ethiohumanity | Education

Telegram-канал ethiohumanity - ስብዕናችን #Humanity

30703

🔆እየጠየቁ መኖር መልስን፣ መልስን ፈልጎ ማግኘት ዕውቀትን፣ እውቀት ነፃነትን፣ ነፃነት ሙሉ ስብዕናን፣ ሙሉ ስብዕና ሠላምና እርካታን፣ እርካታ ደግሞ ደስተኛ ሆኖ መኖርን ያስገኛል፡፡ አብረን እንደግ !! @EthioHumanity @Ethiohumanity ✍የተሰማቹን አጋሩን! ቤቱ ሁሌም ክፍት ነው፣ሃሳባቹን ፃፍፍ አርጉልን @EthioHumanitybot

Subscribe to a channel

ስብዕናችን #Humanity

<< የሚዋደድ ሰው ሁሉ አንድ አይነት ነገር መውደድ የለበትም... >>

📖መነሻ ሃሳብ :- " ማታ ማታ - ገጽ 110

🔺" ማሰብ ተፈጥሮአዊ ባህሪህ ቢሆንም በማሰብ ላይ ያለህ ብስለት ከሚገለጽባቸው መንገዶች አንዱ ደግሞ ካንተ የተለየ ሀሳብ ሲያጋጥምህ ለሃሳቡ በምትሰጠው ምላሽ(ግብራዊ) ነው ። እምትወደው ሰው የግድ ባንተ ሃሳብ የሚስማማ ወይም አንተ የምትወደውን ብቻ የሚወድ መሆን የለበትም ። እንደዛ አይነት ሰው ከፈለግክ ያንተን ሁሉ አሜን ብሎ የሚቀበል የሀሳብና የፍላጎት_ወዛደር እንጂ አሳቢን አታገኝም ።

❤️የሚዋደድ ሰው ሁሉ አንድ አይነት ነገር በመውደድ አይደለም መዋደዱ የሚገለጸው ። ካንተ ለተለየ ነገር ሁሉ ጥላቻ ከሆነ ምላሽህ በትክክል ማሰብ መቻልህ ጥያቄ ውስጥ ይገባል ። በሃሳብ መፋለስ የልዩነት እንጂ የጥላቻም ሆነ ያለመዋደድ መንስኤም ሆነ ምልክት አይደለም ። አንተ ራስህ በየቀንና በየሰአቱ የምታስባቸው ሃሳቦች ልዩነት ሊኖራቸው ይችላል ግን አቻችለሀቸው እየኖርህ ነው ። ታድያ የሰውን ልዩነት ማቻቻልስ እንዴት ያቅትሀል...…?

ለራሳችን ጥያቄ ሰተነው እንደምድም::

የሀሳብ ልዩነቶችን ለምን በስድብ እናጣጣቸዋለን?…………

ሰዎች እኛ ያልደገፍነውን ስለደገፉ ለምን እንዲያፍሩ እናደርጋቸዋለን?...……"

ፍቅር አሁን !
@keney_serezoch
@EthioHumanity

Читать полностью…

ስብዕናችን #Humanity

#እምወድሽዋ!❤️ ቅዳሜዋ!❤️ሸጋዬ❤️


እንድርያስ ይባላል.... ከወንበሬ ፊት ለፊት ነው የሚቀመጠው ባልደረባዬ ነው ዝምተኛም ተግባቢም ነው....ያነባል ታሪክ ፣ፖለቲካ ፣ ኪነጥበብ ይተነትናል

...አብረን ነው የምንሰራው

ቃል ኪዳን ትባላለች ትህትናዋ ከፍርሃት ጋ የተዋሃደባት ልጅ ነች ፤ በምሰራበት ድርጅት በፅዳት ከተቀጠረች ቆየች.... ያልቆሸሸ ሁለት ልብስ ብቻ እንደምትለብስ አስተውያለሁ . .. .የገንዘብ ውስንነት እንዳለባት ታስታውቃለች

እንድርያስ ለቃልኪዳን ከኔ በተሻለ ያዝንላታል ለሷ እንደሱ ማዘን ስላልቻልኩ እራሴን እወቅሰዋለሁ .....እሱ ከኔ የተሻለ ነፍስ እንዳለው እረዳለሁ!!!

ከዕለታት በአንዱ ቀን የመቶ ብር ኖቶች ፀጉርሽን መሰርያ ብሎ ሲሸጉጥ በጨረፍታ አይቼው አውቃለሁ.... አንገቷን ስብር አድርጋ ተግደርድራ ተቀበለችው። አመሰገነችውም

በልቤ አንተ ከቅዱሳን መሃል ትገኛለህ አልኩት

ከእኔ በተሻለ ይቆረቆርላታል . እሷ ወንበሩን በመወልወል እንዳትደክም ሳትመጣ ሲወለውል አይቸው አውቃለሁ

መልካምነቱ ያደበዝዘኛል

ለእሷ ባለው ቦታ እኔ እራሴ እደስትበታለሁ። የፃዲቅ መልካምነት የሚጀምረው በዙሪያቸው ባሉ ሰዎች ነው።

ከብዙ ጊዜ በኋላ በቀደም ቅዳሜ ደወለችልኝ እንደትንሽ ልጅ ፈራ ተባ እያለች በተሰበረ በለሆሳስ ድምፅ "ላናግርህ ፈልጌ ነበር አለችኝ" .....?መሳቀቋን ላለማድመቅ በቶሎ እሺ አልኳት....ተገናኘን

የለበሰችውን አመድማ ሹራብ እጅጌ ጎትታ ጣቶቿን አልብሳዋለች ። ማድያቷ እንዳ'ፍንጫዋ ከሩቁ መታየት ጀምሯል ። ፊቷ ክስም ፤ግርጥት ብሏል። ልቅም ያለች ወብ መሆኗ ይሄ ሁላ ጉስቁልና አላወደመውም

ይቅርታ በጣም "ከአንተ በላይ የሚቀርበው ሰው ስለማላውቅ ነው"

ዝም ብዬ ተመለከትኳት

* እንድርያስን እንድታናግርልኝ ነው "🙏 ስለምንጉዳይ ???..... አቀረቀረች .... በሆዴ የያዝኩት ልጅ የእሱ ነው አይንሽን ላፈር አለኝ ሳረግዝ ጠላኝ .....

ዞረብኝ ....

አፈጠጥኩኝ......

" አገባሻለሁ ተማሪ እያለ እየመከረ ፣እየወደደ፣ እየተንከባከበ፣ በፍቅር አክንፎ .....በፍቅር አባብሎ .....ስፀንስ ተፀየፈኝ: የደረጃ ልዩነታችን ተገለፀለት ማነሴ ኮሰኮሰው

የትም ስትንዘላዘይ ያመጣሽውን አለኝ😭

አቀርቅራለች

ፀጥታ ሰፈነ .....ቀና ስትል አይኗ በእንባ ተጨማልቋል

*ቢያንስ አባትነቱን ይመንልኝ እኔ ከሱ ውጪ ወንድ እንደማላቅ እሱ እራሱ ምስክር ነው ። ከፈለገ ልጁ የሱ መሆኑን ያስመርምር*
.
.
እንድርያስ እኔንም ነው የከዳኝ ሰውነቴ ውስጥ ድብርት ሲፈስብኝ እየታወቀኝ ነው
በአይኗ ውስጥ በደሏን አይቼ ሰለራሴ... ስለእህቴ .....ስለ ነገ ልጄ.. ስለ ጓደኛዬ .....ውሃ መሳይ ፊቴ ላይ ከአይኔ እየወጣ ሲረማመድ ተሰማኝ
.......

#ማሳሰብያ

የሰይጣን አምሳያ የሆነው ሰው መምጫ መንገዱ መቼ ይታወቃል ።ከሚታዩ መጥፎ ነገሮች መልካም የሚመስሉ
መጥፎ ነገሮች ያከስማሉ
....

ደርባባ ቅዳሚት ትሁንልን!❤️

@EthioHumanity
@EthioHumanity
@Nagayta

Читать полностью…

ስብዕናችን #Humanity

ለጁምኣችን!
💚

በመካ ከተማ አንድ ሰው ግራ ቀኙን እየቃኘ በመንገድ ሲያልፍ አንዲት አሮጊት እርጅና ባጎበጠው እድሜ ባሰለላቸው እጆቻቸው እየተንቀጠቀጠቀጡ ምግብ የሚያበስሉበትን እንጨት ተሸክመው ወደቤታቸው ሊሄድ ሲያጣጥሩ ይመለከታል። በአሮጊቷ ተግባር ልቡ የተነካው ይህ ሰውም በቀስታ ወደሴትየዋ ተጠግቶ « ቤትዎን ያሳዩኝ እኔ ተሸክሜ አደርስልዎታለሁ» አላቸው።
የሴትየዋ ቤት እጅግ እሩቅ ከመሆኑ ባሻገር ጸሀዩ ሲጠብሰው የዋለው አሸዋ ልክ በጋለ ፍም ላይ የመራመድ ያክል እግርን ክፉኛ ይለበልብ ነበር! ጸሀዩዋም መካ ብቻ ጓዟን ጠቅላ የሰፈረች ይመስል እንደእሳት ትፋጃለች። በነፋሱ እየተንሳፈፈ የሚመጣው የአሸዋ ብናኝም ፊትን በሀይል ይጋረፋል! እንግዲህ ይህን ፈተና ችሎ ነው ሰውየው የአሮጊቷን የደረቁ እንጨቶች ለመሸከም የወሰነው
በሰውዬው ድርጊት እየተገረሙና እየተደነቁ ቤታቸው የደረሱት ምስኪኗ አሮጊትም መልካሙን ሰውዬ ትኩር ብለው እየተመለከቱ እንዲህ አሉት ..
«ልጄ ሆይ እንዲያው ባሮጊት አንደበቴ እመርቅሀለሁ እንጂ ላደረግህልኝ ነገር መካሻ ይሆን ዘንድ የምሰጥህ አንዳች የሌለኝ ምስኪን ደሀ ነኝ ልጄ እባክህ ከሰማኸኝ አንድ ምክር ልለግስህ። ወደህዝቦችህ ወደመካ ስትመለስ እዚያ አንድ ነብይ ነኝ የሚል ሙሀመድ የሚሉት ደጋሚ ሰው አለ። በፍጹም እሱን እንዳትከተል እንዳታምነውም!» አሉት።
ሰውዬውም ረጋ ብሎ «ለምን?» ብሎ ጠየቀ!
አሮጊቷም «ልጄ እርሱ መጥፎ ስነምባር ነው ያለው ሲሉ ሰምቻለሁ» ብለው መለሱ።ሰውዬው በሴትየዋ ንግግር ተገርሞ «እኔስ ሙሀመድ ብሆን?» አላቸው። ሴትየዋም የሰሙት ነገር በጣም አስገርማቸው ለካስ ይህ ደግ ሰው ራሳቸው ነብዩ ሙሀመድ (ሰ.አ.ወ) ነበሩ። አስተውሉ ... ነብዩ ለአሮጊቷ ቸርነትን ሲያደርጉ ሀይማኖታቸውን ፈፅሞ አልጠየቁም። ፍቅር የሀይማኖትን ድንበር፣ የዘርና የጎሳን አጥር እንደሚያልፍ ያውቁ ነበርና። ስብከት ያልሰበረውን ልብና ትምህርት ያላንበረከከውን ማንነት ፍቅር ብቻ ትህትናና በጎ ምግባር ብቻ ያንበረክከዋል!

ያማረ ጁምኣ!💚

@EthioHumanity
@EthioHumanity
@Nagayta

Читать полностью…

ስብዕናችን #Humanity

☮ተማሪ ነው ለሱፊው መምህሩ ጥያቄውን ያቀረበው ፡-
‹‹ለመሆኑ ሰው በአምላኩ የሚረካው መቼ ነው?›› የመምህሩ ምላሽ ታዲያ ድንቅ ነው!

💡‹‹በበረከቱ ግዜ የሚያገኘውን ደስታ በመከራው ጊዜ መግለጥ ከቻለ በርግጥም በአምላኩ ረክቷል ማለት ነው››፡፡

❤️በአሁና ደቂቃ ብቻ የተሰጠንን በረከት ብንቆጥር፤ ያለንን መልካም ነገር ብናስተውል ………..
ወደ መሬት ጎንበስ ብለን የምናመሰግንበት አንድ ሺ አንድ ምክንያቶች አሉን!! አንድ ሺ አንድ !!!!

መልካም ዛሬ!!!

💡☮💡☮💡☮💡☮💡☮💡☮💡☮💡☮💡
@EthioHumanity
@EthioHumanity

Читать полностью…

ስብዕናችን #Humanity

https://t.me/joinchat/T2FWFBE_oUNvaHAn

Читать полностью…

ስብዕናችን #Humanity

🔑Conditioned Mind

"It is not because things are difficult that we do not dare; it is because we do not dare that things are difficult." - Seneca
---
🔆በሕንድ መንደሮች ውስጥ ሲዘዋወር የቆየ አንድ እንግዳ ሰው ነዋሪዎቹ ዝሆኖቻቸውን የሚጠብቁበት መንገድ ግራ አጋብቶታል... እጅግ ግዙፍ የሚባሉ ዝሆኖች በቀላሉ ሊበጠሱ በሚችሉ ገመዶች ታስረው በጸጥታ የመቆማቸው ምስጢር እውነትም እንቆቅልሽ ነበር... 'እንዴት ሊሆን ይችላል?'...

⚜️ግራ መጋባቱ እየቀጠለ ሲሄድ ወደ አንድ የዝሆኖች አሰልጣኝ ዘንድ ቀርቦ 'ይህን እንዴት ማድረግ ቻላችሁ?... ዝሆኖች በምድር ላይ በጉልበታቸው ተስተካካይ የሌላቸው ፍጥረታት መሆናቸው ይታወቃል... በዚህ ሰላላ ገመድ ታስረው እንዲቆዩ ያደረጋቸው ምስጢር ምንድነው?...' ሲል ጠየቀ... 'ደህና...' አለ ዝሆኖችን የሚገራው ሰው... በእንግዳው ሰው ጥያቄ አንዳችም መገረም ሳያሳይ... 'በዚህ ገመድ መታሰር የሚጀምሩት ከደረጁ.. ጉልበት ካበጁ በኋላ አይደለም... ገና ግልገል ሳሉ ነው... በዚያ የማለዳ ዕድሜ አሁን የምታየው ገመድ እነርሱን አስሮ ለመቆየት በቂ ነበር... እየቆዩ ሲሄዱ ገመዱን የሚበጥስ አቅም ቢፈጥሩም በልጅነታቸው የታተመባቸው እምነት ግን ዛሬም ገመዱን መበጠስ እንደማይችሉ ይነግራቸዋል'...

🔆ሰውየው በጥበባቸው ተገረመ... ግዙፉን ዝሆን ለማሰር ግዙፍ ሰንሰለት አላስፈለጋቸውም... አስተሳሰባቸውን የሚያስር የማለዳ ልማድ በቂ ነበር... ነገሩ ሰንሰለት ካሰረው ልማድ ያሰረው ነው... 'ልማድ ከብረት ይጠነክራልና' ሼክስፒር እንዳለው...

🔆የኑረት ውበት በየደረሱበት መጠየቅ... የሰውነት ከፍታም በየመዳረሻው መርቀቅ ቢሆንም ከተነገረው ዘሎ 'ለምንና እንዴት' ለማይል አዕምሮ የነበረን ማስጠበቅ እንጂ 'አዲስ ነገር' ማፍለቅ አይሆንለትም... የኑረት ስኬትም ሆነ ውድቀት በእምነትህ ልክ ይገነባል... ቡድሃ "All that we are is the result of what we have thought. The mind is everything. What we think we become. " የሚለውን ቃል በትምህርቱ መጀመሪያ ላይ ያስቀመጠው ለዚሁ ነበር...

💫የምታምናቸውን ነገሮች ለምን እንዳመንካቸው ጠይቀህ ታውቃለህ?... የተቀበልካቸውን እሳቤዎች ልክነት በ'እንዴት' ዓይን መዝነህ ታውቃለህ?... የነገሩህን መጽሐፍትና ያስተማሩህን አንደበቶች መርምረህ ታውቃለህ?... እርግጠኛ ስለሆንክባቸው ጉዳዮች ቢያንስ ለራስህ በታማኝነት የምታቀርበው መልስ አለህ?... ወይስ እንደ ግዙፉ ዝሆን በሰላላ የአስተሳሰብ ወደሮ ታብተሃል?... መጠየቅስ አድክሞህ ይሆን?... Wynn Bullock የተባለ ሰው... "If you stop searching, you stop living, because then you're dwelling in the past. If you're not reaching forward to any growth or future, you might as well be dead." ብሎ ነበር... ሶቅራጥስ በበኩሉ "The unexamined life is not worth living" ብሏል...

✨ከማለዳ ውልደት እስከ ውድቅት ህልፈት የምትሳበው ኑረት ሁለንተናዋ በጠነከረ ልማድ የተቀየደ ነው... ከመጋረጃ ጀርባ ሆኖ የትወናዋን አካሄድ የሚወስንላት መራሔ ተውኔት ልማድ ወይም እምነት ይባላል... የምታምነውን ነው የምትሆነው... ግና.. የማለዳ እምነትህ ረፋድ ላይ... የረፋድ እሳቤህ ቀትር ላይ... የቀትር ግንዛቤህ በተሲዓት... የተሲዓት እውነትህ በምሽት ካልተመረመረ ከልማድ እስረኛነትህ ሳትፈታ ውድቅትህ ይመጣል... "The world is a prison and we are the prisoners.Dig a hole in the prison wall and let yourself out." ይልሃል ሩሚ...

🔑'ተለምዷል' የሚልህ ሰው ሲበዛ ጠርጥር... ቅኝት ነው... 'ምንም ማድረግ አይቻልም' ካለህ ተቃኝቷል በቃ... 'ያለ ነው'... 'ባሕል ነው'... 'አሰራር ነው'... 'እከሌ የሚባል ሰው ወይም መጽሐፍ ላይ ሰፍሯል'... ወዘተረፈዎች የቅኝት መገለጫዎች ናቸው... እዚህ መንደር ውስጥ 'ለምን' ባይ የተገኘለት የእብደት ታፔላ ይለጠፍለታል...

🔆ዕድሜ ልኩን ጥርሱን ሳያጸዳ የኖረ ሰው ለተወሰኑ ቀናት ብሩሽ ተጠቅሞ በመተዉ የአፉን ሽታ ቢያስተውል ሊል የሚችለው አንድ ነገር 'የጥርስ ሳሙና አፍ ያሸታል' ነው... ብሩሽ ከመጠቀሙ በፊት ሽታውን ተላምዶት ስለቆየ 'አፍህ ይሸታል' ቢሉት አይቀበልም ነበር... ብሩሹ ካለመደው ንጽህና በኋላ ግን የትኛውንም ሽታ መረዳት ይጀምራል... ተለማምዶ እስኪዘነጋው ድረስ... ጠረን እንድትለይ የሚረዱህን 'ብሩሾች' ስንቴ 'ያሸታሉ' ብለህ ጣልክ?... ስንቴስ ወደ ቀደመ ሽታህ ተመለስክ?...

ኒቼ በተወልን ድንቅ መስመር የማያልቀውን እንጨርስ... "If you have a 'why' to live by, you can live with any 'how'."

የ'ለምን' እና 'እንዴት' ድፍረት ይስጠን!!
ሰላም...❤️

✍ ደምስ ሰይፉ
✨🔆🔑✨🔆🔑✨🔆🔑✨🔆🔑
@EthioHumanity
@EthioHumanity

@EthioHumanityBot

Читать полностью…

ስብዕናችን #Humanity

ነገ ሸጋዋ ቅዳሚት ነች ዛሬ ዋዜማዋ ነው ለዋዜማዋ እንካቹ.......❤



የ ክ ራ ር ግርፋት እየሰማሁ የቃሎቻችንን ዋጋ እመዝናለሁ። እንደጉም እያየነው ስለተበተነው ትዝታችንም እተክዛለሁ። በእኛ መለያየት መውደቂያ ስለሚያጡ የቀትር ሕልሞቻችንም እጨነቃለሁ። በስስት የተሳሳምንባቸውንም ከንፈሮቻችንን በሚረሱ ሸክም ገላዎቻችን አፍራለሁ።

እ ን ደ ቃ ሎ ቻ ች ን ፥ እንደሕልሞቻችን ዘልዓለማዊነት ቢሆን ጀርባ ስንሰጣጥ ብቻ ሞተናል። ያ ፈጣሪ እንኳ በቃሉ ዓለምን የሠራ ከዘፍጥረት ቀድሞ ዋሾነታችንን አወቀብንና ቃሎቻችንን ኀይል ነሣ። ልንል በምንችለውና ልናደርግ በምንሻው መሀል ፈቃድን ሰጠን። ከእንግዲህ ወዲህ ያልነውን እስከምንሆን ብዙ ፈተና አለብን። ቃላችንና ግብራችን እስከሚገጥም ድረስ ፍጹም መጽደቅ የለም።

ለ ቃ ላ ች ን ስለማንሞት ውብ ሐረጋትን ብቻ የሚተፉ ሕያው መሣሪያዎች ሆነናል። እያንዳንዱ ሰው አዲስ ሰው ሲተዋወቅ በአንደበቱ ከዚህ በፊት ምንም ያለበት አይመስልም። እናም ዛሬም ፥ ነገም ፥ ከነገ ወዲያም እንግዳ ሰው እንቀርባለን። እናሞኛለን ፥ ፍቅርን ከመላመድ እናምታታለን ፥ እንተኛለን ፥ እንከዳለን ፥ ዘወር እንላለን። አዲስ እንለምዳለን። ሌላም ፥ ሌላም ፥ ሌላም።

“እ ን ዲ ህ ብለሺኝ እንዳልነበር
እንዲህ ብለኸኝ እንዳልነበር”

ስ ለ አ ለ ፈ ው ቃል ማን ይጠይቀናል? ቢጠይቀንስ የት ይደርሳል? በመጨረሻስ ሄዶ ሄዶ ምን ያመጣል? እያየን ፥ እየተመለከተን ያልነው ጠፍቶ የወለድነው ያድጋል። ልጃችንም ቢጤያችን ነውና ለቃሉ ሽረት ሞት አያውቅም። ማዕተብ አያሥረውም። ከተማውን ሸንጋይ ሞላው። በተራ ቃሎቻችን ምክንያት ቃላት በውስጣቸው የሚይዙት የትርጉም ልዕልና እየረከሰ ሄደ።

“እወድ ሻ/ሃ ለሁ (!)
አፈቅር ሻ/ሃ ለሁ (!)
እሞትልሻ/ሃ ለሁ (!)
ካን ተ/ቺ በቀር (!)
እስከ ዘልዓለም (!)”

ብ ን ል ም ቃሉ የትርጉም ጥልቀት የለውም። መዋደዳችን ፥ ፍቅራችን ሲፈተን — ዘልዓለማችንም አጭር ነው። አለማፈር ብቻ ሕይወታችንንና ኑሯችንን አራመደው።

እ ና ም ፍቅር ስለማናውቅ ቃሉ አፋችን ላይ አያምርብንም። ባይሆን ዝቅ ያለው ሙዚቃ ድምፁ ከፍ ቢል መልካም ነው።

“አ ራ ት መቶ ፍቅር ፥ ሦስት መቶ ትዝታ
የምችለው ስጠኝ ፥ አቤት የ'ኔ ጌታ”

✍እሱባለውአበራ ንጉሴ


@Ethiohumanity
@Ethiohumanity
@Nagayta

Читать полностью…

ስብዕናችን #Humanity

ለጁምኣችን!
💚

ከዕውቀት አይነቶች በላጩ «ልክህን ማወቅ» ነው እራስን መሆን፤ እራስን መግዛት ፤እራስን ማክበር ፤ራስን ማሸነፍ ፤ እራስን ማወቅ የድሎች ሁሉ መጀመርያ ይመስለኛል።ራስን ማሸነፍ ባላንጣን ከማሸነፍ በላይ ጀግና ያስደርጋል።
ሌሎች ነገሮችን ከመርታት የራስን ፍላጎት ማሸነፍ እውነተኛው ጀግንነት ነው።" አቅም ሲኖርህ ከራስህ ትወዳደራለህ። ራስህን ትተቻለህ። ከትናንትህ መሻልህን ትመዝናለህ። ዋናው የምታስብበት ቦታ ፣ የምትመኘው ሆነ መድረስ የምትፈልግበት ቦታ አለመድረስህ
አያደለም ትልቁ ነጥብ ያለው # የነበርክበት ቦታ አለመገኘትህ ነው። ጉዞ የጀመረ ይደርሳል።ግን እንዳትረሳ "ልክህን ማወቅ ለመንገድህ ጠቃሚ ነው"

@Ethiohumanity
@Ethiohumanity
@Nagayta

Читать полностью…

ስብዕናችን #Humanity

1ኛ ,3ኛ እና 4ኛ ማስረጃዎች (አንድ በል).... ......
አለም ሁሉ አምላክ የለም ወደ ማለት በደረሰበት በዚ ግዜ ሳይታጎል ሚመሰገንበትን ሕዝብናምድርን በተለየ አይን ማየቱ (ሁለተኛ) የአምላካዊ ባህሪውን ይሸረሽረል ብዬ አላምን...... ህጉን የጠበቀ ነውና በረከቱን የሚያገኘው

ሌላው ደግሞ ይኼን ክፉ ወረርሽኝ እንመልከት..... በውጭ ያሉ ወገኖች ሲረፈረፉ የኛ ወገን እንደተፈራው ያልተረፈረፈው በምን ይመስልሀል??? ...ተጠንቅቀን?... ነጭሽንኩርቱ??.. ወይስ... በምትሀት??? .... በአምላክ ልዩ ጥበቃ ነው

ሌላም ላምጣልህ.... እቺ ማነች... ሶርያ.... እና ሌሎችም ማላስታውሳቸው ሀገሮች አይፈርሱም የተባሉት ይኸው ብትንትናቸው ወጥቶ የለም እንዴ... እኛስ እስካሁን በቋፍ ቢሆንም ተ ሰብስበን ያለነው በምናችን ነው??? እጃችንን በምዘረጋለት በጠባቂያችን አይደለምን??

ሰው በሰው ላይ ...መንግስት በመንግስት ላይ... ወንድም በወንድም... ህዝብ በህዝብ...ላይ የመነሳቱ ጉዳይ.... ይህ የጊዜው ጉዳይ ነው.... በመፅሀፉም በግልፅ እንዳለው የግዜው መክፋት የፍፃሜው መቃርቢያ ምልክት ነው....
ደግሞ....
ኢትዮጵያውንያን ከማንም በላይ በማመን ይታወቃሉ! ያመነ ደግሞ ይሆንለታል! ይድናል! በ23 ብንዋጋ ቅዱስ ጊዮርጊስ ይረዳናል ብለው ስላመኑ ቅዱስ ጊዮርጊስ ረዳቸው. ዳኑ! አበቃ!

ይህ የኔ ሀሳብ ነው! ብዙ እውቀት የለኝም ግን የተሰማኝን ከማውቀው አንፃር ገልጫለው... የተሳሳትኩት ካለ ልታረም ዝግጁ ነኝ...

👇👇👇👇

እግዚአብሔር አምላክ ኢትዮጵያን ብቻ ሳይሆን በርሱ አምነው እንደ ሃሳቡ ለሚጓዙ ሁሉ ሊራዳ ይመጣል። ይህን አሳብ በደንብ ለመረዳት የእስራኤልን ታሪክ (በብሉይ ኪዳን ያለውን) ማንበብ ይረዳል። በርሱ ስታምን እርሱም ይታመናል በኃይልህ እና በጉልበትህ ስትታመን ደግሞ ለኃይልህ እና ለጉልበትህ አሳልፎ ይሰጥሃል በጉልበትህ ልክ ትዋጋለህ። እስራኤልን በኤርትራ ባህር አሳልፎ ፈርኦንና ሰራዊቱን ሲያሰጥም ብቸኛው ልዩነት እምነታቸው ነው። እኒህ በርሱ ኃይል እነዚህ በሠራዊት ብዛት ። ከመንገዱ ፈቅ ባሉ ጊዜ ደግሞ ከነርሱ በሚያንስ ሠራዊት ሲረቱም አይተናል። the bottom line is እግዚአብሔር ይረዳል። ይህም ፍትሃዊነቱን አያዛባም። ተበዳይ እና በዳይ መካከል ያለውን ልዩነት እንኳን እሱ እኛ እንረዳለን።

ሌላው መልአክ በፈረስ መጣ የሚል ታሪክ የለንም። ይልቁንም ጊዮርጊስ የሚባል ሰማእት በምልጃው ተራዳን ነው የሚባለው። በነገርህ ላይ እርሱም ሮማዊ ነው። ለዘር ሳይሆን ግን ለእውነት እና ለእምነት አድልቷል። ደግሞ ሰይፍ ይዞ ተዋጋ ማለት ሳይሆን ለሚዋጉት ብርታት ሆናቸው ማለት ነው።
ለምን በሁለተኛው ጦርነት አልመጣም ላልከው ከላይ ያወራነው በደንብ የሚያስረዳ ይመስለኛል። በእምነታችን ልክ ይረዳናል። ትንሽነታቸውን አምነው እርሱን ተስፋ አድርገው ተኳሽ ወታደርና ቀዳሽ ካህን ይዘው በወጡ ጊዜ ጉልበት ሆናቸው። በተቃራኒው የአውሮፓ ኅብረትን አምነው እጃቸውን ወደነርሱ በዘረጉ ጊዜ ደግሞ ለፈቃዳቸው አሳልፎ ሰጣቸው።

Anyways ይህን ሁሉ ለመርዳት አማኝ መሆን ሳያስገልግ አይቀርም።


የሌሎቻቹን መርጠን የምናቀርብ ይሆናል!

@Ethiohumanity
@Ethiohumanity
@balmbaras

Читать полностью…

ስብዕናችን #Humanity

🌊"If you don’t have peace within yourself, it is very difficult to work for peace. [During the Vietnam war] our thinking was, the other person is not our enemy. Our enemies are misunderstanding, discrimination, violence, hatred, and anger. With that kind of insight, we conducted the peace movement.

❄️If you are filled with anger, you create more suffering for yourself than for the other person. When you are inhabited by the energy of anger, you want to punish, you want to destroy. That is why those who are wise do not want to say anything or do anything while the anger is still in them.

🌊So you try to bring peace into yourself first. When you are calm, when you are lucid, you will see that the other person is a victim of confusion, of hate, of violence transmitted by society, by parents, by friends, by the environment. When you are able to see that, your anger is no longer there...”

~Thich Nhat Hanh~
❄️🌊❄️🌊❄️🌊❄️🌊❄️🌊❄️🌊❄️
@EthioHumanity
@EthioHumanity

Читать полностью…

ስብዕናችን #Humanity

• ዛሬ ዕለተ ማግሰኞ የካቲት ፳፫-፳፻፲፫ ለዐዉዳችን እንዲስማማ ኾኖ የቀረ ተንቀሳቃሽ ምስል ነዉ። ቦታዉ ብሔራዊ ሙዚየም ዉስጥ ነዉ ፥ በወፍ በረር የዓድዋ ጦርነትን ለማዉሳት ሙዚየም ዉስጥ ባሉ ጥንታዊ ቅርሶች እና የኅብር የስነ ስዕል ልኺቃን ለሦስተኛ ያበጃጁትን አዉደ-ርዕይ ዋቢ አድርጎ የተቃኘ ነዉ። በነገራችኹ ላይ ይኽ የስነ-ስዕል አዉደ ርዕይ ከየካቲት ፲፱ እስከ መጋቢት ፲፱|፳፻፲፫ ድረስ እነደሚሠነብት ከደጋሾቹ ተነግሮኛል። •

ከ@Mykeyonthestreet የተሰረቀ

Читать полностью…

ስብዕናችን #Humanity

ሰዓት እላፊ!
💚

# መፅሐፍ በዞረበት ከዞርኩኝ ሁለት ወር አልፎኝ ነበር (ለምንም ነገር ስሜት አጥታቹ ታውቃላቹ..?)እንደዛ ነገር! .....አስታወሳችሁት ከዚህ ቀደም ስለዚህ መፅሐፍ አውርቻቹ ነበር #በመሀል ለምን አልደግመውም በሚል መፅሐፉን ደገምኩት በቃ የተለየ ስሜት ነው የተሰማኝ በድጋሚም.......

#ተከተሉኝ
.
.
.


የጊዜ ዑደት የማይለውጠው ነገር አይኖረውም የማይችለው ነገር ቢኖር መሆን ያለብንን እና መሄዳችንን ብቻ ይመስለኛል ከዛ ውጭ ጊዜ ሁሉን እየወለወለ፣ እየከለሰ እያደሰም ሆነ እያፈረሰ እሳቤን፣ማንነትን ያሳየናል።ከጊዜ ጋር የማይበስል፣ በጊዜ እሳት ተጥዶም እንጭጭ የሚሆን አይጠፋም... ላውራላችሁ ያሰብኩት ስለ ጊዜ ሳይሆን ስለ አንድ መፅሀፍ ነው መቼቱን የወያኔ እንቅስቃሴ በተማሪዎች ላይ ሰርፆ በገባበት ወቅት ያረገው ይህ መፅሀፍ ከሀርቡ ተነስቶ በሀሳብ እና በፍልስፍና እየጎለበተ አዲስ አበባ ዩንቨርስቲ የተማሪዎች እንቅስቃሴን ያስቃኘናል....ልጅ ሳለሁ የአንባቢ ጣሪያ የሰብለን እና የበዛብህን ታሪክ ፍቅር እስከ መቃብር ላይ አንቦ መጨረስ ይመስለኝ ነበር(ያኔ ይህ መፅሀፍ ሊነግረን የሚፈልገው ፍቅራቸውን ብቻ ይመስለኝ ነበር) በቃ ፍቅር እስከ መቃብርን ያነበበ ካለ እሱ ለኔ የአንባቢ ጥግ ነበር....ለአሁኖቹ አንባቢያን ደግሞ አደፍርስ ይመስለኛል ገልጦ የጨረሰም አብጠርጥሮ የጨረሰም እኩል የምትወደው መፅሀፍ ሲባል አደፍርስ ይላል ይህን ሊል የሚችለው ግን ንባብን አዘውታሪ ከሆነ ብቻ ነው። ዛሬ ላይ ብዙ በገለጥን ቁጥር ብዙ እንደምናውቅ፤ ብዙ ባሰስን ቁጥር ብዙ እንደምናገኝ አውቃለሁ....አሁን ላወራላችሁ ያሰብኩት ስለ ሚክሎል ነው። ይህን መፅሀፍ ከገዛሁት ከወራቶች ቀደም ብሎም ያህል ቢሆነኝም ሁለቴ ገለጥኩት ሰሞኑን ነው ግን ውስጤን ሰቅዞ ስለያዘው እና ካተረፍኩት ደስታ ብትቃርሙ ብዬ ወደ እናንተ ያሳለፍኩት።


በፍቅር እስከ መቃብር ፣ በአደፍርስ እና አሁን ላወራላችሁ በፈለኩት ሚክሎል ውስጥ አንድ ከማህበረሰቡ በፍልስፍናቸው በእይታቸው እና በክዋኔያቸው አፈንጋጮች የተባሉ ግለሰቦች አሉ....ጉዱ ካሳ፣አደፍርስ እና ጉግሳ ነገር ግን ሁለቱ ከጉዱ ካሳ ጋር ሊያማስላቸው የሚችለው ነገር ማፈንገጣቸው ብቻ ሲሆን ሁለቱን ገፀ-ባህሪያት ግን አንዳንድ ተምሳሎት ስላላቸው ጥቂት ልበልላቸው። ሁለቱም ወጣት ናቸው የተገኙበትን ማህበረሰብ ማንቃት የሚሹ ፤ ሁለቱም ጥያቄ የሚጭሩ ሀሳቦችን የሚያነሱ ፤ ነገር ግን የሚክሎሉ ጉግሳ የማውቀው በቃኝ አይልም ሰው ይሰማል፣ የሚያጋጥሙትን ክስተቶች ችላ አይላቸውም ይማርባቸዋል ፤ በሚያወራው አደፍርስ ሲያደንቁት ሲያሞካሹት ይወዳል ጉግሳ ግን ለሙገሳ ቦታም የለው ፤ አንዳንዴ የአደፍርስ ሀሳቦች ከማህበረሰቡ ሲወርድ(ሲቀል) ይታያል ፤ አደፍርስ መስጠትን እንጂ መቀበልን የህይወቱ ኡደት ውስጥ አልከተታቸውም ምን አልባት ሀሳቦችን ተቀባይ እንዲሆን በጉግሳ የህይወት እንቅስቃሴ ላይ የተሳሉት ይህን ባህሪ ስላደሉት ይሆናል መሬት ወርዶ ከመሀይሙ፣ ከእብዱ፤ ከሴተኛ አዳሪው ይስማማል ይማራል....የልጅነት ፍልስፍናውን በአባቱ ቅኝት ምንም የሚያቅትህ ነገር የለም፣ ሁሌም ቢሆን ከቀልብህ ምከር እያሉ የቃኙት ወጣት የዩንቨርስቲ ተማሪ በንባብ ያካበተውን ወደ ውስጥ ተመልካችነት ክህሎት አንድ እብድ ጋር ያደርሰው እና ያለምክንያት መኖር ክልክል ነው የሚል ፍልስፍና ይቸረዋል....ምርጥ ስነ-ፅሁፍ፣ ቆንጆ የሀሳብ ፍሰት እና የህይወት ፍልስፍና በአንድ ጥራዝ ታትመው ቀርበዋል!!!


አስቸኳይ የንባብ እርምጃ ይወሰድበት!!!!! እውነት አንብቡት ትወዱታላቹ!!


@Ethiohumanity
@Ethiohumanity
@Nagayta

Читать полностью…

ስብዕናችን #Humanity

#እምወድሽዋ!❤ቅዳሜዋ!❤ ሸጋዬ❤


፩ .
ሰዓዲ ይቀጥላሉ

"ከፀደይ ደመና አንዲት የዝናብ ጠብታ ወደ ምድር ወደቀች - ሰፊውን ባህር ስታይ በሀፍረት አቀረቀረች :: እንዲህም አለች :- " ባህሩ ሁሉ በሞላበት ፤ እኔ የት ነኝ ?በእርግጥም በህለውና የለሁም ልበል እንጂ ! "

በሀዘን ስታንጎራጉር በነበረበት ወቅት ነው አንድ የባህር ኦይስተር [Oyster] ወደ ሆዱ ውጦ ያስቀራት ፤ እጣ ክፍሏም ከትንሽ የዝናብ ጠብታ ወደ ክቡር ታላቅ የከበረ - ማዕድን ወደ ዕንቁነተ ቀየራት :: "

"ይሄው ነው" ይላሉ :- "አየህ ትሁት ነበረች ፥ ተከበረች ፤ ያለ መኖርን በር አንኳኳች ፥ ራሷን አሳነሰች ህልው የክቡራን ፅዋ - ተርታ ተቸራት :: "

፪.
አሁንም ሰዓዲ ይቀጥላሉ
ቀዘል አርሰላን ብርቱ የቤተ-መንግስት አጥር ነበረው - ቁመቱ ከ አልወንድ ተራራ የሚስተካከል [alofty mountain situated in Hamden , north-west of Isfahan] :: ከግንብ አጥሩ ውስጥ እንደ ሙሽራ ፀጉር በአፀደ - ፅጌያቱ ውስጥ እየተጠማዘዙ የሚዘልቁ ጎዳናውች ሞልተውታል ፤ በውስጧ ያሉ ኖሪዎቿ ሁሉ ያላንዳች ስጋት የተጠበቁ ነበሩ ::

ቀዘል በአንድ እለት - አንድ ጠቢብ መንገደኛ ያገኝና ይጠይቀዋል - ባንዳች የኩራት መንፈስ

" ከዚህ በፊት ይህን የመሰለ ብርቱ ግርማም የግንብ አጥር በተጏዝክበት ሁሉ አይተህ ታውቅ ይሆን ?"

" በእርግጥ ግሩም ነው !" ብሎ መለሰና :- " ነገር ግን አንዳች ብርታት እንደ ጎደለው አስባለሁ ፤ ካንተ በፊት የነብረው ንጉስ እጅ ላይ እንደ ነበር ሳስታውስ ፣ አሁንም ካንት በኇላ በሚነግሰው እጅ ላይ መውደቁን ሳስብ፣ ከዛም ደግሞ የነገሰው ንጉስ ከተስፋህ አፀድ ውስጥ ያሻውን ፍሬ ሲቢላ ይታየኝና - እውንትም አንዳች ጉልበት ፥ የሚመክትበት የተነሳው ነው እላለሁ :: "

In the estimation of the wise , the world is a false gem that passes each moment from one hand to another .

፫ .
አንድዎን የወሎ ሼኽ አንድ ያዲስ አበባ ሰው ሊኻድማቸው ወስዳቸው አሉ :: አሉ ነው መቼስ

ሁሉ ሁሉ ቀረበ ፣ ተበላም ተጠጣም :: ዱዓ ተያዘ ::

"ሼኾቹ እንግዲህ ያማረ ሀብት ፣ ያማረ መሬት ፣ ያማረ ቦታ ነው 'ምሻ በሉ ዱዓ ያርጉልኝ " አለ ከፊት ሆኖ እያያቸው

"እንግዲህ " አሉ :- " እንግዲህ አላህ ታንዱ ወስዶ ቲያበቃ ላንዱ ነው 'ሚሰጥና .. " እንዳሉ ሳያስጨርሳቸው

" ኧረ እነ ሸኽ እኔ የራሴን ነው 'ምፈልገው "

ቆጣ ብለው መለሱ :-

" ኧረግ ታያ ላንተ ተብሎ አዲስ መሬት አይዘረጋ !"

ምንጭ -Sa'adi collected works (Delphi classics)

@Ethiohumanity
@Ethiohumanity
@balmbaras

Читать полностью…

ስብዕናችን #Humanity

ለጁምኣችን
💚

የሀይማኖት መብት ሳይከበርላቸው በሀገራቸው እንደ ሁለተኛ ዜጋ እየታዩ የሀይማኖት፣የኢኮኖሚ እና የመሳሰሉት ጥያቄ እያለባቸው....ስለ ሀገራቸው ክብር የንጉሱን ጥሪ ተከትለው ለዘመቱት የሙስሊም ገበሬዎችና የጦር አበጋዞች እንዲሁም ለሁሉም የአድዋ ዘማቾች ክብር ለነሱ!

ክርስትያኑ ንጉሥ ነገሥት በማርያም እየማለ ተከተሉኝ ያለውን አዋጅ እና የዘመቻ ጥሪ ተቀብሎ የሃይማኖት ልዩነት ሳይገድበው ለእናት ሀገሩ እና ለራሱ ክብር ሲል የተዋደቀው ይህ ሙስሊም የእግረኛ እና ፈረሰኛ ጦር የሀገራችንን ዳይቨርስቲ ደመቅ አድርጎ ከሚያሳዩ ምንጊዜም ከማይረሱ ሁነቶች ውስጥ የሚመደብ እና ክብር የሚገባው ነው።

#ሙስሊሞቹ የጦር አበጋዞች እና ዓድዋ

በተለያዩ ጠሀፊወች በተደጋጋሚ እንዳስተዋልነው በታላቁ የአድዋ ጦርነት ለድሉ ከፍተኛውን ድርሻ ያበረከተው በራስ ሚካኤል ዓሊ ሥር የዘመተው የፈረሰኛ ጦር ነበር፤ በሌላ ግንባር ሲዋጉ የተማረኩት የጠላት ወታደሮች ሳይቀር የሚወረወረውን የፈረሰኛው ጦር ሚና እጅጉን የላቀ መሆኑን ሳይዘነጉ ቃላቸውን ሰጥተዋል። ይህ ጦር በዓድዋ ጦርነት ወቅት ከንጉሠ ነገሥቱ ምኒልክ በእስከ ቀኝ በኩል ተሰልፎ የጠላትን ጦር እንዳልነበር ያደረገ እና ውሽመጣቸውን የቆረጠ ነበር። በጦርነትም ጄነራል አልበርቶኒን ሊረዳ የመጣውን በጄነራል ዳቦርሜዳ የሚመራውን ሙሉ ብርጌድ ለወሬ ነጋሪ ሳያስቀር የደመሰሰው ይኼ ፈረሰኛ ሰራዊት ነው። የጄነራል ዳቦርሜዳ ሬሳ እንኴን አልተገኘም፤ ምንም ምርኮኛም አልነበረም። እንደሚታውቀው ይኼ ጦር Proper Wollo ከሚባለው የዛሬው ደቡብ ወሎ ክፍል የተውጣጣ በአብዛኛው የእስልምና ተከታይ የነበረ የገበሬ ወታደር ሲሆን በሙስሊም የጦር አበጋዞችም ይመራ ነበር።
.
ከታዋቂወቹ ከእነዚህ ሙስሊም ጦር አበጋዞች ዋናዋናወቹ የእርቄው ገዢ የሞሀመድ ቃንቄ ልጅ ደጅ አዝማች ይመር ሞሀመድ፣ የዓሊ ቤት ገዥ ራስ በሽር፣ የኮሬብ ገዥ ደጅ አዝማች ሊበን በሽር በጉልህ ስማቸው የሚነሳ ነው። አንዳንድ የውጭ ሀገር የታሪክ ጠሀፊወች ሀገራችንን ከውጭ ሆነው ክርስትያን ነገሥታቱን ብቻ በማየት በርካታ ሙስሊም ማህበረሰብ መኖሩን በመዘንጋት በጣፏቸው ማስታወሻወች ይኼን የእስልምና ተከታይ የዓድዋ ዘመቻ እግረኛ እና ፈረሰኛ ጦር በዓድዋ ላይ ያደረገውን ተጋድሎ ለክርስትያን አገር የተከፈለ መስዋትነት በማለት ድሉን ለማጥበብ ይሞክራሉ። ክርስትያኑ ንጉሥ ነገሥት በማርያም እየማለ ተከተሉኝ ያለውን አዋጅ እና የዘመቻ ጥሪ ተቀብሎ የሃይማኖት ልዩነት ሳይገድበው ለእናት ሀገሩ እና ለራሱ ክብር ሲል የተዋደቀው ይህ ሙስሊም የእግረኛ እና ፈረሰኛ ጦር የአገራችንን ዳይቨርስቲ ደመቅ አድርጎ ከሚያሳዩ ምንጊዜም ከማይረሱ ሁነቶች ውስጥ የሚመደብ እና ክብር የሚገባው ነው። ዓድዋ ከተካሄደ ከሁለት ዓመት በኋላ የትግራዩ ራስ መንገሻ ሲያምጥ ከራስ መኮነን ጦር ጋር ተቀናጅቶ በቀላሉ ራስ መንገሻን በቁጥጥር ሥር ያዋለው በእነ ራስ በሽር እና ፊታውራሪ ሥራህ ብዙ የሚመራው ይኼው ጦር ነበር።
.

ሸጋ ጁምኣ!💚

@Ethiohumanity
@Ethiohumanity
@balmbaras

Читать полностью…

ስብዕናችን #Humanity

ለምሽታችን!
❤️💪✌️


ሰብዓዊነት የገዘፈበት የፍትህ ኮከብ!


ምነም እንኳን የአርጀንቲናዊ ተወላጅ ቢሆንም እሱ ለኔ አገር አልባ የዓለም ነው። እሱ ብዙ ነው ፊዚስት፣ፀሀፊ፣አስተማሪ፣ዲፕሎማት፣
የጦርሀይል አዛዥ እና የመብት ተሟጋች ነው ። ይህ ሰው ማነው
ስመ ገናናው ዓለማቀፋዊው የነጻነት ፋኖ ተዋጊ .....ኤርኔስቶ ቼ ጉቬራ
ያላደለው በቀበሌ ፤ በወረዳ ፤በብሄር ፤በሃይማኖት ተሰባጣጥሮ በጎጥ ተተብትቦ
ይጣመዳል ይቧቀሳል የኔ ጀግና ኤርኔስቶ ቼ ጉቬራ ለዘመዶቹ ለሰው ልጆች ዘብ ይቆማል
ይህ ሰው ቅዱስ ነው።ቅድስና ማለት ህይወትቱን ሙሉ ለሰው ልጆች ነፃነት መታገል
ብሎም አንድያ ነፍሱን መገበር አይደለምን ?ካለምንም ስስት ማንነትን ዘርን ሳይቆጥር ሰው
መሆን ክብር ነው ብሎ ለሰው ልጆች ነፃነትን ሊለግስ አቅም አልባዎችን አለሁላቹ እሚል
ለኔ ይህ አለማቀፍ የነፃነት አርበኛ ቅዱሴ ነው።


አለም ህዝቦቿ ሁሉም ሰዎች በእኩልነት እና በሰላም ይኖሩ ዘንድ ለማየት ተመኘ
ህልሙንም እውን ለማድረግ ጣረ ይህ ክንፍ አልባ በምድር የተመላለሰ መልአክ ነው።
እውነተኛ ኮሚኒስት ነው ኮሚንዝም የአለም ማህበረሰብን ወደፊት እሚያስጉዝ እና አዲስ
ማህበረሰብን ለመፍጠር ያስችላል ብሎ ለሰው ልጆች እኩልነት ለማምጣት ከጨቋኞች ጋ ታገለ ማን ?....ዶክተር ኤርኔስቶ ቼ ጉቬራ የአለም ሰዎች በሰላም የመኖር እና ያለመኖር እጣ ፈንታ በልእለ ሃያል አገሮች መውደቅ ፍትሃዊነት የገደለው ነው ያለው ኤርኔስቶ ቼ ጉቬራ ወደ ሰሜን አፍሪካ አቀና በአልጄርያ
እርእሰ ከተማ በአልጀርስ ንግግር አደረገ ቋንቋው ሁሉ ጭቆና ፤ ግፍ ፤በደል ይቁም ነው ።


ይህ ፍትሀዊ የፍትህ ተወርዋሪ ኮኮብ
በምድር እነሆ ላይፈዝ በሰው ልቦች ደሞቆ እና ህያው ሆኖ አልፏል።
# ስለአለማቀfዊነት ! ስለ ሰውነት ጥግ ሳስብ አእምሮዬን ላይ ድቅን የሚልበኝ አንድ ሰው
ነው. ....Che Guevara
ገፁ ሰውነትን የሚያገዝፍልኝ አርማ ነው!!! አለማቀፋዊነት ዜማ የሚያቀነቅን ሰንደቄ
አድራጓቱ ከመረዳት አቅም በላይ ጥልቅ የሰውነት ትርጉምን ተሸክሞል።
ህልመኛም ጭምር ነው 1956 ስምንት ሆነው ከሜክሲኮ ተነስተው የገዜው አንባገነኑን
የባቲስታ መንግሥት ለመገልበጥ ወደ ኩባ አቀኑ ለስምንት
በኩባ ጫካዎችም የጉሬላ ውጊያ ጀመሩ
አምባገነኑ የባቲስታ መንግሥት የመጣል ትግሉም ቼ ወሳኝ ሚና ተጫውቶ በድል
ተጠናቀቀ። ይህ ጀግናዬ ማለም ብቻ ሳይሆን መተግበርም ይችልበታል።
በተተኪው የካስትሮ አስተዳደርም የካስትሮ ቀኝ እጅ ሆኖ እስከ ኢንዱስትሪ ሚኒስቴርነት ድረስ ላልወለደው የኩባ ህዝብ አገለገለ።ምከንያት እሱ ዘመዶቹ የሰው ልጆች ናቸውና ።
ቼኮ ከጨቋኝ ሃያላን ጋ ሲታገል ከተጨቆኝ ጋ ሲያብር ኖሯል የእውነት!!እንደምን ሰው
ከተሸናፊ ጋር በፍቅር ይወድቃል ??
ቼ!! መለክያው እኩልነት ነበር ተጨቆኝና ጨቆኝ የሌለበት ምድር ለመፍጠር ።
ዛሬ የERNESTO CHE GUEVERA መፅሀፍ ባአሜሪካ ሳይቀር በአለም መፅሀፍት ቤቶች
ይገኛል የቼ ምስል ያረፈበት ሰአቶችን ቲሸርቶች በሺዎች ይቸበቸባሉ የላቲን አሜሪካ ተማሪዎች ጠዋት ጠዋት እነደ ብሄራዊ መዝሙር ቼ እንወድሀለን ቼ አንተን እንወርስሀለን
እያሉ ያዜማሉ።


ቼ የፍትህ ተወርዋሪ ኮኮብ ነው !!❤️

@Ethiohumanity
@Ethiohumanity
@balmbaras

Читать полностью…

ስብዕናችን #Humanity

#ዛሬ ሽቅርቅሯ ቅዳሚት ነች..❤ አንድ የቻናላችን ቤተሰብ የሆነች እንዲህ አለችኝ.... በእርግጠኝነት እንደኔ ይሄ ነገር የሚሰማቸው ፣ ግራ የሚያጋባቸው ፣ የተጎዱበት ......ህመሜ ህመማቸው ይኖራሉ እና ይሄን እዚህ ቻናል ላይ ለጥፍልኝ አለችኝ.....#ከዚህ በታች ያለውን ስሜቷን ህመሟን ግራ መጋባቷን እንዲህ አስቀምጣዋለች......#ምናልባት ይሄን የምታነቡ ቤተሰቦች እናተም በዚህ ነገር ውስጥ ናቹ ወይንም አልፋችሁት ይሆናል........ተጋበዙልኝ🙏🙏

👇👇👇



በቃ አንዳንዶች አሉ
.
.
ፍላጎታቸው በትክክል ምን እንደሆነ የማይገቡህ::
የትውውቃችሁ መጀመሪያ አከባቢ ጥሩ ይሆኑልህና ከትንሽ ግዜ በኋላ
የሚቀየሩብህ::አንተን የፍቅር ስሜት ውስጥ ከከተቱህ በኋላ ከነሱ ተመሳሳይ ስሜት
ስትፈልግ የማይመልሱልህ::
.
.
...በቃ አንዳንዶች አሉ!
.
.
ካንተ ጋ መሆን እየፈለጉ ነገር ግን በህይወቴ ሌላ ሰው ቢመጣስ ብለው ወይም ደግሞ
ባለፈ የፍቅር ህይወታቸው ፍራቻ ፍቅርህን የማይቀበሉ::የማይሸሹህ!..የማይቀረቡ!..ሄዱ
ስትላቸው የሚመጡ!..መጡ ስትላቸው የሚሄዱ::
.
.
በቃ አንዳንዶች አሉ!
.
.
ሌላ ሰው እስከሚተዋወቁ አንተን እንደ ባጣ ቆየኝ የመጠቀሙ!
.
.
በቃ አንዳንዶች አሉ!
.
.
ሁሌ አንተ ቀድመህ መልዕክት እንድትልክላቸው ወይም ደግሞ እንድትደውልላቸው
የሚፈልጉ!አንተም አያስችልህም መልዕክት ትልካለህ!..ትደውላለህ!...እንደ ነገሩ
ያዋሩሀል!..ግን ደግሞ ብልጦች ናቸው!...ጨርሰህ እንድትለያቸው ስለማይፈልጉ ተስፋህን
ሙሉ ለሙሉ አይነጥቁህም!..ጭላንጭል ያስቀሩልሀል!..አንተም የቀረህን ጭላንጭል
ተስፋ ይዘህ አብረሀቸው መንገድ ትቀጥላለህ!
.
.
የሆነ ሰዓት ይሰለችሀል!ልትደውልላቸው ስልክህን ታነሳና መልሰህ
ታሰቀምጠዋህ!..ከራስህ ጋ ብዙ ትታገላለህ!..በመርሳትና በፍቅር ስሜት መሀል ሆነ
ለረጅም ግዜ ዝምምም ትላቸዋለህ::
.
.
የዚህን ግዜ የነሱ ተራ ይጀምራል!..እያንዳንዷ የተሰማህ ስሜት የሰማቸዋል!..እያንዳንዷ
ያመምህ ህመም ያማቸዋል!...ይቁነጠነጣሉ!..አስር ግዜ መልዕክት
ይልኩልሀል!...ይደውሉልሀል!...ቀን ሙሉ ያስቡሀል!
.
.
በቃ አንዳንዶች አሉ!...
.
.
ፍቅር ስትሰጣቸው ጀርባ ሰጥተውህ ስትርቃቸው የሚከተሉህ!
.
.
ስታዋራቸው ዝም ብለው ዝም ስትላቸው የሚያዋሩህ!.!
.
.
ግራ የተጋቡ!የተወሳሰቡ..በትክክል ፍላጎታቸው ምን እንደሆነ የማትረዳቸው!....
.

✍ፀዲ

ሀሳብ ካላቹ ....ማካፋል ትችላላችሁ 🙏

ሽብርቅርቅ ያለች ቅዳሜ!❤

@EthioHumanity
@EthioHumanity
@Nagayta

Читать полностью…

ስብዕናችን #Humanity

✨ውበትን ማድነቅ

🔆አለምን የናቀ አንድ መነኩሴ ከሌሎች መነኩሴዎችጋር አብሮ በመንገድ ሲሄድ እጅግ አብዝታ የተዋበች ቆንጆ ሴት አይኑ ውስጥ ትገባለች፡፡ መነኩሴውም በሴቷ ውበት እጅጉን በጣም ከመደነቁ የተነሳ አይኑን ከሷ ላይ መንቀል ጭራሽ አቃተው፡፡ ይህን ድርጊቱን የተመለከቱ አብረውት የነበሩት ሌሎች መነኩሴዎች በድርጊቱ በአፍረት ተሞልተው ተጠጉትና፡-

✨‹‹ወንድማችን አንተ አለምን እንደኛ የናቅህ መነኩሴ ሆነህ ሳለ በሴት ልጅ ውበት እንዲህ ተደንቀህ ፈዘህ ስናስተውልህ አዝነናል፡፡ አለማዊ ድርጊት እየፈፀምህ መሆንህን አላስተዋልክምን?››በማለት ይጠይቁታል፡፡

🔆‹‹ወዳጆቼ በዚህች ቆንጆ ሴት ውበት ውስጥ እየተመለከትኩ የማደንቀው ውበትን እንዳሻው እየለዋወጠ በስራው የሚደሰተውን ፈጣሪዋን እንጂ እሷን አልነበረም፡፡ አይኖቼ የተዋበን ስጋ ሳይሆን የተዋበ ነገር የሚፈጥረውን ፈጣሪ ለማየት እንደተሰሩ አምናለሁ፡፡ በዚያም የተዋበን ነገር መፍጠር የሚችለውን የአምላክ ችሎታ ሥጋ ለብሶ አየዋለሁ መደነቄም በዚህ የተነሳ ነው፡፡››በማለት መለሰላቸው፡፡

✨በውበት ውስጥ የምናደንቀው የተፈጠረውን ነገር ብቻ ሳይሆን ከበስተጀርባው ሆኖ ያንን የተዋበ ነገርን የፈጠረውንም ማድነቅ ከቻልን በርግጥም ታላቅ ፀጋና ጥበብ ከኛ ጋር ነው፡፡

ውብ አሁን!!!❤️

✍ነፀብራቅ ብርሀኔ
✨🔆✨🔆✨🔆✨🔆✨🔆✨🔆✨🔆
@EthioHumanity
@EthioHumanity

Читать полностью…

ስብዕናችን #Humanity

🌗"ትጋት የተስፋ ልጅ ናት።"

🌗 "ዛሬ ላይ ሆኜ ሳስበው በሕይወቴ ውስጥ መልካም ነገሮች ወይም ስኬት ብዬ ከማስባቸው ውስጥ ማስተርስ ዲግሪዬ ወይም ዶክትሬት ዲግሪዬ አይደለም፡፡ ልጆቼ፡ ትዳሬ፡ ቤቴ ናቸው! በሕይወቴ ትልቁ ቁም ነገር ትልቁ ስኬት እነርሱ ናቸው! እናም አሁን ሳስበው የተጓዝኩበት የሕይወቴ አቅጣጫ ትክክል ነበር፡፡ አካሒዴም በእኔ ምኞት እና መምህሬ ባሰበልኝ ሳይሆን ፈጣሪ በመረጠልኝ ስለነበር በጎ መሆኑን የኋላ ኋላ ተገንዝቢያለው፡፡

🌙እናም በሰዎች ዘንድ ተስፋ የሌለን ብንመስልም እንኳን ዋናው ነገር በፈጣሪ ዘንድ ያለው ተስፋችን ነው፡፡ ሕይወት ጠመዝማዛም ብትሆን ውብና ተስፋን የተሞላች ናት! በዚህ ዓለም ሁሉም ነገር አበቃ አከተመ! ባልንበት ጊዜ የሚቀጥል የተሻለ እድል! የምናውቀውና የተለመደው በር የተከረቸመ ቢመስልም ወለል ብሎ የሚከፈት ሌላ በር ዙሪያችን! ጭው ያለ በርሃ ቢሆንም የለመለመ መስክ የሆነ ስፍራ ላይ እንዳለ ተምሪያለው፡፡

🌗ዕድል ፊቷን ያዞረችብን በመሰለን ጊዜም ቢሆን እንኳን አብዝቶ በትጋት መጓዝ እንጂ ተስፋ መቁረጥ አይገባም፡፡ ትጋት የተስፋ ልጅ ናት። ተስፋ ደግሞ በእኛ እና በፈጣሪ መካከል የእምነት ድልድይ ስለመኖሩ ማረጋገጫ ነውና! "

🗞ከሰበዝ መጽሃፍ የተመዘዘ/ገጽ 97/

ጣፋጭ እንቅልፍ❤️❤️
🌗🌙🌗🌙🌗🌙🌗🌙🌗🌙🌗🌙
@EthioHumanity
@EthioHumanity

Читать полностью…

ስብዕናችን #Humanity

ሰዓት እላፊ!
💚


"ሌሎችን በማፅናናት የተዋጣላቸው ሰዎች ራሳቸውን ማፅናናት ግን አይቻላቸውም"

ጊዜው 94 ዓመታትን ወደ ኃላ ይወስደናል... በወቅቱ አንድ ራሺያዊ ከያዘው ድብርት እና ጭንቀት እንዲገላግለው ምክር ፍለጋ ወደ ሳይካትሪስት ይሄዳል... ዶክተሩም አስፈላጊውን ምርመራ ካደረገ በኃላ እንዲ ሲል ምክርን ለታማሚው ይለግሳል...
"አሁን ካለህበት ለመውጣት አስጨናቂ እና አሳዛኝ ከሆኑ ነገሮች መራቅ ይኖርብሃል... ይህ በዕለት ተዕለት ህይወትህ እንደ ልማድ ካደረከው ንባብ ላይም ጭምር ይሁን... አስጨናቂ ፣ ዘግናኝ ፣ አስፈሪ እና አሳዛኝ ታሪክ ካላቸው ንባቦች መራቅ አለብህ... በምትኩም አስደሳች እና አዝናኝ (Comic Stories) ማንበብ አለብህ ለምሳሌም የሚካኤል ዙሽንኮ (Mikhail Zushenko) ፁሁፎችን አንብብ "
ይሄን ጊዜ ታማሚው ለዶክተሩ የሰጠው ምላሽ ዶክተሩን አስገረመው
"እኔኮ ሚካኤል ዙሽንኮ ነኝ"

ለፁሁፉ መጀመሪያ የተጠቀምኩት የ Albert Hubbard አባባል ይህን የ ሚካኤል ዙሽንኮን ታሪክ በትክክል ገላጭ ነው
Those who are good at comforting and comforting others often fail to console themselves...


➬ ሰላም እደሩ!💚

@EthioHumanity
@EthioHumanity
@Nagayta

Читать полностью…

ስብዕናችን #Humanity

☯ ደስታችሁ በግልፅ የሚታይ ሀዘናችሁ ነው ። ሳቃችሁ የሚመነጭበት የዓይናችሁ ጉድጓድም አብዛኛውን ጊዜ በራሳችሁ እንባ የተሞላ ነው ። ከዚህስ ሌላ እንዴት ሊሆን ይችላልን? ....

💙 << ሀዘን የበለጠ ጠልቆ በውስጣችሁ በተቀረፀ ቁጥር የበለጠ ደስታ ማግኘት ትችላላችሁ . . .

💜<< ደስ ሲላችሁ ዘልቃችሁ ወደ ልባችሁ ውስጥ ተመልከቱ ። የዚያኔ ደስታን እየሰጣችሁ ያለው ያ ሀዘን ሰጥቷችሁ የነበረ ነገር ብቻ እንደነበር ትደርሱበታላችሁ . . .

☯ << ሀዘን ባጠላባችሁ ጊዜም እንደገና ወደ ልባችሁ ውስጥ ጠልቃችሁ ተመልከቱ ። አሁንም በእውነቱ የምታለቅሱት በዚያ ደስ ሲያሰኛችሁ በነበረው ነገር መሆኑን ትገነዘባላችሁ . . .

💙<<አንዳንዶቻችሁ <ሀዘን ከደስታ ያይላል> ትላላችሁ ። ሌሎቻችሁ ደግሞ <የለም የሚያይለው ደስታ ነው> ትላላችሁ ። እኔ ግን የማይነጣጠሉ መሆናቸውን እነግራችሁዋለሁ . . .

💜 የሚመጡትም አብረው ነው ። አንዱ ለብቻው ገበታችሁ ላይ ሲቀመጥ ፣ ሌላኛው በአልጋችሁ ላይ መተኛቱን አስታውሱ . . .

☯እውነት እውነት እላችዋለሁ ፣ ልክ እንደ ሚዛን በሀዘናችሁና በደስታችሁ መካከል ተንጠልጥላችሁዋል ። ሳታጋድሉ ሚዛናችሁን ጠብቃችሁ የምትቆዩት፣ባዶ በሆናችሁ ጊዜ ብቻነው ።
✍ካህሊል_ጅብራን

ውብ አሁን❤️
☮💜☯💙☯💙☯💙☯💙
@EthioHumanity
@EthioHumanity

@EthioHumanitybot

Читать полностью…

ስብዕናችን #Humanity

እምወድሽዋ!❤ ቅዳሜዋ!❤ሸጋዬዋ❤


ፌቨን ትባላለች ፤ ፍቅረኛዋን ትወደዋለች ። ሁሌ በትንሹም በትልቁም ታነሳዋለች ፤ ከእለታት በአንዱ እለት ምኑን በደንብ ትወጂለታለሽ ???አልኳት

እ.............የምወድለት

ለኔ ያለውን ግዙፍ ፍቅር ፤ በየስፍራው በየጊዜው ይዳስሰኛል ። ሲፈልገኝ ፤ሲቀና፤ ሲጠረጥረኝ ፤ ለኔ ያለውን የፍቅር አሻራ በነካሁት እና ባየሁት ቁጥር እወድዋለሁ።

የለም

በደንብ የምወደው መልካምነቱን ነው ። በዙርያዎቹ ያሉቱን ሰዎች ፤ሲቆረቆርላቸው ፤ሲጠቅማቸው፤ሲሞገትላቸው ።ለተጠቃ ድምፅ ሲሆን እንድወደው አድርጎኛል ።

ኖ ......እሱም አይመስለኝም

ሲወስበኝ ያለውን ጀብደኝነቱ ነው የምወደው ። ወሲብ ላይ ያለው ወኔ ድፍረት እና ብልግናውን ነው የምወድለት ።

እሱም ብቻ አይደለም !?

ለአምላኩ ያለውን ታማኝነት፤ሃቀኝነቱን ለሚያምንበት ነገር የሚሄደውን ርቀት፤ ብቻውን የመቆም አቅሙን ፤ ሁሉም ታዝቦት ላገኘው ሰው ሁሉ ትክክል ነኝ እያለ ሙሾ አለማውረዱን ነው የምውድለት !!

ኖ ሳቁን ነው

ደመቅ ብሎ ለዛ ያለው ሳቁን ነው የምወድለት ። ያቺ ልቤን የምታርደው ሳቁን ነው የምወድለት ። ያቺ ከልቡ ሲስቀው ብቻ የሚስቃትን ሳቁን ነው የምወድለት ።

ኖ .....የለም

ሲያወራ የሚያወናጭፈው አለንጋ ጣቱ ናቸው የሚስቡኝ ። አወራሩ ጀንተል ብሎ በስሜት ቃል አጣጣሉ ነው የሚማርከኝ

እ..... ይሄ ን ብቻ ግን አይለም የምወድለት

ያለውን Commitment ። ከብዙ ሰው ጋር ሆ አለማለቱን ነው !! ከመዘባረቁ በፊት ስለሁኔታው ለመረዳት አጠያየቁን ፤ አነባበቡን ነው የምወድለት
.
.
ግን ምክንያቴ ነው ብዬ ከዘበዘብኩት በላይ አስሬ የማጣቅሰው ምክንያት ። የመንሰፍሰፌ ምንጭ ምክንያት አንድ ይመስለኛል .........የኔ ስለሆነ( ።)


የኔ ስለሆነ ነው የሚተችበትን ሳይቀር የማቆለባብሰው

ከካደኝ ፤ከተወኝ፤ ከጠላኝ፤ ሀይማኖተኝነቱን አክራሪ እለዋለው፤ ጠያቂነቱን መንቻካ እላለሁ፤ መልካምነቱን ብኩን ማለቴ አይቀርም ።

ማስታወሻ
ከውበት በላይ ፍቅር ያሱባል !!!


የተገማሸረ ደርባባ ቅዳሜ ይሁንላችሁ !❤

@Ethiohumanity
@Ethiohumanity
@Nagayta

Читать полностью…

ስብዕናችን #Humanity

በዲግሪ የተመረቀ/ች
3 አመት የስራ ልምድ ያለው/ት
ብዛት 1
ላይሰንስ ያለው/ት

የስራ ቦታ እሪቼ ባቡር ፌርማታ መስከረም ማዞሪያ የድሮው መስከረም ሆቴል ፊት ለፊት

@Nagayta

Читать полностью…

ስብዕናችን #Humanity

❤️የፍቅር ቦታው ልብ ነው። ልብ ደግሞ ንፁህ ወርቅ ነው። ፈጣሪ በመለኮታዊ ሃይሉ ያነጠፈው፤ ያብረቀረቀው ወርቅ ቢኖር ልብ ነው።

❤️የፍቅር ፀዳል ውበት የሚንፀባረቀው በልብ መስታወት ውስጥ ነው። ነፀብራቁ፣ ደግሞ፣ በፈጣሪ ፍቅር፣ ይገለፃል።

ውብ አዳር❤️

@EthioHumanity
@EthioHumanity

Читать полностью…

ስብዕናችን #Humanity

ለጠየቅነው ጥያቄ .....ከተሰጡን መልሶች መካከል......👇👇👇



Zenit Simeneh:👇👇

እነሱም ፩ አድዋን ተዋግተን ያሸነፍነው መልዕክ በፈረስ ላይ ሆኖ በጎራዴው የጣልያኖችን አንገት እየቀላልን ነው ብላቹ ታምናላችሁ? በደንብ አምናለሁ ይሄ ሀሳብ እኛ ኢትዮጵያዊያን ብቻ ሳንሆን የዛኔ የተዋጉት ጣልያኖች እንዴት ነበር ውጊያው ተብለው ሲጠየቁ የመለሱት መልስ ነው በዛን ጊዜ የነበረ ጋዜጣ አንብብ ቃልበቃል ታገኘዋለህ። የቤት ስራ ይሁን ሲቀጥል አንተ ስታስበው እውነት ዘመናዊ መሳሪያ እስከ አፍንጫው የታጠቀ እና ሙሉ ወታደራዊ ስልጠና ያለውን ሰራዊት እንዴት ነው በገጀራ እና በገበሬ ልናሸንፍ የምንችለው ይሄ እኮ ፊልም አይደለም እውነተኛ ታሪክ እንጂ ፊልም እንኳን ሲቀጣቀጡ እንኳን ተቀራራቢ የጦር መሳሪያ ይዘው ነው ይሄ የሚያሳየው ኢትዮጽያዊነት ሚስጥር፣ ሀይል መሆኑን እና የሚጠብቃት እንደማይተኛ ነው። ሲሰልስ ሚኒሊክ እምነቱ በጣም የሚያስደንቅ ነው ገጀራው ላይ ሳይቀር የሚኒሊክ ተስፋው እግዚአብሔር ነው ይላል። ሂድ እምነትህ አድኖሃል ተብሎ እንደተፃፈ በቅዱስ መፅሐፍ ተዋጊህ ወይም ሰልፉን የሚመራው እግዚአብሔር ነው ብለህ እሱን ስታምን ጉልበት የሱ መሆኑን ስታውቅ እና እሱን ስታስቀድም በተቃራኒው ደሞ በወታደር እና በታንክ ስትመካ ይለያያል።
🔑 ሌሎች ሀገሮች በጣልያን የተገዙት እምነት እና የኢትዮጵያዊያን አይነት ወኔ እና ስሜት ስሌላቸው ነው በርሊን ስምምነት ላይ እኮ እጣ ሲከፋፈሉ ሶስት ምርጫ አስቀምጠውልን ነው በፍላጎት,፣ በግድ እና በስምምነት አብዛኛው እምነት ስላልነበራቸው ሊገዙ ሆኗል እምነት ለምንም ነገር መሰረት ነው ጎልያድ በጠጠር የተሸነፈው በእምነት ነው።
እንደ ዕቃ ሲሸጡ እና ሲለወጡ፣ሲገደሉ አምላክ እንዴት ዝም ይላል ካልክ ለምንድን ነው አንድአንዶች በሞቀ ቤት እየተኙ፣እየበሉ እና እየጠጡ በቤታቸው ውሻን እና ድመትን አንደላቀው እየኖሩ ለምን የጎዳና ልጆች ለምን ይራባሉ፣ይጠማሉ፣ራሳቸውን ለማሞቅ ለምን ቤንዚን ይስባሉ አየህ እግዚአብሔር አለም ላይ አንዱን ሀብታም አንዱን ደሀ አንዱን አካለ ጎዶሎ አንዱን "ሙሉ አካል"አርጎ የሚፈጥረው እኔ እንደወደድኳችው እርስ በእርሳችሁ ተዋደዱ የሚለውን የራሱን ሀይለ ቃል እኛ እርስ በእርሳችን በመረዳዳት እንድንፈፅመው እና በኃላ በፍርድ ጊዜ ሲመጣ ብራብ ብጠማ አላበላችሁኝም አላጠጣችሁኝም እንደሚል ቃሉ እናም እኛ ምን ያህል እሱን እንደምንታዘዝ ለማወቅም ጭምር ነው ስለዚህ እግዚአብሔር ኢፍትሃዊነት አያሳይም።
በሚኒሊክ ጊዜ ያለውን ሁነት በሌላ ጊዜ አንብቤ እከሰታለው ለዚህ ብዬ ለዛሬ የሚሆነውን መልስ ለነገ ማስተላለፍ ስላልፈለኩ ነው።

፪ ማሳያ ኢትዮጵያ ላይ እንደተሴረው ሴራ የእውነት ኢትዮጵያ አሁን ላይ ትኖር ነበር???
፫ ማሳያ ኮረናን ተመልከት እውነት ኢትዮጵያ ላይ ኮረና ያልሰለጠነው የተባሉትን መመርያዎች ተግብረን ነው ውሃ በሌለበት(በሶስት ቀን አንዴ ) በሚመጣበት ሀገር እጃችንን ታጥበን ነው? በጠባብ ቤት ውስጥ ፮ እና ፯ ሰው እየኖረ እርቀታችንን ጠብቀን ነው?
፬ የእውነት በበይነ መረብ ብሄርን መሰረት ያደረጉ ምሁር ነን ባዮች በሚፅፉት፣በሚያፅፉት እና በሚከራከሩበት መጠን እውነት እነሱ ጋር ያለ አስተሳሰብ ህዝቡ ጋር ቢኖር የእውነት ኢትዮጵያ ውስጥ ወጣት ብሎም ሰላም የሚባል ነገር ይኖር ነበር?? ሌላ ብዙ ማሳያ መፃፍ ይቻላል ለዛሬ ግን እዚህ ላይ ላብቃ።ይሄ ሁሉ ችግር ስዘረዝር እንዳፈራ የሀገራችን አምላክ አይተኛም ሀገራችንን ይጠብቃታል!!!

አፍሪቃውያን የኢትዮጵያ አምላክ ቸርች እስከመገንባት ደርሰው ነበር

ክብር ከብረው ላስከበሩን ጀግኖች አያት አባቶቻችን!!!
ሞተው ላኖሩን ጀግኖች ማርያምን!!!!!

ተቆራርጦ ስለደረሰህ በጣም ይቅርታ ቢያልፍም መልካም መቶ ሀያኛ የአድዋ ድል ይሁንልን!!!!!


👇👇👇👇

ስላም እንደት ነህ/ሽ
"አምላክ ኢትዮጵያን በተለየ መልኩ ይመለከታታል ? ማሳያዎችስ አሉት?" የሚል ጥያቄ አንስተህ/ሽ እንድንወያይ ስለጋበዛችሁን አመሰግናለሁ።
እኔ አዎ በሚገባ ባይ ነኝ፡፡ ነገር ግን በእኔ አቅም ሊብራራ የማይችል ሲሆን የተቻለኝን ልሞክር
መጀመሪያ ፈጣሪ እንዲረዳን በእርሱ ማመን እና እርሱን የምንፈልገዉን መጠየቅ ያስፈልጋል፡፡ ምሳሌ እኔ ከራበኝ ምግብ እንዲሰጡኝ ቤተሰቦቼን መጠየቅ አለብኝ፡፡ ስለዚህ ፈጣሪ እንዲረዳቸዉ ሌሎችም እንደ እምየ ምኒልክ አምነዉ መጠየቅ አለባቸዉ፡፡ ክርስቶስ ለኛ ነጻ ፈቃድ ነዉ የሰጠን፡፡ 38 ዓመት የአልጋ ቁራኛ የነበረዉን ወጣት ሲያድነዉ ዝም ብሎ ተነስ አልጋህን ተሸክመኅ ሒድ አላለዉም መጀመሪያ መዳን እንደሚፈልግ ከጠየቀ በኋላ አዳነዉ እንጅ፡፡ ስለዚህ እኛም እንዲረዳን መጠየቅ አለብን፡፡ የእምየ ምንሊክን የክተት አዋጅ ስናይ እንዲህ ይላል “እግዚአብሔር በቸርነቱ እስካሁን ጠላት አጥፍቶ አገር አስፋፍቶ አኖረኝ እኔም እስካሁን በእግዚአብሔር ቸርነት ገዛሁ” በዚህ ዉስጥ ስንመለከት እስካሁንም እምየ ስልጣን ላይ የቆዩት በእርሳቸዉ ሀይል ብቻ ሳይሆን በፈጣሪም ቸርነት እንደሆነ ይናገራሉ፡፡ ይቀጥሉ እና ”……….. ከእንግዲህም ያሳፍረኛል ብየ አልጠራጠርም” በዚህ ዉስጥ ደግሞ እምየ ፈጣሪን ይዘዉ ጦርነቱን እንደሚያሸንፉ ምንም ጥርጣሬ የላቸዉም፡፡ ይሄንንም እራሳቸዉ ጣሊያኖች ”አንድ ሰዉ በነጭ ፍረስ ሆኖ ፈጀን ከፊታቸዉ አላስደርሰን አለ” ብለዉ መጽሀፋቸዉ ላይ እንደጻፉ ይነገራል፡፡ በዚህ ዉስጥ ደሞ እምየ ምኒልክ የሰማዕቱን የቅዱስ ጊዮርጊስን ታቦት ይዘዉ እንደዘመቱ ይታወቃል፡፡ የቅዱስ ጊዮርጊስ ፈረስ ደግሞ ነጭ ነዉ፡፡ ስለዚህ ሰማዕቱን ቅዱስ ጊዮርጊስ አብሮ አድዋ ላይ ተዋግትዋል፡፡ እንግዲህ እናንተ በጎደል ሙሉበት ፡፡ እግዚአብሔር ይስጥልኝ፡፡


👇👇👇👇

አሁን ያነ ሳሀቸው ሀ ሳቦች እውነትም እንደጠየቅከው አይነት ጥያቄ ጭንቅላት ውስጥ ያጭራሉ....

ግን ምን አለ መሰለህ......

አዎ አምላክ ኢትዮጵያን በተለየ አይን ያያታል

ለምን አልሽ ካልክ .... ያልኩበትን ሰበብ ልዘርዝር

1.ኢትዮጵያን ለቅድስት ድንግል ማርያም እንደስጦታ ሲሰጣት(ያስራት ሀገርሽ ብሎ) "ሳያዩ የሚያምኑ ህዝቦች የሚኖሩባት ምድር ናት" ብሎ ራሱ መስክሮልናል
2. ትንቢተ አሞፅ ላይ "እናንት የእስራኤል ልጆች ሆይ ለኔ እንደኢትዮጵያ ልጆች አይደላችሁምን"ብሎ ምን ያህል እንደሚወደን መስክሯል
3.አምላክ ነጋ ጠባ የሚመሰገንባት አገር ናት... ሙስሊሙ ክርስትያኑ ፕሮቴስታንቱ ጆሆባው ሌላውም... ሳያመሰግን አይውልም አያድርም
ምሳሌ ልስጥህ... ሰንበት ሰንበት ይቀደሳል... አርብ አርብ ጁማ ነው... አለመግባባት ላይ "በህግ አምላክ!" ይባላል.... ስላምታ ላይ "እግዛብሔር ይመስገን" " አላህ ይመስገን" ይባላል... ሌላው የገዳማውያን ፀሎትም አይረሳም
4. "ኢትዮጵያ ታበፅዕ እደዊሀ ኀበ እግዚአብሔር" (እጇን ወደ እግዛብሔር ትዘረጋለች) ተብሎላታልም....

Читать полностью…

ስብዕናችን #Humanity

🗣🗣ጉዞ ወደ ሀሳብ..........

በጣም በተደጋጋሚ ከብዙ ሰዎች የምሰማው አባባል አለ "የኢትዮጵያ አምላክ አይተኛም ኢትዮጵያን ይጠብቃታል" የሚባለው አባባል
"

አድዋን ተዋግተን ያሸነፍነው
ጊዮርጊስ በፈረስ ላይ ሆኖ በጎራዴው የጣሊያኖችን አንገት እየቀላልን ነው ብላቹ ታምናላቹ..? እንደዛ ከሆነ ሌሎች ሀገራቶችን በጣሊያን ሲገዙ ፣ እንደ እቃ ሲሸጡ እና ሲለወጡ ፣ ሲገደሉ አምላክ እንዴት ዝም ይላል ? ኢትዮጵያ በተለየ የሚያይ አምላክ አለ..? ካለስ የአምላክነቱ ባህሪ (ፍትሃዊነት) ጥያቄ ውስጥ አይገባም ወይ...?


በሚኒሊክ ግዜ በፈረስ መጥቶ
የጣሊያኖችን አንገት የቀላልን ጊዮርጊስ በሃይለስላሴ ግዜ ለምን አልመጣም..?

ጣሊያኖች ተመልሰው መጥተው በመርዝ ጋዝ እንደ በረሮ ሲረፈርፉን ያ አድዋ ላይ የዘመተው መልአክ የት ሄደ? በ'3 ቀን 33 ሺ ኢትዮጵያዊያን በአካፋ በዶማ በድንጋይ ተወግረው እንደ ዶሮ አንገታቸው ተበጥሶ በየ መንገዱ ሲጣሉ አዲሳባ የደም ባህር ስቶን አድዋ ላይ የጣሊያኖችን አንገት የቀነጠሰው ጊዮርጊስ ምነው ለአዲስ
አበባ ግዜ ሲሆን ፀጥ አለ? ..

#አምላክ ኢትዮጵያን በተለየ መልኩ ይመለከታታል ? ማሳያዎችስ አሉት?


በእነዚህ ሀሳቦች ላይ የምታምኑበትን በጨዋ ደንብ ሀሳባቹን ወርውሩልን🙏🙏🙏

@balmbaras

Читать полностью…

ስብዕናችን #Humanity

,#አድዋ💚💛❤️

እንኳን ለ125ኛው የአድዋ ድል በዓል አደረሳችሁ አደረሰን🇪🇹

መልካም በአል ለሁላችን🇪🇹

Читать полностью…

ስብዕናችን #Humanity

❤️በሰላም ቤትህ ገብተህና ተኝነተህ በነጋታው ጠዋት በሰላም መነሳትህን በፍጹም አትልመደው (Never take it for granted)፤ ይህንን እድል ያላገኙ ብዙ ሰዎች አሉና!

🌗ይህንን ከፈጣሪ ብቻ ልታገኝ የምትችለውን የየቀን ተአምር እንዳልረሳኸው ለራስህ ለማስታወስ ከፈለክ ነገ ጠዋት በጥሩ አእምሮ ስትነቃ አንድን ነገር ለማድረግ አስበህ መተኛት ትችላለህ፡፡ ነገ የአንድን ሰው ችግር የሚያቃልል አንዲትን ተግባር ማከናወን ትችላለህ፡፡

❤️ዋጋ ከፍለህ ብታደርገው የአንተን ህልውና የማይነካ፣ ለሌላው ለጨነቀው ሰው ግን የህልውና ጉዳይ የሚሆን አቅም በእጅህ ካለ የፈቃደኝነት ጉዳይ ነው እንጂ ያንን ከማድረግ ምንም ነገር እንደማይከለክልህ አትዘንጋ፡፡ አንድ ቀን የተጨመረልን አንድን ነገር በሰዎች ሕይወት እንድንጨምር እንደሆነ አትዘንጋ፡፡


ውብ እንቅልፍ❤️

✍ ደ/ር እዮብ ማሞ
❤️✨❤️✨❤️✨❤️✨❤️✨❤️✨
@EthioHumanity
@EthioHumanity

@EthioHumanitybot

Читать полностью…

ስብዕናችን #Humanity

✨ልብህ ያሰበውን ጥሩ ነገር ከመፈጸም አትቦዝን። ሃሳቡ በውስጥህ አርጅቶ እስኪሞት አትጠብቅ። ሰዎች ምን ይሉኝ ብለህ አትፍራ። ሰዎች ብትሠራም ባትሠራም የሆነ ነገር ማለታቸው አይቀርም። ብቻ መጠንቀቅ ያለብህ አንድ ነገር አለ። ያም ነገር ድርጊትህ በጎ መሆን አለመሆኑን ማረጋገጥ ላይ ነው። ድርጊትህ ጥሩ መሆኑን ካመንክበት ለመተግበር ተጣጣር።

🔱 ድርጊትህ ሙሉ በሙሉ ባይሳካ እንኳ በመሞከርህ ብቻ የህሊና እረፍት ታገኛለህ። በተከታታይ ከሠራህ ደግሞ እየሠራህ ማሻሻልህ አይቀርም።

🔆ጥሩ ነገር ለማድረግ ምቹ ጊዜ አትጠብቅ። ምቹው ጊዜ ሃሳቡ ወደ ጭንቅላትህ የመጣበት ጊዜ ነው።

🔱መማር ባለብህ ጊዜ ተማር፣ መሥራት ባለብህ ጊዜ ሥራ፣ መዝፈን ባለብህ ጊዜ ዝፈን፣ መዘመር ባለብህ ጊዜ ዘምር፣ መጻፍ ባለብህ ጊዜ ጻፍ፣ ማረፍ ባለብህ ጊዜ እረፍ።
✍Toughe G kebede

ውብ አሁን❤️
🔆✨🔆✨🔆✨🔆✨🔆✨🔆✨
@EthioHumanity
@EthioHumanity

✍ @EthioHumanityBot

Читать полностью…

ስብዕናችን #Humanity

💙በዚህ አለም ከላይ ስንደርስ ታች የነበርንበት ከንቱ ይሆናል፣ የጨበጥነውን እንረግጣለን፣ ክብር የሰጠነውን እናዋርዳለን፣ <ከዚህ በላይ የለም> ያልነውን ተራ ነገር እናደርገዋለን፤ አለሙ እንደዚሁ ነው። ንፋስ እንደመከተል ነው፣ የሚያረካ የሚያስደስት ምንም ነገር የለም።"

❤️ "ጊዜ ሲረዝም እድሜ ሲያልቅ ደሞ ሞት ነው። ሞት መራራ ከሆነ ምነው የጊዜ መባከን ቢያንስ ህመም አይሆንብንም? ሰው ቀጥሮህ ሲቀር ከእድሜህ እየቀነሰብህ ነው። የሆነ ሰው ያለ አግባብ የወሰደብህን ገንዘብ አንድ ቀን ሊመልስልህ ይችላል፤ የወሰደብህን ጊዜ ግን መቼም አይመልስልህም። አንድ ሊቅ እንዳለው ለሰው የምትሰጠው ትልቁ ስጦታህ ጊዜ ነው። እንዴት? የሰጠኸው ጊዜ ከእድሜህ ላይ የቀነስከው ነውና!"

💙 "...መጥፎ ሰው ጥሩ ባለሙያ ሊሆን አይችልም፤ መጥፎ ባለሙያም መልካም ሰው ሊሆን አይችልም። የተዋጣላችሁ ለሀገር ለወገን መከታ የምትባሉ ምሁር ባለሙያ የምትሆኑት የተስተካከለ ስብዕና ሲኖራችሁ ነው።

❤️ቅንነትን፣ደግነትን፣አዛኝነትን፣ታታሪነትን ለመማር ዝግጁነትንና ፈጣሪን መፍራትን ገንዘብ አድርጉ። በጋራ መስራት እንጂ በጋራ ማሰብ አይቻልም። ብቻችሁን ሁናችሁ አስቡ ስራ ላይ ግን ተባበሩ!"

በፍቅር እደሩ❤️
❤️💙❤️💙❤️💙❤️💙❤️💙
@EthioHumanity
@Ethiohumanity

Читать полностью…

ስብዕናችን #Humanity

❤️ፍቅር የልጅነት ስሜት ነው ።" ልጅነት እውነት ነው። ስሜት ደግሞ የማይዙትና የማይቆጣጠሩት። ፍቅር የማይዙትና የማይቆጣጠሩት እውነት ነው። ከተሰማ ሊክዱት የማይችል ፤ ከሌለም የማይፈጥሩትና ሊያስመስሉት የማይችል እውነት።

💙ፍቅር ዓመፀኛም ነው በምክንያት የማይገዛ ፤ ለዉይይት የማይመች ፤ የማያሰሩት፤ የማይጋልቡት ልጓም የሌለው ፈረሰ። ከፍት ቀዳሚ ፤ ጋላቢ ወሳጅ ፤ እምቢ ባይ ፤ ይቅርብህ አይሆንም የማያውቅ ፤ የፈለገውን እስኪያገኝ የማይተኛ ፤ የልቡ ሳይደረስ የማያርፍ።

💛ካፈቀረክ ፍቅር ምላሽ አይፈልግም ፤ የግድ መፈቀርን አይሻም ። ማፍቀር በራሱ ደሰ ይላል ፤ ቀኑን በመልካም ስሜት ሸፍኖ፤ ሌቱን በመልካም ህልም ያሳርፋል።

📖አለመኖር ከገጽ -239 የተወሰደ
❤️💙💛❤️💙💛❤️💙💛❤️💙
@EthioHumanity
@EthioHumanity

Читать полностью…
Subscribe to a channel