tikvahethiopia | Unsorted

Telegram-канал tikvahethiopia - TIKVAH-ETHIOPIA

1532594

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው። @tikvahuniversity @tikvahethAfaanOromoo @tikvahethmagazine @tikvahethsport @tikvahethiopiatigrigna #ኢትዮጵያ

Subscribe to a channel

TIKVAH-ETHIOPIA

‎" ተጠርጣሪው ጭካኔ በተሞላበት መልኩ ሕፃኑን በመግደል ተከራይቶ ይኖርበት በነበረው የሟች ታዳጊ አያት ግቢ በሚገኝ መፀዳጃ ቤት መጣሉን ከተያዘ በኋላ በሰጠው መረጃ አስክሬኑ ተገኝቷል " - ፖሊስ

➡️ " የአርባምንጭ ነዋሪዎችን ያስቆጣ ድርጊት የፈፀመዉ ግለሰብ በጭር ጊዜ ውስጥ ተገቢዉን ፍርድ ያገኛል "


በአርባ ምንጭ ከተማ ‎በቀን 3/3/18 ዓ/ም ናትናኤል ማይክል የተባለ በግምት የ10 ዓመት ታዳጊ ከቤት መጥፋቱን ቤተሰቦች ለፖሊስ ያሳውቃሉ።

ይህን ተከትሎ ፖሊስ ፍለጋ ይጀምራል።

ፖሊስ ከሁሉም የፀጥታ መዋቅሮች ጋር በመሆን ክትትልና አፕሬሽን ሲያደርግ ቆይቶ ዛሬ አንድ ተጠሪጣሪ ለማምለጥ ሲሞክር በቁጥጥር ስር መዋሉን ‎የአርባ ምንጭ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ኮማንደር ክበበው አዳል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልፀዋል።

‎ተጠርጣሪው ወርቁ አሰፋ ይባላል።

ግለሰቡ በአርባ ምንጭ ከተማ ሴቻ ቀበሌ ዶሳ ቀጠና ፖሪቲ ስፕሪንግ ሆቴል ጀርባ ተከራይቶ በሚኖርበት ግቢ ውስጥ የነበረን ታዳጊ አፍኖ በመውሰድ ከወላጆቹ ገንዘብ መጠየቁንና የሕፃኑ ወላጅ እናት የተጠየቀችውን 50 ሺህ ብር በባንክ ማስተላለፏን መረጃ ማግኘታቸውን ኮማንደር ክበበው ገልፀዋል።

‎ግለሰቡ አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተምሮ የተመረቀ እንደሆነ በሚገልፅ ሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃ ምክንያት በቅርቡ ከሚሰራበት ትምህርት ቤት መባረሩን መረጃዎች እንደሚያመላክቱ ኮማንደር ክበበው ተናግረዋል።

ይኸው ግለሰብ ኢ-ሰብዓዊ በሆነ ጭካኔ በተሞላበት መልኩ ሕፃኑን በመግደል ተከራይቶ ይኖርበት በነበረው የሟች ታዳጊ አያት ግቢ በሚገኝ መፀዳጃ ቤት ውስጥ መጣሉን ከተያዘ በኋላ በሰጠው መረጃ አስክሬኑ መገኘቱንም አስረድተዋል።

‎ግለሰቡ ይህን ሕዝብን ያስቆጣ ዘግናኝ ድርጊት ከፈፀመ በኋላ በሚኒባስ ተሳፍሮ ከከተማ ለመውጣት ሲሞክር የፀጥታ ኃይሉ ከመረጃና ደህንነት ተቋም ጋር በመሆን ባደረገው ክትትል በጋሞ ዞን ምዕራብ አባያ ወረዳ ፉራ ተብሎ በሚጠራው አከባቢ በቁጥጥር ስር መዋሉን አስታውቀዋል።

‎ፖሊስ አስፈላጊውን ምርመራ በማድረግ በአጭር ጊዜ ውስጥ ሕዝቡን ያስቆጣ ዘግናኝ ድርጊት የፈፀመውን ግለሰብ ለሕግ በማቅረብ ፈጣንና ተገቢውን ፍርድ እንደሚያሰጥም ገልፀዋል።

‎ሕብረተሰቡ በትዕግስት እና በመፅናናት የምርመራና የፍርድ ውሳኔዉን እንዲጠባበቅ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ማህበረሰቡ ፦
- መኖሪያ ቤቶችን በሚያከራይበት ወቅት፣
- የአልጋ ቤት አገልግሎት በሚሰጥበት ወቅት፣
- በቅጥርና ውሎች ወቅት ግለሰቦችን ህጋዊ የቀበሌ ነዋሪነት ወይም ፋይዳ የዲጂታል መታወቂያ መያዛቸውንና ትክክለኛ አድራሻቸውንና የመጡበት ምክንያት ፣ የሚሰሩበት ተቋም ወይም ድርጅትን በማጣራት እንዲሁም ህጋዊ ተያዥ መኖሩን በማረጋገጥ ማከራየትና አገልግሎት መስጠት እንደሚያስፈልግ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል አሳስበዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamilyHawssa

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" የበሽታዉ መንስኤ ማርበርግ ቫይረስ (Marburg Virus) መሆኑን መለየት ተችሏል " - ጤና ሚኒስቴር

የጤና ሚኒስቴር በደቡበ ኢትዮጵያ ክልል በጅንካ ከተማ የሄሞራጅከ ፊቨር (Viral Hemorragic Fever) በሽታ መከሰቱን እና የበሽታዉን ምንነት በማረጋገጥ ላይ መሆኑን መግለጹ ይታወቃል፡፡

ሚኒስትሩ በዛሬው ዕለት ባወጣው መግለጫ የበሽታዉ መንስኤ ማርበርግ ቫይረስ (Marburg Virus) መሆኑን መለየት ተችሏል ብሏል።

የዘረመል ምርመራው የተከናወነው በኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ብሄራዊ ሪፈረንስ ላብራቶሪ ነው።

መግለጫው "በዚህም የዘረመል ምርመራ በአሁኑ ሰዓት ኢትዮጵያ ውስጥ የተገኘዉ ቫይረስ ሌሎች ምስራቅ አፍሪካ ሃገራት ላይ ከዚህ በፊት ከተከሰቱት ጋር ተመሳሳይ ዝርያ ያለዉ መሆኑ ታዉቋል" ነው ያለው።

በተጨማሪም በዛሬው እለትም አዲስ የበሽታውን ምልክት ያሳየ ወይም በቫይረሱ የተጠረጠረ ሰው ያልተገኘ መሆኑን ሚኒስትሩ ያሳወቀ ሲሆን በአሁኑ ሰዓት የተለያዩ የሙያ ስብጥር ያካተተ ከፍተኛ ፈጣን ምላሽ ሰጭ ቡድን ወደ ከልሉ በመላከ በሽታዉን የመከላከል እና የመቆጣጠር ስራዎች እየተሰሩ ይገኛሉ ብሏል።

ከነዚህም ውስጥ :-

° የማህበረሰብ አቀፍ የቅኝት ስራዎች፣

° በቫይረሱ የተያዙ ሰዎችን ለይቶ ማከም፣

° የማህበረሰብ ግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎች እና ከተጠረጠሩ ሰዎች ጋር ንክኪ ያላቸዉን ሰዎች የመለየት ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ተገልጿል።

በሃገር አቀፍ እንዲሁም በክልል ደረጃ የሕብረተሰብ ጤና አደጋዎች የክስተት አስተዳደር ስርዓት (Incident Management System) ተቋሞ የፈጣን ምላሽ ስራዎችን በማስተባበር ላይ ይገኛል ተብሏል።

ጤና ሚኒስቴር:-

➢ ከጤና ሚኒስቴር እና ከኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የሚተላለፉ መረጃዎችንና የጥንቃቄ መልዕክቶችን መከታተልና መተግበር፣

➢ የበሽታው ምልከት የሆኑትን በአፍ፣አፍንጫ እና ሌሎች የሰውነት ክፍሎች የመድማት፣ትኩሳት፣ማስቀመጥ እና ማስመለስ ምልከት ሲኖር ወደ ህክምና ተቋማት መሄድና በወቅቱ የላቦራቶሪ ምርመራ ማድረግ፣

➢ ምልክት ከታየበት ማንኛዉም ሰዉ ጋር ንክኪ በሚኖርበት ግዜ ራስን የመከላከያ ዘዴዎችን መጠቀም፣

➢ ሁልጊዜ እጅን በውሃና ሳሙና መታጠብ ወይም በሳኒታይዘር ማጽዳት እንደሚያስፈልግ አሳስቧል።

ማንኛውም ጤና ተቋም ለታካሚዎች ልየታ ልዩ ትኩርት በመስጠት የማርበርግ በሽታ (Marburg viral disease) መሰል በሸታ መለየት፣ ማከም እና በአፋጣኝ ሪፖርት ማድረግ እንደሚያስፈልግም በመግለጫው ጠቁሟል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#Tecno_Spark_40_Pro+

Tecno Spark 40 Pro+ 16 GB RAM እንዲሁም 256 GB የሚሞሪ ስፔስን አካቶ ስለመጣ አግጅ ማራኪ እና ፈጣን ስልክ ከበቂ ስፔስ ጋር በአንድ ላይ ሰጥቶታል፡፡ ታዲያ ምን ይጠብቃሉ የTecno Spark 40 Pro+ ስልኮችን ዛሬ ነገ ሳይሉ በእጆት ያስገቡ!!

#Spark40Pro+ #SlimeverStrongForever #TecnoAI #TecnoSpark40Series

@tecno_et

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

'' ማህበራዊ ሚድያ የልጆቻችንን ጊዜ ፣ ልጅነታቸውን እና ደህንነታቸውን እየሰረቀ ነው " - ካርሎን ስቴጅ ኦልሰን 

ከ15 ዓመት በታች የሆኑ ልጆች የማህበራዊ ሚድያ እንዳይጠቀሙ እገዳ ለመጣል መወሰኑን የዴንማርክ መንግስት አሳወቀ።

የሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ሜት ፍሬድሪክሰን በባለፈው ወር ለፓርላማ መክፈቻ ባደረጉት ንግግር የህፃናት የማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም ላይ እገዳ እንዲጣል ጥሪ አቅርበው ነበር። ይህንን ተከትሎ በዴንማርክ ፓርላማ ውስጥ ያሉ አብዛኛዎቹ ፓርቲዎች ዕቅዱን እንደሚደግፉ ተናግረዋል፡፡

'' ማህበራዊ ሚድያ የልጆቻችንን ጊዜ ፣ ልጅነታቸውን እና ደህንነታቸውን በመስረቅ ላይ ሲሆን እኛም ይህንን በማስቆም ላይ ነን ፤ ይህም የሚደረገው በዲጂታል ዓለም ውስጥ ህፃናትን እና ወጣትቶችን ለመጠበቅ ነው '' ሲሉ የዲጂታል ጉዳዮች ሚኒስትር ካርሎን ስቴጅ ኦልሰን ተናግረዋል፡፡

ሚኒስትሯ የትኞቹ የማህበራዊ ሚዲያ ላይ እገዳ እንደሚጣል እና እንዴት እንደሚተገበር በግልፅ አላሳወቁም ፤ ነገር ግን ወላጆች ከ13 ዓመት ዕድሜ ጀምሮ ያሉ ልጆች የተወሰኑ መተግበሪያዎች ለመጠቀም እንዲችሉ ይፈቀድላቸዋል ብለዋል፡፡

ዴንማርክ በአውሮፓ ህብረት ውስጥ ከመጀመሪያዎቹ ሀገራት አንዷ እንደመሆኗ መጠን በማህበራዊ ሚዲያ ላይ የዕድሜ ገደቦችን ለማስተዋወቅ አንድ ትልቅ እርምጃ እንደምተወስድ ተገልጿል።

#SocialMedia #Denmark

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#እንድታውቁት

ስለ ዓይን ጤና የሚነገሩ የተሳሳቱ እምነቶች / አመለካከቶች ምን ምን ናቸው ?

ብዙ ሰዎች በማህበረሰብ ውስጥ ስለ ዓይን ጤና የሚነገሩ ነገሮችን እውነት እንደሆኑ ያምናሉ። ነገር ግን እነዚህ ብዙ እምነቶች የተሳሳቱ እና ከሳይንስ ውጪ ናቸው።

በእነዚህ አንዳንድ እምነቶች ወይም አመለካከቶች ምክንያት ዓይናችንን በተገቢው መንገድ መንከባከብ ወይም መጠበቅ እንዳንችልና የዓይን ክትትል እንዳይኖረን ያደርጋል።

ማህበረሰብ ውስጥ በስፋት  ከተሰራጩ የተሳሳቱ አመለካከቶች ፦

1. " መነጽር ማድረግ ዓይንን ያበላሻል ወይም አንዴ መነፅር ማድረግ ከተጀመረ በዛው ይለምዳል "

ይህ የተሳሳተ አመለካከት ነው።

መነጽር እይታን አያበላሽም፣ በትክክል እንዲታየን ይረዳናል። ለምሳሌ፦ ለቅርብ ዕይታ ችግር ፣ ለርቀት ዕይታ ችግር ፣ ዕድሜያቸው ከ40 ዓመት በላይ ለሆኑ አዋቂዎች ማንበቢያ ወዘተ... ጥራት ያለው ዕይታ ያስገኛል።

የዕይታችን ጥራት በተፈጥሮ ወይም በሌላ በሽታ ይቀየራል ይህ ደግሞ መነፅር ከማድረግ ጋር ሚያገናኘው ነገር የለም።

ጥንቃቄ ፦ በዓይን ሀኪም ብቻ የታዘዘ መነፅር ይጠቀሙ።

2. " ካሮት መብላት የእይታ ችግርን ይፈውሳል "

ካሮት ቫይታሚን A እናገኝበታለን ይህም ለዓይንም ሆነ ለሌሎች ሰውነታችን ክፍል በጣም አስፈላጊ ነው ነገር ግን በራሱ በሽታን አይፈውስም።

3. " የእይታ ችግር እድሜያቸው የገፋ ሰዎች ላይ ብቻ ነው የማከሰተው "

ይህ ፍጹም ስህተት ነው።

የእይታ ችግር በህፃናትና በወጣቶችም ላይም በሰፊው ይስተዋላል። ለዓይን ጤና እንክብካቤ ካልተደረገ ችግሩ በየትኛውም እድሜ ሊከሰት ይችላል።

በእድሜ ምክኒያት ብቻ የሚመጡ የዓይን ህመሞች ግን አሉ።

4. " የዓይን ምርመራ ሚያስፈልገው የዓይን ህመም ሲኖር ብቻ ነው "

ይህም የተሳሳተ አመለካከት ነው።

መደበኛ የዓይን ምርመራ ማድረግ ቀደም ብሎ የዓይን ችግር እንዲታወቅ ይረዳል።

በርካታ የዓይን ችግሮች በጊዜው ከታወቁ አመርቂ ህክምና አላቸው። ምሳሌ ፦ amblyopia (የዓይን መስነፍ) amblyopia በጊዜ ታውቆ ካልታከመ የህክምናው ውጤት እምብዛም ነው።

5. " የፀሐይ መነጽር ለማጌጥ ብቻ ነው "

ይህ የተሳሳተ አመለካከት ነው።

ትክክለኛ የፀሐይ መነጽር ማድረግ ከፀሀይ የሚመጣ የUV ጨርን ከዓይን ይጠብቃል፣ ስለዚህ የዓይን ጤና መንከባከብያም ጭምር ነው።

💬 በእውነታዊ መረጃዎች የዓይናችንን ጤና  እንከባከብ፣ መደበኛ ምርመራ እናድርግ። የተሳሳቱ አስተሳሰቦች የዓይን ጤና ይጎዳሉ።

ምንጮች፦
- World Health Organization (WHO), Eye Care Guidelines 2023
- American Academy of Ophthalmology (AAO), Common Eye Myths and Facts
- Centers for Disease Control and Prevention (CDC), Vision Health Initiative

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

እኛ እንድንበደር ቴሌብር ዋስ ሆኖልናል!

በቴሌብር በኩል እስከ 15 ሺህ ብር ድረስ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ያለማስያዣ መበደር የምንችል ሲሆን በ60 ቀን ተመላሽ እናደርጋለን። ደሞዛችንን በቴሌብር የምንቀበል የቴሌብር ደንበኞች ደግሞ የደሞዛችንን 4 እጥፍ ድረስ መቀበል እንችላለን!

እንቆጥብም ካልን በየቀኑ በሚታሰብ ወለድ አልያም እንደምርጫዎ ያለወለድ የምንቆጥብበት 'ስንቅ' ቀርቦልናል።

*127# ደውለን ወይም ቴሌብርን በስልካችን በዚህ ሊንክ
https://bit.ly/telebirr_SuperApp ጭነን ስንመዘገብ እንዲህ ነን!

#ደንበኛ_ስንሆን_እንዲህ_ነን
#ስንመዘገብ_እንዲህ_ነን
#ስንጭን_እንዲህ_ነን
#ስናስጀምር_እንዲህ_ነን

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

የዓለም ጤና ድርጅት በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለተከሰተው በሽታ አፋጣኝ ምላሽ ለመስጠት 300 ሺ የአሜሪካ ዶላር ድጋፍ መደረጉን አሳወቀ።

የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባጋሩት መግለጫ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የተከሰተውን ቫይራል ሄሞራጂክ ፊቨር (Viral Hemorrhagic Fever) ህመም አፋጣኝ ድጋፍ ለመስጠት ከአለም ጤና ድርጅት የአደጋ ጊዜ ፈንድ 300 ሺ የአሜሪካ ዶላር ድጋፍ መደረጉን ይፋ አድርገዋል።

ዳይሬክተሩ የዓለም ጤና ድርጅት አስፈላጊ በሚሆንበት ጊዜ ሁሉ ድጋፍን ለማሳደግ ዝግጁ መሆኑንም አክለው ገልጸዋል።

መግለጫው ድንበር ዘለል የሆነ ስርጭትን ለመከላከል በኢትዮጵያ እና በደቡብ ሱዳን የሚገኙ የዓለም ጤና ድርጅት ቢሮዎች በቅንጅት እየሰሩ መሆኑን ጠቁሟል።

የዓለም ጤና ድርጅት በሽታው ወደ ተቀሰቀሰበት አካባቢ ባለሞያዎችን ጨምሮ የተለያዩ መድኃኒት እና ቁሳቁሶችን መላኩንም ዳይሬክተሩ አሳውቀዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" ወንጀል ፈጻሚው በፈጸመው ወንጀል ልክ ተመሳሳይ የሆነ ፍርድ እንዲሰጠው እጠይቃለሁ " - የተማሪ ሊዛ ቤተሰብ

በደሴ ከተማ "ተደፍራና ተገድላ" ተገኘች የተባለችው በዘንድሮው አመት ለምርቃት ስትጠበቅ የነበረችው የሦስተኛ አመት በኮሌጅ ተማሪ ሊዛ ደሳለ ግድያ የተጠረጠረው ግለሰብ በቁጥጥር ስር መዋሉን የደሴ ከተማ ፓሊስ መምሪያ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።

ጉዳዩ በምርመራ ላይ መሆኑን ከዚህ ቀደም ገልጸውልን የነበሩ የፓሊስ አካል ዛሬ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ደግሞ፣ " ሰውየው/ተጠርጣሪው በቁጥጥር ስር ውሏል። ቀጣዩ ሥራ ይቀጥላል "  ብለዋል።

የድርጊቱን ሁኔታ በተመለከተ ዝርዝር ማብራሪያ ስንጠይቃቸውም፣ " ከሳምንት በኋላ ሙሉ መግለጫ ጠብቁ፤ አሁን ብናብራራው የፍትህ ስርዓቱ ይበላሻል " ብለዋል።

" ምርመራው አልቆ የጨመረሻው ውጤት ሲደርስ ሙሉ ማብራሪያ ይሰጣል፤ በመካከል ላይ ካለ ግን ይባላሻል። ወንጀሉ የተፈጸመው ምሽት ላይ ስለሆነ ፓሊስ ጉዳዩን እስከሚጨርስ ድረስ ጥንቃቄ ያስፈልጋል፤ የተጠርጣሪውን ፎቶ ራሱ አለጠፍንም " ነው ያሉት።

የደሴ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ በበኩሉ፣ የተቋቋመው የምርመራ ቡድን ባደረገው የክትትልና ማጣራት " ህዳር 2 ቀን 2018 ዓ/ም ዋና ወንጀል ፈፃሚው በቁጥጥር ስር መዋሉን " ዛሬ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።

ተማሪዋ " መስከረም 28/2018 ዓ/ም የእህቷን የተበላሸ ሞባይል ለማሰራት አምሽታ ወደ ጓደኛዋ ቤት ሰመሀል ዝናቡ  ለማደር ስትሄድ ጭንቅላቷ አንገቷን ከኋላና ከፊት ድብደባ ተፈፅሞባት ወደ ሆስፒታል የሄደች ሲሆን ህይወቷ መትረፍ አለመቻሉ ይታወቃል " ሲልም አስታውሷል።

በተማሪ ሊዛ ግድያ የተጠረጠረው ግለሰብ በቁጥጥር ስር መዋሉን ሰምታችኋል ? ፓሊስ አነጋግሯችሁ ነበር? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ዛሬ የጠየቃቸው አንድ የተማሪዋ ቤተሰብ፣ ተጠርጣሪው መያዙንና ቀጣዩን ሂደት በተመለከተ ፓሊስ እንዳነጋገራቸው ተናግረዋል።

" የኢትዮጵያ ህዝብ በሙሉ እንባ ነው ያነባው፤ እኛ ቤተቦች ደግሞ ደም ነው ያለቀስነውና ወንጀሉን ፈጻሚው አካል በፈጸመው ወንጀል ልክ ተመሳሳይ የሆነ ፍርድ እንዲሰጠው እጠይቃለሁ " ሲሉም ቀጣዩ የፍርድ ሂደት ፍትሃዊ እንዲሆንላቸው ከወዲሁ አሳስበዋል።

‎ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

‎" ያለ ስራ ስነምግባር በስራ ቦታ ባልተገባ መንገድ ሰራተኛን የደበደበ ቻይናዊን ጨምሮ በአራት ሰዎች ላይ እርምጃ ተወስዷል " - የሀዋሳ ኢንዱስትሪያል ፓርክ

➡️ ‎" ልጁ ሕክምና ተደርጎለት በመልካም ጤንነት ላይ ይገኛል "


‎በሀዋሳ ኢንዱስትሪያል ፓርክ የሚሰሩ ሰራተኞች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ባደረሱት ቅሬታ በፓርኩ ውስጥ በተለያዩ ጊዜያት በውጭ ሀገራት ዜጎች አካላዊና ስነልቦናዊ ጥቃት እንደሚደርስባቸው ገልጸዋል።

ባሳለፍነው እሁድም በፓርኩ ውስጥ በሚገኝ 'ቶዮ ሶላር' በተባለ ኩባንያ አንድ ቻይናዊ አንድን ኢትዮጵያዊ ሲደበደበዉና ልጁም መሬት ላይ ወድቆ የሚያሳይ ቪዲዮም ልከዋል።

‎ቲክቫህ ኢትዮጵያም ቪዲዮዉን ከተመለከተ በኋላ የቶዮ ሶላር ካምፓኒ ሰራተኞችንና አመራሮች እንዲሁም የሀዋሳ ኢንዱስትሪያል ፓርክ ሥራ አስኪያጅ ለማነጋገር ሞክሯል።

ሰራተኞች ምን አሉ ?

‎ቲክቫህ ኢትዮጵያ የቶዮ ሶላር ካምፓኒ ሰራተኞች አግኝቶ ለማነጋገር ቢሞክርም ለደህንነታቸው ሲሉ ለጊዜዉ ያለውን ችግር ለማውራት እንዳልተመቻቸው ገልፀው በሌላ ጊዜ መረጃ እንደሚሰጡ ተናግረዋል።

በሌላ መልኩ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የቶዮ ሶላር ካምፓኒ አመራሮችን ለማግኘት ጥረት ቢያደርግም ስልክ ባለማንሳታቸው ለጊዜው አልተሳካም።

ነገር ግን በሀዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ ውስጥ የሚሰሩ ሌሎች ሰራተኞች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ፥ " መብታችን ተረግጦ ነው እየሰራን ያለነው። የዚህ ልጅ ድብደባ በቪድዮ ወጣ እንጂ ሌሎችም ብዙ መሰል ነገር ያጋጥማቸዋል። ለሰው ኃይል ክፍል ሲከሱ ብር ይቀጧቸውና ወደ ስራ ነው የሚመልሷቸው " ብለዋል።

" አቤት የምንልበት አጥተናል ሰው እንዴት በሀገሩ እንዲህ ይደረጋል ? የምንሰራው አስራ ሁለት ሰዓት ነው። በዛ ላይ ክፍያው ልፋታችንን የሚመጥን አይደለም ለመኖር ነው የምንሰራው። እንደዛም ሆኖ ግን ክብር በሌለበት ነው የምንሰራው። ኢትዮጵያውያን ሰራተኞች ድብደባ፣ ስድብ ፣ ማንቋሸሽ ይደርስባቸዋል፤ የጉልበት ስራ እንደ አህያ እያሸከሙ ነው የሚያሰሩት " ሲሉ ገልጸዋል።

" ይሄን ነገር መንግሥት ያውቀዋል ? ከባድ ነገር ነው እየገጠመን ያለው፤ ድምጻችንን ስሙልን " ብለዋል።

‎ፓርኩ ምን ምላሽ ሰጠ ?


ቲክቫህ ኢትዮጵያ ‎በኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን የሀዋሳ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን ስራ አስኪያጅ አቶ ማቴዎስ አሸናፊን አግኝቶ አነጋግሯል።

አቶ ማቴዎስ ፤ " በፓርኩ በሚገኘዉ ቶዮ ሶላር ኩባንያ ውስጥ ተቀጥሮ በሚሰራ  ኢትዮጵያዊ ሞያተኛ እና የውጪ ሀገር (ቻይናዊ) ዜግነት ባለው ሱፐር ቫይዘር መካከል በስራ ቦታቸዉ ላይ በተፈጠረ አለመግባባት የተስተዋለው ጠብና ድብድብ ፍፁም ከስራ መርህ ውጭ የሆነና የፓርኩን መተዳደሪያ ደንብ የሚፃረር ነው ፤ የሚወገዝም ተግባር ነው " ብለዋል።

‌‎ፓርኩ ከኢትዮጵያ ኢንዱትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ጋር በመሆን አስፈላጊውን ማጣራት አድርጎ በሂደቱ ውሰጥ ቀጥተኛ ተሳትፎ የነበራቸውን ሁለት የውጪ ዜጎች ከስራ እንዲባረሩና #ከሀገር_እንዲወጡ እንዲሁም በካምፓኒዉ ውስጥ ያሉ በጉዳዩ ቀጥተኛ ተሳታፊ ያልሆኑ ሶስት አመራሮች ደግሞ ከባድ የፅሁፍ ማስጠንቀቂያ እንዲደርሳቸው መደረጉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስታውቀዋል።

ከዚህ ባለፈ ፥ ‎ካምፓኒው ጉዳዩ በቪዲዮ ከተላለፈው በዘለለ በሰራተኛውና በቅርብ አለቃው መካከል ለተስተዋለው ግጭት መነሻ የነበሩ ምክንያቶችን በመዘርዘር ሁለቱም የተጋጩበትን መንገድ ፤ ኢትዮጵያዊውም የነበረውን ጥፋቶች በመዘርዘር ከስራ እንዲባረር ወስኖ የነበረ ሲሆን ፓርኩ ባስቀመጠው አቅጣጫ መሰረት ወደ ስራ እንዲመለስ መወሰኑን ተናግረዋል።

‎ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ በማህበራዊ ሚዲያዎች የሚዘዋወሩ መረጃዎች መበራከታቸውን በመግለፅ " ልጁ ሞቷል፣ አጥንቱ ተሰብሯል " የሚሉና መሰል መረጃዎች የተሳሳቱ መሆናቸውን ገልጸዋል።

" ልጁ ሕክምና ተደርጎለት በመልካም ጤንነት ላይ ይገኛል " ሲሉ አክለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamilyHawssa

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#Tecno_Spark_40_Pro+

አዲሱ የTecno Spark 40 Pro+ ሁለት የ Dolby Atmos የድምፅ ቴክኖሎጂ የተገጠመላቸው ስፒከሮች ያሉት ሲሆን ሙዚቃ ለመስማት፣ ማህበራዊ ሚዲያ ለመጠቀም፣ ፊልም ለማየት እንዲሁም ኩልል ያለ ጥራት ያለው ድምፅ የሚሰጥ በመሆኑ ስፒከሩ ተመስክሮለታል!!

#Spark40Pro+ #SlimeverStrongForever #TecnoAI #TecnoSpark40Series

@tecno_et

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" እስከአሁን ድረስ ስምንት ሰዎች (08) በበሽታው የተጠረጠሩ መሆኑ ታውቋል " - ጤና ሚኒስቴር

የጤና ሚኒስቴር በደቡበ ኢትዮጵያ ክልል በጅንካ ከተማ ምንነቱ በመረጋገጥ ላይ ያለ የሄሞራጂክ ፊቨር (Hemorrhagic Fever) በሽታ መከሰቱን በቅኝት መረጋገጡን ባወጣው መግለጫ ገለጸ።

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የተከሰተውን የሄሞራጂክ ፊቨር (Hemorrhagic Fever) በሚመለከት የጤና ሚኒስቴርና የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የጋራ ጋዜጣዊ መግለጫ አውጥተዋል።

መግለጫው የተከሰተውን በሽታ " ምንነቱ በመረጋገጥ ላይ ያለ የሄሞራጂክ ፊቨር " ሲል የጠራው ሲሆን እስከአሁን ድረስም ስምንት ሰዎች (08) በበሽታው የተጠረጠሩ መሆኑ አሳውቋል።

ስለ ሞቱ ሰዎች በመግለጫው ያለው ነገር የለም።

የጤና ሚኒሰቴር ከኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት እና ከክልሉ ጤና ቢሮ ጋር በመሆን በደቡብ ኢትዮጵያ ከልል የተመዘገበውን ይህንን የበሽታ መንስኤ ለማወቅ እና ተጨማሪ ስርጭትን ለመግታት እንዲሁም ለመቆጣጠር ፈጣን ምላሽ ሰጪ ቡድን ወደቦታው በመላክ ፦
° የመስከ ግምገማዎች እና የላብራቶሪ ምርመራዎችን
° የማህበረሰብ ቅኝት
° የንከኪ ልየታ
° የቤት ለቤት ልየታ እንዲሁም የህከምና አገልግሎት አሰጣጥን እያጠናከረ እንደሚገኝ አሳውቋል።

በሚመለከታቸዉ የባለድርሻ አካላትና ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ሌላ ተጨማሪ መግለጫ እስከሚሰጥ ድረስ ህብረተሰቡ ህመሙን ለመከላከል የተላለፉ ምክረ ሃሳቦችን እና ጥንቃቄዎችን ተግባራዊ እንዲያደርግ አሳስቧል።

ሚኒስቴሩ ያስተላለፋቸው ምከረ-ሃሳቦች እና ጥንቃቄዎች:-

- በአፍ፣ አፍንጫ እና ሌሎች የሰውነት ክፍሎች የመድማት፣ ትኩሳት፣ ማስቀመጥ እና ማስመለስ ምልከት ሲኖር ወደ ህክምና ተቋማት መሄድና በወቅቱ የላቦራቶሪ ምርመራ ማድረግ፣

- ምልክት ከታየበት ማንኛዉም ሰዉ ጋር ንክኪ በሚኖርበት ጊዜ ራስን የመከላከያ ዘዴዎችን መጠቀም፣

- ሁልጊዜ እጅን በሳኒታይዘር ወይም በውሃና በሳሙና በመታጠብ ማጽዳት፣

ማንኛውም ጤና ተቋም በታካሚዎች ልየታ አካባቢ ልዩ ትኩረት በመስጠት የቫይራል ሄሞሬጅከ ፊቨር (Viral Hemmoragic Fever) መሰል በሸታ መለየት፣ መመርመር፣ ማከም እና ሪፖርት ማድረግ እንደሚያስፈልግ በመግለጫው ጠቅሷል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#ችሎት

የቀድሞው የሰላም ሚኒስትር ዴኤታ እና የኦሮሚያ ክልል ምክር ቤት አባል አቶ ታዬ ደንደአ በዐቃቤ ሕግ ከቀረቡባቸው ሦስት ክሶች ፍርድ ቤት በሁለቱ በነጻ ሲያሰናብታቸው በአንዱ ግን ጥፋተኛ ተብለዋል።

ዛሬ ማክሰኞ ኅዳር 3/2018 ዓ. ም. የአቶ ታዬን ጉዳይ የተመለከተው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ የሕገ መንግሥት እና በሕገ መንግሥት ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎች ችሎት ከቀረቡለት ሦስት ክሶች የጦር መሣሪያ ሕግን በመተላለፍ በቀረበባቸው ክስ ጥፋተኛ ሆነው እንዳገኛቸው ወስኗል።

አቶ ታዬ ነጻ የተባሉባቸው ክሶች " ከጠላት ጋር ማበር " አና የአገር መከላከያ ሠራዊትን ለመምታት " ዝግጅት አድርገዋል " የሚሉት ሁለት ከባድ ክሶች ናቸው።

የመጀመሪያው ነጻ የተባሉበት ክስ፤ "የወንጀል ሕግ 251 ንዑስ ሐ በመተላለፍ ከጠላት ጋር (ከሸኔ እና ከፋኖ ጋር) ተባብረዋል" የሚል እንደሆነ ጠበቃቸው አበራ ንጉስ ለቢቢሲ ተናግረዋል።

ይህ ክስ ከ20 ዓመት እስከ ዕድሜ ልክ ወይም ሞት የሚያስቀጣ እንደሆነ ጠቅሰዋል።

ሁለተኛው ነጻ የተባሉበት ክስ፤ የወንጀል ሕን 257 ንዑስ ሠ በመተላለፍ " መንግሥትን ለመጣል የፕሮፖጋንዳ እና ሌሎች ድጋፎችን ለጠላቶች በማድረግ ግዙፋዊ መሰናዶ አድርገዋል " የሚለው ከ10 ዓመት በማይበልጥ ጽኑ እስራት የሚያስቀጣ እንደሆነ ገልጸዋል።

ጥፋተኛ ሆነው በተገኙበት ሕገ ወጥ መሣሪያ ይዞ በመገኘት ክስ የግራ ቀኝ የቅጣት አስተያየት ለመስማት ለኅዳር 15/2018 ዓ. ም. ቀጠሮ እንደተሰጠ ጠበቃው ተናግረዋል። #ቢቢሲ

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#ETHIOPIA🇪🇹

" በኢትዮጵያ ሕዝብና መንግሥት ላይ እምነት ስለተጣለ እናመሰግናለን " - አምባሳደር ልዑልሰገድ ታደሰ

ኢትዮጵያ ከ50 ሺህ በላይ ተሳታፊዎች የሚታደሙበትን ጉባኤ እንድታስተናግድ ተመርጣለች።

ኢትዮጵያ ከሁለት ዓመት በኋላ የሚካሄደውን የዓለማችን ዋነኛውን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአየር ፀባይ ለውጥ ጉባኤን እንድታስተናግድ ብራዚል ውስጥ እየተካሄደ ባለው የዘንድሮ ስብሰባ ላይ ተመረጠች።

ኮፕ በመባል የሚታወቀውን እና በየዓመቱ ከሚካሄደውን የአየር ፀባይ ለውጥ ጉባኤ በአውሮፓውያኑ 2027 የሚደረገውን "ኮፕ32" ኢትዮጵያ እንድታስተናግድ የተመረጠችው ናይጄሪያን በመብለጥ ነው።

ኢትዮጵያ በአውሮፓውያኑ 2027 የሚካሄደውን ጉባኤ በአዲስ አበባ እንድታስተናግድ የአፍሪካ አገራትን ድጋፍ አግኝታለች።

ኮፕ የሚለው ስያሜ 'ኮንፈረንስ ኦፍ ፓርቲስ' የሚሉት ቃላት ምህጻረ ቃል ሲሆን በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአየር ፀባይ ለውጥ ስምምነት ማዕቀፍ ስር የሚካሄድ የዓላማችን ዋነኛው የአካባቢ ጥበቃ ጉባኤ ነው።

በጉባኤው ከአሜሪካ በስተቀር (አሜሪካ በትራምፕ አስተዳደር ራሷን አግልላለች) መላው የዓለም አገራት እና ሌሎችም በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ተሳታፊዎች የሚታደሙ ሲሆን፣ ወሳኝ ድርድሮች እና ስምምነቶች የሚደረሱበት ነው።

ኢትዮጵያ ይህንን ጉባኤ ለማዘጋጀት መመረጧ በጉባኤው አጀንዳ ላይ እና በማብቂያው ላይ በሚተላለፉ ውሳኔዎች ላይ ከፍተኛ ሚና እንዲኖራት ያደርጋል።

በብራዚል የኢትዮጵያ አምባሳደር ሉልሰገድ ታደሰ ኢትዮጵያ ጉባኤውን እንድታስተናግድ መመረጧን አስመልክቶ ባሰሙት ንግግር " በኢትዮጵያ ሕዝብ እና መንግሥት ላይ እምነት ስለተጣለ እናመሰግናለን " ብለዋል።

ሰላሳኛው የኮፕ ጉባኤ በብራዚሏ ቤሌም ከተማ ውስጥ እየተካሄደ ሲሆን፣ የቀጣዩን ዓመት ጉባኤ አውስትራሊያ እና ቱርክ ለማስተናገድ እየተፎካከሩ ነው። 31ኛውን የኮፕ ጉባኤ አስተናጋጅ በቀጣዮቹ ቀናት ይታወቃል ተብሎ ይጠበቃል።

አሁን ብራዚል ውስጥ እየተካሄደ በሚገኘው ኮፕ 30 ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ ከዓለም ዙሪያ 50 ሺህ በላይ ሰዎች ለመሳተፍ ተመዝግበዋል።

በጉባኤው ላይ፦
- ጋዜጠኞች፣
- የአየር ፀባይ ሳይንቲስቶች፣
- የቀደምት ማኅበረሰብ መሪዎች እና የ195 አገራት ተወካዮችን ጨምሮ ሌሎች በአካባቢ ጥበቃ ላይ ተሳትፎ ያላቸው አካላት ይገኛሉ።

የ2027ቱን ጉባኤ እንድታስተናግድ የተመረጠችው ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው የዛፍ ችግኞችን እየተከለች እና ግዙፍ ታዳሽ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫዎችን እየገነባች ነው። በዚህም በአካባቢ ጥበቃ በኩል ስሟ ግሎቶ ይጠቀሳል።

ይህን መረጃ ሮይተርስን ዋቢ በማድረግ ያስነበበው ቢቢሲ ነው።

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#Tigray

የኢትዮጵያ ገነት ቸርች ሪሊፍ ኤንድ ደቨሎፕመንት የተባለው አገር በቀል የምግባረ ሰናይ ተቋም ከኮምፓሽን ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ ባገኘው የገንዘብ ድጋፍ በትግራይ ለከፋ ሁኔት ለተጋለጡ ተፈናቃዮች 61 ሚሊየን ብር ዋጋ የሚያወጣ የምግብ ድጋፍ በእንዳስላሰ ሽር ከተማ አድርጓል።

የምግባረ ሰናይ ተቋሙ ስራ አስኪያጅ ሊበን ፀጋዬ ፥ " ያደረግነው የእህልና ዘይት ድጋፍ ነው ፤ የስራ አጋራችን ከሆነው ኮምፓሽን ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ በተገኘ የ61 ሚሊዮን ብር ነው ድጋፍ የተደረገው " ሲሉ ገልጸዋል።

በተገኘው የገንዘብ ድጋፍ የተገዛው ድጋፍ ከ17 ሺህ 400 በላይ ለሆነ ተፈናቃዮችና የተቸገሩ ወገኖች የዋለ እንደሆነ አመልክተዋል።

የምግባረ ሰናይ ተቋሙ ከዚህ ቀደም በመቐለና ዓድዋ ከተሞች ተመሳሳይ እርዳታ መስጠቱን መሰል የሰብአዊ ድጋፍ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተቋማቸው ጥረቱን እንደሚቀጥል ቃል ገብተዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

ሁለት ወረዳ ቤተ ክህነቶች የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ያወጣውን የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርት ውድቅ አደረጉ።

ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ፥ " የቀረበው መግለጫ ተንሻፎ የቀረበ ነው፤ የአካባቢው ህዝብም በዚህ አዝኗል " ብለዋል።

የኢትዮጵያ የሃማኖት ተቋማት ጉባኤ አጣሪ ኮሚቴ በአርሲ ዞን ፦
- ጉና፣
- ሽርካ፣
- ሆንኩሎ አቤ፣
- መርቲ ወረዳዎች በቅርቡ የተፈጸሙ ግድያዎችን፣ እገታዎችንና ዝርፊያዎችን በተመለከተ ያካሄደውን የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርት ይፋ ማድረጉ ይታወቃል።

አጣሪ ኮሚቴው በመጀመሪያ ደረጃ የምርመራ ሪፖርቱ የሰሞኑን ግድያ " አንድን ሃይማኖት እና ብሄር ትኩረት ያደረገ አይደለም " ብሏል።

ከሌሎች ወረዳዎች ተለይተው ስማቸው ቢነሳ ተፅእኖ እንደሚደርስባቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የገለጹ ሁለት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የወረዳ ቤተክህነቶች የጉባኤው አጣሪ ኮሚቴ ያወጣውን ሪፖርት ውድቅ አድርገዋል።

ሪፖርት የቀረበበት የአንዱ ወረዳ ቤተክህነት አመራር ምን አሉ ?

" ጮኸታችንን ሰምቶ ወደሚመለከተው አካል ያቀርባል ተብሎ የታሰበ አንድ ትልቅ የሃይማኖት ተቋም 'ግድያው የአንድን ሃይማኖትና ብሄር ያተኮረ አይደለም ' ሚል በግልፅ የወጣውን ነገር አንሻፎ አቅርቧል።

ሰዎቹ በትክክል ' ከቤት ውጡ፣ አገሩን ልቀቁ አይመለከታችሁም፣ ቤቱ ንብረቱ የእናንተ አይደለም ' መባላቸውን ከሞት የተረፉት በሕይወት ያሉት ጭምር እየተናገሩ ብሄር ተኮር አይደለም ተብሎ ሲቀርብ እተገደልን፤ ' ጨክኑ፤ በርቱ ' እንደማለት ነው።

የቀረበው መግለጫ የውሸት ነው፤ እንዲህ እየተገደሉ እየታየ እንኳ ተንሻፎ የቀረበው መግለጫ አካባቢው ላይ ያለውን ህዝብ እጅግ በጣም አሳዝኖታል።

ከዚህ በኋላ ወደ ሃይማኖትም ተቋማትም ወደ መንግስትም አንሄድም ወደ ሰማይ አምላክ ብቻ እንጮኻለን የሰማይ አምላክ ፍርዱን ይስጥ እያልን ህዝቡን እያጽናናን ነው ያለነው።

በአንድ ወረዳ ብቻ በዚህ ዓመት ከ17 ያላነሱ ተገድለዋል (ታግተው ገንዘብ ከሰጡትና ከጠፉት ውጭ) 17ቱም ኦርቶዶክሳውያን ናቸው። ማነው ገዳዩ ለሚለው እሱን አናውቅም። የሞተውን፣ የሚገደለውን ግን እናውቃለን። ይሄ እየታዬ ግድያው አንድ ሃይማኖትና ብሄር ተኮር አይደለም ከተባለ እሺ ምን እንበለው ታዲያ ? " ብለዋል።


የሌላኛው ወረዳ ቤተ ክህነት አካል ምን አሉ ?

" ሪፖርቱን አይተነዋል፤ ውሸት ነው። ከሆነው ነገር በላይ (ከግድያው) የሚሰማው ያማል።

ልዑካኑ ከቀኑ 10 ሰዓት ነው የመጡት፤ ከአካባቢው የተውጣጡ የሀገር ሽማግሌዎች ውይይት ነበረን ከጠዋት እስከ 10 ሰዓት።
በዚህም ግድያው ይቁም፣ በሃይማኖት መካከል የሚነሳው ነገር ከፍተኛ ውድመት ያመጣል የሚለው ሲነገር ተውሎ ማጠቃለያው ላይ የጉባዔው ልዑካን መጡ።

በስብሰባው የተባለው ነገር ነው የተነገራቸው። ለየብቻ ሀሳብ ለማንሳት ሞክረን ነበር፤ ግን እነርሱ (ልዑካኑ) የመዘገቡትን ጥያቄ ለመጠየቅ እንጂ እኛ የምንሰጣቸውን ነገር ለመቀበል ፈቃደኛ አይደሉም። አሁን የተነሳውን ጫጫታ ለመሸፈን የታሰበበት አመጣጥ ነው።

በዚች በጥቅምት ወር የተደረገችውን እንጂ ሌላውን ለማየት አልሞከሩም። 10 ሰዓት መጡ 11 ሰዓት ተመለሱ። ከማንም ጋር አልተገናኙም። ስለዚህ የአካባቢው ችግር በ1 ሰዓት ውስጥ የሚፈታ አይደለም። ማጣራት ከተፈለገ በየክፍሉ ማጣራት ነበር የሚያስፈልገው፤ ማጣራት አልተደረገም።

ደርሶ እንደመመለስ አይነት ነገር ነው የተደረገው። በአመጣጣቸውም፣ በጥያቄያቸም (በልዑካኑ) ቅሬታ አለ። የወጣው መግለጫ ደግሞ እንደተባለው ከሆነ ለምን ዝርዝር አይቀርብም ? እኛ ዝርዝር ልንሰጣቸው ፈቃደኞች ነበርን የሞቱትን። በሪፓርቱ 'ሁሉም ተጎድቷል' የሚል ነገር ነው ያየነው ሁሉም ከተጎዳ ለምን ከሌላኛው እምነት አይጠቀስም ? ሃይማኖት ተኮር ካልሆነ።

በእኛ በኩል ከመስከረም 2 ቀን 2016 ዓ/ም ጀምሮ እስከ ጥቅምት 18 ቀን 2018 ዓ/ም ድረስ በወረዳው ብቻ የተገደሉ 120 ምዕመናን ዝርዝር አለን። ግን ዝርዝሩን ለመውሰድ ፈቃደኞች አይደሉም። ግድያው ሃይማኖት ተኩር ለመሆኑ ማረጋገጫው ይሄ ነው።

በእርግጥ በወረዳ ላይ የወረዳ አስተዳደር፣ ፖሊስ፣ የቀበሌ ሊቀመንበር የሆኑ የሌላ ሃይማኖት አባላት ተገድለዋል ግን እነዚህ ባለስልጣናት ናቸው ሲቪል ነዋሪዎች አይደሉም።

በሌላ በኩል ፋኖ ነው ግድያ የፈጸመው ተብሏል፤ ፋኖ በየት መስመር ነው እዚህ አካባቢ ሊመጣ የቻለው? ፋኖ ያለው አማራ ክልል ድርጊቱ የተፈጸመው አርሲ ነው " ብለዋል።


(ሌሎች በጉባዔው ሪፓርት የቀረበባቸው ቀሪ ወረዳዎችን ሀሳብ ለማካተት ያደረግነው መከራ አልተሳካም። ጥረቱ ይቀጥላል)

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ፤ በወረዳ ቤተክህነት በኩል  ለተነሱት ቅሬታዎች የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የበላይ አካላት እና የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤን በማነጋገር ምላሽ ይዞ ለመቅረብ ጥረት ያደርጋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#MoE

በዛሬው እለት የህዝብ ተወካዮች የሰው ሃብት ልማት ሥራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የትምህርት ዘርፉን የ1ኛ ሩብ ዓመት ሥራ አፈፃፀም ተመልክቶ ነበር።

በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በከፍተኛ ትምህር ተቋማት የክብር ዶክትሬት አሰጣጥን በተመለከተ ችግር የነበረበት በመሆኑ ወጥ አሰራር መከተል በማስፈለጉ የክብር ዶክትሬት አሰጣጥን ሀገራዊ መመሪያ ተዘጋጅቶ ለትግበራ ዝግጁ መሆኑን ገልፀዋል።

ሁሉም የከፍተኛ ትምህርት ተቋም በመመሪያው መሰረት ተፈፃሚ ማድረግ ያለባቸው ሲሆን የክብር ዶክትሬት ማዕረግ የሚያገኙ ሰዎች ዶክተር ወይንም የክብር ዶክተር በሚል መጠሪያነት መጠቀም እንደማይቻል አሳስበዋል።

የከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የክብር ዶክትሬት ማዕረግ ለመስጠት ሀገራዊ እና አለም አቀፍ መስፈርቶችን ማሟላት እንዳለባቸው በመመሪያ መመላከቱን አንስተዋል።

በሙያው የተለየ ስራ ያበረከተ ኢትዮጵያዊም ሆነ ሌላ ዜጋ በመመሪያው የተዘረዘረውን መስፈርት የሚያሟላ ከሆነ የክብር ዶክትሬት ማዓረግ ማግኘት እንደሚችል ጠቅሰዋል። ይሁን እንጂ የተሠጠውን የክብር ዶክትሬት ለመጠሪያነት መጠቀም እንደማይቻል አብራርተዋል።

ትምህርት ሚኒስቴር የክብር ዶክትሬት መስጠት የሚችሉ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን በተመለከተ እንዲሁም የክብር ዶክትሬት የተሰጠው ግለሰብ ዶክተር፣ የክብር ዶክተር እና መሰል መጠሪያዎችን በየትኛውም ግለሰብ ወይም ድርጅት መጠቀም እንደማይችል መመሪያ አዘጋጅቶ ለሚመለከታቸው መላኩ ይታወቃል።

#MoE

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

በታጣቂዎች የሚገደሉት በመንግስት የፀጥታ ሀይሎች ደግሞ ታፍሰው የሚታሰሩበት አሳሳባቢው የአማራ ክልል  የጤና ባለሙያዎች ጉዳይ ! 

የአማራ ክልል የጤና ባለሙያዎች ማህበር ፀሀፊ አቶ ተስፋ መኮነን በክልሉ ባሉ የጤና ባለሙያዎች ላይ በመንግስትም በታጣቂዎችም እየደረሰ ያለው ግድያ፣ እስር አስመልክተው ሰፋ ያለ ማብራሪያ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ሰጥተዋል።

አቶ ተስፋ ምን ምን አሉ ?

" በያዝነው ሳምንት ብቻ 2 የጤና ባለሙያዎች ተገድለዋል።

አንዷ ቤተልሄም አዲስ የምትባል በምዕራብ ጎጃም ዞን በደንበጫ ጤና ጣቢያ በስራ ላይ እያለች ጥቅምት 29/2018 ዓ.ም በታጣቂዎች ተገድላለች። 

ባለፈው ጥቅምት 19/2018ዓ.ም በምዕራብ ጎንደር ዞን ገንደ ውሃ ሆስፒታል የሚሰራ ዶ/ር ዳንኤል ነጋ የተባለ የአይን ስፔሻሊስት በታጣቂዎች ታግቶ ገንዘብ እንደተጠየቀበት ሰምተን ነበር ህዳር 1/2018ዓ.ም መገደሉን ሰምተናል።

ይህ የአንድ ሳምንት አሳዛኝ ክስተት ነው።

ሌላው በምስራቅ ጎጃም ዞን ስናን ወረዳ አርብ ገበያ በተባለ ከተማ ውድነህ አንዳርጋቸው የተባለ ነርስ ባለፈው መስከረም ወር 2018 ዓ.ም በታጣቂዎች መገደሉን መረጃ ደርሶኛል።

ሌላው ደግሞ፥ ከጥቅምት 23 እስከ 27 ድረስ 5 የጤና ባለሙያዎች በመንግስት የፀጥታ ኃይሎች ተይዘው 8ተኛ ፖሊስ ጣቢያ ይገኛሉ።

የዋስትና መብት ተሰጥቷቸው ከእስር እንዲለቀቁ ቤተሰቦቻቸው ቢጠይቁም የሰማቸው አልነበረም። ከሳምንት በኃላም የዋስ መብታቸው ተጠብቆ እላንት ህዳር 3/2018ዓ.ም 4ቱ ዶክተሮች ሲለቀቁ አንዱ ነርስ ግን እስካሁን አልተፈታም።

ታስረው የነበሩ የጤና ባለሙያዎች ስም፦

1. ዶ/ር መኩ ዳምጤ የአዲናስ ጠቅላላ ሆስፒታል ስራ አስኪያጅና እውቅ የቀዶ ህክምና ባለሙያ
2. ዶ/ር ስመኘው ዘላለም የጠቅላላ ቀዶ ህክምና ስፔሻሊስት
3. ዶ/ር ዳምጤ ዘውዴ የጥበበ ግዮን የነርቭ እና የጭንቅላት ቀዶ ህክምና ስፐሻሊስት
4. ዶ/ስመኘው  ተስፋ ከአሜን ሆስፒታል የቀዶህክምና ባለሙያ
5, ታደሰ ዳቤ ነርስ ከአሜን ሆስፒታል አሁን ያልተፈታ

እነዚህ በቅርቡ የተከሰቱ ግድያዎችና አፈሳዎች ናቸው።

እኔም በመንግስት የፀጥታ ኃይሎች ተይዤ ታስሬ ነበር። ባለቤቴ ደግሞ ለዘረፋ በተደራጁ ታጣቂዎች ተይዛ ገንዘብ ከፍለን ነው ያስለቀቅናት።

ነገሩ እንዲህ ነበር ጥቅምት 5/2018 ዓ.ም ሆምላንድ በተባለ ሆቴል ከ5 ባለደረቦቼ ጋር  ስብሰባ አምሽተን ስንወጣ ፖሊሶች መጥተው ያዙን ከዚያም 4ተኛ ፖሊስ ጣቢያ ወስደው አሰሩን። ምን አደረግን ? ብለን ጠየቅናቸው ' ስልጣናችሁን ያለ አግባብ ተጠቅማችኃል ' አሉን የቱን  ስልጣን ? እኛኮ የጤና  ባለሙያዎች ነን የምንሰራውም በማህበሩ ውስጥና ጤና ቢሮ ነው አልናቸው ሁለት ቀን በእስር ካቆዩን በኃላ የወሰዱን ፖሊሶች በመጥፋታቸው ይቅርታ ብለው  ሌሎች ለቀቁን።

እንደገና ሰኔ 25/2017 ዓ.ም ባለቤቴን  ጨምሮ 3 ነርሶች ከፈለገ ህይወት ስፒሻላይዝድ ሆስፒታል አምሽተው በሰርቪስ ወደ ቤታቸው ሲሂዱ ከምሽቱ 2:00 ላይ ታጣቂዎች ከመኪና አስወርደው አግተው ወሰዷቸው። በብዙ ድርድር ብር ከፍለን ነው ያስለቀቅናቸው።

ይህ ጥቃት የሆነው በክልሉ ርዕሰ መዲና ባህር ዳር ነው በወረዳና በዞኖች ላይ ደግሞ በጣም የከፋ እንደሆነ መረጃ ይደርሰናል ግን ለማን አቤት እንደሚባል ግራ ገብቶናል " ብለዋል።

በአማራ ክልል በጤና ባለሙያዎች ላይ እየተፈጸመ ያለው ግድያና አፈና ምን አስከትሏል ?


አቶ ተስፋ መኮነን እንደሚሉት ባለፈው አመት የጥበበ ጊዮን ስፔሻላይዝ ሆስፒታል የቀዶ ጥገና ህክምና ክፍል ዳይሬክተር የነበሩት ዶ/ር አንዱአለም ዳኜ  በክልሉ ርዕሰ መዲና ባህር ዳር ጥር 24/2017 ዓ.ም ከስራ አምሽተው ወደ ቤታቸው  በመጏዝ ላይ እያሉ  በዘራፌዎች  ከተገደሉ በኃላ ከ30 እስከ 40 የሚሆኑ እውቅ የጤና ባለሙያዎች ክልሉን ለቀው ወደ መሀል ከተማ ሂደዋል።

ሰሞኑን በተከሰተው ግድያና እስራትም ብዙ የጤና ባለሙያዎች ክልሉን ለመልቀቅ አኮብኩበዋል።

በዚህም በህክምና እጥረት ህዝቡ እየተሰቃየ ነው። ሆስፒታሎችም የባለሙያ ያለህ እያሉ ነው።

" ሀኪሙስ የትም ቦታ ተዘዋውሮ ሰላም ያለበት ሀገር ሄዶ ተቀጥሮ ይሰራል ህዝቡ የት ይሄዳል ? " ሲሉም ይጠይቃሉ።

" በተለይ በአሁኑ ሰዓት እየተሰቃየ ያለው የገጠሩ ማህበረሰብ ነው ከተሜውስ በአውሮፕላን ተሳፍሮ ሄዶ ታክሞ እየመጣ ነው " ሲሉ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።

ጥቃት አድራሾቹ እነማን ናቸው ?

" እስርን በተመለከተ የመንግሰት የጸጥታ ኃይሎች ናቸው፤ ምክንያታቸው ደግሞ ' ታጣቂዎችን ታክማላችሁ ' በሚል ነው።

ታጣቂዎቹ ደግሞ 'ለብልፅግና ታግዛላችሁ' ነው የሚሉት እንደሚታወቀው ህክምና ሰብዓዊ አገልግሎት የሚሰጥበት ነው ሀኪም ዘርን፤ ቀለምን፤ ሀይማኖትን እንዲሁም ብሄርን ሳይለይ አገልግሎት እዲሰጥ ነው ቃል የገባው ይህንን መንግስትም ታጣቂዎችም መረዳት አለባቸው።

ከሁለቱ ውጭ ያለው ደግሞ የታጠቀ ዘራፈ ቡድን ነው እነዚህን ለህዝብ ቁመናል የሚሉ ሁለቱ ኃይሎች ተባብረው ማጥፋት አለባቸው። "
ማህበሩ ምን እያደረገ ነው ?

" የአማራ የጤና ባለሙያዎች ማህበር ከአማራ የግል ጤና ድርጅቶች ማህበር ጋር በመሆን በጤና ባለሙያው ላይ እየደረሰ ያለው አፈናና ግድያ ይቁም! ህግ ይከበር! ቤተሰቦቻችን የህክምና አገልግሎት ያግኙ ! የሚል ደብዳቤ በመያዘ፦
-ለአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ፅ/ቤት
-ለአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን
- ለአማራ ክልል አስተዳደርና ፀጥታ ቢሮ አስገብተናል።

ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናትንም ለማነጋገር እየጣርን ነው። በቀጣይም ለሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ድምፃችን እናሰማለን " ብለዋል።

ሰሞኑን እንደገና ባገረሸው የሙያ አጋሮቻቸው ግድያና እስር ምን ይላሉ ?

በምዕራብ ጎንደር ዞን ገንዳውሃ ከተማ የገንዳዋ አጠቃላይ ሆስፒታል ሀኪም የሆነውና ስሙ እንዳይጠቀስ የጠየቀን አንድ የጤና ባለሙያ ስራውን እና ከተማውን ለመልቀቅ በዝግጅት ላይ መሆኑን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግሯል።

ይህው የመረጃ ምንጫችን በገንዳዋ አጠቃላይ ሆስፒታል ይሰራ የነበረው እና ሰሞኑን በታጣቂዎች ታግቶ ተወስዶ የቤዛ ገንዘብ የተጠየቀበትና ኃላም ተገሎ ተጥሎ ስለተገኘው ዶ/ር ዳንኤል ነጋ እንዲህ ሲል ተናግሯል።

" ዶ/ር ዳንኤልን የማውቀው ከ2015ዓ.ም ጀምሮ ነው በጣም ስነ ምግባር ያለውና ሙያውን የሚወድ ህመምተኞችን አክባሪ ነው።

ዶክተር ባለትዳርና የአንዲት ሴት ልጅ አባትም ነበር።

ባለፈው ጥቅምት 19/2018ዓ.ም በሆስፒታሉ አቅራቢያ ባለ አንድ ምግብ ቤት እራት እየበላ እያለ ነው ከብዙ ሰዎች መካከል ታጣቂዎች እሱን መርጠው አስነስተው ይዘውት የሄዱት ከዚያም 5 ሚልየን ብር እንዲከፈላቸው ጠየቁ።

ብሩን ማሰባሰብ ተጀምሮ ነበር ቤተሰቦቹ 600 ሺህ ብር ለአጋቾቹ እንደከፈሉ ሰማን ግን ብሩን ከመክፈላቸው በፊት ነው ልጁን ገድለው የጣሉት አስከሬኑ ሲገኝ ያመላከተውም ይህንን ነው። "

ከዶክተሩ እገታ ጋር በተያያዘ እርሱን ጨምሮ 6 የጤና ባለሙያዎች ከጥቅምት 21 እስከ 27 /2018 ዓ.ም ማለትም ለ6 ቀናት ታስረው እንደነበር ይህው የመረጃ ምንጫችን ነግሮናል።

ከሀኪሞች በተጨማሪም 7 በምግብ ቤቱ  አቅራቢያ የሚኖሩ ሰዎች ታስረዋል ብሏል።

የመረጃ ምንጫችን በመተማ ሆስፒታል ከ2015 ዓ.ም ጀምሮ እስከ አሁን ድረስ 5 የጤና ባለሙያዎች ታግተው የተገደሉ ሲሆን 4 የጤና ባለሙያውች ደግሞ ብር ተዋጥቶ ተከፍሎላቸው መለቀቃቸውን ተናግሯል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ባሕር ዳር

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#ፍርድ⚖️

የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 2ኛ የግድያና የከባድ ውንብድና ወንጀል ችሎት የአባተ አበበን ገዳይ ተስፋዬ ሆርዶፋ ላይ የ20 ዓመት ፅኑ እስራት ፍርድ አስተላልፏል።

አባተ አበበ ታህሳስ 7 ቀን 2016 ዓ/ም ምሽት አዲስ አበባ ቦሌ ኤድና ሞል ወረድ ብሎ በሚገኝ አንድ የመዝናኛ ስፍራ አካባቢቢ በጥይት ተመቶ መገደሉ ይታወሳል።

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" 753 ሺሕ 000 ብር ወዴት ገባ ? " - የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ዳር ፓሊ ካምፓስ ተማሪዎች

➡️ " አንዳንድ ተማሪዎች የመረጃ እጥረት ስለነበረባቸው ካፌ እየገቡ ልነበረም። ለዚህ ግቢው ተጠያቂ አይደለም" - የካምፓሱ ተማሪዎች ኀብረት


የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፓሊ ካምፓስ ተማሪዎች ከኪሳቸው አውጥተው ከግቢው ካፌ ውጭ የተመገቡበት የአምስት ቀናት ገንዘብ በትክክል እንዳልተከፈላቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

‎ከጥቅምት 7 እስከ 11 2018 ዓ/ም ድረስ የካፌ አገልግሎት እንደተቋረጠ በማስታወቂያ እንደተነገራቸው ያስረዳው አንድ የግቢ ተማሪ፣ "ጥቅምት 11 ቀን 2018 ዓ/ም ከሰዓት የካፌ አገልግሎት አልተቋረጠም ተባለ። እኛ ግን ለ5 ቀናት የካፌ አገልግሎት እንደተቋረጠ ነው የምናውቀው። አንድ ተማሪ ለ5 ቀን ካፌ አልገባም ማለት በቀን 100 ብር ሲታሰብ በአምስተኛው ቀን 500 ብር ይጠብቃል" ብሏል።

ሌሎች ተማሪዎች በበኩላቸው ይህንኑ ሀሳብ ተጋርተው፣‎ አጠቃላይ የነን ካፌ ተማሪዎች ቁጥር "1,506" እንደሆነ፣ በዚህም አንድ ተማሪ 500 ብር ሲደመደብ፣ ድምሩ 753 ሺሕ ብር እንደሚሆን በመግለጽ፣‎ "ይሄ 753 ሺሕ ብር ወዴት ገባ?" ሲሉ ጠይቀዋል።

የፓሊ ካምፓስ ተማሪዎች ኀብረት ፕሬዚዳንት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ምን መለሰ ?

በዩኒቨርሲቲው የፓሊ ካምፓስ ተማሪዎች ፕሬዚዳንት ቃለዓብ ሰሙንጉስ፣ " እውነት ለመናገር በቀን 7 የተለጠፈ ማስታወቂያ ነበር። በማግስቱ ግን ተማሪዎች 'ብራችን እየገባ አይደለም ካፌ መግባት አለብን' አሉ። የግቢው ኃላፊዎች ተነጋግረው አስገቧቸው " ብሏል።

" ከዚያን ቀን ጀምሮ እንደገና መግባት ትችላላችሁ ተብሎ ማስታወቂያ ተለጠፈ፥ ግን ተማሪው መረጃ እጥረት ነበረበት ሁለተኛ የተለጠፈውን አላዩትም፥ ያዩት ግን ገብተው ካፌ ሲመገቡ ነበር፤ አንዳንድ ተማሪዎች የመረጃ እጥረት ስለነበረባቸው ካፌ እየገቡ አልነበረም። ለዚህ ደግሞ ግቢው ተጠያቂ አይደለም " ሲል አክሏል።

ሲጀመር ለምን ብሩ በወቅቱ አልተላከላቸውም ? ገብተው የተመገቡትስ በቀን ስንት ነው ? የመረጃ እጥረት ካለስ ማሳወቅ የእናንተ ፋንታ አይደለም ወይ ? ስንል ላቀረብነው ጥያቄም፥ " ብሩ ዘግይቶ ነው የሚገባው፤ ፋይናንስ ላይ ችግር ስለሚፈጠር በጣም ቀስ ብለው ነው የሚሰሩት። ከቀን 8 ጀምሮ ገብተው እየተመገቡ ነበር፤ ግቢው እንዳሳወቀ መረጃው አለኝ " ሲል መልሷል።

" ተማሪው እየተመገበ ነበር ስለዚህ ግቢው ያወጣውን ወጭ ሊከፍል አይችልም " ብሏል።

ስለዚህ ተማሪዎች ከቀን 8 እስከ 11/2018 ዓ/ም የግቢው ካፌ ገብተው እየተመገቡ ነበር ባይ ነህ ? ለሚለው ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄም፣ " በደንብ ነው እየተመገቡ የነበረው " ሲል ምላሽ ሰጥቷታ።

ፕሬዚዳንቱ ቀጠል አድርጎም " ነገር ግን የመረጃ እጥረት የነበረባቸው ተማሪዎች ነበሩ፤ ያልተመገቡ ተማሪዎች እንዳሉ መረጃው አለኝ " ሲል በራሱ መስክሯራ።

ነንካፌ ተጠቃሚ ተማሪዎች 1506 እንደሆኑ፣ የ5 ቀናት ገንዘብ ሙሉው እንዳልተከፈላቸው፣ ከቀን 12 በኋላ ቢሆን ለእያንዳንዱ ተማሪ መከፈል ከነበረበት 3,000 ብር የተፈላቸው 1,800 ብር እንደሆነ በመግለጽ፣ " 753 ሺሕ ብር የት ገባ?" የሚል ጥያቄ አላቸው። ለዚህ ያላችሁ ምላሽ ምንድን ነው ? የሚል ጥያቄም ለፕሬዚዳንቱ አቅርበናል።

በምላሹም " እንደ ተማሪ ህብረት ለመጠየቅ ሞክረናል፤ የተማሪ ተወካዮችን ሰብስበን ያለውን ነገር አሳውቀናል። መረጃ ባለማግኘታቸው የተጎዱ ተማሪዎች አሉ። ግቢውም ብሩን ማጣት አይገባውም። ብሩ አልጠፋም በነገራችን ላይ። ስለዚህ ያለን አማራጭ ተማሪውም ግቢው በጣም በማይጎዱበት መልኩ ባላንስ ማድረግ ነበር ከ12 ጀምሮ እንዲከፈላቸው አድርገናል " ብሏል።

አንድ የግቢው ተማሪ ግን፣ "በጣም የሚያሳፍር ስራ ነው እየተሰራ ያለው። በ5 ቀናት ክፍተት የትኛውም ነንካፌ ተማሪ ካፌ አልገባም። ውጭ ነበር ሲጠቀም የነበረው በብድርም በምንም እያደረገ" ሲሉ ከሰዋል።


ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

የኢትዯጰያ ሎተሪ አገልግሎት!

የ1 ሚሊዮን ብር ሽልማት ለእርስዎ!
ከ48 ሠአታት በኋላ የ1 ሚሊዮን ብር ሽልማት፤ ዛሬ ደግሞ ለ 30 እድለኞች ለእያንዳንዳቸው የ1ሺህ ብር ሽልማት ተዘጋጅቷል።
እድልዎን እጅዎ ድረስ አምጥተናል🤳 በእጅ ስልክዎ *8989# በመጫን፣ ወደ www.ethiolottery.et ድረ ገፅ በመግባት፣ በቴሌ ብር ሱፐር አፕ እንዲሁም በነጻ የስልክ መስመር 8989 በመደወል ሎተሪ መቁረጥ ይችላሉ።
መልካም እድል!

#60ሚሊዮን

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#ትኩረት🚨

ሄሞራጂክ ፊቨር (Hemorrhagic Fever ) ምንድን ነው ?

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጂንካ ከተማ ምንነቱ በመረጋገጥ ላይ ያለ Hemorrhagic Fever (ሄሞራጂክ ፊቨር) መከሰቱን የጤና ሚኒስቴር በትላንትናው ዕለት በሰጠው መግለጫ ማሳወቁ ይታወቃል።

ምንነቱ በመረጋገጥ ላይ ያለው በሽታ ምክንያት በጂንካ ከተማ ሁለት የጤና ባለሞያዎችን ጨምሮ በአጠቃላይ ስድስት ሰዎች ህይወት ማለፉን መዘገባችን ይታወሳል።

እስካሁን ስለበሽታው በጤና ሚኒስቴር የተገለጹ መረጃዎች ምንድን ናቸው ?

እንደ ጤና ሚኒስቴር መረጃ እስካሁን በበሽታው ስምንት ሰዎች ተጠርጥረዋል።

ተጨማሪ ስርጭትን ለመግታት እና ለመከላከል እንዲሁም ምንነቱን ለማወቅ የላብራቶሪ ምርመራዎች እየተከናወኑ ነው።

በላብራቶሪ ምርመራ ውጤቱ እና በምንነቱ ዙሪያ እስካሁኗ ሰአት ድረስ ከጤና ሚኒስቴርም ሆነ ከኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የተሰጠ መግለጫ የለም።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቫይራል ሄሞራጂክ ፊቨር ምንድነው ? ምልክቶቹ እና መከላከያ መንገዶቹስ ? በሚለው ዙሪያ የውስጥ ደዌ ስፔሻሊስት እና የተላላፊ በሽታዎች ፌሎ የሆኑትን ዶ/ር ሰላም ቦጋለን አነጋግሯል።

ቫይራል ሄሞራጂክ ፊቨር (Viral Hemorrhagic Fever) ምንድን ነው ?

" ቫይራል ሄሞራጂክ ፊቨር (Viral Hemorrhagic Fever) በተለያዩ  ምድቦች ሚከፈሉ  የቫይረስ አይነቶች ሚከሰት ከባድ ምልክቶችን ያከተተ የህመም አይነት ስብስብ ሲሆን ፦
- ትኩሳት፣
- ደም መድማት፣
- የሰውነት ክፍሎች (ኦርጋኖች) ስራ እክል የእነዚህ ህመሞች ምልክት ነው።

በተለያዩ የቫይረስ አይነቶች ሲከሰት ሚያመሳስላቸው ምልክት እንዳለ ሆኖ የህመሙ መተላለፊያ፣ ክብደት እና መከላከያ እንደየ ቫይረሱ አይነት ይለያያል። "
 
ለቫይራል ሄሞራጂክ ፊቨር መከሰት መንስኤዎች ምንድን ናቸው ?

" ለቫይራል ሄሞራጂክ ፊቨር መከሰት :-
➡️ ኢቦላ (Ebola virus)
➡️ ማርበርግ (Marburg virus)
➡️ Lassa fever virus(ላሳ ፊቨር ቫይረስ)
➡️ ደንጉ (Sever Dengue virus)
➡️ የሎው ፊቨር (Yellow fever virus)
➡️ ሪፍት ቫሊ ፈቨር ቫይረስ (Rift Valley Fever virus)
➡️ ክሪሚየን ኮንጎ (Crimean-Congo haemorrhagic fever) እና ሌሎች ቫይረሶች መንስኤ ናቸው። "

በበሽታው የተያዘ ሰው የህመሙን ምልክቶችስ በምን ያህል ቀናት ውስጥ ማሳየት ይጀምራል ?

" እነዚህ ህመሞች አንድ ሰው ከተያዘ በአማካኝ  ከ2 እስከ  21 ቀን ምልክት ማሳየት ይጀምራሉ። "

በበሽታው የተያዘ ሰው የሚያሳያቸው ምልክቶች ምንድን ናቸው ?

" ሲጀምሩ እንደሌሎች ትኩሳት አምጪ ተላላፊ ህመሞች ፦
• ራስ ምታት፣
• ትኩሳት፣
• ብርድ ብርድ ማለት፣
• ጡንቻ ህመም፣
• ድካም ፣
• ትውከት እና የምግብ ፍላጎት መቀነስ  ያስከትላሉ።

ቀስ በቀስ ከበድ በማለት ደም ከተለያዩ የሰውነት ክፍሎች መድማት ይጀምራል።

እንዲሁም የሰውነት ክፍሎች (ኦርጋኖች) ለምሳሌ ሳንባ፣ ኩላሊት ፣ ጉበት ስራቸው ይዳከማል እንዲሁም ደም ግፊት መውረድና ሌሎችም የሰውነት አካሎች ጉዳትና ሞት ሊያስከትሉ ይችላሉ። "

የበሽታው ክብደት እና የሞት ምጣኔ ምን ይመስላል ?

" የሞት ምጣኔ እንደየ ቫይረሱና ክብደቱ ሲለያይ ደንጉ (Sever Dengue virus) ከባድ ህመም ሳያመጣ ከመዳን እስከ ተወሰነ ሞት ያስከትላል፣ ላሳ (Lassa fever virus) እስከ 20 በመቶ ሞት ሲያስከትል እንዲሁም እነ ማርበርግ ቫይረስ ደግሞ እስክ 80 በመቶ ሞት ሊያስከትሉ ይችላሉ።

ከላይ የተጠቀሱት ምልክቶች በሂሞራጂክ ፊቨር ብቻ ሳይሆን በሌሎች ህመሞችም ምክንያትም ሊከሰቱ ይችላሉ ለምሳሌ ከባድ ወባ፣ በባክቴርያ የሚመጣ ሴፕሲስ (sepsis)፣ ሜኒንጆኮከስ ተብሎ ሚጠራው ማጅራት ገትር አምጪ ተህዋስ እነዚህን መሰል ምልክቶች ሊያስከትሉ ይችላሉ ስለዚህ የህመሙ ምንነት በምርመራ መረጋገጥ አለበት። "

መተላለፊያ መንገዶቹ አስተላላፊዎቹስ ምን ምን ናቸው ?

" የቫይራል ሄሞራጂክ ፊቨር (Viral Hemorrhagic Fever) መተላለፍያ መንገዶች እንደየ ቫይረሱ ይለያያል።

ቢንቢ (Aedes aegypti ተብሎ ሚጠራው ትንኝ) ፡- ደንጉ (Sever Dengue virus) እና የሎው ፊቨር (Yellow fever virus) ያስተለልፋል።

የለሊት ወፍ  (bat) ፡ ኢቦላ (Ebola virus) እና ማርበርግ (Marburg virus) ያስተላልፋል።

የአይጥ አይነቶች ( rodents) ፦ ላሳ የተሰኘውን ፊቨር ቫይረስ (Lassa) ያስተላልፋል።

መዥገር (tick) :- ክሪሚየን ኮንጎ (Crimean-Congo haemorrhagic fever) የተሰኘውን ያስተላልፋል።

ከላይ የተጠቀሱት የቫይረሱ አይነት እና አስተላላፊዎች ሲሆኑ በተለይ ኢቦላ (Ebola virus) እና ማርበርግ (Marburg virus) በበሽታው ከታመመ ሰው ጋር በሚኖር የቅርብ አካላዊ ንክኪ (ደም ወይም ፈሳሽ) ይተላለፋሉ። "

በበሽታው መያዛችንን ከጠረጠርን ምን እናድርግ ?

" ከላይ የተጠቀሱ ምልክቶች ሲከሰቱ በቶሎ ጤና ተቋም መሄድ ያስፈልጋል።

እነኚህ ህመሞች ሰውነት ላይ ያስከተሉት ጉዳት በተለያዩ ምርመራዎች ይታያል እንዲሁም ትክክለኛ መንስኤው በደም ወይም ሰውነት ፈሳሽ ናሙና ምርመራ መረጋገጥ አለበት።

የህክምና እርዳታ በቶሎ ማድረግ ለማገገም እንዲሁም መተለለፍን ለመቀነስ ይረዳል። "

በበሽታው መያዛችን ከተረጋገጠ ምን አይነት ህክምናዎች ይሰጣሉ ?

" ባለሞያዎች የተለያየ ለምሳሌ ግሉኮስ ወይም እንዳስፈላጊነቱ ደም መስጠት፣ ህመም ማስታገስ፣ ኦክስጅን እንዲሁም መተንፈሻና የኩላሊት ህክምና እንደየ ክብደቱና አይነቱ ያደርጋሉ።

በስፋት ባይገኙም ለተወሰኑት አይነቶች የተዘጋጁ  መድሃኒቶች አሉ።

የቫይረሱን ስርጭት ለመግታት የታወቀን ህመምተኝ ለይቶ ማከም፣ ንክኪን ማስወገድ መሰረታዊ ነው ሌሎች መተላለፍያ ዘዴዎችን መቆጣጠርም ያሻል።

የሎው ፊቨር እና ደንጉ ለረጅም ግዜ ሚታወቁ ክትባቶች አላቸው ኢቦላም ክትባት አለው። "

ዶ/ር ሰላም ስለህመሙ የበለጠ ለማወቅ የህብረተሰብረተሰብ ጤና ኢንስቲቱት እና ጤና ሚኒስተር ስለመንስኤው የሚሰጡዋቸውን የክትትል ውጤቶችን እና መግለጫዎች መከታተል አስፈላጊ መሆኑን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል አሳስበዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" ድምፃችን ይሰማ ፤ ፍትህ እስክናገኝ እንታገላለን ፤ አሁንም ለመብታችን እንሰዋለን ! " - የትግራይ ኃይል አባላት ሰላማዊ ሰልፈኞች

በፀደቀ ደንብ መልስ እንደተሰጠው የተነገረውና በሚድያዎች በይፋ የተዘገበው የትግራይ ኃይል አባላት የመብት ጥያቄ እንደገና አግርሽተዋል።

ዛሬ ሀሙስ ህዳር 4/2018 ዓ.ም ከዓዲግራት ወደ መቐለ የሚወስደው ዋናው የመኪና መንገድ የመብት ጥያቄ ባነሱ የትግራይ ኃይል አባላት ተዘግቶ ውሏል።

የሰራዊት አባላቱ ዛሬ በዓዲግራት ከተማ ዋና ዋና መንገዶች ባካሄዱት ሰላማዊ ሰልፍ ፦
- ደመወዛችንና መሬታችን ይሰጠን !
- መሪዎቻችን ድምፃችን ሰምተው መልስ መስጠት ሲገባቸው ተደብቀውብናል !
- ፍትህ እስክናገኝ እንታገላለን !
- አሁንም ለመብታችን እንሰዋለን !
- ድምፃችን ይሰማ !
- ጥያቄያችን የማይመልስ አይመራንም !

የሚሉና ሌሎች መፈክሮች አሰምተዋል።

" ጥያቂያችን አልተመለሰም የተገባልን ቃል አልተፈፀመም " ያሉት ሰላማዊ ሰልፈኞቹ ከጥዋት ጀምሮ የዘጉት ዋና መንገድ እንዲከፍቱ በአገር ሽማግሌዎችና በከተማው አስተዳደሮች ቢለመኑም የሚመለከተውን አመራር ሳያገኙ አንደማይከፍቱ በመንገር ይህን መረጃ እስከተዘጋጀበት እስከ ቀኑ 11:00 ድረሰ ፍቃደኞች ሳይሆኑ ቀርተዋል።

ከጥቅምት 3- 7/2018 ዓ.ም ለተከታታይ አምስት ቀናት ዋና የመኪና መንገድ በመዝጋት የተካሄደ የትግራይ ኃይል አባላት ሰልፍና ተቃውሞ ተከትሎ የትግራይ ጊዚያዊ እስተዳደሩ የክልሉ የፀጥታ ሃይሎች ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ረቂቅ ደንብ ማፅደቁ ይታወሳል።

የፀደቀው ደንብ መሰረታዊ ፍላጎቶች ፣ የህክምና አገልግሎት ፣ የቤት መስሪያ መሬት ፣ በመንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት የሚሰጥ የክብር አገልግሎት ፣ ትምህርት ስልጠናና ሌሎች ጥቅማ ጥቅሞች ያካተተ እንደሆነ  ዘግበናል።

የፀደቀው የትግራይ ኃይል አባላት ተጠቃሚነት ደንብ ለረጅም ጊዜ ጥናት የተደረገበት ከፀጥታ አመራሮች ውይይት ሲካሄድበት የቆየ ነው ቢባልም ፤ ከአንድ ወር በኋላ የትግራይ ኃይል አባላት ተቃውሞ መልሶ አገርሽቷል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ

@tikvahethiopia            

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

ከዘመን ፈጥነው እንዲራመዱ IPHONE 17 PRO MAX እንሸልምዎት!

ዛሬ የ60 ሚሊዮን ብር ሎተሪ ከሚቆርጡ ደንበኞች መካከል 1 እድለኛ የ IPHONE 17 PRO MAX ባለቤት ይሆናል!

በተጨማሪም ለ 30 እድለኞች የ 1ሺህ ብር እንዲሁም በሳምንቱ መጨረሻ የ 1 ሚሊዮን ብር ሽልማት ተዘጋጅቷል!

ይፍጠኑ ይቁረጡ!

በቴሌብር ሱፐር አፕ፤ www.ethiolottery.et፤ *8989# እንዲሁም 8989 ላይ በመደወል አሁኑኑ ይቁረጡ!

መልካም ዕድል!

የኢትዮጵያ  ሎተሪ አገልግሎት!

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

የንግድ ድርጅቶች ቆጠራ ምን ፋይዳ አለው? 

ከጥቅምት ወር መግቢያ ጀምሮ በሁለት ምዕራፍ እስከ የካቲት 30 ድረስ በአዲስ አበባ ከ5 ሺህ 600 በላይ ባለሙያዎች የሚሳተፉበት የንግድ ተቋማት ቆጠራ መጀመሩ ተነግሮ ነበር።

ቆጠራውን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፕላንና ልማት ቢሮ እንዲሁም የኢትዮጵያ ስታትስቲክስ አገልግሎት በጋራ የሚያከናውኑት ሲሆን ከወረቀት ነፃ በሆነ መንግድ በዲጂታል የሚደረግ ነው።

በዚህ የኢኮኖሚ ቆጠራ ከአንስተኛ ንግዶች እስከ ግዙፍ ተቋማት እንደሚካተቱም ተገልጾ ነበር።

ለመሆኑ የንግድ ድርጅቶች ቆጠራ ምንድን ነው ?

ዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቀቋም አይ ኤም ኤፍ (IMF) የንግድ ድርጅቶች ቆጠራ በአንድ ግዛት ውስጥ በተወሰነ ጊዜ የሚደረግ የተሟላና ስልታዊ (systematic) የንግድ ተቋማት ቆጠራና ምዘገባ እንደሆነ ይገልፃል።

ይህ ቆጠራ የግዛቱን የንግድ መዋቅር እና ክንውን የተመለከተ መረጃ (Data) ያመነጫል።

የንግድ ተቋማት ቆጠራ ጥቃቅን፣ አነስተኛ፣ ከፍተኛ፣ መደበኛና መደበኛ ያልሆኑ የንግድ ድርጅትና እንቅስቃሴዎችን እንደሚያካትት የመንግስታቱ ድርጅት የስታስቲክስ ሥራ ክፍል (Statistics Division/ UNSD) አስቀምጧል።

የንግድ ድርጅቶች ቆጠራ ምን ፋይዳ አለው ?

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፋይናንስና ኢንቨስትመንት ረዳት ፕሮፌሰር የሆኑት ዶ/ር ሰውአለ አባተ የንግድ ተቋማት ቆጠራ ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን የገቢ መጠን ለመለካት እንደሚረዳ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

" በቆጠራው ወቅት የሚሰበሰቡት የተለያዩ መረጃዎች በአገልግሎት አሰጣጥ ወቅት ክፍተቶችን ለመለየት እና አሰራርን ለማሳለጥ ይረዳል… [ቆጠራው] መንግስት ምን፣ እንዴትና መቼ መስራት አለብኝ የሚለውን ለማወቅ ከፍተኛ ግብዓት ይሰጠዋል ፤ የኢኮኖሚው ተዋናዮች የሆኑ ተቋማትን በየፈርጅ በየፈርጁ አስቀምጦ ለመተንነተን እና ለተለያዩ ፓሊሲ ግብአቶች ጠቀሜታ አለው " ብለዋል።

" መንግስት፣ መንግስታዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት የሚያስችለውን ሪሶርስ ለመሰብሰብ የሚችልበት አንዱ መንገድ ኢኮኖሚ ውስጥ አሉ ብሎ ሚያስባቸውን የንግድ ድርጅቶች በአግባቡ ማወቅ ሲችል ነው " ሲሉም ጨምረዋል።

የስታትስቲክስና የጂኦግራፊ መረጃ ባለሙያው አቶ አለሙ ሰለሞን ደግሞ የንግድ ድርጅቶች ቆጠራ በአንድ ሀገር ወይም ከተማ ያለውን የንግድ አይነት ሰብጥር ለመለየትና ለፖሊስ ውሳኔ ግብዓት እንደሚረዳ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልፀዋል።

" ምንድን ነው ተደራሽ የሆነው? ምንድን ነው ችግሩ? የትኛወ ዘርፍ ነው የበዛው፣ በየትኛው ዘርፍ ደግሞ ምን ማድረግ አለበት የሚለውን " ለመወሰን እንሰሚያግዝም ጠቁመዋል።

ዶ/ር ሰውአለ በንግድ ድርጅቶች ቆጠራ አማካኝነት የሚገኘው መረጃ የመንግስትን እቅድ ስኬታማ ለማድረግ ይጠቅማል ይላሉ።

" እነዚህ ዴታዎች በሌሉበት የቢሮ ሥራ ነው የሚሆነው።  ቢሮ ላይ የሚሰራው ዕቅድ ደግሞ ወደ መሬት ሲወርድ ለመፈፀም የማይቻልበት ሁኔታ አለ። የዕቅድ አፈፃፀም ክፍተት የሚመጣው አውዱን እና እውነተኛውን ኢንቫይሮመንት ሳያውቁ ከሚሰሩ ሥራዎች ጋር በተያያዘ ነው " ሲሉም አክለዋል።

በተጨማሪም ግብር መክፈል ያለባቸውን የንግድ ድርጅቶች በአግባቡ ለማወቅ ቆጠራው ይጠቅማል ሲሉ አንስተዋል።

አቶ ዓለሙ ከግብርና ወደ ሌሎች ዘርፎች እየተደረጉ ያሉ ሽግግሮችን ለማወቅ " ቆጠራ ግድ ነው " ሲሉ ገልፀዋል። 

ጨምረው የንግድ ቆጠራ መንግስት ግልጽ የሆነ ለውሳኔ የሚረዳ መረጃ እንዲያገኝ ይረዳል ብለዋል።

" አለበለዚያ፣ ድካሞች በሙሉ ከንቱ ነው ሚሆነው። በደፈናው መመራት ነው ሚሆነው። ዳታ ካልሰበሰበ እያንዳንዱ ነገር በግምት ነው ሚሆነው " ብለዋል።

ዶ/ር ሰውአለ ጥቅሙ ከመንግስት ተቋማት እንደሚሻገር አንስተዋል።

" ቆጣሪ ድርጅቱ ለምን ዓለማ እየቆጠረ ያለው? ምን ለማሳካት ነው የሚለው መሠረታዊ ነገር ሆኖ ይኼ ዴታ ግን ለብዙ ነገር ጠቃሚ ነው። ዴታው ለህዝብ ይፋ የሚሆን ከሆነ ለጥናት እና ምርምር ይሆናል። ለመንግስት ብቻ ሳይሆን ለሌሎች የመረጃ ቋት ሆኖ ያገለግላል " ብለዋል።

ባለሙያዎቹ ቆጠራው ቤት ለቤት የሚካሄድ በመሆኑ አድካሚ እና ውስብስብ ሊሆን እንደሚችል ጠቅሰዋል። 

በቆጠራው እንዲሳተፉ የሚጠበቁ ሰዎች ጉዳዩን ከግብር ወይም ከሌሎች ነገሮች ጋር በማያያዝ የተሳሳተ መረጃ ሊሰጡ ይችላሉ የሚል ስጋት እንዳላቸውም ነው ያነሱት።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

አቢሲንያ ባንክ

ባንካችን ለመቄዶንያ ከ14 ሚሊዮን ብር በላይ ድጋፍ አደረገ

ባንካችን አቢሲንያ ለመቄዶንያ የበጎ አድራጎት ማኅበር  ከብር 14 ሚሊዮን በላይ የገንዘብ ድጋፍ አደረገ።  

የባንካችን ዋና የኮርፖሬት የሰው ሃብት ኦፊሰር አቶ ሰይፉ ቦጋለ በማዕከሉ ተዘዋውረው ባዩት ነገር መደሰታቸውን ገልጸው የ14,488,000.00 (አሥራ አራት ሚሊዮን አራት መቶ ሰማንያ ሥምንት ሺሕ) ብር የገንዘብ ድጋፉን ለማኅበሩ መሥራች እና በጎ አድራጊ አቶ ቢንያም በለጠ (የክብር ዶ/ር) አስረክበዋል።

አቶ ቢንያም በበኩላቸው ድጋፉ የበጎ አድራጎት ማህበሩ በከፍተኛ ደረጃ ገንዘብ በሚያስፈልገው ሰዓት የተደረገ እገዛ መሆኑን ገልጸው በዚህም ባንካችን ላደረገላቸው ድጋፍ በማመስገን ባንካችን አቢሲንያ በየዓመቱ ኅዳር 2 ቀን 2018 በመቄዶንያ የሚታወስ መሆኑን በመግለጽ መሰል ድጋፎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ጠይቀዋል።

የባንካችን አመራሮች እና ሠራተኞች ለአረጋውያን መኖሪያ እና የህክምና ማዕከል ሆኖ እንዲያገለግል ተደርጎ እየተሠራ በሚገኘውን ባለ 15 ወለል ዘመናዊ ህንጻ ተጠልለው ያሉና በማዕከሉ ድጋፍ እየተደረገላቸው የሚገኙ ወገኖቻችንን ተዘዋውረው የጎበኙ ሲሆን ለአረጋውያኑ ልዩ የምሳ ግብዣም አድርገዋል።

በመጨረሻም ባንኩ በቀጣይም ከሰራተኞች በየወሩ ከደሞዛቸው በፈቃዳቸው ከሚያደርጉት መዋጮ ከብር 1 ሚሊዮን በላይ እየሰበሰበ ለማህበሩ ለመስጠት ቃል ገብቷል።

አቢሲንያ ባንክ

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

ጂንካ ከተማ የተፈጠረው ምንድነው?

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አሪ ዞን ጂንካ ከተማ ከሰሞኑን ምንነቱ ባልታወቀ ህመም የአምስት ሰዎች ህይወት ማለፉን ተሰምቷል።

ጉዳዩ በጂንካ ከተማ በነዋሪዎች ዘንድ መረበሽ መፍጠሩን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ካነጋገራቸው ነዋሪዎች ተረድቷል።

ቃላቸውን ለቲክቫህ የሰጡ የከተማዋ ነዋሪ "ሰው ተጨንቆ ነው ያለው ሃዘን እንኳን ለመሄድ ፈርቶ የሚቀርም፣በድፍረት የሚሄድም አለ የመረበሽ ስሜት ውስጥ ነው ያለነው"ሲሉ ሁኔታውን ገልጸዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ባሰባሰበው መረጃ ምንነቱ ባልታወቀ ህመም ወደ ጂንካ ሆስፒታል ገብተው የነበሩ ሦስት ሰዎች ውስጥ አንዱ በሆስፒታሉ ህይወቱ ያለፈ ሲሆን ሁለቱ በሪፈር ወደ ሃዋሳ ሪፈራል ሆስፒታል ሲወሰዱ አንደኛው ታማሚ በመንገድ ላይ ፣አንደኛው ታማሚ ደግሞ ሃዋሳ ሪፈራል ሆስፒታል ከደረሰ በኋላ ህይወቱ ማለፉን ስሜ አይጠቀስ ካሉ እና በጂንካ ሆስፒታል ከሚሰሩ ሃኪም አረጋግጧል።

በጂንካ ሆስፒታል ተኝተው ይታከሙ ከነበሩ እና ሪፈር ከተደረጉት ታማሚዎች ጋር ግንኙነት የነበራቸው ሃኪም እና ነርስም ህይወታቸው ማለፉን ተገልጿል።

ለጊዜው ምንነቱ ባልታወቀው ህመም በአጠቃላይ የአምስት ሰዎች ህይወት ሲያልፍ ጉዳዩ በጂንካ ከተማ ከፍተኛ ጭንቀት መፍጠሩን ቲክቫህ ያነጋገራቸው ነዋሪዎች ገልጸዋል።

ቲክቫህ ያነጋገራቸው በጂንካ ሆስፒታል የሚሰሩ ሃኪም ምን አሉ?

ታመው የመጡት እና የሞቱት በአንድ ቤተክርስቲያን የሚያገለግሉ እና አብረው ይንቀሳቀሱ የነበሩ ሦስት ሰዎች ናቸው።

በአስር ቀናት ልዩነት ትላንት ከትላንት ወዲያ እና ዛሬን ጨምሮ በአጠቃላይ አምስት ሰዎች ሞተዋል።

ህይወታቸው ካለፈው ውስጥ ሁለቱ ከታማሚዎቹ ጋር ንክኪ የነበራቸው በጂንካ ሆስፒታል ይሰሩ የነበሩ ሃኪም እና ነርስ ናቸው።

ሐኪሙና ነርሱ ካለው የስራ ባህሪ አንፃር ቀጥተኛ ንኪኪ ከሰዎች ጋር ቢኖራቸውም የሕመማቸው ምክንያት ከንኪኪያቸው የተነሳ ነው ብሎ ለማለት ትንሽ የጠለቀ ማጣራት ይጠይቃል።

ለጊዜው ምልክቶቻቸው ተመሳሳይ መሆኑ ብቻ አዲስ ወረርሺኝ ነው ለማለት አያስደፍርም።

ታማሚዎቹ ሲመጡ ያሳዩት የነበረው ምልክት የወባ አይነት ምልክት ነበር ፣አንዳንዶቹ ደም በአፍንጫቸው መምጣት እና ማስቀመጥ ምልክቶች ያሳዩ ነበር።

አንደኛው ጂንካ ሆስፒታል ነው ያረፈው፣ አንደኛው መንገድ ላይ አረፈ አንደኛው ደግሞ ሃዋሳ ሪፈራል ሆስፒታል እየተረዳ እያለ አርፏል።

የዛሬ ሁለት ሳምንት አካባቢ አንድ ታካሚ ተመሳሳይ ምልክቶችን አሳይቶ አርፎ ነበር ተረስቶ ከቆየ ከአንድ ሳምንት በኋላ ከአረፈው ሰው ጋር ንክኪ የነበራቸው እነዚህ ሰዎች ምልክቱን ማሳየት ጀመሩ።

ሪፈር የተደረጉት ባለፈው ሳምንት አርብ የነበረ ሲሆን አንደኛው ታማሚ በሆስፒታሉ እያለ ሲያርፍ ሁለቱ ሰኞ እና ዛሬ እሮብ ጠዋት ህይወታቸው አልፏል።

የዞኑ ጤና መምሪያ ለጊዜው ምንም ያወጣው ነገር የለም።

ጂንካ ሆስፒታል ውስጥ እንቅስቃሴዎች አሉ ጉዳዩን ለማጣራት ከክልል ከመጡ ሰዎች ጋር እየሰሩ ነው"ብለዋል።

የአሪ ዞን ጤና መምሪያ ምን ምላሽ ሰጠ?

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የአሪ ዞን ጤና መምሪያን በጉዳዩ ላይ አነጋግሮ  " ጉዳዩ በፌደራል ደረጃ ጭምር መግለጫ የሚሰጥበት ስለሆነ ለጊዜው ምንም መረጃ መስጠት አንችልም" የሚል ምላሽ አግኝቷል።

ዞን ጤና መምሪያው "የላብራቶሪ የናሙና ምርመራው ገና አላለቀም ምርመራ ላይ ስለሆነ ሲረጋገጥ በፌደራል ወይም በክልሉ ደረጃ መግለጫ የሚሰጥ ይሆናል" ብሏል።

ጤና መመሪያው ሁሉም መረጃ ሲጠናቀቅ በፌደራል ወይም በክልሉ በኩል ይፋ የደረጋል ከማለት በዘለለ የምርመራ ውጤቱ መቼ እንደሚገለጽ እና ሌሎች በዝርዝር ጉዳዮች ላይ ተጨማሪ ማብራሪያ ለመስጠት ፈቃደኛ ሳይሆን ቀርቷል።

ቲክቫህ የአሪ ዞን አስተዳዳሪ የሆኑትን አቶ አብርሃም አታን በጉዳዩ ዙሪያ ለማነጋገር ተደጋጋሚ የስልክ ሙከራ ቢያደርግም ስልክ ለማንሳት ፈቃደኛ ሳይሆኑ ቀርተዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#SafaricomEthiopia

እንኳን ደስ አላችሁ! 🎉💵

ሰኞ ህዳር 1/2018 የ11ኛው ዙር ዕድለኞች ዕጣ አወጣጥ በቲክቶክ እና ፌስቡክ ገፃችን ላይ በቀጥታ ስናስተላልፍ በነበረዉ መሰረት የ100,000 ብር ዕድለኞች ከመቀሌ ሆኑዋል።

ማን ያውቃል ቀጣይ እርስዎ ሊሆኑ ይችላሉ! የበሽ ጥቅል እየገዛን እንንበሽበሽ! 🥳🎉🎉

📲 የM-PESA መተግበሪያን አሁኑኑ ያውርዱ፡ https://onelink.to/ewsb22

የቴሌግራም ቦታችን👉🏽 /channel/official_safaricomet_bot

ወደ *777*0# ይደውሉ ወይም በM-PESA የበሽ ጥቅል ይግዙ!

#MPESASafaricom
#furtheraheadtogether
#besh

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#Hawassa

ዳግም የሐዋሳ ከተማ ከንቲባ ሆነው የተሾሙት አቶ ጥራቱ በየነ ፤ የኑሮ ውድነትን እና የስራ አጥነት ችግሮችን ለመፍታ እንደሚሰሩ ቃል ገብተዋል።

ከንቲባ አቶ ጥራቱ በየነ ፤ " የከተማዋን የወደፊት ልማት አጠናክረን በማስቀጠል ለነዋሪዎችና ለእንግዶች ምቹ ለማድረግ መላውን ሕብረተሰብ በማሳተፍ እንሰራለን " ብለዋል።

የሐዋሳን ሰላም በማፅናት የቱሪዝምና የኮንፍረንስ ማዕከል ለማድረግ እንደሚሰሩ ገልጸዋል።

የልማት፣ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመመለስ የኑሮ ውድነትንና የስራ አጥነት ችግሮችን ለመፍታ እንደሚሰሩም ቃል ገብተዋል።

#ENA

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

ሐዋሳ ከተማ አዲስ ከንቲባ ተሾመላት።

የሐዋሳ ከተማ ም/ቤት ዛሬ ባካሄደው አስቸኳይ ጉባኤ አቶ ጥራቱ በየነን የሐዋሳ ከተማ ከንቲባ አድርጎ ሾሟል።

‎አቶ ጥራቱ በየነ ከዚህ ቀደም ከነሐሴ 24 ቀን 2011 ዓ.ም እስከ 2013 ዓ/ም የሐዋሳ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ሆነው ሲመሩ የቆዩ ሲሆን ላለፉት ሶስት ዓመታት ደግሞ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የከተማው ከፍተኛ አመራር ሆነው አገልግለዋል።

በአዲስ አበባ አመራርነት ጊዜያቸውም በአመራር ብቃታቸው ስማቸው ጎልቶ ሲነሳ ቆይቷል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" ያለኝ ብቸኛ ወንድም እሱ ብቻ ነው ኢትዮጵያውያን ወገኖቼ አፋልጉኝ " - ፈላጊ

ከላይ በፎቶው የምትመለከቱት አኩማል አዳም አብዱራህማን ይባላል።

የተወለደው በጃጁ ወረዳ በአርሲ አውራጃ በኮሎባ ካሎ መንደር ነው።

መኖሪያ ቤቱም በዴራ ከተማ 02 ቀበሌ ከመስጂዱል ሰላም (ጎልባ) አቅራቢያ ነው።

በቅርቡ ከ3 ወይም ከአራት ወራት በፊት ከቤት እንዳወጣ እንዳልተመለሱ ፈላጊ ወንድሙ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።

" ያለኝ ብቸኛ ወንድሜ እሱ ነው ፤ ኢትዮጵያውያን ወገኖቼ ወንድሜን አፋልጉኝ " ሲል ጥሪ አቅርቧል።

ይህ ታዳጊ ልጅ ያለበትን የምታውቁ ወይም ያያችሁት በነዚህ የስልክ ቁጥሮች ፦
0941673006
0913882367
0910252367 በመደወል እንዳታስውቁ እንማፀናለን።

@tikvahethiopia

Читать полностью…
Subscribe to a channel