tikvahethiopia | Unsorted

Telegram-канал tikvahethiopia - TIKVAH-ETHIOPIA

1532594

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው። @tikvahuniversity @tikvahethAfaanOromoo @tikvahethmagazine @tikvahethsport @tikvahethiopiatigrigna #ኢትዮጵያ

Subscribe to a channel

TIKVAH-ETHIOPIA

#Ethiopia

ባንኮች እስከ ህዳር አጋማሽ ድረስ ከብሔራዊ መታወቂያ (ፋይዳ) ጋር የማስተሳሰር ሥራ ማጠናቀቅ ይኖርባቸዋል ተባለ።

ብሔራዊ ባንክ እና የብሔራዊ መታወቂያ በጋራ ባወጡት አዲስ የአተገባበር ሥርዓት መሰረት የፋይናንስ ተቋማት ብሄራዊ ኦፕሬተር በሆነው ኢት-ስዊች በኩል ከብሔራዊ መታወቂያ (ፋይዳ) ጋር የማስተሳሰር ሥራ መስራት መጀመራቸው ተገልጿል።

እስካሁን 10 የሚሆኑ የፋይናንስ ተቋማት ከብሔራዊ መታወቂያ (ፋይዳ) ጋር የማስተሳሰሩን ሥራ ጨርሰዋል ሲባል ሌሎች ባንኮች በሙከራ ደረጃ ላይ ይገኛሉ።

የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ይለበስ አዲስ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ እንደገለጹት ይህ አሰራር ባንኮች አገልግሎታቸው ቀልጣፋ እንዲሆንና ማዕከላዊ የመረጃ አያያዝ እንዲኖር ያስችላል ሲሉ ገልጸዋል።

አክለውም ትስስሩ ባንኮች ከደንበኞቻቸው ጋር ያላቸውን አገልግሎት ያሳልጥላቸዋል፤ ወጪንም ይቆጥብላቸዋል ነው ያሉት።

የኢት-ስዊች ቺፍ ፖርት ፎልዮ ኦፊሰር (CPO) አቤኔዘር ወንደሰን በበኩላቸው ከዚህ በፊት ደንበኞች አካውንት ሲያወጡ ባንኮች የደንበኛውን መታወቂያ ለማረጋገጥ ሁለት መቶ ብር በአንድ ሰው ክፍያ እንደሚጠበቅባቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

በአዲሱ አሰራር ባንኮች ስንት እንደሚከፍሉ ተመን ባይወጣላቸውም ክፍያው ሲወሰን ከሀምሳ ብር እንደማይበልጥና ይህም ባንኮችን ከብዙ ወጪ እንደሚያድናቸው አክለው ተናግረዋል።

ባንኮች እስከ ህዳር አጋማሽ ድረስ ጥምረት አድርገው መጨረስ እንዳለባቸውም ነው አቤኔዘር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የተናገሩት።

ባንኮቹ ከብሔራዊ መታወቂያ ጋር በቀጥታ ትስስር አይኖራቸውም ሲባል ትስስር የሚኖራቸው በኢት-ስዊች በኩል እንደሆነም ተገልጿል።

ኢት-ስዊች ሁሉንም ባንኮች ያስተሳሰረ ስለሆነ ብሔራዊ መታወቂያ ከኢት-ስዊች ጋር በመቀናጀት ሁሉንም ባንኮች በአንድ ጊዜ ማግኘት ይችላል።

የባንክ አካውንት ሲከፈት ባንኮች የብሔራዊ መታወቂያ ቁጥሩን ወደ ኢትስዊች ልከው ኢት-ስዊች ባንኩ ስለደንበኛው የሚያስፈልገውን መረጃ (KYC) ከብሔራዊ መታወቂያ ተቀብሎ ለባንኮቹ መልሶ ይልካል።

የብሔራዊ መታወቂያ የጣት አሻራን በክፍያ ወቅት እንደ ይለፍ ቃልም መጠቀም እንዲቻል አሁን ላይ የተጀመሩት ትስስሮች እንደሚያግዙም ተጠቅሷል።

ኢት-ስዊች የፋይናንስ ሪፖርቱን በቅርቡ ሲያቀርብ በባለፈው በጀት ዓመት፥ ጠቅላላ ገቢው 2.2 ቢሊዮን ብር መሆኑን ጠቅሶ ከታክስ በፊት 1.42 ቢሊዮን ብር ማትረፉንና ይህም ካለፈው የበጀት ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ34% ጭማሪ ማሳየቱን ገልጿል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ


@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

ዳሸን ባንክ እስከ 30 ሚሊዮን ብር ሽልማት ያለውን የ"ዳሸን ዕድል" ጨዋታ ይፋ አደረገ

ዳሸን ባንክ በዳሸን ሱፐር አፕ ላይ ብቻ የሚገኝ አዲስ የዲጂታል ሽልማት እና የጨዋታ ተሞክሮ የሆነውን ዳሸን እድልን በይፋ መጀመሩን አሳወቀ።

ይህበአይነቱ ልዩ የሆነው የሱፐር አፕ እድል እስከ 30 ሚሊዮን ብር የሚደርስ ጠቅላላ የሽልማት ገንዘብ ያለው ሲሆን፣ ይህም የዳሸን ሱፐር አፕ ተጠቃሚዎች የባንኩን ዘመናዊ ዲጂታል አገልግሎቶች በመጠቀም አስደሳች ሽልማቶችን የማግኘት ልዩ እድል የሚሰጣቸው ነው።

የዳሸን ዕድል ሎተሪ ደንበኞች እንዲሳተፉ እና እንዲያሸንፉ በአርኪ መንገድ የቀረበ ጨዋታ ነው፡፡ የዳሸን ሱፐር አፕ ተጠቃሚዎች በዕለት ተዕለት በሚያደርጓቸው ዲጂታል ግብይቶች፣ (ማለትም የገንዘብ ዝውውሮችን በማድረግ፣ ሱፐር አፕን በማውረድ እና በመጠቀም፣ ከሌሎች ባንኮች ገንዘብ በመቀበል፣ የንግድ ክፍያዎችን በመፈፀም፣ የአየር ሰዓት በመሙላት እንዲሁም ሌሎች በመተግበሪያው ውስጥ የሚገኙትን የቻት ባንኪንግና የበጀት አገልግሎቶችን) እና ሌሎች አገልግሎቶችን በመጠቀም በቀላሉ "ሳንቲሞችን" መሰብሰብ ይችላሉ፡፡

ደንበኞች ከዚያም የሰበሰቡትን ሳንቲሞች በመጠቀም ስልኮቻቸውን "በማወዛወዝ" እና ከሞባይል ዳታ ፓኬጆች አንስቶ ከ100 ብር እስከ 100,000 ብር የሚደርሱ የኤሌክትሮኒክስ የገንዘብ (e-money) ሽልማቶችን፣ ሳምሰንግ ጋላክሲ ኤስ 23 እና ኤ 54፣  አይፎን 16 ሞዴል ስልኮችን እንዲሁም አዲስ የቢዋይዲ መኪና ሽልማቶችን ማሸነፍ ይችላሉ።

ከጥቅምት 22 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ዳሸን ባንክ በዳሸን ዕድል የማስተዋወቅ ዘመቻው በሺዎች የሚቆጠሩ ሽልማቶችን ለአሸናፊዎች መስጠት ጀምሯል። ይህ የማስተዋወቅ ዘመቻ የዳሸንን ደንበኞች ለመሸለም ብቻ የቀረበ ሳይሆን ደንበኞች በዳሸን ሱፐር መተግበሪያ ላይ የቀረቡትን በርካታ የአገልግሎት አይነቶች እንዲጠቀሙ ለማነሳሳት የተነደፈ ነው።

ዛሬውኑ ይህን አስደሳች ጨዋታ ይቀላቀሉ!

የዳሸን ሱፐር መተግበሪያን ያውርዱ፣ ሳንቲሞችን ማግኘት ይጀምሩ፣ እና በዳሸን ባንክ የዲጂታል ባንክ ሕይወትን የሚቀይሩ ሽልማቶችን ለማሸነፍ እድልዎን ይጠቀሙ።

የዳሸን ባንክ ሱፐር አፕ መተግበሪያ ያውርዱ 👇  https://www.dashensuperapp.com/download

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" ሕዝቡ ' እምቢ ለጦርነት ' ማለት አለበት " - የትግራይ ሙሁራን እና ባለሙያዎች ማሕበር

🚨" ህወሓት እና አንዳንድ የጦር ጀነራሎች የፕሪቶሪያ የተኩስ አቁም ስምምነትን መሰረት በማድረግ ነገሮችን በሰላማዊ መንገድ ከመፍታት ይልቅ ትግራይን ወደ ሌላ ዙር ጦርነት ለማስገባት እየፎከሩና የጦርነት ዝግጅት እያደረጉ ነው ! "

የትግራይ ሙሁራን እና ባለሙያዎች ማሕበር (GSTS) በትግራይ ያንዣበበው የጦርነት ዳመና በሰላማዊ መንገድ እንዲፈታ ጥሪ አቀረበ።

ማሕበሩ ባወጣው አስቸኳይ መግለጫ " የትግራይ ሕዝብ ዋናው ፍላጎት ሰላምና ሰላም ብቻ ነው " ብሏል።

ከጫፍ እስከጫፍ ያለው የትግራይ ህዝብ ጦርነትና የጦርነት ወሬ መስማት አይፈልግም ያለው ማሕበሩ " ህወሓት እና አንዳንድ የጦር ጀነራሎች የፕሪቶሪያ የተኩስ አቁም ስምምነትን መሰረት በማድረግ ነገሮችን በሰላማዊ መንገድ ከመፍታት ይልቅ ትግራይን ወደ ሌላ ዙር ጦርነት ለማስገባት እየፎከሩና የጦርነት ዝግጅት እያደረጉ ነው " ብሏል።

" ሕዝብን የሚመራ አካል ጦርነት ለማስቀረት ይጥራል እንጂ ወደ ጦርነት የሚያመሩ ንግግሮችና ተግባራትን መፈጸም የለበትም " በማለትም የክልሉን ጊዚያዊ አስተዳደርም ወቅሷል።

አሁን በአካባቢው እያንዣበበ ያለውን የጦርነት ድባብን ለማስቀረት ሕዝቡ፣ በትግራይ ሐይሎችና በዓፋር ያሉ የታጠቁ ሐይሎች እንዲሁም የዳያስፖራው ማሕበረሰብ ለሰላም መቆም እንዳለባቸው አሳስቧል።

የማሕበሩ የአመራር አባል የሆኑት ዶ/ር ገብረኪዳን ገ/ስላሴ ለዶቼ ቨለ ሬድዮ በሰጡት ማብራሪያ ምን አሉ ?

" የትግራይ ሕዝብ ፍላጎት ሰላም ነው።

ሁለተኛ ጦርነት እንዳይመጣ እንጸልያለን።

ሆኖም ግን እንደዛ አይነት ጥሪ (የጦርነት ጥሪ) የሚያደርጉ በሁሉም ወገን ካሉ ወጣቱ የዚህ ሰለባ እንዳይሆን፤ ሕዝባችንም በሰራዊት ያሉም አንዱ ሀራ መሬት የሚባል አለ፤ ሌላው ቲዲኤፍ ትግራይ ውስጥ ያለው በመካከላቸው ምንም ወደ ግጭት የሚወስዳቸው ነገር ስለሌለ ወደዛ እንዳይሄዱ፤ እና ወጣቱ የጦርነት ሰለባ እንዳይሆን ጥሪ አድርገናል።

ሕዝቡ ' እምቢ ለጦርነት ' ማለት አለበት።

ያለው ልዩነት የፖለቲካ ልዩነት ነው። በፖለቲካ ውይይት እንዲፈቱት ነው የምንጠይቀው። ከዚህ በተጨማሪ ግን ህብረተሰቡ እራሱ ሕብረተሰቡ ፖለቲከኞች በሚፈጥሩት ግጭት ወደ ጦርነት እንዳይገባ የራሱን ተፅዕኖ ማድረግ አለበት። ለጦርነት ' እምቢ ' ማለት አለበት። " ብለዋል።

#Tigray #Peace

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" ኃላቀሩ ቡድን የወሰደው እርምጃ የትግራይና የዓፋር ህዝቦች የጀመሩት መልካም ዝምድና የሚያበላሽ የአጥፍቶ ጠፊ ውሳኔ ነው " - ስምረት

ዲምክራሲያዊ ስምረት ትግራይ ፓርቲ (ስምረት)  " ተስፋ አልባ ኋላቀር ቡድን " ሲል የገለፀው ኃይል " የእርስ በርስ ጦርነት ጥዶ ወደ እልቂት ከማስገባቱ በፊት የለውጥ ኃይሎች ተደራጅተን መመከት አለብን " አለ።

ስምረት ፓርቲ  ባወጣው መግለጫ " ኋላቀር ቡድን " ሲል የገለፀው አካል የፓለቲካ ፓርቲዎች ፣ የሃይማኖት መሪዎች ፣ የአገር ሽማግሌዎችና የዓለም አቀፍ ማሕበረሰብ ተማፅኖ ችላ በማለት ጥቅምት 26/2018 ዓ.ም የሻዕብያ ተልእኮ ለመፈፀም ዓፋር ክልል ዘልቆ በመግባት 6 መንደሮቾ ተቆጣጥሮ ይገኛል ብሏል።

" ድርጊቱና እርምጃው የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ከማፍረስ በዘለለ የትግራይና የዓፋር ህዝቦች የጀመሩት መልካም ዝምድና የሚያበላሽ የአጥፍቶ ጠፊ ውሳኔ ነው " ሲል ስምረት ፓርቲ ኮንኗል።

ድርጊቱና የትግራይ ህዝብ ፍላጎትና ዓላማ ሳይሆን የሻዕብያ ትእዛዝ ለመፈፀም የተቃጣ መሆኑ ያብራራው ስምረት ፓርቲ ድርጊቱን አውግዞ ጦርነቱ ለማስቀረት በሰላማዊ መንገድ ትግሉ እንደሚቀጥል አሳውቋል።

" እምቢ በሻዕብያ ወታደራዊ ኮማንድ በሚመራ ስር ሆነን አንዋጋም በሉ " ሲል ስምረት ፓርቲ ለትግራይ ሰራዊት አባላት ጥሪውን አቅርበዋል።

ፓርቲው ለትግራይ ዳያስፓራ ማህበረሰብ ባስተላለፈው መልእክት ደግሞ " ከነዚህ ዕድሜ ልክ ደማችንን መጠው የማይጠግቡ መዥገሮች ለመላቀቅ እጅ ለእጅ ተያይዘን ትግላችን ከፍ እናድርገው " ብሏል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" የእናቶች ለቅሶ እስካሁን ሊቆም አልቻለም። ያለቅሳሉ እናቶች። ያለው ቁስል አልተሻረም " - አቶ ገብሩ አስራት

➡️ " በጦርነት የሚነግዱ አሉ። በትግራይ ጦርነት በልፅገው የወጡ ፣ በጣም ሃብታሞች ሆነው የወጡ ሰዎች አሉ! "

የቀድሞው የህወሓት ታጋይ እንዲሁን የትግራይ ክልል ፕሬዚዳንት የነበሩት ጉምቱው ፖለቲከኛ አቶ ገብሩ አስራት በወቅታዊ ጉዳይ ዙሪያ ምን አሉ (ለኤንቢሲ ቴሌቪዥን) ?

" ከጦርነት የሚገኝ ትርፍ የለም።

እልቂት ፣ ጉዳት፣ ውድመት እንጂ ምንም አይነት ትርፍ ከጦርነት አይገኝም።

ማወቅ ያለብን ግን በጦርነት የሚያተርፉ አሉ። ስልጣናቸውን ማስጠበቅ የሚፈልጉ፣ ስልጣናቸውን ከፍ ማድረግ የሚፈልጉ አሉ።

በጦርነት የሚነግዱ አሉ። ይሄ  በግልጽ ታይቷል በትግራይ ጦርነት ወቅት። በትግራይ ጦርነት በልፅገው የወጡ ፣ በጣም ሃብታሞች ሆነው የወጡ ሰዎች አሉ። ሌላው ግን የነበረውን ሃብት ነው የጨረሰው፤ የነበረው ሃብት ተንኮታኮተ ፤ በመቶ ሚሊዮኖች የነበራቸው ኢንቬስተሮች፣ ነጋዴዎች ከስረዋል በዚህ ጦርነት ፤ ፋብሪካቸው ተቃጥሏል ፤ የነበራቸው ሃብት ተሽጦም ለእዳ አይበቃም ተበድረው ስለነበር። ይሄን ያየ ባለሃብት እና ነጋዴ እንደገና ጦርነት ሊል አይፈልግም።

ከዚህ በተጨማሪ በጣም የሚያሳዝነኝ የእናቶች ለቅሶ እስካሁን ሊቆም አልቻለም። ያለቅሳሉ እናቶች። ከእያንዳንዱ ቤተሰብ አንድ ሰው ፣ ከዛም በላይ የሞተበት ነው የትግራይ አካባቢ ሁኔታ። ይሄን መድገም (ጦርነት መፍጠር) ማለት ሀዘኑን፣ ምሬቱን ፣ አሰቃቂ ገጠመኙን መቀጠል ነው የሚሆነው ያለው ቁስል ሳይሽር።

ስለዚህ ይሄን መገንዘብ አለብን። በምንም መንገድ ወጣቱ ፣ ገበሬው ፣ ኤሊቱም ጭምር የሚገርመኝ ኤሊቱ ነው እያዩ ዝም የሚሉት፣ የሃይማኖት አባቶችም እንዲያውም በቅርቡ ኣክሱም ላይ የምግበይን ንግግር ቁጭ ብለው ሲያዳምጡ ነበር ' አንፈልግም ይሄን ጦርነት ' አላሉም የሃይማኖት አባቶች ጳጳሳት ተብለው ' ሰላም ነው የምንፈልገው ' አላሉም ፤ አንዳንዶቹ እንደውም ይሄን የሚመርቁ አሉ ፤ ይሄ እንዲሆን የሚሰሩ አሉ ይሄ ነገር መቆም አለበት።

የትግራይ ኤሊቶች ከቁጥር በላይ ኃይል ያለው  አቅም ያለው ነው፤ ኮኔክሽንም አለው ስለዚህ ይሄን ጦርነት ማስቆም ዋናው ስራ መሆን አለበት።

ይሄን እያልኩ ያለሁት በህወሓት ፣ በሻዕብያ / ፅምዶም የሚድረገውን ብቻ አይደለም በመንግሥትም በኩል መንግሥት ወደ ሰላም እንዲመጣ የመግፋት ጫና ማድረግ ያስፈልጋል። ጉዳቱ የሁላችንም ነው።

እኔ ትግራይ ስለምንቀሳቀስ ስለ ትግራይ አወራው እንጂ የጦርነት ጉዳት በሌላውም በኩል የሚሞተውን እገነዘባለሁ። የሚገድል ሁል ጊዜም ይሞታል ፤ የሚተኩስ ይሞታል፤ የሚያሸንፍውም ሟች ነው። ስለዚህ በሌላም በኩል የሚሰለፈውም ወጣት ነው።

የኤርትራዎቹ ወጣቶች እንደ ምርኮ የተያዘ ሰራዊት ነው። በዛም ቢሆን ያሳስበኛል። በቃ ዘላለም በጦርነት ውስጥ የተከተቱ። የሚያመልጠው አምልጦ የቀረውን ሰብስበው ወደ ጦርነት ነው የሚማግዱት። ይሄ ነገር ማብቃት አለበት ፤ ምንም ጥቅም የለውም። ከሻዕቢያ አመራሮች ውጭ የሚጠቀም ኤርትራዊ የለም።

እነዚህ (ከላይ የተጠቀሱ) ኃይሎች ሁሉ ጦርነት እንዳያደርጉ ጫና የመፍጠር ጉዳይ የዜጋው የኤሊቱ ፣ የነጋዴውም የባለሃብቱም የሁሉም መሆን አለበት። ድምጻቸውን የሚያሰሙበት ጊዜ አሁን ነው። "

#Tigray #Peace

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

ቀኑ ሊያበቃ ነው!
የ2017 አመታዊ የግብር መክፊያ ጊዜ ሊጠናቀቅ ጥቂት ቀን ብቻ ነው የቀረው።
ግብሮን ከጥቅምት 30 ቀን 2018 ዓ.ም በፊት ይክፈሉ እራስዎን ካላስፈላጊ ቅጣት እና ውጣ ውረድ ይጠብቁ
ግብር ለሀገር ክብር
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#USA 🇺🇸

የ2027 የአሜሪካ ዳይቫርሲቲ ቪዛ (DV) ምዝገባ እስካሁን ክፍት አለመደረጉን ስቴት ዲፓርትመንት አሳውቋል።

" ምዝገባ ተጀምሯል " የሚሉ የማጭበርበሪያ መልዕክቶች እየተዘዋወሩ እንደሚገኙ እንዲሁም አንዳንድ ግለሰቦችና አገልግሎት ሰጪዎች " የምትመረጡበትን ዕድል ከፍ እናደርግላችኋለን ክፈሉ " በማለት የማጭበርበር ተግባር ውስጥ እንደተሰማሩ ገልጿል።

ምዝገባው ገና ይፋ እንዳልተደረገ የገለጸው የአሜሪካ ስቴት ዲፓርትመትን " የምዝገባ ቀኑ እና ለውጥ ስለሚደርግበት የዘንድሮው ፕሮሰስ ዝርዝር መረጃ ዝግጅ ሲሆን ይፋ ይደረጋል " ብሏል።

አሜሪካ በዚህ ዓመት ለዳይቨርሲቲ ቪዛ ምዝገባ 1 ዶላር ማስከፈር እንደምትጀምር ማሳወቋ አይዘነጋም።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
#TikvahEthiopiaFamily

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

ገዳዩ በእድሜ ልክ እስራት ተቀጥቷል !

ወ/ሪት ልዋም ገ/ሄር በ2016 ዓ/ም በመቐለ ኲሓ ክፍለ ከተማ ነው በጭካኔ የተገደለችው።

ጭካኔ በተሞላበት ግድያ የተጠረጠረው ወጣት ኣማኑኤል ኣረጋዊ ይባላል።

በግድያ ወንጀል የተጠረጠረው ወጣት አማኒኤል ለሁለት ዓመታት ያህል ክዶ ሲከራከር ቆይቷል።

ቢሆንም ከሳሽና ተከሳሽ ሲያከራክር የቆየው የመቐለ ማእከላዊ ፍርድ ቤት ዛሬ ጥቅምት 27/2018 ዓ.ም ባዋለው ችሎት ወንጀሉ መፈፀሙ አረጋግጦ ገዳዩ በእድሜ ልክ እስራት እንዲቀጣ ወስኗል።

በችሎቱ የተገኙ የሟች ወ/ሪት ልዋም ገ/ሄር ቤተሰቦችና በሴቶች ጥቃት መከላከል ዙሪያ የሚሰሩ የመብት ተሟጓቾች ውሳኔው የዘገየ መሆኑ ጠቅሰው አስተማሪነቱ መስክረዋል።

" ወጣቶች ከስሜት ስክነት ፣ ከማንአለበኝነት የኃላፊነት ስሜት እንዲያስቀድሙ " መክረዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

ቀኑ ሊያበቃ ነው!
የ2017 አመታዊ የግብር መክፊያ ጊዜ ሊጠናቀቅ ጥቂት ቀን ብቻ ነው የቀረው።
ግብሮን ከጥቅምት 30 ቀን 2018 ዓ.ም በፊት ይክፈሉ እራስዎን ካላስፈላጊ ቅጣት እና ውጣ ውረድ ይጠብቁ
ግብር ለሀገር ክብር
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

አቢሲንያ ማስገረሙን ቀጥሏል! ገንዘብ ገቢ ወይም ወጪ ለማድረግ  ወደ አቢሲንያ ቅርንጫፍ ሲሄዱ ፣ ፎርሙን ቀድመው በአቢሲንያ ሞባይል ባንክ መተግበሪያ በመሙላት ጊዜዎን ይቆጥቡ።
#ወረቀትአልባየባንክአገልግሎት #BoaPaperlessbranch #BanksinEthiopia #AddisAbaba #Ethiopia #የሁሉም_ምርጫ

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#NewsAlert

" ህወሓት የፕሪቶሪያውን ስምምነት በግልጽ አፍርሷል " - የአፋር ክልል መንግስት

" የህወሓት ቡድን በዛሬው ዕለት በአፋር ክልል ወሰን ውስጥ በማግባት 6 መንደሮችን በጉልበት በመቆጣጠር ንጹሃንን በሞርታርና በዙ-23 ደብድቧል " ሲል የአፋር ክልል መንግሥት አስታወቀ።

ክልሉ " ቡድኑ የተለመደውን የሽብር ተግባሩን በግልጽ ጀምሯል " ሲል ከሷል።

" በዛሬው ዕለት ማለትም በቀን 26/02/2018 ዓ/ም የአዛውንቶች የህወሓት ጉጅሌ /ቡድን/ በአፋር ክልል በዞን ሁለት በመጋሌ ወረዳ ቶንሳ ቀበሌ ዋራዓ እና ሚልኪ በሚባሉ ልዩ አካባቢዎች ወሰን ተሻግሮ በመግባት ከምሽቱ አንድ ሰአት አካባቢ በንጹሐን የአፋር አርብቶ-አደሮች ላይ የከባድ መሳሪያ ተኩስ በመክፈት የፕሪቶሪያ ስምምነትን በግጭት አዋጅ በግልጽ አፍርሷል " ሲል አሳውቋል።

" ይህ የህወሓት ጣብ-ጫሪ ቡድን በቶንሳ ቀበሌ ላይ ተኩስ በሚከፈትበት ወቅት ሰላም ወዳድ የአፋር ሽማግሌዎች እንድመለሱ ቢማፀኗቸውም የህወሓት ቡድን ግን አሻፈረኝ በማለት ግጭቱን አስከትሏል " ብሏል።

" ይህ ከትናንት ጥፋቱ የማይማረው ተስፋ ቢሱ የህወሓት ቡድን ከድርጊቱ በአስቸኳይ ካልተቆጠበ የዜጎች ደህንነትና የወሰናችንን ክብር የማስጠበቅ፣ እንዲሁም ራሳችንን ከማንኛውም ውጫዊ ጥቃት የመከላከል ኃላፊነታችን እንደምንወጣ እንገልፃለን " ሲል የአፋር ክልል መንግሥት አስጠንቅቋል።

#Afar #Tigray

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#WolaitaSodo

‎የሶስት ዓመት ታዳጊ ላይ የግብረ ስጋ ድፍረት ወንጀል የፈፀመው ግለሰብ በ17 ዓመት ፅኑ እስራት እንደተቀጠ ተሰምቷል።

‎በወላይታ ዞን ሶዶ ከተማ አስተዳደር ድል በጌሬራ ቀበሌ ቆንቶ መንደር አቶ ቴዎድሮስ ያዕቆብ የተባለ ግለሰብ መስከረም 2018 ዓ/ም የ3 ዓመት ህፃን እናቷ ገበያ በሄደችበት የግብረ ስጋ ድፍረት ወንጀል መፈፀሙን የሶዶ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ አዛዥ ኮማንደር ሀብታሙ አሰፋ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ  ተነግረዋል።

በወቅቱ መረጃው የደረሰው ፖሊስ መረጃ በማሰባሰብ በአጭር ጊዜ ዉስጥ ምርመራ በማጠናቀቅ መዝገቡን ለዐቃቤ ሕግ ማቅረቡን ገልፀዋል።

‎ዐቃቤ ሕግ አስፈላጊዉን ሂደት በማሟላት ለሶዶ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ማቅረቡንና ፍርድ ቤቱም ራሷን መከላከል በማትችል እና ልዩ ጥበቃና እንክብካቤ በሚያስፈልጋት ህፃን ላይ ይህ አስነዋሪ ድርጊት መፈፀሙን በሰዉና በሕክምና ማስረጃ በማረጋገጥ የጥፋተኝነት ዉሳኔ አስተላልፎበታል።

‎ፍርድ ቤቱም ዛሬ በ26/02/2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት ግለሰቡ በፖሊስ እጁ ከተያዘበት ቀን ጀምሮ በሚታሰብ በ17 ዓመት ጽኑ እስራት እንዲቀጣ ዉሳኔ ማስተላለፉንም ኮማንደር ሀብታሙ አሰፋ አስረድተዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#China

የቻይና ፍርድ ቤት ምያንማር ውስጥ የኦንላይን ማጭበርበር ተግባር ላይ ተሰማርተው በነበሩ 5 ዋና የውንብድና ቡድን አባላት ላይ የሞት ፍርድ አስተላለፈ።

ባይ የተባለው ቤተሰብ አባላት እና አጋሮች የሆኑ 21 ሰዎች ፦
- በማጭበርባር፣
- በነፍስ ማጥፋት፣
- በሰዎች ላይ ጉዳት በማድረስ እና በሌሎች ወንጀሎች የጥፋተኝት ውሳኔ ተላልፎባቸዋል።

ይህ ቤተሰብ በእኤአ 2000ዎቹ ላይ ኃይሉ እየጎለበት የመጣ ነው።

በድህነት እና ኋላ ቀርነት ትታወቅ የነበረችውን የምያንማሯን ላውካኢንግ ዞንን ዋነኛ የቁማር እና የወሲብ ንግድ መናኸርያ አድርጓታል።

ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ደግሞ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች በሕገ ወጥ መንገድ ከተዘዋወሩ በኋላ በኦንላይን የማጭበርበር ተግባር ላይ እንዲሰማሩ ተገድደዋል።

ቤተሰቡ በዚህ የማጭበርበር ስራ በቢሊዮኖች የሚቆጠር ዶላር ያገኝ ነበር።

የፍርድ ውሳኔ ከተላለፈባቸው 5 ዋነኛ ሰዎች መካከል የውንብድና ቡድኑ አለቃ ባይ ሱቸንግ እና ልጁ ባይ ዩንግካንግ ይገኙበታል።

ያንግ ሊ ቺያን፣ ሁ ሲያውጃንግ እና ቼን ግዋንዩ ቀሪዎቹ ፍርደኞች ናቸው።

የባይ ቤተሰብ ፦
- የራሱ ታጣቂ ሚሊሻ ያለው።
- ለሳይበር ማጭበርበር ተግባር እና ለቁማር የሚውሉ 41 ካምፖችን ያለው።
- የወንጀሉ እንቅስቃሴ 4.1 ቢሊዮን ዶላር የሚዘዋወርበት እንደሆነም ተገልጿል።

ባለፈው መስከረም ላይ በተመሳሳይ የቻይና ፍርድ ቤት ላውካኢንግ ዞን በዚሁ ተግባር ላይ በተሰማራ ' ሚንግ ' የተባለ ቤተሰብ አባላት ላይ የሞት ፍርድ አስተላልፏል።

መረጃው የቢቢሲ ነው።

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

ፓስፖርት !

ሙሀባው የሱፍ የተባሉ ወንድማችን ትላንት ምሽት ቦሌ ኤርፖርት ፓስፖርትዎት  ወድቆ ተገኝቷል።

እራሶ መሆንዎን የሚያረጋግጥ ማስረጃ በመላክ ፓስፖርቶን ካገኘው ሰው መውሰድ ይችላሉ።

ካታች ባለው የመልዕክት መቀበያ መልዕክት ያስቀምጡ።

የምታውቋቸው ካላችሁም መልዕክቱን ላኩላቸው።

* አንደኛ ወንድማችን ፓስፖርቱን ተቀብሏል (8:40)

(ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት አዲስ አበባ)

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

የቤንዚን ወይም የናፍጣ መኪናን ወደ ጋዝ መቀየር ምን ያህል ያዋጣል ?

የገንዘብ ሚኒስቴር በተፈጥሮ ጋዝ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎች ከቀረጥ ነጻ ወደ ሀገር እንዲገቡ መፍቀዱ ይታወሳል።

ይህም በሶማሌ ክልል ካሉብ በዓመት 111 ሚሊዮን ሊትር ማምረት የሚችለውን የኦጋዴን ፈሳሽ የተፈጥሮ ጋዝ ፕሮጀክት የመጀመሪያ ዙር መመረቁ ከተገለፀ ከቀናት በኃላ ነበር።

ለመሆኑ በቤንዚን ወይም ናፍጣ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎችን የተፈጥሮ ጋዝን ወደሚጠቀሙ መቀየር ይቻላል ?


ቲክቫህ ኢትዮጵያ ያነጋገራቸው ባለሞያዎች “አዎን” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

ሦስተኛ ዲግሪያቸውን በታዳሽና አማራጭ ኃይል የሰሩት ዶ/ር ኃይሉ አበበ ከ20 ዓመት በላይ በአቶሞቲቭ ሥራና ስልጠና ላይ ቆይተዋል።

እንደሳቸው ገለፃ ማንኛውም ተሽከርካሪ የሞተሩ “ጤንነት” ታይቶ ሊቀየር ይችላል ሲሉ ገልፀዋል። ሆኖም ግን ቤንዚን የሚጠቀሙ ተሽከርካሪዎችን ወደ ጋዝ ማሸጋገር ከናፍጣ ይልቅ ቀላል እንደሆነ ያስረዳሉ።

“ከዋጋውም ከምቹነትም አኳያ የቤንዚን መኪናንን መቀየር ነው ብዙ ጊዜ የሚመከረው።” ብለው፤ የናፍጣ ተሽከርካሪን መቀየር ግን በጣም ውስብስብና ከፍ ያለ ዋጋ እንደሚጠይቅ አክለዋል።

የሳሚ አቶሞቲቭ ባለቤት እና የአውቶሞቲቭ ቴክኖሎጂ ባለሙያው ሳሙኤል ደጀኔንም በዚህ ኃሳብ ይስማማሉ።

ሳሙኤል በተፈጥሮ ጋዝ (CNG) የሚሰሩ መኪኖች ከቤንዚንና ከናፍጣ የበለጠ ርካሽ በመሆኑ የነዳጅ ወጪን በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚቆጥቡም ተናግረዋል።

መደበኛ ተሽከርካሪዎችን ወደ ጋዝ መቀየር ምን ያህል ያዋጣል ? ምን ያህል ገንዘብስ ያስፈልጋል ?

መደበኛ ተሽከርካሪዎች የተፈጥሮ ጋዝን መጠቀም እንዲችሉ ሲቀየሩ፤ የነዳጅ ማከማቻው (ስልባቲዮ/ Tanker)፣ የግፊት መቆጣጠሪያና የነዳጅ መርጫ (injector) ይቀየራል። ይህም ተሽከርካሪው ወደ ቤንዝን የሚቀየርበትን ዋጋ ይወስናል።

የአውቶሞቲቪው ባለሙያዊ ሳሙኤል የማስቀየሪያ ወጪ ከፍተኛ መሆን እንደ አንድ ችግር ይቆጥሩታል።

በተጨማሪም ጋዝ በመጠቀሙ ብቻ የመኪናው ጉልበት እሰከ 15 በመቶ ይቀንሳል ይላሉ።

ዶ/ር ኃይሉ የተፈጥሮ ጋዝ ከቤንዝል አንጻር ከ40 እስከ 60 በመቶ ያነሰ ዋጋ እንዳለው ይጠቅሳሉ። ሆኖም ሞተርን ለማንቀሳቀስ ከፍ ያለ ፍጆታ አለው ብለዋል።

“ለምሳሌ አንድ መኪና በአንድ ሊትር ቤንዝን ሁለት ኪሎ ሜትር ይኼዳል ብንል፤ በተፈጥሮ ጋዝ ግን ሁለቱን ኪሎ ሜትር ለመሄድ 1.5 ሊትር ይፈጃል” ሲሉ ገልፀዋል።

ቀጣዩ ጥያቄ የመቀየር ሂደቱ ኪስን ምን ያህል ይፈትሻል? የሚል ነው።

ጋዝ የተለየ ባህሪ ስላለው ከፍ ያለ እና ባለሁለት ሽፋን  (layers)  ነደጅ መያዣ እንደሚፈልግ ያነሱት ዶ/ር ኃይሉ “ለመቀየር የቤንዚን ከሆነ ከ500 እስከ 1500 የአሜሪካ ዶላር ያስፈልጋል። የናፍጣ ከሆነ ከ3000 ዶላር ይበልጣል” ብለዋል።

ሳሙኤል ደግሞ፣ “ከፍተኛ የመቀየሪያ ወጪ አውጥቶ ጋዝ እንደልብ ማግኘት ካልተቻለ ለተራ ተጠቃሚ አዋጭ አይሆንም። ጠቃሚ የሚሆነው በየቀኑ ብዙ ርቀት ለሚጓዙ እና የጋዝ አቅርቦት በቀላሉ ለሚያገኙ ብቻ ነው” ብለዋል።

በተፈጥሮ ጋዝ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎች ከተጠቃሚው አንጻር ምን ጉዳት ወይም ጥቅም አላቸው?

የተፈጥሮ ጋዝን የሚጠቀሙ ተሽከርካሪዎች  አነስተኛ ተፅዕኖ እንዳላቸው ባለሙያዎቹ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልፀዋል።

ዋጋው ከቤንዚን እና ነፍጣ ዝቅ ማለቱ ሌላኛው ጥቅሙ ነው።

“ሆኖም፣ በብዙ ቦታዎች የጋዝ መሙያ ጣቢያዎች ውስን መሆን ትልቅ ተግዳሮት ነው። በተጨማሪም ወደ ጋዝ ለመቀየር የሚወጣው ወጪ ከፍተኛ መሆኑ እና በጋዝ በሚሰሩበት ጊዜ የጉልበት መቀነስ መኖሩ ዋና ዋናዎቹ ጉዳቶች ናቸው” ሲሉ ሳሙኤል ይናገራሉ።

ጉልበት የሚቀንስበትን ምክንያት ሲያስረዱ “ጋዙ ራሱ ያለው የኃይል ይዘት (energy density) ዝቅተኛ መሆኑ ነው። በዚህ ምክንያት በተፈጥሮ ጋዝ የሚሰሩ መኪኖች ተመሳሳይ መጠን ካላቸው የቤንዚን ሞተሮች  ያነሰ ኃይል አላቸው” ይላሉ።

ዶ/ር ኃይሉ ተሽከርካሪዎች ወደ ጋዝ በሚቀየሩበት ወቅት ከባድና መጠኑ ከፍ ያለ ነዳጅ መያዣ (ሲሊንደር) እንደሚገጠምለት ጠቅሰዋል።

“ታንከሩ፣ ከፍተኛ ግፊት መቋቋም  የሚችል ስለሆነ ከፍ ያለ ነው። ስለዚህ ቦታ ይይዝብናል። መኪናችን ላይ እቃ የምናስቀምጥበትን ቦታ ሊወስደው ይቻላል። በተጨማሪም የመኪናውን ክብደት ይጨምርብናል” ሲሉ አስረድተዋል።

ሌላው በጋዝ የሚሠራ መኪና ከመደበኞቹ በተቃራኒ ሞተራቸው ለመነሳት ይዘገያል።

“ የ cold start [በፍጥነት የመነሳት] ችግር ስላለ አንዳንድ ጊዜ በቤንዚን እንዲነሱ ተደርጎ በጋዝ run እንዲያደርጉ (ስራቸውን እንዲቀጥሉ) የሚደረግበት ሁኔታ አለ” ሲሉ ዶ/ር ኃይሉ ገልፀዋል።

ቀድመው የተዘረጉ የነዳጅ ማሰያዎች የተፈጥሮ ጋዝ ሊቀርብባቸው ይችላል?

ባለሙያዎች ለዚህ ጥያቄ ምላሻቸው “አይሆንም” የሚል ነው።

ሳሙኤል “የተፈጥሮ ጋዝ መሙያ ጣቢያዎች የራሳቸው የሆነ ልዩ መሠረተ ልማት ያስፈልጋቸዋል” ብለዋል።

ሆኖም ሥራ ላይ ያሉ ማደያዎች ላይ ከፍተኛ ለውጥ በማድረግ የተፈጥሮ ጋዝን እንዲይዙና እንዲከፋፈልባቸው ማድረግ እንደሚቻል ጠቅሰዋል።

ዶ/ር ኃይሉ፥ የተፈጥሮ ጋዝ ከፍ ያለ ግፊት ስላለው ከፍተኛ የደህንነት ስጋት እንደሚጋርጥ ይናገራሉ። ስለዚህ የተለየ ስርዓት (System) እንደሚፈልጉ አንስተዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" ባለፉት ስድስት ወራት የንቁ ደንበኞችን ቁጥር በእጥፍ በማሳደግ 11.1 ሚሊየን መድረስ ችለናል " - ሳፋሪኮም

የሳፋሪኮም ኩባንያ የኢትዮጵያ ክንፍ የሆነው ሳፋሪኮም ቴሌኮሙኒኬሽን ኢትዮጵያ ኃ.የተ.የግ.ማ. የንቁ ደንበኞች ቁጥር 11.1 ሚሊዮን መድረሳቸውን ይፋ ተደርጓል።

ሳፋሪኮም ባለፉት ስድስት ወራት የንቁ ደንበኞቹን ቁጥር በእጥፍ በማሳደግ 11.1 ሚሊየን መድረስ መቻሉን ገልጿል።

ተቋሙ በኬንያ እያሳየው ያለው ቀጣይነት ያለው እድገት ዋነኛው የትርፍ አንቀሳቃሽ ሆኖ ቀጥሏል የተባለ ሲሆን በኢትዮጵያም እያጋጠመው ያለውን ኪሳራ ማጠበብ መቻሉን ተጠቁሟል።

በኢትዮጵያ የደረሰበት ኪሳራም ካለፈው በጀት ዓመት የመጀመሪያ አጋማሽ ጋር ሲነጻጸር በ59 በመቶ ቅናሽ አለው ነው የተባለው።

የሳፋሪኮም ዋና ሥራ አስፈፃሚ ፒተር ንዴግዋ " አስቸጋሪ የስራ ሁኔታ ቢኖርም፣ በሁሉም ገበያዎች አውታረ መረባችንን በማስፋት እና በማሳደግ ጠንካራ እድገት አሳይተናል " ብለዋል።

ሳፋሪኮም በኢትዮጵያ የሚሰጠው አገልግሎት ባለፉት ስድስት ወራት 47.9 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘቱ የተገለጸ ሲሆን ይህም ከአንድ ዓመት በፊት ካለው አፈጻጸሙ ጋር ሲነጻጸር በእጥፍ ጭማሪ አለው።

ከአጠቃላይ ትርፉ የሞባይል ዳታ 66.7 በመቶ ሲይዝ የድምፅ 22.1 በመቶ እና የመልእክት ልውውጦች 11.2 በመቶ ይይዛሉ።

የሶስት ወራት ንቁ ደንበኞች ቁጥር በ83.7 በመቶ በመጨመር ወደ 11.2 ሚሊዮን ከፍ ማለቱን እና የአንድ ወር ንቁ ደንበኞች ቁጥር ደግሞ ወደ 8.51 ሚሊዮን ማደጉን ተገልጿል።

ሳፋሪኮም " ከኢትዮጵያ የሚገኘው ገቢ ከ60 በመቶ በላይ አድጓል፣ ይህም በሞባይል ዳታ እና በድምጽ አጠቃቀም መጨመር ምክንያት የመጣ ነው " ብሏል።

ይህም ኩባንያው በኬንያም ሆነ በኢትዮጵያ አፈጻጸሙን ማሻሻሉን ማሳያ መሆኑን ተገልጿል።

ኩባንያው በሃገሪቱ ካሉት የኔትወርክ ማማዎች ውስጥ 1847 የሚሆኑት በራሱ የተገነቡ ሲሆን 1,459 የሚሆኑት ደግሞ በኪራይ የሚጠቀማቸው ናቸው።

በተቋሙ በተገነቡ እና በኪራይ በሚጠቀማቸው የኔትወርክ ማማዎች አማካኝነትም 55 በመቶ የህዝብ ሽፋን (Population coverage) መድረስ መቻሉን አሳውቋል።

ኤም-ፔሳ ኢትዮጵያም ባለፉት ስድስት ወራት ውስጥ 12.3 ቢሊዮን ብር እንቅስቃሴ (ግብይት) እንደተከናወነበት ተገልጿል።

ከተንቀሳቀሰው ገንዘብ በተጨማሪም 3.4 ሚሊዮን የ90 ቀናት ንቁ ተጠቃሚዎችን ማፍራቱን ተጠቁሟል።

ኤም ፔሳ በመላ አገሪቱ ከ30,700 በላይ ደንበኞችን ማፍራቱን ይፋ የተደረገ ሲሆን፤316ቱ የነዳጅ ማደያዎች ናቸው ተብሏል።

በኢትዮጵያ የኤምፔሳ ተጠቃሚዎች ቁጥር ቢጨምርም ካለፈው በጀት አመት ጋር ሲነጻጸር ግን ገቢው በ64.3 በመቶ ቀንሷል ነው የተባለው።

ባለፈው ዓመት፣ የሳፋሪኮም ግሩፕ በሴፕቴምበር 30፣ 2024 መጨረሻ ላይ የስድስት ወራት ያልተጣራ ትርፉን ይፋ ሲያደርግ የኤም-ፔሳ በኢትዮጵያ ገቢ 24.4 ሚሊዮን የኬንያ ሽልንግ የነበር ሲሆን የዘንድሮ አመት የኢትዮጵያ የኤም-ፔሳ ገቢ ወደ 8.7 ሚሊዮን የኬንያ ሽልንግ ዝቅ ማለቱን ኩባንያው አሳውቋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#SafaricomEthiopia

2 ቀን ብቻ ቀረው!  ቀጣይ ሚሊየነር ማን ይሆን ?🏆💚 ዛሬዉኑ የበሽ ጥቅልን ይግዙ፤ ሚሊየነር የመሆን እድሎን ያስፉ!

📲 የM-PESA መተግበሪያን አሁኑኑ ያውርዱ፡
https://onelink.to/ewsb22

የቴሌግራም ቦታችን: /channel/official_safaricomet_bot

ወደ *777*0# ይደውሉ ወይም በM-PESA የበሽ ጥቅል ይግዙ!

#SafaricomEthiopia
#MPESASafaricom
#furtheraheadtogether
#besh

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" የፕሮጀክቱ ቁልፍ ስራ ከሆነው የወንዝ ቅልበሳ ስራ በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል " - ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአማራ ክልል ጎንደር እና ባሕር ዳር የስራ ጉብኝት አድርገዋል።

በጎንደር በነበራቸው የስራ ጉብኝት የመገጭ የመስኖ ልማት ፕሮጀክት የስራ ሁኔታ መገምገሙን ገልጸዋል።

870 ሄክታር ላይ እንዳረፈ የገለጹት ይኸው ፕሮጀክት 17,000 ሄክታር መሬት በመስኖ አቅርቦት ይሸፍናል ተብሎ እንደሚጠበቅ አመልክተዋል።

" የፕሮጀክቱ ቁልፍ ስራ ከሆነው የወንዝ ቅልበሳ ስራ በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል " ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ " የተቀሩት ስራዎችም በተያዘላቸው የጊዜ ሰሌዳ እየተካሄዱ ይገኛሉ " ብለዋል።

በሌላ በኩል ፥ ከቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸውና ከከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ጋር በመሆን የታደሰውን የፋሲል ጊቢ መርቀዋል።

አጠቃላይ የእድሳት ሥራው ከአንድ አመት በታች የፈጀ እንደሆነ ተገልጿል።

" በእድሳቱ ፦
- በቅርስ ስፍራው ነባሩን ታሪክ በመጠበቅ ውበቱን እና ተደራሽነቱን የማስፋት ስራ ተሰርቷል።
-  የቤተመንግሥቱ የግንባታ መዋቅር ተጠግኗል።
- የእግር መንገዶችን ማሻሻል ስራ ተሰርቷል።
- ቁልፍ የሆኑ ሕንፃዎችን ከዝግባ እና ዋንዛ ባሕላዊ ቁሳቁሶችን በመጠቀም በማደስ የስፍራውን ግለ ወጥ መልክ እና ባሕርይ የመጠበቅ ስራ ተሰርቷል።
- ለጎብኝዎች ምቾት የተሰናዱ አገልግሎት መስጫዎች ተሻሽለዋል።
- አዲስ የቱሪስት ማዕከል ተከፍቷል።
- ዘመናዊ መጸዳጃ ቤቶች፣ የተሻሻሉ የመብራት እና የደኅንነት ሥርዓቶችም ተሰናድተዋል።
- እንደ አፄ ፋሲል፣ አፄ ቀዳማዊ ዮሃንስ እና አፄ ቀዳማዊ ኢያሱ አቢያተ መንግሥት ብሎም ድልድዮች፣ መታጠቢያ ሥፍራዎች፣ ታሪካዊ በሮች ወዘተ ታድሰዋል።
- ከ40,000 ስኴር ሜትር በላይ የአካባቢው ምድር የማስዋብ ሥራ ተሰርቷል " ተብሏል።

ከዚህ በተጨማሪ ጣናነሽ የተሰኘችው ጀልባ ሥራ መጀመራ ተገልጿል።

" ጣናነሽ በጣና ውሃ ላይ እየቀዘፈች ባሕር ዳር ከተማን ከጎርጎራ ኤኮ ሎጅ ማገናኘት ጀምራለች " ሲሉ ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ ገልጸዋል።

ጀልባዋ ከ180 ተጓዦች በላይ የማጓጓዝ አቅም እንዳላት አመልክተዋል።

" ለጉብኝት፣  ለመዝናናት እና አስደማሚውን የጣና ሀይቅ የተፈጥሮ ከባቢ ለመጎብኘት ወደ ጎርጎራ ኤኮ ሎጅ የሚደረገውን ጉዞ የበለጠ ምቹ አድርጋዋለች " ሲሉ አክለዋል።

#PMOEthiopia

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#Tigray
#Afar

ህወሓት ዛሬ ከሰዓት በኃላ ባወጣው መግለጫ ፤ የዓፋር ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የኮሙኒኬሽን ቢሮ " የትግራይ ሰራዊት የዓፋር ክልል ዘልቀው ገብቷል " ሲል ጥቅምት 27/2018 ዓ.ም የሰጠውን መግለጫ ውድቅ አድርጎታል።

ህወሓት የዓፋር መንግስት "ሓራ መሬት " በሚል ስም በአከባቢው እየተንቀሳቐሱ " ትግራይ ያውካሉ " ያላቸውን ታጣቂዎች ቦታ መስጠቱ በፅኑ ተቃውሟል።

" የኢፌዲሪ መንግስት በዓፋር ክልል ሓራ መሬት ያሉ ታጣቂዎችን በመጠቀም ሌላ ዙር ጦርነት እየጋበዝ ነው " ሲል ከሷል። 

" ትላንት ለሊት የድሮን ድብደባ ተፈጽሟል ፤ በድሮን ድብደባው የትግራይ ሰራዊትና የአከባቢው ነዋሪዎች ተጎድተዋል " ብሏል።

ህወሓት የጉዳቱ መጠኑን በቁጥር አላስቀመጠም።

" የድሮን ድብደባው የፕሪቶሪያ ስምምነት ሙሉ በሙሉ የሚጥስና የከፋ አደጋ የሚያስከትል ተግባር ነው " ሲልም አክሏል።

" የአህጉራዊ አደራዳሪ አገራት ዝምታን ተከትሎ የኢፌዲሪ መንግስት የፕሪቶሪያ ስምምነት እንዳይፈፀም እንቅፋት ሆኖ ቆይቷል " ያለው ህወሓት "  አሁን የድሮን ድብደባ በማካሄድ ስምምነቱን በግልፅ ጥሶታል ሲል " ስሞታ አቅርቧል።

" የኢትዮጵያ መንግስት አሁንም ያሉ ልዩነቶች በሰላማዊ ፖለቲካዊ  ውይይት እንዲፈታ " ሲል ጥሪ አቅርቧል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" ሰዎች ሰርተው ገንዘብ ከማግኘት ይልቅ በአቋራጭ ገንዘብ ማግኘት መፈለጋቸው ለአጭበርባሪዎች ምቹ ሆኗል " - የፌደራል ፖሊስ

በኦንላይን የማጭበርበር መንገዶች በርካቶችን ሲያጭበረብሩ የከረሙ አራት ድርጅቶች ተይዘው ክስ እንደተመሰረተባቸው የፌደራል ፖሊስ አስታውቋል።

የተለያዩ የማማለያ ስልቶችን በመጠቀም በርካታ ሰዎችን ያጭበረበሩት MMG፣ RTF፣ HCZ እና ሺን የተባሉ የኦላይን የማጭበርበሪያ ስልቶች ላይ ተሳትፎ አላቸው የተባሉ ተጠርጣሪዎች ተይዘው ክስ እንደተመሰረተባቸው የፌደራል ፖሊስ ገልጿል።

ድርጅቶቹ የተለያዩ ስያሜዎችን በመያዝ እና የተለያዩ እድሎች እንዳሉ በመግለፅ ሰዎች በቀላሉ በትርፍ ሰዓታቸው ተጨማሪ ስራ ሰርተው ገንዘብ ማግኘት እንደሚችሉ በመንገር በሚሊየኖች የሚቆጠር ገንዘብ አጭበርብረዋል።

ድርጅቶቹ "ኦንላይን ማርኬት" የሚል ሽፋን በመጠቀም ሲያጭበረብሩ ቆይተዋል።

አጭበርባሪዎቹ "ብር ኢንቨስት ካደረጋችሁ እጥፍ አድርገን እንመልሳለን" ብለው ሰዎች ብር በቀነ ገደብ እንዲያስገቡ ካደረጉ በኋላ ሰዎች ገንዘቡን ለማውጣት ሲሞክሩ የሲስተም ችግር በማለት ገፆቻቸውን ያጠፉ ነበሩ።

እነዚህን ድርጅቶች ሲመሩ እና ሲያንቀሳቅሱ ነበሩ የተባሉ #24_ሰዎችም በቁጥጥር ስር ሲውሉ አራቱ የውጪ ሀገር ዜጎች ናቸው ተብሏል።

አብዛኞቹ አጭበርባሪዎች መነሻቸው ከውጪ ሀገር ሆኖ አንዳንዶቹ ድርጅቶች ቢሮ ተከራይተው ኢትዮጵያውያንን ቀጥረው ሲያሰሩም ተይዘዋል።

ድርጅቶቹ በህጋዊ የንግድ ፈቃድ ስምም ሲይቀሳቀሱ የነበረ ሲሆን በባንካቸው ከፍተኛ ገንዘብ ሲንቀሳቀስ መቆየቱ ተገልጿል።

ለማሳያነትም MNG በተባለው ድርጅት የንግድ ባንክ አካውንት በዓንድ አመት ጊዜ ውስጥ ብቻ ከ1.2 ቢሊየን ብር በላይ መንቀሳቀሱን ፖሊስ አስታውቋል።

በ24 ቀን ጊዜ ውስጥም ወደ አንድ የባንክ አካውንት 400 ሚሊየን ብር ገብቷል ያለው ፖሊስ ይህም ምን ያህል ሰው ገብቶበት እንደነበር ያሳያል ብሏል።

ሰዎች ሰው ባስገባችሁ ቁጥር ደረጃችሁ እና የምታገኙት ገንዘብ ያድጋል ስለሚባሉ በርካታ ሰዎችን ያስገባሉ ያለው ፖሊስ በአንድ ተጠርጣሪ ስር ከ20,000 - 30,000 ሰው እንዳለ በምርመራ ማረጋገጡን ገልጿል።

ፖሊስ በዚህ የማጭበርበር ተግባር የተማረ ያልተማረ ሳይለይ የዩኒቨርሲቲ መምህራን፣ ተማሪዎችና የባንክ ሰራተኞች ጭምር ተጠቂ መሆናቸውን ገልፆ  በርካቶች ቤት ንበረታቸውን አጥተውበታል ብሏል።

ፖሊስ በተጠርጣሪዎች ላይ ምርመራውን ማጠናቀቁን ገልፆ ክስ መመስረቱን አስታውቋል።

ከዲጂታል አለሙ ማደግ ጋር ተያይዞ የኦንላይን የማጭበርበር ተግባራት የተስፋፉ ሲሆን ሰዎች ሰርተው ገንዘብ ከማግኘት ይልቅ በአቋራጭ ገንዘብ ማግኘት መፈለጋቸው ለአጭበርባሪዎች ምቹ ሆኗል።

በተደጋጋሚ ሰዎች ራሳቸውን ተገቢ ካልሆኑ የኢንቨስትመንት እና የኦንላይን ስራዎች እንዲጠብቁ በተለያዩ አካላት ቢጠየቅም ዛሬም በየቀኑ በርካቶች በተመሳሳይ መንገድ ገንዘባቸውን እያጡ ነው።

ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የሸገር ኤፍኤም ሬድዮ ጣቢያ ነው።

Via @TikvahethMagazine

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

🌟📱 ዘኔክሰስን ይያዙ፤ ከዓለም ጋር ይጓዙ!

በእጅግ ተመጣጣኝ ዋጋ የላቀ ፍጥነት 4ጂ ኔትወርክ የሚያስጠቅሙ ዘመናዊ የሞባይል ስልኮችን ማቅረባችንን በደስታ እንገልጻለን!

🔆 ለተጠቃሚ ምቹ የሆኑ (keypad + touchscreen)
🔋 ረጅም የባትሪ ዕድሜ ያላቸው
🗂 በ teleStorage አማካኝነት የራሳቸው የፋይል ማከማቻ ያላቸው
🤖 ቴሌብርን ጨምሮ ወሳኝ አፕሊኬሽኖች የተጫኑባቸው
🛜 ዋይፋይና ሆትስፖት ማስጠቀም የሚችሉ

ከ2 ጊ.ባ የሦስት ወራት ነጻ የዳታ ስጦታ ጋር ቀርበዋል፤ ፈጥነው የግልዎ ያድርጓቸው።

📍በአዲስ አበባ የአገልግሎት ማዕከሎቻችን እና ዘመን ገበያ ላይ ያገኟቸዋል፤ በቅርቡ ያሉበት ድረስ እንመጣለን!

ለተጨማሪ መረጃ: https://bit.ly/4hTWxQl

#znexus
#Ethiotelecom #telebirr #telebirrSuperApp #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#Update
#Tigray
#Afar

የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የዓፋር ክልል መንግሥት ትላንት ምሽት ያወጣውን መግለጫ " መሰረተ ቢስ " ሲል ውድቅ አደረገ።

ጊዜያዊ አስተዳደሩ የአፋር ክልል መግለጫን " የትግራይና የዓፋር ወንድማማች ህዝቦች ታሪካዊና ሰላማዊ ጉርብትና ለመጉዳት ያለመ ክፋት ነው " ብሏል።

የዓፋር ክልል ትላንት ምሽት ባወጣው መግለጫ የህወሓት ቡድን ኃይሎች የዓፋር ክልል ወሰንን ዘልቀው በመግባት ጥቃት መክፈታቸውን ፣ 6 መንደሮችን በጉልበት መቆጣጠራቸውን ፣ ንፁሃንን በሞርታር መደብደባቸውን እና የፕሪቶሪያውን ስምምነት ማፈረሳቸውን አሳውቆ ነበር።

የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ፤ የዓፋር ክልል መንግስት ' ሓራ መሬት ' በሚል ስም የሚንቀሳቀሱ ታጣቂዎች ትግራይን እንዲያውኩ ቦታ በመፍቀድ መተባበሩን ወቅሶ " የትግራይ ሰራዊት የዓፋር ወሰን አልፎ አልዘለቅም  " ሲል የቀረበበት ክስ አስተባብሏል።

ጊዚያዊ አስተዳደሩ " የፌደራል መንግስት የፕሪቶሪያ ስምምነት በአግባቡ እንዳይፈፀም እንቅፋት ሆኗል። ድርጊቱ ሰላማዊ ሃደት ከመጉዳት አልፎ የህዝብ ስቃይና መከራ እንዲቀጥል የሚያደርግ ሰላማዊ ትግል የሚረብሽ መሆኑ ግልፅ ነው " ብሏል።
 
" በኃይልና ህይደት በመክፈል የሚለወጥ ሁኔታ የለም " ያለው አስተዳዳሩ " ውይይት ብቸኛ የችግሮች መፍትሄ ነው " ሲል ገልጿል።

" የፕሪቶሪያ ስምምነት በተሟላ መልኩ መተግበር የዘላቂ ደህንነትና ሰላም ዋስትና መሆኑ በፅኑ እናምናለን ፤ ጊዚያዊ አስተዳደሩ ከፌደራል መንግስት ያለው ግንኙነት እንዲጎለብት ስምምነቱ ሳይውል ሳያድር ይተግበር " ብሏል።

" የትግራይ ህዝብ በዚህና በዚያ ከሚሰራጭ ወሬ ' ከጦርነትና ከትግራይ ጥፋት እናተርፋለን ' በሚል እንቅልፍ ያጡት ነውረኞች በሚፈጥሩት ያለመረጋጋት ሳይረበሽ የቀን ተቀን ውሎው ማእከል በማድረግ ተረጋግቶ እንዲረባረብ ጥሪ እናቀርባለን ፤ የዓለም አቀፍ ማህበረሰብም ከጎናችን ይሰለፍ " ብሏል።

ምንም እንኳን የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር " ወደ ዓፋር አልፌ አልዘለቅኩም " ቢልም ህወሓት በከፈተው ጥቃት በሺዎች የሚቄጠሩ የዓፋር ክልል ነዋሪዎች ተፈናቅለዋል ተብሏል።

የፌዴራል መንግሥት እስካሁን ለሚነሱት ጉዳዮች ምንም የሰጠው አስተያየት ሆነ ግብረ መልስ የለም።

የጠቅላይ ሚኒስትሩ የምስራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር አቶ ጌታቸው ረዳ ትላንት በሰጡት ቃል ፤ " ኃላቀር ቡድን " ሲሉ የሚጠሩት የህወሓት አመራር ቡድን የፌዴራል መንግሥት ላይ ትንኮሳ እንደጀመረ ገልጸዋል።

ቡድኑ የፕሪቶሪያ ስምምነትን ለመቅደድ ሁሉም ዓይነት ትንኮሳ ቢፈፅምም የፌደራል መንግስት የአፀፋ ምላሽ ከመስጠት እንደተቆጠበ ገልጸዋል።

ይህ ኃላቀር የህወሓት አመራር ቡድን የፌደራል መንግስትን ወደ ግጭት ለማስገባት ፤ በዓፋር በኩል ትንኮሳዎች እንደፈጸመ ይህንንም የአዛዡና ጌታውን #ሻዕብያ አጀንዳ ለማስፈፀም የተደረገ እንደሆነ ተናግረዋል።

በዓፋር ክልል በኩል በፌደራል መንግስት ላይ የተደረገው ትንኮሳ ጀነራል ፍስሃ ማንጁስና  ጀነራል ዮሃንስ መዲድ እንደመሩት በስም ጠርተው በመግለጽ ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ አስጠንቅቀዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

የኢትዮጵያ የፋርማሲ ማህበር (ኢፋማ) በመድሐኒት እና የህክምና መሳሪያዎች አከፋፋዮች ላይ ተግባራዊ እንዲሆን የተጣለው የ2.5 በመቶ አነስተኛ የግብር ምጣኔ ቀሪ እንዲሆን ጠየቀ።

የኢትዮጵያ የፋርማሲ ማህበር (ኢፋማ) የመድሀኒትና የህክምና መገልገያ መሳሪያዎችን የጅምላ አከፋፋዮች ንኡስ ዘርፍ በቅርቡ በወጣው አዋጅ ቁጥር 1395/2017 የዝቅተኛ አማራጭ ግብር ምጣኔ ምክንያት ከፍተኛ ተጎጂ መሆናቸውን በመግለጽ ውሳኔው ቀሪ እንዲሆንለት ለገንዘብ ሚኒስቴር በላከው ደብዳቤ ጠይቋል።

ማህበሩ "ውሳኔው በዚህ ዘርፍ የተሰማሩ የማህበሩን አባላት የሚጎዳ በመሆኑ የማስተካከያ እርምጃ እንዲወሰድ" ሲል ጥቅምት 24/2018 ዓም ለገንዘብ ሚኒስቴር ጥያቄውን በደብዳቤ አቅርቧል።

የኢትዮጵያ የፋርማሲ ማህበር (ኢፋማ) በማህበራዊ ትስስር ገጹ ያጋራው ደብዳቤ በዝርዝር ምን ይላል ?

" በቅርቡ የተከበረው ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ካወጣው የገቢ ግብር አዋጅ 1395/2017 ላይ እንደተመለከትነው አነስተኛው የግብር መጠን ከአጠቃላይ ሽያጩ 2.5 በመቶ መሆን እዳለበት ተገልጿል የዚህም ድንጋጌ መነሻ በገቢዎች ሚኒስቴር ተጠንቶ የቀረበው አማካኝ የ31 በመቶ Gross margin መሆኑን ለመረዳት ችለናል፡፡

ሆኖም ይህ ጥናት ካለው እውነታ ጋር በፍፁም የማይጣጣም ነው፡፡

እንደሚታወቀው የመድኃኒት አከፋፋዮች አማካይ Gross margin ከ 7.5 በመቶ እስከ 10 በመቶ ሲሆን ይህንን እውነታም የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በቀላሉ ሊያረጋግጠው የሚችለው ነው፡፡

ዘርፋችን መድሀኒትና የህክምና መገልገያ መሳሪያዎችን በማከፋፈል ማሀበረሰቡን በማገልገል ረገድ የአንበሳውን ድርሻ የሚወጣ ሆኖ ሳለ ይህ ዉሳኔ ዘርፉን ለኪሳራ በመዳረግ የሚያቀጭጭ እና ሊያጠፋውም የሚችል ነው።

የዘርፉ መጎዳት ደግሞ በዘርፉ ዉስጥ በቀጥታ የተሰማራውን ማህበረሰብ ብቻ ሳይሆን የመድሐኒት አቅርቦቱንም በከፍተኛ ሁኔታ በማስተጓጎል የጤናውን ዘርፍ የሚጎዳ ነው፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ የባንክ ብድር፣ገበያ ከፍ ዝቅ በማለቱ ምክንያት የሚከሰት የመድሃኒቶች የመጠቀሚያ ጊዜ ማለፍ፤ በየመድሃኒት ቤቶቹ ለማከፋፈል የሚወጣዉ ወጪ፣እንዲሁም ለማከማቻ እና ስራ ማስኬጃ የምናወጣቸዉ ወጪዎች መጨመር የመድሐኒት አከፋፋዬችን ትርፋማነት በእጅጉ እየፈተነው ይገኛል፡፡

በዚሁም ምክንያት የተጣራው ትርፍ ከጠቅላላው ሽያጭ ሲሰላ ከ 3 በመቶ የማይበልጥ ሆኖ ይታያል፡፡

በመሆኑም ይህንን ነባራዊ ሁኔታ በማገናዘብ የ2.5 በመቶ አነስተኛ የግብር ምጣኔው በ መድሐኒት እና የህክምና መሳሪያዎች አከፋፋዬች ላይ ተግባራዊ መሆኑ ቀርቶ በሂሣብ መዝገብ ወጪና ገቢ ተሰልቶ እንድንከፍል እንዲደረግልን " ሲል ማህበሩ ጠይቋል፡፡

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

እጥፍ ድርብ የማሸነፍ እድል በM-PESA!
አሁኑኑ የሳፋሪኮምን የበሽ ጥቅል በM-PESA በመግዛት 2 የእጣ ቁጥር በማግኘት ሚልየነር የመሆን እድላችንን በእጥፍ እንጨምር።

መተግበሪያውን ለማውረድ ይህንን ይጫኑ:
https://play.google.com/store/apps/details?id=et.safaricom.mpesa.lifestyle

ለተጨማሪ መረጃ በቴሌግራም ያግኙን፥
/channel/MPesaETCustomerCare

#MPESASafaricom #MPESAEthiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#NewsAlert
#Tigray #Afar

" ኃላቀሩ ቡድን የፌደራል መንግስትን ወደ ግጭት ለማስገባት በዓፋር በኩል ትንኮሳዎች ፈፅሟል ይህንንም የአዛዡና ጌታውን ሻዕብያ አጀንዳ ለማስፈፀም የተደረገ ነው " - አቶ ጌታቸው ረዳ

ጥቂት የትግራይ ኃይል አመራሮች በሻዕብያ ትእዛዝ ሰጪነት በፌደራል መንግስት ላይ ትንኮሳ እንደጀመሩና ይህን ትንኮሳ እንዲያቆሙ አቶ ጌታቸው ረዳ አሳሰቡ።

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚንስትር የምስራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ሚንስትር አቶ ጌታቸው ረዳ  ፤ " ፍስሃ ማንጁስና ዮሃንስ መዲድ የተባለችሁ የትግራይ ሰራዊት አመራሮች የጀመራችሁትን የግጭት ቀስቃስ እንቅስቃሴ አቁሙ " ሲሉ አስጠንቅቀዋል።

ሚንስትሩ " ኃላቀር ቡድን " ሲሉ የጠቀሱት የህወሓት አመራር የፕሪቶሪያ ስምምነት ለመቅደድ ሁሉም ዓይነት ትንኮሳ ቢፈፅምም የፌደራል መንግስት የአፀፋ ምላሽ ከመስጠት ተቆጥቧል ብለዋል።

" ኃላቀር " ያሉት የህወሓት አመራር ቡድን የፌደራል መንግስትን ወደ ግጭት ለማስገባት " በዓፋር በኩል ትንኮሳዎች ፈፅሟል ይህንንም የአዛዡና ጌታውን ሻዕብያ አጀንዳ ለማስፈፀም የተደረገ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።

በዓፋር ክልል በኩል በፌደራል መንግስት ላይ የተደረገው ትንኮሳ " ጀነራል ፍስሃ ማንጁስና  ጀነራል ዮሃንስ መዲድ ናቸው የመሩት ማቆም ያለባቸው እነሱ ናቸው " ሲሉ አሳስበዋል።

" ጦር አውርድ በሚል ፀሎት በራስ ህዝብ ላይ መከራና ጭፍጨፋ መጋበዝ ክህደት ነው " ያሉት ሚንስተር ጌታቸው " በትግራይና በዓፋር በኩል ያላችሁት የትግራይ ሰራዊት (TDF ) እና የትግራይ የሰላም ሃይል (TPF) የሻዕብያን ፍላጎት ለማሳካት ወደ እርስ በርስ ግጭት መግባት የለባችሁም " ብለዋል።

" ለትግራይ የሚያስብና እርባና ያለው ሰው ሦስተኛ ዓመቱ ያስቆጠረውን የፕሪቶሪያ ውል ከወዴት ደረሰ ? ብሎ መጠየቅ ብቻ ነው የሚያዋጣው " ሲሉ አቶ ጌታቸው ረዳ ገልጸዋል።

ትላንት ማክሰኞ ጥቅምት 25 /2018 ዓ.ም ከሰዓት በኃላ በትግራይ ኃይሎች እና በትግራይና ዓፋር ክልል አዋሳኝ በሚገኙት ራሳቸውን " የትግራይ የሰላም ኃይል ታጣቂዎች (TPF) " ብለው በሚጠሩት መካካል ግጭት መቀስቀሱ በማህበራዊ የትስስር ገፆች በስፋት ተነግሯል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" ያለኝ ሕይወት የኔ አይደለም። የእግዚአብሔር ነው። የምኖረው እሱ የሰጠኝን ነው !! " - ሌሊሴ ዱጋ

🙏 " የካንሰር አራተኛ ደረጃ ላይ ነው ያለሁት። የሚጎዳኝ ነገር ቢሆንም በፈጣሪ አምናለሁ። ፈጣሪን አስቀድማለሁ። እፀልያለሁ !! "

የኦሮሚያ የቱሪዝም ኮሚሽን ኮሚሽነር ሌሊሴ ዱጋ የካንሰር ሕክምና እየተከታተሉ መሆናቸውን በመግለጽ ፎቷቸውን ጭምር አያይዘው በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ከቀናት በፊት አጋርተው ነበር።

ሌሊሴ ፀጉራቸውን አጥተው ከሚሠሩበት ላፕቶፕ ፊት ለፊት በፈገግታ የተሞላ ፎቶ ግራፋቸውን " እየሠራሁ፣ እየታገልኩ፣ እያሳካሁ " ከሚል የእንግሊዝኛ ጽሑፍ ጋር አጋርተዋል።

ኮሚሽነሯ ይህንን ፎቶ እና መልዕክት ካስተላለፉ በኋላ በርካታ ሰዎች እንዲፈወሱ መልካም ምኞታቸውን በመግለጽ ፎቷቸውን እያጋሩት ነው።

እንዲህ ያለውን የጤና ሁኔታ ለሕዝብ ማጋራት ባልተለመደበት ማኅበረሰብ ውስጥ ኮሚሽነር ሌሊሴ ይህንን ማድረጋቸው በብዙዎች ዘንድ መነጋጋሪያ ከመሆኑ በላይ አድናቆት እንዲቸራቸው አድርጓል።

ሌሊሴ ሕክምና እየተከታተሉ የሚገኙበት በመካከለኛው ምሥራቋ ዮርዳኖስ ውስጥ ነው።

ስላሉበት ሁኔታ ለቢቢሲ አማርኛ ቃላቸውን ሰጥተዋል።

ሌሊሴ ዱጋ ምን አሉ ?

" ሊምፎሚያ በተባለው የካንሰር ዓይነት መያዜን ያወቁት ከአራት ወራት በፊት ለሌላ ምርመራ ወደ ጤና ተቋም በሄድኩበት ወቅት ነው።

ይህ የካንሰር ዓይነት ነጭ የደም ሕዋስን የሚያጠቃ ነው።

የጋስትሮኢንተስታይን ችግር / ሰውነት ምግብ የሚያብላላበት ሆድ ዕቃ ሕመም / መስሎኝ ወደ ሆስፒታል ሄድኩ። ካንሰር እንደሆነ ተነገረኝ።

ቀላል አይደለም። የካንሰር አራተኛ ደረጃ ላይ ነው ያለሁት። የሚጎዳኝ ነገር ቢሆንም በፈጣሪ አምናለሁ። ፈጣሪን አስቀድማለሁ። እፀልያለሁ።

ባለቤቴ፣ ልጆቼ፣ ቤተሰቦቼ እና ጓደኞቼ ከጎኔ ናቸው። ይፀልዩልኛል። ያበረታቱኛል። ሕልም ስላለኝ ብታመምም መኖር፣ መታገል እና ታትሮ መሥራት አላቋርጥም።

አሁን ላይ የኬሞቴራፒ ሕክምና እያገኘው ነው። ብዙ የጎንዮሽ ጉዳት አልደረሰብኝም።

ፀጉሬን አጥቻለሁ። ቆንጆ ፀጉር ነበረኝ። ፀጉር ማጣት ለሴት ልጅ ከባድ ነው። ፀጉርን ማጣት የተለየ ዝግጅት ይጠይቃል።

ፈጣሪ ረድቶኝ ወደ አገሬ ከተመለስኩ ለሕክምና ገንዘብ የሌላቸውን የካንሰር ሕሙማን የሚደግፍ ማዕከል ማቋቋም እፈልጋለሁ።

በባለቤቴ በኩል የተባበሩት መንግሥታት የጤና መድኅን አለኝ፤ መንግሥትም እያሳከመኝ ነው። የገንዘብ ችግር ስለሌለብኝ ነው እየታከምኩ ያለሁት። እርዳታ የሚያሻቸው ብዙ ሰዎች አሉ። ሲሻለኝ እነዚህ ሰዎች ለመርዳት ማዕከል አቋቁማለሁ።

አሁን ላይ ብርታት የሰጠኝ የሕይወት ፍልስፍናዬ ነው።

የሕይወት ፍልስፍናዬ ቀላል ነው። በየቀኑ የምችለውን ማድረግ፣ ዋጋ ያለው ነገር ማድረግ እና ጥሩ መሆን። ፈጣሪ ያስተማረን ይሄንን ነው። ምድር ላይ እስካለን ድረስ ጥሩ ነገር ብናደርግ መልካም ነው።

ያለኝ ሕይወት የኔ አይደለም። የእግዚአብሔር ነው። የምኖረው እሱ የሰጠኝን ነው። ያለ ፀፀት መኖር ነው የምሻው። ለመኖር የሚያበረታኝ እና ወደፊት የምቀጥለው በዚህ ነው።

በየዕለቱ ጥሩ እንዳደረኩ ለራሴ እየነገርኩት  ከፈጣሪ ምሕረትን ጠይቄ ነው የምተኛው።

ሕክምናውን ለመጨረስ ከአራት እስከ አምስት ወራት ይወስዳል " ብለዋል።

ሌሊሴ ዱጋ አሁን ላይ ካሉበት ዮርዳኖስ ሆነው ስራቸውን ቀጥለዋል።

ከሚከታተሉት ሕክምናቸው ጎን ለጎን ሥራቸውን የሚያከናውኑበት ቢሮ አላቸው። አንድም ቀን " ታምሜያለሁ " ብለው እያሰቡ እንደማያድሩ ተናግረዋል።

የኦሮሚያ የቱሪዝም ኮሚሽን የአምስት ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድን እያወጡ ሲሆን በቀጣይ አምስት ዓመታት ምን መሠራት አለበት የሚለውን እየሰሩበት እንዳለ ገልጸዋል።

ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የቢቢሲ አማርኛ አገልግሎት ነው።

🙏 ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለብርቱዋ ሴት ሌሊሴ ዱጋ ህክምናቸው እንዲሳካ ፤ ሙሉ ጤንነታቸውም እንዲመለስ ዘንድ ይመኛል። ሙሉ ጤንነትን ከረጅም እድሜ ጋር እንመኝላቸዋለን። የሚያምኑት ፈጣሪ ከዚህ በሽታ ይፈውሳቸው ዘንድም እንማጸናለን።

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#SafaricomEthiopia

እንኳን ደስ አላችሁ! 🎉💵

ሰኞ ጥቅምት 24/2018 የአስረኛው ዙር ዕድለኞች ዕጣ አወጣጥ በቲክቶክ እና ፌስቡክ ገፃችን ላይ በቀጥታ ስናስተላልፍ በነበረዉ መሰረት የ100,000 ብር ዕድለኛ ከደቡብ ጎንደር ሆኑዋል።

ማን ያውቃል ቀጣይ እርስዎ ሊሆኑ ይችላሉ! የበሽ ጥቅል እየገዛን እንንበሽበሽ! 🥳🎉🎉

📲 የM-PESA መተግበሪያን አሁኑኑ ያውርዱ፡ https://onelink.to/ewsb22

የቴሌግራም ቦታችን👉🏽 /channel/official_safaricomet_bot

ወደ *777*0# ይደውሉ ወይም በM-PESA የበሽ ጥቅል ይግዙ!

#MPESASafaricom
#furtheraheadtogether
#Besh100Winner

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" ኢትዮጵያ 🇪🇹 የባህር በር ማግኘቷ አይቀርም ! "

ጄነራል ዓለምሸት ደግፌ ፦

" የባህር በር የማግኘት ጉዳይ ጥያቄው ቀርቧል ፤ ተነስቷል። ብዙዎቹ ሀገሮችም አምነውበታል።

አፈጻጸሙ ላይ ችግር ሊኖረው ይችላል ፤ ሊያንገታግተን ይችላል ፤ ጊዜ ሊወስድ ይችላል ግን ኢትዮጵያ የባህር በር የማግኘቷ ጉዳይ የግድ ነው ፤ ማግኘቷም አይቀርም።

ይሄ ትልቅ ህዝብ ፣ ይሄ ትልቅ ሀገር በፍጹም ታፍኖ ሊኖር አይችልም። የባህር በር እናገኛለን ይሄን የምናገኝበት መንገድ በዋናነት በሰላማዊ መንገድ ነው ብለን ነው የምናስበው።

ይሄ ከተረጋገጠ ደግሞ እኛም ባህር ኃይላችንን እዛ ላይ አጠናክረን እናዘጋጃለን። ስለዚህ የባህር ኃይል መደራጀቱ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበር ነው።

የባህር በር ካገኘን በኃላ ' ቀስ ብለን እንደርስበታለን ' የሚባል ጉዳይ አይደለም። እያዘጋጀን እንቆያለን፣ እናሰለጥናለን ፣ ትጥቆቻችንን እናዘጋጃለን የባህር በሩ በተገኘ ሰዓት ኃይላችንን እናሰፍራለን። የራሳችንን ብሔራዊ ጥቅም እናስከብራለን። "

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#AmazonFashion

ኳሊቲ አዳዲስ ሙሉ ልብሶች አስገብተናል። ከ10ሺ እስከ 16ሺ የተለያዩ ሱፎች ገብተዋል።ዛሬዉኑ መተዉ የእርሶን ድርሻ ይዉሰዱ።ሱፍ መግዣ ጊዜዉ አሁን ነዉ።ሳይመረጥበት እና ሳያልቅቦት ይምጡ።

ቴሌግራም ቻናላችን ላይ ፎቶዋቸው ተለቀዋል። follow ያድርጉ ከፎቶቹ ላይ ይምረጡ።

በተጨማሪም 100% cotton ሸሚዝ high quality ፤በጅንስም በሱፍም የሚለበስ በ2900 ብር ብቻ፤በ1 ሺ 500ም ኳሊቲ ሸሚዞች አለን፤ አሪፍ ኮቶችንም  አስመጥተናል፤ በርካታ አማራጭ ስላለን ለብዛት ፈላጊዎች በብዙ አማራጭ አለን።   
   👉በተጨማሪም የሙሉ ልብስ ኪራይም  በሌላኛው ብራንቻችን አለን።
አድራሻ ፒያሳ downtown ህንፃ ምድር ላይ 
    ☎️0911072936 /0919339250
https://t.me/joinchat/AAAAAEc8iQJX1Zjgepjq1w

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን " ትላንትም 5 ምእመኖቼ ተገድለውብኛል " አለች።

" በአርሲ መርቲ ወረዳ የሚኖሩ 5 ኦርቶዶክሳውያን ተገድለው ፤ 3 ምዕመኖቼ ታግተው ተወስደዋል " ነው ያለችው።

" ግድያው እና እገታው የተፈጸመው በትናንትናው ዕለት ጥቅምት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 6፡00 ሰዓት ጋዶ ቀበሌ ነው " ብላለች።

" 5 ምእመናን የእርሻ ሥራቸውን አጠናቀው ምሳቸውን እየበሉ ባሉበት ጊዜ ነው በታጠቂዎች በተከፈተባቸው የተኩስ የተገደሉት " ስትል አክላለች።

ሥርዓተ ቀብራቸው በአቦምሳ ከተማ በሚገኘው በደብረ ገነት ትንሣኤ ብርሃን መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን እንደተፈጸመ ገልጻለች።

የታገቱት 3 ምእመናን እስከ አሁን የደረሰቡት እንዲሁም ያሉበት ሁኔታ አይታወቅም ብላለች።

" ይህን የምእመናኑ የግድያ እና የአፈና ተግባር ከሰሞኑ በሀገረ ስብከቱ እንደነበረው ሁሉ ተባብሶ የቀጠለ ነው " ያለችው ቤተክርስቲያኗ " በተለይም ላለፉት ሁለት ዓመታት የገጠር ቀበሌው እና በውስጡ የሚኖሩ ምእመናን ከስጋት ነጻ ሆነው ኖረው አያውቁም " ስትል አሳውቃለች።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia

Читать полностью…
Subscribe to a channel