🔆እየጠየቁ መኖር መልስን፣ መልስን ፈልጎ ማግኘት ዕውቀትን፣ እውቀት ነፃነትን፣ ነፃነት ሙሉ ስብዕናን፣ ሙሉ ስብዕና ሠላምና እርካታን፣ እርካታ ደግሞ ደስተኛ ሆኖ መኖርን ያስገኛል፡፡ አብረን እንደግ !! @EthioHumanity @Ethiohumanity ✍የተሰማቹን አጋሩን! ቤቱ ሁሌም ክፍት ነው፣ሃሳባቹን ፃፍፍ አርጉልን @EthioHumanitybot
ምክር ለወዳጅ
🔴 በወጣትነት ሁሉም ነገር ትክክል ነው ከሚል መመሪያ ውጣ ፤ ሁሉንም ካላየሁ አላምንም አትበል ። ሰምቶ ማመን ፣ ከተጎዱት መማር አስተዋይነት መሆኑን አትርሳ ። የሰማንያ ዓመት ዕውቀትን ለመገብየት ግድ ሰማንያ ዓመት መኖር የለብህም ። ሰማንያ ዓመት ከኖሩት በትሕትና መጠየቅ ይገባሃል ።
📕ምክርን ብትሰማ በነጻ ትማራለህ ። ምክርን አልሰማ ብትል ግን በዋጋ እንደምትማር እወቀው ። በዋጋ መማር ግን አድካሚ ደግሞም የሚያስመርር ነው ። ብልህ ከሆንህ በሰው ከደረሰው ትማራለህ ፣ ሞኝ ከሆንህ ግን በራስህ ሲደርስ ትማራለህ ።
📘 የታየህን አሳይ ፣ ያልታየህን አጥራው ። በደንብ ያልተረዳኸውን አታስተምረው። ያልቀመስከውን ለሰው አትጋብዝ ። የሰማኸውን ሁሉ አትመን ። ያየኸውን ሁሉ ስጡኝ ፣ የተናገርከውን ሁሉ ፈፅሙ አትበል ። የሰጠኽውን እርሳ እንጂ አታውራ። ፍፃሜውን ሳታይ ምስጋና አታብዛ ። ቀኑ ሳይመሽ ቀኑ ጥሩ ነው አትበል ።
📘ዓይንህ የፊቱን ቢያይ ልብህ የኋላውን ያስብ ። ነገ ላይ እንድትደርስ የትናንቱን አትርሳ ። የምትሄድበት እናዳይጠፋህ የመጣህበትን አትዘንጋ ።
🔴የአባቶችህን መልካም ሥራ አብነት አድርግ ። ካሳለፉት ሕይወት ተማር እንጂ አወዳሽና ወቃሽ አትሁን ። ሌሎች መሆን ያለባቸውን ስታውቅ አንተ መሆን ያለብህ እንዳይጠፋህ ተጠንቀቅ ። ደግሞም አንተም በታሪክ ፊት መሆንህን እወቀው ።
🔵 ክፋት አይሙቅህ ፣ መልካም ነገርም ብርድ ብርድ አይበልህ ። ለክፋት አቅም ካለህ ለበጎ ነገርም አቅም አለህና ተግባርህ የምርጫ ውጤት ነውና አስብበት ።
📕 ገንዘብ የሚመልሰው የገንዘብን ጥያቄ ብቻ ነውና ሁሉንም ነገር ገንዘብ ያስገኝልኛል ብለህ አታስብ ። ላለው አትሩጥ ፣ ምጽዋትህና ተግባርህ በአቅምህ መጠን ይሁን እንጂ ከአቅምህ አትነስ ። ድሃም ሆነህ ተበድረህ ስጦታ አትስጥ ። በጣም ካልቸገረህ ለቅንጦት አትበደር ። ያንተን ድርሻ ከጨረስህ ያልተጨረሰ የሌሎችን ድርሻ ፈፅምላቸው ።
💎 ለሀብታም አትሳቅ ፣ የደሀ ጉልበት አይለፍብህ ፣ ያለ ሰው ሰው አልሆንክምና ሰው አትጥላ ፣ የወጣህበትን መሰላል አትገፍትር ፣ ለመውረድም ያስፈልግሃልና ፣ ያየኽውን ሴት ሁሉ የመውደድ ጠባይህ ካለቀቀህ ትዳር አትያዝ ፣ ካልጋበዙህ በቀር አማካሪ አትሁን ፣ ባልጠሩህ ሥፍራ አቤት አትበል ፣ ካልሾሙህ መሪ አትሁን ፣ ጉድለት በሌለበት ቦታ ጊዜህን አታባክን ፣ የሰው ፊት ጥገኛ ሁነህ ሲስቁልህ የምትስቅ ሲቆጡህ የምታለቅስ አትሁን ፣ ነገርህን በልክ ፣ ቃልህን በጣዕም ፣ ድምፅህን በዝግታ ፈፅመው ።
🔵እውር እንዳይሉህ ያልታየኽን አያለሁ አትበል ። ጨካኝ እንዳይሉህ ያልተሰማህን ጩኸት እሰማለሁ አትበል ። ንፉግ እንዳይሉህ ያለ አቅምህ እረዳለሁ አትበል ። ነገር አይገባውም እንዳይሉህ ያልገባህን እንደገባህ አድርገህ አትለፍ ። አንድ በጎ ዕውቀት ሳትጨብጥ የዋልክበትን ቀን እንደ ኖርክበት አትቁጠረው ፣ ስለዚህ መፅሐፍትን አንብብ ፣ አዋቂዎችን ጠይቅ ፣ ሁሉን ሳትንቅ ስማ ።
🔵 ሥልጣን ሲሰጥህ መሪ እንጂ አለቃ አትሁን ፤ ከፊት እየቀደምህ አስከትል እንጂ ከኋላ ሆነህ አትቅደም ።
🔴 በዓላማ ኑር ፤ እንቅፋቶች የሚያጸኑህ እንጂ ተግባርህን የሚያስተውህ አይሁኑ ። ሕይወት ትምህርት ቤት መሆኑና ባለማወቅ ብዙ ትህምርቶች እንዳያመልጡህ ተጠንቀቅ ።
:
📕 የመከራ ቀን ወዳጆችህን አትርሳ ፤ የዛሬ ሰው ብቻ አትሁን ፤ የትላንቱንም አስብ ፤ አንገት የተፈጠረው ዞሮ ለማየት ነውና ።
🔵ዓለም ዋዣቂ ናት ። ከፍና ዝቅ ስትል አትደናገጥ ፤ ፀሐይ ዝናብን ተከትላ ትፈነጥቃለች ። ከመከፋትም በኋላ ትልቅ መፅናናት ይሆናል ። ከሌሊት በኋላም ሌሊት አይመጣም ። ከሀዘን በኋላ ደስታ ይሆናልና በርታ!
🔴 መነቀፍን አትፍራ ፤ ነቀፋህን ግን አጥራው ፤ ስለ ሀሰት ሳይሆን ስለ እውነት ተገፋ ፤ ሌሎችን ውደድ ፍቅር ስጦታ እንጂ ብድር አይደለምና አልወደዱኝም ብለህ በአበዳሪዎች አንቀጽ አትካሰስ ፤ የገባህን አድርግ የዚህ ዓለም ሰው ሲወድህም ሲጠላህም ባለማወቅ ነው ። ብዙዎች ስለወደዱህ ይወድሃል ፤ ብዙዎች ስለጠሉህ ይጠላሃል ።
🔵 ሁልጊዜ የበላዮችህን አትመልከት ፤ የበታቾችህንም ተመልከት ። ለድምፅ አልባዎች ጩህላቸው ፣ ለተጠቁት ተሟገትላቸው ። እውነት እውነት በማለትህ የምታጣው ሀሰተኛ ወዳጅህን ብቻ ነው ። እውነት እውነት በማለትህ የምታተርፈው ግን እውነተኛ ወዳጅን ነው ።
🛑ደጋፊዎች ተከታዮች አይደሉም ። ሰዎች ስለደገፉህም የያዝኩት እውነት ነው ብለህ መንቻካ አትሁን ፤ ምናልባት ዛሬ የሚጮሁልህ ዛሬን ሊረሱብህ ሊሆን ይችላልና ። ሲያለቅሱልህም ቃልህ ማርኳቸው ሳይሆን የሞተ ዘመዳቸው ትዝ ብሏቸው ሊሆን ይችላልና አለቀሱ ብለህ ንግግርህን ድንበር አታሳጣው ። እውነትንም በደጋፊ ብዛት እንዳትመዝናት ተጠንቀቅ ።
🔴ለእውነታ እንጂ ለይሉኝታ አትኑር ፤ ያን ስልህ የምትኖርበት ሕዝብና ባሕል ከእውነት ጋር እስካልተጋጨ መጋፋት የለብህም። ሠዎች የሚቀበሉህ ባሕላቸውን ስታውቅና ስታከብርላቸው ነው ።
🔵ልጅነት የለሰለሰ መሬት ፣ ወጣትነት የአዝመራ ዘመን ፣ ሽምግልና ደግሞ የአጨዳ ዘመን መሆኑን አስተውል ። በሽምግልናህ የምታጭደው የወጣትነትህን አዝመራ ነውና ዛሬ ለምትዘራው ተጠንቀቅ ።
📍 የሰዎችን ያለማወቅ አግዝ ፤ ዕውቀትህ ባላወቁት ላይ እንድትኮራና እንድትፈርድ አያድርግህ የአዋቂ ኩሩ ቁጥሩ ካላዋቂዎች ነውና ማወቅ ባለዕዳነት እንዳይሆን አላዋቂዎችን እርዳቸው ።
🔵 ዛሬ የመዝራት ዘመንህ ነገ መከርህ ነውና በእምነት እውነትን ዝራ ፤ በምታውቀው ቦታ ላይ አገልጋይ በማታውቀው መልካም ተግባር ላይ ደጀን ሁን ፤ በቦታህ መምህር ያለቦታህ ተማሪ ሁን ፤ ክብሩ እንዳይቀንስብህ ከዕቃ ትምክህት ፣ ከዕውቀት ሙግት ራቅ ።
🔴ሁሉን ወሬ ላውራ አትበል ፣ የደበቁህን ምስጢር አታውጣጣ ፣ የሰማኽውን ወሬና የተገለጠልህን ምስጢር ምን መፍትሔ ሰጠኸውና ? ያየህውን ሥራ ሁሉ እሰራለሁ የሰማኸውን ትምህርት ሁሉ እማራለሁ አትበል ። ይህ የተሰወረው የቅንዓት ጠባይ ነውና ሁሉን ልያዝ ማለትም ዝንጉ አድረጎ እንዳያስቀርህ ሁሉም ውስጥ ልኑር አትበል ።
🔵ቆንጆዎች ቁንጅናቸው ሁሉን የሚተካ እየመሰላቸው ከዕውቀትና ከትሕትና ይርቃሉ ። ሁሉንም ሰው በመልካቸው የሚማርኩት ስለሚመስላቸው ኩሩና ተንኮለኞች ይሆናሉ ። አንተ ግን ቆንጆ ወዳጅን እንጂ ቆንጆ ቁመናን አትሻ ፤ ቆንጆ ትዳርን እንጂ ቆንጆ ሴትን አትመኝ ፤ የላይ ነገር ከንቱና ኀላፊ ነውና በሚፈርስ አካል ፣ ኑሮ በሚለውጠው መልክ አትደለል ።
🛑እወድሃለሁ ብለህ የምትናገረውን ቃል ውለታ አታድርገው ፣ መውደድህን የምትናገረው እንወድሃለን እንዲሉህ አይሁን ፣ ሠላም ያለው አፍቃሪ የራሱን ፍቅር ያለ ምክንያት መፈፀም የሚችል ብቻ እንደሆነ እወቅ ። መወደድህን ለመስማት አትጠብቅ ።
🌀የሰዎችን ያለማወቅ አግዝ ፤ ዕውቀትህ ባላወቁት ላይ እንድትኮራና እንድትፈርድ አያድርግህ የአዋቂ ኩሩ ቁጥሩ ካላዋቂዎች ነውና ማወቅ ባለዕዳነት እንዳይሆን አላዋቂዎችን እርዳቸው ።
🛑ዛሬ የመዝራት ዘመንህ ነገ መከርህ ነውና በእምነት እውነትን ዝራ ፤ በምታውቀው ቦታ ላይ አገልጋይ በማታውቀው መልካም ተግባር ላይ ደጀን ሁን ፤ በቦታህ መምህር ያለቦታህ ተማሪ ሁን።
ውብ አዳር ❤️
@Ethiohumanity
@EthioHumanity
✍ @EthioHumanitybot
ለባለ ሱቆች በብዛት መረከብ የምትፈልጉ
☎0991208847 ወይም @Nagayta
ለጁምኣችን!
💚
" መወደድም ሲሳይ ነው" አሉ ። ምነው ቢሉ ነብዩ ዩሱፍን ዓ.ሰ (ዮሴፍን) አርቀው የጣሉት የገዛ ወንድሞቹ ፥ አንስተው ያከበሩት መኳንንት ባዶቹ ።
መውደቅ መጨረሻ አይሆንም ፥ ምነው ቢሉ ዮሴፍ ዓ.ሰ ለንግስና የታጨው እስር ቤት እያለ ነውና ፥ መነሳትም ተክትሎታልና ።
ሰው ኹሉን አወቅ ነኝ ይላል እንጂ ስለ ህልውናው በመተርጎም ፥ ውስጥ ውስጡን ትርጉምን ሁላ የምታስከነዳ ገራም የመለኮት ሥርዓት አለች ።መታገስ ነጃ ያወጣል ምነው ቢሉ የመለኮት ሥርዓት ኹሉን በገራምነት እንደምታስከነዳ ማመን ነውና ።
📝ሰለዲን አሊ
@Ethiohumanity
@Ethiohumanity
📍መስጠት ካልቻልኩ መቀበል አይሆንልኝም "
🔵ደግነት ልቤ ውስጥ በተዘራ ጊዜ ፍሬውን አጭጄ እሰበስብና ለተራቡት እሰጣቸዋለሁ . . .ነፍሴ የወይን ፍሬ ባበቀለች ጊዜ ፍሬዎቹን ጨምቄ የተጠሙትን አጠጣቸዋለሁ ::
🟢ውስጤ በብርሃን በተሞላች ጊዜ የውስጤን ፋኖስ የመስኮቴ ጫፍ ላይ አስቀምጣትና በጨለማ ለሚጉዋዙት ብርሃን እሆናቸዋለሁ :: ጥላቻን ከልቤ ያጠፋልኝ ዘንድ ሁልጊዜም የፍቅርን ችቦ መጨበጥ እሻለሁ ::
🟡ሰዎች በዘርና በቀለም ተለያይተው በተለያዩ አህጉራትና ሀገራት ይኖራሉ ,,,,, እኔ ግን ለሁሉም ማህበረሰቦች እንግዳ ነኝ ከየትኛውም ሀገር አልወግንም። መላው ዓለም ሀገሬ ነው፣
የሰው ልጅ ሁሉ ወገኔ ነው ።
🔴የአዳም/አደም ልጆች ደካማ ሆነው በተለያዩ ጉዳዮች መከፋፈላቸው የሚያሳዝን ነው , ዓለም ሳትከፋፈልም ጥብብ ያለች ናት ይህችን ጠባብ ዓለም በግዛት ፣ በሰፈር፣በአውራጃ መከፋፈሉ በአላዋቂነት የታጀበ ሞኝነት ይመስለኛል . . . . !
✍ "ካህሊል ጂብራን"
ውብ ምሽት ❤️
@EthioHumanity
@EthioHumanity
✍ @EthioHumanityBot
☯በአንዲት ትንሽየ ከተማ ውስጥ ለብዙ ዘመናት ማራኪ ስዕሎችን በመሳል ለከተማዋ ነዋሪዎች እና ከሩቅ አካባቢ ለሚመጡ እንግዶች በጥሩ ዋጋ እየሸጠ ደስታ የተሞላበት ሕይወት የሚኖር አዛውንት ነበር። ከዕለታት አንድ ቀን በከተማዋ ውስጥ ከሚገኙ ድሃዎች
መካከል አንዱ መጣና ሰዓሊውን «በሥራህ ብዙ ገቢ እያገኘህ ለምንድን ነው በከተማዋ ያሉ የኔ ቢጤ ደሃዎችን ለመርዳት ንፉግ ያደረገህ ??...
የዚያ ልኳንዳ ቤት ባለቤት እዚህ ግባ የሚባል ገንዘብ ሳይኖረው ለድሃዎች በየቀኑ ስጋ ያድላል፤ በተመሳሳይ ሁኔታ የዚያ ዳቦቤት ባለቤት ዘወትር በየቀኑ በነፍስ ወከፍ ለድሃዎች ዳቦ ይሰጣል» በማለት ጠየቀው። ሰዓሊው ምንም መልስ ሳይሰጠው በሰከነ መንፈስ ታጅቦ በስሱ ፈገግ አለ።
✨ድሃው በሰዓሊው ዝምታ ተበሳጭቶ ከቤቱ ውስጥ ተስፈንጥሮ ወጣ። ወደ መሃል ከተማ በመገስገስ አላፊ አግዳሚውን እያስቆመ «ሰዓሊው ብዙ ኃብት ቢያከማችም ድሃወችን
ለመርዳት ፍላጎት የሌለውና ስስታም ነው» በማለት ወሬ መንዛት ጀመረ። የአካባቢው ነዋሪዎች በሰዓሊው ላይ ጥርስ ነከሱበት። ማህበራዊ መገለል ደረሰበት። የሚያናግረው አንድ ሰው እንኳ አጣ።
ከተወሰኑ ቀናት በኋላ አዛውንቱ ሰዓሊ ክፉኛ ታመመ። ከአካቢቢው ነዋሪዎች መካከል አንድም ሰው ትኩረት የሰጠው አልነበረም። ከጎኑ ማንም ሳይኖር ብቻውን ሞተ።
☯ቀናት በንፋስ ፍጥነት ነጎዱ። የከተማዋ ነዋሪዎች የልኳንዳ ቤቱ ባለቤት ለድሃዎች በነጻ የሚያድለውን ስጋ እንዳቆመ አስተዋሉ። የዳቦ ቤቱ ባለቤትም ለሚስኪኖች በነጻ
የሚያከፋፍለውን ዳቦ እንዳቋረጠ ተገነዘቡ። ድሃዎቹ በልኳንዳ ቤቱ በር ፊት ለፊት ቆመው የለመዱትን ስጋ ለማግኘት ቢማጸኑም ሰሚ አጡ። በዳቦ ቤቱ መስኮት ዙሪያ ቢያንዣብቡም
ለስም እንኳ የሚያዳምጣቸው አንድ ሰው አጡ።
✨የከተማዋ ነዋሪዎች ተሰብስበው የልኳንዳ እና ዳቦ ቤቶቹን ባለቤቶች «ዘወትር በየቀኑ ለድሃዎች ትሰጡ የነበረውን ስጋ እና ዳቦ ለምን
አቆማችሁ» ብለው ሲጠይቋቸው «በየቀኑ ለከተማዋ ድሃዎች በነጻ የምንሰጠውን የስጋና ዳቦ ዋጋ በየወሩ የሚከፍለን አዛውንቱ ሰዓሊ ነበር። ከሱ ህልፈት በኋላ ክፍያ የሚፈጽምልን
ሰው ባለመኖሩ በነጻ ማደሉን አቋርጠነዋል» በማለት ወሽመጥ ቆራጭ ምላሽ ሰጧቸው።
💫የተወሰኑ ሰዎች ባንተ ላይ ክፉ ጥርጣሬ ሊያሳድሩ ይችላሉ። አንዳዶች ደግም እንደ ሐጫ በረዶ የጠራህ አድርገው ሊስሉህ ይችላሉ። ሁለቱም አይጠቅሙህም። አይጎዱህምም።
ቁም ነገሩ ያለው ፈጣሪ ስላንተ የሚያውቀው ትክክለኛ ማንነትህ ላይ ነው። ለክፉ አሳቢዎች ክፋ ምላሽ ላለመስጠት ጥረት አድርግ።
🌔 ደግነትህ ለብዙዎች የዕድሜ ማራዘሚያ ሰበብ ስለሆነ እንዳይከስም ጠብቀው። ለጋስ በመሆንህ በምላሹ ከሌሎች ምንም ነገር አትጠብቅ። የጊዜ ጉዳይ ቢሆን እንጂ መልካም ነገር ሁሌም ከፈጣሪህ በጎ ምላሽ አለው።
ህሊናህ ይረካ ዘንድ ከመቀበል ይልቅ ሰጪ ሁን። በምግባርህ ፈጣሪህን ለማስደሰት ሁሌም ጥረት አድርግ። እርሱ ከወደደህ ደስታ በእጅህ ትገባለች።በመልካም ስነ ምግባር ሽቶ የተርከፈከፈ ስብዕና ከመሬት በታች አፈር ለብሶ እንኳ መዓዛው ያውዳል።
ውብ አሁን❤️
@EthioHumanity
@EthioHumanity
@EthioHumanitybot
🌗የሚያልፍ ዝናብ አይምታህ!!
🌬እዚህች ምድር ላይ ስንኖር በትንሹም ይሁን በትልቁ በየደቂቃው እንለዋወጣለን። ቢታወቀንም ባይታወቀንም ነው እንግዲህ ቢያንስ ገላችን የበላውን ያንሸራሽራል፣ ሕዋሳት ይሞታሉ ይወለዳሉ። ቢያንስ አንዲት ፀጉር ትበቅላለች ወይም ትረግፋለች። ፊኛችን ሳያቋረጥ በፈሳሽ ይሞላል። ጊዜው ሲደርስም ይጎላል።
⛈ ሕይወት እንግዲህ እንዲህ ነው፤ ይሄ ዑደትና የዝግመት ለውጥ አይበቃንምና ደሞ አንዳንድ ጊዜ እጅግ የሚለውጠን ቀውስ ይመጣብናል ገላችን፣አዕምሮአችን ይታመማል እንረበሻለን፣እንጨነቃለን።ሕይወት እንግዲህ ይሄ ነው ሰው በግሉ፣ ሕብረተሰብም ተፈጥሮው ይመስሉኛል።
📍ይሄን ደጋግሜ መገንዘቤ፣ደጋግሜም በነዚህ ሁኔታዎች ውስጥ ማለፌ ያስተማረኝ ነገር አለ።መረባበሽ ፋይዳ እንደሌለው የተረጋጋ ታዛቢ፣ የመነኩሴ አመለካከት አለኝ። ከፍ ዝቅ ያለ ነገር ሲያጋጥመኝ በረጉ ዓይኖቼ አያለሁ። በቀዘቀዘ መንፈስና አካል እቀበለዋለሁ እንደሚለወጥ ስለማውቅ!"የሚያልፍ ዝናብ አይምታህ" ሲሉ አዛውንት ዝናቡን ፍራው ማለታቸው አይደለም። ዝናቡን ማወቃቸው ነው። የተወሰነለት ዕድሜ አለው፣ ያውም አጭር ማለታቸው ነው። ሰው ቢያንስ በተስፋ የችግሮቹን ዘመን ያልፋል ማለታቸው ነው።
/ከአዳም ረታ አንደበት/
🌪በእርግጥም የሚገጥሙንና የሚያጋጥሙንን ክስተቶችና ፈተናዎች መወሰን ባንችል እንኳን፣ ምላሻችንንና ግብረ-መልሳችንን መወሰን እንችላለንና ዘወትር የመጣው እስኪያልፍ፣ የቀለጠው እስኪ ረጋ፣ የነደደው እስኪ ከስል፣ በሰከነ አዕምሮ፣ በተረጋጋ መንፈስ፣ በአንድ ልብ መቀበሉንና ማሳለፋን እንወቅበት።
ሰናይ ምሽት ይሁንልን❤️
@EthioHumanity
@EthioHumanity
✍ @EthioHumanityBot
📍ደስታ የምኞት ውጤት፣ የማሳደድ ትርፍም አይደለም። ደስታን ተመኝቶ ያገኘ፣ አሳድዶ የያዘ የለም።
🔶ደስታ ከገንዘብ ብዛት፣ከስልጣን ሹመት፣ ስጋዊ ስሜትን ከማርካት ወይም ከሳይንስ አይመነጭም፡፡ ደስታ በቁጥር አይመጠንም፡፡ መጋዘኖች አያከማቹትም፡፡ ዩሮ ወይም ዶላር አይገዛውም፡፡ ደስታ ከውስጥ የሚሰማ ነገር ነው፡፡ የነፍስ መስከን፣ የቀልብ መረጋጋት፣ የልቦና መስፋት፣ የሕሊና መርካት ውጤት ነው፡፡የአዕምሮአችንን ተፈጥሮ በትልቅ ተረድተን ከተጠቀምበት እውነተኛ ደስታ እና ነፃነት ማግኘት እንችላለን ፡፡
🔷አትኩሮትህን በሌለህ ነገር ላይ ሳይሆን ባለህ ነገር ላይ አድርገው። ደስተኛ ለመሆን ሁሉም ነገር ሊኖርህ አይገባም። በደንብ ካስተዋልከው አሁን ያለህ ነገር ደስተኛ ለመሆን በቂ ነው።ምክንያቱም አንተ ያለህን ሙሉ ጤና የሚመኙ ምስኪኖች ብዙ ናቸውና።
ቁሉፉ ነን እኛ…የራሳችን ደስታ
ውብ አሁን!!❤️
@EthioHumanity
@EthioHumanity
✍ @EthioHumanityBot
ሰዓት እላፊ! (ፀዴ ቀደዳ ነው ሳትሰለች አንብበው)
💛
. [Restoring Faith in Humanity]
. ∞ ∞ ∞ ∞
እነሱም ይላሉ፣
ተኩሰን አንስትም፣
እኛም እንላለን፣
ቃታ አናስከፍትም።
እንዲህ ተባብለን፣ የተገናኘን 'ለት፣
ተሰብሰብ አሞራ ትበላለህ ዱለት።
-
የአዲስ አበባ ሠው ሆይ።
ይሄ የተጣድንበት እሳት፣ ይሄ እቶን፣ ይሄ ነበልባል፣ ይሄ ድውይ ጦርነት ስሙ የርስ በራስ ጦርነት (Civil War) ነው። በቀላል አማርኛ - የቀድሞው ኢህአዴግ ግንባር በስልጣን እና በሪሶርስ መስማማት አቅቶት #እርስ_በራሱ ስለተጣላና ስለተከፋፈለ ያወደቀብን ዳፋ፣ ያመጣብን ሲቪል ዋር ነው። የሲቪል ዋር ደግሞ ጀግና የለውም። ፈሪም የለውም። ፀጉረ ልውጥ - ባዳና ባንዳ የለውም። ድሉም ችንፈቱም፣ ገድሉም ውርደቱም የኔና ያንተ ነው። #የኛው ገመና፣ የኛው ነውር ነው።
እውነት ነው።
ት*ግሬዎቹ ላመኑበት ባመኑበት በታላቅ ጀግንነት ተዋግተዋል። እኛም ላመንንበት ባመንንበት በታላቅ ጀግንነት ገጥመናቸዋል። እነሱም ዘራችንን ሊያጠፉ ወጉን ብለዋል። እኛም አገር ሊያፈርሱ ወጉን ብለናል። ሁሉም የየራሱን Narrative ይዞ አውደ ውጊያ ወርዷል። አፋፍ ለአፋፍ፣ ምሽግ ለምሽግ፣ ጢሻ ለጢሻ፣ ቆረንጦ ለቆረንጦ በታላቅ ወንዳ ወንድነት ገጥሟል። ታላቅ ገድልን ተጋድሏል። አቸናፊም ተቸናፊም ታሪክ አስጽፏል። ታሪክ ሰርቷል።
የሸገር ሰው ሆይ።
አሁን በቀጣይ ሳምንታት አቸነፍን ብለን፣ መቀሌ ገባን ብለን። ምናልባትም የህወሃት አመራሮችና የጦር ጄነራሎች በወንድ ልጅ/ በማርያም መንገድ እንዲሼሹ ተደረጉ ብለን። አልያም አይበለውና ተማርከው ወታደራዊ ፍርድ ቤት ቀረቡ ብለን የት*ግሬውን ቅስም የመስበርና የማሳጣት ፕሮፓጋንዳ ውስጥ ከገባን #ትልቁን ስእል (The Big Picture) እንስታለን። የቅሽምናን Cycle እናስቀጥላለን።
አትርሳ።
ት*ግሬው እኮ የአገርህ ልጅ ነው። በደም፣ በባህል፣ በእምነት፣ በአኗኗር፣ በወኔ በኑሮ አንተን መሳይ ነው። ቢያኮርፍም፣ በቃኝ ካንተ ጋራ አብሮ መኖር፣ ፍታኝ ልፋታህ ቢልም ዘመድህ ነው። በሕግ በዜግነት ያንተ አይነት መብትና ግዴታ ያለው ኢትዮጵያዊ ነው። በታሪክ ደግሞ ሃገር ግንባታ ላይ፣ ዳር ድንበር ማስጠበቅ ላይ፣ ኢትዮጵያን ማቅናት ላይ አኩሪ ገድል ያለው፣ ታላቅ አስተዋጽኦን ካበረከቱ ጥቂት ነገዶች ውስጥ #ከላይ የሚመደብ ነው።
በዚህ።
ወደ ገደለው - አሁን በዚህ አስቀያሚ ጦርነት ሳቢያ Average ኢትዮጵያዊ ከተጋፈጠው መከራ በላይ ት*ግሬው ተጋፍጧል። ከየትኛውም ክልል በላይ የትግራይ ክልል የፈርኦን ዘመን ዳፋዎችን ተቀብሎ ኖሯል።
አስበው።
ለሁለት አመት ልጆቹን ት/ቤትና ኮሌጅ አልላከም። ብሩን አውጥቶ አስቤዛ እንዳይገዛ ባንክ ተዘግቶበታል። ስልክ ኢንተርኔት ተቋርጦበታል። እንዳይነግድ፣ እንዳይወጣ እንዳይገባ መንገድ ተዘግቶበታል። ደሞዝ አልተሰጠውም። ባጀት አልተለቀቀለትም። አልዘራም፣ አልነገደም። እዚህ ግባ የሚባል ምርጥ ዘር፣ ማዳበሪያና መድሃኒት አላገኘም፤ አልተሰራጨለትም። በላዩ ላይ ህወሃት አልዋጋ ያላትን ወጣት በሙሉ በግድም በውድም በአፈሣ ወስዳ ማግዳዋለች።
እና።
እናማ ጦርነትን እና ረሃብን አንድ ላይ ሲያስተናግድ የነበረ ክልል ሕዝብ ተቸነፈ፣ ጊዜ ጣለው ብለን የቅስም ሰበራና የማቅለል፣ የማዋረድ (Humiliation) ፕሮጀክት ውስጥ ከገባን ነግ በኔን የማናውቅ፣ ያልበሰልን፣ ከታሪክ የማንማር ጉፋያዎች ነን ማለት ነው።
እኔ ልፍረድ።
ወደ ኋላ እንይ። መላውን የትግራይ ስፍራ አጠቃላዩን የትግራይ 52 ወረዳዎችና አራት ዞኖች በተደጋጋሚ ጎቦኝቻለሁ። በስራ የአለም አቀፍ NGO የResearch ጥናት ሃላፊ ሆኜ አጥንቻለሁ። ዞሬ ሰርቼበታለሁ። ሕዝቡን፣ ኑሮውን፣ ባህሉን፣ ውሎውን፣ ደግነቱን፣ አዲስ ሰው ወዳጅነቱን፣ በትክክል አውቀዋለሁ። ከእጁ በልቻለሁ - ጠጥቻለሁ። እንደ ሠው ተከብሬ ተስተናግጃለሁ። ዘርህ ሐማሴን፣ ዘመዶችህ ኤርትራ ናቸው ነው ብሎ የጠላኝ የገፋኝ አልነበረም።
ትግሬውን የማውቀው 22 ላይ ሲጨስ፣ ሲጨፍርና ብር ሲበትን ሳይሆን ትግራይ ላይ ሠርክ ኑሮን ሲገፋና ሲጋፋ ነው።
አንተ ፍረድ።
ከሌላው ክልል #በተለየ መልኩ ከትግ*ሬዎቹ ክልል ሄዶ የሰራ ሠው። መቀሌ/አክሱም/አዲግራት ዩንቨርሲቲ የተማረ ሠው፣ ከትግሬዎቹ ጋራ በክልላቸው የኖረ ሠው፣ ሰዎቹንና ባህሪያቸውን ሲወድዳቸው እንጂ ሲጠላቸው አጋጥሞኝ አያውቅም። ሲናፍቅ እንጂ ሲያማርር ሰምቼ አላውቅም። እንግዳን መውደድ፣ የመሃል አገርን ሰው ማክበር ጥጉና ማሳያው ናቸው። ያያቸው የሚመሰክርላቸው ጥሬ ሐቃቸው ነው። ካየህ ከኖርክ፣ ከተማርክ ከነበርክ ምስክር ነህ አንተ።
ስማኝ የሸገር ልጅ።
አገርህን የምትወድድ ከሆነ፣ ኢትዮጵያን የምታፈቅር ከሆነ፣ ሕዝቦቿ ወገኖቼ ናቸው የምትል ከሆነ፣ በት*ግሬ ዘመድህ ችንፈትና ውድቀት አትደሰትም። አትፈነጥዝም። በቀል እያሰብክ የመጨረሻውን ሳቅ ልገልፍጥ አትልም።
ሞክር።
የድርሻህን ሞክር። የአቅምህን ወርውር። DO Something.
. . . ደውል።
በቅርብህ የምታውቀው የትግራዋይ ወዳጅህ፣ ጓደኛህ፣ ባልደረባህ፣ ጎረቤትህ፣ ደንበኛህ ጋራ አሁኑኑ ደውል። ወይንም ቴክስት ጻፍለት። ጠፋሁበት ብለህ፣ እስከዛሬ የት ነበርኩ ብለህ ሼም #አይያዝህ።
ዝም አትበለው።
አዋራው፣ ጠይቀው። ዘመድ አዝማድ፣ ቤተሰቦችህ እንዴት ናቸው ብለህ ጠይቀው። ስራ ላጣ፣ ተሰድዶ ለመጣ፣ ለተፈናቀለ፣ እዚህ ለተቸገረ፣ ቤት ኪራይ ለጎደለው፣ ወይንም እዛ ላለ ሰው ምን ልርዳ ምን ላግዝ ብለህ ጠይቀው። ያቅሜን ልወርውር በለው። እሱ ሼም #ይሉኝታ ስለሚቆልፈው፣ አንተው አደፋፍረው። ከድባቴው አውጣው። አበረታታው። ያልፋል ይሄም በለው። መጣላት መታረቅ በኛ አልተጀመረም ብለህ አስረዳው። . . . ዘር ብሔር ሳትቆጥር መከታ ሁነው።
¤
. [ይሄ መልካምነትህ #ላንተ ሶስት ጥቅም አለው]
1 - የምታምንበት ፈጣሪ ብድራትህን ይከፍልሃል።
2 - የምትወዳት አገርህ ላይ ቂምና ቁርሾ ትቀንሳለህ።
3 - ህሊናህ፣ አእምሮህ ሰላም ያገኛል።
-
. . . ማን ያውቃል - ነገ የዚህ ገበሬ ስድራ ገዛ፤ የዚህችን ምንም የማታውቅ ንጽህት ትግራወይቲ ህጻን የወደፊት እጣፈንታ ላይ የተስፋ ጭላንጭል ያበራኸው አንተ ትሆን ይሆናል።
¤
“Love and kindness are never wasted. They always make a difference. They bless the one who receives them, and they bless you, the giver.”
– Barbara De Angelis
📝Eyob Mihreteab
@Ethiohumanity
@Ethiohumanity
💎በዚህ ምድር ላይ ሰው ሁሉ የዘራውን ያጭዳል። ይህ ህገ ተፈጥሮ ነው። በየትኛውም የዓለም ክፍል የሚሰራ ህግ ነው። እንደ ህገ-መንግስት በአንድ ሉአላዊ ሀገር ብቻ የተገደበ አይሆንም። በምድር ላይ ለሰራው ደግነት ይሁን ክፋት ብድራት መከፈሉ የማይቀር ይሆናል።በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ የቻልከውን ያህል መልካም ውለታ ብትውል ብድራት ተከፋይ ትሆናለህ። ካለህ ላይ መስጠት ማለት ነው። … የምትሰጠው ነገር ባይኖርህ ጥሩ ፈገግታ ስጥ። ምናልባት ይህች ፈገግታ አንተ ባታውቅ እንጂ አንዲት የጨነቃት ነፍስ ትታደጋለች ።
💛ያንተ መልካም ስነምግባር ሌላውን ተመልካች ከተኛበት የመቀሰቀስ መግነጢሳዊ የስበት ኃይል እንዳላት አንተ አታውቅም ይሆናል። በዚህ ምድር ላይ የተዘራ ማንኛውም ነገር እንዲሁ ወድቆ የሚቀር ላይሆን ይችላል።
💫መልካም ገበሬ ለነፍሱም ለቤተሰቦቹም ብሎም ለሃገር ለህዝብ የሚተርፍ ዘር ዘርቶ ፍሬውን ይመግባል። በየትኛውም የህይወት ሜዳ ላይ የሚገኝ እያንዳንዱ ግለሰብ መልካም ገበሬ ለመሆን የሚያግደው የለም።
🔆ሁሌም በጎ በጎውን ማሰብ ስትለማመድ መልካም ገበሬ ትሆናለህ። ከራስህ አልፎ ተርፎ ለሌላው የሚጠቅም መልካም ሐሳብ ወደ ዓለም ብትልክ መልካምነት ዞሮ ይከፍልሃል። ብድራቱን ታገኛለህ። የጣልከው አልያም ያካፈልከው ሁሉ መልሶ ብድራቱን ይከፍልሃልም። …መልካም መሆን ኪሳራ ከሌለው ክፉ መሆን ምንም ትርፍ የለውም። … ወዲህም ባንተ ላይ እንዲሆንየማትፈልገውን ነገር በሌላው ላይ አታድርግ። …ፍቅር ትሻ እንደሆን ፥ ቀድመህ አንተ ፍቅር ስጥ። ያልሰጡትን ለማግኘት ማሰብ ፥ ስንዴ ዘርቶ የጤፍ ምርት እንደመጠበቅ እንዳይሆን። … ከመስተዋት የተሰራ ቤት ውስጥ የሚኖር ሰው ከቤቱ ሆኖ ወደ ውጭ ድንጋይ መወርወር የለበትም።
💡ጋን በጠጠር ይደገፋል እንዲሉ ፤ እያንዳንዱ ሰው በሌላው ህይወት በቀጥታም ይሆን በተዘዋዋሪ ተፅእኖ ማሳደሩ ህገ-ተፈጥሮ ነው።አይመለከተኝም፥ አይደርስብኝም የምትለው ነገር ላይሆን ይችላል። … ጉንፋን የያዘው ሰው አጠገብህ ተቀምጦ ቫዮረሱ አንተ ዘንድ እንዳይደርስ ለማድረግ አትችልም። በአንድም በሌላ መልክ ኢንተርአክሽን ይኖራል።
ውብ ምሽት❤️
@EthioHumanity
@EthioHumanity
@EthioHumanitybot
☮ሁለት ሱፊዎች በመንገድ ላይ ሲሄዱ ይገናኙና በመተቃቀፍ ተሳስመው አንዱ የቋጠረውን ስንቅ በጋራ ሊመገቡ ተቀመጡ ። ይኸንን ትዕይንት ለአፍታ የተመለከተው የክርስቲያን ልዑል ወደሁለቱ ሰዎች ተጠግቶ ስለትውውቃቸው ጠየቃቸው ።
💟 መመገባቸውን ሳያቋርጡ አንዱ ቀና ብሎ ፦
"ካለዛሬ አይቼው አላውቅም ..." አለው ።
" ምናልባት የአንድ ሀገር ልጆች ትሆኑ ...?" ሲል ጠየቀ ልዑሉ ።
"ሀገሩንም አላውቅም ..." አለ ሰውየው አሁንም መመገቡን ሳያቋርጥ ።
"ታዲያ ለምንድ ነው እንዲህ ዓይነት ፍቅር ያሳየኸው...?" አለ ልዑሉ ተደንቆ
"በእኔ መንገድ ላይ ሲጓዝ ስላገኘሁት ነው" አለው ።
☯ልዑሉም ተደንቆ ዝም ብሎ አልሄደም ። በዚያ ቦታ ለሱፊዎች ማረፊያ የሚሆን ትልቅ አዳራሽ ሰራ ። ዛሬ አዳራሹ ዘመናዊ መልክ ተገንብቶ የሱፊዎች መፍለቂያ "ዩኒቨርስቲ" ሆኗል ።
📖ጥበብ ከጲላጦስ
☯ሰው መሆን እኮ እንዲህ ነው ፣ በሀይማኖት ተለያይቶ ፣ በደም ሳይተሳሰሩ ፣ በባህል ሳይገናኙ ፣ ነገር ግን ለመረዳዳት ፣ አብሮ ለመብላት ፣ እንደሰው ተያይቶ አብሮ ችግርን መካፈል ማለት ነው ፣ ባጠቃላይ በፍቅር ለመኖር ሰው መሆንና እንደ ሰው ማስተዋል ብቻ በቂ ነው ።
መልካም ቀን💜
☮☯☮☯☮☯☮☯☮☯
@EthioHumanity
@EthioHumanity
እምወድሽዋ!❤ቅዳሜዋ!❤ሸጋዬዋ❤
እቴ!❤'ለነገ ብለሽ ፊት የምትነሺው ትላንት አለ'
ደባሪውን ትላንትን ካስተያየሺው ፤ፊት ከሰጠሺው ይጎትትሻል። ንፍጣም ነው ቀሚስሽን ይዞ አያራምድሽም ፤ላባብለው ካልሽ ዝርክርክ ነው አይፅናናም ።አይጠራም ያጨማልቅሻል ነገሽን ፤ህልምሽን ፤ሳቅሽን ያንገራግጨዋል ።
ዛሬሽን ይኮረሽምብሻል ። ውበት እና እድሜሽ ከሚኮረሸሙት ዋነኛቹ ናቸው።
እና የትላንት ጎታች ፊት ነስተሽ ነገ ላይ መንጠራራት ይበልጣል ትላንት ላይ ከማጎንበስ viva ነገ💪🏾💪🏾💪🏾✌️
ድምቅምቅ ያለች ቅዳሚት!❤
@EthioHumanity
@EthioHumanity
@Nagayta
ለጁምኣችን!
💚
«ሌባው» የመስጂድ ኢማም
ባልና ሚስት ከረመዷን ወራት ባንዱ በሰፈራቸው የሚገኙትን ታዋቂ የመስጂድ ኢማም ለፊጥራ ጋበዟቸው። ኢማሙም ግብዣውን በክብር ተቀበሉ። የቤቱ እማወራ የምግብ ማዕዱን ለማዘጋጀት ተፍ ተፍ እያለች ሳለ ገንዘቧን ጠረጴዛው ላይ ጥላ ወደ ኩሽና አመራች። ፊጥራው ተጠናቀቀ። ኢማሙም ሄዱ። ሚስት ገንዘቧ እንደጠፋ አስተዋለች። «ገንዘቡን የሰረቀው ማን ነው?» ተብሎ አይጠየቅ ነገር ባልና ሚስት ልጆች የሏቸውም። በወቅቱ ወደቤት የመጡት የመስጂዱ ኢማም ብቻ ናቸው። ውስጧ በጥርጣሬ ተናጠ። ታሪኩን ለባለቤቷ አጫወተችው። የመስጂዱን ኢማም እንዲያማክራቸውና ጉዳዩን እንዲያረጋግጥ ጠየቀችው። «ኧረ ነውር ነው ፤ ባይሆን ከኢማሙ ጋር የፈጠርነውን ስር የሰደደ ግንኙነት አቋርጠን ፋይሉን እንዘጋለን እንጂ እንዲህ አይነት ጥያቄ ማንሳት የማይታሰብ ነው» በማለት መለሰላት።
ቀናት በንፋስ ፍጥነት ከነፉ። ቀጣዩ ረመዷን ገባ። ባል ከሚስቱ ጋር ተቀመጠ። «እንግዲህ የእዝነት እና የይቅርታ ወር ስለገባ ያለፈውን መርሳት አለብን። እንደምታውቂው ኢማሙም ቤተሰብ የላቸውም። የኛው ስለሆኑ ዘንድሮም ቢሆን ፊጥራ ልንጋብዛቸው ይገባል» በማለት ሚስቱን አማከራት። ሚስት ለአፍታ ዝም ካለች በኋላ «በሃሳብህ እስማማለሁ፤ ነገር ግን የማስቀምጠው ቅድመ ሁኔታ ይኖራል። እርሱም የባለፈው ዓመት ረመዷን ላይ ስለተሰረቀው የገንዘብ ጉዳይ በግልጽ እንድታወሩ እፈልጋለሁ» አለችው። ባቀረበችው ሃሳብ ተስማማ።
የመስጂዱ ኢማም ግብዣውን ተቀብለው ከቤት መጡ። ፊጥራውን ከጨረሱ በኋላ የቤቱ አባወራ ጉዳዩን በይፋ አነሳው። ስለ ገንዘቡ ሁኔታ በቀጥታ ጠየቃቸው። ከፍተኛ የሀፍረት ስሜት ተሰማቸው። እንባቸው በጉንጮቻቸው ላይ ተንኳለለ። ካቀረቀሩበት ቀና አሉ። አይኖቻቸው የእንባ ቋጠሯቸውን እንደፈቱ ነው። ሚስት ፈጠን ብላ «ኢማም ሆይ! ምን ሆነው ነው የሚያለቅሱት ?» በማለት ጠየቀቻቸው። «አዎ! ገንዘቡን ያነሳሁት እኔ ነኝ። ያስቀመጥኩትም የመጽሃፍት መደርደሪያው ላይ ከተቀመጠው ብቸኛ ቁርኣን ውስጥ ነው። እንባዬ የፈሰሰውም ረመዷንን ጨምሮ ለ 365 ቀናት ያህል የአላህን መጽሃፍ ገልጣችሁ አንድ ፊደል እንኳ ባለመቅራታችሁ ውስጤን ተሰምቶት ነው» በማለት ምላሽ ሰጡ። በዚህ ጊዜ የቤቱ አባወራ በፍጥነት መደርደሪያው ላይ ወደተቀመጠው ቁርኣን አመራ። ገንዘቡንም የቁርኣኑ የመጀመሪያ እና ሁለተኛ ምዕራፍ መሃል ላይ ተቀመጦ አገኘው። ሚስት እንባዋ ግድቡን ጥሶ ፈሰሰ። ኢማሙን በክፉ በመጠርጠሯም ይቅርታ ጠየቀቻቸው። «ልጄ ሆይ! እኔ ደካማ የአላህ ባሪያ ነኝ፤ ይልቅ አመቱን ሙሉ ቁርኣኑን ችላ በማለትሽ ይቅርታና ምህረት ከአላህ ጠይቂ» በማለት መከሯት።
👉 እኛስ መቼ ይሆን ለመጨረሻ ጊዜ የአላህን (የፈጣሪን) ቃል ከፍተን ያነበብነው ? ነፍሳችንን ሳንዋሽ እውነቱን ለራሳችን እንገረው‼‼‼
ወገኖቼ የአላህ (የፈጣሪ) ቃል እየጠራን ቢሆንም ችላ ብለነዋል።
ሸጋ ጁምኣ!💚
📝መሀመድ አህመድ
@EthioHumanity
@EthioHumanity
@Nagayta
ለውብ ቀን!
🖤
አብሮ መጨፈርን ሰጥቶ፣ አብሮ ማልቀስን ማን ነጠቀን?
ሁሉም ከሳሽ ፤ሁሉም ምሁር ፤ሁሉም ጨዋ፤ ሁሉም ወቃሽ ፤ሁሉም ሊቅ፤ ሁሉም አዛኝ፤ ሁሉም አቅጣጫ ጠቋሚ ፤ ሁሉም አውሪ ፤ሁሉም ብያለው ባይ ፤ ሁሉም ጆሮ አልባ ነው።
ተመሳሳይ ሃሳብ፤ ተመሳሳይ ምልከታ፤ ተመሳሳይ ህልም ፤ተመሳሳይ ዜና ፤ተመሳሳይ ክስ ፤ተመሳሳይ ውዳሴ ፤ተመሳሳይ አቋም ፤ተመሳሳይ ድጋፍ ፤ተመሳሳይ ሙግት ።
የቡድን ጀግና፤የቡድን ተቆርቋሪ ፤የቡድን ተከራካሪ ፤የቡድን ተከላካይ ፤ቡድናም እይታ ፤የቡድን ጭብጨባ ፤ የቡድን ሳቅ ፤የቡድን ሙሾ ፤ የቡድን ሙግት ፤የቡድን መልስ ። የቡድን ጩኸት
ሃላፊነት የሚወስድ አንድም የለም ። ዝቅጠት ላይ አስተዋፅዖ እንደ አበረከተ የሚያወራ ።አንድም የለም። ሁሉም ጣት ቀሳሪ ፤ ሁሉም ዳር -ነኝ ባይ ነው ።
ሃይማኖታችን ጥንጥ ሞራል ፤ጥንጥ ርህራዬ ትንሽ መተዛዘን ካልፈጠረልን ምን ይሰራልናል ???
የሃይማኖት ስፍራዎች ለምን ግንባቸው ተሸንሽኖ ቤት አልባ ሰዎች አይኖሩበትም??
መስበኪያ ስፍራዎች ለምን ወደ መበየጃ ወደ መሸመኛ ፤ወደ መጥለፍያ ቦታዎች አይቀየሩም ።
እምነት አልባ ህዝብ ውስጥ ይሄ ሁላ ማምለክያ ግንብ ምን ይረባል !!
በዚህ ደረጃ እርስ በእርስ ተጠያይፈን እርስ በርስ ተጨካክነን እርስ በእርስ እየተሳደድን ምን ያስተሳስረናል ???
እርስ በእርስ በሚበላላ ህዝብ ውስጥ ያለች አገርን እንደምን ማፍቀር ይቻላል? ?? ምኗ ይናፍቃል ??
ከዚህ በኋላ የትኛው አገዳደል ፤የትኛው አበዳደል ፤የትኛው ግፍ ያስበረግገን ይሆን ??
የቱም !
ይታክታል!!! እውነት ይታክታል!!!!!
@EthioHumanity
@EthioHumanity
@Nagayta
☯“The most beautiful people we have known are those who have known defeat, known suffering, known struggle, known loss, and have found their way out of the depths.
💜These persons have an appreciation, a sensitivity, and an understanding of life that fills them with compassion, gentleness, and a deep loving concern. Beautiful people do not just happen.”
✍Elisabeth Kübler-Ross
@EthioHumanity
@EthioHumanity
ቃላት ስሜትን መሸከምም ሆነ መግለጥ አቅቷቸዋል!!!💚💛❤
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹 🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹 🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹 🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹 🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹 🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹 🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹 🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹 🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹 🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹 🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹 🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹 🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹 🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹 🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹 🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹 🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹 🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹 🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹 🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹 🇪🇹🇪🇹
🇪🇹🇪🇹 🇪🇹🇪🇹
እንኳን ደስ አለን!!!!💚💛❤💚💛❤💚💛❤
💡ሕይወት በ’የኔ’ እና ‘የኛ’ የምናሳንሰው ነገር የላትም… ከጽንፍ አልባው ምልዓት ላይ በተገለጸልን ልክ የገባንን ሁሉ የእኔ/ኛ አንልም… እኛ ራሳችንን ያንን ምልዓት አይደለን? “You are not a drop in the ocean; you are the entire ocean in a drop” ይላል Rumi
❤️ ይህን ሁለንተና በግላዊነት መያዝ አይቻልም… የኔ ብሎ ማሳነስ አይቻልም… እኛው ራሳችን ሁለንተናውን ነንና ፣ ብዙ የአለማችን እሳቤዎች ከሕይወት በተናጥሎ የመኖርን ቅዠት ይሰብካሉ… ውቅያኖሱን ሆነህ ሳለ የውቅያኖሱን ‘አንድ ጠብታ ወስደህ’ የኔ ማለት ከራስም ያሳንሳል…ከራስህ ተነጥለህ ‘የራስህ’ ሊኖርህ አይችልም።
💡የግዙፍ ውቅያኖስ አካል ነን ፣ከኔ ቤት ላይ የረጨኸው እሳት ከሆነ ነበልባሉ ያንተን ቤት ይነካል ሽቶ ስትረጨኝ የመዓዛው ቅንጣቶች ለአፍንጫህ ውብ ጠረን ይለግሳል ሰው የዘራውን ያንኑ ደግሞ ያጭዳል ይህን ምስራቃውያኑ Karma ሲሉት ሌሎች ደግሞ Boomerang ይሉታል Boomerang አውስትራሊያኖቹ አቦርጂኒስቶች ከእንጨት የሚሰሩት ደጋን ቅርጽ ያለው የአደን መሳሪያ ሲሆን ወርዋሪው ዘንድ ተመልሶ እንዲመጣ ተደርጎ የሚነደፍ ነው… ለሃሳብ፣ ለስሜትና ድርጊትህ መጠንቀቅ የሚኖርብህ ወላፈኑ ‘ለእኔም’፣ ‘ለእርሷም’፣ ‘ለእነርሱም’ እንደሚተርፍ በማሰብ ነው ምክንያቱም We are all One!
💎በረከት በላይነህ "የመንፈስ ከፍታ" ላይ እንዲህ ይለናል
“የግልህ ወንዝ ስለሌለህ ብቻህን የምትሰራው ድልድይ የለም! የሰማዩ ርቀት፣ የምድሪቱ ስፋት በ’እኛ’ እንጂ በ’እኔ’ አይለካም፡፡ ውዱ ‘እኔ’ ከ’እኛ’ የተሰራው ነውና!”
✍ደምስ ሰይፉ
ውብ አሁን!!❤️
@EthioHumanity
@EthioHumanity
✍ @EthioHumanityBot
❤️ሁሉም ሰው ዋጋ አለው!
💎ሰው የሚሰጥህ ክብር አንተ ለራስህ በምትሰጠው ሚዛንና መጠን ነውና ለራስህ ትልቅ ዋጋና ብዙ ክብር ይኑርህ፣ ማንኛውም ሰው በማንኛውም አይነት ስራ ዘርፍ ቢሰማራ የተወሰነ ቀናት እስኪለምደው ይቸገራል እንጂ ስራውን የማይወጣበት ምንም አይነት ምክንያት የለም !
💡ዕድሉን ስላላገኘ እንጂ ሰው ሁሉ ወሳኝ ጠቃሚ ነው ነገር ግን በሌሎች ዘንድ ቦታውን ባለመግኘቱ እና ተቀባይ ባለመኖሩ ሊወድቅ ይችላል !ሰው ቦታን ይለምዳል እንጅ ቦታ ሰውን አይለምድም !ከደካማ ስር ብትሆን ማንነትህ አይወርድም እንዲውም ምርኩዝ ትሆነዋለህ !ከጠንካራ ጎን ብትቆም በሱ ወንበር አትመራም በራስህ ህሊና እንጅ !
💎ሰውን በአስተሳሰቡ እንጅ በፍፁም በአለባበሱ አትመዝነው፡፡ ምክንያቱም ሰው ቦታን ይቀይራል እንጅ ቦታ ሰውን አይቀይርም! ጠንካራ ሰዎች ሌሎችን ከፍ እንጅ ዝቅ አያደርጉም እና ጠንካራ ከሆንክ ለሰው ትልቅ ቦታ ስጥ ብዙ ዋጋም ይኑርህ።
🐝 Bee A Good Human
Our life can be translated into love,We can color our whole life with kindness, transforming our everyday activities and ejoying our everyday ways of being with human warmth. Our Life Can Be Translated into Love.
💙እራስህን በሰላም ፣ በብርሃን ፣ በጥበብ ፣በንቃተ-ህሊና ሸፍነው፡፡የአንተ ሃላፊነት ይህ ነው ፡፡ደስታ እና ርህራሄ በህይወት መንገድህ አይለዩህ፣ ከተፈጥሮ ጋር እጅ ለእጅ ተያይዘህ ኑር ፡፡ይህን ለማድረግ ሁሌም ከልብህ ጀምር።ሁሌም ይህን አድርግ፣ሁሌም ይህንን ሁን ፡፡
ፏፏቴ የሆነች ቅዳሜን ተመኘን❤️
@EthioHumanity
@EthioHumanity
@EthioHumanitybot
🔑የማንፈልገው ነገር ባይኖር የምንፈልገውም አይኖርም !
📍ልዩነት የምንወደው ሳይሆን የምንቀበለው ነው ። ማንም ለራሱ ሀሳብ ቅድሚያ ቢሰጥ ፣ ተቃራኒውን ለመቀበል ደስታ ባይታይበት አይገርምም ። " የእኔ ሀሳብ ወይም ሞት ! " ማለት ግን ራስን ማስቀደም ሳይሆን ልዩነትን ማጥፋት ነው ። ይህ እውነትን ለመስቀል ገመድ ማዘጋጀት ይሆናል የወደድነውን ያገኘነው ካልወደድነው መሀል መርጠን መሆኑን ልብ ማለት ያሻል ።
🛑 እኛ የወደድነው ብቻ ቢኖር ፣ የምንጠላው ወይም የማንወደው ባይኖር የምንወደውን መውደዳችንን በምን እናውቀው ነበር ? የምንጠላውን የሚወዱት እንዳሉ መረዳት ብቻ ሳይሆን ለምንወደው ነገር ማነፃፀሪያ እንዲሆነንም ያስፈልገናል ። የማንወደውን ነገር ከማጥፋት ለሚወዱት መተው ያስፈልገናል ። የምንፈልገው ነገር መኖሩን ያወቅነው የማንፈልገው በመኖሩም ጭምር ነው ።
✍ቴዎድሮስ ተ/አረጋይ
ውብ አዳር❤️
@EthioHumanity
@EthioHumanity
@EthioHumanitybot
💡'እኔ ማን እንደሆንኩኝ አታውቅም, ግን እኔ ማን እንደሆነች አውቃለሁ'
'She doesn't know who I am, but I know who she is
💎 የ85 አመት አዛውንት ናቸው ከ 60 ዓመት በላይ ከባለቤታቸው ጋር በትዳር ኖረዋል, ባለቤታቸውን በሄዱበት ሁሉ እጃቸውን አጥብቃ እንድትይዛቸው ባለመሰልቸት ይጠይቋታል, ስትቆም ቆመው ስትቀመጥ ተቀምጠው ስታስቸግር አብረው ተቸግረው . . . ሳይሰለቹ የድሮ ፍቅራቸውን ሳይቀንሱ በ 85 ዓመት የአዛውንት ጉልበታቸው አሁንም በትዕግስት አብረዋት አሉ :: ሰዎች ሚስታቸው ምን ሆና እንዲህ እንደሆነች ይጠይቃሉ “አልዛይመርስ' የመርሳት በሽታ አለባት” ሲሉ ይመልሱላቸዋል
💡እና ምንም አታስታውስም ? ምንም !ያን ሁሉ ዓመት የሕይወት ውጣውረዳችንን,ደስታችንን ሀዘናችንን ወልደን ኩለን መዳራችንን ዘመድ አዝማድን ኧረ እኔንም ዘንግታኛለች
እናም "ሚስትህ እጅህን ብትለቅህ ትጨነቃለህ ማለት ነው ?" ለምን አልጨነቅም ምንም ነገር ማንንም አታስታውስም እኮ በዚህ ዓለም ያላትን ነገሮች ሁሉ ረስታለች እኔንም ጭምር , ለብዙ አመታት አላወቀችኝም እና ያለኔ ማን አላትና ነው የማልጨነቀው ?!
💎 "እናም አንተን ባታውቅህም በየቀኑ መንገድ ላይ እየመራሃት ትቀጥላለህ" ማለት ነው ,
ፈገግ አሉና አይኖቼን እምባ ባቀረሩ አይናቸው እየተመለከቱ . "እኔ ማን እንደ ሆንኩኝ አታውቅም ግን እኔ ማን እንደሆነች አውቃለሁ " ውዷ ከ 60 ዓመት በላይ ብዙ ነገር የሰጠችኝ ሕይወቴ ናት " እናም ሕይወቴን ሙሉ በሄደችበት ሁሉ አብሪያት አለሁ , ሰው ካለ ህይወቱ ምን ሕይወት አለው ... እከተላታለሁ።
መልካሞችን ሁሌም ያብዛልን።
ውብ አዳር❤️
@EthioHumanity
@EthioHumanity
@EthioHumanitybot
💫አፍርሰህ አትገነባም.
የሄደ ነገር ተመልሶ ይመጣል። ሰብረህ ያጠፍኸው የመሰለህ ነገር ይዘገይ ይሆናል እንጂ አይቀርምና አፀፍውን መልሶ ሊያስታቅፍህ ምንአልባትም እጥፍ ድርብ አድርጎ ደጃፍህ ላይ ቆሞ በርህን ያንኳኳል። ኃላፊነት በንግግር፣ ተግባርና ሁሉም መስክ ላይ እንዲንፀባረቅ የተገባው በእዚህና መሰል ምክንያቶች ነው።
💡እርግጥ ነው ኃላፊነትን በፀጋ መቀበል እና ሳይሸራርፉ በተጨባጭ መወጣት ፈታኝ ነው። አስተዋይ አእምሮ እና ቅን ልቦና በምርጫና መንገድህ ካልተለየህ ግን በድል ትወጣዋለህ። ድሉም ከበደል የፃዳ ይሆናል። ድሉ ከራስህ አልፎ አለምን ስለሚጠቅም መልካሙ ስርህ ሄዶ ዞሮ ሲመለስ በጎ ምላሽ ማግኘትህ አይቀሬ ነው። ወርቅ ለሰጠ ወርቅ እና ጠጠርም ለሰጠ ጠጠር ማግኘት ተፈጥሯዊ ህግና የህይወት ነባራዊ እውነታ ነውና።
💎መልካምነት ከማንም በላይ ላራስ ነው ጥቅምና ፍይዳው። ቅን ሀሳብ አሳቢውን ይባርካል። ሴራ፣ ተንኮል እና ክፍት ህሊናና ልብህን ከሞላው ግን ሌላው ይቅርና መልካም እንቅልፍ እንኳ ብርቅ እና ሩቅ እንደሚሆኑብህ ልነግርህ እችላለሁ።
🔆አዳርህ በመባነን እና መበርገግ ይሞላል። ቀን ያሳደድከው በህልምህ መግቢያና መሸሸጊያ ጥግ ያሳጣሀል። ቀን ከሌት የዘራሀቸው ክፋቶች ሌሎችን ብቻ ሳይሆን የአንተን የገዛ ራስህንም ገላም ይቧጥጣሉ። ከአንተ የመነጨና ተንደርድሮ የተተኮሰ ኃይል በእኩል መጠን እና ልክ አጥፊ እንደሆነ ራስህንም ያጠፍል፤ አልሚ ከአደረከው ደግሞ ቅድሚያ አንተን እና የእኔ የምትለውን ሁሉ ባርኮ ለሌሎች ይተርፋል።
✨ይህ የህይወት ሀቅ ከፊዚክስ action/reaction ተፈጥሮአዊ ህግ ጋር ይመሳሰላል። አፍርሰህ አትቆምም። ጠልተህ ፍቅርን አታተርፍም። ወደህ ላትከበር፣ ትህትናን ሰጥተህ ልትናቅ፣ አሳቢና አስታዋሽ ሆነህ ሳለ ልትረሳ አትችልም። ምክንያቱ ደግሞ ምዕራባዊያን እንደሚሉት የሄደ ነገር ተመልሶ ይመጣልና ነው (what goes around comes around)። አበውም አሳ ጎርጓሪ ዘንዶ ያወጣል፣ የሰው ፈላጊ የራሱን ያጣል፤ በቆፈሩት ጉድጒድ መቀበር አይቀርም ወዘተረፈ ብለውናል።
✍ ነጋሽ አበበ
ሰናይ ምሽት ይሁንልን❤️
@EthioHumanity
@EthioHumanity
✍ @EthioHumanityBot
💎ጊዜ ሰታችሁ ቀና ምልክታችሁን ስላከፈላችሁን ክበሩልን።ብርታት ስለሆናችሁንን ከልብ እናመሰግናለን።
ፈጣሪ ያክብርልን 🙏
@Ethiohumanity
@Ethiohumanity
💎መዘግየትህን አትጥላው!
⏰ነገሮች በፍጥነት እንዲሳኩልህ አትፈልግ! መዘግየትህን አትጥላው! በትምህርት፣ በስራ፣ በሀብት፣ በፍቅር ግንኙነት ወይ በትዳር አንተ እንዳሰብከው አለመሆኑ ለበጎ እንደሆነ አስብ።
💡ልብ እንበል!!
ጉንደን ካስበችው ለመድረስ ሺ ጊዜ ከምሰሶው ላይ ትወድቃለች።
ንብ ጣፋጩን ማር ለመጋገር ሚሊዮን ጊዜ አበቦች አካባቢ ትመላለሳለች:: ወዳጄ ስኬት ትኩረትንና ትእግስትን ይጠይቃል..
🕰ወደ ኋላ የተንደረደረ ረጅም ርቀት እንደሚተኮስ አስብ፤ ወዳጄ ጥያቄህ ቶሎ ያልተመለሰው ጊዜው ስላልደረሰ ወይ ደግሞ ፈጣሪ የተሻለውን ሊሰጥህ ይሆናል። አንተ ብቻ ጥረትህን ሳታቋርጥ ታገስ፤ የህይወትህ ፀሀይ መውጣቷ አይቀርም!
💎ፋንዲሻ እንዴት አማርሽ ቢሏት እሳቱን ስለቻልኩት አለች ይባላል ፣ በህይወት መስመር ስኬትን ለማግኘት የግድ መከራውን ማለፍ አለብን!!
ውብ ምሽት!❤️
@EthioHumanity
@EthioHumanity
✍ @EthioHumanityBot
❤️ፍቅር ማለት በዚህ በምትመለከተው ጨለማ ውስጥ ከሚብለጨለጩት ቁጥር ስፍር የሌላቸው አምፓሎች መሀል ፣ነፍስ አንዷን መርጣ በብርሃኗ ስትደምቅ ነው።ብርሀን ሁሉ የነፍስን ጨለማ አይገፍም ቢበዛ የራስህን ብርሃን ትፈልግ ዘንድ ያግዝህ ይሆናል።ሰው የቱንም ያህል በደማቅ ብርሀን ቢከበብ፣እውነተኛውን የራሱን ብርሃን እስካላገኘ ድረስ ነፍሱ ጨለማ ውስጥ ናት።
❤️ፍቅርና ዝምታ መለኮታዊ ኃይሎች ናቸው።ፈጣሪን የምንፈራው ከተከታዮቹ ብዙ ጩኸት ይልቅ በጥልቅ ዝምታው ሳይሆን አይቀርም እናም በዝምታ ግርማ ሞገስ ውስጥ ባለ እውነተኛ ፍቅሩ።ዝምታን የሚያሸንፍ ጬኸት ፍቅርን የሚያንበረክክ ብልጣ ብልጥነት የለም።
✍አሌክስ አብርሀም
ውብ ምሽት !!❤️
@EthioHumanity
@EthioHumanity
✍ @EthioHumanityBot
💫ራሳችሁ ላይ ስሩ!
✨ከአንድ ሰው ጋር ያላችሁ ግንኙነት በቤተሰብ አባልነት፣ በጓደኝነት፣ በፍቅር ግንኙነት፣ በትዳርም ሆነ በሌሎች የቅርብ ወዳጅነት ዘርፎች ይሁን፣ ለዚያ ግንኙነት የሚመጥን ቅርበትንና ትኩረትን የመስጠታችሁ ጉዳይ እንደተጠበቀ ሆኖ ከእነሱ በሚነሳ አጉል ባህሪይ ወይም የትኩረት መለዋወጥ ምክንያት በቶሎ እንዳትደናገጡ ከፈለጋችሁ ራሳችሁ ላይ ስሩ፡፡ እነሱ እንዶለወጡ መጠበቅ ትክክለኛ ቢሆንም፣ አስተማማኙ መንገድ ግን ራስ ላይ መስራት ነው፡፡
💫ራስ ላይ መስራት ማለት ለእነሱ የምትሰጡትን መሰረታዊ ፍቅርና አክብሮት ሳትቀንሱ ራስን በመቀበል መደላደል፣ የግልን ዓላማ በማወቅ መንቀሳቀስ፣ አልፎ አልፎ ከእነሱ ውጪ የግል ጊዜን በመውሰድ ራስን ማድመጥና የመሳሰሉትን ልምምዶች ማዳበር ማለት ነው፡፡ ከሰዎች ጋር ምንም ያህል ብትቀራረቡና ራሳችሁን ብትሰጧቸውም እንኳን ማንነታችሁን መካድ ግን አትችሉም፡፡
✨ከእነሱ ጋር መቀራረብ ማለት ከራስ ጋር መራራቅ ማለት አይደለም፡፡ እነሱን መደገፍ ማለት ራስን መጣል ማለት አይደለም፡፡ ይህንን መርህ መከተል የሚጠቅማችሁ ከእነሱ የማትጠብቁትን ጎጂ ነገር ስታገኙ ወይም የምትጠብቁትን መልካም ነገር ስታጡ ከልክ ባለፈ መልኩ ከመጎዳትና ግራ ከመጋባት ራሳችሁን ትጠብቃላችሁ፡፡
✍ ዶ/ር እዮብ ማሞ
የሰላም እንቅልፍ ይሁንላችሁ!❤️
@EthioHumanity
@EthioHumanity
✨ስብዕና(Personality)
💛በዶ/ር ወዳጄነህ ማህርነ
፨ የሰዓት ፍጆታ፦ 25 ደቂቃ
፨ ሳይዝ የቦታ ይዞታ፦ 6.0MB
ውብ ቅዳሜ❤️
✨✨✨✨✨✨✨✨✨
🔆ምርጫችሁ ስለሆንን ስናመሰግኖት ከልብ ነው !!!
@EthioHumanity
@EthioHumanity
✍ @EthioHumanitybot
ነገ ሸጋዋ ቅዳሚት ነች !
❤
የ20❤+ዓመታት የሙዚቃ መልክ!!
ኤልያስ የሙዚቃው ሊቅ ተወርዋሪው ኮከብ....እንቅልፉን ሰጥቶን ሙዚቃውን በሰረገላ ከፍ አድርጓት ከሔደ ዛሬ ዓመት ከመንፈቅ ሆነው።
ኩልል ያለ የጠራ ንፁህ ውበት!!
የልማድን ቅጥር እንደመናድ...በአምክንዮ ነባራዊውን እውነታ እንደመጋፈጥ...
ደፈር ተባ ብሎ የይሉኝታን እስራት እንደመበጠስ... የጥላቻን ገደል ደፍኖ የፍቅር ድልድይ እንደማነፅ... የባርነትን ቀንበር ሰብሮ የነፃነት ብርሃን እንደመፈንጠቅ...በቅንነት ቀና ብሎ በፅድቅ መንገድ በኩራት እንደመራመድ... ከጃጀ ቀኖና አፈንግጦ ቅቡል ተአማኒ ስርዓት እንማፅደቅ...
የተዛባን ፍርድ አቃንቶ ፍትህን በሰው ልጆች ሁሉ እንደማስፈን..
እንደዚህ ሁሉ...ማነው..? ኤልያስ መልካ!!!
ከኤልያስ መልካ ስራዎች እጅግ በጣም የምወደው ሁሌም ሰርክ አዲስ የሚያስገርመኝ አንዱ "መልክሽ አይበልጥሽም" ሙዚቃ ተጋበዙልኝ!!
ሰላም እደሩልኝ!❤ ለኢትዮጵያችን ናካይታ!💚
@EthioHumanity
@EthioHumanity
@Nagayta
ይፈለጋል !
ዝም የሚል የማይጠይቅ ፤ ሲነገረው አሜን አሜን የሚል፤ የግንኙነት ድንበር የማያበጅ፤ሲናቅ የማይቆረቁረው ፤ የበዛ ይሉንተኛ ፤ከቦታ ቦታ የሚለያይ አቋም የሚያንፀባርቅ ፤ ልምጥምጥ ፤ አቋሙን ፈርጠም ብሎ የማይናገር፤ ሳያስቀው የሚስቅ ፤ አላምንበትም የማይል ። ማብራርያ የማይጠይቅ። ቅሬታውን የማይናገር ፤ሸንጋይ ፤በየቦታው የሚያጨበጨብ ።ይገባኛል(ሲጠብቅ) የማይል ፤ ስለመብት እና ግዴታ የማይዘበዝብ
በጣም ነው የምንፈልገው !¡¡
በነገራችን ላይ
የምንፈልገው ልንገለው ነው¡¡¡¡
@EthioHumanity
@EthioHumanity
@Nagayta
:
ጌታ ሆይ - ክፍትም ብሆን
የባለጌ ልቃቂ
ኮረት እንኳ ባልሆን
የአሸዋ ዝርያ ድቃቂ
ቤት ለእንግዳ በለኝ 'በምስራቅ በር' --
አንተ በሌለህበት ቦታ
ሰማይ ተቀዶ ብሰፋ - እንኳን ልሾም የማልከበር --
የሰጠኸኝ ሁሉ ምሉዕ ነው
ግን እኔን የሚያብሰከስከኝ
እጄ የማይደርስበት ጀርባዬ - ባልበላሁት እያሳከከኝ
አወከኝ
:
አያ ሙሌ ❤️
[ጌታ ሆይ ነፍሴን ባርካት]
@EthioHumanity
@EthioHumanity
ለውብ ቀን!
💚
ሰዉ ዉበቱን እንጂ ቁንጅናዉን ሊፈጥር አይችልም።
ተፈጥሮ የሰጠንን አጣጥበን ከመዉጣት በዘለለ ቁንጅናን ልንፈጥረዉ አንችልም።
ማቆንጀት የምንችለው አስተሳሰባችንን ነው!
ውብ ቀን!💚
@EthioHumanity
@EthioHumanity
@Nagayta
የድል ቀን!
💚💛❤️💪
እግርኳስ ከስፖርት በላይ ነው !
አንድነትን ይፈጥራል ፣ ሰላምን ያሰፍናል በጥላቻ ውስጥ ገብቶ ፍቅርን ይገነባል ።
ከ14 አመት በፊት ዲዲየ ድሮግባ የዛሬ ተጋጣሚያችን ለአምስት አመታት የቆየውን እርርስ በርስ ሲጨረሱ ጎል አስቆጥሩ በመማፀን ብቻ ጦርነቱን አስቁሞ ነበር ። ይሄ ሁሉ የሆነው በእግርኳስ ነው !
እግርኳስ ከሴክስ በላይ አስደሳች ነው ይለናል የባርሴሎናው የመሀል መሀንዲሱ ሰርጂዮ ቡስኬትስ ልክ 2010 አለም ዋንጫን ባነሱባት ቅፅበት ደስታውን ሲገልፅ ።
በ1915 እኤአ በእንግሊዝና ጀርመን መካከል በነበረው ጦርነት ለአዲስ አመት ሰላም ያሰፈኑበት ወታደሮቹ እግርኳስን በመጫወት ነው ። ለዚ ነው ከሱስም በላይ ነው ምንለው !!
አሁን የኛም ህዝብ በውስጡ ብዙ ነገሮች አሉበት በብዙ ነገር አንዱ ከአንዱ ተለያየቷል አድነታችን ከምንጊዜውም በላይ እየሻከረ የመጣበት ወቅት ነው 120 ሚሊየን ህዝብን በ90 ደቂቃ ተጋድሎ አንድነት ፍጠሩለት !!🙏🙏🙏
እውቁ ጋዜጠኛ መንሱር አብዱልቀኒ እሁድ እለት እንዲህ ሲል መልእክቱን ለጥቁር አንበሳዎቹ እንዲህ ሲል አድርሷል....
"ስራው አልተጠናቀቀም። እናንት ውድ የሃገራችን ልጆች ዛሬ ጨርሱትና #ፖለቲካ የረበሸውን ህዝባችሁን በእግሮቻችሁ ምትሃት ሰብስቡት፤ ሁሉም ያያችኋል፤ አንድነትን አሳዩት፤ የረሳውን ህብረት አስታውሱት፤ ችግሩን አስረሱት፤ ቁስሉ ባይሽር እንኳን ማስታገሻ ሁኑለት፤ የወዲያኛውን ሠፈር ከዚህኛው ሠፈር ጋር ቀላቅላችሁ ወደ ህብረቱ መልሱት፤ በጋራ የሚደሠትበትን ዕድል ስጡትና እግርኳስ ከስፖርትም በላይ መሆኑን አስተምሩት።"
ድል ያለ ድል ለሃገሬ ዛሬ ሁላችንም የምንደሰትበት በጋራ ስለ ኢትዮጵያችን የምንዘምርበት ካጠላብን ጥላ ትንሽም እንኳን ቢሆን ገፈፍ የሚልበት የድል ቀን!!
💚💛❤
@EthioHumanity
@EthioHumanity
@Nagayta