግጧል።

አቶ ሃፍቱ የተሰጣቸው ተለዋጭ የስልጣን ቦታ በማስመልከት በሰጡት መልስ ኃላፊነቱን እንደማይቀበሉት ገልፀዋል።

አቶ ሃፍቱ ኪሮስ " ጥያቄያችን ለግለሰቦች ስልጣን ስለመስጠትና መንሳት አይደለም። ጥያቄያችን ስለ ህዝብ ተጠቃሚነትና ተሳትፎ ነው። ለኔ ስልጣን የከፍታና የዝቅታ መግለጫ ሳይሆን መንግስታዊ ኃላፊነት በተገቢዉ ከመውጣትና ከህዝብ አገልጋይነት አንፃር ነው የመምዝነው " ብለዋል።

" ስለሆነም ክቡር ፕሬዜዳንት መንግስታዊ መዋቅር የማስተካከል ስልጣን እንዳላቸው በመርህ ደረጃ ባምንም ተገቢ መግባባት ያልተደረገበት፣ አንገብጋቢና የሚያመርቅዝ የህዝብ ጥያቄ ባልተመለሰበት የሚሰጥን ኃላፊነት ከምስጋና ጋር አልቀበለውም " ሲሉ የተሰጣቸውን ሹመት ውድቅ አድርገዋል።

አቶ ሃፍቱ ለሰላም ሲሉ ከፅህፈት ቤታቸው መውጣታቸው ገልፀው " እኔን የወከለ አስተዳዳሪ የለም ፤ ህጋዊ የዞኑ አስተዳዳሪ እኔ ነኝ ፤ አላስፈላጊ ግጭትና ደም መፋሰስ ለማስቀረት በማሰብ ፅህፈት ቤቴን ለቅቄ ወጥቻለሁ " ማለታቸው ይታወሳል።

አንዳንድ መረጃዎች እንደሚያመላክቱት በዞኑ የተካሄደው በፓሊስ የተደገፈ የስልጣን ሹምሽር በመቃወም በማይጨው ከተማ ለሀምሌ 18 ሰላማዊ ሰልፍ ለማካሄድ ቀጠሮ ተይዟል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamliyMekelle

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

በታጣቂዎች አራት ሰዎች ተገደሉ።

በኦሮምያ ክልል ምስራቅ ቦረና ዳስ ወረዳ ራሮ ቀበሌ ውስጥ " ወሰን ተሻግረው የመጡ ናቸው " በተባሉ ታጣቂዎች አራት ሰዎች መገደላቸው የሟች ቤተሰቦች እና የራሮ ቀበሌ አስተዳደር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

አርብ ዕለት ሀምሌ 11 ቀን 2017 ዓ.ም ረፋድ 4:00 አካባቢ ከሱማሌ ክልል ቱማ ቀብሌ የመጡ ታጣቂዎች ናቸው ባሏቸው ከብቶችን በመጠበቅ ላይ የነበሩ ሰዎችን ገድለው ከብቶችን እና ግመሎችን ነድተው መሄዳቸውን የተጎጅ ቤተሰቦች ገልፀዋል።

አቶ ጌዶ ዋርዮ የዳስ ወረዳ ራሮ ቀቤለ ነዋሪ ናቸው። ከተገደሉት ውስጥ አንዷ የዘጠኝ አመት ሴት ልጃቸው እንደሆነች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

" ዳስ ወረዳ ራሮ ቀበሌ ከሱማሌ ክልል ቱማ ቀበሌ ጋር ይዋሰናሉ እናም የታጠቁ ሀይሎች በተደጋጋሚ ወሰን ተሻግረው መጥተው በአርብቶ አደሮች ላይ ጥቃቶችን ሰንዝረው ይሄዳሉ " ሲሉም አክለዋል።

ሌላው የራሮ ቀበሌ ነዋሪ መሆናቸውን የገለፁት እና ስማቸውን እንዳንጠቅስ የጠየቁን አንድ እናት የአምስት ልጆች አባት የሆኑት ባለቤታችው ሰሞኑን ከተገደሉት ሰዎች መካከል አንዱ እንደሆኑ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

በዳስ ወረዳ የራሮ ቀበሌ አስተዳደር አቶ አብዱባ ዶዮ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በስልክ እንደገለፁት ጥቃቱ ከሱማሌ ክልል ታጥቀው ወሰን ተሻግረው በመጡ ስዎች መፈፀሙን ገልጸዋን።

አስተዳዳሪው " ታጣቂዎቹ ጥቃትን ከፈፀሙ በኋላ ቁጥራቸው በውል ያልታወቁ የአርብቶ አደሮችን ከብት፤ ፍየል እና ገመሎቹን ዘርፈው ሄደዋል " ብለዋል።

ጥቃቱን ተከትሎ በርካታ ቁጥር ያለው የአካባቢው ነዋሪዎች ተፈናቅለው ወደ አጎራባች ቀበሌዎች የተሰደዱ ሲሆን ለዳስ ወረዳ አስተዳደር በደረሰው መረጃ መሰረት በአካባቢ ያሉ የሀገር መከላከያ ሰራዊት አባላት ተጠርተው አዋሳኝ ስፍራ ሰፍረዋል ብለዋል።

" በአዋሳኝ ቦታዎች ላይ ያለው ግድያና ዝርፊያ እንዲሁም ግዛትን ማስፋፋት መሰረት ያደረጉ ጥቃቶች አመታትን አስቆጥሯል " ያሉት ዋና አስተዳዳሪው " የፈዴራል ፤የኦሮምያ እና ሱማሌ ክልል መንግስታት መፍትሄ ሊሰጧቸው ይገባል " ሲሉ ሀሳብ አውርበዋል።

ተጨማር ማብራርያ ለማግኝነት ከዳስ ወረዳ እና ከምስራቅ ቦረና አመራሮች ያደረግነው ሙከራ አልተሳካም።

የተጎጅ ቤተሰቦች እና የአካባቢው አስተዳዳሪ ለጥቃቱ የከሰሱት ከሱማሌ ክልል የመጡ ናቸው የተባሉ ታጣቂዎችን በተመለከተ ከክልሉ አመራሮች ምላሽ ለማግኘት ያደረግነው ጥረት ለጊዜው አልተሳካም።

ምላሽ ካገኘን የምንመለስበት ይሆናል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ነቀምቴ
#TikvahEthiopiaFamilyNekemte

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

በ4% ጉርሻ ከወጋገን ባንክ ይመንዝሩ! ይቀበሉ!

ከወጋገን ባንክ ጋር ከሚሰሩ የሃዋላ ድርጅቶች በኩል የባንኩን ስዊፍት አድራሻ WEGAETAA ጨምሮ የሚላክልዎትን ገንዘብ እስከ መስከረም 20 ቀን 2018 ዓ.ም ከባንካችን ሲቀበሉ እና የውጭ ሀገር ገንዘብ ሲመነዝሩ ከዕለቱ የምንዛሬ ዋጋ ላይ የ4 በመቶ ጉርሻ በማከል ገንዘብዎን በፍጥነት እናስረክብዎታለን፡፡

💰 ይፍጠኑ የጉርሻው ተቋዳሽ ይሁኑ!

☎️ ለበለጠ መረጃ ወደ ወጋገን ባንክ የደንበኞች ግንኙነት ማዕከል በ866 ነፃ የስልክ መስመር ይደውሉ!

ከስር የተቀመጠውን ማስፈንጠሪያ (ሊንክ) በመጫን የማህበራዊ ገፆቻችንን ይቀላቀሉ!

𝖩𝗈𝗂𝗇 ➥ Telegram 📲 Facebook

🌍 https://linktr.ee/WegagenBank
📩 info@wegagen.com

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#Hawassa
#ማሳሰቢያ

‌‎የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ጥብቅ ማሳሰቢያ አስተላለፈ።

‎ዓመታዊው የቅዱስ ገብርኤል የንግስ በዓል ቅዳሜ ይከበራል።

በዓሉን አስታኮ ግን አንዳንድ አገልግሎት ሰጪዎች ከፍ ያለ የዋጋ ጭማሪ እያደረጉ እንደሆነ በግልጽ ታይተዋል።

የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ንግድና ገበያ ልማት መምሪያም  " ጥቂት አገልግሎት ሰጪ ተቋማት በዓሉን አስታከው በአንዳንድ አገልግሎቶችና በማረፊያ ቦታዎች ላይ ከወትሮው ውጭ የዋጋ ጭማሬ የሚመስሉ አዝማሚያዎችን እያደረጉ ስለመገኘታቸው ጥቆማዎች ቀርበውልኛል " ብሏል።

" የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር በእነዚህ አብዛኛው አገልግሎት ሰጪ ተቋማትን በማይወክሉ ላይ እርምጃ ከመውሰዱ በፊት ቀደም ብለው እንዲታረሙ በጥብቅ ያሳስባል " ሲል ገልጿል።

" ‎ይህ አይነቱ ድርጊት በተለይም ሁላችንም የአይን ብሌን አድርገን የምናያትን ከተማችን የሀዋሳን ስም የሚያጠለሽ ሆኖ እንዳይገኝ ከወዲሁ በመሰል ድርጊት ላይ የተሰማሩ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ከድርጊታቸው እንዲታቀቡ ማስገንዘብ እንወዳለን " ሲል መምሪያው አሳስቧል።

" ‎በጥቆማው መሰረት በተጨባጭ መልኩ በዓሉን አስታከው ያልተገባ የዋጋ ጭማሬ በማንኛውም አገልግሎት ላይ በሚያደርጉ አካላት ላይ አስተዳደሩ የማያዳግም እርምጃ ይወስዳል " ብሏል።

#TikvahEthiopiaFamliyHawassa

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

ስግብግብነትም ልክ አለው !

" የአንድ አልጋ ዋጋ 800 ብር ከነበረበት 2500 እና 3000 ብር ብለው አስደነገጡኝ ! "


(ጋዜጠኛ ቴዎድሮስ ታከለ)

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታዮች ዘንድ አመታዊው የቅዱስ ገብርኤል በዓለ ንግስ ከሚከበርባቸው ከተሞች መካከል የፍቅር ከተማዋ ሀዋሳ አንዷ ናት።

በርካቶች ከተለያዩ የአለም እና የሀገሪቱ አካባቢዎች ለዚህ መንፈሳዊ በዓል ወደ ከተማዋ በመምጣት በደመቀ መልኩ ያከብራሉ።

የእንግዶቹን መምጣት ተከትሎም የእንግዳ ማረፊያዎች ፣ ሆቴሎች እና ምግብ ቤቶች አለፍ ሲልም ከሊስትሮ እስከ ቡና መሸጫ ቦታዎች እንዲሁም ሌሎች በንግድ የሚተዳደሩ የከተማይቱ ግለሰቦች በዚህ በአል ተጠቃሚ በመሆን ገቢ ያገኛሉ።

ነገር ግን አንዳንድ ስግብግቦች በእጅጉ እንግዶችን የሚያሳቅቁ የዋጋ ጭማሪዎችን በማድረግ ከተማው ላይ ሰዎች ቆይታቸውን እንዳያራዝሙ በአጭሩም  እንዲያጥር እያደረጉ ናቸው።

ትዝብቴ እዚህ ጋር ነው አንድ የቅርብ ወዳጄ ወደ ከተማይቱ ለመምጣት የአልጋ አገልግሎትን ፈልጎ እንዳመቻችለት ስለነገረኝ ወደ አንድ የእንግዳ ማረፊያ ሆቴል / በቅርበት ወደማውቀው ቦታ ሄድኩኝ።

ወደ ቦታው የሄድኩት የአልጋ ዋጋ በቅርብ እንኳን ስምንት መቶ ብር እንደሆነ ስለማውቅ ነው።

የአልጋ ዋጋ በዚሁ በዓል ምክንያት ብቻ ከእጥፍ በላይ በመጨመር ሁለት ሺህ አምስት መቶ እና ሦስት ሺህ ብር ነው ብለው በእጅጉ አስደንግጠውኛል።

ስለሆነም የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ከተማዋ ከፍተኛ ገቢ ከምታገኝበት በዓል መካከል አንዱ የሆነውን የቅዱስ ገብርኤል ክብረ በአልን አክብረው ከተማዋን ጎብኝተው እንግዶች ቀናቸውን አራዝመው ይቆዩ ዘንድ እንዲህ አይነት ራስ ወዳድ የሆኑ ስግብግብ የአልጋ ፣ የሆቴል ፣ የምግብ እና መሰል ነጋዴዎች ላይ በአፋጣኝ ክትትል በማድረግ እልባት ሊሰጠው ይገባል ስል በትዕትና እጠይቃለሁ። "

#TikvahEthiopiaFamliyHawassa

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" ነጻ፤ ፍትሃዊ እና ዲሞክራሲያዊ ምርጫ ያለ ሰላምና መረጋጋት ውጪ ሊታሰቡ አይችልም " - የፓለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት

የኢትዮጵያ ፓለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ከሰላም ሚኒስቴር ጋር በመተባበር " ሰላምን በማጽናት የፓለቲካ ፓርቲዎች ሚና " በሚል ጉዳይ ክልላዊና ሀገር አቀፍ ፓርቲዎች ጋር ለሁለት ቀናት የሚቆይ የውይይት መድረክ ዛሬ ማካሄድ ጀምሯል።

በዚህ መድረክ መክፈቻ ላይ ንግግር ያደረጉት የጋራ ምክር ቤቱ ሰብሳቢ አቶ ሰለሞን አየለ ምክር ቤቱ በ2017 ዓ/ም አገር አቀፍ የሰላም ኮንፈረንስ ለማካሄድ እቅድ እንደነበረውና የዛሬው መድረክም ከባለድርሻ አካላት ጋር ይህንኑ እውን ያደደረገበት ነው ብለዋል።

" የሰላም ኮንፈረንሱ ዓላማ በሀገራችን የተለያዩ አካባቢዎች በተለይም በአማራና በኦሮሚያ ክልሎች ያሉ ግጭቶች እንዲቆሙ ለማስቻል " ሲሉ ነው የገለጹት።

ሰብሳቢው በንግግራቸው መድረኩ ፦

-  በመንግስትና በተፋላሚ ወገኖች መካከል ያለ የፓለቲካ ልዩነትን በዘላቂነት ለመፍታት ውይይት እንዲጀመር ጥሪ ለማስተላለፍ፤

- በቀጣይ ይካሄዳል ተብሎ ለሚጠበቀው ለ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ነጻ፣ ፍትሃዊና ሰላማዊ እንዲሆን አስዋጽኦ ለማበርከት ታሳቢ ያደረገ ነው ብለዋል።

" ነጻ፤ ፍትሃዊ እና ዲሞክራሲያዊ ምርጫ ያለ ከሰላምና መረጋጋት ውጪ ሊታሰቡ አይችልም " ያሉት አቶ ሰለሞን፣ ሀገረ መንግስትን ለመገንባት ሰላም ትልቅ ድርሻ እንዳለው በንግግራቸው አንስተዋል።

" ሀገራችን ባለፉት 6 ዓመታትም ከግጭትና ከጦርነት አልተላቀቀችም " ያሉት አቶ ሰለሞን፣ " በኦሮሚያና በአማራ ክልሎች ዛሬም ድረስ የቀጠለው ግጭት የአያሌ ኢትዮጵያዊያንን ሕይወት ቀጥፏል" ሲሉ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፓለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ ሰለሞን አየለ አክለውም " ኢትዮጵያ ከድህነት አዙሪት እንድትላቀቅ ቅድሚያ ሰላምን ማስፈን ይገባል” ብለዋል።

በመድረኩ የተገኙት የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ምን አሉ ?

" ሰው ሰራሽና የተፈጠሮ አደጋዎች ሰላማችንን ሲነሱን ኖረዋል፤ ድርቅ ወረርሽኝ፣ የመሬት መንቀጥቀጥ፣ ጎርፍ፣ ቸነፈር ህዝባችንን ሲያሰቃዩ ኖረዋል።

እነዚህ ጋብ ሲሉ ደግሞ፣ ግጭት ጦርነትና መፈናቀል መልሰው ሰላማዊ ህይወታችን ይበጠብጡታል፤ እስካሁን ድረስ ለሁለቱም የሚሆነውን ሁነኛ መፍትሄ አላበጀንም።

በዚህ የተነሳ ሁለቱም ተባብረው ለድህነትና ለኋላቀርነት አሳልፈው ሰጥተውናል "
ብለዋል።

በወቅቱ ንግግር ያደረጉት የሰላም ሚኒስትር አቶ መሐመድ እንድሪስ፣ በቅርብ ጊዚያት ችግሮችን ለመፍታት በተሰራ ሥራ፣ " በአብዛኛው በሀገራችን ክፍሎች አንፃራዊ ሰላም ማረጋገጥ ተችሏል " ሲሉ ተደምጠዋል።

የመድረኩ የከሰዓት ውሎ ለሚዲያ ዝግ ሆኖ መካሄዱን በስፍራው የተገኘው የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል መመልከት ችሏል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" የጊዚያዊ አስተዳደሩ ፕሬዜዳንት ታደሰ ወረደ (ሌ/ጀነራል) እና የፋይናነስና ሃብት ማስተባበርያ ሃላፊ ምሕረት በየነ (ዶ/ር) እስረኛ ሆነው ፍርድ ቤት እንዲቀርቡልን እና የፍርድ ቤት ውሳኔ እንዲያስፈፅሙ ትእዛዝ ይፃፍልን " - የትግራይ መምህራን ማህበር ጠበቃ

➡️ " የእስር ትእዛዝ ይፃፍልን ጥያቄው ተቀባይነት የለውም " - የትግራይ ክልል ከፍተኛ ፍርድ ቤት

ከፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ማግስት በ2015 ዓ.ም የተጀመረው የ " 17 ወራት የመምህራን ውዙፍ ደመወዝ ይከፈለን " ጥያቄ ወደ ፍርድ ቤት ከተመራ ወራት ተቆጥረዋል።

ክርክሩ በመዳኘት ላይ የሚገኘው የትግራይ ክልል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሀምሌ 15/2017 ዓ.ም ባዋለው ችሎት የመምህራን ክስ የያዘው የህግ ጠበቃ ባቀረበው ጥያቄ መሰረት በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ  የሂሳብ ቁጥር የሚገኘው የፌደራል የገንዘብ ሚንስቴርና የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ ገንዘብ እንዲታገድ ወስኗል።

የፍርድ ቤት የእግድ ትእዛዝ የተጣለበት ብር ግማሽ ቢሊየን እና 17 ሚሊዮን ሲሆን ግማሽ ቢሊዮኑ የክልሉ ፋይናንስና ሃብት ማሰባሰብ ቢሮ ቀሪው 17 ሚሊዮን ብር ደግሞ የፌደራል የገንዘብ ሚንስቴር እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል።

አቃቤ ህግ የገንዘቡ እግድ በማስመልከት ባቀረበው ክርክር በተጠቀሰው የባንክ ሂሳብ ቁጥር የሚገኘው ግማሽ ቢሊዮን ብር ቢሮው በሃላፊነት ያስቀመጠው የክልሉ መንግስታዊ መ/ቤቶች ያልተጠቀሙበት በአደራ የተቀመጠ ነው ብሏል።

" የይታገድ " ውሳኔ የተላለፈበት የፌደራል የገንዘብ ሚንስቴር 17 ሚሊዮን ብር አስመልክቶ የተባለ ነገር የለም።

የከሳሽ ጠበቃ የመምህራን የ17 ወራት ውዙፍ ደመወዝ እንዳይከፈል እያስተጓጎሉ ናቸው ያላቸው የጊዚያዊ አስተዳደሩ ፕሬዜዳንት ታደሰ ወረደ (ሌ/ጀነራል) እና የፋይናነስና ሃብት ማስተባበርያ ሃላፊ ምሕረት በየነ (ዶ/ር) በእስር  ወደ ፍርድ ቤት ሸርበው እንዲሰረዱ ትእዛዝ ይፃፍልኝ ሲል ያመለከተ ሲሆን ፍርድ ቤቱ ጥያቄውን ውድቅ አድርጎታል።

ፍርድ ቤቱ የቀረበው ክስ አፈፃፀም ለመመልከት ለሀምሌ 22/2017 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" የአውሮፕላን የውስጥ ክፍሎች የሚጠገኑበትን ባለ አራት ወለል ማእከል ብቻ ለመገንባት ከስልሳ ሚሊየን ዶላር በላይ ወጪ ተደርጓል " - የኢትዮጵያ አየር መንገድ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ በአይነቱ የመጀመሪያ ነው ያለውን የአውሮፕላን አካላት የጥገና ክፍል (Aircraft Component maintenance Shop) ፣ ሴንትራል ዌርሃውስ እና ሁለት ጋራዦችን (Hangars) ትላንት አስመርቋል።

በምረቃ ስነ ስርአቱ ላይ የአየር መንገዱ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰውን ፣ የአየር መንገዱ የቦርድ ሰብሳቢ ሌተናንት ጀነራል ይልማ መርዳሳ እና ሌሎችም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተው ነበር።

በአጠቃላይ ከ 150 ሚሊየን ዶላር በላይ እንደወጣባቸው የተገለጹት ሦስቱ ግንባታዎችን ለማጠናቀቅ በአማካይ ከ3 እስከ 5 አመት መፍጀቱን በአየር መንገዱ የሜንቴናንስ፣ ሪፔር እና ኦፈርሃውል ማኔጂንግ ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ዳንኤል ደመቀ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

የተመረቁት ሁለት የአውሮፕላን ጋራጆች አየር መንገዱ ከዚህ ቀደም ከነበሩት አራት የዋይድ ቦዲ እና የስሞል ቦዲ ጋራጆች በአጠቃላይ የስድስት ጋራጆችን ቁጥር ወደ ስምንት ከፍ ያደርገዋል።

የአውሮፕላን የውስጥ ክፍሎች የሚጠገኑበትን ባለ አራት ወለል ማእከል ብቻ ለመገንባት ከስልሳ ሚሊየን ዶላር በላይ ወጪ መደረጉን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከአየር መንገዱ ሰምቷል።

የአየር መንገዱ የአውሮፕላን ክፍሎች መለዋወጫ ጥገና ማዕከል በግንባታ ላይ በነበረበት ወቅት ለውስጥ ሰራተኞች በሃገር ውስጥ እና በውጭ ሥልጠና ሲሰጥ ቆይቷል ተብሏል።

በጥገና ማዕከሉ ከሚከናወኑ ተግባራት መካከል አንዱ በሆነው የአውሮፕላን የፊት እና የዋና የጎማ ክፍሎች የጥገና ማዕከል ውስጥ በአሁኑ ሰአት Bombardier Q400 እና Boing 737 ለተሰኙ አውሮፕላኖች የጎማዎች ጥገና ይከናወናል።

አየር መንገዱ አየተጠቀመባቸው የሚገኙትን ለትሪፕል ሰቨን (ቦይንግ 777 ) አውሮፕላኖች የጥገና ሰአት ሲደርስም በውስጥ አቅም ለማከናወን የሚቻልበትን አቅም መፈጠሩን ተገልጿል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከክፍሉ ሰራተኞች እንዳረጋገጠው የQ400 የፊት የጎማ ክፍል (nose landing gear) ለመጠገን ለአንዱ እስከ 100 ህ የአሜሪካን ዶላር ይጠየቃል።

የዋናው ጎማዎች ጥገና (main landing gear) ጥገና ለማከናወንም ከሁለት እስከ ሦስት መቶ ሺህ ዶላር ይጠየቃል።

ከሌሎች ሃገራት የደንበኞች የጥገና ጥያቄ ከመጣም ከዚህ ቀደም ለ Q400 Bombardia አውሮፕላን የፊት የጎማ ክፍሎችን ጥገና ሰርተናል አሁንም ከመጣ አቅሙ አለን ተብሏል።

የአውሮፕላን የተለያዩ የጥገና ዲፓርትመንቶች በአንድ ቦታ ተሰብስበው ሲሰሩ በአይነቱ ለመጀመሪያ ጊዜ እንደሆነ በምረቃ ስነስርአቱ ወቅት ተገልጿል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamliyAA

ፎቶ፦ የኢትዮጵያ አየር መንገድ + ቲክቫህ ኢትዮጵያ

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" ጥያቄና ፍላጎታችን በሀይል የፈረሰው አስተዳደራችን እንዲመለሰልን ነው " - ሰላማዊ ሰልፈኞች

ሀምሌ 15/2017 ዓ.ም ጊዚያዊ አስተዳደሩ በሰጠው አቅጣጫ በዞኑ አስተዳደር በአድማ በታኝ ፓሊስ ታጆቦ ይደረጋል የተባለው የስልጣን ሹምሽር በአከባቢው በተለይ በማይጨው ከተማ አለመረጋጋት አስከትለዋል። 

ከማይጨው ከተማ 195 ኪሎ ሜትር ተጉዘው መቐለ ድረስ የመጡ ተወካዮች ከፕሬዜዳንት ታደሰ ወረደ (ሌ/ጀነራል) ተወያይተዋል።

ሀምሌ 17/2017 ዓ.ም በፕሬዜዳንት ፅህፈት ቤት የተካሄደውና ድምፂ ወያነና ትግራይ ቴሌቪዥን ሚድያዎች ብቻ በአካል ተገኝተው እንዲከታተሉት የተፈቀደው ውይይት መግባባት የተደረሰበት እንዳልነበር ተወካዮቹ ከውይይቱ መልስ ለተለያዩ  ሚድያዎች ከሰጡት ቃል ለማረጋገጥ ተችሏል።

ከፕሬዜዳንት ታደሰ ወረደ (ሌ/ጀነራል) የተደረገው ውይይትን ተከትሎ ዛሬ ሀምሌ 18/2017 ዓ.ም ጠዋት በማይጨው ከተማ ሰፊ ህዝባዊ ሰላማዊ ሰልፍ ተካሂዷል።

ሰላማዊ ሰልፈኞቹ ፦

- የመረጥነው አስተዳደራችን ይመለስልን !
-ሰላም እንጂ ጦርነት አንሻም !
- ዳግም ልጆቻችን ለጦርነት አንማግድም !
- የዘውትር ፍላጎታችን መዝሙርና ፀሎታችን ሰላም ነው !
- እምቢ ለጦርነት እሺ ለሰላም !

የሚሉ መፈክሮችን በሰልፉ አስተጋብተዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#MakeWay

ወጣቶችን ማብቃት፡ ለሥነ ፆታ እና ሥነ ተዋልዶ ጤና አገልግሎቶች መሻሻል ቁልፍ ነው

ወጣቶች ከዓለም ህዝብ ውስጥ ከግማሽ በላይ የሚሆነውን ይይዛሉ፣ ነገር ግን ብዙውን ጊዜ እንደ ተዋልዶ ጤና ያሉ ወጣት ተኮር ጉዳዮች ላይ ያላቸው ተሣትፎና ተሰሚነት በእጅጉ የተገደበ ነው።

ትርጉም ያለው የወጣቶች ተሳትፎ ማለት ወጣቶችን ወደ ውይይት መድረክ ከመጋበዝ ወይም አስተያየታቸውን ከመጠየቅ ያለፈ የተዋልዶ ጤና አገልግሎቶች አደረጃጀት፣ አቅርቦት እና የአገልግሎት ግምገማ ላይ በንቃት እንዲሁም በባለቤትነት እንዲሳተፉ ማድረግ ማለት ነው።

ተጨማሪ ያንብቡ 👉 አማርኛ
👉 English

#VSO #RTG #Makeway

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#ሐምሌ19 #ቅዱስ_ገብርኤል

የሀዋሳ ቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ በዓለ ንግስ ተከብሮ እስኪጠናቀቅ ጀምሮ በከተማይቱ የተወሰኑ መንገዶች ይዘጋሉ።

ሞተር ሳይክሎችና ባጃጆች ከዛሬ ጀምሮ በዓሉ ተከብሮ እስኪያልፍ ከምሽት 3 ሰዓት በኋላ መንቀሳቀስ አይፈቀድላቸውም።

በየዓመቱ ሐምሌ 19 በሀዋሳ በታላቅ ድምቀት ለሚከበረው የቅዱስ ገብርኤል በዓለ ንግስ እጅግ በርካታ ምዕመናን ወደ ከተማው ገብተዋል። በነገው እለት እንዲሁም በዕለቱም በርካቶች ወደ ከተማዋ ይገባሉ።

የሲዳማ ክልል ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ በዓሉ በሰላም ተከብሮ እንዲያልፍ በቂ ዝግጅት ማድረጉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።

በተለይም በዓሉ ከትራፊክ አደጋ ነጻ ሆኖ እንዲከበር ዝግጅት መደረጉን ጠቁሟል።

ከሐምሌ 18/2017 ሰዓት ጀምሮ በዓሉ ተከብሮ እስኪጠናቀቅ የሚዘጉ መንገዶችንም እንዳሉ አመልክቷል።

ለተሽከርካሪ ሙሉ በሙሉ ዝግ የሚሆኑት መንገዶች የትኞቹ ናቸው ?

- ከቅዱስ ገብርኤል /ሱሙዳ/ እስከ  ሎጊታ 
- ከቅዱስ ገብርኤል /ሱሙዳ/ እስከ  ዳሽን ባንክ ፒያሳ
- ከቅዱስ ገብርኤል /ሱሙዳ/ እስከ  ማርሲል ቸርች
- ከቅዱስ ገብርኤል /ሱሙዳ/ እስከ  ሳዉዝስታር ኢንተርናሽናል ሆቴል
- ከታቦር መለስተኛ ደረጃ ት/ቤት እስከ ኢንጆሪ ላውንጅ
- ከታቦር ትራፊክ መብራት እስከ ኬራውድ ኢንተርናሽናል ሆቴል
- ከሲዳማ ክልል ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ፊት ለፊት እስከ ሰሜናዊ ሲዳማ ዞን አስተዳደር ጽ/ቤት ድረስ ያሉ መንገዶች ሙሉ በሙሉ ዝግ ይሆናሉ።

አሽከርካሪዎች አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ ጥሪ ቀርቧል።

የሰሌዳ ቁጥር የሌላቸው ባለሁለት እግር ሞተር ሳይክሎች እንደሁልጊዜው ሁሉ በሀዋሳ ከተማ በሁሉም ክ/ከተሞች ምንም አይነት እንቅስቃሴ እንዳያደርጉ ጥብቅ ቁጥጥር እንደሚደረግም አመልክቷል።

ከዛሬ ጀምሮ ደግሞ በዓሉ ተከብሮ እስኪያለፍ  ማንኛዉም ባለ ሁለት እግር ሞተር ሳይክሎችና ባጃጆች ከምሽቱ  3 ሰዓት በኋላ መንቀሳቀስ እንደማይፈቀድላቸው የክልሉ ፖሊስ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አሳውቋል።

እንግዶች ለክልሉ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ መረጃና ጥቆማ ማድረስ ሲፈልጉ  8295 ነፃ የስልክ መስመር አልያም ለከተማ ፖሊስ 7614 መደወል ይችላሉ ተብሏል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#ሐምሌ19 #ቁልቢ_ገብርኤል

እጅግ ከፍተኛ ምዕመን የሚገኝበት ዓመታዊው የቁልቢ ገብርኤል የንግስ በዓል በሰላም ተከብሮ እንዲያልፍ የምስራቅ ሐረርጌ ዞን ፖሊስ በቂ ዝግጅት ማድረጉን አሳውቋል።

ምዕመናን ከወዲሁ ለንግስ በዓሉ ወደ አካባቢው እየተጓዙ ሲሆን ነገም በስፋት ይጓዛሉ፤ ቁልቢና አካባቢው ገብተውም ያድራሉ።

ፖሊስ በዓሉ በሰላም ተከብሮ እንዲጠናቀቅ በቂ ዝግጅት መደረጉን አመልክቷል።

በአካባቢው ዳገት፣ ቁልቁለት እና ጠመዝማዛ መንገድ ስለሚበዛና ወቅቱም ደግሞ ክረምት ስለሆነ አሽከርካሪዎች ተገቢውን ጥንቃቄ በማድረግ እንዲሁም የትራፊክ ህግና ደንብ በማክበር እንዲያሽከረክሩ ማሳሰቢያ ተላልፏል።

የበዓሉ ታዳሚዎች ወደ በዓሉ ስፍራ ሲጓዙም ንብረቶቻቸውን በጥንቃቄ መያዝ አለባቸው ተብሏል። #ENA

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#Update

የመሰቦ ስሚንቶ ፋብሪካ ዛሬ ሀምሌ 17 ቀን 2017 ዓ.ም በሰጠው አጭር መግለጫ ከ75 ቀናት በላይ አቋርጦት የነበረውን ስሚንቶ የማምረት ስራ መልሶ መጀመሩን አስታውቋል።

ስራ ባቆመባቸው ቀናት ከ400 ሺ ቶን በላይ ስሚንቶ ሳያመርት ቀርቷል።

መሰቦ ሲመንቶ ከሁለት ወራት ተኩል በላይ ስራውን እንዲያቋርጥ ምክንያት የሆነው ችግር በዘላቂነት በመፈታቱ መልሶ ወደ ማምረት እንደገባ አመልክቷል።

ፋብሪካው ጥሬ እቃ ከሚያገኝበት አከባቢ ከሚኖር ማህበረሰብ ጋር በተፈጠረ አለመስማማት የማምረት ስራውን አቁሞ እንደነበር መግለጹ ይታወሳል። #DW

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#Sidama

" ተከራይተዉ በሚኖሩበት ቤት ነዉ ሞተዉ የተገኙት ! " - የደቡባዊ ሲዳማ ዞን ኮሚኒኬሽን

የደቡባዊ ሲዳማ ዞን አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ የነበሩት አቶ ሙሉነህ ተክሉ በአለታ ወንዶ ከተማ ተከራይተው በሚኖሩበት ቤት ውስጥ እራሳቸውን አጥፍተው መገኘታቸውን የዞኑ ኮሚኒኬሽን ኃላፊ አቶ ቄዲዳ ሻመና ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

ኃላፊዉ ዛሬ ጠዋት ቢሮ ገብተዉ ባለጉዳይ ጭምር ሲያነጋግሩ እንደነበርና ምሳም ከጓደኞቻቸዉ ጋር በልተዉ ወደ ቤታቸዉ መሄዳቸዉንና ከቀኑ 8 ሰዓት አከባቢ ይህ ጉዳይ መሰማቱንም ገልፀዋል።

ከአማሟታቸዉ ጋር በተያያዘ ፖሊስ ምርመራ መጀመሩን የገለፁት ኃላፊዉ ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ ' በግምገማ ምክንያት ነዉ ' የሚሉና ሌሎችም መረጃዎች ከእዉነት የራቁና በቅርቡ የዞና መንግስት ያካሄደዉ ምንም አይነት ግምገማ አለመኖሩን ገልፀዋል።

አቶ ሙሉነህ ተክሉ የደቡባዊ ሲዳማ ዞን አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ ከመሆናቸው በፊት የአለታ ጩኮ ከተማ ከንቲባ ሆነዉ ሲሰሩ መቆየታቸውንና ከስራ ባልደረቦቻቸዉና ከመንግስት የስራ ኃላፊዎችም ጋር ተግባብተው ሲሰሩ እንደነበር አቶ ቄዲዳ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከኃላፊው አሟሟት ጋር በተያያዘ የደቡባዊ ሲዳማ ዞን ፖሊስ መምሪያን አዛዥን ለማነጋገር ሞክሮ ጉዳዩ አሁናዊና መረጃ የማደራጀት ስራ ላይ መሆናቸውን በመግለፅ በቀጣይ ለሕዝብ ይፋ እንደሚደረግ አስታዉቀዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamliyHwassa

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

ኢትዮ ቴሌኮም የ2017 ዓም በጀት አመቱን ማጠናቀቁን ተከትሎ የ1 ጂቢ ነጻ የኢንተርኔት አገልግሎት ለደንበኞቹ ይፋ አድርጓል።

ነጻ አገልግሎቱ ከዛሬ ምሽት ለሊት ሰባት ሰአት ጀምሮ መጠቀም የሚቻል ሲሆን የስጦታ ጥቅሉ የድምጽ፣ የመልእክት እና የኢንተርኔት አገልግሎቶችን ያካትታል።

በዚህም መሰረት ከዛሬ ሐምሌ 17 ለሊት ሰባት ሰአት ጀምሮ እስከ ሐምሌ 20 ከቀኑ 12 ሰአት ድረስ በየቀኑ 5 ደቂቃ የድምጽ፣ 341 Mb የኢንተርኔት እና 8 የSMS አገልግሎት በ ነጻ አገልግሎት መጠቀም ይቻላል።

ላልተገደበ ኢንተርኔት ተጠቃሚዎች የነጻ ስጦታ አገልግሎቱ 10 ደቂቃ አለም አቀፍ ጥሪን ያካትታል።

ለቴሌ ብር ሱፐር አፕ ተጠቃሚ ደንበኞች ደግሞ ተጨማሪ የ 1 ጂቢ ነጻ የኢንተርኔት አገልግሎት ማቅረቡን ተቋሙ አሳውቋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#ethiotelecom

" አዲስ አበባ በአንድ አመት ጊዜ ውስጥ የክልል ከተሞችን ደግሞ በአምስት አመት ጊዜ ውስጥ ከኮፐር ወደ ፋይበር ሞደም ለመቀየር አቅደናል " - ኢትዮ ቴሌኮም

ኢትዮ ቴሌኮም የሶስት አመት መሪ ስትራቴጂክ እቅድ እና የ 2017 በጀት አመት እቅድ አፈጻጸም በሚመለከት ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል።

የተቋሙ አፈጻጸም በሚመለከት ዘለግ ያለ ሪፖርት ያቀረቡት የተቋሙ ስራ አስፈጻሚ ፍሬ ህይወት ታምሩ በዘንድሮ በጀት አመት 162 ቢሊየን ብር ገቢ በማግኘት የእቅዳቸውን 99 በመቶ ማሳካት መቻሉን አሳውቀዋል።

የሶስት አመት መሪ ስትራቴጂክ እቅዱም 331.5 ቢሊየን ብር በማመንጨት ትርጉም ያለው ሥራ አከናውኖ ተጠናቋል ብለዋል።


ስለ ተቋሙ አፈጻጸም ዝርዝር ማብራሪያ በየዘርፉ ያቀረቡት ዋና ስራ አስፈጻሚዋ ፍሬ ህይወት ታምሩ ምን አሉ ?

➡️ በበጀት አመቱ  የ4G ኔትወርክ የህዝብ ሽፋንን ከ37.5 በመቶ ወደ 70.8 በመቶ ማድረስ ተችሏል።

➡️ ከ800 ሺ በላይ ዲቫይዞችን ለደንበኞች አቅርበናል።

➡️ 19 ሚሊየን ዲቫይዞች (የሞባይል ቀፎዎችን) ሽያጭ አከናውነናል።

➡️ በዘንድሮ አመት 1,683 አዳዲስ የሞባይል ጣቢያዎችን ተክለናል።

➡️ የኔትወርክ የታወሮቻችን (ማማዎች) ብዛት ከ 8,327 ወደ 10 ሺ ተሻግሯል። ታወሮቹ የሃይል አቅርቦት የሚፈልጉ በመሆኑ እና በርካታ ሳይቶች የሚገኙት ገጠር አካባቢ ላይ በመሆኑ ሶላር፣ ባትሪ እና ጀነሬተር  በመታገዝ አገልግሎት እንዲያገኙ ሆኗል።

➡️ ኢትዮ ቴሌኮም 4305 አጠቃላይ ጀነሬተሮች አሉት ከዚህ ውስጥ በዚህ አመት 419 አዳዲስ ጀነሬተሮችን  አስገብተናል።

➡️ 43 በመቶ (4305) ሳይቶች የመጠባበቂያ ጀነሬተሮች ገጥመናል።

➡️ 21 በመቶ (2151) ሳይቶች የሶላር የሃይል አቅርቦት ይጠቀማሉ።

➡️ 512 ከተሞች በ4ጂ አገናኝተናል።

➡️ 936 ከተሞች የ 4ጂ እና አድቫንስድ 4ጂ አገልግሎት ተጠቃሚ ሆነዋል።

➡️ የ4 ጂ ሽፋናችን ከ 37.5 በመቶ ወደ 70.8 በመቶ በአንድ አመት ጊዜ ውስጥ ማድረስ ችለናል።

➡️ 871 አዳዲስ ከተሞችን በዚህ ሦስት አመት ስትራቴጂክ ዘመን ማገናኘት ችለናል።

➡️ የ5ጂ አገልግሎትን በአጠቃላይ 26 ከተሞችን ተጠቃሚ አድርገናል በዚህ አመት 16 አዳዲስ ከተሞችን ተጠቃሚ አድርገናል።

➡️ ከዚህ ቀደም ምንም አይነት ኮኔክሽን ያልነበራቸውን 459 ወረዳዎች እና 2,388 ቀበሌዎችን አገናኝተናል በአጠቃላይ 5.9 ሚሊየን ህዝቦችን ተጠቃሚ አድርገናል።

➡️ ዲቫይዞችን(ቀፎዎችን) ለ 529 ወረዳዎች እና ለ 2678 ቀበሌዎች በማቅረብ በአጠቃላይ 6.5 ሚሊየን ዜጎችን ተጠቃሚ አድርገናል።

➡️ በመሰረተ ልማቶች ላይ በግጭት እና በተለያዩ ምክንያቶች ጉዳት ደርሶባቸው አገልግሎት ተቋርጦባቸው የነበሩ 280 ሳይቶችን ፣1151 የሞባይል ጣቢያዎቻችንን ፣1886 የተቆረጡ ፋይበሮችን መጠገን ችለናል።

➡️ አዲስ አበባ በአንድ አመት ጊዜ ውስጥ የክልል ከተሞችን ደግሞ በ አምስት አመት ጊዜ ውስጥ ከኮፐር ወደ ፋይበር ሞደም ለመቀየር አቅደናል።

➡️ ለ24,123 ደንበኞች ባጠናቀቅነው በጀት አመት ብቻ ሙሉ ወጪዉን ተችሎ ከኮፐር ወደ ፍይበር ሞደም አዘዋውረናል።

➡️ 73 ሺ የኤሌክትሪክ መኪኖችን በሁለት የኤሌክትሪክ ቻርጅ ስቴሽኖቻችን ላይ ቻርጅ አድርገዋል።

➡️ ዘመን ገበያ ይፋ ከተደረገበት እስካሁን 7000  ትዛዞችን ተቀብሏል።

➡️ በዘመን ገበያ በ3 ወር ውስጥ ብቻ 15 ሚሊየን ብር ግብይት ተካሂዷል።

➡️ በአሁኑ ሰአት 86.1 ሚሊየን ዲቫይዞች ከኢትዮ ቴሌኮም ላይ ኮኔክትድ ናቸው።

➡️ 29.4 ሚሊየን ዲቫይዞች 4ጂ LTE የሚያስጠቅሙ ናቸው።

➡️ በጀት አመቱን ስናጠናቅቅ የደንበኞቻችን ቁጥር 83.2 ሚሊየን ሆኖ አጠናቀናል።

➡️ ብሮድ ባንድ ኢንተርኔት ተጠቃሚዎች 847.1 ሺ ደርሷል።

➡️ በበጀት ዓመቱ አጠቃላይ 162 ቢሊዮን ብር ገቢ በማግኘት የእቅዱን 99 በመቶ አሳክተናል፡፡

➡️ በበጀት ዓመቱ 193.1 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ከአለም አቀፍ አገልግሎት አግኝተናል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamliyAA

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#ሴጅ_ማሰልጠኛ_ኢንስቲትዩት

61ኛ ዙር የግራፊክ ዲዛይን፣ ቪዲዮ ኤዲቲንግ፣ ሞሽን ግራፊክ እና ዲጂታል ማርኬቲንግ ስልጠና የፊታችን ቅዳሜ ሐምሌ 19/2017 ዓ.ም በፒያሣ እና በመገናኛ ካምፓስ ይጀመራል።

👉 ተግባርን ከንድፈ ሀሳብ ያስተሳሰረ ስልጠና
👉 Advanced Graphic + Video Editing + Motion Graphic + Digital Marketing በአንድ ላይ
👉 ከ50 በላይ ፕሮጀክቶች ያሉት

ስልክ ፦ 0906777799 / 0906777755
አድራሻ፦ ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ እና ቁ.2: መገናኛ ታሜጋስ ህንፃ 2ኛ ፎቅ

የበለጠ ይጠብቁ ...
Instagram
Telegram
sage_training_institute">Tiktok
Linkedin

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#ክረምት : ከኢትዮጵያ ሚቲዮሮሎጂ ኢንስቲትዩት በተገኘው የአየር ትንበያ መረጃ እስከ ሐምሌ 24 ድረስ ፦
- በአዲስ አበባ
- በድሬዳዋ
- በሐረር እና ሌሎችም የሀገሪቱ አካባቢዎች ላይ ከመካከለኛ እስከ ከባድ ዝናብ ይጠበቃል።

አዲስ አበባን ጨምሮ በሌሎችም አካባቢዎች በ24 ሰዓት ውስጥ የሚኖረው የዝናብ መጠን ከመካከለኛ እስከ ከባድ መጠን (ከ11 እስከ 30 ሚ.ሜ) እንደሚሆን ተመላክቷል።

ዛሬም በአዲስ አበባ በረዶ የቀላቀለ ከፍተኛ ዝናብ ጥሎ ነበር። በዚህም ምክንያት በአንዳንድ ቦታዎች መኪኖች ጭምር በጎርፍ ተውጠው ታይተዋል።

(እስከ ሐምሌ 24/2017 ዓ/ም ድረስ በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች ያለውን የአየር ትንበያ መረጃ ከላይ ተመልከቱ - #EMI)

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamliyAA

ፎቶ እና ቪድዮ ፦ ከማህበራዊ ሚዲያ

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#Afar

" በክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን የፌስቡክ ገጽ እየተላላፈ ያለው መልዕክት የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽንንም የክልሉን መንግስትም አይወክልም " - አፋር ክልል

ምሽቱን በአፋር ክልል ፓሊስ ኮሚሽን ኦፊሴላዊ የፌስቡክ ገጽ ላይ " የብልጽግና መንግስት የአፋርን ህዝብ ለሕወሓትና ኢሳ ቡድን አሳልፎ ሰጥቷል " በሚል መንግስትን በብርቱ የሚተች በኮሚሽኑ ገጽ ያልተለመደ መግለጫ ወጥቶ በማህበራዊ ሚዲያው በስፋት እየተሰራጨ ይገኛል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያም፣ የተፈጠረው ነገር ምንድን ነው ? ሲል የአፋር ክልል መንግስት ኮሚኒኬሽን ኃላፊ አቶ መሐመድ አሊን የጠየቀ ሲሆን፣ እሳቸውም " የፓሊስ ኮሚሽኑ የፌስ ቡክ ፔጅ ሐክ ተደርጎ ነው፣ ለመመለስ ጥረት እየተደረገ ነው " ብለዋል።

የክልል ፖሊስ ኮሚሽን የራሱ ማህበራዊ ሚዲያ እንዳለው የገለጹት ኃላፊው፣ " እዛው ውስጥ ይሰራ የነበረና ከተቋሙ የተባረረ፣ አሁን ተቋም ውስጥ የሌለ አዲሚን የነበረ ሰው ነው የማይገቡ መልዕክቶችን እያስተላለፈ ያለው " ሲሉ አስረድተዋል።

ይሄው አካል ሰሞኑን ከአፋር ወደ ሌላ ቦታ መኮብለሉን ገልጸው፣ " ፔጁን በፊት ይጠቀምበት ነበር፡፡ በኋላ ስልኩንም ከፔጁ ሪሙቭ አድርገው እሱንም አስወጥተው ነበር፡፡ በራሱ ኤሜል ስለከፈተው እንደገና ገብቶ ነው የማይገቡ መልዕክቶችን እያስተላለፈ ያለው " ሲሉም ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስረድተዋል፡፡

" አድሚኑ በዚህ ሰዓት አፋር ክልል ውስጥ የለም፡፡ በሌላ አገላለጽ ባንዳ ነው " ያሉት ኃላፊው፣ " ልጁ ከፍተኛ የዲሲፕሊን ችግርም ያለበት፣ ታማኝ ያልሆነ ልጅ ነው። እዚህ የለም ቢኖር እንደዚህ አያደርግም/አይችልም ነበር " ብለዋል።

ይህ የምሽቱ የተለየ መልዕክት በፖሊስ ኮሚሽኑ የፌስቡክ ገጽ ፖስት ከተደረገበት ሰዓት ጀምሮ በክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን የፌስቡክ ገጽ እየተላላፈ ያለው መልዕክት የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽንንም የክልሉን መንግስትም የማይወክል መሆኑን ኃላፊው አሳውቀዋል፡፡

ስለዚህ " የአፋር ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ከዚህ በፊት በቀጥታ ተጠሪነቱ ለክልሉ ሰላምና ደህንነት ቢሮ የነበረ ቢሆንም ከዚህ በኋላ የአፋር ፖሊስ ኮሚሽን በቀጥታ ተጠሪነቱ ለክልሉ ርዕሰ መስትዳድር ጽሕፈት ሆኗል " በሚል እየተሰራጨ ያለው መረጃ ከፌስቡክ ገጹ ሐክ መደረግ ጋር በተያያዘ ነው ? ስንልም ኃላፊውን ጠይቀናል፡፡

እሳቸውም በምላሻቸው፣ " እሱ እኛ ጋ ብቻ አይደለም፣ ፌደራል ፖሊስም፣ የሌሎች ክልሎችም እንደዛ ነው፡፡ ዋናው ምክንያቱ ፔጁ ሐክ ተደርጎ ነው " ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል፡፡

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#Update

ተስተካክሏል !

አዲስ አበባ አስኮ አዲስ ሰፈር ወደ መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን መንገድ ላይ የእንጨት ኤሌክትሪክ ፖል ተንጋዶ ለመውደቅ እጅጉን መቃረቡን የአካባቢው ነዋሪዎች ጠቁመው ነበር።

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በላከው መረጃ በጥቆማው መሰረት " የዘመመውን ምሰሶ አቃንተን ከአደጋ ነፃ አድርገናል " ሲል ገልጾልናል።

#እናመሰግናለን
@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" የሶስት ሰዎች አስክሬን ተገኝቷል፤ ዝናብና አስቸጋሪዉ መልክአምድር ፈታኝ ቢሆንም የቀሪ አስከሬኖች ፍለጋ ቀጥሏል " - የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ

ዛሬ ሶስተኛ ቀኑን በያዘዉ የአስክሬን ፍለጋ ከማለዳ ጀምሮ በሰዉና በማሽን ታግዞ የቀጠለ ሲሆን ረፋዱን የ3 ሰዎች አስክሬን መገኘቱን የደቡብ አሪ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ግዛዉ ሃይሌ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

ተጨማሪ የመሬት መሰንጠቅ አደጋዎች በአከባቢው መከሰታቸውን የገለፁት ዋና አስተዳዳሪዉ በዚህም ምክንያት የተፈናቃዮች ቁጥር ከ1 ሺህ ማለፉን አስረድተዋል።

አሁን ላይ ለተፈናቃዮችም ሆነ ጉዳት ለደረሰባቸው የአከባቢው ነዋሪዎች እየተደረገ ያለዉ እርዳታ በቂ አለመሆኑንና በአከባቢው ያለዉ ከፍተኛ የወባ በሽታ ስርጭት ተፈናቃዮች አከባቢ መገኘቱን ጉዳቱን የከፋ ሊያደርገዉ ይችላል ሲሉም አቶ ግዛዉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ በጉዳዩ ላይ ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት የክልሉን አደጋ ስጋትና ስራ አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ጋንታ ጋምኣን ለማነጋገር ቢሞክርም ኃላፊው ጉዳዩን ከሰሙ በኋላ ጆሯችን ላይ ስልክ በመዝጋት መረጃ ከመስጠት ተቆጥበዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጉዳዩን እየተከታተለ መረጃ የሚያጋራ ይሆናል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamliyHawassa

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#MakeWay

በተዋልዶ ጤና አገልግሎቶች ላይ ድርብርብ ቀንበር ያለባቸው ወጣቶችን አካታች ያደረገ የማህበረሰብ ሀሳብ መስጫ ካርድ ምንድን ነው? 

ተጨማሪ ይመልከቱ 👉 ለአማርኛ
👉 English

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#MillenniumHall

ሚሊኒየም አዳራሽ ፈርሶ በአዲስ መልኩ ሊገነባ ነው።

በሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ስር የሚገኘው ሚሊኒየም አዳራሽ በመባል የሚታወቀው አዲስ ፓርክ እና ማኔጅመንት ከታህሳስ 2018 ጀምሮ ሙሉ በሙሉ ፈርሶ በአዲስ መልኩ እንደሚገነባ መገለጹን ካፒታል ጋዜጣ ዘግቧል።

በ2000 ዓ.ም. አገልግሎት መስጠት የጀመረው ይህ ግዙፍ አዳራሽ በኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገኙ ታላላቅ አዳራሾች ግንባር ቀደሙ ነው።

አዲሱ ግንባታ የአዳራሹን አቅም እና ዘመናዊነት ይበልጥ ያሳድጋል የተባለ ሲሆን ለግንባታው የሚወጣው ኢንቨስትመንት መጠን እና የስራ ተቋራጩ ማንነት በቀጣይ ይፋ ይደረጋል ተብሏል።

ሚሊኒየም አዳራሽ በ20 ሺህ ስኩዌር ሜትር ስፋት ላይ ያረፈ ሲሆን በአንድ ጊዜ እስከ 25,000 ሰዎችን የማስተናገድ አቅም አለው።

ይህ አዳራሽ ከትልልቅ ብሔራዊ ፕሮግራሞች፣ ዓለም አቀፍ ስብሰባዎች፣ ኤግዚቢሽኖች፣ ኃይማኖታዊ ፕሮግራሞች፣ የምርቃት ስነስርዓቶች በተጨማሪ፣ ታላላቅ ሰዎች ህይወታቸው ሲያልፍ ለሽኝት ስነስርዓቶች ጭምር ሚናውን ሲጫወት ቆይቷል።

በሰኔ ወር 2017 ምሽት ላይ ሚሊኒየም አዳራሽ የተለመደውን አገልግሎት እየሰጠ በነበረበት ወቅት ድንገተኛ የእሳት አደጋ እንደገጠመው ታውቋል። የዚህ ችግር ምንጭ ለጊዜው በሚመለከተው አካል እየተጣራ በመሆኑ ጊዜው ሲደርስ ይፋ እንደሚደረግ ተገልጿል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ ከ17 ዓመታት በኃላ አዳራሹ ሙሉ በሙሉ ፈርሶ በአዲስ መልኩ መገንባት ለወደፊቱ ለተለያዩ ዝግጅቶች የተሻለ እና ዘመናዊ የመስተንግዶ አማራጭ እንደሚሰጥ ይጠበቃል ተብሏል።

#CAPITAL

@tikvahethiopia

Читать полностью…
Subscribe to a channel