🔆እየጠየቁ መኖር መልስን፣ መልስን ፈልጎ ማግኘት ዕውቀትን፣ እውቀት ነፃነትን፣ ነፃነት ሙሉ ስብዕናን፣ ሙሉ ስብዕና ሠላምና እርካታን፣ እርካታ ደግሞ ደስተኛ ሆኖ መኖርን ያስገኛል፡፡ አብረን እንደግ !! @EthioHumanity @Ethiohumanity ✍የተሰማቹን አጋሩን! ቤቱ ሁሌም ክፍት ነው፣ሃሳባቹን ፃፍፍ አርጉልን @EthioHumanitybot
🕯🕯📜🕯🕯🕯📃🕯🕯🕯📜
ከመሰበር እንቃና፣ከማጎንበስ እንበል ቀና
ሃገር በእኛ እንድትቀና....ሃገር የምትቀናው እውቀት ላይ በተመሰረተ፣ በመከባበር መንፈስ ውስጥ ባደረ፣ ለለውጥ እራሱን ባሰናዳ ባለቅኔ ትውልድ ብቻ ነውና ባለቅኔ የሆናችሁ የነገይቱ ተስፋ ልጆች ተቀላቀሉን! ሃሳባችሁን፣ እምነታችሁን እና እውቀታችሁ እያጋራችሁ በመጋራት መንፈስ ለታላቅነት በእውቀት ክነፉ. .
🕯📃🕯🕯……………🔰🔰
ተቀላቀሉን
👇👇👇👇👇👇👇
@keneyalew
@keneyalew
@keneyalew
@keneyalew
❤️የልብህን ቁስል ትተው የደረትህን ንቅሳት ያደንቃሉ፤ ጫማ ስለሌለህ እግርህ አይታይም ፤ የጭንቅላትህን ዋጋ በኮፍያክ ይተምኑሀል ፤ መከራ ተሸክሞ ሲኖር ያላዩት ትከሻ ኮት ሲለብስ ያጨበጭቡለታል፤ ታሪክህን ጨርቅህ ላይ ስምህን ልብስህ ላይ ለማንበብ ይሽቀዳደማሉ።
🌗እኔ ትንሽነቴን አልረሳም ማወቄም አያመፃድቀኝም ።ጀግና ማለት ታግሎ የጣለ ሣይሆን ታግሎ ያለፈ ነው። ሁሌም ቢሆን እራስህን ተመልከት። የምትወድቀው ሌላውን ለመጣል የሞከርክ ቀን ነው።
ልትጥለው የሞከርከው ሰው ግን ገልብጦህ ከላይ ሆኖ ታገኘዋለህ።
❤️ሁሉንም በገንዘብ እገዛዋለው ብለህ አታስብ በገንዘብ የምትገዛው ርካሹን ነገር እንጂ ውድ ነገሮች የዋጋ ተመን የላቸውም።🙏
ውብ ምሽት
🌗❤️🌗❤️🌗❤️🌗❤️🌗❤️
@EthioHumanity
@EthioHumanity
ሰዓት እላፊ! (የቅዳሚት መዳረሻ!)
❤
".....እኔና አንቺ ተለያይተን እዚህና እዚያ ስንቆም ቃሎቻችን ወደ የት ይሄዳሉ? ያልኩሽ÷ ያልሺኝ÷ የተባባልናቸው ነገሮች መጨረሻቸው ምንድነው?
Does they even exist anymore?°°°°?
📝እሱባለው አበራ ንጉሤ
@EthioHumanity
@EthioHumanity
ለጁምኣችን!
💚
ብርሌ በመሰለ ዓለም ፡ መውጪያው ጠባብ በሆነ ፡ በግንባር መደፋት ማለት ማምለጥ ነው ፡ መቃናት ማለት መቅረት ነው ።
📝fksh Ayelgn
በዙፋን ላይ ካለ ንጉስ በሱጁድ ላይ ያለ ሙእሚን ይበልጣል!!
አላህም እንዲህ ብሎ እውነትን ተናገረ
(و اسجد و اقترب) 19 – العلق
«ስገድ፤ወደ አላህ ተቃረብም።»
.
.
አንድ ሰው ከአላህ ይበልጥ ቅርብ የሚሆነው ሱጁድ ላይ እያለ እንደሆነ የአላህ መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) ተናግረዋል።
ኢብነል አልጀውዚ ውብ የሆነ ንግግር አላቸው....
የአላህን ስፍር ቁጥር የለሽ ውለታ ብትገነዘብ ኖሮ ነፍስህን የሃያጥት ባሪያ ባላደረካት ነበር። አላህ "ኢብሊስን" ከእዘነቱ ያባረረው ላንተ የክብር ሱጁድ ለማድረግ አሻፈረኝ በማለቱ መሆኑን እንዴት ዘነጋኸው? ... አግራሞትን የሚያጭረው ጉዳይ የጠላትህ ኢብሊስ ወዳጅ በመሆን ወዳጅህ የሆነው አላህን መክዳትህ ነው።
ከመንገዱ በፊት!!!!!
ረጅም ነው ዙሩ፤ የዱንያ ጎዳና፤
በመሮጥ በመክነፍ፤ መች ይደረስና፤
እባክህ ጀሊሉ፤ ሶብር ይዘህ ናማ።
የመንገዱ ነገር፤ አቀበት ጉብታው፤
ቁልቁለት ሸለቆ፤ ሜዳና ኮረብታው፤
አላስኬድም ካለ፤
ገደላ ገደሉ፤ጭቃና ዝቅታው፤
ከመንገዱ በፊት፤
በርከክ ሲሉ ነው፤ ቁጥሩ የሚፈታው።
እናማ፤
ከመንገዱ በፊት፤
መንገዱን ጀምረው፤ ስጁድ ያለፋቸው፤
ይኸ ሁላ መንገድ፤
በሩጫ ሚደፈር እየመሰላቸው፤
ተቆጥረው አያልቁም፤
መንገድ እየሄዱ፤መንገድ የበላቸው።
እመዋ እመዋ!!!!
((( ጃ ኖ )))💚💛❤
ሸጋ ጁምኣ!💚
@EthioHumanity
@EthioHumanity
@Nagayta
ሸጋ ብስራት!
📗📒📕
ጀመኣው እንዴት አመሻቹ.... ማንበብ ለሚወዱ ብቻ ሳይሆን የድሮ መፅሐፍት መሸመት የምትወዱ ሰዎች በየአመቱ ሰፍ ብለን የምንጠብቀውን የጠፉ መፅሃፍት አውደርእይ ተዘጋጅቷል።
እስጢፋኖስ ቤተክርስቲያን ፊትለፊት የሚገርም የከተማ ማእከል አለ::
እዚያ ከመጋቢት 24-26 ከች በሉና ያሻችሁን ሸምቱ!!!
@EthioHumanity
@EthioHumanity
@balmbaras
ለውብ ቀን!
💚
፩ (አንድ)
ግለ-ሰብ የትግል አርማ ሊሆን አይገባም። የትግል አርማ መሆን ያለበት የትግሉ ውጤት ነው። ግለሰብ ግለሰብ ነው። ይውሸለሸላል፤ይማልላል፤ይሻፍዳል፤
ይታበያል፤ይሰርቃል ፤ይደክማል ፤ይሳሳታል፤ ይደለላል። ግለሰብ ላይ የተንጠለጠለ ድል ግለ-ሰብ ላይ ያልተንጠለጠለ ስርአት ካልተዘረጋ ድሉ ድል አይደለም ።
፪ (ሁለት)
በየትኛውም የግፍ ዘመን ውስጥ ዳር ሆኖ ያየ ትልቅ ነኝ ባይ፤ የተሳተፈ ፤ዝምታን የመረጠ አባት፤ ያልመከረ ምሁር ፤ በደልን ያስተባበለ አንዱም ሳይቀር በየደረጃው ሃጥያተኛ ነው።
፫ (ሷስት )
.....
ብልህ በተበጀለት ሽል ውስጥ ሆኖ አይወራጭም። የራሱን መወራጫ ነገን ያማከለ ርእይ በውብ ሃሳብ በልኩ ያጎለብታል እንጂ ።
፬ (አራት)
ከተወለድንበት ሰፈር፤ ከምንከተለው ሃይማኖት ፤ አሽቆልጠን ከምናገኘው ፍርፋሪ፤ ግዜ ከሚያፈዘው ስልጣንም ሆነ ሳንቲም ሁሉ ሰውነት ይገዝፋል።
፭ (አምስት)
ሁሌም ጥግ ለጥግ ሆነው ከሚካረሩት አክራሪዎች ይልቅ መሃል ላይ ያሉ እንዳይበጠስ የሚዳክሩት ቅዱስም ምስጉንም ናቸው🙏🙏
ውብ ቀን!💚
@EthioHumanity
@EthioHumanity
@balmbaras
💎ፊት ለፊት ትይዩ የተገነቡ ሁለት ቤቶች አሉ ። በሁለቱ ቤቶች ጣሪያዎች ላይ ደግሞ የእግር መርገጫ ስፋት ብቻ ያለው የጣውላ መረማመጃ ድልድይ ቢጋደምና በላዩ ላይ ተራምዳችሁ ከአንዱ ጣርያ ወደሌላው እንድትሻገሩ ብትጠየቁ ፈቃደኛ ላትሆኑ ትችላላችሁ ። ይኸው ጣውላ መሬት ላይ ተጋድሞላችሁ እንድትራመዱበት ብትጠየቁ ግን ህፃን ፣ ወጣት ፣ አዛውንት ሳይባል ፣ ሁላችሁም ሳትወድቁ ትራመዱበታላችሁ ።
📜 የጣውላ መረማመጃው ያው ነው ፤ እናንተም ያው እናንተው ናችሁ ፤ ታድያ ጣውላው በቤቶቹ ጣሪያዎች ላይ በተጋደመ ጊዜ እንድትራመዱበት ስትጠየቁ ለምን እምቢ አላችሁ? መሬት ላይ በተደጋጋሚ ጊዜ ብዙ ሰዎች ሳይወድቁ ተረማምደውበታል ። ታድያ ችግሩ ምንድን ነው? ችግሩ ያለው ሌላ ቦታ ነው ።
🔑 መሬት ላይ ተጋድሞ ሳለ ጣውላው ላይ ለመረማመድ ንቁ መሆን አያስፈልግም ።ንቃት አልባ ሆናችሁ ልትራመዱ ትችላላችሁ ። በጣውላው ላይ ተረማምዳችሁ ከጣሪያ ጣርያ ለመሻገር ግን ንቁ መሆን ይኖርባችኋል ። ንቃት እንደሌለን እናውቃለን ፤ በዚህም ምክንያት ወድቀን እንዳንሞት እንፈራለን ። መሬት ላይ ስንራመድ ግን ብንወድቅ እንኳን እንደማንሞት እናውቃለን ።
💎 አልፎ አልፎ አደጋ በሚያጋጥመን ቅፅበት ንቃት ይኖራል ። ሌላ ግዜ ግን እንቅልፍ ላይ ነን ። ሞት ሲቀርበን ንቃት ይኖራል ፤ አለዚያ ግን ንቁ አይደለንም ። ልማዶቻችንን መቀየር የማንፈልገው ለዚህ ነው ፤ ምክንያቱም ልማዶች ሲለወጡ ንቁ መሆን ያስፈልጋል ። አሮጌ ልማዶች የእናንተን ንቃት አይፈልጉም ።
📖 የንቃት ፀሃይ /ኦሾ/
ገጽ 99-100
ትርጉም ✍ መርሻ በነበሩ
💎🔑💎🔑💎🔑💎🔑💎🔑💎🔑
@EthioHumanity
@EthioHumanity
✍ @EthioHumanitybot
❤️" ፍቅር የሚጀመረውም ሆነ የሚፈፀመው በራሱ ነው። እናንተ ልትጨነቁበት አይገባም። ከእናንተ በላይ ነው። ከእናንተ እጅግ የገዘፈ ነው።
እናንተ ግን ፍቅርን ልትቆጣጠሩት ወደ ምትችሉት ግንኙነት ቀየራችሁት። ለዚህም ነው እናንተ ወደ ፍቅር ሀይል ያልገባችሁትና ስለሱም ምንም የማታቁት። የእናንተ ራስወዳድነት ሊቆጣጠረው አይችልም። ራሳችሁን በቁጥጥር ስር አውላችሁአል።
💙ማንም ፍቅርን ሊጀምር አይችልም። ልክ እንደ ማብርያና ማጥፍያ የምታበሩትና የምታጠፉት አይደለም። ራሳችሁን ብቻ በአሁኑ ጊዜ ብቻ አስቀምጡት። ሲሆን ይሆናል። ከምንም ተነስቶ ነው የሚፈጠረው። ልክ እንደ መሬት መንቀጥቀጥ ይወዘውዛችሁአል ከስራችሁ ይነቅላቹሃል ከእግራችሁ በታች ያለው መሬት ይጠፋል። ለዚህ ነው ፍቅር "በፍቅር መውደቅ" ተብሎ ሚጠራው። ራሳችሁን መሆን ታቆማላችሁ። መቆጣጠሩ ስነምግባሩ በፍቅር ውስጥ ቦታ የለውም። መጀመር ሳትችሉ እንዴት ልታቆሙት ትችላላቹ?
የፍቅር መንገዶች ከናንተ በላይ ናቸው። ትክክለኛውን ጊዜ ለማወቅ አይቻላችሁም።
❤️በፈለጋችሁ ጊዜ ጀምራችሁ ምትጨርሱት ፍቅር እርሱ ፍቅር አይሆንም ። ሰው ሰራሽ ነው የሚሆነው።በሚስቱ ቁጥጥር ስር ያለ ባል አስቀያሚ ፍቅር የማያውቅ ፍቅር የማይገባው ይመስላል። ስለዚህ ሚስቱ እራሷ ከልብ ልታፈቅረው አትችልም። ለናንተ ባርያ የሆነች ሴት እንዴት ልታፈቅሩ ትችላላችሁ?
💙ፍቅር በጓደኞች መካከል እንጂ በባርያና በጌታ መካከል አይሆንም። ባርያን ልታዙ እንጂ ልታፈቅሩ አትችሉም። ፍቅር ሊያፈቅር የሚችለው እኩዮችን ነው።"
✍ኦሾ
@EthioHumanity
@EthioHumanity
🌗የሌሊት ወፍ
🌙“የሌሊት ወፍ በቀን የመኖር ስልጣን የላትም” ይላል ምንጩ ያልታወቀ የጥንት አፈ-ታሪክ፡፡ “ለዚህ ነው ሌሊቱን እየጠበቀች ከመሸ ተደብቃ ወጥታ ሳይነጋ ተደብቃ የምትገባው”፡፡
🌗በጥንት ጊዜ በሰማይ አእዋፍና በምድር አራዊት መካከል ውጊያ ነበር ይባላል፡፡ የአሁኗ የሌሊት ወፍ ያን ጊዜ እንደማንኛውም የወፍ ዝርያ ነበረች፡፡ ይህቺ ወፍ (የአሁኗ የሌሊት ወፍ) በውጊያው ጊዜ የምድር አራዊት ሲያሸነፍ ለእነሱ ታግዝ ነበር፤ የሰማዩ ሲያሸነፍ ደግሞ ተገልብጣ ለእነሱ ታግዝ ነበር፡፡
🌗አንድ ጊዜ ግን እነዚህ ሁለት ጸበኞች ታረቁና የጦርነቱ ሁኔታና ትውስታ ሲነሳ ምን ስታደርግ እንደነበረ ታወቀባት፡፡ ከዚያ ቀን ጀምሮ በሁሉም የተጠላችና የተገፋች ወደመሆን ስለመጣች በቀን የመኖር ስልጣኗን አጣችና ሌሊት መኖር ጀመረች ይባላል፡፡
🌙አስመሳይነት፣ ሁለት መልክ ያለው ሕይወት፣ አቋም የለሽነት፣ ውሸተኛነት፣ አታላይነት፣ መስሎ አዳሪነት፣ ባለ ሁለት ምላስነት፣ ሸንጋይነት፣ ለሆድ አዳሪነት . . . የዘመኑ ችግር!
🌑የብዙዎችን በነጻነትና ቀና ብሎ በድፍረት የመኖር አቅም ያሳጣ የዘመኑ ወረርሽኝ!
አስመሳይ ሆነህ ወዳጅህ ከሚበዛ፣ እውነተኛ ሆነህ ጠላትህ ቢበዛ ይሻላል፡፡ ሁለት መልክ ይዘህ ትርፋማ ከምትሆን፣ አንድ መልክ ይዘህ ባለህ ነገር መኖር ይሻልሃል፡፡
✍ከዶ/ር እዮብ ማሞ
በሰላም እደሩ❤️
🌙🌗🌙🌗🌙🌗🌙🌗🌙🌗
@EthioHumanity
@EthioHumanity
🔱በሌሎች ስኬት አትቅና!
💫“ቅንአት (jealousy) ሲብራራ፣ አንተ ያለህን ነገር ወስጄ የእኔ ማድረግ እፈልጋለሁ የማለት ስሜት ሲሆን፣ ይህ ቅንአት መራራነት (resentment) ሲጨመርበት፣ አንተ ያለህን ነገር የእኔ ማድረግ እፈልጋለሁ፣ አንተ ደግሞ ምንም ነገር እንዲኖርህ አልፈልግም ወደሚለው ከረር ያለ ስሜት ይሻገራል . . . ወደመራራነት የተሸጋገረ ቅንአት ፍትህ እንደጎደለ ከማሰብ ሊመጣ እንደሚችልና ከዚያም ባሻገር በውስጣችን ከተደበቀ በራስ ያለመተማመንና የዝቅተኝት ስሜት ሊነሳ ይችላል፡፡
🔱በሕይወትህ ከሌሎች የምትሻልበት ነገር እንዳለህ ሁሉ ሌሎች ሰዎች ከአንተ የሚሻሉበት ነገር እንዳለም አምነህ ተቀበል፡፡ ይህንን አመለካከት ከመብለጥና ከመበለጥ ስሜት አንጻር ሳይሆን አንተ እንዲሳካልህ የመፈለግህን ያህል ሌሎችም እንዲሳካላቸው ከመፈለግ አንጻር ልትይዘው ይገባሃል፡፡ በሌሎች ሰዎች ስኬት የሚቀኑ ሰዎች ልቀው በተገኙበት መስክ ሳይቀር የተበለጡ ሰዎች ናቸው፡፡ ምክንያቱም ትኩረታቸውን ከግባቸው ላይ አንስተው ሌላውን ሰው ለመጣልና በልጦ ለመገኘት ስለሚጣጣሩ ነው፡፡
💫አንዳንድ ሰዎች በአንድ አቅጣጫ ልቀው የሚገኙት ምናልባት ለዚያ ነገር ከአንተ የተለየ ትኩረት ስለሰጡት ሊሆን ይችላል፡፡ ምክንያቱ ያም ሆነ ይህ አንተም ደግሞ ከእነዚ ሰዎች የተሻልክባቸው ሁኔታዎች እንዳሉ በማሰብ ወደፊት ካልቀጠልቅ ከቅንአት ህመም አታመልጥም፡፡
🔱ሰውን ለማሸነፍ ከመሯሯጥ ወጥተህ ራስህን በማሸነፍ ወደ ትክክለኛ ስኬት ለመድረስ ከፈለግህ በመጀመሪያ ከዓላማህና ከራእይህ ጋር የሚመጥን ግብ ማውጣት አለብህ፡፡ የዚህ ግብህ ከፍታ በፍጹም ከሌላው ሰው ሁኔታ ጋር መነካካት የለበትም፡፡ የሌላው ሰው ስኬት የራስህን ግብ ለመከታተል ሊያነሳሳህ ይገባል እንጂ ወደ ፉክክር ሊጨምርህ አይገባም፡፡
(“ራስን ማሸነፍ” ከተሰኘው የዶ/ር ኢዮብ መጽሐፍ የተወሰደ)
መልካም ምሽት
🔱💫🔱💫🔱💫🔱💫🔱💫
@EthioHumanity
@EthioHumanity
#ዛሬ ሽቅርቅሯ ቅዳሚት ነች..❤ አንድ የቻናላችን ቤተሰብ የሆነች እንዲህ አለችኝ.... በእርግጠኝነት እንደኔ ይሄ ነገር የሚሰማቸው ፣ ግራ የሚያጋባቸው ፣ የተጎዱበት ......ህመሜ ህመማቸው ይኖራሉ እና ይሄን እዚህ ቻናል ላይ ለጥፍልኝ አለችኝ.....#ከዚህ በታች ያለውን ስሜቷን ህመሟን ግራ መጋባቷን እንዲህ አስቀምጣዋለች......#ምናልባት ይሄን የምታነቡ ቤተሰቦች እናተም በዚህ ነገር ውስጥ ናቹ ወይንም አልፋችሁት ይሆናል........ተጋበዙልኝ🙏🙏
👇👇👇
በቃ አንዳንዶች አሉ
.
.
ፍላጎታቸው በትክክል ምን እንደሆነ የማይገቡህ::
የትውውቃችሁ መጀመሪያ አከባቢ ጥሩ ይሆኑልህና ከትንሽ ግዜ በኋላ
የሚቀየሩብህ::አንተን የፍቅር ስሜት ውስጥ ከከተቱህ በኋላ ከነሱ ተመሳሳይ ስሜት
ስትፈልግ የማይመልሱልህ::
.
.
...በቃ አንዳንዶች አሉ!
.
.
ካንተ ጋ መሆን እየፈለጉ ነገር ግን በህይወቴ ሌላ ሰው ቢመጣስ ብለው ወይም ደግሞ
ባለፈ የፍቅር ህይወታቸው ፍራቻ ፍቅርህን የማይቀበሉ::የማይሸሹህ!..የማይቀረቡ!..ሄዱ
ስትላቸው የሚመጡ!..መጡ ስትላቸው የሚሄዱ::
.
.
በቃ አንዳንዶች አሉ!
.
.
ሌላ ሰው እስከሚተዋወቁ አንተን እንደ ባጣ ቆየኝ የመጠቀሙ!
.
.
በቃ አንዳንዶች አሉ!
.
.
ሁሌ አንተ ቀድመህ መልዕክት እንድትልክላቸው ወይም ደግሞ እንድትደውልላቸው
የሚፈልጉ!አንተም አያስችልህም መልዕክት ትልካለህ!..ትደውላለህ!...እንደ ነገሩ
ያዋሩሀል!..ግን ደግሞ ብልጦች ናቸው!...ጨርሰህ እንድትለያቸው ስለማይፈልጉ ተስፋህን
ሙሉ ለሙሉ አይነጥቁህም!..ጭላንጭል ያስቀሩልሀል!..አንተም የቀረህን ጭላንጭል
ተስፋ ይዘህ አብረሀቸው መንገድ ትቀጥላለህ!
.
.
የሆነ ሰዓት ይሰለችሀል!ልትደውልላቸው ስልክህን ታነሳና መልሰህ
ታሰቀምጠዋህ!..ከራስህ ጋ ብዙ ትታገላለህ!..በመርሳትና በፍቅር ስሜት መሀል ሆነ
ለረጅም ግዜ ዝምምም ትላቸዋለህ::
.
.
የዚህን ግዜ የነሱ ተራ ይጀምራል!..እያንዳንዷ የተሰማህ ስሜት የሰማቸዋል!..እያንዳንዷ
ያመምህ ህመም ያማቸዋል!...ይቁነጠነጣሉ!..አስር ግዜ መልዕክት
ይልኩልሀል!...ይደውሉልሀል!...ቀን ሙሉ ያስቡሀል!
.
.
በቃ አንዳንዶች አሉ!...
.
.
ፍቅር ስትሰጣቸው ጀርባ ሰጥተውህ ስትርቃቸው የሚከተሉህ!
.
.
ስታዋራቸው ዝም ብለው ዝም ስትላቸው የሚያዋሩህ!.!
.
.
ግራ የተጋቡ!የተወሳሰቡ..በትክክል ፍላጎታቸው ምን እንደሆነ የማትረዳቸው!....
.
✍ፀዲ
ሀሳብ ካላቹ ....ማካፋል ትችላላችሁ 🙏
ሽብርቅርቅ ያለች ቅዳሜ!❤
@EthioHumanity
@EthioHumanity
@Nagayta
✨ውበትን ማድነቅ
🔆አለምን የናቀ አንድ መነኩሴ ከሌሎች መነኩሴዎችጋር አብሮ በመንገድ ሲሄድ እጅግ አብዝታ የተዋበች ቆንጆ ሴት አይኑ ውስጥ ትገባለች፡፡ መነኩሴውም በሴቷ ውበት እጅጉን በጣም ከመደነቁ የተነሳ አይኑን ከሷ ላይ መንቀል ጭራሽ አቃተው፡፡ ይህን ድርጊቱን የተመለከቱ አብረውት የነበሩት ሌሎች መነኩሴዎች በድርጊቱ በአፍረት ተሞልተው ተጠጉትና፡-
✨‹‹ወንድማችን አንተ አለምን እንደኛ የናቅህ መነኩሴ ሆነህ ሳለ በሴት ልጅ ውበት እንዲህ ተደንቀህ ፈዘህ ስናስተውልህ አዝነናል፡፡ አለማዊ ድርጊት እየፈፀምህ መሆንህን አላስተዋልክምን?››በማለት ይጠይቁታል፡፡
🔆‹‹ወዳጆቼ በዚህች ቆንጆ ሴት ውበት ውስጥ እየተመለከትኩ የማደንቀው ውበትን እንዳሻው እየለዋወጠ በስራው የሚደሰተውን ፈጣሪዋን እንጂ እሷን አልነበረም፡፡ አይኖቼ የተዋበን ስጋ ሳይሆን የተዋበ ነገር የሚፈጥረውን ፈጣሪ ለማየት እንደተሰሩ አምናለሁ፡፡ በዚያም የተዋበን ነገር መፍጠር የሚችለውን የአምላክ ችሎታ ሥጋ ለብሶ አየዋለሁ መደነቄም በዚህ የተነሳ ነው፡፡››በማለት መለሰላቸው፡፡
✨በውበት ውስጥ የምናደንቀው የተፈጠረውን ነገር ብቻ ሳይሆን ከበስተጀርባው ሆኖ ያንን የተዋበ ነገርን የፈጠረውንም ማድነቅ ከቻልን በርግጥም ታላቅ ፀጋና ጥበብ ከኛ ጋር ነው፡፡
ውብ አሁን!!!❤️
✍ነፀብራቅ ብርሀኔ
✨🔆✨🔆✨🔆✨🔆✨🔆✨🔆✨🔆
@EthioHumanity
@EthioHumanity
🌗"ትጋት የተስፋ ልጅ ናት።"
🌗 "ዛሬ ላይ ሆኜ ሳስበው በሕይወቴ ውስጥ መልካም ነገሮች ወይም ስኬት ብዬ ከማስባቸው ውስጥ ማስተርስ ዲግሪዬ ወይም ዶክትሬት ዲግሪዬ አይደለም፡፡ ልጆቼ፡ ትዳሬ፡ ቤቴ ናቸው! በሕይወቴ ትልቁ ቁም ነገር ትልቁ ስኬት እነርሱ ናቸው! እናም አሁን ሳስበው የተጓዝኩበት የሕይወቴ አቅጣጫ ትክክል ነበር፡፡ አካሒዴም በእኔ ምኞት እና መምህሬ ባሰበልኝ ሳይሆን ፈጣሪ በመረጠልኝ ስለነበር በጎ መሆኑን የኋላ ኋላ ተገንዝቢያለው፡፡
🌙እናም በሰዎች ዘንድ ተስፋ የሌለን ብንመስልም እንኳን ዋናው ነገር በፈጣሪ ዘንድ ያለው ተስፋችን ነው፡፡ ሕይወት ጠመዝማዛም ብትሆን ውብና ተስፋን የተሞላች ናት! በዚህ ዓለም ሁሉም ነገር አበቃ አከተመ! ባልንበት ጊዜ የሚቀጥል የተሻለ እድል! የምናውቀውና የተለመደው በር የተከረቸመ ቢመስልም ወለል ብሎ የሚከፈት ሌላ በር ዙሪያችን! ጭው ያለ በርሃ ቢሆንም የለመለመ መስክ የሆነ ስፍራ ላይ እንዳለ ተምሪያለው፡፡
🌗ዕድል ፊቷን ያዞረችብን በመሰለን ጊዜም ቢሆን እንኳን አብዝቶ በትጋት መጓዝ እንጂ ተስፋ መቁረጥ አይገባም፡፡ ትጋት የተስፋ ልጅ ናት። ተስፋ ደግሞ በእኛ እና በፈጣሪ መካከል የእምነት ድልድይ ስለመኖሩ ማረጋገጫ ነውና! "
🗞ከሰበዝ መጽሃፍ የተመዘዘ/ገጽ 97/
ጣፋጭ እንቅልፍ❤️❤️
🌗🌙🌗🌙🌗🌙🌗🌙🌗🌙🌗🌙
@EthioHumanity
@EthioHumanity
ሰዓት እላፊ!
💚
"ሌሎችን በማፅናናት የተዋጣላቸው ሰዎች ራሳቸውን ማፅናናት ግን አይቻላቸውም"
ጊዜው 94 ዓመታትን ወደ ኃላ ይወስደናል... በወቅቱ አንድ ራሺያዊ ከያዘው ድብርት እና ጭንቀት እንዲገላግለው ምክር ፍለጋ ወደ ሳይካትሪስት ይሄዳል... ዶክተሩም አስፈላጊውን ምርመራ ካደረገ በኃላ እንዲ ሲል ምክርን ለታማሚው ይለግሳል...
"አሁን ካለህበት ለመውጣት አስጨናቂ እና አሳዛኝ ከሆኑ ነገሮች መራቅ ይኖርብሃል... ይህ በዕለት ተዕለት ህይወትህ እንደ ልማድ ካደረከው ንባብ ላይም ጭምር ይሁን... አስጨናቂ ፣ ዘግናኝ ፣ አስፈሪ እና አሳዛኝ ታሪክ ካላቸው ንባቦች መራቅ አለብህ... በምትኩም አስደሳች እና አዝናኝ (Comic Stories) ማንበብ አለብህ ለምሳሌም የሚካኤል ዙሽንኮ (Mikhail Zushenko) ፁሁፎችን አንብብ "
ይሄን ጊዜ ታማሚው ለዶክተሩ የሰጠው ምላሽ ዶክተሩን አስገረመው
"እኔኮ ሚካኤል ዙሽንኮ ነኝ"
ለፁሁፉ መጀመሪያ የተጠቀምኩት የ Albert Hubbard አባባል ይህን የ ሚካኤል ዙሽንኮን ታሪክ በትክክል ገላጭ ነው
Those who are good at comforting and comforting others often fail to console themselves...
➬ ሰላም እደሩ!💚
@EthioHumanity
@EthioHumanity
@Nagayta
☯ ደስታችሁ በግልፅ የሚታይ ሀዘናችሁ ነው ። ሳቃችሁ የሚመነጭበት የዓይናችሁ ጉድጓድም አብዛኛውን ጊዜ በራሳችሁ እንባ የተሞላ ነው ። ከዚህስ ሌላ እንዴት ሊሆን ይችላልን? ....
💙 << ሀዘን የበለጠ ጠልቆ በውስጣችሁ በተቀረፀ ቁጥር የበለጠ ደስታ ማግኘት ትችላላችሁ . . .
💜<< ደስ ሲላችሁ ዘልቃችሁ ወደ ልባችሁ ውስጥ ተመልከቱ ። የዚያኔ ደስታን እየሰጣችሁ ያለው ያ ሀዘን ሰጥቷችሁ የነበረ ነገር ብቻ እንደነበር ትደርሱበታላችሁ . . .
☯ << ሀዘን ባጠላባችሁ ጊዜም እንደገና ወደ ልባችሁ ውስጥ ጠልቃችሁ ተመልከቱ ። አሁንም በእውነቱ የምታለቅሱት በዚያ ደስ ሲያሰኛችሁ በነበረው ነገር መሆኑን ትገነዘባላችሁ . . .
💙<<አንዳንዶቻችሁ <ሀዘን ከደስታ ያይላል> ትላላችሁ ። ሌሎቻችሁ ደግሞ <የለም የሚያይለው ደስታ ነው> ትላላችሁ ። እኔ ግን የማይነጣጠሉ መሆናቸውን እነግራችሁዋለሁ . . .
💜 የሚመጡትም አብረው ነው ። አንዱ ለብቻው ገበታችሁ ላይ ሲቀመጥ ፣ ሌላኛው በአልጋችሁ ላይ መተኛቱን አስታውሱ . . .
☯እውነት እውነት እላችዋለሁ ፣ ልክ እንደ ሚዛን በሀዘናችሁና በደስታችሁ መካከል ተንጠልጥላችሁዋል ። ሳታጋድሉ ሚዛናችሁን ጠብቃችሁ የምትቆዩት፣ባዶ በሆናችሁ ጊዜ ብቻነው ።
✍ካህሊል_ጅብራን
ውብ አሁን❤️
☮💜☯💙☯💙☯💙☯💙
@EthioHumanity
@EthioHumanity
@EthioHumanitybot
ለሰንበታችን!
💚
የመኖራችን ህያው ምልክት ፣ የትናንሽ ትውስታ ሰነድ ፣የትናንት መንገድ አሻራ ፣ የዛሬ እውነት የነገ ታሪክ ፣ የትናንሽ ትርክት ዳና ፣ የነገ የገዘፈ ጣዕማም ሀውልት ይመስለኛል ትዝታ ለኔ።
ዛሬን በትናንት መነፅር ስመለከተው የመግዘፍም የመስነፍም ማንነት በህይወቴ ብራና ላይ ተከትቦ ይገኛል ፣ ከአትሮኖሱ አኑሬ ሳስሰው ፣ ስፈትሸው ደግሞ ይህ ነው የህይወት መስህቡ ፣ የመኖር ውሉ ያሰኘኛል....እንደ እድሜዬ ሁሉን ላይ መታደልን ደግሞ ኖርኩት ያሰኛል።
የአፍላነት የፍቅር ትኩሳት የሚጀመርባት ፣ በተወጋ እና የደም ነጠብጣብ ያሸበረቀ የደብዳቤ ዘመን ፍቅር ፣ የየዋህነት ዓለም ፣ ምግብ የማያስበላ ስሜት ፣ የአመት በዓል ፖስት ካርድ ፣ ንፁህ ስሜት ፣ ከቁሳዊ አለም የራቀ ቁርኝት ፣ ብዙ ያለመመኘት ፣ በትንሽ የመርካት እድሜዬ ውል ትለኛለች
ለፀብ ተጋግዘን ፣ ተቧድነን የምንራኮትበት ፣ እንደምን ናቀከኝ ብለን የተቧቀስንበት ፣ ስለት የመያዝ ትልቅ ጀብድ የሚያሰኝበት ፣
ጉርምስናዬ ትናፍቀኛለች ፣
በዚህ የእኔ የህይወት አምድ ውስጥ አብራችሁ የከተማችሁ ፣ በህይወት ግሳንግስ ላለመውደቅ የምትባትሉ ፣ የህይወት ማዕበል ወደ እዛኛው የህይወት አለም የገፋችሁ ፣ እንደ ምሰሶ በጠነከረ ወዳጅነት ዛሬ ድረስ የዘለቃችሁ ነፍሴ አብዝታ ታከብራችኋለች..... የትዝታ ማህደራችሁን እየፈተሻቹ ትናንታችንን ታስዳስሱን ዘንድ እየተጠየቃችሁ ካላችሁበት ይህን ዘፈን ተጋበዙልኝማ
ወንድሙ ጅራ
የእኔ ትዝታ
መልካም ሰንበት!💚
@EthioHumanity
@EthioHumanity
እምወድሽዋ!❤ቅዳሜዋ!❤ሸጋዬዋ!❤
የግጥም ጥግ (ርዕሱ አይደለም) ዛሬ ደርባባዋ ቅዳሚት ነች!❤ እና የዛሬ ቀናችንን ለቅዳሜ በሚመጥኑ በልኳ በወርዷ ልክክ ባሉ ግጥሞች ስንሞሽራት እንውላለን!!❤ የግጥም ጥግ አንድ...
ማነህ ላለኝ ....
በዘመን ላይ የበቀልኩ
የአንድ ሰሞን አበባ ነኝ ።
📝ቴዎድሮስ ካሳ
ኦ ፥ የሽቱዉ ቅመም
የሁሉ ቃና
እባክህ አትሂድ ፥ እባክህን .. ና !
ሁሌም ከጎኔ እንደክንፍ ኹነኝ
ከሚንበለበል ከኩራዝህ ፍም ፥ እንደ እሳትራት ለሞት አቅርበኝ ።
~
በልቤ ፍሰስ በልቤ ሙላ
ሌት ቀን ስባዝን የሚያጫዉተኝ ፥ ካንተ በስተቀር ምናለ ሌላ !!
የመናፈቅ ጥም ጉም ካለበሰዉ
ቀረበኝ ያልኩት እየነካካ ከሚያስለቅሰዉ
ከስጋየ ስር ፥ ከዚህ ቀርቀሃ
ከነፍሴ በታች ካለዉ በረኻ
ማነህ ተጫዋች ፥ ባለ ሙዚቃ
ይኸን ሙት በድን የምታስደንስ በጠፍ ጨረቃ
✍ቴዎድሮስ ካሳ
ሸጋ ሸጊቱ ቅዳሜ!❤
@EthioHumanity
@EthioHumanity
@Nagayta
🛑 አንድ ሊቅ ተጠየቀ :- ማነው ብልህ . . . ? ቢሉት - ከእያንዳንዱ ሰው ሊማር የሚችል
~ ማነው ጠንካራ ሰው ? ስሜቱን የሚቆጣጠር ,
~ ማነው ሀብታም ቢሉት . . . በቃኝን የሚያውቅ ,
~ ማነው የተከበረ ሰው . . . ሰውን የሚያከብር ,
~ ማነው ቶሎ ነገር የሚገባው ? ቢሉት . . . በትዕግስት ሰውን የሚያደምጥ ሰው ,,
ድንቅ ሊቅ ድንቅ እይታ❤️
ውብ ቀን❤️
✍ በዓሉ ግርማ ' ሀዲስ
@EthioHumanity
@EthioHumanity
ማራኪ ገፆች! (ለምሽታችን)
📗📗
ጀመኣው ዛሬ ከመሸ የመጣሁት ስለ አንድ ቆንጆ መፅሀፍ ማራኪ ገፅ ለመግለጥ ነው። "የመሀል ልጅ" ይሰኛል በቤዛዊት ዘሪሁን በቅርብ የወጣ መፅሐፍ ነው።ከመፅሐፉ ማራኪ ገፆች ከመቆንጠራችን በፊት ግን አንድ ማለት የምፈልገው እና ሁሌ ጥያቄ የሚሆንብኝ ነገር አለ። እሱም ምንድነው እንደ ሌሎቹ የሙያ ዘርፎች የሴት ደራሲያት ቁጥር እጅግ በጣም አነስተኛ የሆነበት ምክንያት ምንድነው ? እስቲ ምክንያት ብላቹ የምታስቡትን ነገር ብትነግሩኝ ደስ ይለኛል ። ከቀድሞቹ ማለት ከአንጋፋዎቹ የሴት ደራሲያት የተሳካላቸው 4 ሴቶችን አውቃለሁ ፀሐይ መላኩ ፣ የዝና ወርቁ ፣ ሕይወት ተፈራ ፣ ውዳላት ገዳሙ ....በኔ ትውልድ ደሞ የተሳካላቸው ጥራ ብባል በእኔ የንባብ እውቀት ሜሪ ፈለቀ ብዬ አፌን ሞልቼ እናገራለሁኝ ምናልባት ወደፊት እንደ ቤዛዊት አይነት ደፋር ደራሲያት ከመጡ ቁጥሩን ከፍ ያደርጉታል ብዬ አስባለሁ። መፅሐፉን ገዝታቹ ብታነቡት ትጠቀሙበታላቹ በጣም ደስ የሚሉ ፍልስፍናዎች የያዘ ሸጋ መፅሐፍ ነው። ከመፅሐፉ ማራኪ ገፆች አንዱን እንግለጥ እንግዲህ.........
.
.
.
የኛ ሰው <ጦስህን ይዞት ይሂድ> የሚያውቀው ብርጭቆ ስትሰብር ብቻ ነው አንተ ስትወድቅ ግን <ብዬ ነበር> ይላል እንጂ ማንም እጁን ሰዶ ሊያነሳህ አይጥርም አይዞህ እኔም አልፌበታለሁ ማለት ክብሩን መሳት ይሆንበታል ። ደግመህ እንደማትንሰራራ እርግጠኛ ነው። ምፅ ብሎ በቁምህ ይቀብርሃል። ከትቢያ አራግፈህ ለመነሳት ትንፈራፈራለህ ምፅ ይሉልሀል ምፅ እናቱ ሞታ እኮ ነው ምፅ በጣም አንባቢ ስለነበር እኮ ነው ምፅ ካይሆኑ ሠው ጋር ገጥሞ እኮ ነው እያሉ በምፅ ሲፈራረቁብህ ፈሪ ትሆናለህ። የሚቀጥለውን እርምጃህን መቼም አታምነውም ወደኋላ ስታይ ግዜህ ይነጉዳል። በዚህ ሁሉ መሀል ህይወት እንደ ክፉ አስተማሪ መቅጣቷን አታቆምም። አይምሮህ ከገደብ በላይ ይሆንበታል ትደክማለህ በቃ ሰው ነሃ!!
#የመሀል_ልጅ
ያማረ ምሽት ጀባታ!💚
@EthioHumanity
@EthioHumanity
@Nagayta
❤️ደግነት በቃላት ሲገለጽ ልበ ሙሉነትን ያመጣል፡፡
ደግነት በኃሳብ ሲሆን የስብዕና ጥልቀት ይፈጥራል፡፡
ደግነት በመስጠት ሲሆን ፍቅር ከውስጡ ያብባል፡፡
ውብ ምሽት❤️
@EthioHumanity
@EthioHumanity
☯There's a reason you can learn from everything: you have basic wisdom, basic intelligence, and basic goodness.“Would you like to save your country from destruction ? Then step away from Mass movements and quietly go to work on your own self-awareness.
☯If you want to Awaken all of humanity, then Awaken all of yourself. If you want to eliminate the suffering in your country, then eliminate all that is dark and negative in yourself. Truly, the greatest gift you have to give is your own self-transformation.”
🔆we can simply explore Humanity and all of creation in the form of ourselves. Everything that human beings feel, we also feel. We can become extremely wise and sensitive to all of Humanity and the whole universe simply by knowing ourselves,Just as we are.
የሰው ልጅ እኩልነትን እንደማስረጃ ከሚያሳዩት አንዱ"ሰው"መሆን ነው።
🔆ሰው መሆን ማለት ደግሞ፤ ራቁታችንን ከተወለድን በኋላ፤ ከልብስ ጀምሮ አካላችንን ከሚሸፍኑት የማንነት ሽፋኖች መላቀቅ ነው። ሰው ራቁቱን በመወለድ ይዞት የመጣውን መሰረታዊ ማንነት፦ ማለትም መወለድ፣ መኖርና መሞትን ይዘነጋል።
☯ገላው በእናቱ ሆድ የለመደው ሙቀት ሲቀርበት እንዳይበርደውና እንዳይቆረፍድ ልብስ መደረብን፣ ቆይቶ መለያ ስምን፣ ሃይማኖት፣ ዘር፣ ብሄር፣ በተሰብ፣ ሙያ፣ ትምህርትና ስፍርን የመሰሉ ግዑዝና ምናባዊ አልባሳትን በመደረብ" ሰው- ነቱን" ያጣል።
🔆በቀረ ዘመኑ ሁሉ ይዞት የተወለደውን ማንነት ፍለጋ አውቆም ሆነ ሳያውቅ ሲዳክር ይኖራል። ሰው መሆን ከዚህ ሁሉ ድርብርብ ሽፋን የበለጠ መሆኑን ሳያውቅ ወይንም ሳይረዳ ህይወቱን ይገፋል። ሰው መሆንን ለማወቅ የሚሄድበት ትግል፣ ሁሉም ከብርድ ለመሽሽ ከሌላና ጥላ፣ እንዲሁም ሽፋን እንደመፈለግ ነው።
☯ለዚህ ማሳያው የአብዛኛው ሰው ቋሚ ፍላጎት ህይወትን"መለወጥ" ነው። ሁሉም ሰው "ራሴን ለውጬ" ፣ "በተሰቤን ለውጬ" ፣ "መለወጥ አለብኝ ...።" ፤ " ቤተሰቤን ልለውጥ" ፣ "ሀገሬን ልለውጥ" ፣ " ሀይማኖቴን ልለውጥ "እያለ ይኖራል።
✨ከዚህ ሁሉ ለውጥ ውስጥ እያንዳንዱ አድስ ለውጥ አሮጌ ህይወት እየሆነ እንደ ልብስ ከመደረብ ውጭ እውነተኛ ለውጥ ሳይሆን ይቀራል ። እውነተኛ ለውጥ የማይኖረው ሰው ስላልጣራና ስላልሞከረ ሳይሆን ለውጥ ሂደት እንጂ መድረሻ ባለመሆኑ ነው ።
🔆በአንድ ለውጥ መርጋት በሰው ተፈጥሮ ውስጥ ከማይቻሉት ሀቆች አንዱ ነው። በመሆኑም ሰው ቢለውጥ፣ ቢለውጥ ከደረባቸው የማንነት አልባሳት አንዱን ወይንም ሌላውን እንጂ ሰው -- ነቱን" ሊሆን አይችልም።
☯ከዚህ የማንነት ግራ መጋባት ነፃ የሚወጣው በሞቱ ነው።
ሞት ትልቁ ነፃ አውጪ ነው። እንዳልነበረ ይረሳል። ስሙና ማንነቱን ሌላ ይወርሰዋል ።
✍አለመኖር ገፅ፡ 111- 112
በዳዊት ወንድምአገኝ /ዶክተር /
☮🔆☯🔆☮🔆☯🔆☮🔆☯🔆
@EthioHumanity
@EthioHumanity
✍ @EthioHumanityBot
እምወድሽዋ!❤️ቅዳሜዋ!❤️ሸጋዬዋ!❤️
ማለዳ ከአልጋዬ ስነሳ አይኔን በአይበሉባዬ እያሸሁና የቆሙ ጸጉሮቼን ወደታች ለመመለስ እየታገልኩ ወደመጸዳጃ ቤት በእንግድግድ እርምጃዎች እገባና በሩን በሚዘጋበት ሀይል መጥኜ አሽቀንጥሬ እስኪዘጋ ሳልጠብቅ በፍጥነት ለተወጠረው ፊኛዬ ምላሽ ልሰጥ እቀመጣለሁ,,,,።
<<ኡፍፍ,,,,, መተንፈስን የፈጠርክ ፈጣሪ አለመተንፈስንም ፈጥረሀልና ትመሰገናለህ,,,,,!!>>
ጥርሴን ልቦርሽ መስታወቱ ፊለፊት ስቆም በህሊናዬ ተከስሼ ፍርዴን እየተጠባበቅኩ እንደቆምኩ አስቤው ቀፈፈኝ ።
የጥርስ ሳሙናውን ሆድ በጣቶቼ ተጭኜ ብሩሼ ላይ ካደረግኩ በኋላ በደመነፍስ አሁንም መስታወቱ ላይ አፈጣለሁ።
ጨብራራ ጸጉሬ ፣ ኩሉ የገፈፈ ቅንድቤን ፣ ወደአንድ በኩል ያጋደለው ሰፊው ቲሸርቴ ፣ የተጨናበሱ አይኖቼን አንገቴን አስግጌ ይበልጥ ቀርቤ በጣቶቼ ጥግ ማዕድን እንደሚፈልግ ሰው በረበርኳቸውና አጸዳኋቸሁ።
<< ለምንድነው ዳኛ መስለህ እፊቴ የተገተርከው,,,,? ለምንስ ከውበቴ እንከኔን ታሳየኛለህ,,,? ብሽቅቅ,,,,! >> ብሩሹ ላይ ያለውን ሳሙና ውሀ አስነካሁና መስታወቱ ላይ ረጫጨሁት ። አሁንም ይዳኘኛል,,,?
የአፌን አረፋ ተፋሁበት ።
<<ቱ! ግድ አይደለም ባንተ ውስጥ እራሴን ማየቴ እሺ ,,,,? በውጫዊው አካሌማ አትዳኘኝም! ከቻልክ ውስጤን እያሳየህ ጉድለቴን ነቅሰህ አውጣ ደካማ,,,,,!!>>
ጥርሴን ተጉመጥምጬና ታጥቤ ስጨርስ "እኝኝ "እንዳልኩ እንደልማዴ ወደመስታወቱ ፊቴን ሰገግ ሳደርግ በሳሙና ጭጋግ ተሸፍኗል። በስራዬ ተገርሜ እንከተከት ጀመር። እራሴው እንከኔን እንዳይነግረኝ ሸፍኜው የጸዳሁ ሲመስለኝ ፈለግኩት "ቂቂቂቂ...." አለ መኪ።
<< ለምንድን ጉድለታችንን ከሚነግሩን ይልቅ የሚክቡን ጋር መሆን ምቾት የሚሰጠን ? ደካሞች ነን,,,።
ብዙ ጠንካራ ጎን እያለን ለመጽናናት ፈንታ በድክመታችን ተሸማቀን ስለምንኖር ብርታታችንን መስካሪ እንጂ ጉድለታችንን ነቃሽ የማይመቸን,,,,,!! >>
(የሚቀጥል ግን የማይቀጥል,,)
✍መርየም
@EthioHumanity
@EthioHumanity
❤️የሰው አእምሮ በውሸትና በተጣመመ! መረጃ ላይ እንደሚበላሽ በምንም አይበላሽም። በተለይም ውሸትን ሥራዬ ብለው በራስ ወዳድነት ስሜት የሚረጩ ሰዎች በሌሎች ልብና አእምሮ ውስጥ እሾህና አሜኬላን ይዘራሉ።
💡 ስንት ጥሩ ሰዎች በክፉና በስግብስግብ ውሸተኞች ኑሯቸው ፈርሷል። ትዳራቸው ተበትኗል!
❤️ስንት ሥልጣኔዎችንና አገሮችን ከጥቅም ውጭ አድርገዋል። አያለ ጨቅላዎች በውሸት በተመረዘ ንግግር እንጭጭ አእምሯአቸው ከንቱ ሆኖ ቀርቷል።
💡ዓለምን በአንደኝነት ያጠፋው ክፉ ሰዎች የዘሩት ውሸት ነው። የሰው ውድቀት የጀመረውም በውሸት ነው። እውነትን በትዕግሥትና በሰከነ ልቦና እንደ መልካም ዘር ካልፈለግናትና ካልተንከባከብናት ውሸት እንደ አረም ከክፉ ሰዎች የልብ ዕርሻ ላይ እየተዛመተ መልካም ልቦችን ማጥፋትና መውረስ አይቀርም።
❤️እውነትን ታውቃላችሁ እውነትም ነጻ ያወጣችኃል'የሚለው የትልቁ መጽሐፍ ቃል እንደት ያለ እውነት ነው?
💡በዓለም ላይ ከሁሉ አስከፊው እስር ቤት የሰው አእምሮ ባመነጨው ውሸት ሲጠፈርና በዚያ ቀንበር ውስጥ ሲኖር ነው። እውነተኛ ነጻነት የኀሊና ነጻነት ነው። የኀሊና ነጻነት ደግሞ እውነትን በማወቅና በመኖር ነጻ ከወጣ አእምሮ ብቻ የሚገኝ ጸጋ ነው።
❤️የብዙ አእምሮዎች መቆለፍና መዛግ መንሥኤው ባንድም በሌላም መንገድ ወደ ውስጣቸው የገባው ውሸትና ነጻ የሚያወጣቸውን እውነት አለማወቃቸው የፈጠረው ገደል ነው።
💡ከእውነት በፊትም ሆነ በላይ ለአእምሮ ጠንነትና ነጻነት ምን ምን መድኀንት ይገኛል?እውነት ማወቅ ነጻ ቢያወጣም፣ እውነት ዋጋዋ እጅግ ውድ መድኀኒት ናት።
የተቆለፈበት ቁልፍ[ገፅ፡278]
✍ምህረት ደበበ
❤️💡❤️💡❤️💡❤️💡❤️💡
@EthioHumanity
@EthioHumanity
ለውብ ቀን!
💚
ነፍስን ፍለጋ!
ይሉኝታ በሚሉት የውሸት አጋም አጥር ተሸብበን ውስጠታችን ከሚሻው እውነተኛ ማንነት ግልባጭ ፅንፍ የቆምን ስንቶቻችን እንሆን? በተበላሸው አቅራቦታችን ምክንያት ልንናገራቸው ፈልገን ያልተናገርናቸው ፣ ልንወቅስ ፈልገን ያልወቀስናቸው ፣ ልናደንቅ ከጅለን ያላደነቅናቸው በታወሱን ጊዜ ነፍሶቻችንን በቁጭት ወረንጦ የሚሸነቁጡ ስንት ኩነቶች አልፈዋል?
በየእለቱ ከምናገኛቸው በአካል ቅርብ ከሆኑ ባልንጀሮቻችን በሆያሆዬ ደምቀን እና ተሰብስበን ሳለን ከልባችን ያን እውነተኛ ሀሴት መጎናፀፍ ተስኖን በነፍስ በስንት ሺህ ማይል ተራርቀን ይሆን?
በህይወት ዑደት ውስጥ ወደኛ ህይወት የገቡ እልፍ ሰዎችን በመጀመሪያ መስተጋብራችን እራሳችንን በተንሸዋረረ መልኩ አሳይተን ከአካላችን ባሻገር እውነታችንን እና ነፍሳችንን የገለጥልናቸው ምን ያክሉን ነው?
በጓደኝነት አለም አልያም በማህበራዊ ህይወት ከልብ የሆነ መቆራኘትን ሳንቆራኝ ፣ ውስጣዊ እኛነታችን ለየቅል ሆኖ ሁላችንም ታመን ሳለ ከመንጋው ላለመፈንገል የወየበ ጥቀርሻ ልብ ይዘን ሀጫ በረዶ ጥርስ እየመፀወትን ስንቶቻችን ይሆን የምንጋፋው?
ንግግራችን ፣ ሰላምታችን ፣ ሳቃችን ፍቅራችን ምን ያክል ነፍሳዊ ነው? ምን ያክል ጥልቅ ነው? እንጃ!!
✍አብድል ማሊክ
@EthioHumanity
@EthioHumanity
<< የሚዋደድ ሰው ሁሉ አንድ አይነት ነገር መውደድ የለበትም... >>
📖መነሻ ሃሳብ :- " ማታ ማታ - ገጽ 110
🔺" ማሰብ ተፈጥሮአዊ ባህሪህ ቢሆንም በማሰብ ላይ ያለህ ብስለት ከሚገለጽባቸው መንገዶች አንዱ ደግሞ ካንተ የተለየ ሀሳብ ሲያጋጥምህ ለሃሳቡ በምትሰጠው ምላሽ(ግብራዊ) ነው ። እምትወደው ሰው የግድ ባንተ ሃሳብ የሚስማማ ወይም አንተ የምትወደውን ብቻ የሚወድ መሆን የለበትም ። እንደዛ አይነት ሰው ከፈለግክ ያንተን ሁሉ አሜን ብሎ የሚቀበል የሀሳብና የፍላጎት_ወዛደር እንጂ አሳቢን አታገኝም ።
❤️የሚዋደድ ሰው ሁሉ አንድ አይነት ነገር በመውደድ አይደለም መዋደዱ የሚገለጸው ። ካንተ ለተለየ ነገር ሁሉ ጥላቻ ከሆነ ምላሽህ በትክክል ማሰብ መቻልህ ጥያቄ ውስጥ ይገባል ። በሃሳብ መፋለስ የልዩነት እንጂ የጥላቻም ሆነ ያለመዋደድ መንስኤም ሆነ ምልክት አይደለም ። አንተ ራስህ በየቀንና በየሰአቱ የምታስባቸው ሃሳቦች ልዩነት ሊኖራቸው ይችላል ግን አቻችለሀቸው እየኖርህ ነው ። ታድያ የሰውን ልዩነት ማቻቻልስ እንዴት ያቅትሀል...…?
ለራሳችን ጥያቄ ሰተነው እንደምድም::
የሀሳብ ልዩነቶችን ለምን በስድብ እናጣጣቸዋለን?…………
ሰዎች እኛ ያልደገፍነውን ስለደገፉ ለምን እንዲያፍሩ እናደርጋቸዋለን?...……"
ፍቅር አሁን !
@keney_serezoch
@EthioHumanity
#እምወድሽዋ!❤️ ቅዳሜዋ!❤️ሸጋዬ❤️
እንድርያስ ይባላል.... ከወንበሬ ፊት ለፊት ነው የሚቀመጠው ባልደረባዬ ነው ዝምተኛም ተግባቢም ነው....ያነባል ታሪክ ፣ፖለቲካ ፣ ኪነጥበብ ይተነትናል
...አብረን ነው የምንሰራው
ቃል ኪዳን ትባላለች ትህትናዋ ከፍርሃት ጋ የተዋሃደባት ልጅ ነች ፤ በምሰራበት ድርጅት በፅዳት ከተቀጠረች ቆየች.... ያልቆሸሸ ሁለት ልብስ ብቻ እንደምትለብስ አስተውያለሁ . .. .የገንዘብ ውስንነት እንዳለባት ታስታውቃለች
እንድርያስ ለቃልኪዳን ከኔ በተሻለ ያዝንላታል ለሷ እንደሱ ማዘን ስላልቻልኩ እራሴን እወቅሰዋለሁ .....እሱ ከኔ የተሻለ ነፍስ እንዳለው እረዳለሁ!!!
ከዕለታት በአንዱ ቀን የመቶ ብር ኖቶች ፀጉርሽን መሰርያ ብሎ ሲሸጉጥ በጨረፍታ አይቼው አውቃለሁ.... አንገቷን ስብር አድርጋ ተግደርድራ ተቀበለችው። አመሰገነችውም
በልቤ አንተ ከቅዱሳን መሃል ትገኛለህ አልኩት
ከእኔ በተሻለ ይቆረቆርላታል . እሷ ወንበሩን በመወልወል እንዳትደክም ሳትመጣ ሲወለውል አይቸው አውቃለሁ
መልካምነቱ ያደበዝዘኛል
ለእሷ ባለው ቦታ እኔ እራሴ እደስትበታለሁ። የፃዲቅ መልካምነት የሚጀምረው በዙሪያቸው ባሉ ሰዎች ነው።
ከብዙ ጊዜ በኋላ በቀደም ቅዳሜ ደወለችልኝ እንደትንሽ ልጅ ፈራ ተባ እያለች በተሰበረ በለሆሳስ ድምፅ "ላናግርህ ፈልጌ ነበር አለችኝ" .....?መሳቀቋን ላለማድመቅ በቶሎ እሺ አልኳት....ተገናኘን
የለበሰችውን አመድማ ሹራብ እጅጌ ጎትታ ጣቶቿን አልብሳዋለች ። ማድያቷ እንዳ'ፍንጫዋ ከሩቁ መታየት ጀምሯል ። ፊቷ ክስም ፤ግርጥት ብሏል። ልቅም ያለች ወብ መሆኗ ይሄ ሁላ ጉስቁልና አላወደመውም
ይቅርታ በጣም "ከአንተ በላይ የሚቀርበው ሰው ስለማላውቅ ነው"
ዝም ብዬ ተመለከትኳት
* እንድርያስን እንድታናግርልኝ ነው "🙏 ስለምንጉዳይ ???..... አቀረቀረች .... በሆዴ የያዝኩት ልጅ የእሱ ነው አይንሽን ላፈር አለኝ ሳረግዝ ጠላኝ .....
ዞረብኝ ....
አፈጠጥኩኝ......
" አገባሻለሁ ተማሪ እያለ እየመከረ ፣እየወደደ፣ እየተንከባከበ፣ በፍቅር አክንፎ .....በፍቅር አባብሎ .....ስፀንስ ተፀየፈኝ: የደረጃ ልዩነታችን ተገለፀለት ማነሴ ኮሰኮሰው
የትም ስትንዘላዘይ ያመጣሽውን አለኝ😭
አቀርቅራለች
ፀጥታ ሰፈነ .....ቀና ስትል አይኗ በእንባ ተጨማልቋል
*ቢያንስ አባትነቱን ይመንልኝ እኔ ከሱ ውጪ ወንድ እንደማላቅ እሱ እራሱ ምስክር ነው ። ከፈለገ ልጁ የሱ መሆኑን ያስመርምር*
.
.
እንድርያስ እኔንም ነው የከዳኝ ሰውነቴ ውስጥ ድብርት ሲፈስብኝ እየታወቀኝ ነው
በአይኗ ውስጥ በደሏን አይቼ ሰለራሴ... ስለእህቴ .....ስለ ነገ ልጄ.. ስለ ጓደኛዬ .....ውሃ መሳይ ፊቴ ላይ ከአይኔ እየወጣ ሲረማመድ ተሰማኝ
.......
#ማሳሰብያ
የሰይጣን አምሳያ የሆነው ሰው መምጫ መንገዱ መቼ ይታወቃል ።ከሚታዩ መጥፎ ነገሮች መልካም የሚመስሉ
መጥፎ ነገሮች ያከስማሉ
....
ደርባባ ቅዳሚት ትሁንልን!❤️
@EthioHumanity
@EthioHumanity
@Nagayta
ለጁምኣችን!
💚
በመካ ከተማ አንድ ሰው ግራ ቀኙን እየቃኘ በመንገድ ሲያልፍ አንዲት አሮጊት እርጅና ባጎበጠው እድሜ ባሰለላቸው እጆቻቸው እየተንቀጠቀጠቀጡ ምግብ የሚያበስሉበትን እንጨት ተሸክመው ወደቤታቸው ሊሄድ ሲያጣጥሩ ይመለከታል። በአሮጊቷ ተግባር ልቡ የተነካው ይህ ሰውም በቀስታ ወደሴትየዋ ተጠግቶ « ቤትዎን ያሳዩኝ እኔ ተሸክሜ አደርስልዎታለሁ» አላቸው።
የሴትየዋ ቤት እጅግ እሩቅ ከመሆኑ ባሻገር ጸሀዩ ሲጠብሰው የዋለው አሸዋ ልክ በጋለ ፍም ላይ የመራመድ ያክል እግርን ክፉኛ ይለበልብ ነበር! ጸሀዩዋም መካ ብቻ ጓዟን ጠቅላ የሰፈረች ይመስል እንደእሳት ትፋጃለች። በነፋሱ እየተንሳፈፈ የሚመጣው የአሸዋ ብናኝም ፊትን በሀይል ይጋረፋል! እንግዲህ ይህን ፈተና ችሎ ነው ሰውየው የአሮጊቷን የደረቁ እንጨቶች ለመሸከም የወሰነው
በሰውዬው ድርጊት እየተገረሙና እየተደነቁ ቤታቸው የደረሱት ምስኪኗ አሮጊትም መልካሙን ሰውዬ ትኩር ብለው እየተመለከቱ እንዲህ አሉት ..
«ልጄ ሆይ እንዲያው ባሮጊት አንደበቴ እመርቅሀለሁ እንጂ ላደረግህልኝ ነገር መካሻ ይሆን ዘንድ የምሰጥህ አንዳች የሌለኝ ምስኪን ደሀ ነኝ ልጄ እባክህ ከሰማኸኝ አንድ ምክር ልለግስህ። ወደህዝቦችህ ወደመካ ስትመለስ እዚያ አንድ ነብይ ነኝ የሚል ሙሀመድ የሚሉት ደጋሚ ሰው አለ። በፍጹም እሱን እንዳትከተል እንዳታምነውም!» አሉት።
ሰውዬውም ረጋ ብሎ «ለምን?» ብሎ ጠየቀ!
አሮጊቷም «ልጄ እርሱ መጥፎ ስነምባር ነው ያለው ሲሉ ሰምቻለሁ» ብለው መለሱ።ሰውዬው በሴትየዋ ንግግር ተገርሞ «እኔስ ሙሀመድ ብሆን?» አላቸው። ሴትየዋም የሰሙት ነገር በጣም አስገርማቸው ለካስ ይህ ደግ ሰው ራሳቸው ነብዩ ሙሀመድ (ሰ.አ.ወ) ነበሩ። አስተውሉ ... ነብዩ ለአሮጊቷ ቸርነትን ሲያደርጉ ሀይማኖታቸውን ፈፅሞ አልጠየቁም። ፍቅር የሀይማኖትን ድንበር፣ የዘርና የጎሳን አጥር እንደሚያልፍ ያውቁ ነበርና። ስብከት ያልሰበረውን ልብና ትምህርት ያላንበረከከውን ማንነት ፍቅር ብቻ ትህትናና በጎ ምግባር ብቻ ያንበረክከዋል!
ያማረ ጁምኣ!💚
@EthioHumanity
@EthioHumanity
@Nagayta
☮ተማሪ ነው ለሱፊው መምህሩ ጥያቄውን ያቀረበው ፡-
‹‹ለመሆኑ ሰው በአምላኩ የሚረካው መቼ ነው?›› የመምህሩ ምላሽ ታዲያ ድንቅ ነው!
💡‹‹በበረከቱ ግዜ የሚያገኘውን ደስታ በመከራው ጊዜ መግለጥ ከቻለ በርግጥም በአምላኩ ረክቷል ማለት ነው››፡፡
❤️በአሁና ደቂቃ ብቻ የተሰጠንን በረከት ብንቆጥር፤ ያለንን መልካም ነገር ብናስተውል ………..
ወደ መሬት ጎንበስ ብለን የምናመሰግንበት አንድ ሺ አንድ ምክንያቶች አሉን!! አንድ ሺ አንድ !!!!
መልካም ዛሬ!!!
💡☮💡☮💡☮💡☮💡☮💡☮💡☮💡☮💡
@EthioHumanity
@EthioHumanity
🔑Conditioned Mind
"It is not because things are difficult that we do not dare; it is because we do not dare that things are difficult." - Seneca
---
🔆በሕንድ መንደሮች ውስጥ ሲዘዋወር የቆየ አንድ እንግዳ ሰው ነዋሪዎቹ ዝሆኖቻቸውን የሚጠብቁበት መንገድ ግራ አጋብቶታል... እጅግ ግዙፍ የሚባሉ ዝሆኖች በቀላሉ ሊበጠሱ በሚችሉ ገመዶች ታስረው በጸጥታ የመቆማቸው ምስጢር እውነትም እንቆቅልሽ ነበር... 'እንዴት ሊሆን ይችላል?'...
⚜️ግራ መጋባቱ እየቀጠለ ሲሄድ ወደ አንድ የዝሆኖች አሰልጣኝ ዘንድ ቀርቦ 'ይህን እንዴት ማድረግ ቻላችሁ?... ዝሆኖች በምድር ላይ በጉልበታቸው ተስተካካይ የሌላቸው ፍጥረታት መሆናቸው ይታወቃል... በዚህ ሰላላ ገመድ ታስረው እንዲቆዩ ያደረጋቸው ምስጢር ምንድነው?...' ሲል ጠየቀ... 'ደህና...' አለ ዝሆኖችን የሚገራው ሰው... በእንግዳው ሰው ጥያቄ አንዳችም መገረም ሳያሳይ... 'በዚህ ገመድ መታሰር የሚጀምሩት ከደረጁ.. ጉልበት ካበጁ በኋላ አይደለም... ገና ግልገል ሳሉ ነው... በዚያ የማለዳ ዕድሜ አሁን የምታየው ገመድ እነርሱን አስሮ ለመቆየት በቂ ነበር... እየቆዩ ሲሄዱ ገመዱን የሚበጥስ አቅም ቢፈጥሩም በልጅነታቸው የታተመባቸው እምነት ግን ዛሬም ገመዱን መበጠስ እንደማይችሉ ይነግራቸዋል'...
🔆ሰውየው በጥበባቸው ተገረመ... ግዙፉን ዝሆን ለማሰር ግዙፍ ሰንሰለት አላስፈለጋቸውም... አስተሳሰባቸውን የሚያስር የማለዳ ልማድ በቂ ነበር... ነገሩ ሰንሰለት ካሰረው ልማድ ያሰረው ነው... 'ልማድ ከብረት ይጠነክራልና' ሼክስፒር እንዳለው...
🔆የኑረት ውበት በየደረሱበት መጠየቅ... የሰውነት ከፍታም በየመዳረሻው መርቀቅ ቢሆንም ከተነገረው ዘሎ 'ለምንና እንዴት' ለማይል አዕምሮ የነበረን ማስጠበቅ እንጂ 'አዲስ ነገር' ማፍለቅ አይሆንለትም... የኑረት ስኬትም ሆነ ውድቀት በእምነትህ ልክ ይገነባል... ቡድሃ "All that we are is the result of what we have thought. The mind is everything. What we think we become. " የሚለውን ቃል በትምህርቱ መጀመሪያ ላይ ያስቀመጠው ለዚሁ ነበር...
💫የምታምናቸውን ነገሮች ለምን እንዳመንካቸው ጠይቀህ ታውቃለህ?... የተቀበልካቸውን እሳቤዎች ልክነት በ'እንዴት' ዓይን መዝነህ ታውቃለህ?... የነገሩህን መጽሐፍትና ያስተማሩህን አንደበቶች መርምረህ ታውቃለህ?... እርግጠኛ ስለሆንክባቸው ጉዳዮች ቢያንስ ለራስህ በታማኝነት የምታቀርበው መልስ አለህ?... ወይስ እንደ ግዙፉ ዝሆን በሰላላ የአስተሳሰብ ወደሮ ታብተሃል?... መጠየቅስ አድክሞህ ይሆን?... Wynn Bullock የተባለ ሰው... "If you stop searching, you stop living, because then you're dwelling in the past. If you're not reaching forward to any growth or future, you might as well be dead." ብሎ ነበር... ሶቅራጥስ በበኩሉ "The unexamined life is not worth living" ብሏል...
✨ከማለዳ ውልደት እስከ ውድቅት ህልፈት የምትሳበው ኑረት ሁለንተናዋ በጠነከረ ልማድ የተቀየደ ነው... ከመጋረጃ ጀርባ ሆኖ የትወናዋን አካሄድ የሚወስንላት መራሔ ተውኔት ልማድ ወይም እምነት ይባላል... የምታምነውን ነው የምትሆነው... ግና.. የማለዳ እምነትህ ረፋድ ላይ... የረፋድ እሳቤህ ቀትር ላይ... የቀትር ግንዛቤህ በተሲዓት... የተሲዓት እውነትህ በምሽት ካልተመረመረ ከልማድ እስረኛነትህ ሳትፈታ ውድቅትህ ይመጣል... "The world is a prison and we are the prisoners.Dig a hole in the prison wall and let yourself out." ይልሃል ሩሚ...
🔑'ተለምዷል' የሚልህ ሰው ሲበዛ ጠርጥር... ቅኝት ነው... 'ምንም ማድረግ አይቻልም' ካለህ ተቃኝቷል በቃ... 'ያለ ነው'... 'ባሕል ነው'... 'አሰራር ነው'... 'እከሌ የሚባል ሰው ወይም መጽሐፍ ላይ ሰፍሯል'... ወዘተረፈዎች የቅኝት መገለጫዎች ናቸው... እዚህ መንደር ውስጥ 'ለምን' ባይ የተገኘለት የእብደት ታፔላ ይለጠፍለታል...
🔆ዕድሜ ልኩን ጥርሱን ሳያጸዳ የኖረ ሰው ለተወሰኑ ቀናት ብሩሽ ተጠቅሞ በመተዉ የአፉን ሽታ ቢያስተውል ሊል የሚችለው አንድ ነገር 'የጥርስ ሳሙና አፍ ያሸታል' ነው... ብሩሽ ከመጠቀሙ በፊት ሽታውን ተላምዶት ስለቆየ 'አፍህ ይሸታል' ቢሉት አይቀበልም ነበር... ብሩሹ ካለመደው ንጽህና በኋላ ግን የትኛውንም ሽታ መረዳት ይጀምራል... ተለማምዶ እስኪዘነጋው ድረስ... ጠረን እንድትለይ የሚረዱህን 'ብሩሾች' ስንቴ 'ያሸታሉ' ብለህ ጣልክ?... ስንቴስ ወደ ቀደመ ሽታህ ተመለስክ?...
ኒቼ በተወልን ድንቅ መስመር የማያልቀውን እንጨርስ... "If you have a 'why' to live by, you can live with any 'how'."
የ'ለምን' እና 'እንዴት' ድፍረት ይስጠን!!
ሰላም...❤️
✍ ደምስ ሰይፉ
✨🔆🔑✨🔆🔑✨🔆🔑✨🔆🔑
@EthioHumanity
@EthioHumanity
@EthioHumanityBot