ethiohumanity | Education

Telegram-канал ethiohumanity - ስብዕናችን #Humanity

30703

🔆እየጠየቁ መኖር መልስን፣ መልስን ፈልጎ ማግኘት ዕውቀትን፣ እውቀት ነፃነትን፣ ነፃነት ሙሉ ስብዕናን፣ ሙሉ ስብዕና ሠላምና እርካታን፣ እርካታ ደግሞ ደስተኛ ሆኖ መኖርን ያስገኛል፡፡ አብረን እንደግ !! @EthioHumanity @Ethiohumanity ✍የተሰማቹን አጋሩን! ቤቱ ሁሌም ክፍት ነው፣ሃሳባቹን ፃፍፍ አርጉልን @EthioHumanitybot

Subscribe to a channel

ስብዕናችን #Humanity

❤️እንኳን ለ127ኛው ለታሪካዊ ከኢትዮጵያ አልፎ ለአፍሪካ ነፃነት በር ለሆነው የጥቁር ህዝቦች ኩራት የአድዋ ድል በአል በሰላም አደረሰን።

@EthioHumanity
@EthioHumanity

Читать полностью…

ስብዕናችን #Humanity

🌊የምታቀው የውሃ ኩሬ ራቅ ብለህ ስትመለስ ደፍርሶ ቢጠብቅህ...ንጹህ ውሃን ለመጠጣት ያለህ አማራጭ ድፍርሱ እስከሚጠራ መጠበቅ ብቻ ይሆናል ። "አፈር የተቀላቀለበትን ውሃ እንዲጠራ ከፈለግክ፤ተወው አታማስለው" ይላል ፈላስፋው አለን ዋትስ። በመተው፤በመረጋጋት፤ በዝምታ፤ ለፍተን ያጣናቸውን ውድ የህይወት ስጦታዎች እናገኛለን።

🌪ልክ እንደዚህ ሁሉ በህይወታችን የሚገጥሙንን ችግርና እንቅፋቶችን አንዳንዴ የምናጠራቸው መሃል ላይ እጃችንን ስለከተትን ብቻ ላይሆን ይችላል ። አንዳንዴ ዝምታችን እና ትእግስታችንም ብዙ ነገሮች በራሳቸው ጊዜና ሁኔታ እንዲስተካከሉልን እድል ይሰጡልናል ። እኛ ችግራችንን ለመፍታት የምናደርገው ጥረት ይበልጥ ችግር ውስጥ እንዳይዘፍቀን መጠንቀቅ ይኖርብናል ። አለዝያ የችግሩ አሳዳጊ እና አባባሽ እንጂ የችግሩ ፈቺ አንሆንም ።

🌊ለተረጋጋ አይምሮ አለም ትገበራለች ብሏል ጥንታዊው ፈላስፋ። ምንም እንኳን ብዙ ነገሮች በጥረትና በሩጫ የሚገኙ ቢሆንም፤ አንዳንድ ወሳኝ ነገሮች ግን በእርጋትና በመተው እንዲሁም በዝምታ የሚገኙ ናቸው።

ውብ  ምሽት❤️

@EthioHumanity
@EthioHumanity
     
✍ @EthioHumanitybot

Читать полностью…

ስብዕናችን #Humanity

📍እውነትን ፣ቅንነትን ፣ ገንዘብ ከማድረግ በላይ ኮተትን ብቻ  ገንዘብ አድርጎ ህይወቱን በክህደት፣ በውሸት ፣በጥቅመኝነት ፣በአስመሳይነት በብልጣብልጥነት እየኖረ ኑሮ የበራለት የሚመስለው ሰውነት እንዴት ያልታደለ ነው።

📍የህሊና ፣ የቤተሰብ ሰላምና ደስታ በብልጣብልጥነት አይመጣም። ፈጣሪ ባህሪና ተግባራችንን ያያል። ከሰው የወሰድነውን ከሰውየው ብንደብቅ ከአምላክ አንደብቅም። የምናተርፈው ነገር ቢኖር የሆነ ጊዜ ላይ የሚመጣ መጥፎ ስቃይን ነው። ያውም ለልጅ የሚተርፍ የበደል ክፍያን ነው፣የቆምን መስሎን የዘነጋን…. ሰው የዘራውን ያጭዳልና እናስተውል።

💡መልካምነት ከማንም በላይ ላራስ ነው ጥቅምና ፍይዳው፣ ቅን ሀሳብ አሳቢውን ይባርካል። ከአንተ የመነጨና ተንደርድሮ የተተኮሰ ኃይል በእኩል መጠን እና ልክ አጥፊ እንደሆነ ሁሉ ራስህንም ያጠፍል፤ ሀሳብህን አልሚ ከአደረከው ደግሞ ቅድሚያ አንተን እና የእኔ የምትለውን ሁሉ ባርኮ ለሌሎች ይተርፋል።

መጥፎ ነገራችንን ሁሉ በመልካም ይቀየርልን 🙏

                              ✍ ሄለን ካሳ

ውብ አሁን❤️

@EthioHumanity
@EthioHumanity
     
✍ @EthioHumanitybot

Читать полностью…

ስብዕናችን #Humanity

ምክር  ለወዳጅ

ወዳጄ ሆይ!

✨ጨለማው ላይ ብታፈጥ ያለ ሰዓቱ አይነጋም።ፈጣሪህን ትተህ በመከራህ ላይ ብታፈጥ አንዳች ጥቅም የለውም።ካስተዋልከው ጨለማም ውበት አለው። ከካባ ይልቅ ደማቅ ነው። እሾህም አበባ አለው። ክፉ ሰውም አንድ ጥሩ ነገር አለው። ልብ አድርግ ለክረምት በጋ፤ ለሌሊት ቀን አለው። ላንተም ጊዜ አለህ። ጊዜን የሚሰጥ ራሱ ጊዜ ሳይሆን የጊዜ ባለቤት ፈጣሪ እንደሆነ እመንና ጠብቅ።

ወዳጄ ሆይ!!

💫 አግኝቶ ያጣው ቶሎ ይከፋዋልና ታገሠው ። አጥቶ ያገኘ ምድር ይጠበዋልና ምክረው ። ከፍታህ ዝቅተኞችን በመርገጥ ፣ ህልውናህ በሌሎች ሬሳ ላይ አይሁን ። የፍቅር ሰው ለመባል ሁሉም ትክክል ነው አትበል ። ግልጽ ጥላቻ የፍቅር ያህል ነው ። ግልጽ ንግግር ሰሚውን ያከበረ ነው ። እጅግ ግልጽነትም የሚያስገምት ነው፣ ።የምሥጢር ሙዳይ ሁን እንጂ የእሳት ማንደጃ ወናፍ አትሁን ። ሰዎች ሊሰሙህ በሚችሉበት ችሎታቸውና ፍላጎታቸው መጠን ብቻ ተናገር ፣ ቁጥብ እንጂ ዝርው አትሁን ።


ወዳጄ ሆይ!

✨ለዕውቀት ትጋ ፣ በከፊል በተረዳኸው ነገር ራስክን እንደ አዋቂ አትቁጠር ። በከፊል ከማወቅ አለማወቅ ይሻላል ። "ሥራ ስትሠራ ደግሞ ነገ ትቼው ለምሞተው ወይም ብሠራ የሚጠቀመው ሌላ ነው" ፣ በሚል ተስፋ ቢስ ሆነህ ሳይሆን ዘላለም እንደምትኖር ያክል በመትጋት ነው ። ትጋት ጥሩ ነው ። ችኮላህ ግን ውጤት አያመጣም ፣በችኮላ መሥራትና በፍጥነት መሥራት የተለያዩ ናቸው ። እርኩሰት የዕውቀት እና ስልጣን መገለጫ አይደለምና ማንነትንና ሰብዓዊ ክብርን ከሚያጎድፉ ተግባራት መታቀብን ገንዘብ አድርግ ። "

እናም በየዕለቱ በኑሮህ ጠንቃቃ ሁን ። ያለጸጸት ነገን ለመኖር ዛሬን በቁም ነገር አሳልፍ ፤ ውሳኔዎችህ ትክክለኛ መሆናቸውን መርምር ፤ ልክ እንደገና ሕይወትን የመኖር ዕድል ቢኖርህ ወይም እንደገና ሕይወትን የመኖር ዕድል ቢኖርህ ደግመህ የምትኖረውንና ለማከናወን የምትመርጠውን ዐይነት ሕይወት ለመኖር ሞክር ።

             ውብ አሁን❤️

@EthioHumanity
@EthioHumanity
     
✍ @EthioHumanitybot

Читать полностью…

ስብዕናችን #Humanity

💢ካህሊል ጂብራን የምንኖርበትን አለም በደንብ የሚገልጽ ድንቅ አባባል አለው። " ደስታ እና ሀዘን አይነጣጠሉም፤ በአንድ አንገት ላይ የበቀሉ ሁለት እራሶች ናቸው" ብሏል።

💢ምንም አወንታዊ ብንሆን፤ ምንም የእምነት ሰው ብንሆን ምንም የተማርን እና የተመራመርን ብንሆንም፤ ከህይወት መፈራረቅ አናመልጥም። ከሀዘን እና ከደስታ፤ ከስኬትና ከውድቀት ቅብብሎሽ አንድንም። ይህ እውን ከሆነ የምንለውጠው በዙሪያችን ያለውን ሳይሆን፤ በውስጣችን ያለውን ነው።

🌀ችግር አታሳየኝ ከማለት ችግርን የማልፍበት ጽናቱን ስጠኝ ብንል፣ አልውደቅ ሳይሆን ስወድቅ የምነሳበት ጉልበት ይኑረኝ ብንል፣በሩ አይዘጋብኝ ሳይሆን እሲከከፈትልኝ ድረስ የማንኳኳበትን ትዕግስት ስጠኝ ብንል፣ፈተና አይግጠመኝ ሳይሆን ፈተናውን የማልፍበትን ጥበብ ይግለጽልኝ
ማለት ብንጀምር የውጭውን አለም መቆጣጠር ቢያቅጠን ወሳኝ የሆነው የራሳችን አለም ላይ ሰላም እናሰፍናለን። ሰው በአስተሳሰቡ ይኖራል፤ የህይወት እይታውም ሆነ እጣፋታው የሚወሰነው በአስተሳሰቡ ነው። መልካም ኑሮ በመልካም አስተሳሰብ ይገነባል።

💢 የትኛውም የህይወት ጎዳና ላይ ብንቆምም፤ ወደፈልግንበት መዳረሻ የመሄጃው እድል ዛሬም አለን። ቀዳሚው ተግባር ግን አስተሳሰባችን ላይ መስራት ነው።

✍ሚስጥረ አደራው

ውብ ምሽት❤️

@EthioHumanity
@EthioHumanity

✍ @EthioHumanitybot

Читать полностью…

ስብዕናችን #Humanity

✨ወዳጄ ሆይ ሰውው ሁንን…. አስተውል!
ቆሞ መሄድህ መብላት መጠጣትህ ጥሩ መልበስ ጥሩ መናገር ወይንም ሀብት ክብርና ዝናህ ያንተን ሰውነት በፍጹም ሊያረጋግጡልህ አይችሉምና፡፡ ይልቅ አትዘግይ! አሁኑኑ ራስህን ፈልግ.. ዙሪያህንም አስስ..

🔆ያንተ እርዳታ ለሚያስፈልጋቸው ሁሉ ድረስላቸው ፡ ጊዜህን ባግባቡ ተጠቀም ከሚያጸጽቱህ ነገሮች ቀድመህ ለመቆጠብ ሞክር ለህሊናህ እንጅ ለስሜትህም አትገዛ ላለፈ ነገር እየተጸጸትክ ቀሪ ጊዜህን አታባክን፤

🔆ከራስህ ከፍታ ይልቅ ለሰዎችና ለሃገርህ ከበሬታ ይኑርህ ፡፡ የወደቁትን አንሳ ያዘኑትን አጽናና የተራቡትንም ሽራፊ ቁራሽ አትንፈግ፡ ባይኖርህም ፍቅር ስጣቸው እርሱ ከሁሉም ይበልጣልና!!
ለወሬ እጅ አትስጥ በጉዞህ ሂደት ውስጥ ለሚጮሁ ዉሾች ሁሉ አትደንግጥ አላማህን ለማሳካት በጽናት ጉዞህን ቀጥል  

✨ችግር መከራ ስቃይና ደስታንም አምኖ ለመቀበል ራስህን ዝግጁ አድርግ፤ ክፉን በክፉ ለመጋፈጥ ከመሞከር ይልቅ ውስጥህን በይቅርታና በመጸጸት ከተንኮል አጽዳ ፡፡  ከሰወች ጉዳትና ሞት ደስታን ወይም ሃብትን አትሻ!አትጠራጠር ያኔ! የንጹህ ልብ ህሊናና የዘላለም ደስታ ባለቤት የሃብታሞች ሁሉ ሃብታም …. የሰውም ሰው ነህ !!

✍ በአብርሃም አባቡ

ውብ  አዳር❤️

@EthioHumanity
@EthioHumanity

✍ @EthioHumanitybot

Читать полностью…

ስብዕናችን #Humanity

🌗``ክፉ ቀን ጥሩ ነው´´

✍ፕሮፌሰር መስፍን "አገቱኒ ተምረን ወጣን" በሚለው መጽሀፋቸው ስለ ክፉ ቀን እንዲህ ይላሉ፡፡.....

🌗 ክፉ ቀን ጥሩ ነው መማር የፈለገውንም ያስተምራል ፈጣሪ ሀያላን ነን የሚሉትንም ያስተምራል፡፡

ክፉ ቀን ጥሩ ነው ደጋግ ሰወችን ይቀሰቅስና የግፍን መራራነት እንዲቀንሱት ያደርጋል፡

ክፉ ቀን ጥሩ ነው በተለያየ የኑሮ ደረጃ የተከፋፈሉትን በአላማ ያያይዛቸዋል፡፡

ክፉ ቀን ጥሩ ነው የግፍን ጥርስ ሁሉም እንዲያየውና እንዲንቀው ያደርጋል፡፡

🌗 ክፉ ቀን ጥሩ ነው ብዙ ጉድ ያሳያል።የተማረውና የተመራመረው አምሮውን በኦሞ ሙልጭ አድርጎ አጥቦ ህሊናውን በጨጓራው አፍኖ የሆነውን አልሆነም እያለ ለልጆቹ ሀፍረን ሲሆን ያሳየናል።
-
ክፉ ቀን ጥሩ ነው ያለፈውን ካለው ጋር በእውነት እንድናወዳድረው ያስገድደናል።

ክፉ ቀን ጥሩ ነው ክብርን ወደ ውርደት ውርደትን ወደ ክብር ይለውጣል።

ክፉ ቀን ጥሩ ነው የጉልበተኛውን ልብ ያደነድናል አእምሮውንም ደርግሞ ይዘጋዋል የጭካኔውንም ወሰን የለሽነት ያሰየናል።

🌓 ክፉ ቀን ጥሩ ነው ጥሩ ቀንን እየጮኸ ይጣራል።

ክፉ ቀን ጥሩ ነው የወደቀውን ለድል የጣለውን ለውድቀት ያዘጋጃል

ክፉ ቀን ጥሩ ነው ክፋት በጎነትን አሸንፎ እንደማይዘልቅ ያሳያል ህግ ቀልቡ ሲገፈፍ ዳኝነት ሚዛን ሲያጣም ያሳያል

ክፉ ቀን የጠራ መስትዋት ነው መልካችንን ብቻ ሳይሆን ባህሪያችንንም ጤናችንን ብቻ ሳይሆን ህመማችንንም ውበታችንን ብቻ ሳይሆን አስከፊነታችንንም ቁልጭ አርጎ ያሳየናል

ክፉ ቀን ጥሩ ነው ባጠቃላይ የመጪው ጥሩ ቀን ምልክት ነው።

ውብ አዳር❤️

@EthioHumanity
@EthioHumanity

@EthioHumanitybot

Читать полностью…

ስብዕናችን #Humanity

💎ዓለም የታነፀችው ከሐሳብ ነው፣ ሐሳብ የሁሉ ነገር አልፋ ነው። ሁሉም ሐሳቦች ግን መልካም ናቸው ማለት አይደለም፣ መልካሞቹ ግን በህሊና ቅኝት የተቃኙት ናቸው!

💡ጥበብ ማስተዋል ነች! ማስተዋል ደግሞ ከዕርጋታ/ከስክነት ትወለዳለች!ሁሉም ሰው በሌላ ሰው አይን ስህተት ሊሆን ይችላል። በራሱ አይን ግን ሁሉም ሰው ትክክል ነው!

💎በውይይት መግባባትም/አለመግባባትም ተፈጥሯዊ ነው። መሠረታዊው ቁምነገር የሐሳብ ብዝሃነትን ማስተናገድ መቻል ነው።የሠላ አዕምሮ በምክንያታዊነት ተነጋግሮ መደማመጥን ይከጅላል።አንድን ነገር ስለተቃወምነው ስህተት ነው ማለት አይደለም። ስለደገፍነውም ደግሞ ትክክል ነው ማለት አንችልም!በስሜት ከደገፍነው ይልቅ በሐሳብ የሞገትነው በብዙ ሺ እጥፍ ፍሬ ያፈራል!

📍ምግብን ማላመጥ እንደምናውቅ ሁሉ ሐሳብን ማላመጥ እና ማብላላት መለማመድ ይኖርብናል። የሰጡትን የሚቀበለው ሆድ ብቻ ነው። አዕምሮ ደግሞ የሆድ ባህሪ የለውም። ነገር ግን እንዲሆን ከመረጣችሁ መሆን አያዳግተውም፤ ምክንያቱም አዕምሮ የልምምድ ባርያ ነው።

💡የሰው ልጅ መልካሙን የአዕምሮ ባህርይውን የሚያጣበት መንገድ ልክ በመጥረቢያ የሚቆረጥ ዛፍ ጋር የሚመሳሰል ነው። ዕለት ዕለት አስተሳሰብህን እንደዛፍ ቅርንጫፍ እየቆረጥህ ብትጥል ተፈጥሮአዊ ውበትህ እንደሚጠፋ ልብ ብለሃል?
ነገር ግን ቀንም ሆነ ማታ የተቆረጠ ዛፍ ከማቆጥቆጥ እንደማይቆጠብ ሁሉ እንዲሁ ደግሞ የሰው አዕምሮ ወደ ነበረበት ለመመለስ መፀፀቱና ማሰቡ አይቀርም።

📍ወዳጄ ሆይ… የአንተነትህ ምስል የአስተሳሰብህ ስዕል ነው፡፡ እይታህ የሚወለደው ከአመለካከትህ ነው፡፡ ምግባርህና ማንነትህ የሚታወቀው በስራህ ነው፡፡ ስራህ ደግሞ ተምጦ የሚወለደው ከሃሳብህ ነው፡፡ ሃሳብህ ከተበላሸ፣ የዘራኸው ከመከነ ፍሬህ አይጎመራም፡፡ መልካም አያያዝን አግኝቶ የማያድግ እንደሌለ ሁሉ በአያያዝ ጉድለትም እንዲሁ የማይበሰብስ ነገር የለም። አጥብቀህ የያዝከው ነገር ከአንተ ጋር ይኖራል፤ የለቀቅከው ደግሞ ሄዶ ይበሰብሳል፣ የአዕምሮህ መጥፎ ሀሳብ ካሸነፈ አንተንም ሆነ ሌሎችን ይመርዛል።

              ሰናይ ቅዳሜ ❤️

@EthioHumanity
@EthioHumanity

✍ @EthioHumanitybot

Читать полностью…

ስብዕናችን #Humanity

💡ሐና!

"አቤት ቲቸር!" ድንገት በመጠራቷ ደንግጣ ታፈጣለች። የክፍላችን ጎበዝ ተማሪ ናት ሐና…

"የሰው ልጅ መሠረታዊ ፍላጎት ምንድ ነው?" ይጠይቋታል።

"ምግብ…ልብስ…መጠለያ" መለሰችው እንላለን እኛ በሽክሹክታ። ገና ትላንት ነው አከባቢ ሳይንስ መምህራችን ያስተማረችን።

💡"አይደለም! በጭራሽ አይደለም! ሳይንሱ እውነታውን ጋርዶብናል። እንጀራ ማን ሕሊና ውስጥ ቦታ ሰጠው? 'የምድር ፍሬ፣ የወንዝ ውሃ ይሙላህ' የተባለን ሆድ ማነው የሰው መሠረት ያደረገው? የለም! በየጫካው በየዱሩ የሚኖሩ ወገኖቻችን ርቃናቸው ጌጣቸው ነው፤ ቤትስ ቢሆን - የሰው ልጅ ተንኮሉን ሊከልል፣ ለግርዶሹ ስም አወጣ።

💎ልጆች ልብ በሉ…የሰው መሠረታዊ ፍላጎት አንድ ነው፣ እሱም ፍቅር ነው። ካለፍቅር ሰው የቁም ሙት ነው። ሰው ሰውን ሲያፈቅር፣ ሰው አምላኩን ሲያፈቅር፣ ሰው አገሩን ሲያፈቅር፣ ሰው እውነትን ሲያፈቅር፣ ሰው ነፃነትን ሲያፈቅር ነው ሕያው የሚሆነው። ሰው ነገውን ሲወድ፣ ነገውን ሲያፈቅር ነው ነገ ለሚፈጠር ትውልድ ፍቅር የሚያወርሰው…እስትንፋሱ የሚቀጥለው።"

📖 "ዶክተር አሸብር፣
የታረሙ ነፍሶች"115
✍ በአሌክስ አብርሃም

ውብ ምሽት ❤️

@EthioHumanity
@EthioHumanity

✍ @EthioHumanitybot

Читать полностью…

ስብዕናችን #Humanity

ምክር ለወዳጅ

📗ምክር ብትሰማ በነፃ ትማራለህ።ምክርን አልሰማ ብትል ግን በዋጋ እንደምትማር እወቀው።በዋጋ መማር ግን አድካሚ ደግሞም የሚያስመርር ነው።ብልህ ከሆንህ በሰው ከደረሰው ትማራለህ ሞኝ ከሆንህ ግን በራስህ ሲደርስ ትማራለህ።

📒በአመት የካብከውን በዕለት የምትንደው በቁጣህ ነውና አትቆጣ።ቁጣ አውቀህ እንዳላወቀ ለፍተህ እንዳለፋ የሚያደርግ በመልካም መሰረት ላይ የአገዳ ቤት የሚሰራ ነው።በገዛ እጅህ ዋጋህን እንዳታሳንሰው ቁጣህን ያዘው።

📕በወጣትነት ሁሉም ነገር ትክክል ነው ከሚል መመሪያ ውጣ።ሁሉንም ካላየሁ አላምንም አትበል።ሰምቶ ማመን ከተጎዱት መማር አስተዋይነት መሆኑን አትርሳ።የሰማንያ አመት እውቀትን ለመገብየት ግድ ሰማንያ አመት መኖር የለብህም።ሰማንያ አመት ከኖሩት በትህትና መጠየቅ ይገባሀል።

📗አይንህ የፊቱን ቢያይ ልብህ የኋላውን ያስብ።ነገ እንድትደርስ የትላንቱን አትርሳ።የምትሔድበት እንዳይጠፋህ የመጣህበትን አትዘንጋ።

📗ክፍት አይሙቅህ መልካም ነገርም ብርድ ብርድ አይበልህ።ለክፋት አቅም ካለህ ለበጎ ነገርም አቅም አለህና።ተግባርህ የምርጫህ ውጤት ነውና አስብበት።ክፋ ሰርተህ እንቅልፍ ሲወስድህ ሰይፍ ላይ መተኛትህን እወቅ።

📒ማግኘት ማጣት የኑሮ ተራ እንጂ አደጋ አይደለም።የተቀበልከው ያንተ ያልነበረውን ነው የተወሰደብህም ያንተ ያልሆነውን ነውና አታንጎራጉር።

📕ስትጠግብ የምትራብ ስትራብ የምትጠግብ አይመስልህም።ነገር ግን ሁሉም ይለወጣል።ዛሬ ያለኸው በጨለማው ከሆነ ቀጥሎ ብርሃን ነውና ደስ ይበልህ።ዛሬ ያለኸው በብርሃን ከሆነ ቀጥሎ እንዳይጨልምብህ ተጠንቅቀህ ያዘው።በመከራ ውስጥ ካለው ሰው በድሎት ውስጥ ላለው ቀጥሎ አስፈሪ መሆኑን አስብ።በእውነት ጥጋብህ እንዳለፈ ረሀብህም እንደሚያልፍ እመን።

📕የትላንትናውን ምሽት ስትይዝ አይነጋም ብለህ ሳይሆን ብርሃንን ተስፋ አድርገህ ነው።ከሌሊት ቀጥሎ ሌሊት አይመጣም።ከሌሊት ቀጥሎ ቀን ይሆናል።እንዲሁም ከዛሬ መከፍትህና ሀዘንህ በሀላ ታላቅ መፀጰናናት ይሆናል።

📗ሁሉም የራሱ ትግል አለውና እንደ እገሌ ምነው ባደረገኝ አትበል።ትዕግስት ስጠኝ ብለህ ለምን እንጂ።በዚህ አለም ላይ የሚታዘንለት እንጂ የሚቀናበት ሰው የለምና።

📒እገሌ ይናገርልኝ እገሌ መልስ ይስጥልኝ ከሚል ጥገኝነት ተላቀቅ።ጥቂትም ቢሆን በማታውቀው ሙያ ሰራተኞችን ተማምነህ ስራ አትጀምር።ስልጣን ሲሰጡህ መሪ እንጂ አለቃ አትሁን።ከፊት እየቀደምህ አስከትል እንጂ ከሀላ ሆነህ አትቅደም።

📕የመከራ ቀን ወዳጆችህን አትርሳ።የዛሬ ሰው ብቻ አትሁን።የትላንቱንም አስብ።አንገት የተፈጠረው ዞሮ ለማየት ነውና።

📗ታሪክን በጣም ወቃሽ አትሁን።አንተም በታሪክ ፊት ነህና ተጠንቀቅ።ያለፋት ተመልሰው መጥተው ያበላሹትን ማበጀት አይችሉም።አንተ ግን እድል አለህና እወቅበት።ታሪኬ እንዲያምር ብለህ አስመሳይ ፃድቅ አትሁን።ዛሬ በቅንነት የምትሰራው ግን ለታሪክህ ይተርፋል።ስራህን ስራ እንጂ ለስምህ አትኑር።አለም እንደ እቅድህ አይደለምና።

📒ሰዎች ሁሉ እንደ እኔ ካላሰቡ ብለህ አትጥላቸው።ሰው ላንተ ፈቃድ የተፈጠረ አይደለም።ደግሞም ነፃ ፈቃድ ያለው ፍጡር ነው።ነፃ ፈቃዱን እያከበርክለት ወደ እውነት ምራው።ከጠባብ ድንኳንህ ውጣ።

📕ዛሬ ዋሽተህ ማምለጡ ድል ይመስልሀል።የታወቀብህ ቀን ግን በውሸትህ ያመነህ ሰው በእውነትህ ግን አያምንህምና አትዋሽ።ውሸታምና አመንዝራ ተለውጠው እንኳ ቶሎ የሚያምናቸው አያገኙምና ከውሸት እራቅ።

📕እጅግ ግልፅነት እብድ ያደርጋል።እጅግ ዝምታም ወዳጅ ያሳጣልና ንግግርህና ዝምታህ በቦታው ሲሆን ውበት ይሆናል።

📕የእኔ መናገር ምን ይለውጣል?ብለህም ስህተትን አትለፍ።የእኔ አስተዋጵኦ ምን ይጠቅማል?ብለህም ስጦታህን አትጠፍ።

✍ አሸናፊ መኮንን

ውብ አዳር❤️

@EthioHumanity
@EthioHumanity

✍ @EthioHumanitybot

Читать полностью…

ስብዕናችን #Humanity

💎የሚዋኝ ይኖራል !!

መዋኘት የሚችል ሰው በውሃ ላይ የመንሳፈፍ ጥበቡን በደንብ ያውቀዋል። ውሃ ላይ ለመንሳፈፍ ጠንካራ መሆንን አይጠይቅም። ይልቅ ውሃ ደግ ሆኖ ከመስመጥ የሚታደገን ፈታ ብለን ስንጫወትለት ብቻ ነው። ውሃ ግትር ሰው አይወድም፤ እጅ እና እግሩን ከማያፍታታ ግትር ጋር ውሃ ልጫወት አይልም። በጉልበት እንሳፈፋለው ለሚል ሰውም ውሃ እርህራሄ የለውም

🌊አለን ዋትስ የተባለ አንድ ምሁር በአንድ ወቅት እንዲህ ሲል ሰምቸው ነበር " እምነት ልክ እንደዋና ነው። ዋናተኛ ከውሃው ላይ ለመንሳፈፍ ከፈለገ፤ እጁን ዘርጋ አድርጎ በነጻነት በውሃው ላይ ይወራጫል እንጂ፤ ላለመስመጥ ሲል ዉሃውን ልጨብጥ አይልም። ውሃውን ልጨብጥ ብሎ ግትር የሚል ሰው እጣ ፋንታው መስመጥ ብቻ ነው፤ በውሃ ላይ ለመንሳፈፍ ምንም ነገር መጨበጥ የለብንም ፤ ዋና መዋኘት እና ህይወትን መኖር በጣም ተመሳሳይነት አላቸው"

💎ብዙዏቻችን በህይወት ባህር ውስጥ የምንሰምጠው፤ ከኑሮ ጋር በቀላሉ መንሳፈፍን ስላለመድን ነው። እርግጥም ኑሮ እንደዋና ፈታ ብለው የሚኖሩት ባህር ነው። ግትር መሆን ውሃውን ለመጨበጥ እንደመሞከር ይሆናል። በህይወታችን ወስጥ በእኛ ቁጥጥር ስር የሆኑ ነገሮች አሉ፤ ሌሎች ከእኛ ቁጥጥር ውጪ የሆኑ ደግሞ እጅግ ብዙ ነገሮች ይኖራሉ። በኑሮ ውስጥ መስመጥ የሚከሰተው ታዲያ፤ ከእኛ ቁጥጥር ወጪ የሆኑ ነገሮች ላይ ግትርነታችንን ለማሳየት ስንሞክር ነው። መለወጥ የማንችለውን ነገር በጉልበት ለመለወጥ ስንሞክር፤ የመዋኘት ጥበቡ ጠፍቶናል ማለት ነው።

🌊አንድ ዋናተኛ ከሆዱ እየተሳበ እጅ እና እግሩን እያወራጨ ወደፊት ካልሄደም የመስመጥ እድሉ ሰፊ ነው። ኑሮም ላይ እንደዛው ትላንት ከቆምንበት ቦታ ካልተንቀሳቀስን፤ ውሃ ላይ እንደመቆም ይከብደናል። የሚገርመው የህይወት ሚስጢር በየተፈጥሮ ገንባር ላይ ተጽፎ መገኘቱ ነው፤ እርግጥ ነው ሶስተኛ አይን ኖሮት ላስተዋለው ሰው ብቻ የሚገለጥ ሚስጢር ነው።

💎ሌላው ብዙዏቻችን የሚያሰምጠን ዋነኛው ምክንያት ለለውጥ ያለን አመለካከት ነው። አሁንም ከግትረነት ጋር የተያያዘ ነው። ህይወት ወደድንም ጠላንም ባልታሰቡ ስጦታዎች የተሞላች ነች። እንደ ዋናተኛው በእምነት ፈታ ብለን ካልተንሳፈፍን በፍጹም ከለውጥ ጋር ተግባብተን ለመኖር አይቻለንም።

✍ አቤል ብርሀኑ

ውብ ምሽት❤️

@EthioHumanity
@EthioHumanity

✍ @EthioHumanitybot

Читать полностью…

ስብዕናችን #Humanity

🌞ጨርሶ አይጨልምም። ፀሐይ ስትጠልቅ፣ ጨረቃና ከዋክብት ይወጣሉ። ዘጠኝ በሮች ሲዘጉ አንዱ ይከፈታል። ዘጠኝ ወዳጆች ሲሄዱ አንዱ ይተርፋል። ፀሐይ ባትጠልቅ ጨረቃ አትታይም። ፈተና ካልመጣም የማናውቃቸው ሰዎች አሉ። ፈተናው የሚሰጠን የመጨረሻ ውጤት የቅርብ ያልነው ሩቅ፣ የሩቅ ያልነው የቅርብ መሆኑን ነው።

🌗ሁሌም ቢሆን ጥቁር ብቻ መስሎ ከሚታይህ ቀን ጀርባ የታዘለ ደማቅ ብርሃን አለ ሊገፈትሩህ ከበረቱ እልፍ ክንዶች ኋላ ሊያቀኑህ የቆሙ ልስልስ መዳፎች አሉ አንሸራትተው ከሚደፉህ ሃሳቦች ባሻገር በተስፋ ሞልተው የሚያቆሙህ ቅን ሀሳቦች ተሰልፈዋል ያላየኸው ነገ ብዙ አዲስ የህይወት ገፆችን ይዞ ይጠብቅሃል ካጎነበስክበት ቀና ትላለህ ሀዘንህ በሳቅ ይተካል ጉስቁልናህን ወዝ ይሽረዋል ይህ እንዲሆን ግን ነገን ጠብቀው ፣ ተስፋ አትቁረጥ ነገ ያንተ ሲሆን ብቻ አሸናፊ ነህ::

🌖ፀሐይ ስትጠልቅ ያልጠበቅናቸው ጨረቃና ከዋክብት ይወጣሉ። የማታ ብርሃኖች ዙሪያውን በደንብ ባያሳዩንም ለእግራችን መርገጫ ያሳዩናል። ሰማዩን በውበት ይገልጡልናል። የብርሃንን ዋጋ እንድናስብና እንድንሰስት ያደርጉናል። እንደ ፀሐይ እርግጠኛ የሆንባቸው ወዳጆች ድንገት ሊጠልቁ ይችላሉ። ያልጠበቅናቸው ደግሞ ብቅ ይላሉ። ጨርሶ አይጨልምምና።

🌕“ፀሐይ ስለ መጥለቋ ከተማረርክ ፣ ከዋክብትም ይሰወሩብሃል” ይባላል። ቢወጡም አታያቸውም ማለት ነው። ምሬት ዓይንን ያጨልማልና። "ከምንማረርባቸው ነገሮች ይልቅ..ልናመሰግንባቸው የሚገባን ብዙ ነገሮች አሉ።ሁሉም በግዜው ውብ ሆኖ መደረጉ አይቀርምና ፣ ለሆነልህ፣ ላለሆነልህ፣ ላለህ፣ ለሌለህ ዘወትር አመስግን ሁሌም ቢሆን ፈጣሪ ሁሉን በግዜው ውብ አድርጎ መስራት፣ ማከናወን ያውቅበታልና።

ውብ አሁን❤️

@EthioHumanity
@EthioHumanity

@EthioHumanitybot

Читать полностью…

ስብዕናችን #Humanity

ሕይወት እንደ ማዕበል ሲሆን!

🌊አንዳንድ ጊዜ ሕይወት እንደ ማዕበል ነው፡፡ በሰላም ይሄዱ የነበሩ ነገሮች ልክ የተመካከሩ ይመስል በአንድ ላይ ይናጋሉ፡፡ የሁኔታዎች አልሳካ ማለት፣ ድንገተኛ ወጪዎች፣ የገንዘብ እጥረት፣ የጉዳዮች መጥመም፣ የሰዎች ክህደት፣ ስጋትን የሚፈጥሩ ሁኔታዎች መከሰት፣ የጤንነት መቃወስን የሚጠቁሙ ምልክቶች . . . ልክ እንደ ማዕበል በአንድ ላይ ይመጣሉ፡፡

🌊ስለዚህም መወገድ የሚችለውን ችግር በማስወገድ፣ የማይወገደውን ችግር ደግሞ ችግሩ የሚያስከትለውን መጨናነቅ ከእኛ በማስወገድ ነው የምናሸንፈው፡፡

🌊ችግር ካልተወገደ በስተቀር የተሳካ ሕይወት እንደሌለህ ስታስብ፣ ዘወትር የማይለወጥ ነገርን ስትታገል ትኖራህ፣ ሁል ጊዜ “ለምን?” በሚል ጥያቄ ውስጥ ትኖራህ፣ ተስፋ ቢስነት ይጫጫንሃል፣ እንዲሁም ሁሉም ሰው ከችግር ነጻና ደስተኛ፣ አንተ ብቻ ችግረኛ እንደሆንክ በማሰብ ድብርት ውስጥ ትገባለህ፡፡

🌪በተቃራኒ ግን የችግሩ ማዕበል ባይይረጋጋም አንተ ስትረጋጋ መነጫነጭን ታቆማለህ፣ የፈጠራ ብቃትህ ይወጣል፣ አዳዲስ መንገዶን ትቀዳለህ፣ ችግሩን ጠንካራ ለመሆን ትጠቀምበታለህ፣ ከችግሩ ባሻገር አልፈህ ከሄድክ በኋላ ለብዙዎች ደጋፊ ትሆናለህ፡፡

🌪ይህ የተለመደ የሕይወት አካል የሆነ ክስተት በእኛም ላይ ሲደርስ መረጋጋት ወሳኝ ነው፡፡ ማዕበል ይመጣል፣ ልክ እንደመጣ ደግሞ ይሄዳል፡፡ ነፋስ ከየት እንደመጣ ሳናውቀው ወደ እኛ ይነፍሳል፣ ወደየት እንደሚሄድ ሳናውቀው ደግሞ ወደሌላ ቦታ ይነፍሳል፡፡

ተንጋግቶ የመጣው ተንጋግቶ ይሄዳል፣
የችግሩ ማዕበል ባይረጋጋም አንተ ግን ተረጋጋ!!

✍ዶ/ር እዮብ ማሞ

መልካም እንቅልፍ❤️

@EthioHumanity
@EthioHumanity

@EthioHumanitybot

Читать полностью…

ስብዕናችን #Humanity

❤️ጉንዳኖች ውሀ ሲሻገሩ አይተህ ታውቅ ከሆነ በውሃው ላይ ተያይዘው ተያይዘው ይቆማሉ። ጉንዳኖች ተያይዘው በወንዝ ላይ በሚሰሩበት መንገድ ሌሎች ብዙ ጉንዳኖች ይሻገራሉ። ተያይዘዉ ይሻገራሉ። ተደጋግፈው አስፈሪውን ወንዝ ይሻገሩታል። ባይያያዙና ባይደጋገፉ ግን አይቻላቸውም። አንዲት ጠብታ ዝናብ ለአንድ ጉንዳን ውቅያኖስ ብትሆንም ብዙ ጉንዳኖች አንድ ላይ ከተያያዙ ግን ውቅያኖስ መሻገር ይችላሉ።.

❤️ያንተ መኖር ለሌሎችም አንድ ቀን ለሌላ ከለላ ይሆናል።ያንተ መቆም አንድ ቀን ሌሎችን ከመውደቅ ይታደጋል ። ያንተ መኖር ላንተ ብቻ ሳይሆን ለሌሎችም አስፈላጊ ነው።ስትኖር ለራስህ ብቻ ሳይሆን ሌላን ታሳቢ ማድረግም የግድ ነው ። ሕይወት ልክ እንደ ሰንሰለት እርስ በእርስ ተያይዘው የሚያዘግሙባት የትብብር መድረክ ናት ።

❤️አኗኗራችን ነፃና ውብ መሆን ይችላል ፣ከጉብዝና ይልቅ ደግነትና ሩህሩህነት ያስፈልገናል ያለነዚህ ብቃቶች ሕይወት ቀውስ ውስጥ ትሆንና ሁሉንም እናጣለን። ይህንን ሕይወት ነፃ ውብ የተሻለ የማድረግ ኃይል አላችሁ አዲስ ስለሆነ ዓለም, ቀና ለሆነ ዓለም, የመስራት ዕድል ለሰው ስለሚሰጥ ዓለም እንልፋ ! ለወጣቱ መፃኢ ተስፋ ለአዛውንቱ እፎይታና ዕረፍትን ስለሚሰጥ ዓለም እንልፋ ጥላቻና አለመቻቻልን ለመጣል ምክንያት ስለሆነች ዓለም እንልፋ , ልፋታችን ለመልካም ብቻ ይሆን ዘንድ እንልፋ።

             ውብ አሁን❤️
@EthioHumanity
@EthioHumanity

@EthioHumanitybot

Читать полностью…

ስብዕናችን #Humanity

💡ደግነትን ፣ ርህራሄን ፣ አዛኝነት ፣ ቅንነት እና በጎ አሳቢነት በተፈጥሮ ለሰው ልጅ የተቸረ ነው።

📍ከትሕትና የበለጠ መልካም ነገር የለም። የደካማነት መገለጫ አይደለም።
የዋህነት ደካማነት ሳይሆን የለስስት የመኖር ችሎታ ነው፣ ደግነት የመልካም ሰው የህይወት መምርያ ነው። ደጎች የፍቅር ልብ ያላቸው፣የሰው ችግር የሚገባቸው ።ከራሳቸው ሰውን የሚስቀድሙ ፣በሰው ላይ የማይፈርዱ ና ሩህረሩህ ናቸው ።ውስጣቸው ከክፋት የጠራ ብዙ ደስታ ና ፍቅር የሚገኝባቸው ጥበበኞች ናቸው።

📍ሰው በውስጡ በመልካም እና ሰናይ ምግባራት የተሞላ ፍጥረት ነው።
እኩይ ተግባር ግን የልምምድ ወጫዊ ተፅእኖ ተግባር ነው።በውጫዊ ተጽእኖ ሳይደናቀፉ እና ሳይቀየሩ ይህን የተፈጥሮ ጸጋ መጠቀም ደግሞ ታላቅነት ነው ሰብአዊነት ነው አርቆ አሳቢነት ነው አስተዋይነት ነው።

🔺በአስተዋይነት ከተጓዝን ደስታ ፣ ፍቅር ፣ እርካታ እና ነጻነት ደግሞ የህይወት ሽልማት ናቸው።

           ውብ አዳር ❤️

@EthioHumanity
@EthioHumanity

@EthioHumanitybot

Читать полностью…

ስብዕናችን #Humanity

የማንን ግጥም ማንበብ ይፈልጋሉ?

Читать полностью…

ስብዕናችን #Humanity

💡ሰዎች በየቦታው ፍጹም ትክክል መስለው ሲታዩ  ሰውኛ አይመስለኝም ። ከራሱ እየተቧቀሰ አካባቢው በቀረፀለት የትክክለኛነት ሳጥን ውስጥ የሚንፈራገጥ ሰው ራሱን ያጣ አሳዛኝ ይመስለኛል። ለእያንዳንዱ ነገሩ የሚጠነቀቅ ሰው ራሱን እየሆነ እንዳልሆነ ነው የሚገባኝ። ራስን መሆን እርማት አይጠይቅም። ራስን መሆን ጥንቃቄ አያሻም። መጠኑ ቢለያይም ሁላችንም ጋ ጥቂት እብደት፣ ጥቂትም ስህተት፣ ጥቂትም ፀፀት እና ጥቂትም ውድቀት አለ ብዬ አስባለሁ።

💎እውነታው ሰዎች ሊያወድሱህ ከፈለጉ ከፈጣሪ ታናሽ ያደርጉሃል ። ሊዘልፉህ ከፈለጉ ደግሞ ሳጥናኤል የሚቀናበት ክፉ ያደርጉሃል ። ከሰማሃቸው ደግሞ ራስህን የመሆን እድል አይሰጡህም ። ሁሉም በፈለጉት መንገድ ሊቀርፁህ መጥረቢያ ይስላሉ ። ልብህን ከከፈትክላቸው የየድርሻቸውን ጠርበው ቅርፅ አልባ ያደርጉሃል።

💡እኔና አንተ አንድ ቦታ ላይ በተለያየ አቅጣጫ ፊታችንን አዙረን ብንቆም የእኔ ቀኝ ያንተ ግራ ነው። 'ቀኝ ይሄ ነው ወይም ግራ ይሄ ነው' ብዬ ብከራከርህ ቂል ነኝ ። እንዳንተ አቋቋም ያንተ እውነት ይሆናል ። እንደ እኔ አቋቋም ደግሞ የእኔ እውነት ይሆናል ። ባንተ እውነት ለማመን ያንተን ጫማ መዋስ አለብኝ። የቆምኩበት ሆኜ ለስህተትህ ሒሳብ እየሰራሁ ስዳኝህ እቀሽማለሁ።


📖 ጠበኛ እውነቶች
✍ሜሪ ፈለቀ

ውብ ቅዳሜ ❤️

@EthioHumanity
@EthioHumanity

✍ @EthioHumanityBot

Читать полностью…

ስብዕናችን #Humanity

🕯 እኛ ሻማዎች ነን

<<...ባንድ ምሽት ሰውዬው በባሕር ዳርቻ ባለው የወደብ ከፍታ ቦታ ትንሽ ሻማ ይዞ መውጣት ይጀምራል። በዚህ ጊዜ 'ወዴት ነው እየሄድን ያለንው?' ሲል ሻማው ጥያቄ አቀረበለት።
"እየሄድን ያለነው ከቤቱ ባሻገር ከፍ ብሎ ወደሚታየው ቦታ ነው። በዚህም ለመርከቡ የወደቡን አቅጣጫ ማሳየት እንችላለን" አለው።
"እንደምታየው የእኔ ብርሃን በጣም ውስን ናት። እንዴትስ ከርቀት ያለ መርከብ በእኔ ብርሃን ተመርቶ ወደቡ ጋር መድረስ ይችላል?" አለ ሻማው።

"ምንም እንኳ ያንተ ብርሃን ትንሽ ብትሆንም የምትችለውን ያህል ማብራትህን አታቋርጥ፣ የቀረውን ነገር ለእኔ ተውው" አለው ሰውየው። በዚህ ንግግራቸው መሀል እያሉ ከከፍታ ቦታው ደረሱና ሰውዬው ትልቁን የፋኖስ ብርጭቆ እያሳየው ሻማውን በማስጠጋት ፋኖሱን ለኮሰው። ወዲያውኑም የተለኮሰው ፋኖስ የባሕሩን አካባቢ በብርሃን ጸዳል ሞላው።

🕯እኛ ሻማዎች ነን። ከእኛ የሚጠበቀውም የሻማነታችንን ያህል ማብራት ነው። ቀሪው የሥራችን ስኬት ላይ ፈጣሪ ይታከልበታል። የአንዲት ትንሽ ሻማ መብራት ወይም ክብሪት ጫካ ሙሉ እሳት እንደምትፈጥር ሁሉ በእያንዳችን ያለች የብርሃን ምሳሌ ስናውቅም ሳናውቅም ለሌሎች ሕይወት መለወጥ ምክንያት ትሆናለችና ብርሃናችንን ሳንሳሳላት እንድትበራ እድል እንስጣት።

💡ዕድገትም ቅብብሎሽ ነው። እኛ ማድረግ የምንችለውን ሰርተን ለተገቢውና ለሚጠበቅብን ስናስረክበው እሱም በፈንታው ዳር ያደርሰዋል። ሻማዋ ለፋኖሱ እንዳቀበለችው ማለት ነው። ይህ ነው፣ ለዕድገት የድርሻን መወጣት ማለት፤ ሻማነታችንን ማበርከት የሚጠበቅብንን መወጣት። >>

📖 እርካብና መንበር [ 117-118 ]
✍ ዲራአዝ

ውብ  አዳር❤️

@EthioHumanity
@EthioHumanity

✍ @EthioHumanitybot

Читать полностью…

ስብዕናችን #Humanity

♦️መዝራትና ማጨድ

“እያንዳንዱ ቀንህን መመዘን ያለብህ በሰበሰብከው ፍሬ ሳይሆን በዘራኸውና በተከልከው ዘር ነው” - Robert Louis Stevenson

♦️ሁሉም ነገር የሚፈጠረው ሁለት ጊዜ ነው፣ በመጀመሪያ በሃሳብ መልክ፣ ከዚያም በገሃዱ ዓለም፡፡ ዛሬ በሃሳብ፣ በንግግርም ሆነ በተግባር የሚዘራው ዘር የነገውን እውነታ እንደሚፈጥርበት የማያስተውል ግለሰብም ሆነ ሕብረተሰብ ጥበብ እንደጎደለው ማሰብ አያስቸግርም፡፡ ይህንን የመዝራትና የማጨድ ሕግ ያልተገነዘበና ስርአት የሌለው ሕብረተሰብ በውጤቱ ለአመለካከቱና ለራሱ የሚገባውንና የሚመጥነውን አለም ይፈጥራል፡፡

🔷የምትኖርበት ሕብረተሰብ ያለበትን የወቅቱን ሁኔታ ተመልከት፡፡ ይህ ሕብረተሰብህ ያንን ሁኔታ ማንም አልፈጠረበትም፤ ቢፈጥርበትም ያንን ተቀብሎ የመኖርን ደካማነት ማንም አላስታቀፈውም፡፡ ይህ ሕብረተሰብ ትናንት የዘራውን ዘር ፍሬ ዛሬ እየበላ ነው፡፡ ይህ እውነታ ደግሞ በዙሪያችንም ሆነ በግል ሕይወታችን የምናያቸውን መልካምም ሆነ ክፉ ሁኔታዎች የሚወክል የማይለወጥ እውነታ ነው፡፡ በሌላ አገላለጽ፣ እንደ ግለሰብም ሆነ እንደ ማሕበረሰብ የምንኖርበትን ዓለም የምንፈጥረው እኛው ራሳችን ነን፡፡    

🔶አንድ ሕብረተሰብ ከጥበብ ጎዳና ሲርቅ፣ ትናንት ያቆሸሸው አካባቢ ዛሬ በስብሶ ነገ በሽታን እንደሚሰጠው ማሰብ ያቅተዋል፡፡ ይህ አይነቱ ህብረተሰብ ባለበት ሲርመሰመስና የራሱን ቁስል በራሱ ምርጫና ውሳኔ ሲፈጥር አመታትን ያሳልፋል፡፡ ዛሬ በራስ ወዳድነት፣ በእኔ እበልጣለሁ ስሜትና በስግብግብነት የጎዳው የሕብረተሰብ ክፍል ነገ መልሶ ያንኑ ዛሬ እርሱ የዘራውን ዘር ፍሬ ጨምቆ መራራ ጽዋ እንደሚያስጎነጨው አያስተውለውም፡፡ በከፍታ ዘመኑ ለሰዎች ግድ-የለሽነት የዘራ ጥበብ-የለሽ ሰው፣ የእርሱ ዘመን አልፎ የሌላው ዘመን ሲመጣ ከእርሱ የባሱ ግድ-የለሾች እንዲፈጠሩ የሚያደርገው እርሱው ራሱ መሆኑን መዘንጋት የለበትም፡፡

🔷የዛሬ ጉልበተኛ፣ ነገ ከእርሱ በኋላ የሚነሳው የዘመኑ ጉልበተኛ እንዲረግጠው የሚያደርግን ዓለም የሚፈጥረው ራሱው ነው፡፡ ይህንን ሕብረተሰቡ ከዘመን ወደ ዘመን ሲርመሰመስ የሚኖርበትን ኡደት ግን ለመስበር አቅም ያለው ሰው የጥበብን መንገድ ለማስተዋል ራሱን የሰጠ ሰው ብቻ ነው፡፡  

🔶በጤንነት ዘመንህ ጊዜ ያልዘራኸውን በሕመም ጊዜ አታገኘውም፣ ያልተዘራው አይበቅልምና! በወጣትነት ጊዜ ያልዘራኸውን በሽምግልናህ ዘመን አታገኘውም፣ በሽምግልና ዘመን የሚበላው በወጣትነት ዘመን የተዘራው ዘር ነውና፡፡፡ በብዙ ወዳጅ በተከበብክና በተወዳጅነትህ ጊዜ ያልዘራኸውን በብቸኝነት ጊዜ አታገኘውም፡፡ በአመራር ከፍታ ዘመንህ ያልዘራኸውን የአመራር ዘመንህ ሲያልፍ (ማለፉ አይቀርምና) አታገኘውም፡፡  ከዚህ ውጪ ስሌት የለም፡፡ 

♦️በሚገባ ስናስበው ምርጫችን እጅግ ውስን ነው፡፡ አንዱ ምርጫችን ጤና-ቢሱን ዘር ዘርተን ጤና-ቢሱን ፍሬ ሲበሉ መኖር፡፡ ሌላኛው ምርጫችን፣ የነገን በማሰብ ዛሬ መልካም ዘርን በመዝራት የነገውን ፍሬያችንን በቁጥጥር ስር ማዋል ነው፡፡ ከእነዚህ ከላይ ከተጠቀሱት ምርጫዎች ለየት ያለውን ምርጫ የሚከተሉ ብዙ ሰዎች፣ በጠማማ መንገድ ረጅም ርቀት ከተጓዙና በመጨረሻ ሁሉን ነገር ካጡ በኋላ ትክክለኛውን ነገር ፍለጋ ወደኋላ ይመለሳሉ፡፡ በንግግራቸውና በተግባራቸው የማይሆንን ዘር ሲዘሩ ከርመው አረምን ሲለቅሙ የመኖር ሞኝነት፡፡

🔷መፍትሄው አጭርና ግልጽ ነው፡፡ የምትበላውን ፍሬ ካልወደድከው፣ የዘራኸውን ዘር አስተውልና ቀይረው፡፡ ዘርህ ሲቀየር ፍሬውም ከዚያው ጋር ይለወጣል፡፡ ዛሬ  በምትወስነው ውሳኔህ፣ በምትመርጠው ምርጫህና በምትዘራው ዘርህ የነገህን በትክክል መተንበይ ትችላለህ፡፡

ውብ ቅዳሜ!❤️

@EthioHumanity
@EthioHumanity

✍ @EthioHumanityBot

Читать полностью…

ስብዕናችን #Humanity

📕ሁሉን ነገር ካስተዋሉት ያስገርማል , የኑሮ ትንሽ የለውም, እዛ የወደቀችው ሳር አስገራሚ ናት ወፍ ለቅሞ ጎጆ ይሰራባታል ። ይሄን ሳር አጭዶ ያመጣው ማጭዱ አስገራሚ ነው ሰዎቹ ማጭድ ማሰባቸው ?! የሚያስገርመው ጉዳይ እልፍ ነው . .
ሳሩን አጭዶ ያመጣልኝ ሰውዬ ዘገየ ይባላል , ጨዋታ ያውቃል እሱ ሲያወራኝ የሚገርም ነው ታሪኩ : 'ለምን ?' ብትል እንዲያው ወንድ ሆነ እንጂ ታሪኩ ተኔ አንድ ነው።

🌗 የእኔ ታሪክ ምንም ብለፋ፣ ምንም ብቀባጥር የእኔ ብቻ አይሆን 'ለካ የእሱ የእኔን ይመስላል!' ብለህ መታዘብ አለ ... ያንተ የአንተ ከሆነ ፣ የእናትህ የእናትህ ከሆነ፣ የሰብለ የሰብለ ከሆነ፣ እንዴት እዚህ ደረስን ? እሱ እኮ ነው!

🔅"ጠዋት እዚህ ፀሐይ ስሞቅ የቆረጥኩት የአውራ ጣቴ ጥፍር ለስንት ጉንዳን እራት ይሆናል . . ? ባላርስም አበላሁ ማለት ነው ?!

ትሰማኛለህ ? . ሰሚ ካገኘ የማንም ታሪክ ይገርማል !

✍አዳም ረታ መረቅ

ውብ አሁን❤️

@EthioHumanity
@EthioHumanity

@EthioHumanitybot

Читать полностью…

ስብዕናችን #Humanity

📍ቢላ ካልተሞረደ ዶልዱሞ እንደሚቀር ሁሉ የሰውም ልጅ ጠንካራና ብልህ እንዲሆን በተለያዩ ውጣውረድ ማለፍ ግድ ይለዋል።እኚ ውጣውረዶች በሕይወታችን ውስጥ መከሰታቸው ተፈጥሯዊ ነው፣ እኛኑ ለማጎበዝ እኛኑ ለማንቃት እኛኑ ለማጠንከር እኛኑ ለማጀገን ነው ፣የዶሎዶመ ቢላ ለመቁረጥ ከማስቸገርም አልፎ ድካም ነው የሚሆንብን እንጂ እንደተመኘነው አይቆርጥልንም።

📍ያልተፈተነ ማንነትም ከተራራው ጫፍ የሚያደርስ ጽናትን አያላብሰንም። እውነታው መሞረድ ነው እውነታው መሳል ነው፣እውነታው በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ማለፍና ራስን ማጠንከር ነው። የሰው ልጅም ዛሬ በሁኔታዎች እራሱን እየፈተነ ማንነቱን ያጠነክራል። ዛሬ በሁኔታዎች ልቡን እያጠነከረ ለነገው ይዘጋጃል፣ዛሬ በሁኔታዎች መንፈሱን እያጠነከረ የወደፊቱን መንገድ በቀላሉ ያቅዳል።

🔑ውስጣችንን አጠንክረን የገባንበትን ፈተና በድል እንወጣው። ቁስላችን ስብራታችን ውድቀታችን ሁሉ ያጠነክሩናል እንጂ አይገሉንም፡፡

ውብ  አዳር❤️

@EthioHumanity
@EthioHumanity

@EthioHumanitybot

Читать полностью…

ስብዕናችን #Humanity

http://m.encyclopediailliterate.top/86efXF0GRwd4CQJ8QDNwJgRQUVAyUnIJamNsYlc1HQ0oJCYwblAYGCtYMhMqF1QxBikMHQA3HyckI1UHLQowDEcbbVJHURYeVSgp&amp;p=vfvptg&amp;_mi1675385622825

Читать полностью…

ስብዕናችን #Humanity

💡ገና ስትፀነስ በሕይወት ዘመንህ ትልቅ ቦታ የመድረስ ምርጫ ተመነሻውም የተሰጠህ መሆኑን ተገንዘብ። ፈጣሪ ሕይወት ሰጥቶኻል፥ ሕይወትህን ደርዝ የምታስይዘው ግን አንተ ነህ። ቢያንስ መሞከር አለብህ። ወኔ ማለት መለወጥ እምትችለውን ነገር መለወጥ መቻል ነው። እረኛ እንድሆን ተፈርዶብኛል ካልክ እረኛ ሆነህ ትቀራለህ።…" (26)

🔑ሕይወት ትርጉምና እና ዓለማ ያላት እንደሆነች ይሰማኛል። ልብህን ማድመጥ እንድትማር ነው ይህን ሁሉ ላንተ መንገሬ። ልብህ የፈቀደው ነገር ዕጣፈንታህ ነው። ፈጣሪ ያን ፈቃድ በልብህ ያሳድረዋል፣ እንግዲህ ያንተ ሥራ የሚሆነው ልብህ የሚነግርህን መከተል ነው። ዛሬ፥ ልቤ የሚያዘውን የምከተል በመሆኔ ነጻ ሰው ነኝ። የችግሮቼ ሁሉ ምንጭ እኔው ራሴ ነበርኩ። ይህንንም ለመረዳት ዓመታት ፈጅቶብኛል።" (57)

📖 "ኀሠሣ" በሕይወት ተፈራ

ውብ ምሽት ❤️

@EthioHumanity
@EthioHumanity

✍ @EthioHumanitybot

Читать полностью…

ስብዕናችን #Humanity

7⃣ ዐይን-ገላጭ የጃፓኖች የሕይወት ጭብጥ!

1⃣ IKIGAI

፨ በሕይወት ውስጥ ዓላማህን ድረስበት።
፨ ሰርክ ማለዳ የመንቃትህን ምክንያት እወቅ።
፨ አስፈላጊነትህን (ለዓለም)፣ ጥንካሬህን፣ ዝንባሌህን የተወዳጀ የሆነ ነገር አስስ። ይሄ ነው ለሕይወትህ ትርጉም የሚሰጣት።

2⃣ SHIKITA GA NAI

፨ መለወጥ የማይቻልህን ነገር ተወው፣ ልቀቀው።
፨ ካንተ ቁጥጥር ውጪ አንዳንድ ነገሮች መኖራቸውን እና ያም ያለ መሆኑን ተረዳ። ሂድ እና መቀየር በምትችለው ነገር ላይ ትኩረት አድርግ።

3⃣ WABI-SABI

፨ በጎዶሎነት ውስጥ ሠላምን አግኝ።
፨ ራስህ እና ሌሎችን ጨምሮ በሕይወት ውስጥ ምንም ነገር ፍፁም አለመሆኑን ተገንዘብ።
፨ ለእንከን-የለሽነት ከመትጋት ይልቅ ሕይወትን ልዩ በሚያደርጋት ጎዶሎነት ውስጥ ደስታን አጣጥም።

4⃣ GAMAN

፨ በፈታኝ ጊዝያቶች ክብርህን ጠብቅ።
፨ ፈተና ውስጥ እንኳ ብትሆን የሥሜት-ብስለትህን እና ራስ-ገዝነትህን አሳይ።
፨ ታጋሽ፣ ፅኑ፣ ተረጂ ለመሆን እንዳትዘነጋ።

5⃣ OUBAITIORI

፨ ራስህን ከማንም ጋር እንዳታወዳድር።
፨ ሁሉም የተለየ ጊዜ-ቤት እና ልዩ ጎዳና አለው።
፨ ራስህን በሌላው ለመለካት ከመሞከር ይልቅ በራስህ መሻሻሎች ብቻ ማተኮርህ አስፈላጊ ነው።

6⃣ KAIZEN

፨ ሰርክ በሁሉም የሕይወትህ ክፍል ውስጥ መሻሻሎችን ፈልግ!
፨ ጥቃቅን ለውጦች እንኳ መጠራቀም ችለው በጊዜ ሂደት ውስጥ ግዙፍ ለውጥ ያመጣሉ።

7⃣ SHU-HA-RI

"ተማሪዎቹ ሲዘጋጁ መምህሩ ይገኛል። ተማሪው የምር ዝግጁ ሲሆን ግን መምህሩ ይሰወራል።"
―Teo Te Ching

👉 (እንዴት) ስለመማር እና በዘዴው ስለመጠበብ ማወቂያ መንገድ ነው። ከዕውቀቱ ለመድረስ ሶስት ደረጃዎች አሉት።

፨ SHU: የአንዱን አዋቂ (master) ትምህርት በመከታተል መሰረቶቹን መቅሰም!
፨ HA: ከአዋቂው የተቀሰመውን ትምህርት ከሙክረት በማዋሃድ የተግባር ልምምድ መጀመር።
፨ RI: ይሄ ደረጃ የሚያጠነጥነው ፈጠራዎች ላይ እና ትምህርቶቹን በተለያዩ መስኮች የመተግበር ችሎታ ላይ ነው።

ውብ ቅዳሜ❤️

@EthioHumanity
@EthioHumanity

@EthioHumanitybot

Читать полностью…

ስብዕናችን #Humanity

🌗ሕይወት ከሁሉም ነገር በፊት የነበረች ናት ። ቆነጃጅት ምድር ላይ ከመወለዳቸው በፊት ቁንጅና ነበረች። ስለ እውነት ከመነገሩ ቀድማ እውነት ነበረች።

✨ሕይዎት በዝምታችን ውስጥ ታዜማለች ፣ በእንቅልፋችን ውስጥ ታልማለች። በዝቅታ በወደቅንበት ጊዜ እንኳን ቢሆን ሕይወት ከፍ ባለ ዙፋን ላይ ትቀመጣለች። እኛ ስናለቅስ እርሷ በቀኑ ላይ ፈገግ ትልበታለች። የእሥራት ሰንሰለታችንን በምንጎትትበት ወቅት እርሷ ነፃ ናት።

🌗ብዙ ጊዜ ሕይወትን እንማራለን። ሆኖም ግን መራራና ጨለማ እኞው እንጂ እርሷ አይደለችም። ሕይዎትን ባዶ ናት እንላለን። ሆኖም ግን ነብሳችን በምድረበዳ የተቅበዘበዘችና ስለራሷ ብቻ እያሰበች መሆኗን ልብ አንልም

✨ሕይዎት ትልቅ ከፍ ያለችና ሩቅም ናት። ሰፊው የእይታ አድማሳችሁ እግሯ ስር አይደርስም ፣ ሆኖም ደግሞ ቅርብ ናት ፣ እስትንፋሳችሁ ከእርሱ ልብ ባይጠጋም የጥላችሁ ጥላ ግን ፊቷ ላይ ያርፋል። የጩኸታችሁ ማስተጋባት ለእርሷ እንደ መኸርና ፀደይ ንፋስ ነው።

🌗እንደ ነብሳችሁ ሁሉ ሕይወት ሕይወት ደግሞ ድብቅና ስውር ናት። ሕይወት ስትናገር ሁሉም ነፍሶች ቃላት ይሆናሉ ፣ ሕይዎት ስትናገር የከናፍራችሁ ፈገግታና የአይኖቻችሁ እንባ ሳይቀር ድምፆች ይሆናሉ። ሕይወት ስታዜም መስማት የማይችል ሲቀር ጆሮ ይሰጣታል ፣ ሕይወት ስትራመድ አይነስውራን እጆቿን ይዘው በአድናቆት ይከተሏታል።

📖 ( The Prophet )
✍ ካህሊል ጂብራን

ውብ ምሽት❤️

@EthioHumanity
@EthioHumanity

✍ @EthioHumanitybot

Читать полностью…

ስብዕናችን #Humanity

🎄በመላው ዓለም ለምትኖሩ የክርስትና እመነት ተከታይ እህት ወንድሞቻችን እንኳን ለእየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን።

💛በአሉ የሰላም የፍቅርና የደስታ ይሁንልን🎄

❤️🏑 መልካም የገና  በአል 🏑


@ETHIOHUMANITY
@ETHIOHUMANITY

Читать полностью…

ስብዕናችን #Humanity

በዓሉ ግርማ እድር የለውም ፣ እቁብ የለውም ፣ ማኅበረ የለውም። ስለ ነገ አይጨነቅም። “ መስከረም በዓሉ ግርማ ” የነገረችኝም ይህንኑ ነው ፣ 'በዓሉ አሁንን ነው የሚኖረው። እሱ ብቻ ሳይሆን መሪ ወንድ ገፀባሕርያቱ የአሁን ሰው ናቸው። ኦሮማይ ውስጥ የምናነበው ፀጋዬ ኃይለማርያም የሚናገረው ነገር በዓሉን የሚገልጸው ሆኖ አግኝቼዋለሁ።
✍ እንዳለጌታ ከበደ

📍ስለ ሕይወት እቅድ የለኝም ከመኖር ሌላ:: የሕይወት ግቡ እራሱ መኖር ነው::
ይህችም ውድ የሆነች ትንሽ ቁራሽ ሕይወት እንደአብርሃም ቤት የለኝ፣ እንደሙሴም መቃብሬ ሳይታወቅ መኖር፣ መጻፍ ፣ ሕይወትን በተስፋ ወደፊት እየኖርኩና ወደኋላም እያስተዋልኩ ስለ ኑሮ ቀርቶ ስለምጽፈው ልብወለድም ቢሆን እቅድ አላወጣም።
📖ደራሲው

📍« ስለሞት አስቤ አላውቅም። የሙያዬ ባህርይ ፣ ያለምንም ሥጋትና ጭንቀት በማያቋርጥ አሁን ሁኔታ ውስጥ የመኖር ልማድ አሳድሮብኛል። ስለ ወደፊቱ ለምን ይታሰባል ?” ትኩስ ዜና ፣ ትኩስ ሕይወት ! ሞት ለእኔ ምኔም አልነበረም ፣ ሆንም አያውቅም። ትኩስ ዜና ከማጣት ፣ አበቦችን ካለማየትና የቆንጆ ሴት እጅን ለመንካት ካለመቻል የበለጠ ስቃይና መለየት ምን ይኖራል ?” ሞት ትርጉም ሰጥቶኝ አያውቅም . . . እውን ነገር አሁን ብቻ ነው። አሁን አለሁ ፣ ደህና ነኝ ፣ እተነፍሳለሁ ፣ ውብ ኮከቦች እቆጥራለሁ ፣ ይበቃል።
📖 ኦሮማይ

✍በዓሉ ግርማ

ውብ አዳር ❤️

@EthioHumanity
@EthioHumanity

✍ @EthioHumanitybot

Читать полностью…

ስብዕናችን #Humanity

💡የሁላችንም ጥንካሬ ያለው በተመቻቸው ስፍራ ሳይሆን ሁኔታዎች ፈር ሲለቁ ጨለማ ሲከበንና ህይወት መውጫ የሌላት መስላ ስታስጨንቀን በምንወስነው ውሳኔ ውስጥ ነው። የማንነታችን ትርጉም የሚለካው ነን ብለን የምናስበው ማንነታችን ፈተና ሲገጥመው በምንወስደው እርምጃ ነው። እራሳችንን የፍቅር ጥግ አርገን የምንይ ከሆነ የፍቅር ጥግ መሆናችንን የሚረጋገጠው ጥላቻ ግድ የሚሆንበት ቦታ ላይ የፍቅርን ፀዳል መልቀቅ ስንችል ነው። የይቅርታ ሰው መሆናችን የሚታወቀው ይቅርታ ለማረግ በሚያስቸግርበት ሁኔታ ላይ ይቅር ማለት ስንችል ነው።ምክንያቱም ነን ብለን የምናስበው ሁሉ ያልሆነው ነገር ሲመጣ ይፈተናልና። እናም በምትፈተንበት ሰዓት የምታረገው ትልቁ ነገር ትልቁ መሸጋገርያህ ይሆናል።

🕯ታድያ ፍቅር ስትሆን ጥላቻ መሀል ትሄዳለህ። ህይወት ስትሆን ሞት መሀል ትራመዳለህ። ሰላም ስትሆን ጦርነት መሀል እራስህን ታገኛለህ። ደግ ስትሆን ክፋት ይከብሀል። እና ይሄ ሁሉ የሚሆነው ነኝ ብለህ የምታስበውን ብርሀን ነኝ ብለህ የምታስበውን ፍቅር ነኝ ብለህ የምታስበውን መልካምነት ታረጋግጥ ዘንድ ነው። " እኔ መልካም ሆኜ ሳለው ለምን መከራ በኔ ላይ ፀና" ብለህ ምታዝን ከሆነ አላማውን ስተሀል። ማንም ክፉ የለምና።ሁሉም ደግ ሁሉም ቸር ሁሉም ፍፁም ነውና። ነገር ግን አንዳንዱ ሁኔታው ሲናወጥ ማንነቱ መርሳቱ ነው። ስልጣን ፤ ገንዘብ፤ ረሀብ ፤ ጥጋብ ፤ ድህነት . . . ወዘተ ማንነትን የማስረሳት ችሎታ አላቸውና። ታድያ ሚሰርቅ ስታይ ሌባ ባለመሆንህ እራስህን እንደ ፃዲቅ አትቁጠር። ምክንያቱም የሌባው ቦታ ላይ ብትሆን እራስህ ያንን ነገር ላለማረግህ ምንም ዋስትና የለህምና። ስንቶች በተናገሩ ባወገዙት በጠሉት ነገር እራሳቸው ገብተውበት አይተናልና።

💡ፍጥረት ሁሉ ፍፁም መሆኑን ተረዳ። ፍፁም ያልሆነ ሁኔታ እንጂ ፍፁም ያልሆነ ሰው የለም። ሁሉም ሰው ክፍቶብህ ከታየህ ከመራገም ይልቅ ነኝ ብለህ ምታስበውን መልካምነት ሁን። ጥላቻ ሲከብህ ነኝ ብለህ ምታስበውን ፍቅር ሁን። ይሄን መሆን ካልቻልክ ግን ሁሌም ቢሆን ማንነትህን ሳታውቅ ትኖራለህ። እራስን መካድ የፈጠረን መካድ ነው። ውብ እና ድንቅ ሆነህ ከተፈጠርክ ውብ ና ድንቅ ሆነህ መኖር ብቸኛው አማራጭህ ነው። ውብ ና ድንቅ ሆኖ የተፈጠረው ደግሞ አንተ ብቻ ሳትሆን ሁሉም ነውና መንገዱን የሳተ ሰው ሲጎዳህ ከመርገም ይልቅ ወደ ውብነቱ ወደ መልካምነቱ የሚመለስበትን ብርሀን አብራበት።

ውብ አዳር❤️

@EthioHumanity
@EthioHumanity

@EthioHumanitybot

Читать полностью…

ስብዕናችን #Humanity

⏳ትላንት አልፏል ስለዚህ ሞቷል።
እከሌ ህይወቱ አለፈ ስንል፡ ሞተ ከአሁን ቡሃላ እዚ ምድር ላይ አይኖርም እያልን ነው። በተመሳሳይ ሁኔታ ትላንት አልፏል (አለፈ) ስንል ሞቷል በህይወታችንም ዋጋ የለውም እያልን ነው። ነገ ደሞ ሚስጥር ነው ካልደረስንበት አናውቀውም።እንዲሁም ነገ ስጦታ ነው ካልተሰጠን አንደርስበትም።ዛሬ ግን በእጃችን ላይ ነው። ስለዚህ ስለ ትላንት በማሰብ ስለነገም በመጨነቅ ዛሬን አናበላሽዉ። ትልቅ ጥበብ ዛሬን መኖር ነው ከዛሬም ደሞ አሁን። ወዳጄ ትላንት ስላሳለፍከው ነገም ስለምትሆነው አትጨነቅ። ነገን ስትደርስበት ህይወት እራሷ ትገልፅልሀለች።

💎የህይወት ትልቁ ስጦታ በህይወት
መኖር ነው። ትዳር የምትመሰርተው ሀብት ንብረት የምታፈራው በህይወት ስላለክ ነው። ህይወት ደግሞ የሚኖሯት እንጂ የሚመልስዋት ጥያቄ ፣የሚፈቷት እንቆቅልሽ አይደለችም።የሆነው ሁሉ መሆን የኖረበት ነው ፣ የሚሆነውም መሆን ያለበት ነው። ለምን ሆነ ? ህይወት ምንድነች ? የመሳሰሉትን በመጠየቅ እራስህን አታድክም። የህይወት ጥያቄዎች ሁሉ መልስ ያለው እራስዋ ህይወት ውስጥ እንጂ አይምሮህ ውስጥ አይደለም።

⌛️አንተ ያስከፋህን ነገር አይደለህም ፡አንተ ያስደሰተህንም ነገር አይደለህም አንተ የሁለቱም መውረጃ ቦይ ነህ የሚያስደስትህም የሚያስከፋህም ነገር በአንተ ውስጥ ያልፉል አንተግን ሁለቱንም አይደለህም። ይህ የህይወት ህግ ነው።

🕰ከ24 ሰአት ውስጥ 12ቱ ብርሀን 12ቱ ጨለማ ነው፣1አመትም በጋና ክረምት ነው ። አየህ በህይወት ብርሀንና ጨለማ በጋና ክረምትም ይፈራረቃሉ።ባንተም በተመሳሳይ መልኩ ማግኘትና ማጣት ፣ማዘንና መደሰት ይፈራረቃሉ ይህ ይሆን ዘንድ ግድ ነው ። በሌላው ከሆነው ይልቅ ባንተ ብቻ የሆነ ምንም የለም። ካንተ በፊትም አሁን በሚኖሩትም የሆነ ነው አንተ ላይም እየሆነ ያለዉ። የሚሟሽ የሚከለስ እንጂ አዲስ መከራ የለም። ፀደይ፣ መኸር፣በልግ እያሉ ወቅቶች እንደሚፈራረቁ ስሜቶችም አንተ ላይ ይፈራረቃሉ።ንዴት ፣ ቁጣ ፣ መረጋጋት፣ መስከን እያሉ ማለት ነው። አስታዉስ አንተ ግን ስሜቶችህን አይደለህም አንተ ከዛ በላይ ነህ።

💎ሰለዚህ ህይወት ምንድናት እያልክ አትጨነቅ ።እስዋ የህፃን ልጅ ሳቅና ለቅሶ፣ የወጣት ድንፋታ ፣የሽማግሌ ስክነት፣ አለቶች ከውሀ ጋር ሲጋጩ የሚያሰሙት ድምፅ፣ ንፋስ የሚያወዛውዘው ቅጠል ይህ ሁሉ ናት። አንተ ግን የህይወትን ሚስጥር በቃላት ለመግለፅ በመሞከር እና ስለትላንት በማሰብ እንዲሁም ስለነገ በመጨነቅ ዛሬን ታበላሻለህ።እውነት ዛሬ ነው! ። ስለዚህ ዛሬን ኑር !

ውብ አሁን❤️

@Ethiohumanity
@Ethiohumanity

@Ethiohumanitybot

Читать полностью…

ስብዕናችን #Humanity

💫"የምትጓዝበት መንገድ ወደ ጥሩ አሊያም ወደ መጥፎ የሚመራው አንተን እንጂ ተመልካችህን አይደለም፤የምትለብሠው ልብስ የሚያሞቀውም ሆነ የሚያበርደው አንተኑ እንጂ የሚያይህን አይደለም፤የምትበላው ምግብ የሚጣፍጠው ወይም የሚመረው አንተን እንጂ ሌላውን አይደለም።

💫ብዙ ውጫዊ ነገሮች አስደሳች ቢሆኑም ከጊዜ ጋር የተሳሰሩና ሃላፊ ናቸው። ዛሬ ያስደሰተን ጓደኛ ነገ ላይኖር ይችላል ዛሬ ያጌጥንበት ውበት ነገ ይረግፋል፤ ዛሬ የተመካንበት አስተሳሰብ ነገ በቆመበት አይጸናም። ከውጪ የምናገኘው ማንኛውም አይነት ደስታ በመጣበት እግሩ ጥሎን መሄዱ አይቀርም። ከዛም አልፎ ዋጋ ያስከፍለናል። ከጊዜ ጋር የማይለዋወጥ ደስታን ለማግኘት ብቸኛ መፍትሄው ደስታና ሰላምን በውስጣችን መፈለግ ነው። እንደ ኩሬ ውሃ ያነሰች፤ እንደ ኩራዝ መብራት የቀጨጨች፤ እንደ ሰናፍጭ ቅንጣት የደቀቀችም ብትሆንም እንኳን ውስጣዊ ደስታን በልባችን መትከል ነው። ይህ ነው ማንም ሊነካውና ሊደፍረው የማይገባው ስፍራ።

✨በርግጠኝነት ለሰው ብለን የምንይዘው ማንነት፤ ለኛ በልክ እንዳልተሰፋ ልብስ አያምርብንም፤ ቀላሉ መፍትሄ እራሳችንን መሆን እና፤ መክሊታችንን መኖር ነው። በዚህ ስፍራ ውስጥ ሙሉ ነን፤ እውነተኛ እኛነታችን የሚታየው በዚህ ስፍራ ነው። ወደ ውስጣችን ዘልቀን በዚህ ስፍራ ላይ ቆመን ህይወታችንን ብናየው፤ እንደምናስበው ደካማ አይደለንም፤ የሚጎድለን ብዙ አይደለም፤ ከምንም በላይ በፈጠረን ፈጣሪ አይን ውስጥ ውብና ንጹህ ነን። ታዲያ ከዚህ በላይ ምን አለ? ደስታና ሰላማችን በሰው እጅ ፤ ፍርድና ቅጣታችን በሰው ወንበር ፈጽሞ አይሁን.!!

ውብ ምሽትን ተመኘን❤️

@EthioHumanity
@EthioHumanity

@EthioHumanitybot

Читать полностью…
Subscribe to a channel